id
stringlengths
4
5
url
stringlengths
39
537
title
stringlengths
2
65
text
stringlengths
2.04k
162k
16044
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%86%E1%88%9D%E1%8C%AC%20%E1%8A%A0%E1%88%9D%E1%89%A3%E1%8B%8D
ቆምጬ አምባው
እዚህ የጎጃም ክፍለ ሀገር የአንድ ወረዳ ገዢ ነበሩ ። ቆምጬ አስተዳዳሪ ሳሉ የአንበሳ ሰል አሰርተው ከግርጌው «ጎጃም አንበሳ ነው» የሚል ጽሁፍ አሰፈሩበት ። ህዝቡም በዚህ ተደስቶ ሲኖር ሳለ ገበሬው ግብር በጊዜ አላስገባ ብሎ አስቸገራቸው ። ይህእኔ ቆምጬ ገበሬውን ሰብስበው «አሁን ይሄን አምበሳ ላም ላድርገው ?» በማለት ግዳጁን እንዲወጣ አደረጉት ይባላል ። አዎን፣ በቆምጬ ስም የሚነገሩ በርካታ ቀልዶች አሉ ። ያለማጋነን ቆምጬ የዘመነ ደርግ አለቃ ገብረሀና ነበሩ ። እርሳቸው ግን ይሄንን ክብር በመቀዳጀታቸው ደስተኛ አይደሉም ። "ብቻ የትም ቦታ በምሄድበት ጊዜ ሰዎች የጠቆአቆሙብኛል ። በብዛት ዞረው ያዩኛል ። እኔ ሰዎቹን አላውቃቸውም ። አሁን በሄ ሰሞን እንክዋ አዲስ አበባ ሄጄ ነበር ። ቅድም እንዳልኩህ ልጄን ጠይቄ ነው የመጣሁኝ ። እዚያ አንድ ለቅሶ ነበር ። እዚያው ነው ደርሼ የመጣሁኝ ። እና ታድያ ያው እዚያ ያው እዚያ .. ይሉኛል ። እንዴ ? አልሰረቅኩ : አልቀጠፍኩ ። እኔ ከሰው የተለየ ስራ አልሰራሁ ። ...እና ይሄ ሁሉ እኮ ሰው ያወጣልኝ ስም ነው ።" ስለ ቆምጬ ሲነሳ አያሌ ቀልዶች ትዝ ይሉናል ። እኒያ በቆምጬ አምባው ስም የሚነገሩት ቀልዶችና የግለሰቡን ህይወት የተመለከተ ቃል ምልልስ አዋህጄ እንዲህ አቅርቤዋለሁ ። "ትክክለኛ ስሞ ማን ይባላል ?" "ቆምጬ አምባው ይልማ ፤ እንደዚያ ነው የምባለው ።" "የህይወት ታሪክዎን ባጭሩ ቢነግሩኝ " "በ1933 ጎዛምን ወረዳ ውስጥ ማያ አንገታም ቀበሌ ነው የተወለድኩት ። ከዚያ ለትምህርት እንደደረስኩኝ እናትና አባቴ ቤተ እየሱስ የተባለ ትምህርት ቤት አስገቡኝ ። ከዚያም ዳዊትና ድጉአ ጽሞ ድጉዋ ወጥቼ ደብረ ኤልያስ ቅኔ ትምህርት ቤት ገባሁኝ ። እዚያ እንደገባሁ በችታ ገባ ። አባቴ ከዚያ አውጥቶ አገሬ መልሶ ወሰደኝ ፤ አያይ በሽታው ይበርዳል መልሰህ እዚያው ጨምረኝ ብለው አባቴ እምቢ አለኝ ። ከዛ እዚያው ደብረ ኤልያስ ትምህርት ቤት ገባሁና የስድስተኛ ክፍል ትምህርቴን አጠናቀቅኩ ። ከዚያም የነበረው ባህል መሰረት በልጅነቴ ጋብቻ መሰረትኩ ። አሁን የአስር ልጆች አባት ነኝ ። ከዚያ የናት ያባቴን ከብቶች ገንዲ የሚባል በሽታ ገብቶ ስለፈጃቸው በ1958 ወህኒ ፖሊስ በወታደርነት ተቀጠርኩ ። የ10 አለቅነት ማእረጌን እንደያዝኩ በ1971 የወረዳ አስተዳዳሪ ሆኜ ተሾምኩ ።" "እስከ 6ተኛ ክፍል ብቻ ነው የተማሩት ?" "በወረዳ አስተዳዳሪነት ከቢቡኝ ደብረወርቅ እንደተዛወርኩኝ ከ7ተኛ - ዘጠነኛ ክፍል ትምህርቴን ፈጽሜ በተለኮ (በኮርስፓንዳንስ ) 12ኛ ክፍል ትምህርቴን አጠናቅቄያለሁ ።" "የት የት ቦታ ሰርተዋል ?" "ቢሆን : እነሴ : እናርጅ እናውጋ : አቸፈር : ማቻከል : ወረዳዎች በወረዳ አስተዳዳሪነት ሰርቻለሁ ።" "የሰሩዋቸው ስራዎች ምን ምን ናቸው ?" "እንግዲህ እኔ በተዘዋወርኩበት ወረዳ ሁሉ ትምህርት ቤቶች : የጤና ማህበራዊ መገልገያዎች : መንገዶች : ንጹህ የመጠጥ ውሀ ያልሰራሁበትና ያልመሰረትኩበት የለም ። በተለያዩ ወረዳዎች ከ20 በላይ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከ10 ያላነሱ ኪሊኒኮች 1 የጤና ጣብያ ሰርቻለሁ ። የተለያዩ የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራዎችንም ሰርቻለሁ ። በዚህ መስክ ለምሳሌ በሞጣ ዙርያ አንድ ከፍተኛ የስፖርት ሜዳ አዘጋጅቼ በ1977 የኢትዮጵያ ትቅደም ዋንጫ ውድድር እንዲደረግበት አድርጌያለሁ ። ከዚህም በተጨማሪ በተለያዩ ብሄራዊ ዘመቻዎች ባለትም በመሰረተ ትምህርት ዘመቻ በተለያየ የጤና ነክ ዘመቻዎች በክትባትና በመሳሰሉት ህዝቡን በማንቀሳቀስ ከአለም አቀፍ ድርጅቶች ሳይቀር ሽልማትና እርዳታ አግኝተናል ። በነዚህ ህዝቡን አስተባብሮ ግብር የሚያስገባ ካለ ይህንኑ መሳርያ ያገኛል ብዬ አስነግራለሁ ። ታድያ ሁሉም ባንድ ጊዜ አስገብቶ ያንን መሳርያ ለማግኘት ገበሬውን ለምኖና ቢሆን እባክህ ቶሎ አምጣ እነ ልሸለምበት እያለ በማስተባበር ያንን የዘመኑን ግብር ወድያው ያስገባል ። እና መሳርያ እንጨት ነው ምን ችግር አለ ። ሌላ ነገር የምርምር መሳርያ እንደዚህ መስጠት ነው እንጂ እማያቅተን ሰው እሚያጠፋ ነገር መስጠት ምን ይቸግረናል ። ያንን እያነሳን እንሸልመዋለን ።" "ሬድዮና ጋዜጣ ይጠቀማሉ የሚባለውስ ?" "እሱማ ዋናው ነው እንጂ ። የኔ ዋናው ማበረታቻ እሱ ነው ። በቀጥታ የተሰራውን ስራ ወስጄ በሬድዮና በጋዜጣ አስነግርለታለሁ ። ያንን ጋዜጣ ደግሞ በባህር ዳር ወይም ደብረ ማርቆስ በመውጣት ቶሎ አምጥቼ እየው እንዲህ ያለ ስራ ብትሰሩ ስማችሁ በጋዜጣ ይወጣል ብየ ያንን ጋዜጣ ወስጄ ቢሯቸው ላይ እለጥፍላቸዋለሁ ። ያነ የገለ ስም በሬድዮ ተጠርቶ በጋዜጣ ወትቶ የኔ ቀበለ ሊቀር ነው ወይ ? እያለ እሚቆጭ ይበዛል ። እንዲያውም የኛ አይነገርም ባዩ እየበዛ ስለመጣ የሰራኸውን አይቼ ትክክለኛ ሆኖ ካገኘሁት ይተላለፍልሀል እምላቸው ብዙ ነበሩ ። "የርሶ ስም ብዙ ጊዜ በሬድዮ ይተላለፋል ?" "አዎ ፤ እንዲያውም ማስታወቅያ ሚኒስቴር የቆምጬ አምባው ነው ። ሁልጊዜ የሚነገረው የሱ ነው ። እሱ ገዝቷቸዋል ። ጋዜጠኞች ሲሄዱ ይጋብዛቸዋል ። ቢራ ያጠጣቸዋል ። መስተንግዶው ከባድ ነው እያሉ ይሰድቧቸዋል ። ይህንን ግን የሚያስወሩብን እንደኔ ያልሆኑ መስራት የተሳናቸው ሁላ ናቸው ። ታድያ እነሱም የት አለ ስራ ? የሰራችሁትን አሳዩንና እናስተላልፍላችሁ ሲሏቸው ምናም ዘመቻዎችም ሆነ ግብር በማሰባሰብ ሂደት የተስተካከለኝ አልነበረም ። አንደኛ ነው ሁልጊዜ የምወጣው ።" "እነዚህን ሁሉ ስራዎች ሲያከናውኑ ህብረተሰቡን ለማግባባት የሚጠቀሙበት ዘዴ ምንድነው ?" "እንግዲህ አንደኛ የበለጠ ውጤት ለማግኘት አርሶ አደሩን አለመለያየት ነው ። ሁለተኛ ደግሞ በየጊዜው ማስተማር መቀስቀስ ነው ። አብዛኛውን በማያመርትበት ቀን ስራ በማይሰራበት ቀን ሁሉም ሀላፊ ተበትኖ እሱ ዘንድ እንዲሄድ ስለምፈልግ ሁላችንም እንሄዳለን ። በዝያ በረፍት ቀን ለምን ቤተክርስቲያን አይሆንም እንዲያው እዚያ ጥሩ ነው ። ሰው አዳራሹ ተኮፍሶ ንግግር የሚጥም አይመስለውም ፤ ደሞ ሰው ሙቶም ከሆነ ባንድ በኩል ለቅሶው አያለ ባንድ በኩል ስለትምህርት ብናስተምረው ገለጻ ብናደርግለት ይሰማል ። ለላው ያው ሽልማት ማበረታቻ መስጠት ነው ።" "በችልማት ማበረታቻ ሲሉ እንዴት ነው ? ምን ምንድነው የሚሸልሙት ?" "ለምሳሌ እኔ አንድ ዝግጅት ወይም ስብሰባ እንደዚህ አዘጋጅና ደካማ የሆነውን ሊቀመንበር መጨረሻው ወንበር ላይ እንዲቀመት ነው የማደርገው ። በጣም ጎበዝ ኮከብ የሆነውን ደግሞ ግንባር ላይ ነው እማስቀምጠው ። ግብር እሚያስገባ በጸረ ስድስት ክትባት ጥሩ ውጤት ያሳየውን «ና ያንተ ወንበር ይሄ ነው» ብዬ ከፊት አስቀምጠዋለሁ ። እንደሱ ለመቀመጥ ሲል ሌላው የግድ ይሰራል ። ሌላ ደግሞ ለምሳሌ ግብር በደንብ አድርጎ ለማስገባት እነ የማሰር የማስገደድ ስልት አልጠቀምም ። ይሄ ምንድነው ተመንጃ እሱን አስመጣና 3ስቱን አንድ ላይ በማዋቀር አውላላ ሜዳ ላይ አቆመዋለሁ ። እና ቶሎ የሰሩት የላቸውም ።" "ሬድዮ ሲሉ ትዝ አለኝ ይሄስ ምንድነው አንድ ቀን እርስዎ አውቶቡስ ውስት ሆነው ወደክፍለሀገር በመጉዋዝ ላይ እያሉ እንደአጋጣሚ የዜና ሰአት ነበርና ዘና ሲወራ የእርስዎ ስም በመጠራቱ ሹፌሩን አቁም አቁም በማለት ወደመንገደኞቹ በመዞር ስሙ ስሙ ቆምጬ አምባው ማለት እኔ ነኝ በማለት ....?" "ይሄ ሀሰት ነው ። ጨርሶ ካንደበተ አልወጣም ። ለማንኛውም ጥያቄው በመቅረቡ ደስ ነው ያለኝ ። ይሄ ሊወራብኝ የቻለው እንዴት መሰለህ ? ገና የወረዳ አስተዳዳሪ ሆኜ ቢሆን እንደሄድኩኝ አንድም ወፍጮ በወረዳው አልነበረም ። እና ደካሞች እርጉዞችሰቶች ድንጋይ ከድንጋይ እያፋጩ ፍዳ ያዩ ነበር ። ስለዚህ ህዝቡን አስተባበርኩና 15 ሺ ብር እንዲያዋጣ አድርጌ ወፍጮ ቤት አስተከልኩ ። እና ያ ወፍጮ ተገዝቶ ስራ ሲጀምር በሞጣ የሚገኘው ወፍጮ ስራ ጀመረ ተብሎ በሬድዮ ተነገረ ። እና በስራና በልማት የቀደምኩዋቸው አስተዳዳሪዎች ያንን አስወሩብኝ ።" "ምን ብለው ነው ያስወሩብዎት ?" "እንደው ዝም ብለው ስራ ሳይሰሩ እየተንጠራሩ ወደ ህዋላ ይቀሩና እኔ በልማት የቀደምኩዋቸው ምን ይላሉ «ወፍጮ ስራ ጀመረ» ተብሎ በሬድዮ ሲነገር ቆምጬ አባይ ላይ ነበር ። ከአዲሳባ ወደጎጃም ይመጣ ነበር ። እና እኔ ነኝ ቆምጬ አምባው እወቁኝ ብሎ በአውቶብሱ ላይ ተናገረ ብለው ይህንን አስወሩ ። ያስወሩ ። እሚያሸንፍ ተግባርና ስራ ነው ። ሌላ ማንም ቢያወራ አይለጠፍብኝም ። የህዝቡ ማህበራዊ ችግር ግን ካለችኝ ጭላንጭል እውቀት ጋር ከዚያ ህዝብ ጋር በማገናኘት ችግሩን ልፈታለት ሞክሬያለሁ ። እንዴ ወፍጮውን እኮ እንዲያ ሳስተክለው ህዝቡ «የታለ ያ ወፍጮ እሚፈጨው ሰውዬ» እያሉ ወፍጮ አይቶ ስለማያውቅ «ለመሆኑ ምን ይመስላል ምን አይነት ሰው ነው» እስከማለት ደርሶ ነበር እኮ ።" "ደሞ ለሎች አሉ ። በርሶ ስም የሚነገሩ ቀልዶች እንደዚህ ። ስለነሱ እሚያውቁት ነገር አለ ?" "እንግዲህ እንዲህ ያለ ጥያቄ ተዚህ ቀደም ቀርቦልኝ አንድም ቀልድ እንዳልቀለድኩ ተናግሬያለሁ ። እኔ ስራ እንጂ ቀልድ አልወድም ። ለቀልድ ጊዘ አልነበረኝም ። እንዴው በየጊዘው አሁን ድረስ እዚህ እየመጡ እሚያስቸግሩኝ አሉ ። ከተለያዩ መጽሄቶች እንደዚህ መጣን እያሉ ይጠይቁኛል ። አንዳንዶቹ እንደው ባንተ ስም መጽሀፍ ልንጽፍ ፈልገን ነበር ። ወድያውም ታሪክ ነው እያሉ ይጠይቁኛል ። እኔ ግን ወይዱ እኔ የናንተ መጽሄት ማሻሻጫና ማዳመቅያ አይደለሁም ደሞም ያላልኩትን ብትሉ እከሳለሁ እያልኩ ብዙዎቹን መልሻለሁ ። "ታድያ እነዚህ ቀልዶች ከምን የመነጩ ይመስልዎታል ?" "እንግዲህ በምሳለ ልንገርህ ። ለምሳሌ እንደዚህ እንደዝያ አስወሩብኝ ። የክፍለ ሀገሩ ፓርቲ ኮሚተ ተሰብስቦ «በቀጥታ ወደሶሻሊዝም መግባት ሲቻል የብሄራዊ ዲሞክራሲ አብዮት ፕሮግራም ለምን አስፈለገ ?» በማለት ቆምጬን ጠየቀው ። ታድያ ቆምጨም «እንዴ ! ታድያ ሶሻሊዝምን በቀጥታ አታደርጉትም ? ባለስልጣኖቹ እናንተው አይደላችሁ ? ቆምጬ ከለከላችሁ ታድያ ?» ብሎ መለሰላቸው በማለት አስወሩብኝ ። እንግዲህ ይህ ምንን ያመለክታል ? እኔ ደካማ አላዋቂ መሆኔን በማሳየት ምንም አይነት የልማት ስራ መስራት እንደማልችል ለማሳየት ከማሰብ የመነጨ ነው ።" "ለምሳለ ቀድሞ በሞጣ አካባቢ አንድ ትልቅ የስፖርት ሜዳ ማሰራትዎን ገልጸውልኛል ። እና ያንን ሜዳ መርቀው ሲከፍቱ «እንግዲህ ይህን ሜዳ የምንጠቀመው በቁጠባና በእቅድ ነው ፤ በይህ መሰረት በጋ በጋ ትጫወቱበታላችሁ ። ክረምት ክረምት ደግሞ ይታረሳል .....» ብለዋል እሚባል ነገር አለ ። እና ...?" "ደግሞ እንዲህ አሉ ? ይበሉ ምናለ ። እኔ ግን ካንደበቴ አለመውጣቱን ነው እማውቀው ። ደሞ ይሄኛውን አልሰማሁትም ። እኔ የሰማሁት ሌላኛውን ነው ።" "ምንድነው የሰሙት ?" "አዎ አንደዜ ቆምጬ የስፖርት ሜዳ ሲሰራ ... እንግዲህ ያነ ሜዳው ሲሰራ ይህእ ሩል መንገድ ይጠቀጥቅ ነበር ...እና እኔም ቱታ ለብሼ ያንን መንገድ እጠቀጥቅ ነበር ። እና ምናሉ ካሳዬ አራጋው ያነ ወደሞጣ ይሄዱ ነበርና እግረ መንገዳቸውን ቆምጬን አንደ ላናግረው ብለው ና ብለው ቢጠሩት ያንን የስፖርት ሜዳ እየሰራ "አይይ እኔ አልመጣም አብዮት የማያቁዋርጥ እንቅስቃሴ ነው ። እና እኔም በአብዮታዊ ስራ እንቅስቃሴ ላይ ስለሆንኩ አቁዋርጬ አልመጣም" ብሏቸው እምቢ ብሎ ቀረ ...እያሉ አስወሩብኝ ። እና ይህእ ምንን ያሳያል ? ማእከላዊነት አለመጠበቅ ብልግናን የሚያሳይ ነው ። ግን እውነቱ እሳቸው አልመጡም ። እኔም እንዲያ አላልኩም ።" "ፖለቲካ ትምህርት በት ገብተው ነበር ?" "አዎ ገብቻለሁ ። አዎ ደሞም ከዚያ አንድ ቀልድ ነበረች ። ያነ እምፔርያሊዝም የሚባል ነገር ነበርና አንዱ ተነስቶ ክፍል ውስት ሲያወራ "ብዚ አገሮች ከቅኝ አገዛዝ ነጻ በመውጣታቸው እምፐርያሊዝም እርቃኑን ቀርቷል ..." ብሎ አለ ። እና ቆምጨም ብድግ ብሎ "ቁጭ በል አንተ ውሸታም ። እምፔርያሊዝም እርቃኑን ሲሆን ሽንት ቤት ነው ወይ ቆሞ ያየኽው ? የታባክ ነው ያየኸውን ነው የምታወራው ?" ብሎ ተናገረ እያሉ አውርተውብኛል ። እኔ ግን አላልኩም ። ""ግን የፖለቲካ ትምህርት ቤት ህይወትዎ እንዴት ነበር ? ይሄው አሁን እንኩዋን ከበተክስያን ነው የመጡት ። ሀይማኖትና ማለን እንዴት ያስከዱት ነበር ?" "አዎ እኔ መንፈሳዊነተ መቼም ቢሆን አይለየኝም ። በዚህም የተነሳ ፖለቲካ ትምህርት ቤት ውስት እየጸለየ ዳዊት ተያዘበት ብለው አስወርተዋል ። እርግጥ ግን እግዜርን መቼም ልበ አልካደውም ። ደሞም እዚያ ስገባ ማርኪሲዝም ሌኒኒዝም ያራምዳል ብለው ሳይሆን በትምህርት ቢታገዝ ህብረተሰቡን አስተባብሮ ልማትን ሊያፋትን ይችላል ብለው ነው ። በተረፈ ፖለቲካ ትምህርት በት ውስት ትዝ የሚለኝ አንድ ጊዜ ተከስሼ ነበር ። ትምህርት ቤቱ አካባቢ የሆነ ቡድን የልማት አስተባባሪ አድርገውኝ ነበር ። እና እነ ልማትና ስራ የለመድኩ ስለሆነ ካድሬዎቹ ለዘራቸውን ወርቃቸውን አድርገው ሲንጎራደዱ እነ ቱታ ለብቼ እሰራ ነበር ። እና ውሀ እጠልፋለሁ ። ድንጋይ እፈነቅላለሁ ። ምን እላለሁ ። እና ባንደዘ ሶስት ሜዳ ቆፍረ ጨረስኩ ። ይህእንን ያዩ ካድሬዎች ኡኡ ብለው ከሰሱኝ ። ገበሬውን አምጥታችሁብን በቁፋሮ ፈጀን ብለው አመለከቱብኝ ። አንሰራም ብለው አመጹ ። እና እኔም አልሰራ ካሉ ይቅር እንጂ የምን ክስ የምን ጣጣ ነው ብየ ተከራከርኩ ። ህዋላ ከሰራችሁ ስሩ ተብለው በነሱ ተፈረደ ። እንግዲህ የማስታውሰው ይሄን ይህእን ነው ።" "ከቀድሞ ባለስልጣናት ጋር የነበረዎት ግንኙነት ምን ይመስል ነበር ? ከፕሬዚዳንት መንግስቱ ጋርስ ተገናኝተው ያውቃሉ ?" "ከፕሬዚዳንቱ ጋ የሚያገናኘኝ ነገር የለም ። እነ አግኝቻቸውም አላውቅ ። ግን እኔ ያልተናገርኩትን ነገር እየተናገሩ ብዙ ነገር ተወርቷል ። እና እነም እሰጋ ነበር ። ግን የደረሰብኝ ነገር የለም ። ለምሳለ አንደዜ ምናሉ ባንድ ወቅት ሊቢያና ቻድ ተጣልተው ነበር ። እና ያነ ደሞ የወቅቱ የአፍሪካ ሊቀመንበር ፕሬዚዳንት መንግስቱ ነበሩ ። እና ካሳየ አራጋው ቆምጬን ጠርተው "ቆምጬ አንተ ጎበዝ ነህ እና ባንተ አስተያየት የሊቢያና የቻድ ግጭት ምን ይመስልሀል ?" ብለው ጠየቁትና ቆምጨም ..."እንዴ እኔን ምን ትጠይቁኛላችሁ ሊወመንበር መንግስቱ ያልቻሉትን ሂጀ ላስታርቅላችሁ ነው ወይ ..?" አለ ብለው አስወሩብኝ ። እና በለላ በኩል ደግሞ እነ ከባለስልጣናት ጋር ግንኙነት የለኝም ። እንዴውም ያን ያህል ስደክም ለአውራጃ አስተዳዳሪነት ስሾም ስመን በፍሉድ አጥፍተው ለላ ሰው ሹመውበታል ::" "እንዴው ምንም ቀልድ ወጥቶኝም አያውቅም ነው ሚሉት ?" "እኔ በጭራሽ ። እርግጥ ምንድነው እነ ያልኩትን በሌላ እያዞሩ እሚያወሩት ነገር አለ ። እነን ለማጣላት ። ለምሳሌ አንደዜ ከደብረኤልያስ ድርጃ ገብረኤል እሚባል አገር ከአንድ ዋና አስተዳዳሪ ጋር እየሄድን ነበር ። በመኪና ነበር እምንሄድ ። እሳቸው የእህል ኮታ ሊገመግሙ ነው የመጡት ። እኔ ደሞ የመሰረተ ትምህርት የምስክር ወረቀት ልሰት ነው ። እና ስንሄድ ከፊታችን 3 አህዮች እየጋለቡ ይሄዳሉ ። ይሄነዜ አስተዳዳሪው ወደነ ዞር አሉና "ቆምጬ እነዚህ አህዮች ምንድናቸው ? ከቅድም ጀምሮ ከፊት ከፊታችን ይጋልባሉ ? "ብለው ጠየቁኝ ። እና እነም "እየውልዎ እንግዲህ እርሶ በደንብ አድርገው የሚገመግሙ ከሆነ እነ ሀገር እንኩዋን ሰው ይኸው አህያውም ነቅቷል ። እናም አቀባበል መሆኑ ነው "ብዬ አልኩአቸው ። እና ይቺን ወስደው አስተዳዳሪውን "አህያ ስለሆንክ አቀባበል እሚያደርግልህ አህያ ነው "አለ ብለው ዞር አደረጉአት ።" "ሌባ አይወዱም ይባላል ለመሆኑ እንዴት እንዴት አድርገው ነበር ለባን የሚቀቱት ?" "አዎ ለባ አልወድም ። አንደዘ ቢሆን ወረዳ እያለሁ ለባ በጣም በዛብኝ ። ይሰርቃሉ የተባሉትን ሁሉ ጠራሁና ጠበንጃ እያሸከምኩ ሾምኩአቸው ። በሉ እንግዲህ ጠብቁ አልኩና ሁለት ሁለት ካርታ ጥይት ሰጠሁዋቸው ። እናንተ ታጠፋላችሁ ተብሎ በሚስጥር ተነግሮኛልና አሁን እስቲ የሚያጠፋውን እናያለን ። እናንተ ግን ጠብቁ ብየ አደራ አልኩዋቸው ። ከዝያ ከብት አይሰረቅ ። ምን አይሰረቅ ሌባ ቀጥ አለ ። ታድያልህ ቆየት ብሎ አንደዘ ልበ ጠረጠረና ጋበዝኩዋቸውና አረቄ እየጠጣን "አይ " የናንተ ነገር አሁንም ትሰርቃላችሁ አሉ "ምነው እየለመንኩዋችሁ ? መሳርያ መግፈፍ ማሰሩ አይረባም ያጣላል ። ስለዚህ እባካችሁ ?" አልኩዋቸው ። በዚህ ጊዘ አንዱ ሞቅ ብሎት ነበርና "አይይ አያ ቆምጬ እኛኮ አንሰርቅም ። ብንሰርቅም ከርሶ አገር አይደለም ከዳሞት (ዋኖስ ...ቅቅቅቅ ) ነው "አለና አረፈው ። እና እኔም አለመተዋቸውን አወቅሁ ። እና እንዲያ እያደረኩ ነው ለባ የምይዘው ። ከማባረር ከማሰር እንዲህ ቀርቦ እያጫወቱ መያዝና መክሮ መመለሱን እመርጣለሁ ።"" "ብዙ ጊዜ እንዲህ እንዲህ ገጠር ውስጥ ተዘዋውረው ሲሰሩ መቸም አስተዳዳሪ ነዎትና የቢሮዎን ስራ ምን ጊዘ ነው የሚሰሩት ? ደሞ ስብሰባ ወደላይም ወደታችም ሊኖርብዎት ይችላል ?" "እኔ ብዙ ጊዘ የቢሮ ስራ አልወድም ። 10 ቀን ቢሮ ካለሁ 20 ቀን እዳሪ ነኝ ። ስብሰባ እንኩዋን ስጠራ አልመጣም እያልኩ ብዙ ጊዜ እቃወማለሁ ። ዛሬ ተሰብስበን ነገ ስብሰባ ይሉኛል ። እነ ስንት የገጠር ስራ አለብኝ ፤ ከተቻለኝ አስፈቅዳለሁ ። ካልሆነም እምትወያዩበትን አጀንዳ በስልክ ንገሩኝ እያልኩ እጠይቃለሁ ። እና ያኔ "ስለ እህል ኮታ ስለትምህርት ስለምናምን ድክመት ነው ...." ይሉኛል ፤ አይይ እኔጋ ደህና ነው ፡ የደከመውን ጠይቁ ፤ ከደከመው ጋር ተሰባሰቡ እያልኩ ወደስራዬ እህእዳለሁ ::" የመፈክር ጋጋታ የበዛበት ሰሞን ነው ። ኢሰፓ ከመምጣቱ በፊት በኢሰፓኮ ጊዜ ። እና የጊዜው መፈክርም "ኢሰፓአኮ ተልኮ ይሳካል !" የሚል ነበር ። ታድያ ቆምጬ አንድ ቀን ንግግር አድርገው ካበቁ በሁዋላ ተገቢውን መፈክር በማሰማት ህዝቡ እንዲበተን ያደርጋሉ ። ሁዋላ በማግስቱ ትዝ ሲላቸው ከመፈክሮቹ ሁሉ "የኢሰፓአኮ ተልኮ ይሳካል !" የምትለዋን ዘንግተዋታል ። ስለዚህ ቶሎ ብለው ህዝብ እንዲሰበሰብ ያደርጉና በሉ ግራ እጃችሁን ወደላይ ይላሉ ። ህዝቡ ግራ እጁን ይሰቅላል ። ታድያ በመሀል ያቺ መዘዘኛ በፈክር አሁንም ትጠፋለች ። ቢያስቡዋት ቢሉዋት ቢሰርዋት ትዝ አልላቸው አለች ። ይሄኔ ቆመው ተናደዱና እንዲህ የሚል መፈክር አሰሙ ይባላል ። "ሰሞኑን ከመጣው መፈክር ጋ ወደፊት !" ቆምጬ የካቲት 66 ፖለቲካ ትምህርት ቤት ገብተው ለ6 ወራት የፖለቲካ ትምህርት ቀስመው ነበር ። ታድያ በዚያችው እውቀት ሲንቀሳቀሱ ከርመው ሳለ ለሎች ካድሬዎች ለተጨማሪ የፖለቲካ ትምህርት ወደ ጀርመን መሄዳቸውን ይሰማሉ ። እንዲያ ከሆነ ታድያ እሳቸው እናርጅ እናውጋ ውስት የሚቀመጡበት ምክንያት ምንድነው ? ባስቸኩዋይ ማመልከቻ ማስገባት ነበረባቸው ። ማመልከቻውን ታድያ እንዲህ ሲሉ ነው የጻፉት ይባላል ። ግዋድ ካሳዬ አራጋው የ ....ተጠሪ ። ከዚህ በፊት የካቲት 66 ገብቼ ለ6 ወራት የፖለቲካ ትምህርት መቅሰሜ ይታወቃል ። ስለሆነም በዚች ባገኘሁት ትምህርት ህብረተሰቡን ሳስተምር ቆይቼ ትምህርቱ አሁን ያለቀብኝ ስለሆነ ሌላ ተጨማሪ ትምህርት ከወደጀርመን አገኝ ዘንድ ወደዚያው እንዲልኩኝ እጠይቃለሁ ። ጋዜጠኛው ፦ ጓድ ቆምጬ አምባው ኢምፔርያሊዝምን እንዴት ያዩታል ? ቆምጬ ፦ እናንተ እንዳሻችሁ እዩት እኔ ግን በጎሪጥ ነው እማየው (አሉ ይባላል)። አንድ ከፍተኛ ባለስልጣን ቆምጬን ሊጎበኛቸው ብቅ ብሎ ኖሮ "እሺ ጓድ ቆምጬ አምባው አጠቃላይ እንቅስቃሴዎ ምን ይመስላል ?" በማለት ይጠይቃቸዋል ። ቆምጬም ሲመልሱ "...እንግዲህ በዚህ በኛ ወረዳ አብዮታዊው እንቅስቃሴ ጦፏል ። በኢኮኖሚው በኩል ገበሬው ቆላውን ሰንጎ ይዞታል ። በፖለቲካው በኩል ደሞ እነና ካድሬው ህዝቡን ሰንገን ይዘነዋል ።" አሉ ይባላል ። 5. ጋዜጠኛው ፣ “ለመሆኑ ማህበራችሁ ሴቶችን ያቅፋል ¿’’ ቆምጬም ሲመልሱ “ሲመሽ መች ይቀራል” የኢትዮጵያ ሰዎች
9591
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%89%80
ተረት ቀ
ቀለም ሲበጠበጥ ብርእ ሲቀረጥ ቀለም በቀንድ ውስጥ ጨለማ ነው ሲፃፍ ግን ብርሃን ነው ቀለም ሲበጠበጥ ብርእ ቅረጹልኝ ቀለበት ለቆማጣ ሚዶ ለመላጣ ቀሊል አማት ሲሶ በትር አላት ቀላጅ የሰይጣን ወዳጅ ቀላዋጭ ወጥ ያውቃል ቀልብ የሌለው ውሻ ጠዲቅ አምጡልኝ ይላል ቀልድና ቅዘን ቤት ያጠፋል ቀልደኛ አልቅሶ ካልተናገረ የሚያምነው የለም ቀልደኛ ገበሬ ሲያስቀን አደረ ቀልደኛ ገበሬ ናይት ክለብ ከፈተ ቀልደኛ ጎረምሳ እያራ ያፏጫል ቀልድና ቅዘን ቤት ያበላሻል ቀሙን ላይቀር ከነጫማቸው ቀማኛና ሽፍታ ጭለማና ማታ ቀርቀሬ ወርጄ ማር ስልስ ማር ልከፍል ቀስ በመቀስ አንቁላል በአግሩይሂዳል ቀስ እንዳይደፈረስ ቀስ እንዳይፈስ ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል ቀስ በቀስ አባይም ዝናብ ይሆናል ቀበሮ ናት የገጠሩዋ ሚዳቋ ናት የሰፈሩዋ ቀበሮ የበሬ ቆለጥ ይወድቅልኛል ብላ ስትከተል ዋለች ቀበቶ ለማፈኛ ሰንሰለት ለማቆራኛ ቀበኛ ማሰሪያውን በልቶ ያሳጥራል ቀበኛ ከብት ዋጋውን ያደርስ ቀባሪ በፈጣሪ ቀብረው ሲመለሱ እግዜር ይማርዎ ቀብሮ የሚመለስ የሚመለስ አይመስለውም ቀኑ የጨለመበት መንገዱ ዘንግ ነው ቀና ሲታጣ ይመለመላል ጎባጣ ቀና ቢታጣ ይመለመላል ጎባጣ ቀናውን ብነግራት ውልግድግዱን አለች ቀን ስው መስሎ ማታ ጅራት አብቅሎ ቀን ሲከፋ በግ ይነክሳል ቀን ሲጥለው ሁሉ ይጠላው ቀን ሲገለበጥ ውሀ ወደ ላይ ይፈሳል ቀን ሲደርስ አምባ ይፈርስ ቀን ሳይቆጥሩ ውሻ ሳይጠሩ ደረሰ በእግሩ ቀንበር ታርቆ ጣውንት ታርቆ ምን ይሆናል ቀንበር ታንቆ ጣውንት ታርቆ ምን ይሆናል ቀን በበቅሎ ማታ በቆሎ ቀን በቅሎ ማታ ቆሎ ቀን ቢረዝም ልብ ያደክም ቀን ቢረዝም ልብ ይደክም ቀን ቢቆጥሩ ውሻ ቢጠሩ ደረሰ በእግሩ ቀን ቢቆጥሩ ውሻ ቢጠሩ ይደርሳል በእግሩ ቀን ባጀብ ሌት በዘብ ቀን አይጥለው የቀለም ሰረገላ አያሰናክለው ቀን አይጥለው ጠጅ አያስክረው ቀን አይጥለው ጠጅ አያሰክረው የለም ቀን እስኪወጣ ያባቴ ገበሬ ያግባኝ ቀን እስኪያልፍልሽ ያባትሽ ሎሌ ያግባሽ ቀን እስኪያልፍ ያለፋል ቀን እስኪያልፍ ያባቴ ባሪያ ያግባኝ ቀን እስኪያልፍ ያባቴ ባሪያ ይግዛኝ ቀን እንደተራዳ ሌት እንደ ግርግዳ ቀን ከህዝብ ሌት ከጅብ ቀን ከጣለው ሁሉ ይጥለው ቀን ካልለቀሙ ሌት አይቅሙ ቀን ካለቀሙ ሌት አይቅሙ ቀን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል ቀን የጎደለበት ጠገራ አይጥ ይበላዋል ቀን ይነዳ እንደ ፍሪዳ ቀንና ጨርቅ እንደምንም ያልቅ ቀንና ጨርቅ ያልቃል ብልህ ያውቃል ቀንዳምን በሬ ቀንድ ቀንዱን ቀንዱ ሰማይ ጠቀስ ጭራው ምድር አበስ ቀንድ ካላት ላም ጎዳ ትከፋለች ቀንድና ጅራት ለዋንጫ አለፉ ቀንድ እገባበት ጅራት አይቀርም ቀንድ ውስጥ ገብቶ ጅራት አይቀርም ቀኝም ሰገሩ ግራም ሰገሩ መገናኛው ኮሩ ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ ቀድሞ ነበር እንጂ ተራምዶ ማለፍ አሁን ምን ይሆናል ተይዞ መለፍለፍ ቀይ ምላሱ ጥቁር እራሱ ቀይ ሰው መልክ አይፈጅም ቀይ እንደበርበሬ ጥሩ እንደ ብርሌ ቀዳዳ ያፈሳል ግቢ ያፈርሳል ቀድሞ ሰኞን አለመሆን ነው ቀድሞ የሸተውን ወፍ ይበላዋል ቀድሞ የሚናገረውን ሰው ይጠላዋል ቀድሞ የሸተውን ወፍ ይበላዋል ቀድሞ የተናገረውን ሰው ይጠላዋል ቀዶ ያለበሰ ቆርሶ ያጎረሰ ቀጥኜ ቢያየኝ ጅማት ለመነኝ ቀጥኜ ቢያዩኝ ጅማት ለመኑኝ ቀጥኜ ቢያዩኝ ሞዴል ነሽ አሉኝ ቁልቢጥ የላት ቁና አማራት ቁልቢጥ የላት ድርጎ አማራት ቁመህ ተከራከር ዙረህ ተመካከር ቁመህ ተናገር ዙረህ ተመካከር ቁመቷ ቢያጥር እንደ ድምብላል ውዷ ክፉ ነው ይደበልላል ቁም እንደአላማ ቁረጥ እንደጫማ ቁም እንዳላማ ጥልቅ እንደጫማ ቁም ነገረኛ መምሰል የተለመደ አመል ቁም ነገር ይዞ ተረት ቂም ይዞ ጸሎት ቁራ ሲነጣ አህያ ቀንድ ያወጣ ቁራ ስሙን የጠራ ቁርበት ምን ያንቋቋሀል ቢሉት ባያድለኝ ነው እንጂ የነጋሪት ወንድም ነበርኩ አለ ቁርበት ምን ያንጓጓሀል ቢሉት ባያድለኝ ነው እንጂ የነጋሪት ወንድም ነበርኩ አለ ቁርጥማት ቢያብር አልጋ ላይ ያማቅቃል ቁርጥ ያጠግባል ተስፋ ያታልላል ቁቅም ከፈስ ተቆጠረች ቁና ለመስፈሪያ ብርብራ ለማስከሪያ ቁንጥጫ ይሻላል ከግልምጫ ቁንጫ ለትልቅ ሰው ይበረታል ይባላል ቁንጫ መሄድ ሳትማር መዝለል ትማራለች ቁንጫ ሞኝ ናት ቀን ትበራለች ተለቃቅማ ታልቃለች ቁንጫ ውሀ ወረጅ ቢሏት ስፈናጠር የሰው ዶጮ እሰብር አለች ቁጥቋጦም ሲያድግ ዛፍ ይሆናል ቁጥቋጦ ሲያድግ ዛፍ ይሆናል ቁጥቋጦ ያለዛፍ አይሆንም ቁጩና ብስጩ አልማችሁ ፍጩ ቁጭትና መረቅ ለጊዜው ይጣፍጣል ቁጭትና መጠጥ ለጊዜው ይጣፍጥ ቁፍ ቁፍ አሰኘሽ እንደቄብ ዶሮ ለመከራ ላሳርሽ ኖሮ ቂል ሲረግሙት የመረቁት ይመስለዋል ቂል አይሙት እንዲያጫውት ቂልን ለብቻው ስደበው ራሱን ባደባባይ እንዲሰደብ ቂልን አንድ ጊዜ ስደበው ሲሰደብ ይኖራል ቂልን ድንጋይ ተማትቶ ጌታና ሎሌ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ ቂል ከጠገበበት አይወጣም ቂል ያገኘው ፈሊጥ ውሻ የደፋው ሊጥ ቂምህን አትርሳ የወደቀን አንሳ ቂም ይዞ ጸሎት ሳል ይዞ ስርቆት ቂም ይዞ ጸሎት ጭድ አዝሎ ወዘት ቂጡን የተወጋ ውሻ እንደልቡ አይጮህም ቂጡ የቆሰለ ውሻ እንደልቡ አይጮህም ቂጥ ቢወድል ፈስ አያድን ቂጥ ቢያብጥ ልብ አይሆንም ቂጥኛም ከውርዴ ይማከራል ቂጥኛም ከውርዴ ይውላል ቂጥ ገልቦ ክንብንብ ቂም ቂም ያሰኘሽ እንደዶሮ ለካስ ለመከራሽ ላሳርሽ ኖሮ ቂፍ ቂፍ ያሰኘሽ እንደ ቄብ ዶሮ ለመከራሽ ላሳርሽ ኖሮ ቃልህ ሳይዘጋ እግርህ ሳይዘረጋ ቄሱም ዝም መጽሀፉም ዝም ቄስ ለኑዛዜ ፍቅር ለሚዜ ቄስ ምን ይሻል ጠላ ነገር ምን ይሻል ችላ ቄስ ኤርክሶን መምህሩ እናት አያስቀብሩ ቄስ እበር አረመኔ ከማህበር ቄስ ካናዘዘው እድሜ ያናዘዘው ቄስ ካፈረሰ ዲያቆን ከረከሰ ቄስና ንብ እያዩ እሳት ይገባሉ ቄስና ንብ እያየ እሳት ይገባል ቄስ ያዘዘህን አድርግ እንጂ ቄስ ያደረገውን አታድርግ ቅል ባገሩ ድንጋይ ይሰብራል ቅል ባገሩ ደንጊያን ይሰብራል ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ሎሌና ጌታ ተሟግቶ ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ሎሌና ጌታ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ጌታና ሎሌ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ ቅልውጥ አሳስቦ ይጥላል ዘመቻ ቅምሙ የበዛበት ወጥ አይፋጅ አይኮመጥጥ ቅማል እንኳን ካቅሟ ጥብጣብ ታስፈታለች ቅማል ውሀ ውረጅ ቢሏት ስንዳሰስ ለመቼ ልደርስ ቁንጫ ውሀ ውረጅ ቢሏት ስፈናጠር የሰው ዶጮ እሰብር አሉ ቅማል በጥፍር ቢድጧት ራስ ደህና አለች ቅማል ከአካላት ምስጢር ከቤት ቋንጣና ባለሟል ሳያር አይቀርም ቅዝምዝም ወዲያ ፍየል ወዲህ ቅርብ ያለ ጠበል ልጥ ይነከርበታል ቅርናታም ለቅርናታም ሰንቡሌ ሰንቡሌ ይባባላል ቅርንጫፉ እንደዛፉ ቅቤ መዛኝ ድርቅ ያወራል ቅቤ ሲለግም ወስፌ አይበሳውም ቅቤ ተነጥሮ ለመብላት ያባት የናት ቅቤና ቅልጥም ወዴት ግጥምጥም ቅቤ ይፍሰስ ከገንፎ አይተርፍ ቅቤ ይፍሰስ ከገንፎ አይለፍ ቅብጥና ቅልጥ አንድ ላይ ሲሄዱ ቅልጥ ብላ ቀረች ሶራስ ክመንገዱ ቅል በአገሩ ድንጋይ ይሰብራል ቅናት ያደርሳል ከሞት ቅናት ጥናት አያገናኝ ካባት ከናት ቅናት ጥናት አይገኝም ከናት ካባት ቅና ያለው በአባቱ ከረባት ይቀናል ቅና ያለው በናቱ ብልት ይቀናል ቅን በቅን ከማገልገል ፊት ለፊት ማውደልደል ቅንቡርስ የት ትሄዳለህ መተማ ትደርሳለህ ልብማ ቅንነት ለነፍስ መድሀኒት ቅንድብ ለአይን ጥቅሻ አስተማረች ቅዝምዝም ሲወረወር ጎንበስ ብለህ አሳልፈው ቅዠት ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም ቆላና ደጋ እመቤትና አልጋ ቆሎ ለዘር እንዶድ ለድግር አይሆንም ቆሎን ቢቆረጥሙት እንጂ ቢያሹት አያልቅም ቆመው የሰቀሉትን ቁጭ ብለው ለማውረድ ይቸግራል ቆማጣ ቤት አንድ ጣት ብርቅ ናት ቆማጣ ብለው ያው ቁምጥና ነው ሌላ ምን ይመጣል አለ ቆማጣን ቆማጣ ካላሉት ገብቶ ይፈተፍታል ቆሩ መቀበሪያው ያው ፈሩ ቆሩ በማን ምድር ትለፋ ቆርሶ ያላጎረሱትን ቀዶ ያላለበሱትን ብላቴና ማዘዝ አይገባም ቆቅ ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ቆንጆና እሸት አይታለፍም ቆዳ ማንጓጓቱን ስሱ መጓጓቱን ቆዳ ማንጓጓቱን ስሱ መጓጓቱን አይተውም ቆዳ ሲወደድ በሬህን እረድ ቆጥሮ የማይሰጥ ሌባ ቆጥሮ የማይቀበል ሌባ
14356
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%BE%E1%88%98%20%E1%8D%8D%E1%88%8D%E1%88%B0%E1%89%B3
ጾመ ፍልሰታ
ጾመ ፍልሰታ (ከዋርካ የተወሰደ፦) <ፍልሰታ > የሚለው ቃል የሚገልጸው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለቆ መሔድን መሰደድን መፍለስን ያመለክታል። ይህም የእመቤታችንን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን በኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለማመልከት ይነገራል። ጾመ ፍልሰታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፷፬ ዓመት በዚች ምድር ኖራ እንደ አንድ ልጇ መሞቷን መነሣቷንና ማረጓን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት የጾሙት ጾም ነው። ጾሙ ከነሐሴ ፩ ቀን እስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን ሲጾም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዐዋጅ ከደነገገቻቸው ሰባቱ አጽዋማትም አንዱ ነው። ሃይማኖታዊ መሠረት እመቤታችን ከአባቷ ከኢያቄም እና ከናቷ ከሐና ነሐሴ ፯ ቀን ተፀንሳ ግንቦት ፩ ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች። <እምሊባኖስ ትወጽዕ መርአት ፦ ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች > እንደተባለ ። እመቤታችን በእናት አባቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ አሥራ ኹለት ዓመት፤ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ፡ ከዮሐንስ ወልደዘብዴዎስ ዘንድ አሥራ አራት ዓመት ከዘጠኝ ወር ቆይታ በ ፷፬ ዓመት ዕድሜዋ በ፵፱ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። የእመቤታችንን ስም የሚገልጹ የውዳሴ ጽሑፎችም በዕድሜዋ ልክ ተደርሰዋል። ለምሳሌ የውዳሴ ማርያም ቁጥር ፷፬ ነው፤ የመልክዐ ማርያም ቁጥርም ፷፬ ነው። ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰባስበው አስከሬኗን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ለማሳረፍ ሲሄዱ አይሁድ ለተንኮል አያርፉምና ተተናኮሏቸው። ቀድሞ ልጇ ሞቶ ተነሣ፣ ዐረገ እያሉ ሲያስቸግሩን ይኖራሉ: ደግሞ አሁን እሷም ተነሣች፣ ዐረገች ሊሉ አይደል በማለት አይሁድ ተሰባስበው አስከሬኗን ለማቃጠል ሲተናኮሉ እግዚአብሔር በተአምር ከነዚያ አይሁዶች አድኗቸዋል ። የእመቤታችንንም አስከሬን ነጥቆ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አኑሮታል። ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በዐረፈች በስምንተኛው ወር ከነሐሴ ፩ ጀምሮ እስከ ነሐሴ ፲፬ ቀን ድረስ ኹለት ሱባዔ ይዘው በአሥራ አራተኛው ቀን ሥጋዋን ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በምህላ በፍጹም ደስታ በጌቴሰማኔ አሳረፉት ። በሦስተኛውም ቀን ተነሥታ ስታርግ ከሰኡቃዊያን ወገን የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አያት። እርሱም በቀብር ሥርዓቱ ጊዜም አልነበረም። ሀገረ ስብከቱ ህንድ ስለነበር ሊያስተምር ወደዛው ሂዶ ነበርና። በዚያም ሲያስተምር ሰንብቶ በደመና ተጭኖ ሲመጣ ያገኛታል። ትንሣኤዋን ከርሱ ሰውራ ያደረገች መስሎት አዝኖ «ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀርቼ ነውን ?» ብሎ ቢያዝንባት እመቤታችንም ከርሱ በቀር ማንም ትንሣኤዋን እንዳላየ ነግራ አጽናናችው። ለሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲነግራቸው ለምልክትም /ለምስክርም እንዲሆነው ሰበኗን /መግነዟን ሰጥታው ዐረገች። ቶማስም ኢየሩሳሌም ደርሶ ሐዋርያትን «የእመቤታችን ነገርስ እንደምን ሆነ?» ሲል ቢጠይቅ «አግኝተን ቀበርናት እኮ» አሉት። እርሱ ምስጢሩን አዉቆ ደብቆ «ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር» እንዴት ይሆናል ? አይደረግም ይላቸዋል። ሊያሳያቸውም መቃብሩ ዘንድ ሂደው ቢከፍቱት አጧት። እርሱም «አታምኑኝም ብዬ እንጂ እርሷስ ተነሥታ ዐርጋለች» በማለት ኹኔታውን ተረከላቸውና ለምስክር ይሁንህ ብላ የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው። ከዚህ በኋላ ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ ሰበኑን ተካፍለው ወደየአህጉረ ስብከታቸው ሄዱ። ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የዚያ ሰበን ምሳሌ ነው። በዓመቱ ሐዋርያት ከያሉበት ተሰባስበው ቶማስ ትንሣኤሽን አይቶ እኛስ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምርው ሱባዔ ቢይዙ ከኹለት ሱባዔ በኋላ እንደገና ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ለማየት በቅተዋል። ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናም ምእመኖቿ ከእመቤታችን በረከትን እንዲያገኙ ይጾሙ ዘንድ ይህን ሐዋርያት የጾሙትን ጾም እንዲጾሙ ዐዉጃለች። ምእመናንም በተለየ መልኩ በጾም በጸሎት በሱባዔ ጽሙድ ሆነው ይህን ወቅት ያሳልፋሉ። የእመቤታችን ትንሣኤ ድንገት እንደእንግዳ ደራሽ እንደ ውሃ ፈሳሽ የተደረገ ሳይሆን በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት የተገለጸ ነው። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር ፻፴፩ ቁጥር ፲ ላይ «አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦትም» ይላል። በዚህም ምእመናንን ወደ ምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህ ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ አለ። ታቦት የጽላት ማደርያ እንደሆነ ሁሉ እመቤታችንም ለክርስቶስ ማደርያ በመሆኗ አማናዊት ታቦት ትባላለች። ንጉሥ ሰሎሞንም በመኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፲ ላይ «ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ፤ ወዳጄ ሆይ ተነሽ፡ ውበቴ ሆይ ነይ» ብሏል። እዚህ ላይ «ወዳጄ ...ውበቴ»" የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት ። ክቡር ዳዊት መዝሙር ፵፭ ቁጥር ፱ ላይ «በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች» እንደሚል ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛነቱን ከፈጸመ በኋላ ወደ ቀደመ ክብሩ እንዳረገ እመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም በቀኙ ትቀመጥ ዘንድ «ተነሽ ነይ» አላት ። እንግዲህ ይህንና የመሰለዉን ሁሉ ይዘን የእናታችንን ዕረፍቷንና ትንሣኤዋን እንዘክራለን እንመሰክራለንም። ዋቢ ምንጮች
44202
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8D%E1%88%AC%E1%8B%B2%20%E1%88%98%E1%88%AD%E1%8A%A9%E1%88%AA
ፍሬዲ መርኩሪ
የእንግሊዝ ሰዎች ፍሬዲ ሜርኩሪ (ፋሮክ ቡልሳራ ተወለደ፤ ሴፕቴምበር 5 1946 - ህዳር 24 ቀን 1991) የሮክ ባንድ ንግስት እንግሊዛዊ ዘፋኝ፣ ዘፋኝ፣ ሪከርድ አዘጋጅ እና መሪ ድምፃዊ ነበር። በሮክ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከታላላቅ ዘፋኞች አንዱ እንደሆነ የሚነገርለት፣ እሱ በሚያምር የመድረክ ስብዕና እና ባለአራት-ኦክታቭ የድምጽ ክልል ይታወቅ ነበር። ሜርኩሪ በከፍተኛ የቲያትር ስልቱ የንግስት ጥበባዊ አቅጣጫ ላይ ተጽዕኖ በማድረግ የሮክ ግንባር ሰውን ስምምነቶች ተቃወመ።እ.ኤ.አ. በ1946 በዛንዚባር ከፓርሲ-ህንድ ወላጆች የተወለዱት ከስምንት አመቱ ጀምሮ በህንድ የእንግሊዘኛ አዳሪ ትምህርት ቤት ገብተው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ዛንዚባር መለሱ። በ1964 ቤተሰቡ የዛንዚባርን አብዮት ሸሽተው ወደ ሚድልሴክስ፣ እንግሊዝ ሄዱ። ሙዚቃን ለአመታት አጥንቶ በመፃፍ በ1970 ከጊታሪስት ብራያን ሜይ እና ከበሮ መቺው ሮጀር ቴይለር ጋር ንግስት ፈጠረ። ሜርኩሪ “ገዳይ ንግስት”፣ “ቦሄሚያን ራፕሶዲ”፣ “የምትወደው ሰው”፣ “እኛ ሻምፒዮንሺፕ ነን”፣ “አሁን አታስቁመኝ” እና “ፍቅር የሚባል ትንሽ ነገር”ን ጨምሮ ሜርኩሪ ለንግስት በርካታ ስራዎችን ጽፏል። በ1985 የቀጥታ እርዳታ ኮንሰርት ላይ እንደታየው የካሪዝማቲክ የመድረክ ትርኢቶቹ ብዙ ጊዜ ከተመልካቾች ጋር ሲገናኝ አይተውታል። በብቸኝነት ሙያ መርቷል እና ለሌሎች አርቲስቶች ፕሮዲዩሰር እና እንግዳ ሙዚቀኛ ሆኖ አገልግሏል። ሕይወትና ሙያ ፍሬዲ መርኩሪ መስከረም 5 ቀን 1946 በብሪታንያ የዛንዚባር (የአሁኗ የታንዛኒያ ክፍል) ግዛት ውስጥ በሚገኘው የድንጋይ ከተማ ውስጥ ፋሮክ ቡልሳራ ተወለደ ። ወላጆቹ ጄር እና ቦሚ ቡልሳራ ናቸው ። ሁለቱም ፓርሲዎች ነበሩ ። አባቱ የመንግሥት ቅርንጫፍ ቢሮ በሆነው በብሪታንያ ቅኝ ግዛት ቢሮ ውስጥ ገንዘብ በመክፈል ይሠራ ነበር ። መርኩሪ ካሽሚር የምትባል ታናሽ እህት ነበረችው ። በትምህርት ቤት ጓደኞቹ "ፍሬዲ" የሚል ስም ሰጡት። ከዚያም ቤተሰቦቹ ፍሬዲ ብለው መጥራት ጀመሩ ። ሜርኩሪ ስምንት ዓመት ሲሆነው በሕንድ ወደሚገኝ አዳሪ ትምህርት ቤት ተላከ ። በፓንችጋኒ የሚገኘው የቅዱስ ፔተርስ ኢንግሊሽ አዳሪ ትምህርት ቤት ከቦምቤይ ከተማ (አሁን ሙምባይ ይባላል) 50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። እንደ ሠዓሊና ስፖርተኛ ተሰጥኦ ማሳየት ጀመረ ። አሥር ዓመት ሲሆነው የጠረጴዛ ቴኒስ የትምህርት ቤት ሻምፒዮን ሆኖ ተሾመ ። አሥራ ሁለት ዓመት ሲሞላው ጁኒየር ኦል ራውንደር የተባለ ሽልማት አገኘ። ከምረቃ በኋላ መርኩሪ ከተከታታይ የሙዚቃ ቡድኖች ጋር በመተባበር ለንደን ውስጥ በኬንሲንግተን ማርኬት ውስጥ ከሮጀር ቴይለር ጋር ሁለተኛ እጅ ያላቸውን የኤድዋርድያን ልብሶችና መጎናፀፊያዎች ሸጠ። ቴይለር እንዲህ በማለት ታስታውሳለች፦ "በዚያን ጊዜ እንደ ዘፋኝ የማውቀው ነገር አልነበረም፤ የትዳር ጓደኛዬ ብቻ ነበር። የኔ እብድ የትዳር ጓደኛ! ደስ የሚለኝ ነገር ካለ እኔና ፍሬዲ አብዛኛውን ጊዜ በዚህ ሥራ እንካፈል ነበር።"በተጨማሪም በሂትሮ አውሮፕላን ማረፊያ የሻንጣ አስተናጋጅ ሆኖ ተሠራ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሌሎች ጓደኞቹ ደግሞ ለሙዚቃ ከፍተኛ ፍላጎት ያለው ጸጥታ የሰፈነበትና ዓይናፋር ወጣት እንደሆነ ያስታውሱታል። በ1969 በሊቨርፑል የሚገኘውን ኢቤክስ የተባለ የሙዚቃ ባንድ ተቀላቀለ። ከጊዜ በኋላ የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን ይህ የሙዚቃ ባንድ "እጅግ ሄንድሪክስ ስታይል፣ ከባድ ብሉስ" የሚል ስያሜ ተበየነበት። ለጥቂት ጊዜ የሚኖረው በሊቨርፑል ሞስሊ ሂል አውራጃ በፔኒ ሌን አቅራቢያ በሚገኝ ዶቭዴል ታወርስ በተባለ ማረፊያ ውስጥ ነበር።ሜርኩሪ በንግስት ታላቅ ሂትስ አልበም ላይ ካሉት 17 ዘፈኖች 10 ቱን ጽፏል፡- “ቦሄሚያን ራፕሶዲ”፣ “ሰባት የባህር ራይ”፣ “ገዳይ ንግሥት”፣ “የሚወደው ሰው”፣ “የድሮው ዘመን ፍቅረኛ ልጅ”፣ “እኛ ሻምፒዮን ነን። "፣ "የብስክሌት ውድድር"፣ "አሁን አታስቁምኝ"፣ "ፍቅር የሚባል ትንሽ ነገር" እና "ጨዋታውን ተጫወት"። በ2003 ሜርኩሪ ከቀሪዋ ንግሥት ጋር ወደ ዘፈን ጸሐፊዎች አዳራሽ ገብቷል እና እ.ኤ.አ. በ 2005 አራቱም የባንዱ አባላት ከብሪቲሽ የዘፈን ጸሐፊዎች፣ አቀናባሪዎች እና ደራሲያን የላቀ የዘፈን ስብስብ ለሆነው የአይቮር ኖቬሎ ሽልማት ተሸልመዋል። የዘፈኑ አጻጻፍ በጣም ታዋቂው ገጽታ የሚጠቀማቸው ዘውጎችን ያካተተ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ሮክቢሊ፣ ተራማጅ ሮክ፣ ሄቪ ሜታል፣ ወንጌል እና ዲስኮ ይገኙበታል። እ.ኤ.አ. በ 1986 ቃለ መጠይቅ ላይ እንዳብራራው ፣ "እኔ ያንኑ ነገር ደጋግሜ ደጋግሜ እጠላለሁ ። አሁን በሙዚቃ ፣ በፊልም እና በቲያትር ውስጥ ምን እየሆነ እንዳለ ማየት እና እነዚህን ሁሉ ነገሮች ማካተት እፈልጋለሁ ። " ከብዙ ታዋቂ የዘፈን ደራሲዎች ጋር ሲነጻጸር፣ ሜርኩሪ በሙዚቃ የተወሳሰቡ ነገሮችንም የመፃፍ ዝንባሌ ነበረው። ለምሳሌ፣ "ቦሂሚያን ራፕሶዲ" በአወቃቀሩ ዑደታዊ ያልሆነ እና በደርዘን የሚቆጠሩ ኮረዶችን ያካትታል። እንዲሁም በርካታ ቁልፍ ለውጦችን እና ውስብስብ ነገሮችን የሚመለከቱ ስድስት ዘፈኖችን ከንግስት ጽፏል። "ፍቅር የሚባል ትንሽ ነገር" በአንፃሩ በውስጡ ጥቂት ኮረዶችን ብቻ ይዟል። ምንም እንኳን ሜርኩሪ ብዙ ጊዜ በጣም የተወሳሰበ ስምምነትን ቢጽፍም ሙዚቃ ማንበብ እንደማይችል ተናግሯል። አብዛኞቹን ዘፈኖቹን በፒያኖ የጻፈ ሲሆን የተለያዩ ቁልፍ ፊርማዎችን ተጠቅሟል። የግል ሕይወት እ.ኤ.አ. በ1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ ሜርኩሪ ከሜሪ ኦስቲን ጋር የረዥም ጊዜ ግንኙነት ነበረው ፣ እሱም በጊታሪስት ብሪያን ሜይ በኩል አገኘው። በሎንዶን ፉልሃም የተወለደችው ኦስቲን ሜርኩሪን በ1969 ዓመቷ 19 አመቷ እና 24 አመቱ ነበር ንግስት ከመፈጠሩ ከአንድ አመት በፊት ተገናኘች። በለንደን ዌስት ኬንሲንግተን ውስጥ ለብዙ ዓመታት ከኦስቲን ጋር ኖሯል። እ.ኤ.አ. በ1970ዎቹ አጋማሽ ላይ በኤሌክትራ ሪከርድስ ውስጥ የአሜሪካ ሪከርድ ሥራ አስፈፃሚ ከሆነው ዴቪድ ሚንስ ጋር ግንኙነት ጀመረ። በዲሴምበር 1976 ሜርኩሪ ስለ ጾታዊ ስሜቱ ለኦስቲን ነገረው፣ ይህም የፍቅር ግንኙነታቸውን አቆመ።ሜርኩሪ ከተጋሩት አፓርታማ ወጥታ አውስቲን የራሷን ቦታ ገዛችው በአቅራቢያው በሚገኘው የ12 ፣ ። ሜርኩሪ እና ኦስቲን በዓመታት ውስጥ ጓደኛሞች ሆነው ቆይተዋል፣ ሜርኩሪ እንደ ብቸኛ እውነተኛ ጓደኛው ይጠቅሳት ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1985 ቃለ መጠይቅ ላይ ሜርኩሪ ስለ ኦስቲን ሲናገር ፣ "ሁሉም ፍቅረኞች ማርያምን ለምን መተካት እንደማይችሉ ጠየቁኝ ፣ ግን በቀላሉ የማይቻል ነው ። ያለኝ ብቸኛ ጓደኛ ማርያም ናት ፣ እና ሌላ ማንንም አልፈልግም። ለእኔ። እሷ የእኔ የጋራ ሚስት ነበረች, ለእኔ, ጋብቻ ነበር, እርስ በርሳችን እናምናለን, ይህ ለእኔ በቂ ነው. የሜርኩሪ የመጨረሻ ቤት ፣ የአትክልት ስፍራ ሎጅ ፣ ሃያ ስምንት ክፍል የጆርጂያ መኖሪያ በኬንሲንግተን በሩብ ሄክታር መሬት ላይ ባለው የአትክልት ስፍራ ውስጥ በከፍተኛ የጡብ ግድግዳ የተከበበ ፣ በኦስቲን ተመርጧል። ኦስቲን ሥዕሉን አርቲስት ፒርስ ካሜሮን አገባ; ሁለት ልጆች አሏቸው. ሜርኩሪ የበኩር ልጇ የሪቻርድ አባት ነበር በፈቃዱ፣ ሜርኩሪ የለንደን ቤቱን ለኦስቲን ለቆ ሄደው ነግሯታል፣ "አንቺ ሚስቴ ትሆኚ ነበር፣ እና ለማንኛውም ያንቺ ይሆን ነበር።" እ.ኤ.አ. በ1980ዎቹ መጀመሪያ ላይ እስከ 1980ዎቹ አጋማሽ ድረስ በቪዲዮው ላይ “ከባድ ሕይወት ነው” ከሚለው ኦስትሪያዊቷ ተዋናይ ባርባራ ቫለንቲን ጋር እንደተገናኘ ተዘግቧል። በዚህ ጊዜ ሜርኩሪ ከጀርመናዊው ሬስቶራንት ዊንፍሪድ "ዊኒ" ኪርችበርገር ጋር ተገናኘ። ሜርኩሪ የሚኖረው በኪርችበርገር አፓርታማ ሲሆን እ.ኤ.አ. ኪርችበርገር የሰጠውን የብር የሰርግ ባንድ ለብሶ ነበር። አንድ የቅርብ ጓደኛው በጀርመን ውስጥ የሜርኩሪ "ታላቅ ፍቅር" በማለት ገልጾታል. እ.ኤ.አ. በ1985 ሌላ የረጅም ጊዜ ግንኙነት ከአይሪሽ ተወላጅ ፀጉር አስተካካይ ጂም ኸተን እሱም እንደ ባሌ ከጠራው ጋር ጀመረ። ሜርኩሪ ግንኙነታቸውን በመጽናናት እና በመረዳት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጾ "በታማኝነት የተሻለ ነገር መጠየቅ አልቻለም" ብሏል። እ.ኤ.አ. በ1990 የኤችአይቪ ፖዘቲቭ ምርመራ ያደረገው ሑተን ከሜርኩሪ ጋር በህይወቱ ላለፉት ሰባት አመታት ኖሯል፣ በህመም ጊዜ ሲያጠቡት እና ሲሞት በአልጋው አጠገብ ተገኝቷል። ሜርኩሪ እስከ ህይወቱ ፍጻሜ ድረስ በ 1986 በ የተሰጠውን የወርቅ የሰርግ ባንድ ለብሷል። በእሱ ላይ ተቃጥሏል. ሁተን በኋላ ከለንደን እሱ እና ሜርኩሪ አየርላንድ ውስጥ ለራሳቸው ወደገነቡት ባንጋሎው ተዛወረ። ወሲባዊ ግንኙነት አንዳንድ ተንታኞች ሜርኩሪ የፆታ ስሜቱን ከህዝብ እንደደበቀ ሲናገሩ፣ ሌሎች ደግሞ በታህሳስ 1974 "ግልፅ ግብረ ሰዶማዊ" ነበር ሲሉ በቀጥታ ሲጠየቁ "ታጠፈ እንዴት ነው?" በኒው ሙዚካል ኤክስ ፕረስ ሜርኩሪ እንዲህ ሲል መለሰ፡- "አንተ ተንኮለኛ ላም ነህ። እስቲ እንዲህ እናድርገው፡ ወጣት እና አረንጓዴ ሆኜ የነበርኩባቸው ጊዜያት ነበሩ። ይህ የትምህርት ቤት ልጆች የሚያልፉበት ነገር ነው። በትምህርት ቤት ልጅ ቀልዶችን አግኝቻለሁ። ከዚህ በላይ ማብራሪያ አልሰጥም።"ከ21 አመት በላይ በሆኑ አዋቂ ወንዶች መካከል የተፈፀመው የግብረ-ሰዶማዊነት ድርጊት ከሰባት አመት በፊት በ1967 በዩናይትድ ኪንግደም ከወንጀል ተፈርዶበታል። እ.ኤ.አ. በ1980ዎቹ ህዝባዊ ዝግጅቶች ወቅት ሜርኩሪ ብዙውን ጊዜ ከባልደረባው ጂም ሀተን ይርቃል። እ.ኤ.አ. በ1982 ሜርኩሪ የኤችአይቪ ምልክቶችን እያሳየ መሆኑን የሚጠቁሙ ምልክቶች ነበሩ። ማት ሪቻርድስ እና ማርክ ላንግቶርን የተባሉ ደራሲዎች ስለ ሜርኩሪ፣ ሰሚው ቱ ሎቭ፡ ዘ ላይፍ፣ ሞት እና የፍሬዲ ሜርኩሪ ቅርስ በሚለው የህይወት ታሪካቸው መጽሃፋቸው ላይ ሜርኩሪ በድብቅ ጎበኘ ብለው ተናግረዋል። በኒውዮርክ ከተማ የሚኖር ዶክተር በምላሱ ላይ ነጭ ጉዳት እንዲደርስበት (ይህም ጸጉራም ሉኮፕላኪያ ሊሆን ይችላል፣ የኢንፌክሽን የመጀመሪያ ምልክቶች አንዱ ሊሆን ይችላል) ከጥቂት ሳምንታት በፊት ንግስቲቱ የመጨረሻ አሜሪካዊቷ ሜርኩሪ በሴፕቴምበር 25 ቀን 1982 በቅዳሜ የቀጥታ ስርጭት። በቅርቡ በኤችአይቪ ከተያዘ ሰው ጋር ተያይዞ ለመጨረሻ ጊዜ በአሜሪካ በተገኙበት በዚያው ቀን ተጨማሪ ምልክቶችን ማሳየት እንደጀመረም ገልጿል።በጥቅምት 1986 የብሪቲሽ ፕሬስ ሜርኩሪ ደሙ ለኤችአይቪ/ኤድስ በሃርሊ ስትሪት ክሊኒክ መፈተኑን ዘግቧል። እንደ ባልደረባው ጂም ኸተን ገለጻ፣ ሜርኩሪ በኤፕሪል 1987 መጨረሻ ላይ ኤድስ እንዳለበት ታወቀ። በዚያን ጊዜ አካባቢ ሜርኩሪ በቃለ ምልልሱ ላይ የኤችአይቪ ምርመራ እንዳደረገ ተናግሯል።የብሪታንያ ፕሬስ ወሬውን በሚቀጥሉት ጥቂት አመታት ውስጥ ተከታትሏል, ይህም በሜርኩሪ እየጨመረ መምጣቱ, ንግስት ከጉብኝት መቅረት እና ከቀድሞ ፍቅረኛሞች እስከ ታብሎይድ ጆርናሎች ዘገባዎች ተነሳሳ. እ.ኤ.አ. በ 1990 ስለ ሜርኩሪ ጤና ብዙ ወሬዎች ነበሩ ። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ.ሜርኩሪ እና የስራ ባልደረቦቹ እና ጓደኞቹ ውስጣዊ ክበብ ታሪኮቹን ያለማቋረጥ ክደዋል። ሜርኩሪ ስለ ህመሙ ቀደም ብሎ በመናገር የኤድስን ግንዛቤ ሊረዳ ይችላል ተብሏል። ሜርኩሪ የቅርብ ሰዎች ለመጠበቅ የእሱን ሁኔታ በምስጢር ይጠብቅ ነበር; ሜይ በኋላ ሜርኩሪ ህመሙን ለቡድኑ ያሳወቀው በጣም ቀደም ብሎ መሆኑን አረጋግጧል። በግንቦት 1991 የተቀረፀው "እነዚህ የህይወታችን ቀናት ናቸው" የተሰኘው የሙዚቃ ቪዲዮ ከካሜራ ፊት ለፊት ባደረገው የመጨረሻ ትዕይንት ላይ በጣም ቀጭን የሆነ ሜርኩሪ ያሳያል። የቪዲዮው ዳይሬክተር ሩዲ ዶልዛል አስተያየታቸውን ሲሰጡ "ኤድስ መቼም ቢሆን ርዕሰ ጉዳይ አልነበረም። ተወያይተንበት አናውቅም። ስለ ጉዳዩ መነጋገር አልፈለገም። አብዛኛው ሰዎች ከባንዱ በቀር 100 ፐርሰንት በሽታው እንዳለበት አያውቅም ነበር። እና በውስጠኛው ክበብ ውስጥ ያሉ ጥቂት ሰዎች። ሁልጊዜም እንዲህ ይላል፡- 'ያጋጠመኝን አሳዛኝ ነገር በመንገር በሌሎች ሰዎች ላይ ምንም አይነት ሸክም መጫን አልፈልግም።'" ሜርኩሪ ወደ ውስጥ መግባት እንደሚችል ሲሰማው የቀሩት የባንዱ ለመቅዳት ተዘጋጅተው ነበር። ስቱዲዮው, ለአንድ ወይም ለሁለት ሰአት በአንድ ጊዜ. ሜይ ስለ ሜርኩሪ ተናግራለች: "በቃ ደጋግሞ ተናገረኝ. ብዙ ፃፉኝ. ነገሮችን ፃፉልኝ. ይህን ብቻ መዘመርና ላደርገው እፈልጋለሁ እናም እኔ ስሄድ ልጨርሰው ትችላለህ." እሱ ምንም ፍርሃት አልነበረውም። የእነዚያ የመጨረሻዎቹ ክፍለ ጊዜዎች ረዳት መሐንዲስ ጀስቲን ሺርሊ-ስሚዝ “ይህን ለሰዎች ለማስረዳት ከባድ ነው፣ ግን የሚያሳዝን አልነበረም፣ በጣም ደስተኛ ነበር። ከእሱ ጋር ብዙ ጊዜ እየሳቅኩ ነበር. ፍሬዲ ስለ [ህመሙ] 'ስለ ጉዳዩ አላስብም, ይህን አደርጋለሁ' እያለ ነበር. " በሰኔ 1991 ከንግሥት ጋር የሠራው ሥራ ከተጠናቀቀ በኋላ ሜርኩሪ በምዕራብ ለንደን ወደሚገኘው ቤቱ ጡረታ ወጣ። የቀድሞ ባልደረባው ሜሪ ኦስቲን በመጨረሻዎቹ ዓመታት ልዩ ምቾት ነበረው እና ባለፉት ጥቂት ሳምንታት እሱን ለመንከባከብ መደበኛ ጉብኝት አድርጓል። በህይወቱ መገባደጃ አካባቢ ሜርኩሪ ዓይኑን ማጣት ጀመረ እና ከአልጋው መውጣት ስላልቻለ እምቢ አለ። ሜርኩሪ መድሃኒት በመከልከል ሞቱን ማፋጠንን መርጧል እና የህመም ማስታገሻ መድሃኒቶችን ብቻ ወሰደ. እ.ኤ.አ. ህዳር 22 ቀን 1991 ሜርኩሪ የንግሥቲቱን ሥራ አስኪያጅ ጂም ቢች ወደ ኬንሲንግተን ቤታቸው ጠርተው ሕዝባዊ መግለጫ በማግሥቱ የተለቀቀውን፡- ባለፉት ሁለት ሳምንታት በፕሬስ ላይ የወጣውን ግዙፍ ግምት ተከትሎ፣ የኤችአይቪ ፖዘቲቭ መሆኔን እና ኤድስ እንዳለብኝ ማረጋገጥ እፈልጋለሁ። በዙሪያዬ ያሉትን ሰዎች ግላዊነት ለመጠበቅ ይህን መረጃ እስከ ዛሬ ሚስጥራዊ ማቆየት ትክክል ሆኖ ተሰማኝ። ሆኖም በዓለም ዙሪያ ያሉ ጓደኞቼ እና አድናቂዎቼ እውነቱን የሚያውቁበት ጊዜ አሁን ደርሷል እናም ሁሉም ሰው ከእኔ ፣ ከዶክተሮቼ እና በዓለም ዙሪያ ካሉት ሁሉ ጋር ይህንን አስከፊ በሽታ ለመዋጋት እንደሚተባበር ተስፋ አደርጋለሁ። ግላዊነቴ ሁል ጊዜ ለእኔ ልዩ ነው እና በቃለ መጠይቅ እጦት ታዋቂ ነኝ። እባክዎ ይህ ፖሊሲ እንደሚቀጥል ይረዱ። የሜርኩሪ የቀብር ሥነ ሥርዓት የተካሄደው በኅዳር 27 ቀን 1991 በዞራስትራሪያን ቄስ በምዕራብ ለንደን ክሪማቶሪየም የተከናወነ ሲሆን በልደቱ ስም በፕሊንዝ ይከበራል። በሜርኩሪ አገልግሎት ቤተሰቦቹ እና 35 የቅርብ ጓደኞቹ ኤልተን ጆን እና የንግስት አባላትን ጨምሮ ተገኝተዋል። የእሱ የሬሳ ሣጥን በአሬታ ፍራንክሊን "እጄን ውሰድ፣ ውድ ጌታ"/"ጓደኛ አለህ" የሚለውን ድምፅ ለማግኘት ወደ ጸሎት ቤቱ ተወሰደ። በሜርኩሪ ፍላጎት መሰረት ሜሪ ኦስቲን የተቃጠለውን አስክሬን ወስዳ ባልታወቀ ቦታ ቀበራቸው። አመድ ያለበት ቦታ የሚያውቀው በኦስቲን ብቻ እንደሆነ ይታመናል, እሱም እሷ ፈጽሞ እንደማትገልጽ ተናገረች። ሜርኩሪ በህይወት በነበረበት ወቅት ብዙ ሀብቱን አውጥቶ ለበጎ አድራጎት ሰጠ፣ በሞተበት ወቅት ንብረቱ 8 ሚሊዮን ፓውንድ ይገመታል። ቤቱን፣ ገነት ሎጅን እና አጎራባችውን ሜውስን፣ እንዲሁም 50% የሚሆነውን በግል ባለቤትነት የተያዘውን አክሲዮን ለማርያም አውስቲን አስረክቧል። እህቱ ካሽሚራ ኩክ 25% ተቀብላለች፣ ልክ እንደ ወላጆቹ ቦሚ እና ጄር ቡልሳራ፣ ኩክ በሞቱበት ጊዜ ያገኙታል። ለጆ ፋኔሊ £500,000 ፈቅዷል; £500,000 ወደ ጂም ሁተን; £500,000 ለፒተር ፍሪስቶን; እና £100,000 ለ ። በሎጋን ቦታ የሚገኘው የገነት ሎጅ ውጫዊ ግድግዳዎች የሜርኩሪ መቅደስ ሆነ፣ ሀዘንተኞችም ግድግዳውን በግራፊቲ መልእክቶች በመሸፈን ግብር እየከፈሉ ነው። ከሞተ ከሶስት አመታት በኋላ ታይም አውት መጽሔት "ከቤቱ ውጭ ያለው ግድግዳ የለንደን ትልቁ የሮክ 'ን ሮል ቤተመቅደስ ሆኗል" ሲል ዘግቧል። አድናቂዎች ኦስቲን ግድግዳውን እስከሚያጸዳበት ጊዜ ድረስ በግድግዳዎች ላይ እስከ 2017 ድረስ በግድግዳዎች ላይ በሚታዩ ፊደላት ለማክበር ጉብኝታቸውን ቀጠሉ። ሁተን በ2000 የሜርኩሪ የሕይወት ታሪክ፣ ፍሬዲ ሜርኩሪ፣ ያልተነገረው ታሪክ ውስጥ ተሳትፏል፣ እና በሴፕቴምበር 2006 የሜርኩሪ 60ኛ ልደት ለሚሆነው ለታይምስ ቃለ መጠይቅ ሰጥቷል። ቅርስ እና ትውስታ በሮክ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከታላላቅ መሪ ዘፋኞች አንዱ ተብሎ የሚታሰበው፣ እሱ በሚያስደንቅ የመድረክ ሰው እና በአራት-ኦክታቭ የድምፅ ክልል ይታወቅ ነበር። ሜርኩሪ በከፍተኛ የቲያትር ስልቱ የንግስት ጥበባዊ አቅጣጫ ላይ ተጽዕኖ በማድረግ የሮክ ግንባር ሰውን ስምምነቶች ተቃወመ። የሜርኩሪ ሞት ምን ያህል የንግሥቲቱን ተወዳጅነት እንዳሳደገው ግልጽ አይደለም። እ.ኤ.አ. በ1980ዎቹ የንግስት ተወዳጅነት ባነሰባት ዩናይትድ ስቴትስ የንግስት አልበሞች ሽያጭ በ1992 እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በ1992 አንድ አሜሪካዊ ተቺ “ሲኒኮች ‘የሞተ ኮከብ’ ብለው የሚጠሩት ነገር ሥራ ላይ እንደዋለ—ንግሥት በትልቅ ትንሳኤ መሃል ላይ ትገኛለች” ብለዋል። "ቦሄሚያን ራፕሶዲ" የተሰኘው የዌይን ወርልድ ፊልምም በ1992 ወጣ። የአሜሪካ ሪከርዲንግ ኢንዱስትሪ ማህበር እንደገለጸው፣ ንግስት በ2004 በዩናይትድ ስቴትስ 34.5 ሚሊዮን አልበሞችን ሸጠች፣ ከእነዚህ ውስጥ ግማሹ ሜርኩሪ ከሞተ በኋላ ተሽጧል። በ 1991 የአውሮፓ የቀን መቁጠሪያ.የንግስት አጠቃላይ የአለም ሪከርድ ሽያጭ ግምት እስከ 300 ሚሊዮን ደርሷል። በዩናይትድ ኪንግደም ንግስት አሁን በዩኬ አልበም ገበታዎች ላይ ከሌሎች የሙዚቃ ስራዎች (ቢትልስን ጨምሮ) የበለጠ የጋራ ሳምንታት አሳልፋለች እና የ የንግስት ምርጥ ስኬቶች በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የምንጊዜም ከፍተኛ የተሸጠ አልበም ነው። ሁለቱ የሜርኩሪ ዘፈኖች "እኛ ሻምፒዮን ነን" እና "ቦሄሚያን ራፕሶዲ" እንዲሁም እያንዳንዳቸው በሶኒ ኤሪክሰን እና በጊነስ ወርልድ ሪከርዶች በታላላቅ ምርጫዎች የምንጊዜም ታላቅ ዘፈን ሆነው ተመርጠዋል። ሁለቱም ዘፈኖች ወደየግራሚ ዝና አዳራሽ ገብተዋል; "ቦሂሚያን ራፕሶዲ" በ 2004 እና "እኛ ሻምፒዮን ነን" በ 2009. በጥቅምት 2007 "የቦሄሚያን ራፕሶዲ" ቪዲዮ በ መጽሔት አንባቢዎች የሁሉም ጊዜ ታላቅ ተብሎ ተመርጧል። እ.ኤ.አ. በ 2001 ንግስት ከሞቱ በኋላ ወደ ሮክ ኤንድ ሮል ኦፍ ዝና ገብተዋል እና አራቱም ባንድ አባላት እ.ኤ.አ. በ 2003 ወደ ዘፈን ጸሐፊዎች አዳራሽ ገብተዋል ። የእነሱ የሮክ አዳራሽ ዝና ጥቅስ እንዲህ ይላል ፣ “በግላም ሮክ ወርቃማ ዘመን እና የ70 ዎቹ ዓለት ቅርንጫፍን የሚገልጹ እጅግ በጣም የተዋቡ የቲያትር ትርኢቶች ምንም ቡድን በፅንሰ-ሀሳብም ሆነ በአፈፃፀም ወደ ንግሥቲቱ አልቀረበም። ቡድኑ እ.ኤ.አ. በ 2004 በዩናይትድ ኪንግደም የሙዚቃ አዳራሽ ከተመረቁት መካከል አንዱ ነበር ። ሜርኩሪ እ.ኤ.አ. በ 1992 ለብሪቲሽ ሙዚቃ የላቀ አስተዋፅዖ ላበረከተው የብሪቲሽ ሽልማት በግል ተሸልሟል። ከብሪቲሽ የዘፈን ጸሐፊዎች አካዳሚ የላቀ የዘፈን ስብስብ የአይቮር ኖቬሎ ሽልማት አግኝተዋል። በ 2005 አቀናባሪዎች እና ደራሲያን እና በ 2018 የግራሚ የህይወት ዘመን ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።
13308
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%AB%E1%88%8D%E1%8A%A9%E1%88%88%E1%88%B5
ካልኩለስ
ካልኩለስ የሂሳብ ትምህርት ክፍል ሲሆን ለውጥን ለማጥናት የሚጠቅም መሳሪያ ነው። የካልኩለስ ዋና ዋና ክፍሎች ጥግ (); ውድድር(); ጥርቅም () እና በመጨረሻም አዕላፍ ዝርዝር () ሲሆኑ እነዚህ አራቱ ጽንሰ ሓሳቦች በሁለት ዋና ዋና የጥናት ክፍሎች ይከፈላሉ እነርሱም ሥነ ማወዳደር () እና ሥነ ማጠራቀም() ናቸው። ካልኩለስ አዲስ የተገኘ የሂሳብ መሳሪያ ቢመስልም የጥንቶቹ ምሁራን ሳይቀር ጭላንጭሉን በማየት ግኝቶቻችቸውን ለታሪክ ትተው አልፈዋል። ከነዚህ ውስጥ የጥንታዊ ግብጽ ጸሃፍት ሳይጠቀሱ አይታለፉም። ለምሳሌ የሞስኮው ፓፒሪ ተብሎ በሚታወቀው ክርስቶስ ከመወለዱ 1820 አመታት በፊት የተጻፈው የግብጻውያን መዝገብ ላይ፣ የጥረዛ ካልኩለስ ጭላንጭልን እናገኛለን። በዚህ የጥንቱ ዘመን ጽሁፍ ላይ ደራሲው የቁና (እራሱ የተቆረጠ ሾጣጣን ) መጠነ ይዘት እንድናገኝ ጥያቄ ያቀርብና መልሱን በትክክል ያስቀምጣል። ይህን አይነት ጥያቄ በጥንታዊ ባቢሎናውያንም የተመዘገበ ቢሆንም መልሳቸው ግን ስህተት ነበር። በዚህ ምክንያት የጥንቶቹ ግብጻውያን የካልኩለስ ጀማሪወች ናቸው ማለት ይቻላል ምንም እንኳ መልሱን ያገኙበትን መንገድ ቢደብቁም። ከግብጻውያኑ ጻህፍት ብዙ ከፍለ ዘመናት በኋላ የተነሱት የጥንቶቹ ግሪካውያንም ለዚህ ዕውቀት ዘርፍ የተቻላቸውን አበርክተዋል። ግሪኮቹ ዩዶክሱስ (408 - 355 ዓ.ዓ) እና አርኪሜድስ (287 - 212 ዓ.ዓ.) ካልኩለስ-መሰል ዘዴወችን በመጠቀም የተለያዩ ቅርጾችን መጠነ-ስፋትና መጠነ-ይዘት ለማግኘት ችለዋል። ከክርስቶስ ልደት በኋላም የቻይና ተማሪወችም እንደ ሊዩ ሂዩ፣ ዙ ቾንግዚ የተባሉት የዩዶክሱስን መንገድ አይነት በመጠቀም ስፋትንና ይዘትን ለማግኘት ችለዋል። ይህ በንዲህ እንዳለ ከአንድ 600 መቶ አመታት በኋላ አረቡ ኢብን አል-ሃያታም፣ ቻይናው ሸን ኮ፣ ህንዶቹ ባስቃራ፣ ማዳቫ ሳንጋማግራማ ፣ ኢራናዊው ሻራፍ አል-ዲናቱስ አሁን ለምናውቀው የካልኩለስ ትምህርት አዳዲስ እና ከፍተኛ አስተዋጾ አደረጉ። አንዳንዶቹም ባሁኑ ዘመን ከምንጠቀምባቸው ብዙ ያልተለዩ የሥነ-ልዩና ሥነ-ውህድ እውንታወችን በጥናት ሊያገኙ ቻሉ። ይሁንና አውሮጳ ውስጥ የካልኩለስን መሰርት ጣለ ተበሎ የሚታወቀው ካቫሊየሪ (1598-1647 ዓ.ም) በሚባል ጣሊያናዊ ሲሆን የዚህ ሰው ዋና ሃሳብ ምን ነበር መጠነ ይዘትና መጠነ ስፋታቸው ከሁሉ በታች ትንሽ የሆኑ ኢምንት () ክፍልፍዮችን በመደመር ያቃፊያቸውን አካል ሙሉ ስፋትና ይዘት እናገኛለን የሚል ነበር። ሆኖም ግን ይህ አስተሳሰብ፣ ምንም እንኳ ትክክል ቢሆንም፣ ብዙ ትኩረት ሳይሰጠው 17ኛው ክፍለ ዘመን ላይ እነ ዮሃንስ ዋሊስ፣ ኢሳቅ ባሮ እና ጄምስ ግሪጎሪ የተሰኙት ተማሪወች የካቫሊሪንን ሃሳብና የራሳቸውን ሃሳብ በመቀየጥ ክፍተኛ አስተዋጾ አደረጉ። በተለይ የመጨረሻወቹ ሁለቱ የካልኩለስ ሁለተኛ መሰረታዊ ቴረምን በ1675 በትክክል በማረጋገጥ ታሪክ ሰርተው አልፉ። በዚሁ ዘመን፣ የኢሳቅ ባሮ ተማሪ የነበረው እንግሊዛዊው ኢሳቅ ኒውተን የማባዛት ደምብ፣ የሰንሰለት ደምብ፣ ከፍተኛ ውድድር፣ የቴይለር ዝርዝር እና የፍትሃት ፈንክሽን የተሰኙትን የካልኩለስ ጽንሰ ሃሳቦችን ለሰው ልጅ አበረከተ። ኒውተን እራሱ ያገኛቼውን የካልኩለስ ዘዴወች በመጠቀም የፈለኮችን ምህዋር፣ የሚሽከረከርን ፈሳሽ ቅርጽ፣ የመሬትን ቅርጽ (ትክክለኛ ድብልብል እንዳልሆነች)፣ በክብ ውስጥ የሚንቀሳቀስ እቃን ባህርይ እና የመሳሰሉትን ድንቅ ነገሮች ያለምንም ስህተት ሊያሳይ እና ሊተነብይ ቻለ። ከኒውተን በተቃራኒ፣ በዚያው ዘመን የነበረው ጀርመናዊው ሌብኒትዝ ካልኩለስን ከጥራዝ ነጠቅነት በተላቀቀ መልኩ፣ ወጥ በሆነ ስሌት ማነጽ ጀመረ። ሌብኒትዝ በጊዜው ከኒውተን ኮረጀ ተብሎ ቢከሰስም ባሁኑ ዘመን ግን እራሱን ችሎ የካልኩለስን ህጎች እንዳገኘ ይታመናል። ሌብኒትዝ፣ ከኒውተን በጣም በተሻለ መልኩ የካልኩለስን ህጎችና ደምቦች በጠራ መንገድ ከጻፈው በሁዋላ ከኒውተን ቀድሞ ይህን ጽሁፉን ለህትመት አብቅቷል። በተረፈ የውድድርና የጥረዛ ምልክቶች ብሎ የፈጠራቸው ፊደላት አዲሱን ትምህርት በማቅለል በኒውተን ከባድ ጽሁፎች ውስጥ ተሸሽገው የነበሩትን ሃሳቦች በቀላሉ ለግንዛቤ እንዲመቹ ሆኑ። የሌብኒትዝ ያጻጻፍ ስልቶች ከቀላልነታቸው የተነሳ እስካሁን የምንጠቀምብቸው ሲሆን በኒውተንና በሌብኒትዝ መካከል የተነሳው «ማን መጀመሪያ ካልኩሊን አገኘ?» ጥል ግን ሁለቱን ሰወች ብቻ ሳይሆን በጊዜው የነበሩትን የእንግሊዝና የጀርመን ሳይንቲስቶችን ያናቆረ ነበር። ከሁለቱ ሰወች በኋላም ካልኩለስ ባለበት አልቆየም፤ እንደውም እያደገና እየተሻሻለ ሄደ እንጂ። በ19ኛው ክፍለ ዘመን ለምሳሌ እነ ካውሺ፣ ራይማን፣ ወይስትራስ የተባሉት ሂሳብ አጥኝወች ጥግ የተስኘውን አዲስ ጽንሰ-ሃሳብ በመጠቀም ውሽልሽል የነበረውን የካልኩለስ መሰረት በማይነቃነቅ ቋጥኝ ላይ አሳረፉት። በዚሁ ዘመን ካልኩለስ ከነበረበት ጠበብ ያለ እይታ ወደ ከፍተኛ ማጠቃለያወች አመራ። ባሁኑ ዘመን ይህ የዕውቀት ዘርፍ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና በዩንቬርስቲወች ውስጥ እንደ ዋና የትምህርት ክፍል ሆኖ ይሰጣል። የካልኩለስ መሰረት ኒውተን እና ሌብኒትዝ ዋና ዋና የካልኩለስ ሃሳቦችን ቢያገኙም ቅሉ የነዚህን ሃሳቦች መሰረታዊ እውነታ ላይ ብዙ ትኩረት አልሰጡም ነበር። ከነሱ በኋላ የተነሱት ቀማሪወች ይህን መሰረት ለማግኘት በመፈለግ ባደረጉት ትጋት የካልኩለስን እውነተኛ መሆን በሁለት መንገድ አረጋግጠዋል፡ እነዚህ ዘዴወች የጥግ እና የኢምንት ዘዴወች በመባል ይታወቃሉ። ባሁንኑ ዘመን እነዚህን መሰረቶች የሚያጠና የሂሳብ ክፍል ሪል አናላይሲስ ወይም የውኑ ፍትሃት ይባላል። መሪ ሃሳቦች ጥግና ኢምንት ካልኩለስ የተሰራው ጥቃቅን ብዛትንና ቁጥርን ( ብዘት ን በመጠቀም ነው። በታሪኩም በኩል ብንሄድ የመጀመሪያወቹ የካልኩለስ ዘዴወች ኢምንት የተባውን ጽንሰ ሃሳብ ይጠቀሙ ነበር። ኢምንት ማለት እንደቁጥር መጠቀም የምንችለው ነገር ግን ትንሽነቱ የትየለሌ የሆነ ብዘት() ነው። የኢምንት ምልክት ሲሆን ትርጉሙም ከሁሉ ቁጥር በመጠኑ ያነሰ ነገር ግን ከ0 ብቻ የበለጠ ብዘት ማለት ነው። ይህን ኢምንት በማንኛውም ሙሉ ቁጥር ብናበዛው ከትንሽነቱ የተነሳ ውጤቱ ያው ኢምንት ነው የሚሆነው። ከዚህ አንጻር ካልኩለስ ማለት <<እንዴት አድርጌ ይህን ኢምንት መጠቀም እችላለሁ?>> ለሚለው ጥያቄ መልስ የሚሰጥ ነው። ዘዴውን በትክክል ለመረዳት አስቸጋሪ ስለነበር ከነኒውተንና ሌብኒዝ ዘመን ወደ 19ኛው ክፍለ ዘመን ስንሻገር ሂሳብ ተመሪወች ችላ ቢሉትም፣ በ20ኛው ክ/ዘመን በተነሱ አዳዲስ ግኝቶች ምክንያት እንደገና ሊያንሰራራ ችሏል። ከላይ እንደተጻፈው የኢምንት ዘዴ በ19ኛው ክፍለ ዘመን ሲከስር በጥግ ጥናት ተተካ። ጥጎች አንድ ፈንክሽን የተወሰነ ግቤት (ግቤቶታ) () (ግቤት የውጤት ተቃራኒ ነው) ሲያገኝ የዚያን ግቤት ውጤት ዋጋ ከማግኘት ይልቅ ከግቤቱ በጣም ተጠግተው ያሉ ቁጥሮችን በማስገባት ተቀራራቢ ውጤቱን የምናሰላበት ዘዴ ነው። : ቢሆን ፣ ግቤቱ(ግቤቶታ) 0 ሲሆን ውጤቱ 0/0 ይሆናል ማለት ነው። ዜሮን በዜሮ ስናካፍል ውጤቱ ስንት እንደሆነ ስለማናውቅ ቀጥታ ውጤቱ በርግጥ ስንት እንደሆነ ማወቅ ይቸገርናል። ይህን አጣብቂኝ ችግር ለመፍታት የጥግን ዘዴ እንጠቀማለን። ግቤቱ ወደ ዜሮ እየተጠጋ በሄደ ቁጥር ውጤቱም ወደ ዜሮ እየተጠጋ እንደሚሄድ ማስተዋል አይከብድም። በዚህ ምክንያት የ ጥግ፣ ግቤቱ ወደ0 ሲጠጋ 0/0 ነው ከማለት 0 ነው እንላለን ማለት ነው። ከላይ እንደምናስተውለው ጥግ የ ኢምንትን አስተሳሰብ አይጠቀመም ይልቁኑ እውነተኛ ቁጥርቾን ነው የሚጠቀመው። የጥግ ዘዴ የካልኩለስን መሰረት በማይናወጥ አለት ላይ ለመጣል በጣም ቀላሉ ዜዴ ሆኖ በመገኘቱ በአሁኑ ጊዜ አብዛኞች መጻህፍት ይህን መንገድ እንደ ካልኩሉስ መሰረት አድርገው ሲጠቀሙበት እናያለን። የውድድር ካልኩለስ የውድድር ካልኩለስ የውድድርን ትርጉም፣ ጸባይ፣ እና ተግባር ያጠናል። ያንድ ፋንክሽንን ውድድር የምናገኝበት ዘዴ መለየት () ይባላል። አንድ ፈንክሽን ሲስጠን ያንን ፈንክሽን ነጥብ በነጥብ ለውጡን በማስላት ሌላ አዲስ ፈንክሽን እንሰራለን። ይህ የምንሰራው አዲ ስብስብ የውድድር ፈንክሽን ወይም በቀላሉ ውድድር በመባል ይታወቃል። እንግዲህ ከላይ እንዳየነው እኒህንና መሰል የሂሳብ ሂደቶችን ለማቃለል ሌብኒትዝ አዲስ ምልክቶችን ፈጥሯል። ከነዚህ ውስጥ በጣም ታዋቂ የሆነቸው የውድድር ምልክት <<አፖስትሮፍ>> ` ናት። ስለዚህ የፈንክሽን "> ውድድር ′ ሲሆን ሲነበብም " ፕራይም " ይባላል ። ለምሳሌ፦ የ 2 ውድድር የሄን ይመስላል ማለት ነው። ፍጥነት እንደ ውድድር ያንድ ፈንክሽን ግቤት () ጊዜ/ሰዓት ከሆነ፣ ለውጡ እንግዲህ የዚያን ፈንክሽን ውድድር ከጊዜ አንጻር ይለካል። ለምሳሌ የሚባል ፈንክሽን ቢኖርና ሰዓትን ስንመግበው በዚያ ሳአት ላይ አንድ ኳስ የት እንደተቀመጠ አውጥቶ የሚንግረን ቢሆን ፣ የ ውድድር እንግዲህ የኳሱ አቀማመጥ በጊዜ ውስጥ እንዴት እንደሚቀያየር ይነገርናል ማለት ነው፣ በሌላ አነጋገር የኳሱን ፍጥነት እናገኛለን ማለት ነው። ኩርባ እንደ ውድድር እንደምናውቀው አንድ ቀጠ ያለ መስመር ከነ የሊኒያር እኩልዮሹ ቢሰጠን ኩርባው መስመሩ ቀጥ ያላለ የተንጋደደ ከሆነ ግን የ ውድድር ሲካፈል ለ ውድድር በየነጥቡ ይቀያየርል (ማለት አንድ ጊዜ ከፍ አንድ ጊዜ ዝቅ ይላል)። በዚህ ጊዜ ኩርባውን በቀላሉ ማግኘት ስለማንችል፣ በየቦታው የተለያየውን ኩርባ ለማግኘት የውድድር መንገድን እንጠቀማለን ማለት ነው። ይህን መንገድ ለመጠቀም ገቢው በጥቃቅን ብዛቅ እየቀያየርን ወጭው እንዴት እንደሚቀየር በማስላት ኩርባውን በየቅጽበቱ ማግኘት ይቻላል። ለምሳሌ <" አንድ ፈንክሽን ቢሆን እና አንዲት ቋሚ ግቤት ብናበላው እንግዲህ የ "" ግራፍ ላይ ያለ ነጥብ ሲሆን ደግሞ ወደ ዜሮ በጣም የተጠጋ ቁጥር ቢሆን፣ ለ በጣም የተጠጋ ቁጥርን ነው ማለት ነው። ስለዚህ ከ ጋር የተጠጋጉ ነጥቦች ናቸው። . በነዚህ ነጥቦች መካከል ያለውን ኩርባ ስናሰላ ይህ ቀመር የ"ውድድር ክፍፍል" ይባላል። በሁለት ነጥቦች መካከል ያለው መሰመር የሴካንት መስመር ሲባል ደግሞ የሴካንቱ ኩርባ ናት ወየም የሁለቱ ነጥቦች እና ኩርባ ናት። በዚህ መንገድ በ "" አጠገብ ሚሆነውን ማወቅ ብንችልም በ እና መካከል ያለውን ሁኔታ ማወቅ አንችልም ምክንያቱም ተዘሏል። በሌላ አንጻር ን ዘሮ በማድረግ "" ላይ ምን እንደሚሆን ማወቅ እንፈልግ ይሆናል ነገር ግን ይህ በዜሮ ማካፈል ሊኖርብን ነው ነገር ግን በዜሮ ማካፈል በሂሳብ ህግ ክልክል ነው። ይህን አጣብቂኝ ለመፍታት፣ ከላይ እንዳየነው፣ የጥግ ን ጽንሰ ሃሳብ እንጠቀማለን። ማለት ወደ ዘሮ ሲጠጋ፣ ኩርባው የሚያሳየው ቋሚ ባህርይ ያ ፈንክሽን በነጥብ ላይ ካለው ቅጽበታዊ ኩርባ ጋር እኩል ነው ማለት ነው። ከጂኦሜትሪ አንጻር አንድ ፈንክሽን "" በነጥብ "" ላይ ያለው ውድድር፣ በዚያ ነጥብ ላይ ክሚያርፈው የጨራፊ መስመር ኩርባ ጋር እኩል ነው። ለምሳሌ 2 የሚባል ፈንክሽን እንውሰድና ገቢው 3 ሲሆን የሚታየውን <<ውድድር>> በጥግ () መንገድ እናስላ፦ እንግዲህ ከዚህ የምንረዳው የፈንክሺኑ ጨራፊ መስመር ኩርባ በነጥብ ላይ 6 ነው, ይህም ማለት ፈንክሽኑ ወደላይ የሚያድግበት ፍጥነት ከወደጎን ከሚያድግበት ፍጥነት ጋር ሲነጻጸር 6 ጊዜ እጥፍ ነው። ይህም የሚያሳየው ዳገት መሆኑን ነው። ነጌቲቭ ቢሆን ኖሮ ቁልቁለት ይሆን ነበር። የሌብኒዝ ምልክቶች ሌላው በሌብንኒዝ የተዋወቀውና እስካሁን የሚሰራበት የውድድር መቀመሪያ ምልክት ይህን ይመስላል፦ ምንም እንኳ ምልክቱ ፣ ፣ የማካፈል ቢመስልም እኛ ግን መተርጎም ያለብን የጥግ መፈለጊያ መሆኑን ነው። ሌብኒዝ ዕርግጥ ነው ይህን ምልክት እንደሁለት ኢምንቶች ክፍልፋይ አደርጎ ነበር የወሰደው .... ማለት የ ኢምንታዊ ውድድር ሲሆን ደግሞ የ ኢምንታዊ ውድድር። እንደ ኦፕሬተር ሲቆጠር ግቤቱ ፈንክሽን ሲሆን ውጤቱም ፈንክሽን ነው። ቁልጭ አድርገን ስናስቀምጠው ውጤቱ የግቤቱ ፈንክሽን ውድድር ፈንክሽን ይሆናል ማለት ነው። በዚህ ጊዜ ሲነበበ "ከ አንጻር ያለ ውድድር" ይባላል። አጠራቃሚካልኩሊ ውሱን ጥረዛ እና ያልተወስነ ጥረዛ የተባሉትን ሁለት የውህድ ካልኩለስ ቅርጫፎች ትርጉም፣ ጸባይ፣ እና ተግባር ያጠናል፡፡ ያልተወሰነ ጥረዛ () የውድድር ግልባጭ ወይም ተቃራኒ ኦፕሬሽን ነው። ማለት የ ያልተወሰነ ጥርምር ነው ካልን የ ውድድር ነው ማለታችን ነው።. ( በሌላ ቋንቃ ትንሹ ውድድርን ሲያመልከት ...ትልቁ ጥረዛን ያመለክታል) ሌላው ቅርንጫፍ፣ የተወሰነ ጥረዛ ()፣ ፈንክሽንን ይወስድና የተወሰነ ቁጥርን እንደውጤት ይሰጣል። ይህ ውጤጥ በፈንክሽኑና በ መካከል ያለውን መጠነስ ስፋት ያክላል። ማለት የተወሰነ ውህድ ባንድ የተንጋደደ መስመር እና በ መካከል ተጠልለው ያሉ ህልቁ መሳፍርት ኢምንት አራት ማዕዘኖች ሲደመሩ (ሲጣመሩ) የሚጠጉት ቁጥር ነው ( ራይማን ድምር ይባላል) ለምሳሌ፡ የአንድ መኪና ፍጥነቱ ይሰጠንና በየጊዜው ከኛ ያለውን ርቀት ለማወቅ እንሞክር ፍጥነቱ ቋሚ ከሆነ (ለምሳሌ 10 ሜትር በ ሰከንድ)፣ ርቀቱን ለማግኘት በጊዜ ማባዛት ብቻ ነው ሚያስፈልግ። ለምሳሌ በ5 ሰከንድ ውስጥ 5*10 = 50 ሜትር ሄዷል ማለት ነው። ነገር ግን ፍጥነቱ በአንድ የማይረጋ ተለዋዋጭ ከሆነ ርቀቱን በማባዛት ብቻ ማወቅ አይቻልም ምክንያቱም ቋሚ የምናባዛው ፍጥነት የለም። ይህን ችግር ለመፍታት በአይምሮአችን አምስቷን ሰከንደ ከፋፍለን የብዙ ጥቃቅን ሰኮንዶች ድምር አድርገን ካቀረብን በኋላ በነዚያ ጥቃቅን ጊዜያት ከሚኖሩት ተለዋዋጭ ፍጥነቶች አንድኛውን መርጠን በጊዜው ክፍልፋይ ስናባዛ በዚያች ትንጥ ጊዜ መኪናው ስንት ሜትር ገደማ እንደተጓዘ እናሰላለን። በያንዳንዷ ጥቃቅን የጊዜ ክፍልፋይ ያገኘናቸውን <<ገደማ ርቀቶች>> ስንደምር ከዋናው ርቀት ጋር በጣም ተቀራራቢ መልስ እናገኛለን። የዚህ ምክንያቱ በጣም ትንጥ የጊዜ ክፍል ከወሰድን ፍጥነቱ እምብዛም ስለማይቀያየር አንዱን ፍጥነት መርጠን ማባዛታችን የምናገኘውን ውጤት ብዙም አይጎዳውም ከሚል ነው። ይህ መንገድ ራይማን ድምር ሲባል የሚስጠውም ውጤት ከእውነተኛው ውጤት ተቀራራቢ እንጂ እውንተኛውን ውጤት ራሱን አይደለም። ነገር ግን፣ የጊዜ ክፍልፋዩችን ወደ ዜሮ ጥግ ከወሰድናቸው፣ የድምሩ ውጤት ትክክለኛውን መልስ ይስጣል። ይህ ክፍልፍዩን ወደዜሮ ጥግ ወስዶ የመደመር ዘዴ አጠራቃሚካልኩለስ ይባላል። በግራ ባለው ስዕል ላይ ) በየጊዜው ተለዋዋጭ የሆነ የመኪና ፍጥነትን ቢወክል, የጠቆረው ክፍል መጠነ ስፋት በ ሰከንድና በ ሰኮንድ መካከል መኪናው የተጓዘውን ርቀት ይወክላል። ያንን መጠነ ስፋት በጥሩ ለመገመት፣ ቀላሉ ዘዴ በ ና በ መካከል ያለውን የጠቆረውን ክፍት ቦታ ወደ ጥቃቅን አራት ማዕዘኖች ቀይሮ የነዚያን ስፋት ካገኙ በኋላ በመደመር ለትክክለኛው ስፋት ተቀራራቢ ስፋት ማግኘት ነው። በሌላ ቋንቋ አድማሳዊ መሰመር 'ን ፣ በተባሉ ጥቃቅን ስፋቶች መጀመሪያ መከፋፈል አለብን። ለያንዷ ትናንሽ ክፍል አንድ የተወሰነ የ ) ዋጋ ከመረጥን በኋላ ያንን ዋጋ እንለዋለን። ከዚያ በ እና በ ቁመቱ የሚሰራውን አራት ማዕዘን መጠነ ስፋት ስናሰላ ( ጊዜ ቢወክል እና በዚያች ጊዜ ውስጥ የሚገኘን አንዱን ፍጥነት ቢሆን) በዚያች ቅጽበት ውስጥ የተኬድውን ርቀት እናገኛለን። በየክፍልፍዩ የምናገኘው የዚያ ክፍል አማካይ ቁመት መሆንኑን አንዘንጋ። የነዚህ ሁሉ ጥቃቅን አራት ማዕዘናት ድምር እንግዲ በ ታችኛው አድማሳዊ መስመርና በተንጋደደው ላይኛው መስመር ያለውን መጠነ ስፋት ይጠጋል፣ ይህ ስፋት ደግሞ ከላይ እንዳየነው መኪናው በአጠቃላይ የተጓዘውን ርቀት ይለካል። የክፍልፋዩን መጠን እያሳነስንና እያሳነስን በሄድን ቁጥር የድምሩ ስፋት ከዋናው ስፋት ጋር እየተቀራረበ እና እየተቀራረበ ይሄዳል። ግን ከመቅረብ አልፎ አንድ አይነት እንዲሆኑ የ ጥግ ዜሮ ሲሆን የስፋቱ መጠን ጥግ ስንት እንደሆነ መቀመር ያሻል።. የአጠራቃሚምልክት , ሲሆን የተመዘዘ ይመስላል፣ ይህ የሆነበት ምክንያት በእንግሊዝኛ ፊደል "" ወይም ድምርን ስለሚወክልን ነው።. ይህን ምልክት ተጠቅመን የተወሰነ ጥረዛን ስንጽፍ ይሄን ይመስላል፦ ሲነበብም << የ ኤፍ-ኦፍ-ኤክስ አጠራቃሚከ እስከ በ አንጻር >> ይሆናል። ከጥግ ካልኩለስ አንጻር የሚከተለው ምልክትን መረዳት የሚገባን ኦፕሬተር ሲሆን አንድ ፈንክሽንን እንደ ግቤት ወስዶ ቁጥርን እንደ ውጤት የሚያወጣ ሲሆን ቁጥሩም መጠነ ስፋትን የሚወክል ነው። ቁጥር አይደለም፣ ) ንም አያባዛም። ያልተወሰነ ጥረዛ ወይም ኢ-ውድድር ደግሞ በንዲህ አይነት መንገድ ይጻፋል፦ ፈንክሽኖች በቋሚ ቁጥር ብቻ ከተለያይዩ ያልተወሰነ ጥምራቸው ወይም ኢ-ለውጣቸው አንድ አይነት ነው። በዚህ ምክንያት ያንድ ፈንክሽን ኢ-ውድድር አንድ ፈንክሽን ሳይሆን በቋሚ ቁጥር የሚለያዩ የፈንክሽን ቤተሰቦች እንጂ። ለምሳሌ የ ቋሚ ቁጥር ቢሆን)፣ የ ውድድር , ነው ...ስለዚህ የዚህ የለውጡ ኢ-ውድድር : የካልኩለስ መሰረታዊ እርግጥ የካልኩለስ መሰረታዊ እርግጥ የሚነግረን ሥነ ውድድርና ሥነ ጥረዛ ተገልባጭ ኦፕሬሽን እንደሆኑ ነው። በትክክል ለመግለጽ፣ የኢ-ውድድር አስረካቢዎች የተወሰነ ጥረዛን ዋጋ ለማስላት ያስችላል ይላል መሰረታዊ እውነቱ። ተወዳዳሪን ማስላት የተወሰነ ጥረዛን በጥግ ከማስላት በጣም ስለሚቀል፣ ይህ እውነት በርግጥም ካልኩለስን በተግባር ለመጠቀም ጠቃሚ አድርጎታል። እንግዲህ ወደ ይዘቱ ስንመጣ፣ የካልኩለስ መሰረታዊ እርግጥ የሚለው፡ የተባለ ፈንክሽን ቢሰጠና በ[] መካከል ያልተቋረጠ ቢሆን፣ እንዲሁም የአስረካቢ ውድድር ቢሆን በ () መካከል በተጨማሪ, በ() መካከል ለሚገኝ ለያንዳንዱ ይህን እውነታ የተገነዘቡትና ለጽሁፍ ያበቁ ኢሳቅ ኒውተን እና ሌብኒትዝ ሲሆኑ፣ ከነዚህ እውነታ መገኘት በኋላ ነበር የካልኩለስ እድገት በጅጉ ፈጣን የሆነው። ይህ መሰረታዊ እውንታ የተወሰኑ ጥመረቶችን ያለምን የጥግ ፍለጋ፣ በአልጀብራ ብቻ ለማስላት አስችሏል። በዚህ ምክንያት ድሮ መጠነ-ስፋታቸውን ለማግኘት አስቸጋሪ የነበሩ የአስረካቢ ግራፎች፣ በጥግ ሂሳብ አንዳንዶቹ መልሳቸው ቢገኛም ይህ መንገድ አሰልቺና እልህ አስጨራሽ ሲሆን፣ እነ ኒውተን ያገኙት የካልኩለስ መሰረታዊ እውነታ ግን በቀላሉ የአስረካቢዎቹን ተወዳዳሪ በማግኘት፣ ስፋታቸውን ለማንሰላሰል አስችሏል። የካልኩሊ ጥቅም ባሁኑ ዘመን ካልኩለስን የማይጠቀም የዕውቀትም ሆነ የቴክኖሎጂ ዘርፍ የለም። ግን ዋና ዋና የካልኩለስ ጥቅም ናቸው ተብሎ የሚነገሩት እነዚህ ናቸው፦ ቅጽበታዊ ፍጥነት ለመለካት ፍጥንጥነትን ለመልካት የመስመርን ኩርባ ለመለካት የገዳዳ መስመርን ርዝመት ለመልካት በተንጋደደ መስመር ስር ያለን መጠነ ስፋት ለመለካት መጠነ ይዘትን ለመለካት የክብደት መካከልን ለመለካት ስራሃይልግፊትን ለማንሰላሰል የፎሪየር ድርድር፣ የሃይል ድርደር፣ የላፕላስ ውድድር ና የመንኮራኩርን የጉዞ ምህዋር ለመተንበይና ወዘተረፈ..... ያገልገላል። በፍልስፍናው ዘርፍ ሳይቀር ስለ ኅዋ፣ ጊዜ፣ ሥነ እንቅስቃሴ በጠነከረ መልኩ ለመፈላስፈ ይረዳል። የውጭ መያያዣዎች ኢንተርኔት ላይ ያሉ የእንግሊዝኛ መፃህፍት ኢንተርኔት ድረ ገጾች
16045
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%88%E1%89%83%20%E1%89%B3%E1%8B%A8
አለቃ ታየ
የአለቃ ታየ ገብረማርያም ልደት በዘመነ ወንጌላዊ ሉቃስ፣ ኅዳር ፳፩ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ/ም። ይህም አፄ ቴዎድሮስ በነገሡ በሰባተኛው ዓመት መሆኑ ነው። በጣና ሐይቅ በስተምስራቅ በምትገኘው ልዩ ስሟ ይፋግ ተብላ በምትታወቀው መንደር የተወለዱት አለቃ ታየ በልጅነታቸው ወራት ወላጆቻቸውን በማጣታቸው፣ የእናታቸው ወንድም ትግራይ ይኖሩ ስለነበር አጎታቸውን ፍለጋ ወደ ትግራይ ያመራሉ። እዚያም እንደደረሱ አጎታቸውን ስላጡዋቸው ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ አቅደው ምፅዋ ደረሱ። ምፅዋ ይገኝ በነበረው የስዊድናውያን ሚሲዮን ትምህርት ቤት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት የጀመሩትም ያኔ ነበር። በዚያው ትምህርት ቤት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስን ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ኦሮምኛ የተረጎሙት ኦኔሲሞስም ይማሩ ነበር። እምኩሉ በተባለው በዚህ ትምህርት ቤት ለብዙ ዓመታት የወንጌልን ቃል ከተማሩ በኋላ ወደ ትውልድ አገራቸው ጎጃም ተመለሱና የግዕዝ ቅኔ ትምህርት ቤት ገቡ። ቅኔውን ከሙሉ አገባቡ ጋር አሳምረው ከዘረፉ በኋላ አለቃ የሚለውን ከፍተኛ ማዕረግ አግኝተው እንደገና ምፅዋ በመመለስ በተማሩበት እምኩሉ ትምህርት ቤት በመምህርነት አገለገሉ ። በዚህ ጊዜም "መጽሐፈ ሰዋሰው " የተሰኘውን የመጀመርያ መፅሐፋቸውን ፅፈዋል። አለቃ በሕይወት ዘመናቸው ከደረሷቸው መፅሐፍቶቻቸው ዋና ዋናዎቹ እስካሁን ድረስ የሚገኘው በስዊድንኛ ቋንቋ የጻፉት ....ወይም ነገረ መለኮታዊ ክርክር በራስ መንገሻ ችሎት ) እና በእጅ ፅሑፋቸው የተዘጋጀውና አብዛኛው ማጣቀሻው በግዕዝ የሆነው የአማርኛ መዝገበ ቃላት ወይም የፅንሰ-ሐሣብ መዝገብ ናቸው ። እንደገና ወደ ትውልድ መንደራቸው የተመለሱት አለቃ ታዬ በወቅቱ ቤጌምድርን ይገዙ በነበሩት በራስ መንገሻ አቲከም ዘንድ ሞገስ በማግኘታቸው በ፲፰፻፺፩ ዓ/ም ወደ ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ላኩዋቸው ። ለንጉሠ ነገሥቱም የበኩር ሥራቸው የሆነውን መፅሐፈ ሰዋሰውን በገጠ በረከትነት ሰጡ። ንጉሠ ነገሥቱም የግል ፀሐፌያቸውን ፀሐፌ-ትዕዛዝ ገብረሥላሴን ባልደረባ አድርገው ሰጡዋቸው። በንጉሠ ነገሥቱ እና በመኳንንቱ ዘንድ ከፍተኛ ከበሬታ በማግኘታቸው የቀኑ አንዳንድ የቤተ ክህነት ሰዎች «አለቃ ታዬ ትምህርቱን የቀሰመው ከሚስዮናውያን ነው» በሚል ሰበብ ብቻ ክስ ያበዙባቸው ስለነበር ይህኑኑ ጉዳይ ለአፄ ምኒልክ አመልክተው የሚከተለውን ደብዳቤ ተቀበሉ፦ «ሞዐ አንበሳ ዘዕምነገደ ይሁዳ፣ ዳግማዊ ምኒልክ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ። አለቃ ታየ ገብረማርያም የሚባል ምጥዋ የነበረ ሀይማኖቱን እኛ መርምረነዋልና ማንም አንዳች አይበለው በሀይማኖት ነገር ። በኅዳር ወር በስድስተኛው ቀን ፲፰፻፺፩ ዓ/ም በወረኢሉ ከተማ ተፃፈ ።» ከዚህ በኋላ ወደ ቤጌምድር ተመልሰው ሥራቸውን ቀጠሉ። ዳሩ ግን አሁንም «የታዬ ሀይማኖት የፈረንጅ ነው። ንጉሡ ሳያውቁ ነው ማህተም የሰጡት።» የሚሉ ከሳሾች በመነሳታቸው እንደገና ተከሰው ግብፃዊው ሊቀ-ጳጳስ አቡነ ማቴዎስ ፊት ቀረቡ። አቡነ ማቴዎስም ጉባዔ ከተው አለቃ ታዬን ካስጠሩ በኋላ «አንት አህያ ! ሀይማኖትህ ምንድነው?» በማለት ሲጠየቁዋቸው፤ አለቃም «እኛን አህያ የሚያስብለን እናንተን በመሾማችን ነው።» ብለው ስለመለሱ፣ ነገሩ እየከረረ መጥቶ ንጉሠ ነገሥቱ ፊት ድረስ ደረሰ። ዳግማዊ ምኒልክም አለቃንም ሊቀ-ጳጳሱንም ገስጸው ነገሩን ካበረዱት በኋላ ወደ ቤጌምድር መልሰው ላኩዋቸው። ወድያውኑም እንዲህ የሚል ደብዳቤ ደረሳቸው፦ «ሞዐ አንበሳ ዘዕምነገደ ይሁዳ ዳግማዊ ምኒልክ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ። ይድረስ ከአለቃ ታዬ፣ እንደምን ሰንብተሀል? ከንምሳ መንግሥት ተልከው የመጡ ሰዎች ወደ ሀገራቸው ለመሄድ በጎጃም በኩል ወጥተዋል። ነገር ግን በኢትዮጵያ ቋንቋ የተፃፉ የጥንት መፅሐፍት በአገራችን አሉ ያንን የሚያውቅ ብልህ ሰው ይሂድና እንዲመለከት ይሁን ብለውኛል። አንተ የዚያን ሀገር ባህል ለምደኸዋልና እናንተ ዘንድ በደረሱ ጊዜ አንተም ከነሱ ጋር አብረህ ሂድ። መጋቢት ፱ ቀን ፲፰፻፺፯ ዓ/ም አዲስ አበባ ከተማ ተፃፈ። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ 'የሕይወት ታሪኬ' በሚለው መፅሐፋቸው ይህኑኑ ሁኔታ እንዲህ ገልጠውታል፦ «የጀርመን መንግሥት የግዕዝ ቋንቋ የሚያስተምር አንድ ሊቅ ይሰጠኝ ብሎ ዓፄ ምኒልክን በለመነ ጊዜ ስመ-ጥሩውን ሊቅ አለቃ ታዬን መርጠው ሰደዱዋቸው። በጀርመን መንግሥት ሦስት ዓመት ሙሉ የግዕዝ ቋንቋ አስተምረው ኒሻን ተሸልመው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ ዓፄ ምኒልክም ኒሻን ሸልመው የአባታቸውን አገር ሰጥተው ወደ ቤጌምድር ሰደዱዋቸው። አለቃ ታዬ በአውሮፓ አኅጉር በቆዩበት ጊዜ ብዙ ሀገራትን ጎብኝተዋል። የሚከተለው ከግል ማስታዋሻ ደብተራቸው የተገኘ ነው። ማክሰኞ ግንቦት ፳፪ ቀን ፲፰፻፺፯ ዓ/ም በዚህ ቀን ሌሊቱን ስንሄድ አድረን ማለዳ ሲቂልያ በ፮ ሰዓት ደረስን። ስንሄድ ውለን ማታ በ፯ ሰዓት ኒያፓል ገብተን አደርን። ሲቂልያ የኢጣልያ ክፍል ናት እርስዋም ቃሮዳን የምታህል ታላቅ ደሴት ናት። ከተሞቿም በባሕር ዳር ተሠርተው እጅግ የሚያምሩ ናቸው። ኒያፓልም በባሕር ዳር የተሠራ የጥንት የጣልያን ነገሥታት ከተማ ነው። ዛሬ ግን ራሱ ከተማው ሮማ ነው። ቅዳሜ ግንቦት ፳፮ ቀን ፲፰፻፺፯ ዓ/ም በዚህ ቀን በማርሴል ዋልን። ባቡሪቱ ዕቃ ስታወርድ ዕቃ ስትቀበል ዋለች። እኔና ዮሴፍ ሱማሊ በ፰ ሰዓት ከባቡር ወጥተን በሰረገላ ከተማ ለከተማ እኩል ሰዓት ሄድነ። ወርደን በእግራችን ደግሞ እየዞርን ብዙ ነገር አየነ። በዚያም እጅግ ሀፍረት የሌላቸው ደፋሮች ጋለሞቶች አየነ። በ፭ ሰዓት ወደ ማታ ባቡራችን ገብተን አደርነ። አለቃ በጀርመን ቆይታቸው ከዓፄ ምኒልክ ጋር እየተፃፃፉ በግዕዝ የተፃፉትን መፅሐፍት ከመሰብሰብና ከመመርመር በተጨማሪ አማርኛንና ግዕዝን በበርሊን ዩኒቨርሲቲ አስተምረዋል። ጳጉሜ ፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ/ም ለንጉሠ ነገሥቱ የፃፉት ደብዳቤ እንዲህ ይነበባል፦ «.....እኔ ያስተማርኩዋቸው አማርኛና ግዕዝ ያነባሉ ይፅፋሉ። ...ደህና ሰዎች ናቸው ....የጃንሆይ መልክተኛ ብለው አክብረውና አፍቅረው ይዘውኛል ...ከአገር ናፍቆት በቀር የጎደለብኝ ነገር የለም ......ለጥበባቸው ፍፃሜ የለውም ....በየዕለቱ አዲስ ነገር አያለሁ .....አዲስ ነገር እሰማለሁ።» «ጃንሆይ ከአገርዎ ልጆች ወደ አውሮፓ ሰደው ቢያስተምሩ መልካም በሆነ ....የያጆንና የሞሮኮ መንግሥት ሰው እየሰደዱ አስተማሩ ....ይህን አይቼ ለአገሬ መንግሥት ቅንአት እንደ እሳት በላኝ ....ምንኮ አደርጋለሁ ? አዝኘ ወደ መቃብር እወርዳለሁ .....የጃንሆይ ብር እንዲሰለጥን (እንዲለመድ ማለታቸው ነው) የፊተኛውን ብርና አሞሌ ያጥፉ .....» በማከታተልም በግንቦት ወር ፲፰፻፺፱ ዓ/ም እንዲህ የሚል ደብዳቤ ለንጉሠ ነገሥቱ ፃፉ፦ «...እኛ ሀበሾች በመንፈሳዊና በሥጋዊ ጥበብ ወደፊት የማንገፋበት ምክንያት ምን ይሆን? ብሎ ለሚጠይቅ ሕዝቡ ሁሉ ባይማርና የወንጌልን ስብከት በብዙው ባይሰማ እውነተኛ እውቀትና አፍቅሮ-ቢጽ፣ ትህትና ቢጠፋ ነው .....ባገራችን ጥቂት ዕውቀት ያላቸው ሰዎች በመከበር ፈንታ ስለሚሰደቡና ስለሚዋረዱ ስለሚጠቁም የሚያውቁትን ጠቃሚ የጥበብ ሥራ ትተው በቦዘን መኖርን መረጡ።» «የአዳምን ልጆች ሁሉ የፈጠረ አድልዎ የሌለበት አንድ ልዑል እግዚአብሔር ነው። ላንዱ ወገን ሕዝብ ሙሉ ላንዱ ጎደሎ ልብ አልፈጠረም .....እንዲህ ከሆነ ስለምን ያውሮፓና የእስያ ልጆች ካፍሪካ ክፍልም ጥቂቶች ብልሀተኞች ሲሆኑ ....እኛ ሀበሾች መፅሐፍ ቢማሩ፣ 'ኮቸሮ ለቃሚ'፤ ብር እና ወርቅ ቢሠሩ፣ 'ቀጥቃጭ፣ ቡዳ'፤ እንጨት ቢሠራ፣ 'አናጢ፣ እንጨት ቆርቋሪ'፤ ቆዳ ቢፍቅ 'ጥንበ-በላ፣ ፋቂ' እየተባለ ስም እየተሰጠው ስለሚሰደብ የጥበብ ሥራ ጠፋ። ስለዚህ ጉዳይ ጃንሆይ አስበው እንዲህ ያለው ነገር በአዋጅ እንዲከለከል፣ ሰዎች እንዲከበሩ ቢያደርጉ በሌላ መንግሥት ስምና መልክ በተቀረጸ ገንዘብ (የማሪያ ተሬዛ'' ብር ማለታቸው ነው) ከመገበያየት በጃንሆይ መልክና ስም ገንዘብ እንዲወጣ ቢያደርጉ ነፃ መንግሥትም ራሱን የቻለና የተምዋላም ይሆናል።» ይህ ደብዳቤ ከተፃፈ ከአራት ወር በኋላ ጥር ፲፯ ቀን ፲፱፻ ዓ/ም ዓፄ ምኒልክ የትምህርትን አስፈላጊነትና የሥራን ክቡርነት ያካተተውን፤ «ሠራተኛን በሥራው የምትሰድብ ተወኝ» የሚለውን አስደንጋጭና ብርቱ አዋጅ አወጁ። ከጀርመን አገር ሲመለሱ የኢትዮጵያን ሦስተኛ ደረጃ የክብር ኮኮብ ኒሻን የተሸለሙት አለቃ ታዬ፣ በቤጌምድር እንደገና ታላቅ ተቃውሞ ተነሳባቸው። የአገሩ ገዢ የነበሩት ራስ ወልደጊዮርጊስ አቦዬም (በኋላ ንጉሥ) የሚከተለውን ደብዳቤ ሰደዱላቸው፦ «የተላከ ከራስ ወልደጊዮርጊስ፤ ይድረስ ከአለቃ ታዬ እንዴት ሰንብተሀል? እኔ እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነኝ። ዝም ብለህ ተቀመጥ ስንልህ እንደዚህ ያል ትምህርት ከየት ነው ያመጣኸው? በምን ተጣላኝ እንዳትል! በ ፲፱፻፫ ዓ/ም ኅዳር ፳፬ ቀን ተፃፈ።» አለቃም ሀይማኖታቸው ተዋሕዶ መሆኑንና የተፈጠመባቸውም ግፍ መሆኑን በመግለፅ ደብዳቤ ፅፈው ላጼ ምኒልክ መልስ ላኩ። ንጉሠ ነገሥቱም የተወሰደባቸው መሬት እንዲመለስላቸው ትዕዛዝ ሰጡ። ሁኔታው ያልተዋጠላቸው የቤተ ክህነት ሰዎች ታዬ ፀረ ማርያም ነውና አገር መግዛት አይገባውም የሚል ሌላ ክስ አመጡ። ነገሩ የሀይማኖት ጉዳይ በመሆኑ ወደ ግብፃዊው ሊቀ-ጳጳስ ዘንድ ነገር ተመራና ጥር ፳፬ ቀን ፲፱፻፫ ዓ/ም በዋለው ጉባዔ አለቃ ፈለቀ የተባሉ የቤተ-ክህነት ወኪል ከሳሽ ሆነው በመቅረብ፣ «አለቃ ታዬ ለስዕልና ለመስቀል አይሰግድም፤ በሞቱ ቅዱሳን አማላጅነት አያምንም፤ ዝክርና ምፅዋት የሞተ ሰውን ሊያፀድቅ እንደማይችል ይናገራል፤ የልማድ ፆም ዋጋ እንደሌለው ይናገራል፤ ቀናትን አያከብርም» ሲሉ የክሱን ጭብጥ አስረዱ። በቀረቡት ክሶች ላይ ከፍተኛ ክርክር ተደርጎ ሊቀ-ጳጳሱ ከመሳፍንቱና ከባልደረቦቻቸው ጋርዔ በመሆን አለቃ ታዬን ከገሰፁ በኋላ በነፃ ቢለቁዋቸውም፤ በነፃ መለቀቃቸው ያበሳጫቸው ካህናት የንጉሠ ነገሥቱ ባለ ሙሉ ሥልጣን እንደራሴ ለነበሩት ለራስ ተሰማ ናደው አቤት በማለታቸው ያለ ሕግ ወደ ታላቁ ወህኒ ቤት እንዲገቡ ተደረገ። ከጥቂት ጊዜ እሥራት በኃላ ተፈተው በቁም እሥር እንዲቆዩ ተደርገው፣ በ፲፱፻፲፪ ዓ/ም ለመንግሥት አማካሪነት ተመርጠው መሥራት ጀምረው ነበር። ምሁሩ አለቃ ታዬ ነሐሴ ፲፭ ቀን ፲፱፻፲፮ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። በቀብራቸው ወቅት እህታቸው ወይዘሮ ላቀች አምነህ እንዲህ ሲሉ ተቀኙላቸው ከወህኒ ቤት አስረው የዘጉበት ሳንቃ ብሎ ተናግሮ ነው የወንጌል ቃል ይብቃ የወንጌልን ስራት ተማሩ ቢላቸው ትልቁም ትንሹም ሁሉም ደደብ ናቸው አሉት ጸረ ማርያም መልስ ቢሳናቸው እውቀትና ምግባር ጉድጓድ ተከተተ አራት ነው እንጂ መች አንድ ሰው ሞተ ወዝውዘው ወዝውዘው ጣሉት እንደ ዝሆን ያው ወደቀላቸው ይበሉት እንደሆን ከጨለማ መሀል ቢወጣ ብርሀን ኣጥፉት አጥፉት አሉ እንዳይታየን የግርጌ ማስታወሻ ዋቢ ጽሑፍ አለቃ ታየ
1537
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%86%E1%88%AD%E1%8C%85%20%E1%8B%8B%E1%88%BD%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%89%B0%E1%8A%95
ጆርጅ ዋሽንግተን
ጆርጅ ዋሽንግተን ወይም ጊዮርጊስ ሽንግተን እ.ኤ.አ. ዋሽንግተን የአሜሪካን አብዮታዊ ጦርነት የአርበኞቹን ጦር ወደ ድል በመምራት በ1787 የዩናይትድ ስቴትስ ሕገ መንግሥት እና የፌዴራል መንግሥትን ባቋቋመው የሕገ መንግሥት ኮንቬንሽን መርታለች። ዋሽንግተን በሀገሪቱ የምስረታ ጊዜ ውስጥ ላሳዩት ልዩ ልዩ የአመራር አባላት “የሀገር አባት” ተብላለች። የዋሽንግተን የመጀመሪያው የህዝብ ቢሮ ከ1749 እስከ 1750 የኩልፔፐር ካውንቲ ቨርጂኒያ ኦፊሴላዊ ቀያሽ ሆኖ እያገለገለ ነበር። በመቀጠልም በፈረንሳይ እና በህንድ ጦርነት ወቅት የመጀመሪያውን የውትድርና ስልጠና (እንዲሁም ከቨርጂኒያ ክፍለ ጦር ጋር አዛዥነት) ተቀበለ። በኋላም ለቨርጂኒያ የበርጌሰስ ቤት ተመርጦ የአህጉራዊ ኮንግረስ ተወካይ ተባለ። እዚህ የአህጉራዊ ጦር አዛዥ ጄኔራል ሆነው ተሹመዋል። በዚህ ማዕረግ፣ በአሜሪካ አብዮታዊ ጦርነት ወቅት በዮርክታውን ከበባ እንግሊዞችን በመሸነፍ እና እጃቸውን ሲሰጡ የአሜሪካ ኃይሎችን (ከፈረንሳይ ጋር በመተባበር) አዘዙ። እ.ኤ.አ. በ 1783 የፓሪስ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ኮሚሽኑን ለቋል ። ዋሽንግተን የዩናይትድ ስቴትስን ሕገ መንግሥት በማፅደቅ እና በማፅደቅ ረገድ ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። ከዚያም ሁለቴ በምርጫ ኮሌጅ በአንድ ድምፅ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል። እንደ ፕሬዝዳንት በካቢኔ አባላት ቶማስ ጄፈርሰን እና አሌክሳንደር ሃሚልተን መካከል በተደረገው ከፍተኛ ፉክክር ገለልተኛ ሆኖ እያለ ጠንካራ እና ጥሩ የገንዘብ ድጋፍ ያለው ብሄራዊ መንግስት ተግባራዊ አድርጓል። በፈረንሣይ አብዮት ወቅት የጄይ ስምምነትን በማገድ የገለልተኝነት ፖሊሲ አወጀ። ለፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት "ሚስተር ፕሬዝዳንት" የሚለውን ማዕረግ ጨምሮ ዘላቂ ምሳሌዎችን አስቀምጧል እና የስንብት ንግግራቸው በሪፐብሊካኒዝም ላይ እንደ ቅድመ-ታዋቂ መግለጫ በሰፊው ተወስዷል። ዋሽንግተን ከባርነት ጋር የተወሳሰበ ግንኙነት የነበራት የባሪያ ባለቤት ነበረች። ዋሽንግተን በአንድ ጊዜ ወይም በሌላ ከ577 የሚበልጡ ባሮች ተቆጣጥረው ነበር፤ እነዚህ ባሪያዎች በእርሻው ላይ እና ዋይት ሀውስን ጨምሮ በቤቱ ውስጥ እንዲሰሩ ተገድደዋል። እንደ ፕሬዝደንትነት፣ ባርነትን የሚከላከሉ እና የሚገድቡ በኮንግረሱ የወጡ ህጎችን ፈርመዋል። ኑዛዜው ከባሪያው አንዱ የሆነው ዊልያም ሊ ሲሞት ነፃ መውጣት እንዳለበት እና ሌሎቹ 123 ባሪያዎች ለሚስቱ ሠርተው በሞተች ጊዜ ነፃ መውጣት አለባቸው ይላል። ሞቷን ለማፋጠን ያለውን ማበረታቻ ለማስወገድ በህይወት ዘመኗ ነፃ አወጣቻቸው። የአሜሪካ ተወላጆችን ከአንግሎ አሜሪካዊ ባህል ጋር ለመዋሃድ ሞክሯል፣ ነገር ግን በአመጽ ግጭት ወቅት የአገሬው ተወላጆችን ተቃውሞ ተዋግቷል። እሱ የአንግሊካን ቤተክርስቲያን እና የፍሪሜሶኖች አባል ነበር፣ እና በጄኔራልነት እና በፕሬዝዳንትነት ሚናው ሰፊ የሃይማኖት ነፃነትን አሳስቧል። ሲሞት በሄንሪ “ብርሃን-ሆርስ ሃሪ” ሊ “በጦርነት አንደኛ፣ መጀመሪያ በሰላም፣ እና በመጀመሪያ በአገሩ ሰዎች ልብ” ተሞገሰ። ዋሽንግተን በመታሰቢያ ሐውልቶች ፣ በፌዴራል በዓል ፣ በተለያዩ ሚዲያዎች ፣ በጂኦግራፊያዊ አካባቢዎች ፣ በብሔራዊ ዋና ከተማ ፣ በዋሽንግተን ግዛት ፣ በቴምብር እና በገንዘብ ፣ እና ብዙ ምሁራን እና ምርጫዎች ከታላላቅ የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች መካከል ፈርጀውታል። እ.ኤ.አ. በ 1976 ዋሽንግተን ከሞት በኋላ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ኃይሎች ጄኔራልነት ማዕረግ አገኘች። ቅድመ ህይወት (1732-1752፣ አውሮፓውያን) የዋሽንግተን ቤተሰብ በመሬት ግምት እና በትምባሆ እርባታ ሀብቱን ያፈራ የቨርጂኒያ ባለጸጋ ቤተሰብ ነበር።የዋሽንግተን ቅድመ አያት ጆን ዋሽንግተን በ1656 ከሱልግሬብ፣ ኖርዝአምፕተንሻየር እንግሊዝ ወደ እንግሊዝ ቨርጂኒያ 5,000 ሄክታር መሬት ተሰደደ። (2,000 ሄክታር) መሬት፣ በፖቶማክ ወንዝ ላይ ትንሹን አደን ክሪክን ጨምሮ። ጆርጅ ዋሽንግተን በየካቲት 22, 1732 በዌስትሞርላንድ ካውንቲ ቨርጂኒያ ውስጥ በፖፕስ ክሪክ ውስጥ ተወለደ እና ከአውግስጢኖስ እና ከሜሪ ቦል ዋሽንግተን ስድስት ልጆች የመጀመሪያው ነበር። አባቱ የሰላም ፍትሃዊ እና ከጄን በትለር የመጀመሪያ ጋብቻ አራት ተጨማሪ ልጆች የነበራት ታዋቂ የህዝብ ሰው ነበር። ቤተሰቡ በ1735 ወደ ትንሹ አደን ክሪክ ተዛወረ። በ1738 በሪፓሃንኖክ ወንዝ ላይ በቨርጂኒያ ፍሬድሪክስበርግ አቅራቢያ ወደሚገኘው የፌሪ እርሻ ተዛወሩ። አውጉስቲን በ 1743 ሲሞት ዋሽንግተን የፌሪ እርሻን እና አሥር ባሪያዎችን ወረሰ; ታላቅ ወንድሙ ላውረንስ ትንሹን አደን ክሪክን ወርሶ ተራራ ቬርኖን ብሎ ሰይሞታል። ዋሽንግተን ታላላቅ ወንድሞቹ በእንግሊዝ አፕልቢ ሰዋሰው ትምህርት ቤት የተማሩትን መደበኛ ትምህርት አልነበራቸውም፣ ነገር ግን በሃርትፊልድ የታችኛው ቸርች ትምህርት ቤት ገብተዋል። የሂሳብ፣ ትሪጎኖሜትሪ እና የመሬት ዳሰሳ ተማረ እና ጎበዝ ረቂቅ እና ካርታ ሰሪ ሆነ። ገና በጉልምስና ዕድሜ ላይ እያለ “በሚታመን ኃይል” እና “በትክክለኝነት” ይጽፍ ነበር። ነገር ግን የሱ ጽሁፍ ትንሽ ብልሃት ወይም ቀልድ አላሳየም። አድናቆትን፣ ማዕረግን እና ስልጣንን ለማሳደድ ድክመቶቹን እና ውድቀቶቹን የሌላውን ሰው ውጤት አልባነት ወደ ማላከክ ያዘነብላል። ዋሽንግተን ብዙ ጊዜ የሎረንስ አማች ዊልያም ፌርፋክስ የሆነውን ተራራ ቬርኖንን እና ቤልቮርን ጎበኘ። ፌርፋክስ የዋሽንግተን ደጋፊ እና ምትክ አባት ሆነ እና በ1748 ዋሽንግተን አንድ ወር አሳልፋለች የፌርፋክስ የሼናንዶአ ሸለቆ ንብረትን ከዘለቀ ቡድን ጋር። በቀጣዩ አመት ከዊልያም እና ሜሪ ኮሌጅ የቅየሳ ፈቃድ አግኝቷል። ምንም እንኳን ዋሽንግተን የልማዳዊ ተለማማጅነትን ባያገለግልም ፌርፋክስ የኩልፔፐር ካውንቲ ቨርጂኒያ ቀያሽ ሾመው እና እ.ኤ.አ. ጁላይ 20 ቀን 1749 ቃለ መሃላ ለማድረግ በ ተገኘ። በኋላም እራሱን ከድንበር አካባቢ ጋር ጠንቅቆ ያውቅ ነበር፣ እና ምንም እንኳን ስራውን ለቋል። በ 1750 ከሥራው, ከብሉ ሪጅ ተራሮች በስተ ምዕራብ የዳሰሳ ጥናቶችን ማድረጉን ቀጠለ. በ1752 በሸለቆው ውስጥ ወደ 1,500 ኤከር (600 ሄክታር) የሚጠጋ ገዝቶ 2,315 ኤከር (937 ሄክታር) ነበረው። እ.ኤ.አ. በ 1751 ዋሽንግተን ከሎውረንስ ጋር ወደ ባርባዶስ ሲሄድ ብቸኛ ጉዞውን አደረገ ፣ የአየር ሁኔታው ​​​​የወንድሙን የሳንባ ነቀርሳ ይፈውሳል ። ዋሽንግተን በዚያ ጉዞ ወቅት ፈንጣጣ ያዘ፣ ይህም ክትባት ሰጠው እና ፊቱን በትንሹ ጠባሳ አድርጎታል። ሎውረንስ በ 1752 ሞተ, እና ዋሽንግተን ተራራ ቬርኖንን ከመበለቲቱ አን አከራይቷል. በ1761 ከሞተች በኋላ ወረሰ። የቅኝ ግዛት ወታደራዊ ሥራ (1752-1758፣ የአውሮፓ የቀን መቁጠሪያ) የሎውረንስ ዋሽንግተን የቨርጂኒያ ሚሊሻ ረዳት ጄኔራል በመሆን ያገለገለው ግማሽ ወንድሙ ጆርጅ ኮሚሽን እንዲፈልግ አነሳስቶታል። የቨርጂኒያ ሌተና ገዥ ሮበርት ዲንዊዲ ጆርጅ ዋሽንግተንን ከአራቱ የሚሊሻ አውራጃዎች ዋና እና አዛዥ አድርጎ ሾመ። ኦሃዮ ሸለቆን ለመቆጣጠር ብሪቲሽ እና ፈረንሳዮች ይፎካከሩ ነበር። እንግሊዞች በኦሃዮ ወንዝ ላይ ምሽጎችን እየገነቡ በነበሩበት ወቅት፣ ፈረንሳዮችም ተመሳሳይ ነገር ያደርጉ ነበር—በኦሃዮ ወንዝ እና በኤሪ ሀይቅ መካከል ምሽግ ይገነቡ ነበር። በጥቅምት 1753 ዲንዊዲ ዋሽንግተንን ልዩ መልዕክተኛ አድርጎ ሾመ። ጆርጅን ልኮ የፈረንሣይ ጦር በእንግሊዝ እየተጠየቀ ያለውን መሬት ለቀው እንዲወጡ ጠየቀ። ዋሽንግተን የተሾመችው ከ ጋር ሰላም ለመፍጠር እና ስለ ፈረንሣይ ኃይሎች ተጨማሪ መረጃ ለመሰብሰብ ነው። ዋሽንግተን ከፊል ንጉስ ታናካሪሰን እና ሌሎች የኢሮብ አለቆች ጋር በሎግስታውን ተገናኝተው ስለ ፈረንሣይ ምሽግ ብዛት እና ቦታ እንዲሁም በፈረንሣይ የተያዙ ግለሰቦችን በተመለከተ መረጃ ሰብስቧል። ዋሽንግተን በታንቻሪሰን ኮንቶካውሪየስ (ከተማ አጥፊ ወይም መንደር በላ) የሚል ቅጽል ስም ተሰጠው። ቅፅል ስሙ ከዚህ ቀደም ለቅድመ አያቱ ጆን ዋሽንግተን በአስራ ሰባተኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በሱስክሃንኖክ ተሰጥቶ ነበር። የዋሽንግተን ፓርቲ በህዳር 1753 ኦሃዮ ወንዝ ላይ ደረሰ፣ እና በፈረንሳይ ፓትሮል ተጠልፏል። ፓርቲው ወደ ፎርት ለ ቦኡፍ ታጅቦ ዋሽንግተንን በወዳጅነት አቀባበል ተደረገላት። የብሪታንያ ጥያቄን ለፈረንሳዩ አዛዥ ሴንት ፒየር አሳልፎ ሰጠ ፣ ግን ፈረንሳዮች ለመልቀቅ ፈቃደኛ አልሆኑም። ሴንት ፒየር ለዋሽንግተን ይፋዊ መልሱን በታሸገ ኤንቨሎፕ ከጥቂት ቀናት መዘግየት በኋላ እንዲሁም ለፓርቲያቸው ወደ ቨርጂኒያ ለሚደረገው ጉዞ ምግብ እና ተጨማሪ የክረምት ልብስ ሰጠ። ዋሽንግተን በ 77 ቀናት ውስጥ አስቸጋሪ የሆነውን ተልእኮውን በአስቸጋሪ የክረምት ሁኔታዎች ውስጥ አጠናቀቀ, ይህም ዘገባው በቨርጂኒያ እና በለንደን ታትሞ በነበረበት ጊዜ የልዩነት መለኪያን አግኝቷል. የፈረንሳይ እና የህንድ ጦርነት እ.ኤ.አ. ዋሽንግተን በሚያዝያ ወር ግማሽ ክፍለ ጦርን ይዞ ወደ ሹካዎች ሄደች እና ብዙም ሳይቆይ 1,000 ያህሉ የፈረንሣይ ጦር የፎርት ዱከስኔ ግንባታ እንደጀመረ ተረዳች። በግንቦት ወር በግሬት ሜዳውስ የመከላከያ ቦታ ካዘጋጀ በኋላ ፈረንሳዮች በሰባት ማይል (11 ኪሎ ሜትር) ካምፕ እንደሰሩ ተረዳ። ጥቃት ለመሰንዘር ወሰነ። የሌሊት ትዕይንት ዋሽንግተን መሃል ላይ፣ በመኮንኖች እና በህንዶች መካከል ቆሞ፣ በመብራት ዙሪያ፣ የጦር ካውንስል ይዟል ሌተና ኮሎኔል ዋሽንግተን በፎርት ኔሴሲቲ የምሽት ምክር ቤትን ያዙ የፈረንሣይ ጦር ወደ ሃምሳ የሚጠጉ ሰዎች ብቻ ስለነበሩ ዋሽንግተን ግንቦት 28 ቀን ከቨርጂኒያውያን እና ከህንድ አጋሮች ጋር ትንሽ ጦር አስከትሎ አድፍጦ ዘመተባቸው። የጁሞንቪል ጉዳይ” ተከራክሯል፣ እናም የፈረንሳይ ወታደሮች በሙስኪት እና በ ተገድለዋል። ብሪታኒያን ለቀው እንዲወጡ ዲፕሎማሲያዊ መልእክት ያስተላለፉት የፈረንሣይ አዛዥ ጆሴፍ ኩሎን ደ ጁሞንቪል ተገድለዋል። የፈረንሣይ ጦር ጁሞንቪልን እና አንዳንድ ሰዎቹ ሞተው እና ጭንቅላታቸውን አግተው ዋሽንግተን መሆኗን ጠረጠሩ። ዋሽንግተን የፈረንሳይን አላማ ባለማስተላለፍ ተርጓሚውን ወቅሳለች። ዲንዊዲ ዋሽንግተን በፈረንሳዮች ላይ ስላደረገው ድል እንኳን ደስ አላችሁ። ይህ ክስተት የፈረንሳይ እና የሕንድ ጦርነትን አቀጣጠለ፣ በኋላም የታላቁ የሰባት ዓመታት ጦርነት አካል ሆነ። ሙሉው የቨርጂኒያ ሬጅመንት የሬጅመንታል አዛዥ ሲሞት ወደ ሬጅመንት እና ኮሎኔልነት ማዘዙን በሚገልጽ ዜና በሚቀጥለው ወር ዋሽንግተንን በፎርት ኔሴሲቲ ተቀላቀለ። ሬጅመንቱን ያጠናከረው በካፒቴን ጀምስ ማካይ የሚመራው የመቶ ደቡብ ካሮሊናውያን ገለልተኛ ኩባንያ ሲሆን የንጉሣዊው ኮሚሽኑ ከዋሽንግተን የበለጠ ብልጫ ያለው እና የትእዛዝ ግጭት ተፈጠረ። በጁላይ 3 የፈረንሳይ ጦር ከ900 ሰዎች ጋር ጥቃት ሰነዘረ እና የተከተለው ጦርነት በዋሽንግተን እጅ መስጠት ተጠናቀቀ። ከዚህ በኋላ ኮሎኔል ጀምስ ኢንስ የኢንተር ቅኝ ግዛት ኃይሎችን አዛዥ ወሰደ፣ የቨርጂኒያ ክፍለ ጦር ተከፍሎ ነበር፣ እና ዋሽንግተን የመቶ አለቃ ቀረበላት፣ እሱም ፈቃደኛ አልሆነም እና ኮሚሽኑን በመልቀቅ። ከሌሎች ወታደሮች ጋር በጦር ሜዳ መካከል ዋሽንግተን በፈረስ ላይ የዋሽንግተን ወታደር፡ ሌተና ኮሎኔል ዋሽንግተን በሞኖንጋሄላ ጦርነት ወቅት በፈረስ ላይ ነበር (ዘይት፣ ሬይኒየር፣ 1834) እ.ኤ.አ. በ 1755 ዋሽንግተን ፈረንሳዮችን ከፎርት ዱከስኔ እና ከኦሃዮ ሀገር ለማባረር የብሪታንያ ጉዞን ለሚመራው ለጄኔራል ኤድዋርድ ብራድዶክ ረዳት በመሆን በፈቃደኝነት አገልግሏል። በዋሽንግተን ጥቆማ፣ ብራድዶክ ሰራዊቱን ወደ አንድ ዋና አምድ እና ቀላል የታጠቀ “የሚበር አምድ” ብሎ ከፍሎታል። በከባድ የተቅማጥ በሽታ ሲሰቃይ ዋሽንግተን ወደ ኋላ ቀርታለች እና ብራድዶክን በሞኖንጋሄላ ሲቀላቀል ፈረንሣይ እና የሕንድ አጋሮቻቸው የተከፋፈለውን ጦር አድፍጠው ያዙ። በሟች የቆሰለውን ብራድዶክን ጨምሮ የእንግሊዝ ጦር ሁለት ሶስተኛው ተጎጂዎች ሆነዋል። በሌተና ኮሎኔል ቶማስ ጌጅ ትእዛዝ በዋሽንግተን አሁንም በጣም ታምማ የተረፉትን ሰብስቦ የኋላ ጠባቂ በማቋቋም የኃይሉ ቅሪቶች እንዲለቁ እና እንዲያፈገፍጉ አስችሎታል። በእጮኝነት ጊዜ ሁለት ፈረሶች ከሥሩ ተረሸኑ፣ ኮፍያውና ኮቱ በጥይት ተመትተዋል። በእሳቱ ውስጥ የነበረው ባህሪው በፎርት ኔሴሲቲ ጦርነት ውስጥ በትእዛዙ ላይ ተቺዎች የነበረውን መልካም ስም ዋጅቶታል፣ ነገር ግን በተተኪው አዛዥ (ኮሎኔል ቶማስ ዳንባር) ተከታታይ ስራዎችን በማቀድ አልተካተተም። የቨርጂኒያ ክፍለ ጦር በነሀሴ 1755 እንደገና ተመሠረተ እና ዲንዊዲ በኮሎኔል ማዕረግ ዋሽንግተንን አዛዥ አድርጎ ሾመ። ዋሽንግተን በፎርት ዱከስኔ ላይ ለሚሰነዘረው ጥቃት ትዕግሥት የለሽ በሆነው በፎርት ዱከስኔ ላይ ትዕግሥት የጎደለው ፣ በዚህ ጊዜ ከከፍተኛ የንጉሣዊ ማዕረግ ካፒቴን ከጆን ዳግዎርድ ጋር ተፋጠጠ። ንጉሣዊ ኮሚሽን ሰጠው እና ጉዳዩን በየካቲት 1756 ከብራድዶክ ተተኪ ዊልያም ሸርሊ ጋር እና እንደገና በጥር 1757 ከሸርሊ ተከታይ ሎርድ ሉዶውን ጋር ጠየቀ። ሸርሊ በዋሽንግተን ደግነት በዳግማዊት ጉዳይ ላይ ብቻ ገዝቷል; ሉዱውን ዋሽንግተንን አዋረደ፣ የንጉሣዊውን ኮሚሽን አልተቀበለውም እና ፎርት ኩምበርላንድን ከማስተዳደር ኃላፊነት ለማላቀቅ ብቻ ተስማማ። እ.ኤ.አ. በ 1758 የቨርጂኒያ ክፍለ ጦር ፎርብስ ፎርብስን ለመያዝ ለብሪቲሽ ፎርብስ ጉዞ ተመደበ። ዋሽንግተን ከጄኔራል ጆን ፎርብስ ዘዴዎች እና ከተመረጠው መንገድ ጋር አልተስማማችም። ሆኖም ፎርብስ ዋሽንግተንን የብሬቬት ብርጋዴር ጄኔራል አድርጎ ምሽጉን ከሚያጠቁት ከሶስቱ ብርጌዶች አንዱን ትእዛዝ ሰጠው። ጥቃቱ ከመጀመሩ በፊት ፈረንሳዮች ምሽጉን እና ሸለቆውን ጥለው ሄዱ; ዋሽንግተን 14 ሰዎች ሲሞቱ እና 26 ቆስለዋል ያለው የወዳጅነት የእሳት አደጋ ብቻ ነው የተመለከተው። ጦርነቱ ለተጨማሪ አራት ዓመታት ቀጠለ፣ እና ዋሽንግተን ኮሚሽኑን ትቶ ወደ ተራራ ቬርኖን ተመለሰ።በዋሽንግተን ስር፣ የቨርጂኒያ ሬጅመንት 300 ማይል (480 ኪሜ) ድንበር ከሃያ የህንድ ጥቃቶች በአስር ወራት ውስጥ ተከላክሏል። ከ 300 ወደ 1,000 ሰዎች ሲጨምር የሬጅመንቱን ሙያዊነት ጨምሯል ፣ እናም የቨርጂኒያ ድንበር ህዝብ ከሌሎች ቅኝ ግዛቶች ያነሰ መከራ ደርሶበታል። አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች ይህ በጦርነቱ ወቅት የዋሽንግተን “ብቸኛ ብቃት የሌለው ስኬት” ነበር ይላሉ። ምንም እንኳን የንጉሳዊ ኮሚሽንን እውን ማድረግ ባይችልም, በራስ መተማመንን, የአመራር ክህሎቶችን እና በብሪቲሽ ወታደራዊ ዘዴዎች ላይ በዋጋ ሊተመን የማይችል እውቀት አግኝቷል. በቅኝ ገዥ ፖለቲከኞች መካከል ዋሽንግተን የታየዉ አጥፊ ፉክክር ከጊዜ በኋላ ለጠንካራ ማዕከላዊ መንግስት ድጋፍ አድርጓል። ጋብቻ፣ ሲቪል እና ፖለቲካዊ ህይወት (1755-1775፣ የአውሮፓ የቀን መቁጠሪያ) በጃንዋሪ 6, 1759 ዋሽንግተን በ26 ዓመቷ ማርታ ዳንድሪጅ ኩስቲስ የተባለችውን የ27 ዓመቷን ባለጸጋ የእርሻ ባለቤት ዳንኤል ፓርኬ ኩስቲስ አገባች። ጋብቻው የተካሄደው በማርታ ንብረት ነው; እሷ አስተዋይ፣ ደግ እና የተክላይ ንብረትን በማስተዳደር ረገድ ልምድ ያለው ነበረች፣ እና ጥንዶቹ ደስተኛ ትዳር ፈጠሩ። ከቀድሞ ትዳሯ ልጆች የሆኑትን ጆን ፓርኬ ኩስቲስ (ጃኪ) እና ማርታ "ፓትሲ" ፓርኬ ኩስቲስን ያሳደጉ ሲሆን በኋላም የጃኪ ልጆችን ኤሌኖር ፓርክ ኩስቲስ (ኔሊ) እና ጆርጅ ዋሽንግተን ፓርኬ ኩስቲስ (ዋሺን) አሳድገዋል። እ.ኤ.አ. በ1751 በዋሽንግተን ከፈንጣጣ በሽታ ጋር የተደረገው ጦርነት ንፁህ እንዳደረገው ይገመታል፣ ምንም እንኳን “ማርታ የመጨረሻ ልጇን ፓትሲ በወለደች ጊዜ ጉዳት አጋጥሟት ሊሆን ይችላል፣ ይህም ተጨማሪ መውለድን የማይቻል ያደርገዋል። ጥንዶቹ አንድም ልጅ አንድ ላይ ባለመውለድ አዝነዋል።በአሌክሳንድሪያ አቅራቢያ ወደምትገኘው የቬርኖን ተራራ ተዛወሩ፣ እዚያም የትምባሆና የስንዴ ተከላ ሆኖ ሕይወትን ወስዶ የፖለቲካ ሰው ሆኖ ብቅ አለ። ጋብቻው ዋሽንግተን በ18,000 ኤከር (7,300 ሄክታር) የኩስቲስ ርስት ላይ የማርታ አንድ ሶስተኛ ዶወር ወለድ ላይ ለዋሽንግተን ቁጥጥር ሰጠ እና የቀረውን ሁለት ሶስተኛውን ለማርታ ልጆች አስተዳድሯል። ንብረቱ 84 ባሪያዎችንም አካቷል። ከቨርጂኒያ በጣም ሀብታም ሰዎች አንዱ ሆነ፣ ይህም ማህበራዊ አቋሙን ከፍ አድርጎታል። በዋሽንግተን ግፊት፣ ገዥ ሎርድ ቦቴቱርት በፈረንሳይ እና በህንድ ጦርነት ወቅት ለሁሉም በጎ ፈቃደኞች ሚሊሻዎች የዲንዊዲን 1754 የመሬት ስጦታ ቃል ገብቷል። በ1770 መገባደጃ ላይ ዋሽንግተን በኦሃዮ እና በታላቁ የካናውሃ ክልሎች ያሉትን መሬቶች መረመረ፣ እና እሱን ለመከፋፈል ቀያሽ ዊልያም ክራውፎርድን ተቀላቀለ። ክራውፎርድ 23,200 ኤከር (9,400 ሄክታር) ለዋሽንግተን ሰጠ። ዋሽንግተን ለአርበኞች መሬታቸው ኮረብታማ እና ለእርሻ ስራ የማይመች መሆኑን ነግሯቸው 20,147 ሄክታር (8,153 ሄክታር) ለመግዛት ተስማምተው፣ አንዳንድ ሰዎች እንደተታለሉ እንዲሰማቸው አድርጓል። በተጨማሪም የቬርኖንን ተራራ በእጥፍ ወደ 6,500 ኤከር (2,600 ሄክታር) በማሳደግ የባሪያ ህዝቦቿን በ1775 ከመቶ በላይ አሳደገ። የዋሽንግተን የፖለቲካ እንቅስቃሴ የጓደኛውን ጆርጅ ዊልያም ፌርፋክስን እ.ኤ.አ. በ1755 አካባቢውን በቨርጂኒያ ሃውስ ኦፍ ቡርጌሰስ ለመወከል ባደረገው ጨረታ መደገፍን ያካትታል። ይህ ድጋፍ በዋሽንግተን እና በሌላኛው የቨርጂኒያ ተክል ነዋሪ ዊልያም ፔይን መካከል አካላዊ አለመግባባት አስከትሏል። ዋሽንግተን ከቨርጂኒያ ሬጅመንት መኮንኖች እንዲቆሙ ማዘዙን ጨምሮ ሁኔታውን አረጋጋለች። ዋሽንግተን በማግስቱ በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ ፔይንን ይቅርታ ጠየቀች። ፔይን በድብድብ ለመወዳደር ሲጠብቅ ነበር። እንደ የተከበረ ወታደራዊ ጀግና እና ትልቅ የመሬት ባለቤት ዋሽንግተን የአካባቢ ቢሮዎችን ይይዝ እና ከ 1758 ጀምሮ ለሰባት ዓመታት በበርጌሰስ ቤት ውስጥ ፍሬድሪክ ካውንቲ ወክሎ ለቨርጂኒያ ግዛት ህግ አውጪ ተመረጠ። መራጮችን በቢራ፣ ብራንዲ እና ሌሎች መጠጦች አቀረበ ምንም እንኳን በፎርብስ ጉዞ ላይ በማገልገል ላይ እያለ ባይኖርም. በምርጫው 40 በመቶ የሚሆነውን ድምጽ በማግኘት አሸንፏል፣ ሌሎች ሶስት እጩዎችን በበርካታ የሀገር ውስጥ ደጋፊዎች ታግዞ አሸንፏል። ገና በህግ አውጭነት ስራው ብዙም አይናገርም ነበር፣ ነገር ግን ከ1760ዎቹ ጀምሮ በአሜሪካ ቅኝ ግዛቶች ላይ የብሪታንያ የግብር ፖሊሲ እና የመርካንቲሊስት ፖሊሲዎች ላይ ታዋቂ ተቺ ሆነ። የማርታ ዋሽንግተን ሜዞቲንት፣ ቆማ፣ መደበኛ ጋውን ለብሳ፣ በ1757 በጆን ወላስተን ፎቶ ላይ የተመሰረተ ማርታ ዋሽንግተን በ1757 በጆን ዎላስተን የቁም ሥዕል ላይ የተመሠረተ በወረራ ዋሽንግተን ተክላ ነበር, እና የቅንጦት እና ሌሎች ሸቀጦችን ከእንግሊዝ ያስመጣ ነበር, ትምባሆ ወደ ውጭ በመላክ ይከፍላል. ያካበተው ወጪ ከዝቅተኛ የትምባሆ ዋጋ ጋር ተዳምሮ በ1764 1,800 ፓውንድ ዕዳ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፣ ይህም ይዞታውን እንዲያሻሽል አነሳሳው። እ.ኤ.አ. በ 1765 በአፈር መሸርሸር እና በሌሎች የአፈር ችግሮች ምክንያት የቬርኖንን የመጀመሪያ ደረጃ ገንዘብ ሰብል ከትንባሆ ወደ ስንዴ ለውጦ የበቆሎ ዱቄት ወፍጮ እና አሳ ማጥመድን ይጨምራል። , እና ቢሊያርድስ. ብዙም ሳይቆይ ዋሽንግተን በቨርጂኒያ ውስጥ ካሉ የፖለቲካ እና ማህበራዊ ልሂቃን መካከል ተቆጥራለች። ከ1768 እስከ 1775 ወደ ተራራው ቬርኖን ርስት 2,000 የሚያህሉ እንግዶችን ጋብዟል፣ በተለይም “የደረጃ ሰዎች” ብሎ የሚጠራቸውን። በ1769 በቨርጂኒያ ምክር ቤት ከታላቋ ብሪታንያ የሚመጡ እቃዎች ላይ እገዳ ለማቆም ህግ በማውጣት በፖለቲካዊ ንቁ ተሳትፎ አድርጓል። የዋሽንግተን የእንጀራ ልጅ የሆነው ፓትሲ ኩስቲስ በ12 ዓመቷ በሚጥል በሽታ ተሠቃይታለች፣ እና በ1773 እቅፏ ውስጥ ሞተች። በማግስቱ ለቡርዌል ባሴት እንዲህ ሲል ጽፏል፡- “የዚህን ቤተሰብ ችግር ከመግለጽ ይልቅ መፀነስ ቀላል ነው” . ሁሉንም የንግድ እንቅስቃሴዎች ሰርዞ በየምሽቱ ከማርታ ጋር ለሦስት ወራት ያህል ቆየ። የብሪቲሽ ፓርላማ እና የዘውድ ተቃውሞ ዋሽንግተን ከአሜሪካ አብዮት በፊት እና ወቅት ማዕከላዊ ሚና ተጫውታለች። ለእንግሊዝ ጦር የነበረው ንቀት የጀመረው ወደ መደበኛው ጦር ሠራዊት ለማደግ ሲሻገር ነው። የብሪቲሽ ፓርላማ በቅኝ ግዛቶች ላይ ተገቢውን ውክልና ሳይሰጥ የጣለውን ቀረጥ በመቃወም እሱ እና ሌሎች ቅኝ ገዥዎች በ1763 በወጣው የሮያል አዋጅ አሜሪካ ከአሌጌኒ ተራሮች በስተ ምዕራብ ያለውን ሰፈር በመከልከል እና የብሪታንያ የጸጉር ንግድን በመጠበቅ ተቆጥተዋል። ዋሽንግተን እ.ኤ.አ. በ 1765 የወጣው የቴምብር ህግ "የጭቆና ድርጊት" ነው ብሎ ያምን ነበር እና የተሻረበትን በሚቀጥለው አመት አከበረ። በ1760ዎቹ መገባደጃ ላይ፣ የብሪቲሽ ዘውዱ በአሜሪካ አትራፊ በሆነው የምዕራባዊ መሬት ግምት ውስጥ ጣልቃ የገባው በአሜሪካ አብዮት ላይ ነው። ዋሽንግተን ራሱ የበለጸገ የመሬት ግምታዊ ነበር እና በ 1767 "ጀብዱዎች" ወደ ኋላ አገር ምዕራባዊ አገሮችን እንዲያገኝ አበረታቷል. ዋሽንግተን በ 1767 በፓርላማ የወጣውን ሐዋርያትን በመቃወም ሰፊ ተቃውሞዎችን እንዲመራ ረድቷል እና በግንቦት 1769 በጆርጅ ሜሰን የተዘጋጀውን ሀሳብ አስተዋወቀ ። ቨርጂኒያውያን የብሪታንያ ዕቃዎችን እንዲከለከሉ የሚጠራው; የሐዋርያት ሥራ በ1770 ተሰርዟል። ፓርላማ የማሳቹሴትስ ቅኝ ገዥዎችን በ1774 በቦስተን ሻይ ፓርቲ ውስጥ በነበራቸው ሚና ዋሽንግተን “የመብቶቻችን እና ልዩ መብቶች ወረራ” በማለት የጠቀሰውን የማስገደድ ድርጊቶችን በማለፍ ለመቅጣት ፈለገ። እንደ ጥቁሮችም በዘፈቀደ እየገዛን እንደ ተገራች ባሪያዎች ያደርገናል። በዚያ ጁላይ፣ እሱ እና ጆርጅ ሜሰን ዋሽንግተን ለሚመራው የፌርፋክስ ካውንቲ ኮሚቴ የውሳኔዎችን ዝርዝር አዘጋጅተዋል፣ እና ኮሚቴው የፌርፋክስ ውሳኔዎችን ለአህጉራዊ ኮንግረስ ጥሪ እና የባሪያ ንግድን አቁሟል። በነሀሴ 1፣ ዋሽንግተን የመጀመሪያውን ተሳትፏል። ከሴፕቴምበር 5 እስከ ኦክቶበር 26, 1774 ለአንደኛው ኮንቲኔንታል ኮንግረስ ውክልና ሆኖ የተመረጠበት የቨርጂኒያ ኮንቬንሽን፣ እሱ ደግሞ ተገኝቷል። እ.ኤ.አ. የአሜሪካ አብዮታዊ ጦርነት ሚያዝያ 19, 1775 በሌክሲንግተን እና በኮንኮርድ ጦርነት እና በቦስተን ከበባ ተጀመረ። ቅኝ ገዢዎቹ ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት በመላቀቅ ለሁለት ተከፍለው የእንግሊዝ አገዛዝን ያልተቀበሉ አርበኞች እና ለንጉሱ ተገዢ መሆን የሚሹ ታማኞች ነበሩ። ጄኔራል ቶማስ ጌጅ በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ በአሜሪካ የብሪታንያ ጦር አዛዥ ነበር። የጦርነት መጀመሪያውን አስደንጋጭ ዜና ሲሰማ ዋሽንግተን “ታዘነች እና ደነገጠች” እና በግንቦት 4 ቀን 1775 ከደብረ ቬርኖን በፍጥነት ተነስቶ በፊላደልፊያ ሁለተኛውን ኮንቲኔንታል ኮንግረስ ተቀላቀለ። ዋና አዛዥ ኮንግረስ ሰኔ 14, 1775 ኮንቲኔንታል ጦርን ፈጠረ እና ሳሙኤል እና ጆን አዳምስ ዋሽንግተንን ዋና አዛዥ አድርጎ ሾሙ። ዋሽንግተን በጆን ሃንኮክ ላይ የተመረጠችው በወታደራዊ ልምዱ እና አንድ ቨርጂኒያዊ ቅኝ ግዛቶችን አንድ ያደርጋል የሚል እምነት ስለነበረ ነው። ‹ምኞቱን በቁጥጥሩ ስር ያደረገ› እንደ ቀስቃሽ መሪ ይቆጠር ነበር። በማግስቱ በኮንግረስ ዋና አዛዥ ሆነው በሙሉ ድምፅ ተመርጠዋል። ዋሽንግተን ዩኒፎርም ለብሶ በኮንግሬስ ፊት ቀርቦ ሰኔ 16 ቀን የመቀበል ንግግር ሰጠ፣ ደሞዙን አሽቆለቆለ - ምንም እንኳን በኋላ ላይ ወጭ ተመልሷል። ሰኔ 19 ላይ ተልእኮ ተሰጥቶት ነበር እና ጆን አደምስን ጨምሮ የኮንግረሱ ተወካዮች አድናቆት ያተረፉት እሱ እሱ ቅኝ ግዛቶችን ለመምራት እና አንድ ለማድረግ የሚስማማው ሰው እንደሆነ ተናግሯል። ኮንግረስ ዋሽንግተንን "የተባበሩት ቅኝ ግዛቶች ጦር ጄኔራል እና አዛዥ አዛዥ እና የተነሱት ወይም የሚነሱ ሀይሎች ሁሉ" ሾመ እና በሰኔ 22, 1775 የቦስተንን ከበባ እንዲቆጣጠር አዘዘው። ኮንግረሱ ዋና ዋና መኮንኖቹን መረጠ፣ ሜጀር ጀነራል አርቴማስ ዋርድ፣ አድጁታንት ጀነራል ሆራቲዮ ጌትስ፣ ሜጀር ጀነራል ቻርልስ ሊ፣ ሜጀር ጀነራል ፊሊፕ ሹይለር፣ ሜጀር ጀነራል ናትናኤል ግሪን፣ ኮሎኔል ሄንሪ ኖክስ እና ኮሎኔል አሌክሳንደር ሃሚልተንን ጨምሮ ዋሽንግተን በኮሎኔል ቤኔዲክት አርኖልድ ተደንቀዋል። የካናዳ ወረራ እንዲጀምር ኃላፊነት ሰጠው። እንዲሁም የፈረንሳይ እና የህንድ ጦርነት ባላገሩን ብርጋዴር ጄኔራል ዳንኤል ሞርጋን ጋር ተቀላቀለ። ሄንሪ ኖክስ አዳምስን በመሳሪያ እውቀት አስደነቀው፣ እና ዋሽንግተን ኮሎኔል እና የጦር መሳሪያ አዛዥ አድርጎ አሳደገችው። በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ ዋሽንግተን ጥቁሮችን፣ ነፃም ሆነ ባርነት ወደ ኮንቲኔንታል ጦር መመልመልን ተቃወመች። ከሹመቱ በኋላ ዋሽንግተን ምዝገባቸውን ከልክሏቸዋል። እንግሊዞች ቅኝ ግዛቶችን የመከፋፈል እድል አዩ፣ እና የቨርጂኒያ ቅኝ ገዥ ገዥ አዋጅ አወጣ፣ ባሪያዎች ከእንግሊዝ ጋር ከተቀላቀሉ ነፃነታቸውን እንደሚያገኙ ቃል ገባ። እ.ኤ.አ. በ 1777 መገባደጃ ላይ የሰው ኃይል ለማግኘት ተስፋ ቆርጣ ፣ ዋሽንግተን ተጸጸተ እና እገዳውን ገለበጠች። በጦርነቱ ማብቂያ ላይ ከዋሽንግተን ጦር አንድ አስረኛው አካባቢ ጥቁሮች ነበሩ። የብሪታንያ እጅ ከሰጠች በኋላ ዋሽንግተን የፓሪስ የመጀመሪያ ስምምነት ውሎችን ለማስፈጸም በብሪቲሽ ነፃ የወጡትን ባሪያዎች በማንሳት ወደ ባርነት በመመለስ ፈለገች። ይህንን ጥያቄ ለሰር ጋይ ካርሌተን በግንቦት 6, 1783 እንዲያቀርብ አዘጋጀ። በምትኩ ካርሌተን 3,000 የነጻነት ሰርተፍኬቶችን ሰጠ እና በኒውዮርክ ሲቲ ይኖሩ የነበሩ ባሪያዎች በሙሉ ከተማዋን በብሪታንያ ህዳር 1783 ከመውጣቷ በፊት ለቀው መውጣት ቻሉ። ከጦርነቱ በኋላ ዋሽንግተን በአገር ወዳድ አታሚ ዊልያም ጎድዳርድ የታተመው በጦርነቱ ወቅት እንደ ዋና አዛዥነቱ አጠያያቂ ምግባሩ በጄኔራል ሊ የተከሰሱበት ክስ ኢላማ ሆናለች። ጎድዳርድ እ.ኤ.አ. ." ዋሽንግተን መለሰ፣ ጎድዳርድ የሚፈልገውን እንዲያትም እና "... የማያዳላ እና የማይናቅ አለም" እንዲፈቅድላቸው የራሳቸውን ድምዳሜ እንዲሰጡ ነገረው። የቦስተን ከበባ በ1775 መጀመሪያ ላይ፣ እያደገ ለመጣው የአመጽ እንቅስቃሴ ምላሽ፣ ለንደን ቦስተን እንዲይዝ በጄኔራል ቶማስ ጌጅ የሚታዘዝ የብሪታንያ ጦር ላከ። በከተማዋ ላይ ምሽጎችን አቆሙ, ለማጥቃት የማይቻል አድርገውታል. የተለያዩ የአካባቢ ሚሊሻዎች ከተማዋን ከበቡ እና ብሪታኒያዎችን ውጤታማ በሆነ መንገድ በማጥመድ ግጭት ተፈጠረ። ዋሽንግተን ወደ ቦስተን ሲያቀና የሰልፉ ቃል ከእርሱ በፊት ነበር፣ እና በሁሉም ቦታ ሰላምታ ተሰጠው። ቀስ በቀስ የአርበኞች ግንባር ምልክት ሆነ። እ.ኤ.አ. ሐምሌ 2 ቀን 1775 ፓትሪዮት በአቅራቢያው በሚገኘው ባንከር ሂል ከተሸነፈ ከሁለት ሳምንታት በኋላ የካምብሪጅ ፣ የማሳቹሴትስ ዋና መሥሪያ ቤትን አቋቋመ እና አዲሱን ጦር እዚያ መረመረ ፣ ግን ዲሲፕሊን የሌለው እና መጥፎ አለባበስ ያለው ሚሊሻ አገኘ። ከተመካከረ በኋላ፣ የቤንጃሚን ፍራንክሊን የተጠቆመ ማሻሻያዎችን አስጀምሯል - ወታደሮቹን በመቆፈር እና ጥብቅ ተግሣጽ፣ ግርፋት እና እስራት ያስገባ። ዋሽንግተን ሹማምንቱን የውትድርና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የተቀጣሪዎችን ብቃት እንዲለዩ እና ብቃት የሌላቸውን መኮንኖች በማንሳት ትእዛዝ አስተላለፈ። የተማረኩትን የአርበኞች ግንቦት 7 መኮንኖችን ከእስር እንዲፈታ እና በሰብአዊነት እንዲይዛቸው ለቀድሞ የበላይ ለሆነው ለጌጅ ተማጽኗል። በጥቅምት 1775 ንጉስ ጆርጅ ሳልሳዊ ቅኝ ግዛቶቹ ግልጽ በሆነ አመጽ ላይ መሆናቸውን አውጀው እና ጄኔራል ጌጅን በብቃት ማነስ ምክንያት ከትዕዛዝ ነፃ አውጥቶ በጄኔራል ዊልያም ሃው ተክቷል። የአጭር ጊዜ የምዝገባ ጊዜ በማለፉ እና በጥር 1776 በግማሽ ቀንሶ ወደ 9,600 ሰዎች የተቀነሰው ኮንቲኔንታል ጦር፣ ከሚሊሻዎች ጋር መሟላት ነበረበት እና ከፎርት ቲኮንዴሮጋ በተያዘ ከባድ መሳሪያ ከኖክስ ጋር ተቀላቅሏል። የቻርለስ ወንዝ ሲቀዘቅዝ ዋሽንግተን ቦስተን ለመሻገር እና ለመውረር ጓጉታ ነበር፣ ነገር ግን ጀነራል ጌትስ እና ሌሎች ያልሰለጠኑ ሚሊሻዎች በደንብ የታሰሩ ምሽጎችን ይቃወማሉ። ዋሽንግተን እንግሊዛውያንን ከከተማዋ ለማስወጣት በቦስተን 100 ጫማ ከፍታ ላይ ያለውን የዶርቼስተር ሃይትስ ጥበቃ ለማድረግ ሳትወድ ተስማምታለች። ማርች 9፣ በጨለማ ተሸፍኖ፣ የዋሽንግተን ወታደሮች የኖክስን ትላልቅ ሽጉጦች አምጥተው በቦስተን ወደብ የብሪታንያ መርከቦችን ደበደቡ። በማርች 17፣ 9,000 የብሪታንያ ወታደሮች እና ታማኞች በ120 መርከቦች ላይ ተሳፍረው ቦስተን ለአስር ቀናት ያህል የተመሰቃቀለ ስደት ጀመሩ። ብዙም ሳይቆይ ዋሽንግተን ከተማዋን እንዳትዘርፍ በግልፅ ትዕዛዝ ከ500 ሰዎች ጋር ወደ ከተማዋ ገባ። በኋላ በሞሪስታውን፣ ኒው ጀርሲ እንዳደረገው የፈንጣጣ በሽታ መከላከያ ክትባቶች ከፍተኛ ውጤት እንዲሰጡ አዘዘ። በቦስተን ውስጥ ወታደራዊ ስልጣንን ከመጠቀም ተቆጥቧል, የሲቪል ጉዳዮችን በአካባቢው ባለስልጣናት እጅ ውስጥ ጥሏል. የኩቤክ ወረራ የኩቤክ ወረራ (ሰኔ 1775 – ኦክቶበር 1776፣ ፈረንሣይ፡ ወረራ ዱ ኪቤክ) በአሜሪካ አብዮታዊ ጦርነት ወቅት አዲስ በተቋቋመው አህጉራዊ ጦር የመጀመሪያው ትልቅ ወታደራዊ ተነሳሽነት ነበር። ሰኔ 27 ቀን 1775 ኮንግረስ ለጄኔራል ፊሊፕ ሹለር እንዲመረምር ፈቀደለት እና ተገቢ መስሎ ከታየ ወረራ እንዲጀምር ፈቀደ። ቤኔዲክት አርኖልድ ለትእዛዙ አልፏል፣ ወደ ቦስተን ሄዶ ጄኔራል ጆርጅ ዋሽንግተን በእርሳቸው ትእዛዝ ወደ ኩቤክ ከተማ ደጋፊ ኃይል እንዲልክ አሳመነ። የዘመቻው አላማ የኩቤክ ግዛትን (የአሁኗ ካናዳ አካል) ከታላቋ ብሪታንያ ነጥቆ ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ካናዳውያንን ከአስራ ሶስት ቅኝ ግዛቶች ጎን ያለውን አብዮት እንዲቀላቀሉ ማሳመን ነበር። አንድ ጉዞ ፎርት ቲኮንዴሮጋን ለቆ በሪቻርድ ሞንትጎመሪ፣ ፎርት ሴይንት ጆንስን ከበባ እና ማረከ፣ እና ሞንትሪያል ሲይዝ የብሪቲሽ ጄኔራል ጋይ ካርሌተንን ለመያዝ ተቃርቧል። በቤኔዲክት አርኖልድ የሚመራው ሌላኛው ጉዞ ከካምብሪጅ፣ ማሳቹሴትስ ተነስቶ በታላቅ ችግር በሜይን ምድረ በዳ ወደ ኩቤክ ከተማ ተጓዘ። ሁለቱ ኃይሎች እዚያ ተቀላቅለዋል, ነገር ግን በታህሳስ 1775 በኩቤክ ጦርነት ተሸነፉ. የሎንግ ደሴት ጦርነት ከዚያም ዋሽንግተን ወደ ኒውዮርክ ከተማ አቀና፣ ኤፕሪል 13፣ 1776 ደረሰ፣ እና የሚጠበቀውን የብሪታንያ ጥቃት ለማክሸፍ ምሽግ መገንባት ጀመረ። የቦስተን ዜጎች በእንግሊዝ ወታደሮች በወረራ ጊዜ ይደርስባቸው የነበረውን ግፍ ለማስቀረት፣ ወራሪው ሰራዊቱ ሲቪሎችንና ንብረቶቻቸውን በአክብሮት እንዲይዟቸው አዘዘ። የኒውዮርክ ታማኝ ከንቲባ ዴቪድ ማቲውስን ጨምሮ እሱን ለመግደል ወይም ለመያዝ የተደረገ ሴራ ተገኝቶ ከሽፏል፣በዚህም የተሳተፉ ወይም ተባባሪ የሆኑ 98 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ (56ቱ ከሎንግ ደሴት (ኪንግስ (ብሩክሊን) እና ኩዊንስ አውራጃዎች) የመጡ ናቸው። የዋሽንግተን ጠባቂ ቶማስ ሂኪ በአመፅና በግፍ ተሰቅሏል ።ጄኔራል ሃው የተሰጣቸውን ጦር ከእንግሊዝ የጦር መርከቦች ጋር ከሃሊፋክስ ወደ ኒውዮርክ በማጓጓዝ ከተማዋ አህጉሪቱን ለማስጠበቅ ቁልፍ እንደሆነች በማወቁ የእንግሊዝ ጦርነትን የመራ ጆርጅ ዠርማን በእንግሊዝ ውስጥ በአንድ “በወሳኝ ምት” እንደሚሸነፍ ታምኗል።የብሪታንያ ሃይሎች ከመቶ በላይ መርከቦችን እና በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ጨምሮ ከተማይቱን ለመክበብ እ.ኤ.አ ሀምሌ 2 ቀን ወደ ስታተን ደሴት መድረስ ጀመሩ።የነጻነት መግለጫ ከወጣ በኋላ። በጁላይ 4 ላይ ተቀባይነት አግኝቷል ፣ ዋሽንግተን በጁላይ 9 አጠቃላይ ትዕዛዙ ኮንግረስ የተባበሩት መንግስታት “ነፃ እና ገለልተኛ መንግስታት” እንደሆኑ እንዳወጀ ለወታደሮቹ አሳወቀ። የሃው ሰራዊት ጥንካሬ በድምሩ 32,000 መደበኛ እና የሄሲያን አጋዥዎች፣ እና የዋሽንግተን 23,000፣ በአብዛኛው ጥሬ ምልምሎች እና ሚሊሻዎችን ያቀፈ ነበር። በነሀሴ ወር ሃው 20,000 ወታደሮችን በግሬቨሴንድ ብሩክሊን አሳርፎ ወደ ዋሽንግተን ምሽግ ቀረበ፣ ጆርጅ አመጸኞቹን የአሜሪካ ቅኝ ገዥዎች ከሃዲዎች ብሎ ሲያወጅ ዋሽንግተን ጄኔራሎቹን በመቃወም የሃው ጦር 8,000 ብቻ እንደነበረው ትክክል ባልሆነ መረጃ መዋጋትን መረጠ። በተጨማሪም ወታደሮች. በሎንግ አይላንድ ጦርነት፣ ሃው የዋሽንግተንን ጎራ በመዝመት 1,500 የአርበኝነት ሰለባ አድርጓል፣ እንግሊዛውያን ስቃይ 400. ዋሽንግተን አፈገፈጉ፣ ጄኔራል ዊልያም ሄትን በአካባቢው የወንዞችን የእጅ ሥራዎች እንዲይዙ መመሪያ ሰጠ። እ.ኤ.አ. ኦገስት 30 ጀኔራል ዊሊያም አሌክሳንደር እንግሊዛውያንን ያዙ እና ጦሩ የምስራቅ ወንዝን በጨለማ ወደ ማንሃተን ደሴት ሲሻገር ህይወት እና ቁሳቁስ ሳይጠፋ ምንም እንኳን እስክንድር ቢያዝም ሽፋን ሰጠ። በሎንግ አይላንድ ድል በመደፈር ዋሽንግተንን እንደ “ጆርጅ ዋሽንግተን፣ ኢስኩ” ላከ። በሰላም ለመደራደር በከንቱ. ዋሽንግተን ፈቃደኛ አልሆነችም ፣ እንደ ጄኔራል እና እንደ ጦር ባልደረባው ፣ እንደ “አመፀኛ” ሳይሆን በዲፕሎማሲያዊ ፕሮቶኮል እንዲገለጽ ጠየቀ ፣ ምክንያቱም የእሱ ሰዎች ከተያዙ እንደዚያ እንዳይሰቀሉ ። የሮያል የባህር ኃይል በታችኛው የማንሃተን ደሴት ላይ ያልተረጋጋ የመሬት ስራዎችን ደበደበ። ዋሽንግተን፣ በጥርጣሬ፣ ፎርት ዋሽንግተንን ለመከላከል የጄኔራሎቹ ግሪን እና ፑትናም ምክር ተቀበለች። ሊይዙት አልቻሉም፣ እና የጄኔራል ሊ ተቃውሞ ቢኖርም ዋሽንግተን ተወው፣ ሰራዊቱ ወደ ሰሜን ወደ ነጭ ሜዳ በተመለሰ። የሃው ማሳደድ ዋሽንግተን መከበብን ለማስወገድ በሃድሰን ወንዝ በኩል ወደ ፎርት ሊ እንድታፈገፍግ አስገደዳት። ሃው ወታደሮቹን በኖቬምበር ላይ በማንሃታን አሳርፎ ፎርት ዋሽንግተንን በመቆጣጠር በአሜሪካውያን ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል። ምንም እንኳን ኮንግረስን እና ጄኔራል ግሪንን ቢወቅስም ዋሽንግተን ማፈግፈሱን የማዘግየት ሃላፊነት ነበረባት። በኒውዮርክ ያሉ ታማኞች ሃዌን እንደ ነፃ አውጪ በመቁጠር ዋሽንግተን ከተማዋን በእሳት አቃጥላለች የሚል ወሬ አወሩ። ሊ በተያዘበት ወቅት የአርበኝነት ሞራል ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። አሁን ወደ 5,400 ወታደሮች ተቀንሶ፣ የዋሽንግተን ጦር በኒው ጀርሲ በኩል አፈገፈገ፣ እና ሃው ማሳደዱን አቋርጦ ፊላደልፊያ ላይ ግስጋሴውን አዘገየ እና በኒውዮርክ የክረምት ሰፈር አዘጋጀ። ደላዌርን፣ ትሬንተንን እና ፕሪንስተንን መሻገር ዋሽንግተን የዴላዌርን ወንዝ ወደ ፔንስልቬንያ ተሻገረች፣ የሊ ምትክ ጆን ሱሊቫን ከ 2,000 ተጨማሪ ወታደሮች ጋር ተቀላቀለ። የአህጉራዊ ጦር የወደፊት እጣ ፈንታ በአቅርቦት እጥረት፣ በአስቸጋሪ ክረምት፣ ጊዜው ያለፈበት ምዝበራ እና መሸሽ አጠራጣሪ ነበር። ዋሽንግተን ብዙ የኒው ጀርሲ ነዋሪዎች ታማኞች በመሆናቸው ወይም የነጻነት ተስፋን በመጠራጠራቸው ቅር ተሰኝቷል። ሃው የብሪቲሽ ጦርን ከፈለ እና ምዕራባዊ ኒው ጀርሲ እና የደላዌርን ምስራቃዊ የባህር ዳርቻ ለመያዝ የሄሲያን ጦር ጦርን በ ለጠፈ። “ድል ወይስ ሞት” ብሎ የሰየመው። ሠራዊቱ የደላዌርን ወንዝ በሦስት ክፍሎች ወደ ትሬንቶን አቋርጦ መሄድ ነበረበት፡ አንደኛው በዋሽንግተን (2,400 ወታደሮች)፣ ሌላው በጄኔራል ጀምስ ኢዊንግ እና ሦስተኛው በኮሎኔል ጆን ካድዋላደር ። ኃይሉ መከፋፈል ነበረበት፣ ዋሽንግተን የፔኒንግተን መንገድን እና ጄኔራል ሱሊቫን በወንዙ ዳርቻ ወደ ደቡብ ተጉዘዋል። የዴላዌር ማለፊያ፣ በቶማስ ሱሊ፣ 1819 (የሥነ ጥበባት ሙዚየም፣ ቦስተን) ዋሽንግተን በመጀመሪያ የዱራም ጀልባዎች ሠራዊቱን ለማጓጓዝ 60 ማይል ፍለጋ እንዲደረግ አዘዘ እና በብሪቲሽ ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ መርከቦች እንዲወድሙ አዘዘ።ዋሽንግተን በገና ምሽት ታህሳስ 25 ቀን 1776 የዴላዌር ወንዝን ተሻገረ ፣ እሱ በግላቸው ለመያዝ አደጋ ጣለ። የጀርሲውን የባህር ዳርቻ ማስወጣት ። የእሱ ሰዎች በማክኮንኪ ፌሪ በበረዶ የተዘጋውን ወንዝ ተሻግረው በአንድ መርከብ 40 ሰዎች ይዘው ይከተላሉ። ንፋሱ ውኆቹን አንኳኳው፣ በበረዶም ተወረወረ፣ ነገር ግን ታኅሣሥ 26 ከጠዋቱ 3፡00 ላይ፣ ያለምንም ኪሳራ አቋርጠውታል። ሄንሪ ኖክስ የተፈሩ ፈረሶችን እና ወደ 18 የሚጠጉ የመስክ ጠመንጃዎችን በጠፍጣፋ-ታች ጀልባዎች ላይ በማስተዳደር ዘግይቷል። ካድዋላደር እና ኢዊንግ በበረዶው እና በኃይለኛ ሞገድ ምክንያት መሻገር አልቻሉም፣ እና ዋሽንግተንን በመጠባበቅ ላይ የነበሩት በትሬንተን ላይ ያቀደውን ጥቃት ተጠራጠሩ። ኖክስ ከደረሰ በኋላ ዋሽንግተን ሠራዊቱን ወደ ፔንስልቬንያ ሲመልስ ከመታየት ይልቅ ወታደሮቹን በሄሲያውያን ላይ ብቻ ለመውሰድ ወደ ትሬንተን ሄደ። ወታደሮቹ ከትሬንተን አንድ ማይል ርቀት ላይ ሄሲያንን አዩ፣ ስለዚህ ዋሽንግተን ኃይሉን በሁለት አምድ ከፍሎ ሰዎቹን አሰባስቦ "ወታደሮች በመኮንኖቻችሁ ጠብቁ። ለእግዚአብሔር ብላችሁ በመኮንኖቻችሁ ጠብቁ።" ሁለቱ ዓምዶች በበርሚንግሃም መስቀለኛ መንገድ ላይ ተለያይተዋል። የጄኔራል ናትናኤል ግሪን አምድ በዋሽንግተን የሚመራውን የላይኛውን የፌሪ መንገድ ወሰደ እና የጄኔራል ጆን ሱሊቫን አምድ ወደ ወንዝ መንገድ ገፋ። (ካርታውን ተመልከት።) አሜሪካውያን በዝናብ እና በበረዶ ዝናብ ዘምተዋል። ብዙዎች በደም የተጨማለቁ እግራቸው ጫማ የሌላቸው ሲሆኑ ሁለቱ በመጋለጥ ሞተዋል። ፀሐይ ስትወጣ ዋሽንግተን በሜጀር ጄኔራል ኖክስ እና በመድፍ በመታገዝ በሄሲያውያን ላይ ድንገተኛ ጥቃት ሰነዘረባቸው። ሄሲያውያን 22 ተገድለዋል (ኮሎኔል ዮሃን ራልን ጨምሮ)፣ 83 ቆስለዋል፣ እና 850 በቁሳቁስ ተማርከዋል። በትሬንተን ላይ ከተካሄደው ጦርነት በኋላ የሄሲያን ወታደሮች እጅ መስጠትን በመቀበል ዋሽንግተንን በፈረስ ላይ የሚያሳይ ሥዕል በታህሳስ 26 ቀን 1776 የሄሲያውያን ቀረጻ በትሬንተን በጆን ትሩምቡል ዋሽንግተን ደላዌር ወንዝን አቋርጦ ወደ ፔንስልቬንያ በማፈግፈግ ጥር 3 ቀን 1777 ወደ ኒው ጀርሲ በመመለስ በፕሪንስተን በብሪታንያ ሹማምንት ላይ ጥቃት በመሰንዘር 40 አሜሪካውያን ተገድለዋል ወይም ቆስለዋል እና 273 እንግሊዛውያን ተገድለዋል ወይም ተማረኩ። የአሜሪካ ጄኔራሎች ሂዩ ሜርሰር እና ጆን ካድዋላደር በብሪቲሽ እየተነዱ ነበር ሜርሰር በሟችነት ቆስሎ ነበር፣ ከዚያም ዋሽንግተን ደርሳ ሰዎቹን በመልሶ ማጥቃት ከብሪቲሽ መስመር 30 ያርድ (27 ሜትር) ገፋ። አንዳንድ የብሪታንያ ወታደሮች ለአጭር ጊዜ ቆመው ወደ ኋላ አፈገፈጉ ፣ ሌሎች ደግሞ በናሶ አዳራሽ ተሸሸጉ ፣ ይህም የኮሎኔል አሌክሳንደር ሃሚልተን መድፍ ኢላማ ሆነ ። የዋሽንግተን ወታደሮች ተከሰው፣ እንግሊዞች አንድ ሰአት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እጃቸውን ሰጡ እና 194 ወታደሮች መሳሪያቸውን አኖሩ። ሃው ወደ ኒው ዮርክ ከተማ አፈገፈገ እና ሠራዊቱ እስከሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ድረስ ምንም እንቅስቃሴ አልነበረውም ። የተሟጠጠው የዋሽንግተን ኮንቲኔንታል ጦር የብሪታንያ የአቅርቦት መስመሮችን እያስተጓጎለ እና ከኒው ጀርሲ አንዳንድ ክፍሎች እያባረረ በሞሪስታውን፣ ኒው ጀርሲ የክረምቱን ዋና መሥሪያ ቤት ወሰደ። በኋላ ዋሽንግተን እንግሊዛውያን ወታደሮቹ ከመቆፈር በፊት ሰፈሩን በተሳካ ሁኔታ ማጥቃት ይችሉ እንደነበር ተናግራለች።በዋሽንግተን በትሬንተን እና በፕሪንስተን የተመዘገቡት ድሎች የአርበኝነት ሞራል እንዲታደስ እና የጦርነቱን አቅጣጫ ቀይሮ ነበር። ብሪቲሽ አሁንም ኒውዮርክን ተቆጣጥሮ ነበር፣ እና ብዙ የአርበኞች ግንባር ወታደሮች ከከባድ የክረምቱ ዘመቻ በኋላ እንደገና አልተመዘገቡም ወይም አልለቀቁም። ኮንግረስ ለድጋሚ ለመመዝገብ የበለጠ ሽልማቶችን አዘጋጅቷል እና ለመልቀቅ ከፍተኛ የሆነ የወታደር ቁጥር ተግባራዊ ለማድረግ። ስልታዊ በሆነ መልኩ፣ የዋሽንግተን ድሎች ለአብዮቱ ወሳኝ ነበሩ እና የብሪታንያ ከፍተኛ ኃይል የማሳየትን ስትራቴጂ በመሻር ለጋስ ቃላትን በመስጠት። እ.ኤ.አ. በየካቲት 1777 በአሜሪካ ትሬንተን እና ፕሪንስተን ስላደረገው ድል ቃል ለንደን ደረሰ ፣ እና እንግሊዛውያን አርበኞች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ነፃነታቸውን ሊጠይቁ እንደሚችሉ ተገነዘቡ። ብራንዲዊን፣ ጀርመንታውን እና ሳራቶጋ በጁላይ 1777 የብሪቲሽ ጄኔራል ጆን በርጎይኔ የሳራቶጋን ዘመቻ ከኩቤክ ወደ ደቡብ በኩል በሻምፕላይን ሃይቅ በኩል በመምራት የሃድሰን ወንዝን መቆጣጠርን ጨምሮ ኒው ኢንግላንድን ለመከፋፈል በማሰብ ፎርት ቲኮንዴሮጋን እንደገና ያዘ። ሆኖም በብሪታንያ በኒውዮርክ በያዘው ጄኔራል ሃው ተሳስቷል፣ ሠራዊቱን ወደ ደቡብ ወደ ፊላደልፊያ በመውሰድ በአልባኒ አቅራቢያ ካለው ቡርጎይን ጋር ለመቀላቀል ወደ ሃድሰን ወንዝ ከመሄድ ይልቅ፣ ዋሽንግተን እና ጊልበርት ዱ ሞቲየር፣ ማርኲስ ዴ ላፋይቴ ሃውን ለመግጠም ወደ ፊላደልፊያ በፍጥነት ሄደ እና በጣም ደነገጠ። አርበኞች በጄኔራል ፊሊፕ ሹይለር እና ተተኪው ሆራቲዮ ጌትስ ይመሩበት በነበረው በኒውዮርክ ሰሜናዊ የቡርጎይን እድገት ይወቁ። ብዙ ልምድ ያላቸዉ የዋሽንግተን ጦር በፊላደልፊያ በተካሄደዉ ጦርነት ተሸንፏል። ሃው በሴፕቴምበር 11, 1777 በብራንዲዊን ጦርነት ዋሽንግተንን በማሸነፍ ያለምንም ተቀናቃኝ ወደ የሀገሪቱ ዋና ከተማ ፊላደልፊያ ዘምቷል። በጥቅምት ወር በጀርመንታውን በብሪቲሽ ላይ የአርበኝነት ጥቃት አልተሳካም። ሜጀር ጀነራል ቶማስ ኮንዌይ አንዳንድ የኮንግረስ አባላት (ኮንዌይ ካባል እየተባለ የሚጠራው) ዋሽንግተንን ከትእዛዝ ለማንሳት በፊላደልፊያ በደረሰው ኪሳራ ምክንያት እንዲያስቡ አነሳስቷቸዋል። የዋሽንግተን ደጋፊዎች ተቃወሙት፣ እና በመጨረሻ ከብዙ ውይይት በኋላ ጉዳዩ ተቋርጧል። ሴራው ከተጋለጠ በኋላ ኮንዌይ ለዋሽንግተን ይቅርታ ጠየቀ እና ስራውን ለቆ ወደ ፈረንሳይ ተመለሰ። ዋሽንግተን በሰሜን የሳራቶጋ ዘመቻ ወቅት የሃው እንቅስቃሴዎች ያሳስባቸው ነበር፣ እና ቡርጎይን ከኩቤክ ወደ ደቡብ ወደ ሳራቶጋ እንደሚሄድም ያውቅ ነበር። ዋሽንግተን የጌትስን ጦር ለመደገፍ አንዳንድ አደጋዎችን ወስዳ ወደ ሰሜን ከጄኔራሎች ቤኔዲክት አርኖልድ፣ በጣም ኃይለኛው የመስክ አዛዥ እና ቤንጃሚን ሊንከን ጋር ማጠናከሪያዎችን ላከ። እ.ኤ.አ. ኦክቶበር 7፣ 1777 ቡርጎይን ቤሚስ ሃይትስን ለመውሰድ ሞከረ ነገር ግን ከሃው ድጋፍ ተገለለ። ወደ ሳራቶጋ ለመሸሽ ተገደደ እና በመጨረሻም ከሳራቶጋ ጦርነቶች በኋላ እጅ ሰጠ። ዋሽንግተን እንደጠረጠረው የጌትስ ድል ተቺዎቹን አበረታ። የህይወት ታሪክ ተመራማሪው ጆን አልደን፣ "የዋሽንግተን ሀይሎች ሽንፈት እና በላይኛው ኒውዮርክ ሃይሎች በአንድ ጊዜ ያገኙት ድል መነፃፀሩ የማይቀር ነበር።" ከጆን አዳምስ ትንሽ ክሬዲት ጨምሮ ለዋሽንግተን ያለው አድናቆት እየቀነሰ ነበር። የብሪታንያ አዛዥ ሃው በግንቦት 1778 ሥልጣናቸውን ለቀቁ፣ አሜሪካን ለዘላለም ለቀቁ፣ እና በሰር ሄንሪ ክሊንተን ተተኩ። ሸለቆ አንጥረኛ እና ሞንማውዝ 11,000 ያህሉ የዋሽንግተን ጦር በታኅሣሥ 1777 ከፊላደልፊያ በስተሰሜን በሚገኘው ቫሊ ፎርጅ ወደሚገኘው የክረምቱ ሠፈር ገባ። በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከ2,000 እስከ 3,000 የሚደርሱ ሰዎች በከባድ ብርድ ለሞት ተዳርገዋል፣ ይህም በአብዛኛው በበሽታ እና በምግብ፣ አልባሳት እና መጠለያ እጦት ነበር። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ እንግሊዛውያን በፖውንድ ስተርሊንግ ለሚገዙ አቅርቦቶች እየከፈሉ በፊላደልፊያ በምቾት ተከፋፍለው ነበር፣ ዋሽንግተን ግን በተቀነሰ የአሜሪካ የወረቀት ገንዘብ ታገለ። ጫካው ብዙም ሳይቆይ በጨዋታ ተዳክሞ ነበር፣ እና በየካቲት ወር ሞራላቸው እየቀነሰ እና መራቅ ጨመረ። ዋሽንግተን ለኮንቲኔንታል ኮንግረስ አቅርቦቶች ተደጋጋሚ አቤቱታዎችን አቅርባለች። የሰራዊቱን ሁኔታ ለመፈተሽ የኮንግረሱን ልዑካን ተቀብሎ የሁኔታውን አጣዳፊነት በመግለጽ "አንድ ነገር መደረግ አለበት, አስፈላጊ ለውጦች መደረግ አለባቸው" በማለት አውጇል. ኮንግረስ አቅርቦቱን እንዲያፋጥን ሀሳብ አቅርቧል፡ ኮንግረስ ደግሞ የኮሚሽኑን ክፍል በማደራጀት የሰራዊቱን አቅርቦት መስመሮች ለማጠናከር እና የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ተስማምቷል። በፌብሩዋሪ መገባደጃ ላይ አቅርቦቶች መምጣት ጀመሩ። ዋሽንግተን ወታደሮቹን በ ሞንማውዝ, አማኑኤል ሉዝ በማሰባሰብ ላይ ባሮን ፍሬድሪች ዊልሄልም ቮን ስቱበን ያላሰለሰ ቁፋሮ ብዙም ሳይቆይ የዋሽንግተን ምልምሎችን ወደ ዲሲፕሊን ተዋጊ ሃይል ለወጠው እና የታደሰው ጦር በሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ላይ ከቫሊ ፎርጅ ወጣ። ዋሽንግተን ቮን ስቱበንን ወደ ሜጀር ጄኔራል ከፍ በማድረግ የሰራተኞች አለቃ አደረገችው። እ.ኤ.አ. በ 1778 መጀመሪያ ላይ ፈረንሳዮች ለቡርጎይን ሽንፈት ምላሽ ሰጡ እና ከአሜሪካኖች ጋር የሕብረት ስምምነት ገቡ። ኮንቲኔንታል ኮንግረስ በግንቦት ወር ላይ ስምምነቱን አጽድቆታል፣ ይህም የፈረንሳይ በብሪታንያ ላይ ጦርነት ማወጅ ነው። ሰኔ እና ዋሽንግተን የአሜሪካ እና የፈረንሳይ ጄኔራሎች የጦር ካውንስል ጠሩ። በሞንማውዝ ጦርነት ላይ በማፈግፈግ ብሪቲሽ ላይ ከፊል ጥቃትን መረጠ; እንግሊዛውያን በሃው ተከታይ ጄኔራል ሄንሪ ክሊንተን ታዘዙ። ጄኔራሎች ቻርለስ ሊ እና ላፋዬት ዋሽንግተን ሳታውቅ ከ4,000 ሰዎች ጋር ተንቀሳቅሰዋል እና የመጀመሪያውን ጥቃታቸውን በሰኔ 28 ቀን 2010 ዓ.ም. ዋሽንግተን ሊ እፎይታ አግኝታለች እና ሰፊ ጦርነት ካደረገ በኋላ አቻ ውጤት አገኘች። ምሽት ላይ እንግሊዞች ወደ ኒውዮርክ ማፈግፈግ ቀጠሉ፣ እና ዋሽንግተን ሰራዊቱን ከከተማዋ ውጭ አስወጣ። ሞንማውዝ በሰሜን ውስጥ የዋሽንግተን የመጨረሻ ጦርነት ነበር; ለእንግሊዝ ብዙም ዋጋ ከሌላቸው ከተሞች ይልቅ የሰራዊቱን ደህንነት ከፍ አድርጎ ይመለከተው ነበር። ዌስት ፖይንት ስለላ በብሪቲሽ ላይ የስለላ ስርዓት በመንደፍ ዋሽንግተን "የአሜሪካ የመጀመሪያ ሰላይ ጌታ" ሆነች ። በ 1778 ፣ ሜጀር ቤንጃሚን ታልማጅ በዋሽንግተን አቅጣጫ በኒውዮርክ ስለ ብሪታንያ በድብቅ መረጃ ለመሰብሰብ የኩላፐር ሪንግን ፈጠረ ። ዋሽንግተን በቤኔዲክት አርኖልድ ታማኝ አለመሆንን ችላ ነበር ። በብዙ ጦርነቶች ራሱን የለየ። እ.ኤ.አ. በ1780 አጋማሽ ላይ አርኖልድ ዋሽንግተንን ለመጉዳት እና ዌስት ፖይንትን በሃድሰን ወንዝ ላይ ቁልፍ የሆነውን የአሜሪካን የመከላከያ ቦታ ለመያዝ የታሰበ ሚስጥራዊነት ያለው መረጃ ለእንግሊዛዊው ሰላይ አለቃ ጆን አንድሬ መስጠት ጀመረ። የታሪክ ተመራማሪዎች ለአርኖልድ ክህደት በተቻለ መጠን ለታዳጊ ወጣቶች እድገትን በማጣት ቁጣውን ገልፀዋል ። መኮንኖች፣ ወይም ከኮንግረሱ ተደጋጋሚ ትንሽ። እሱ ደግሞ በከፍተኛ ዕዳ ውስጥ ነበር፣ ከጦርነቱ ትርፍ እያገኘ፣ እና በመጨረሻ በወታደራዊ ፍርድ ቤት በዋሽንግተን ድጋፍ በማጣቱ ቅር ተሰኝቷል። በሠራዊቱ ውስጥ ከቆየ በኋላ የተሰራው የዋሽንግተን የተቀረጸ ጽሑፍ። አርኖልድ የዌስት ፖይንትን ትዕዛዝ ደጋግሞ ጠይቋል፣ እና ዋሽንግተን በመጨረሻ በኦገስት ተስማማ። አርኖልድ አንድሬን ሴፕቴምበር 21 ላይ አገኘው፣ ጦር ሰፈሩን እንዲቆጣጠር እቅድ ሰጠው። የሚሊሻ ሃይሎች አንድሬን ያዙ እና እቅዶቹን አገኙ፣ ነገር ግን አርኖልድ ወደ ኒውዮርክ ሸሸ። ዋሽንግተን ምንም አይነት ችግር እንዳይፈጠር ለመከላከል በአርኖልድ ስር በአርኖልድ ስር የተቀመጡትን አዛዦች አስታወሰ፣ ነገር ግን የአርኖልድን ሚስት ፔጊን አልጠረጠረም። ዋሽንግተን በዌስት ፖይንት የግል ትዕዛዙን ተቀበለች እና መከላከያዋን አደራጀች። የአንድሬ የስለላ ወንጀል የሞት ፍርድ ተጠናቀቀ እና ዋሽንግተን በአርኖልድ ምትክ ወደ ብሪታንያ እንድትመልስ ጠየቀች ፣ ግን ክሊንተን ፈቃደኛ አልሆነም። አንድሬ በጥቅምት 2, 1780 ተሰቀለ፣ ምንም እንኳን የመጨረሻ ጥያቄው የተኩስ ቡድን እንዲገጥመው፣ ሌሎች ሰላዮችን ለመከላከል ቢሆንም የደቡብ ቲያትር እና ዮርክታውን እ.ኤ.አ. በ 1778 መገባደጃ ላይ ጄኔራል ክሊንተን 3,000 ወታደሮችን ከኒውዮርክ ወደ ጆርጂያ በመላክ በ2,000 የእንግሊዝ እና የታማኝ ወታደሮች ተጠናክሮ በሳቫና ላይ ደቡባዊ ወረራ ጀመረ። የአርበኞች እና የፈረንሳይ የባህር ኃይል ሃይሎች የብሪታንያ ጦርነትን የሚያጠናክሩትን ጥቃት መመከት ጀመሩ። እ.ኤ.አ. በ1779 አጋማሽ ላይ ዋሽንግተን የብሪታንያ የህንድ አጋሮችን ከኒውዮርክ ለማስወጣት የስድስቱ ብሄሮች የኢሮብ ተዋጊዎችን አጠቃ። በምላሹ የሕንድ ተዋጊዎች በዋልተር በትለር ከሚመሩት ከታማኝ ጠባቂዎች ጋር ተቀላቅለው በሰኔ ወር ከ200 በላይ ድንበር ጠባቂዎችን ገድለው በፔንስልቬንያ የሚገኘውን ዋዮሚንግ ሸለቆን አጠፉ። ዋሽንግተን የበቀል እርምጃ የወሰደችው ጄኔራል ጆን ሱሊቫን የኢሮብ መንደሮችን “ጠቅላላ ውድመት እና ውድመት” ለማስፈጸም እና ሴቶቻቸውን እና ልጆቻቸውን እንዲይዝ ትእዛዝ በመስጠት ነው። ማምለጥ የቻሉት ወደ ካናዳ ተሰደዱ። የዋሽንግተን ወታደሮች በ1779–1780 ክረምት በሞሪስታውን ኒው ጀርሲ ወደሚገኝ ክፍል ሄዱ እና በጦርነቱ ወቅት በጣም የከፋው ክረምት ገጠማቸው፣ የሙቀት መጠኑም ከቅዝቃዜ በታች ነበር። የኒውዮርክ ወደብ በረዷማ ነበር፣ በረዶ እና በረዶ ለሳምንታት መሬቱን ሸፈነው፣ እና ወታደሮቹ ድጋሚ አቅርቦት አጡ። ክሊንተን 12,500 ወታደሮችን አሰባስቦ በጃንዋሪ 1780 ቻርለስታውን ደቡብ ካሮላይና ላይ ወረረ፣ 5,100 አህጉራዊ ወታደሮች የነበሩትን ጄኔራል ቤንጃሚን ሊንከንን አሸንፏል። ብሪታኒያዎች ምንም የአርበኝነት ተቃውሞ በሌለበት በሰኔ ወር ደቡብ ካሮላይና ፒዬድሞንትን ያዙ። ክሊንተን ወደ ኒውዮርክ በመመለስ በጄኔራል ቻርለስ ኮርንዋሊስ የሚታዘዙትን 8,000 ወታደሮችን ትቶ ሄደ። ኮንግረስ ሊንከንን በሆራቲዮ ጌትስ ተክቷል; በደቡብ ካሮላይና አልተሳካለትም እና በዋሽንግተን በ ናትናኤል ግሪን ምርጫ ተተካ ፣ ግን እንግሊዛውያን ደቡብን በእጃቸው ያዙ። ነገር ግን ዋሽንግተን እንደገና ተበረታታ, ነገር ግን ላፋይቴ ብዙ መርከቦችን, ሰዎችን እና ቁሳቁሶችን ከፈረንሳይ ሲመለስ እና 5,000 አንጋፋ የፈረንሳይ ወታደሮች በማርሻል ሮቻምቤው የሚመሩ በጁላይ 1780 ኒውፖርት, ሮድ አይላንድ ሲደርሱ. የፈረንሳይ የባህር ኃይል ሃይሎች በአድሚራል ግራሴ እየተመሩ. እና ዋሽንግተን ሮቻምቤው መርከቦቹን ወደ ደቡብ በማንቀሳቀስ በአርኖልድ ወታደሮች ላይ የጋራ የመሬት እና የባህር ኃይል ጥቃት እንዲሰነዝር አበረታታቸው። የዋሽንግተን ጦር በታኅሣሥ 1780 በኒው ዊንሶር ኒውዮርክ ወደሚገኝ የክረምት ሰፈር ገባ፣ እና ዋሽንግተን ኮንግረስ እና የመንግስት ባለስልጣናት ሰራዊቱ “እስከ አሁን ባጋጠማቸው ችግሮች መታገሉን እንደማይቀጥል” ተስፋ በማድረግ አቅርቦቶችን እንዲያፋጥኑ አሳስቧል። በማርች 1, 1781 ኮንግረስ የኮንፌዴሬሽን አንቀጾችን አጽድቋል, ነገር ግን በማርች 2 ላይ ተግባራዊ የተደረገው መንግስት ታክስ የመጣል ስልጣን አልነበረውም, እናም ግዛቶችን በአንድነት እንዲይዝ አድርጓል. ጄኔራል ክሊንተን ቤኔዲክት አርኖልድን ከ1,700 ወታደሮች ጋር አሁን የብሪታኒያ ብርጋዴር ጄኔራል ወደ ቨርጂኒያ ላከው ፖርትስማውዝን ያዙ እና ከዚያ ሆነው በአርበኞቹ ላይ ወረራ እንዲያካሂዱ። ዋሽንግተን የአርኖልድን ጥረት ለመቋቋም ላፋይትን ወደ ደቡብ በመላክ ምላሽ ሰጠች። ዋሽንግተን መጀመሪያ ላይ ትግሉን ወደ ኒውዮርክ ለማምጣት ተስፋ አድርጋ፣ የብሪታንያ ጦርን ከቨርጂኒያ በማውጣት ጦርነቱን እዚያው እንዲያጠናቅቅ ቢያደርግም ሮቻምቤው ግን በቨርጂኒያ የሚገኘው ኮርንዋሊስ የተሻለ ኢላማ እንደሆነ ለግራሴ መክሯል። የግሬስ መርከቦች ከቨርጂኒያ የባህር ዳርቻ ደረሱ፣ እና ዋሽንግተን ጥቅሙን አይታለች። በኒውዮርክ ወደ ክሊንተን አመራረጠ፣ ከዚያም ወደ ደቡብ ወደ ቨርጂኒያ አቀና። ጄኔራሎች ዋሽንግተን እና ሮቻምቤው፣ ከሃይቁ ድንኳን ፊት ለፊት ቆመው፣ በዮርክታውን ጥቃት ከመፈጸሙ በፊት የመጨረሻ ትዕዛዝ ሲሰጡ የዮርክታውን ከበባ፣ ጄኔራሎች ዋሽንግተን እና ሮቻምቤው ከጥቃቱ በፊት የመጨረሻ ትእዛዝ ይሰጣሉ የዮርክታውን ከበባ በጄኔራል ዋሽንግተን የሚመራ የአህጉራዊ ጦር ጥምር ጦር፣ የፈረንሳይ ጦር በጄኔራል ኮምቴ ደ ሮቻምቤው እና በአድሚራል ደ ግራሴ የሚታዘዘው የፈረንሣይ ባህር ኃይል የኮርዋሊስ እንግሊዛዊ ሽንፈት የተቀናጀ የተባበሩት መንግስታት ወሳኝ ድል ነበር። ኃይሎች. እ.ኤ.አ. ነሐሴ 19 በዋሽንግተን እና በሮቻምቤው መሪነት ወደ ዮርክታውን የሚደረገው ጉዞ ተጀመረ፣ እሱም አሁን "የተከበረው ሰልፍ" በመባል ይታወቃል። ዋሽንግተን 7,800 ፈረንሳውያን፣ 3,100 ሚሊሻዎች እና 8,000 አህጉራዊ ጦር ሰራዊት አዛዥ ነበረች። በከበባ ጦርነት ውስጥ ጥሩ ልምድ ያልነበረው ዋሽንግተን የጄኔራል ሮቻምቤው ፍርድን በማጣቀስ እና እንዴት መቀጠል እንዳለበት ምክሩን ተጠቅሟል። ሆኖም ሮቻምቤው የዋሽንግተንን ሥልጣን እንደ ጦርነቱ አዛዥ ሆኖ አያውቅም። በሴፕቴምበር መገባደጃ ላይ የአርበኝነት-የፈረንሳይ ሃይሎች ዮርክታውን ከበቡ፣ የብሪታንያ ጦርን አስገቡ እና የብሪታንያ ማጠናከሪያዎችን በሰሜን ከ ክሊንተን ከለከሉ፣ የፈረንሳይ የባህር ሃይል ደግሞ በቼሳፒክ ጦርነት አሸናፊ ሆነ። የመጨረሻው የአሜሪካ ጥቃት በዋሽንግተን በተተኮሰ ጥይት ተጀመረ። በጥቅምት 19, 1781 በብሪታንያ እጅ በመስጠት ከበባው አብቅቷል ። ከ 7,000 በላይ የብሪታንያ ወታደሮች በጦርነት እስረኞች ተደርገዋል, በአሜሪካ አብዮታዊ ጦርነት የመጨረሻው ትልቅ የመሬት ጦርነት. ዋሽንግተን ለሁለት ቀናት የመገዛት ውልን ድርድር ያደረገች ሲሆን ኦፊሴላዊው የፊርማ ሥነ ሥርዓት በጥቅምት 19 ተካሂዷል። ኮርንዋሊስ መታመሙን ተናግሯል እና አልተገኘም ነበር፣ ጄኔራል ቻርለስ ኦሃራን እንደ ተወካይ ላከ። እንደ በጎ ፈቃድ መግለጫ፣ ዋሽንግተን ለአሜሪካውያን፣ ፈረንሣይ እና ብሪቲሽ ጌ ማንቀሳቀስ እና መልቀቂያ በሚያዝያ 1782 የሰላም ድርድር ሲጀመር እንግሊዞችም ሆኑ ፈረንሳዮች ቀስ በቀስ ሰራዊታቸውን ማስወጣት ጀመሩ። የአሜሪካ ግምጃ ቤት ባዶ ነበር፣ ደሞዝ ያልተከፈለ እና ደሞዝ የሚሉ ወታደሮች የኮንግረሱን ስብሰባ እንዲቋረጥ አስገደዱ፣ እና ዋሽንግተን በማርች 1783 የኒውበርግ ሴራን በማፈን ሁከትን አስወገደ። ኮንግረስ ለባለሥልጣናቱ የአምስት ዓመት ጉርሻ እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል። ዋሽንግተን ለሠራዊቱ ያደገውን የ450,000 ዶላር ሂሳብ አስገባ። ሂሳቡ ብዙ ገንዘብ ስለመኖሩ ግልጽ ያልሆነ እና ሚስቱ ዋና መሥሪያ ቤቱን በመጎብኘት ያወጣችውን ወጪ ያካተተ ቢሆንም ሒሳቡ ተፈታ። በሚቀጥለው ወር፣ በአሌክሳንደር ሃሚልተን የሚመራ የኮንግረሱ ኮሚቴ ሰራዊቱን ለሰላም ጊዜ ማስተካከል ጀመረ። በነሀሴ 1783 ዋሽንግተን ስለ ሰላም ማቋቋሚያ በሰጠው አስተያየት የሰራዊቱን አመለካከት ለኮሚቴው ሰጠ። ኮንግረስ የቆመ ጦር እንዲይዝ፣ የተለያዩ የመንግስት አካላትን "ብሔራዊ ሚሊሻ" እንዲፈጥር እና የባህር ኃይል እና ብሔራዊ ወታደራዊ አካዳሚ እንዲቋቋም መክሯል። በሴፕቴምበር 3, 1783 የፓሪስ ስምምነት የተፈረመ ሲሆን ታላቋ ብሪታንያ የዩናይትድ ስቴትስን ነፃነት በይፋ ተቀበለች. ከዚያም ዋሽንግተን ሠራዊቱን በትኖ ለወታደሮቹ የመሰናበቻ ንግግር በኖቬምበር 2. በዚህ ጊዜ ዋሽንግተን የብሪታንያ ጦር በኒውዮርክ ሲወጣ በበላይነት ተቆጣጠረች እና በሰልፍ እና በክብረ በዓላት ተቀበለችው። እዚያም ኮሎኔል ሄንሪ ኖክስ የዋና አዛዥነት ማዕረግ እንደተሰጣቸው አስታውቋል። ዋሽንግተን እና ገዥው ጆርጅ ክሊንተን በኖቬምበር 25 ከተማዋን መደበኛ ያዙ። በታህሳስ 1783 መጀመሪያ ላይ ዋሽንግተን መኮንኖቹን በፍራውንስ ታቨርን ተሰናብቶ ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ዋና አዛዥነቱን ለቀቀ እና ወታደራዊ ትዕዛዙን እንደማይለቅ የታማኝ ትንበያዎችን ውድቅ አደረገ። ዩኒፎርም ለብሶ ለመጨረሻ ጊዜ ለብሶ ለኮንግረሱ መግለጫ ሰጥቷል፡- “የምወዳትን አገራችንን ጥቅም ሁሉን ቻይ በሆነው አምላክ ጥበቃ ላይ በማመስገን ይህንን የኦፊሴላዊ ሕይወቴን የመጨረሻ ተግባር መዝጋት በጣም አስፈላጊ ተግባር እንደሆነ እቆጥረዋለሁ። የዋሽንግተን መልቀቂያ በአገር ውስጥ እና በውጪ የተወደሰ ሲሆን አዲሲቷ ሪፐብሊክ ወደ ትርምስ እንደማትቀየር ተጠራጣሪ ዓለምን አሳይቷል። በዚያው ወር ዋሽንግተን የሲንሲናቲ ማኅበር ፕሬዚዳንት ጄኔራል ተሾመ፣ አዲስ የተቋቋመው የአብዮታዊ ጦርነት መኮንኖች በዘር የሚተላለፍ ወንድማማችነት። በቀሪው የሕይወት ዘመናቸው በዚህ ኃላፊነት አገልግሏል። የአሜሪካ መሪዎች
18982
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%20%E1%8A%A0%E1%8B%A8%E1%88%AD%20%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%88%E1%8B%B5%20%E1%8A%A0%E1%8B%B0%E1%8C%8B%E1%8B%8E%E1%89%BD
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አደጋዎች
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከተመሠረተበት ከታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ጀምሮ በ፷፭ ዓመት ዕድሜው እስከ ፳፻፫ ዓ/ም ድረስ በጠለፋ፤ በብልሽት ወይም በአብራሪ ጥፋት ምክንያት ፷፩ አደጋዎችን አስመዝግቧል። በነዚህ አደጋዎች የ ፫፻፳፪ ሰዎች ሕይወት ሲጠፋ በዓቢይነት የተመዘገቡት ጥፋቶች በ፳፻፪ ዓ/ም በሜድትራኒያን ባሕር ውስጥ የተከሰከሰውና የ፺ ሰዎች ሕይወት የጠፋበት የበረራ ቁጥር ፬፻፱ እና ፻፳፭ ሰዎችን ለሞት የዳረገው የየበረራ ቁጥር ፱፻፷፩ በሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ መከስከስ ናቸው። የብልሽት እና አብራሪ ጥፋት አደጋዎች ሐምሌ ፲፭ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም - ጎሬ፤ ኢሉባቦር አየር መንገዱ በተመሠረተ በሁለት ዓመቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመዘገበው አደጋ፣ በዚህ ዕለት በክረምት ዝናብ ረጥቦ በነበረው የጎሬ አየር ዠበብ ማረፊያ ላይ ሲያርፍ ተንሸራቶ የተከሰከሰው ዲ-ሲ ፫ () አየር ዠበብ (ሰሌዳ ቁጥር -5) ነበር። ማኮብኮቢያውን ስቶ ደንጊያ ላይ ሲከሰከስ የደረሰበት ጉዳት አየር ዠበቡን ከበረራ ጥቅም ውጭ አውሎታል። ሆኖም ከዚህ አደጋ በኋላ የአየር መንገዱ የጎሬ ቢሮ ሆኖ አገልግሏል። ሐምሌ ፫ ቀን ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - ሱዳን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ፫ (የሰሌዳ ቁጥር -35) ከግሪክ ርዕሰ ከተማ አቴና ስድስት አየር-ዠበብተኞችንና አሥራ አራት መንገድኞችን ጭኖ በካርቱም በኩል ወደአዲስ አበባ ለመጓዝ ከአቴና ከምሽቱ አራት ሰዓት ተኩል ላይ ተነሳ። ካርቱም በሰላም ደርሶ ሐምሌ ፫ ቀን ሲነጋጋ የአዲስ አበባ በረራውን በጀመረ በአሥራ አምስት ደቂቃው ከጧቱ አሥራ ሁለት ሰዓት ከአሥር ደቂቃ ሲሆን ሁለተኛው ሞተሩ በእሳት ተያያዘ። አብራሪዎቹ ይኼንን እሳት በመከላከያ ሊያጠፉ ሲሞክሩ ሞተሩ ፈነዳ። በዚህ ጊዜ አብራሪዎቹ በአስቸኳይ ማረፊያ ጎማዎቹን ሳያወርዱ፤ ከካርቱም ከተማ ፵፱ ኪ.ሜ. እርቀት በርሻ መሬት ላይ አሳረፉ። አየር ዠበቡ ለማረፍ ፩ሺ ጫማ ሲቀረው ሁለተኛው ሞተር ተገንጥሎ ሲወድቅ ያስከተለው መናጋት የአየር ዠበቡን የግራ ክንፍ ቁልቁል አዛብቶታል። አደጋው ያደረሰበት ጉዳት አየርዠበቡን ከጥቅም ውጭ ሲያውለው በተዓምር ግን ሁሉም ተሳፋሪዎች ተርፈዋል። ካፕቴን መኮንን ስለዚህ አደጋ ባሠፈሩት ትንተና ላይ፤ «አይሮፕላኑ ገና በረሃው ላይ ለማረፍ ሲጠጋ አስተናጋጆቹ የአደጋ ጊዘ መውጫዎቹን መስኮቶች ከፍተዋቸው ስለነበረ፤ እንደቆመ በጣም አጭር በሆነ ጊዜ ማለትም በ ፳ ሴኮንድ ውስጥ ፳ መንገደኞችና ዘጠኝ ሠራተኞች ምንም ሳይነካቸው ከሚቃጠለው አይሮፕላን ወጥተዋል። እንደ ዕድል ሆኖ ነፋሱ መንገደኞች ወደወጡበት በኩል ይነፍስ ስለነበረ የእሳቱ ወላፈን ሳይነካቸው ከአይሮፕላኑ ለመራቅ ቻሉ» በሚል አስፍረውታል። የአደጋው ምክንያት፣ አየር ዠበቡ ሲያርፍና ሲነሳ በ’ፍሬኖቹ’ መጋል ምክንያት እና የፍሬን ዘይት መፍሰስ ጎማው በመፈንዳቱ በሁለተኛው ሞተር ማዕቀፍ ውስጥ የተቀጣጠለው እሳት እንደሆነ ባለሙያዎች ገምተዋል። ካፕቴን መኮንን ደግሞ በመጽሐፋቸው ላይ ስለአደጋው የምርመራ ውጤት ባሠፈሩት መሠረት «ከካርቱም ሲነሳ የእግሮቹ ፍሬኖች እንደሞቁ ታጥፈው ኑሮ ጎማው ታፍኖ ስለቆየ ፈንድቶ ብዙ ነገሮች ስለጎዳ፣ ከፈሳች ነዳጅ ጋር ተገናኝቶ እሳት ስለተነሳ የአደጋው መነሾ መሆኑ ታወቀ።» በማለት አብራርተውታል። ሐምሌ ፰ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ቡልቂ በረራ ቁጥር ፫፻፸፪ (የሰሌዳ ቁጥር -18) የነበረው የ’ዳግላስ ሲ-፫ () አየር ዠበብ የአየር መንገዱ የመጀመሪያው የሰው ሕይወት ጥፋት የተመዘገበበት በረራ ነው። ከአዲስ አበባ ፭መቶ ፳ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በደቡብ ክልል ጋሞጎፋ ዞን ጎፋ ወረዳ ውስጥ ከምትገኘው ቡልቂ አየር-ዠበብ ማረፊያ ሦስት ዠበብተኞት እና ስምንት መንገደኞች እንዲሁም የቡና ምርት ጭኖ ወደጅማ ለመብረር ከጧቱ ሦስት ሰዓት ላይ ከተነሳ በኋላ ከአየር-ዠበቡ የተላለፈው ድምጽ ሦስት ሰዓት ከአርባ ደቂቃ ላይ አብራሪው ቶማስ ሃሎክ የጅማ የራዲዮ ማስተላለፊያ እንዲከፍተለት ያስተላለፈው ጥያቄ ነበር። አየር ዠበቡ መድረሻውን በ፳፯ ተኩል ኪሎ ሜትር አልፎት ከጅማ በስተደቡብ ከሚገኝ ተራራ ጋር ፱ሺ ፬መቶ ጫማ ከፍታ ላይ ተጋጭቶ ተገኘ። በተዓምር ከዠበብተኞቹ አብራሪው ሃሎክ ብቻ ሲሞት ሌሎች አሥር ተሣፋሪዎች ተርፈዋል። አየር ዠበቡ በደረሰበት አደጋ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። የአደጋው ምክንያት (ሀ) አብራሪው፣ አሜሪካዊው ቶማስ ፒ ሃሎክ የአካባቢውን ዓየር ሁኔታ መጥፎ ቢሆንም አቃልሎ በመገመቱ እና (ለ) የአየር ዠበቡን ሽቅብ የመውጣት ችሎታ ባለማወቅ በቂ ፍጥነት ሳያገኝ የአለአቅሙ ሽቅብ ለማስወጣት መሞከሩ እንደሆነ የአደጋው ጥናት ደምድሟል። ነሐሴ ፴ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም -ሰንዳፋ በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ቲ-፲፮ ተመዝግቦ የነበረው አየር ዠበብ ለአየር መንገዱ ሁለተኛው የነፍስ ጥፋት አደጋ የተከሰተበት በረራ ሲሆን፣ በግል ኪራይ ለዳሰሳ ጥናት ሦስት ዠበብተኞችንና አሥራ ስድስት መንገድኞችን ጭኖ ከአዲስ አበባ ልደታ ማረፊያ ተነሥቶ ወደ አስመራ በረራ ጀምሮ ነበር። ነገር ግን ሰንዳፋ አካባቢ ላይ የሞተሩ ተሽከርካሪ ሲያቆም አብራሪው ወደልደታ ለመመለስ ሞክሮ ነበር። ዳሩ ግን አየር ዠበቡ ወደመሬት ተከሰከሰና አስተናጋጇና አራት መንገደኞች ሕይወታቸው አልፏል። ጥር ፭ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ/ም -ቴፒ በከፋ ጠቅላይ ግዛት (የአሁኑ ከፊቾ ሸኪቾ ዞን) ውስጥ ከሚገኘው የቴፒ አየር-ዠበብ ማረፊያ ተነስቶ ወደ ጅማ ለመሄድ ሦስት ዠበብተኞችንና አሥራ አምስት መንገደኞችን ጭኖ የነበረው ዲ-ሲ ፫ () - የሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ቲ-፩ - አየር ዠበብ ከማኮብኮቢያው ሊነሳ ሲንደረደር ባልታወቀ ምክንያት በአቅራቢያው ከነበረ ወፍጮ ቤት ላይ ተላግቷል። በዚህ አደጋ አንዲት ወጣት ስትሞት ሦስት እግረኞች ደግሞ ክፉኛ ቀስለዋል። ኅዳር ፳ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ.ም - አዲስ አበባ ሰሌዳ ቁጥሩ ኢቲ-ኤ ኤ ቲ የነበረው ዲ-ሲ ፫ () ከጥገና በኋላ በሦስት አብራሪዎች ለፈተና ከአዲስ አበባ ልደታ አየር-ዠበብ ማረፊያ ሊነሳ ሲንደረደር ወደግራ በመሳብ ከማኮብኮቢያው ጥሶ ጉድጓድ ውስጥ ገብቶ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። በጥገናው ሥርዓት ላይ የግራ እና የቀኝ መጠምዘዣ መሪዎቹ በስኅተት ተለዋውጠው መገጠማቸው የአደጋው ምክንያት ሆነዋል። መስከረም ፬ ቀን ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - ጎሬ ዠበብተኞችንና ተሣፋሪዎችን አጠቃሎ አሥራ ሰባት ተሣፋሪዎችን ጭኖ ጎሬ አየር ዠበብ ማረፊያ ላይ በማረፍ አደጋ የጠፋው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኢቲ-ኤቢ አይ () አየር ዠበብ አሥራ ሰባቱም ተሳፋሪዎችና አብራሪዎች ሕይወታቸውን ያጡበት በረራ ነበር። መጋቢት ፫ ቀን ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - አስመራ ከአዲስ አበባ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም-አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሦስት አብራሪዎችና አንድ መንገደኛ ጭኖ ወደአስመራ የበረረው ዲ-ሲ- ፮ የጭነት በረራ ሲሆን አስመራ ላይ ሲያርፍ የፊትም ዋናዎቹም ጎማዎች ሲገነጠሉ አየር-ዠበቡ በእሳት ተያይዞ ከማኮብኮቢያው አልፎ ሜዳ ላይ ተቀጣጥሎ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤ ኤ ዋይ የተመዘገበው ይኽ ዲ-ሲ- ፮ አየር-ዠበብ በአደጋው ምክንያት ከአገልግሎት ውጪ ሲሆን አየር መንገዱ ዋና አብራሪውን ካፕቴን መኩሪያ በለጠን ሲያሳርፉ በስህተት/አውቀው የዓየር መግቻዎቹን () አልተጠቀሙም ብሎ ስለፈረደባቸው ከማዕረጋቸው በሁለት ደረጃ ዝቅ ከማድረጉም በላይ ከአገልግሎታቸውም የሁለት ዓመት ቅነሳ እንዲደረግ በይኖባቸዋል። ካፕቴን መኩሪያ በ፲፱፻፹፰ ዓ/ም በጠላፊዎች ማስገደድ በቆሞሮስ ደሴቶች አጥቢያ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ የወደቀው የዓየር መንገዱ በረራ ቁጥር ፱መቶ ፷፩ ምክትል አብራሪ የካፕቴን ዮናስ መኩሪያ አባት ነበሩ። ጳጉሜ ፭ ቀን ፲፱፻፷፬ ዓ/ም- ጎንደር በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤቢኪው የተመዘገበው ዲ-ሲ ፫ አየር ዠበብ ከአስመራ ተነስቶ በአክሱም፤ ጎንደር እና ባሕር-ዳር በኩል ወደአዲስ አበባ ሊሄድ የተነሳው በረራ ከአክሱም በተነሳ በ ፴፭ ደቂቃው ከጧቱ አራት ሰዓት ከሃያ ደቂቃ ላይ የቀኝ ክንፉ ተገንጥሎ ሲወድቅ ተሣፍረው የነበሩት አሥራ አንዱም ሰዎች ሞተዋል። አየር ዠበቡም ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ሐምሌ ፳፱ ቀን ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ሞጣ በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤቢኢ የተመዘገበው ዲ-ሲ ፫ () ሞጣ አየር-ዠበብ ማረፊያ ላይ ሲያርፍ ማኮብኮቢያውን ስቶ ሲከሰከስ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። በዚህ በረራ ላይ ስንት ሰዎች እንደነበሩ፤አደጋው በሰው አካል ወይም ነፍስ ላይ ያደረሰው ክስተት ምን እንደነበር መረጃ አልተገኘም። ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - ወላይታ ሶዶ በዚህ ዕለት ከወላይታ ሶዶ ተነስቶ በምዕራብ ወለጋ ዞን ወደምትገኘው በጊ ለመብረር ሦስት ዠበብተኞችንና ሃያ አንድ መንገደኞችን የጫነው ዲ-ሲ ፫ () ለመነሳት ሲያኮበክብ ተከስክሶ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። በዚህ አደጋ የዋናውና የምክትል አብራሪዎቹ ሕይወት ሲያልፍ አሥሩ መንገደኞች ቀላል የአካል ጉዳይ ደርሶባቸዋል። አስተናጋጇና የቀሩት አሥራ አንድ መንገደኞች ምንም ሳይሆኑ ተርፈዋል። በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤ ኤ አር የተመዘገበው ይህ አየር-ዠበብ በዚህ አደጋ ጊዜ የ፴፩ ዓምት ዕድሜ የነበረው ሲሆን በጠቃላላው ፳፯ሺ ፰፻ ሰዓታት የበረረ አሮጌ አየር-ዠበብ ነበር። ጳጉሜ ፮ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - ጮቄ ተራራ ይህ በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤቢ ኤክስ የተመዘገበው ዲ-ሲ ፫ () ከባሕር-ዳር ወደ ደብረ ማርቆስ ስድስት መንገደኞች፤ አንድ አስተናጋጅ፤ ዋና እና ምክትል አብራሪውን ጭኖ ሲበር ከዳመና ሽፋን ውስጥ ብቅ ሲል ከፊቱ በቅርቡ ተራራ ያጋጠማቸው አብራሪዎች በሽቅብ እና ዙር በረራ ለማምለጥ በሚሞክሩበት ጊዜ የአየር-ዠበቡ ጭራ ዛፎችን ስለመታ አብራሪዎቹ ለመቆጣጠር አልቻሉም። በዚህ ጊዜ በረራው ጮቄ ተራራ ላይ በጀርባው ተከሰከሰ። ተሳፈሩትም ዘጠኝ ሰዎች መኻል አንድ መንገደኛ ብቻ ሲሞት ሌሎቹ ተርፈዋል። ኢቲ-ኤቢ ኤክስ ለ፴፫ ዓመታት በጠቅላላው ለ፳፫ሺ ፱፻፳፩ ሰዓት የበረራ አገልግሎት ከሰጠ በኋላ በዚህ አደጋ ከጥቅም ውጭ ሆነ። ሚያዝያ ፲፱ ቀን ፲፱፻፷፰ ዓ/ም - ምጽዋ በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤ ኤ ኤስ ተመዝግቦ የነበረው ይህ ዲ-ሲ ፫ () አየር ዠበብ በተሠራ በ ሠላሳ ሁለት ዓመት ዕድሜው፤ ከ፴፫ሺ፻፸፪ ሰዓት የበረራ አገልግሎት በኋላ ምጽዋ አየር ዠበብ ማረፊያ ላይ በእሳት አደጋ ከአገልግሎት ውጭ ሆኗል። ግንቦት ፳፫ ቀን ፲፱፻፷፰ ዓ/ም - ምጽዋ በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤ ዲ ሲ ተመዝግቦ የነበረው ይህ ዲ-ሲ ፫ () አየር ዠበብ በተሠራ በ ሠላሳ ሁለት ዓመት ዕድሜው፤ ከ፴፪ሺ፮፻፹፪ ሰዓት የበረራ አገልግሎት በኋላ ምጽዋ አየር ዠበብ ማረፊያ ላይ ለመነሣት ስያኮበክብ በፍንዳታ የተነሳ ተቃጥሎ ከአገልግሎት ውጭ ሆኗል። ጥቅምት ፫ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓ/ም - አስመራ ከአስመራ አየር ዠበብ ማረፊያ ሊነሳ በማኮበኮብ ላይ ሳለ የቀኝ ጎማዎች ተገንጥለው በመውደቃቸው ከአገልግሎት ውጭ የሆነው ዲ-ሲ ፮ ()፤ ሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤ ኤ ዜድ አየር ዠበብ በአደጋው ምክንያት ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ታኅሣሥ ፭ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓ/ም አቦርሶ በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ-ኤኢጄ ተመዝግቦ የነበረው ዲ-ሲ ፫ () አየር ዠበብ አምሥት መንገደኞች፤ አንድ አስተናጋጅ እና ሁለት አብራሪዎችን ጭኖ በባሌ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ ኦቦርሶ ላይ ሲያርፍ ጎማዎቹ ተገንጥለው በመውደቃቸው ከጥቅም ውጭ ሆኗል። አየር ዠበቡ ያለጎማ በሆዱ አርፎ ከንተሸራተተ በኋላ ከምስጥ ክምር ጋር ተጋጭቶ ቆመ። ሰኔ ፭ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓ/ም - ቀብሪዳር ኢቲ-ኤ ኤ ፒ ዲሲ ፫ አየር ዠበብ በኦጋዴን ውስጥ ቀብሪዳር ላይ ሲያርፍ ዋናው የግራ ጎን ማረፊያ ጎማ በመሰበሩ ከጥቅም ውጭ ውሏል። ሐምሌ ፲፫ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓ/ም - ጅማ ሰሌዳ ቁጥሩ ኢቲ-ኤቢኤፍ () የነበረው ዲ-ሲ ፫ የተገዛው በየካቲት ወር ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ሲሆን፤ ሁለት መንገደኞችንና ሦስት ዠበብተኞችን ጭኖ ከቲፒ ቀን ለአሥራ አንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ላይ ተነስቶ የአርባ ደቂቃ በረራውን ወደ ጅማ ጀመረ። የዓየሩ ሁኔታ በዝቅተኛ ጉም የተሸፈነ ዝናባማ እና የሩቅ እይታም የተወሰነበት ነበር። አሥራ አንድ ሰዓት ከሃያ ላይ የጅማ አየር ዠበብ ማረፊያ ስለዓየር ሁኔታ ለአብራሪው የራዲዮ መልዕክት ካስተላለፈለት በኋላ ከበረራው ምንም የተሰማ ነገር አልነበረም። አየር ዠበቡ በስምንት ሺ ጫማ ከፍታ ላይ ከተራራ ጋር ተጋጭቶ አምስቱም ሰዎች ሕይወታቸው አልፎ ተግኝቷል። ኅዳር ፲ ቀን ፲፱፻፸ ዓ/ም ሚያዝያ ፭ ቀን ፲፱፻፷ ዓ/ም አገልግሎት ላይ የዋለው ኢቲ-ኤሲዲ የመጀመሪያው የአየር መንገዱ ‘ቦይንግ’ ፯መቶ፯ () ነበር። በአደጋው ዕለት ሦስት ዠበብተኞችንና ሁለት መንገደኞችን ይዞ በጭነት በረራ ከሮማ ‘ፊዩሚቺኖ’ ማረፊያ ተነስቶ ሲያሸቅብ፣ ሰባት እና ስምንት ሜትር ከፍታ ላይ የዛፍ ቅርንጫፎችን በመምታቱ ወድቆ ተሰባብሮ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ጥቅምት ፭ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - ወላይታ ሶዶ በሰሌዳ ቁጥር ኢት-ኤጂኬ () የተመዘገበው ዲ-ሲ ፫ () አየር ዠበብ ሦስት ዠበብተኞችንና ሃያ ዘጠኝ መንገደኞችን ጭኖ በበረራ ላይ ሳለ የዠበቡ የሃይድሮሊክ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ በመክሸፉ አብራሪዎቹ በአስቸኳይ ለማረፍ ወደወላይታ ሶዶ አምርተው ሞተሩችን ካተፉ በኋላ ሲያርፉ አየር ዠበቡ ለሺ ሁለት መቶ ሜትር ከተንሸራተተ በኋላ የውሐ ቦይ ውስጥ ገብቶ ቆመ። ዳሩ ግን በዚህ ክስተት በተሳፋሪዎቹ ላይ ክፉ ጉዳት ባይደርስም አየር ዠበቡ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ጥቅምት ፲፭ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - ደገሀቡር ኢቲ-ኤጂኪው () በሰኔ ወር ፲፱፻፸ ዓ/ም ከሌላ አየር መንገድ የተገዛ ዲ-ሲ- ፫ () ነበር። ከነአብራሪዎቹ አሥራ ሦስት ሰዎችን ጭኖ በረዳት አብራሪው ቁጥጥር በሰሜን ኦጋዴን ደገሀቡር ላይ ሲያርፍ ያልተጠበቀ የነፋስ ኃይል መታው። በዚህ ጊዜ ዋናው አብራሪ አየር ዠበቡን ከምክትሉ ተቀብሎ ለማቆም ቢጥርም ማኮብኮቢያውን ስቶ የውሐ ቦይ ውስጥ ሲወረወር ማረፊያ ጎማዎቹ ተገንጥለው ወደቁ። በዚህ አደጋ በሰው ላይ የደረሰ ክፉ ጉዳት ባይኖርም አየር ዠበቡ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ጥር ፳ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም የሰሌዳ ቁጥሩ ኢቲ-ኤጂፒ () የነበረው ዲሲ ፫ () ለአየር መንገዱ አገልግሎት ላይ የዋለው በ፷ዎቹ ማገባደጃ ሁለት አመታት ውስጥ ሲሆን በአደጋው ዕለት ከአስመራ በስተ-ምዕራብ ባልታወቀ ምክንያት ወድቆ ሲከሰከስ ሦስቱም የአየር መንገዱ ሠራተኞች ሞተዋል። አየር ዠበቡም ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ሚያዝያ ፲፪ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - ኦቦርሶ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢቲ-ኤጂዩ () የነበረው ይህ ዲ-ሲ ፫ () አየር ዠበብ ዋናውንና ምክትል አብራሪውን፤ አንድ አስተናጋጅ እንዲሁም አራት መንገደኞችን ጭኖኦቦርሶ ማረፊያ ላይ ሲያርፍ የማኮብኮቢያው ድንበር ላይ የተተከሉትን ድንጋዮች በመምታት የቀኝ ማረፊያ ጎማዎቹ በመሰበራቸው የጥገና ሥራ ከተደረገለት በኋላ ለጥቂት ወራት ወደአገልግሎት ተመልሶ ነበር። ዳሩ ግን በሌላ አደጋ ከጥቅም ውጭ ውሏል፡፡ በዚህ ኦቦርሶ ማረፊያ ላይ ኢቲ-ኤ-ኤ-ጄ ታኅሣሥ ፭ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓ/ም በተመሳሳይ የጎማዎች መገንጠል አደጋ ከምስጥ ክምር ጋር ተጋጭቶ ከጥቅም ውጭ እንደዋለ ተዘግቧል። መስከረም ፲ ቀን ፲፱፻፸፪ ዓ/ም ባረንቱ ሚያዝያ ፲፪ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - ኦቦርሶ ላይ በደረሰበት አደጋ ሰፊ ጥገና ተደርጎለት ወደአገልግሎት የተመለሰው ኢቲ-ኤጂዩ () የነበረው ይህ ዲ-ሲ ፫ () አየር ዠበብ በደቡብ-ምዕራብ ኤርትራ፣ ከባረንቱ ማረፊያ ሊነሳ ሲያኮበኩብ በአፍንጫው ተደፍቶ ሲከሰከስ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ሐምሌ ፭ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ሎንዶን 'ሂዝሮው'' ጥያራ ጣቢያ በሰሌዳ ቁጥር ኢቲ- ኤ ኦ ፒ () የተመዘገበው እና ልዩ ስሙ "ንግሥት ሣባ" የተባለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር ዠበብ በዛሬው ዕለት በሎንዶን 'ሂዝሮው' ጥያራ ጣቢያ እንደቆመ የእሳት አደጋ ደረሰበት። ይኽ አደጋ የተከሰተው ጥያራው መንገደኞችን አሣፍሮ ከአዲስ አበባ ከገባ ከስምንት ሰዓታት በኋላ ነው። አየር መንገዱ ይኽንን ዠበብ ከቦይንግ ኩባንያ ተረክቦ አገልግሎት ላይ ያዋለው ከስምንት ወራት በፊት ኅዳር ፲፩ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ነው። የአየር ጠለፋ እና የአመጽ ጉዳቶች መጋቢት ፪ ቀን ፲፱፻፷፩ ዓ/ም የሰሌዳ ቁጥሩ ኢቲ-ኤሲ ኪው () የነበረው የቦይንግ ፯መቶ፯ () አየር ዠበብ በአየር መንገዱ ታሪክ በሽብርተኞች የአየር ጠለፋ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰለባ የደረሰብት አየር ዠበብ ነበር። ከግሪክ ርዕሰ ከተማ አቴና ተነስቶ ፍራንክፈርት ዓለም አቀፍ የአየር ዠበብ ማረፊያ የደረሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አየር ዠበብ በቆመበት ሥፍራ ላይ በአውሮፕላኑ የቱሪስት ማዕርግ ክፍል ላይ ሁለት ፈንጂዎች ጉዳት አድርሰዋል። አየር ዠበቡን በማጸዳዳት ላይ የነበሩም ሴቶች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጉዳቱን ያደረሰው ‘ለኤርትራ ነጻነት-የአረባዊ ሶርያ እንቅስቃሴ’ የሚባለው ቡድን ነው ሲል የኤርትራ ነጻነት ግንባር ግን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገጠር ነዋሪ ኤርትራውያንን ለማጥቃት የሚላኩትን ወታደሮች ወደኤርትራ ስለሚያጓጉዝ የበቀል ጥቃት ያካሄዱት እነሱ እንደሆኑ አረጋግጧል። ሰኔ ፲፩ ቀን ፲፱፻፷፩ ዓ/ም ፓኪስታን ፦ ካራቺ አየር ዠበብ ማረፊያ ላይ ሦስት የኤርትራ ነጻነት ግንባር ታጣቂዎች፣ በሰሌዳ ቁጥር ኢ.ቲ. - ኤ.ሲ.ዲ. () የተመዘገበውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ ፯፻፯ - ፫፻፷ ሲ () አየር ዠበብ ላይ ፈንጂ ወርውረው ከፍተኛ ጉዳት አድርሰውበታል። ኦኖም አየር ዠበቡ ተጠግኖ አገልግሎት ላይ ውሏል። መሐመድ ኢድሪስ፣ ፍስሐዬ አብርሃምና ዓሊ አብደላ የተባሉት ሦስቱም ታጣቂ አመጸኞች ሲያዙ በሰጡት መግለጫ፣ በኤርትራ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ መንግሥት አስተዳደር ተቃዋሚ መሆናቸውን ለማሳወቅ የወሰዱት የሸፍጥ ድርጊት እንደሆነ ገልጸዋል። ሦስቱም ሸፍጠኞት በድርጊታቸው ምክንያት ለፍርድ ቀርበው የአንድ ዓመት ጽኑ እሥራት ተፈርዶባቸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የኤርትራ ነጻነት ግንባር ቃል አቀባዮች ሐምሌ ፳፬ ቀን ፲፱፻፷፩ ዓ/ም ይፋ ባደረጉት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የኢትዮጵያ አየር ኃይል በ ኤርትራውያን ላይ ለሚያካሂደው የአየር ድብደባ በቀላቸውን በአየር መንገዱ ላይ ለመወጣት ሙከራቸውን ስለሚቀጥሉ በዚሁ ብሔራዊ አየር መንገድ የሚሣፈሩ መንገደኞች ለሕይወታቸው አስጊና አደገኛ እንደሚሆን በመጠቆም የአየር መንገዱን የገቢ ምንጭ ከማዳከም እንደማይመለሱ አስታውቀዋል። ነሐሴ ፭ ቀን ፲፱፻፷፩ ዓ/ም በተማሪው ንቅናቄ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተው፣ አንደበተ ርቱዕ የነበረው ብርሃነ መስቀል ረዳ፤ የሕግ ተማሪ የነበረው ኢያሱ ዓለማየሁ፤ ኃይለ ኢየሱስ ወልደ ሰማያት፤ ገዛኸኝ እንዳለ፤ አማኑኤል ገብረ ኢየሱስ፤ የመንግሥት ሠራተኛ የነበረው አ.አ.፤ በጠቅላላው ሰባት ሆነው ከ ባሕር-ዳር ተነስቶ ወደአዲስ አበባ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አየር-ዠበብ ማረፊያ (ቦሌ) ሊበር የታቀደውን ዲ-ሲ ፫ ወደ ካርቱም እንዲያመራ አስገደዱት። እነኚህ ጠላፊዎች የካርቱም ቆይታቸው ለደህንነታቸው ዋስትና እንደሌለው በመገንዘብ፤ የፖለቲካ ጥገኝነት በመጠየቅ ወደ አልጄሪያ መዲና አልጄርስ አመሩ። መስከረም ፫ ቀን ፲፱፻፷፪ ዓ/ም ከአዲስ አበባ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም-አቀፍ ማረፊያ ፴፱ መንገደኞችንና ፭ ዠበብተኞችን አሳፈሮ ወደ ጂቡቲ በመማራት ላይ የነበረው ዲ-ሲ- ፮ በረራ በሦስት ኤርትራውያን ተጠልፎ ወደ አደን እንዲበር ተገድዶ ወደዚያው ሲበር የአየር መንገዱ የጸጥታ ታጣቂ አንዱን አመጸኛ ተኩሶ አቁስሎታል። አደን ሲያርፉም የአገሪቱ የፖሊስ ኃይል ሦስቱንም ጠላፊዎች በቁጥጥር ሥር አዋላቸው። ጠላፊዎቹ የኤርትራ ነጻነት ግንባር አባላት እንደሆኑ ታውቋል። ታኅሣሥ ፫ ቀን ፲፱፻፷፪ ዓ/ም ከእስፓኝ ርዕሰ ከተማ ማድሪድ ዘጠኝ ዠበተኞችንና አሥራ አራት መንገደኞችን ጭኖ በሮማ በኩል ወደአዲስ አበባ ጉዞውን የጀመረው ቦይንግ ፯መቶ፯ በረራ የየመን ተወላጅ የሆነ ጠላፊ ሽጉጡን መዝዞ በረራ ክፍል ውስጥ ከገባ በኋላ አብራሪውን ወደአደን እንዲያመራ ቢያዘውም ቅሉ፣ አብራሪው ለነዳጅ ሮማ ማረፍ ግድ እንደሚሆንበት አስረድቶ ነበር። የአየር መንገዱ የጸጥታ አስከባሪ በረራ ክፍል ውስጥ ገብቶ ጠላፊውን በሽጉጥ ገድሎታል። በዚህ ጊዜ ሁለተኛው ጠላፊ ጩቤውን ጨብጦ ወደበረራ ክፍሉ ሲሮጥ ሁለተኛው የአየር መንገዱ የጸጥታ አስከባሪ እርሱንም በሽጉጥ ተኩሶ ገድሎታል። ከዚህ ክስተት በኋላ በረራው በሰላም አቴና ላይ አርፏል። የኤርትራ ነጻነት ግንባር ቃል አቀባይ ደማስቆ ላይ ገለጻ ሲሰጥ ሁለቱ የግንባሩ አባላት ቢሆኑም ዓላማቸው አየር-ዠበቡን ለምጥለፍ ሳይሆን ስለድርጅቱ በራሪ ማስታወቂያዎችን ለማደል ነበር ብሏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የ[[እስፓኝ ፖሊስ ታኅሣሥ ፩ ቀን ማድሪድ ዓለም አቀፍ ማረፊያ ላይ ሦሥተኛው አባል ነው ብለው የገመቱትን ሰው ፈንጂ ይዞ ሲገባ በቁጥጥር ስር አውለውታል። ጥር ፲፱ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ/ም አራት የኤርትራ ነጻነት ግንባር ሸፍጠኞች ከባሕር-ዳር ወጎንደር፣ ከነዠበብተኞቹ ሃያ ሰዎችን የጫነውን ዲ-ሲ፫ አየር ዠበብ በኃይል ወደ ቱኒዚያ ዋ ሁለተኛ ከተማ በንጋዚ እንዲበር ካስገደዱት በኋላ ለነዳጅ ቅጅ ካርቱም ላይ አረፈ። ኅዳር ፳፱ ቀን ፲፱፻፷፭ ዓ/ም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ፯መቶ፰ ከአዲስ አበባ ተነስቶ አስመራ፤ አቴና፤ ሮማ እና ፓሪስ ለመሄድ ከነዠበብተኞቹ ዘጠና አራት ሰዎች ጭኖ በተነሳ በአሥራ ሦስት ደቂቃዎች ከመንገደኞቹ መኻል ፭ ወንዶችና ፪ ሴቶች ሽጉጥ መዝዘው በአማርኛ ትዕዛዛቸውን ሲጮኹ የአየር መንገዱ የጸጥታ ሰራተኞች ተኩስ ከፍተው ስድስቱን ጠላፊዎች ሲገድሉ ሰባተኛው በኋላ ሆስፒታል ገብቶ ሞቷል። በተኩሱ ጊዜ ከጠላፊዎቹ አንዱ የያዘውን የእጅ ቦምብ ነቅሎ ሲጥለው ከመንገደኞቹ አንዱ ብድግ አድርጎ ሰው ወደሌለበት ሥፍራ ጥሎት ፈነዳ። ይኽ ፍንዳታ አንድ ሞተር እና የአቅጣጫ መቆጣጠሪያ ከጥቅም ውጭ ሲያደርገው የአየር ዠበቡን የመንገደኞች ክፍል በጢስ አፍኖት ነበር። ኣብራሪው ካፕቴን ቀጸላ ኃይሌ ያለምንም ድንጋጣ አየር-ዠበቡን ወደአዲስ አበባመልሰው በሰላም አሳርፈውታል። ካፕቴኑ ለዚህ ተግባራቸው ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የጀግንነት ሜዳይ ከመሸለማቸውም ባሻገር በአየር ዠበቡ ተሣፍሮ የነበረውና ከእንግሊዝ ለወፎች ጥናት ኢትዮጵያ መጥቶ የነበረው ቡድን፤ ከዚህ አደጋ ላተረፏቸው ለኚህ ካፕቴን ሎንዶን ከተማ ውስጥ ከፍ ያለ ግብዣ አድርገውላቸዋል። ጠላፊዎቹ የኤርትራ ነጻነት ግንባር አባላት ሲሆኑ መሪያቸውም በዚሁ ድርጊት የተገደለችው ማርታ መብርሃቴ ነበረች። መጋቢት ፭ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ላሊበላ ሲያርፍ በአመጸኞች የጥይት እሩምታ የተመታው ዲ-ሲ ፫ () አየር ዠበብ - ሰሌዳ ቁጥር ኢቲ- ኤቢአር - ከጥቅም ውጭ ሲሆን የአንድ ሰውም ሕይወት ጠፍቷል። አየር ዠበቡ በዚህ አደጋ ጊዜ የ፴፫ ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ ሲሆን ለ ፴፫ሺ፮፻፳፮ ሰዓት በረራ አገልግሏል። ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓ/ም ከመቀሌ ወደ ጎንደር ሲበር ሁለት ሰዎች የከሸፈ የጠለፋ ሙከራ ያደረጉበት ዲ-ሲ ፫ አየር ዠበብ ጎንደር ላይ በሰላም አርፏል። ዳሩ ግን ሁለቱን ጠላፊዎች አጠቃሎ የሦስት ሰዎች ሕይወት አልፎበታል። የካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - ባረንቱ ኢቲ-ኤ-ኤፍ ደብልዩ () ዲሲ ፫ () ለአየር መንገዱ አገልግሎት ላይ የዋለው በ፷ዎቹ ማገባደጃ ሁለት አመታት ውስጥ ሲሆን፤ በደቡብ-ምዕራብ ኤርትራ በምትገኘው ባረንቱ ላይ በቦምብ ፍንዳታ ተከስክሶ ሲወድቅ አምስቱም ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። አየር ዠበቡም ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ዋቢ ምንጮች ክፍሉ ታደሰ፤ ያ ትውልድ፤ ቦሌ ማተሚያ ድርጅት (ዓ/ም የለውም) የኢትዮጵያ አየር መንገድ
53924
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A2%E1%89%B5%E1%8A%AE%E1%8B%AD%E1%8A%95
ቢትኮይን
ቢትኮይን እስከዛሬ ከለመድነው እና ከምናውቀው የገንዘብ ስርዓት በእጅጉ የተለየ ነው። የተለመደው እና ለረዥም ዘመናት ስራ ላይ እየዋለ ያለው ገንዘብ ብሄራዊ ባንክ የሚያትመው እና የሚቆጣጠረው ፣ የራሱ የሆነ መለያ ያለው ፣ ከዚያም አለፎ የራሱ የሆነ የብር ኖት ያለው ሲሆን ቢትኮይን ግን ማዕከላዊ የሆነ የሚቆጣጠረው እና የሚያስተዳድረው አካል የለም። ገንዘቡ በመሆኑ የብር ኖት እና ማከማቻ እቃ ሳያስፈልገው ግን እንደፈለጉ ስራ ላይ ማዋል የሚቻልበት ነው። ቢትኮይን በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም። ማንኛውም ሰው እንደ ኮይን ቤዝ // ያሉ ገጾችን በመጠቀም የቢትኮይን ባለቤት መሆን ይችላል። በማን እና እንዴት ተጀመረ? እንደ አውሮፓዊያኑ የዘመን ቀመር በ2008 ዓ.ም ሳቶሺ ናካሞቶ በተባለ ግለሰብ ወይም ግለሰቦች ስለ ቢትኮይን ምንነት እና አሰራር የሚገልጽ ጽሁፍ ከሶፍትዌር ፕሮግራሙ ጋር በበይነ መረብ ለአለም ይፋ ሆኗል። እስካሁን ድረስ ሳቶሺ ማን እንደሆነ ለማወቅ አልተቻለም። በርግጥ አንድ የአውስትራሊያ ዜግነት ያለው የኮምፒውተር ሳይንቲስት ሳቶሺ ማለት እኔ ነኝ ብሎ ብዙዎችን ለማጭበርበር ሙከራ አድርጓል። ሳቶሺ የሚለው ስም የእውነት የአንድ ሰው ስም ይሁን ወይም ሶፍትዌሩን ያበለጸጉት ሰዎች የሚስጥር መጠሪያ ይሁን በውል የሚታወቅ ነገር የለም። የሆነው ሆኖ ስለቢትኮይን የሚገልጸው መረጃ ይፋ ከሆነ ከአመት በኋላ ስራ ላይ ውሏል። የመጀመሪያው የቢትኮይን ብሎክ በሳቶሺ ማይን የተደረገው ጄኔሲስ ብሎክ () ይባላል። ጄኔሲስ ብሎክን ጨምሮ እስከዛሬ ድረስ የተደረጉት የቢትኮይን ሽያጭ እና ግዥዎች በሙሉ ኢንተርኔት ላይ ተመዝግበው አሉ። ስለዚህ ማንኛውም ኮምፒውተር ያለው ሰው እነዚህን ገቢ እና ወጪዎች ሁሉ ማየት ይችላል። ይህም አሰራሩ በአንድ ማዕከላዊ አስተዳደር ብቻ የተገደበ እንዳይሆን ይረዳል። የመረጃው ለማንም ሰው በየትም ቦታ እና በማንኛዉም ሰዓት ተደራሽ መሆን ማንኛውም ፈቃደኛ የሆነ ሰው ሁሉ የቢትኮይንን ግብይት እና ሽያጭ መከታተል ይችላል። ይህንን የሚያደርጉ ሰዎች ማይነርስ () በመባል ይጠራሉ። ማይነርስ እያንዳንዱን ግብይት በመመዝገብ እና ግብይቱ በአግባቡ መካሄዱን ያረጋግጣሉ። ይህም ብሎክቼይኖች በሚገባ እንዲሰሩ እና ትክክለኛ ግብይት መካሄዱን ለማጣራት ሲጠቅም በአንጻሩ ደግሞ ጊዜያቸውን ወስደው ማይን ያደረጉት ሰዎች ለሰሩበት 6.25 ቢትኮይን ይከፈላቸዋል። ብሎኮችን ማይን ለማድረግ ከፍተኛ የፕሮሰሲንግ ያላቸው ኮምፒውተሮች ያስፈልጋሉ። ምክኒያቱም ውስብስብ የሆኑ አልጎሪዝሞችን ፕሮሰስ ለማድረግ ስለሚያስፈልጋቸው ነው። ከዚህ በተጨማሪ ማይኒንግ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሀይል ይወስዳል። ከዚህ የተነሳ የኤሌክትሪክ ዋጋ ርካሽ የሆነባቸው እና የኤለክትሪክ መቀራረጥ የማያስቸግራቸው ሀገራት ላይ ብዙ ማይነርስ አሉ። አብዛኛዎቹ ማይነሮች ቻይናዊያን ናቸው። ለዚህም ምክኒያቱ በኤሌክትሪክ ሀይል ዙሪያ ምንም ስጋት ስለሌለባቸው ነው። ነገር ግን የሀገሪቱ መንግስት ካለፈው አመት ጀምሮ ቢትኮይንን ስለከለከለ ማይነሮቹ ከቻይና ወደ ጎረቤት ሀገራት እየፈለሱ ይገኛሉ። በግል አንድን ብሎክ ማይን ለማደረግ ከሚወስደው ሰዓት አንጻር እንዲሁም በቶሎ ትርፋ ለመሆን ማይነሮች በግሩፕ በመሆን ይሰራሉ። ኮምፒውተራቸውን ዝግጁ አድርገው ይጠብቁ እና ልክ አንድ ግብይት ሲካሄድ ያንን ብሎክ ማይን በማድረግ እያንዳንዱ ሰው ለብሎክ ቼይኑ መሰራት ባደረገው አስተዋጽኦ ልክ ይከፈላዋል። የቢትኮይን ደህንነት እያንዳንዱ ትራንዛክሽን በአደባባይ ሁሉም ሰው ሊያየው በሚችለው መልኩ የሚቀመጥ፣ ለትክክለኛነቱ ደግሞ በተለያዩ የአለም ክፍል ያሉ ማይነሮች በየጊዜው የሚያረጋግጡት መሆኑ በመሆኑ ቢትኮይን ደህነነቱ የተጠበቀ ገንዘብ መሆን እንዲችል ይረዳዋል። ከዚህ ባለፈ እያንዳንዱ ደንበኛ ሁለት ቁልፎች አሉት። አንዱ የግል ቁልፍ () ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የህዝብ ቁልፍ () ነው። የእያንዳንዱ ሰው የተለያየ እና በግለሰቡ ብቻ ሚስጥር ሊያዝ የሚገባው ቁልፍ ነው። ደግሞ ልክ እንደ አካውንት ቁጥር የሚያገለግል ነው። ስለዚህ ማንኛውም ተጠቃሚ የቢትኮይን ግብይት ሲያደርግ ውን ለማረጋገጥ በ ያደርገዋል። ይህ የግል ቁልፉ ልክ እንደመፈረም ያህል ያገለግላል። በተጨማሪም ቢትኮይን መረጃዎችን በኔትዎርክ ውስጥ የሚያስተላልፈው ክሪፕቶግራፊን በመጠቀም ነው። ክሪፕቶግራፊ ከጥንት ጀምሮ ነገስታት ለሰራዊቶቻቸው መልክት በሚያስተላልፉበት ጊዜ መልዕክታቸውን ከተፈለገው አካል በስተቀር ማንም እንዳይረዳዊ የሚያደርጉበት ስልት ነው። በአሁኑ ጊዜም ይሄ አነቱ አካሄድ ኮፕቂውተራይዝድ ሆኖ እና ዘምኖ ተግባር ላይ ይውላል። ክሪፕቶግራፊ እና ከሚሉ ሁለት የግሪክ ቃላት የመጣ ሲሆን ሚስጥር ወይም የተደበቀ ነገር እንዲሁም ደግሞ ጽሁፍን ይወክላሉ። በክሪፕቶግራፊ አንድ ግልጽ የሆነ መልዕክት በመሆን ወደ ይቀራል። የተለያዩ ፊደሎች፣ ምልክቶች እና ቁጥሮች የተዘበራረቀ ስብጥር ሲሆን ማንም ሰው መሀል ላይ ሰብሮ ቢገባ እና ይሄንን መልዕክት ቢያገኘው ምንም አይነት ትርጉም አይሰጠውም። ልክ መልዕክቱ ትክክለኛው ተቀባይ ጋር ሲደርስ ከ ወደ ይሆን እና ትርጉም ያለው ነገር ይሆናል።ይህም ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን አስችሎታል። የቢትኮይን ስጋት ማንኛውም ሰው ከየትም ቦታ ሆኖ ለማንነቱ ማረጋገጫ ሳያስፈልገው አካውንት መክፈት፣ ገንዘብ መላክ፣ መሸጥ እና ማስተላለፍ መቻሉ ለወንጀለኞች ማንነታቸው ሳይታወቅ እንዳሻቸው ገንዘብ ማንቀሳቀስ እንዲችሉ አግዟቸዋል። እነዚህ ሰዎች በባንክ ቤት ገንዘብ ለማንቀሳቀስ ይችሉ ዘንድ አካውንት በሚከፍቱበት ጊዜ ሙሉ ስም፣ አድራሻ፣ የስራ መደብ ፣ ፎቶ እንዲሁም መሰረታዊ እነሱነታቸውን የሚያስረዳ ነገር ስለሚጠየቁ ቢትኮይንን እንደ ትልቅ በረከት በመቁጠር ገንዘባቸውን እንደ ልብ ያንቀሳቅሱበታል። በተለይም የዳርክ ዌብ // ተጠቃሚዎች እንደ እና አይነት ወንጀሎች በሰፊው ይጠቀሙበታል። ከዚህ ባለፈ ቢትኮይንን በበላይነት የሚቆጣጠር መንግስታዊ አካል አለመኖሩ ለመንግስታዊ አስተዳደር ትልቅ ፈተናን አምጥቷል። ተደራሽነቱ ሰፍቶ እና የአለም ህዝብ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የዚህ ስራዓት ተጠቃሚ ከሆኑ የሀይል ሚዛንን ከመንግስታዊ አስተዳደር ይነጥቃል፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውንም በእጅጉ ይቀይራል። ይሄም ይዞት የሚመጣው የራሱ የሆነ መልካም እና ክፉ አድሎች ይኖሩታል። ቢትኮይን አሁን ላይ መጀምሪያ ተግባር ላይ ከዋለበት 2009 ዓ.ም አንስቶ እስካሁን ድረስ አስራ ሶስት አመታትን አስቆጥሯል። በመጀመሪያዎቹ አመታት ተቀባይነትን ያገኘው እና በሰፊው ተግባር ላይ የዋለው በጥቁር ገበያ ነጋዴዎች // ነው። ከ2013 ጀምሮ በዩናይትድ ስቴትስ የፍትህ ተቋማት እና መሰል ተቋማት ላይ ተግባር ላይ ውሏል። ከጊዜ ወደ ጊዜውም ሰዎች ስለ ቢትኮይን ያላቸው እወቀት እየጨመረ እና ተጠቃሚነትም እየጨመረ ሄዷል። በ2021 የ ኤልሳልቫዶር // መንግስት ቢትኮይን በሀገሪቱ እንደ አንድ መገበያያ እንዲያገለግል አጽድቋል። በተከታዩ አመትም የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ይህንኑ አድርጓል። በቅርብ ጊዜም በሩሲያ እና በዩክሬይን መካከል በተነሳው ጦርነት ምክኒያት የተጎዱ ሰዎችን ለመርዳት ገንዘብ እየተሰባሰበበት ይገኛል። ጦርነቱን ምክኒያት በማድረግ አብዛኛው የአውሮፓ ሀገራት ሩሲያ ላይ ማዕቀብ በመጣላቸው ምክኒያት ሩሲያ የነዳጅ ዘይት ምርቷ እንዳይጎዳ ለማድረግ ከዚህ ጋር ለተገናኙ ግብይቶች ቢትኮይንን እንደ ክፍያ አማራጭ መጠቀም ጀምራለች። የቢትኮይን ዋጋ ቢትኮይን ወደ አሜሪካ ዶላር ሲመነዘር ያለው ዋጋ አንዳንድ ጊዜ ከፍተኛ ሌላ ጊዜ ደግሞ ዝቅተኛ ይሆናል። ለዚህም የተለያዩ ምክኒያቶች አሉት። የወቅቱ የኢንፍሌሽን ሁኔታ፣ አለም አቀፋዊ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ፣ እንደ ኮሮና ቫይረስ ያሉ ድንገተኛ አለም አቀፋዊ ተጽዕኖ ያላቸው ክስተቶች ይጠቀሳሉ። በ2011 የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ከ0.3 የአሜሪካ ዶላር ጋር እኩል ነበር። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በዚያው አመት ከ 32 ዶላር እኩል ነበር ብዙም ሳይቆይ ወደ ሁለት ዶላር ወርዶ ነበር። ይሄ ቪዲዮ በሚዘጋጅበት በአሁኑ ጊዜ የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ከ 19,922.3 ዶላር ጋር እኩል ነው። ቀደም ብለን እንደጠቀስነው የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ይጨምራል ይቀንሳልም። ነገር ግን በግልጽ መናገር እንደሚቻለው ቢትኮይን በፊት ከነበረበት 0.3 ዶላር ተነስቶ አሁን ላይ ወደ 19,000 – 20,000 ባለው ከፍ እና ዝቅ እያለ ይገኛል። ከዚህ በግልጽ መረዳይ የሚቻለው የቢትኮይን ዋጋ በጥቅሉ ከፍተኛ የሚባል ጭማሬ እንዳሳየ ነው። በ2010 ግንቦት ወር ላይ አንድ ጄረሚ ስተርዲቫንት // የተባለ የ19 አመት ወጣት አንድ ማስታወቂያ ያያል። በማስታወቂያው ላይ አንድ ግለሰብ ፒዛ ቤቱ ድረስ ላመጣለት ሰው 10,000 ቢትኮይን እንደሚከፍለው ይገልጻል። ያን ጊዜ 10,000 ቢትኮይን ማለት 41 ዶላር ነበር። ይሄም በአሁኑ ጊዜ ካለው የቢትኮይን ዋጋ ጋር ሲሰላ 19,922,300,000 ጋር እኩል ነው። በርግጥ ጄረሚ ገንዘቡን አላስቀመጠውም። ቢያስቀምጠው ኑሮ ቢሊዮነር ሊሆን እንደሚችል ግልጽ ነው።ስለዚህ ዛሬ ላይ የምትገዛ አንዲት ቢትኮይን ወደፊት በብዙ ዶላሮች ትመነዘራለች ማለት ነው።
14376
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8D%88%E1%8B%88%E1%88%AD%E1%89%85%20%E1%89%B0%E1%8A%AD%E1%88%8C
አፈወርቅ ተክሌ
የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባይገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የሰጧቸውን ምክር ሁሌም እንደሚያስታውሱት ይናገራሉ። “ንጉሠ ነገሥቱ ተግታችሁ አጥኑ፣ ተማሩ ብለው ከመከሩን በኋላ ጠንክራችሁ መሥራት እና ሀገራችሁ ኢትዮጵያን የምትገነቡበትን ዕውቀት ይዛችሁ ተመለሱ። ስትመለሱ አዕምሯችሁ ዝግጁ የሆነ እውቀታችሁም ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚችል ጥበብን ሸምቶ እንዲመለስ ነው እንጂ አውሮፓ ውስጥ እንዴት ያሉ ረዣዥም ፎቅ ቤቶች እንዳሉ ወይም መንገዶቻቸው የቱን ያህል ስፋት እንዳላቸው እንድትነግሩን አይደለም።” ነበር ያሏቸው። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በፖካርሲን () እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት () ተመዝግበው ገቡ:: እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል () የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በስየቃ () ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ ሲያጠኑ ቆዩ። “ምኞቴ በዓለም የታወቀ ኢትዮጵያዊ የኪነ ጥበብ ምሑር መሆን ስለነበር፣ የአገሬን ወግና ባሕል ጠንቅቄ ማወቅና ማጥናት እንዳለብኝ አውቄያለሁ። ሥራዬ የዓለም ንብረት ይሆናል ነገር ግን በአፍሪቃዊነት ቅመም የጣፈጠ ሥራ ነው የሚሆነው።” ይሉ ነበር። ከሁሉም በላይ ግን የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ፤ የላቀው ድካማቸውና የምናየውም ውጤት፣ የኪነ ጥበብ ሥራቸው የአገራቸውን ታሪክ የሚያንጸባርቅ ሕብረተ ሰብአዊ መሣሪያ እንዲሆን ነው። በውጭ የተማሩ ቢሆኑም፣ እሳቸው ‘ዋጋ ቢስ’ የሚሉትን፣ እንደሌሎች (ምዕራባውያንም ሆኑ ሌሎች) የሚጠቀሙበትን ‘ኩረጃ’ ላለመከተል በትጋት ተፋልመዋል። ወደ ውጭ ሊሄዱ ሲነሱ የሰሙትን የንጉሠ ነገሥቱን ቃላት ‘….ኢትዮጵያን ለመገንባት አዕምሯችሁ ዝግጁ ይሁን፣ ለዚህም የሚጠቅም ጥበብን ሸምቱ…” ያሏቸው ቃላት አሁንም በውስጠ ጆሯቸው እያስተጋቡ፤ ከውጭ ሲመለሱ የተመደበላቸውን ሚኒስቴራዊ ሥራ ትተው የኪነ ጥበብ ሥራቸው ላይ በማተኮር ስዕሎቻቸውን በአገር ውስጥም በውጭ አገርም እያሳዩ ለማገልገል ቆረጡ። በሀያ ሁለት ዓመታቸውም በ፲፱፻፵፮ ዓ/ም ሥራቸውን የሚያሳይ የመጀመሪያውን የኪነ ጥበብ ትርዒት በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት አቀረቡ። ወዲያውም ከዚህ ትርዒት ባገኙት ገቢ ተመልሰው ወደአውሮፓ በመሄድ ለሁለት ዓመት በኢጣልያ፣ ፈረንሳይ፣ እስፓኝ፣ ፖርቱጋል፣ ብሪታንያ እና ግሪክ አገሮች የጠለቀ የኪነ ጥበብ ጥናት አከናወኑ። በተለይም በነኚህ አገሮች ውስጥ በስደት የሚገኙትን የኢትዮጵያ ጥንታዊ ሃይማኖታዊ የብራና መጻሕፍት በጥልቅ አጠኑ። እንዲሁም የመስታወት ስዕል () እና የ’ሞዜይክ’ አሠራርን ጥበብ ተምረው ወደአገራቸው ተመለሱ። በዚህ በሁለተኛ መልሳቸው ንጉሠ ነገሥቱ የመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን በሃይማኖታዊ የግድግዳና ጣሪያ ስዕሎች፣ የ’ሞዜይክ’ ሥራዎች፣ መስኮቶቹንም በመስታወት ስዕሎች እንዲያሳምሩት ቀጥረዋቸው አሁን የምናያቸውን እንደ “የዳግማዊ ምጽአት ፍርድ”፣ የእመቤታችንን ንግሠት የሚያሳየው “ኪዳነ ምሕረት”፣ እና የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን የዘውድ ስርዓት የሚያሳዩ ሥራዎቻቸው ይገኙበታል። አከታትለውም አሁን በሐረር ከተማ የሚገኘውን የልዑል ራስ መኮንንን ሀውልት ሠሩ። የስዕል እና ሌላ የኪን ሥራዎቻቸው ወዲያው በ’ቴምብሮች’፣ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የኪነ ጥበብ ትርዒት ላይ እጅግ በጣም እየታወቁና እየገነኑ መጡ። የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ ማክሰኞ፣ ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም በተወለዱ በ፸፱ ዓመታቸው፤ በቅርብ ባደረባቸው ጽኑ ሕመም በሕክምና እየተረዱ ሳለ በካዲስኮ ሆስፒታል አርፈዋል። የኢትዮጵያ ሰዓሊዎች
8358
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%88%E1%88%A8%E1%8A%95%E1%88%A3%E1%8B%AD
ፈረንሣይ
ፈረንሳይ፣ በይፋ የፈረንሳይ ሪፐብሊክ (ፈረንሳይኛ፡ ሪፐብሊክ ፍራንሣይዝ፣ ምዕራብ አውሮፓን እና የባህር ማዶ ክልሎችን እና በአሜሪካን እና በአትላንቲክ፣ ፓሲፊክ እና ህንድ ውቅያኖሶችን ያቀፈች አህጉር አቋራጭ ሀገር ነች። እና ከሜድትራንያን ባህር እስከ እንግሊዝ ቻናል እና ሰሜናዊ ባህር፤ የባህር ማዶ ግዛቶች በደቡብ አሜሪካ የፈረንሳይ ጊያና፣ በሰሜን አትላንቲክ ውቅያኖስ ሴንት ፒየር እና ሚኬሎን፣ የፈረንሳይ ዌስት ኢንዲስ እና በኦሽንያ እና በህንድ ውቅያኖስ ውስጥ ያሉ ብዙ ደሴቶች ይገኙበታል። በርካታ የባህር ዳርቻ ግዛቶች ፣ ፈረንሳይ በዓለም ላይ ትልቁ ብቸኛ ኢኮኖሚያዊ ቀጠና አላት ። ፈረንሳይ ከቤልጂየም ፣ ሉክሰምበርግ ፣ ጀርመን ፣ ስዊዘርላንድ ፣ ሞናኮ ፣ ጣሊያን ፣ አንድራ እና ስፔን በአውሮፓ እንዲሁም ኔዘርላንድስ ፣ ሱሪናም እና ብራዚል በአሜሪካ ትዋሰናለች። የተዋሃዱ ክልሎች (አምስቱ የባህር ማዶ ናቸው) በድምሩ 643,801 ኪ.ሜ. (248,573 ካሬ ማይል) እና ከ67 ሚሊዮን በላይ ሰዎች (ከግንቦት 2021 ጀምሮ) ይሸፍናሉ። ፈረንሳይ አሃዳዊ ከፊል ነው። -የፕሬዝዳንት ሪፐብሊክ ዋና ከተማ ፓሪስ ውስጥ, የአገሪቱ ትልቁ ከተማ እና ዋና የባህል እና የንግድ ማዕከል; ሌሎች ዋና የከተማ አካባቢዎች ማርሴይ፣ ሊዮን፣ ቱሉዝ፣ ሊል፣ ቦርዶ እና ኒስ ያካትታሉ። ከፓሌኦሊቲክ ዘመን ጀምሮ የሚኖረው፣ የሜትሮፖሊታን ፈረንሳይ ግዛት በብረት ዘመን ጋውልስ በሚባሉ የሴልቲክ ጎሳዎች ተቀምጧል። ሮም አካባቢውን በ51 ከክርስቶስ ልደት በፊት ቀላቀለች፣ ይህም የፈረንሳይ ቋንቋን መሰረት የጣለ ወደ የተለየ የጋሎ-ሮማን ባህል አመራ። ጀርመናዊው ፍራንካውያን የፍራንሢያ መንግሥት አቋቋሙ፣ እሱም የካሮሊንግያን ኢምፓየር ዋና ከተማ ሆነ። የ843ቱ የቨርዱን ስምምነት ኢምፓየርን ከፍሎ ምዕራብ ፍራንሢያ በ987 የፈረንሳይ መንግሥት ሆነች። በከፍተኛ መካከለኛው ዘመን ፈረንሳይ ኃይለኛ ነገር ግን ከፍተኛ ያልተማከለ የፊውዳል መንግሥት ነበረች። ፊሊፕ የንጉሣዊ ኃይልን በተሳካ ሁኔታ አጠናክሮ እና ተቀናቃኞቹን የዘውድ አገሮችን በእጥፍ በማሸነፍ; በንግሥናው መገባደጃ ላይ ፈረንሳይ በአውሮፓ ውስጥ እጅግ በጣም ኃያል መንግሥት ሆና ብቅ አለች ። ከ14ኛው አጋማሽ እስከ 15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ ፈረንሳይ በእንግሊዝ ወደተከታታይ የስርወ-መንግስት ግጭቶች ገባች፣በጥቅሉ የመቶ አመት ጦርነት እየተባለ የሚጠራ ሲሆን በውጤቱም የተለየ የፈረንሳይ ማንነት ተፈጠረ። የፈረንሣይ ህዳሴ ጥበብ እና ባህል ሲያብብ፣ ከሀብስበርግ ቤት ጋር ግጭት እና ዓለም አቀፋዊ የቅኝ ግዛት ግዛት መመስረት፣ በ20ኛው ክፍለ ዘመን በዓለም ላይ ሁለተኛው ትልቁ ይሆናል። ሀገሪቱን ክፉኛ ያዳከሙ በካቶሊኮች እና በሁጉኖቶች መካከል የተደረጉ ሃይማኖታዊ የእርስ በርስ ጦርነቶች። የሰላሳ አመት ጦርነትን ተከትሎ ፈረንሳይ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሉዊ አሥራ አራተኛ ጊዜ የአውሮፓ የበላይ ሀገር ሆና ብቅ አለች ። በቂ ያልሆነ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ፣ ኢፍትሃዊ ግብሮች እና ተደጋጋሚ ጦርነቶች (በተለይ በሰባት ዓመታት ጦርነት ውስጥ ሽንፈት እና በአሜሪካ የነፃነት ጦርነት ውስጥ ብዙ ውድ ተሳትፎ) በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ መንግሥቱን አሳሳቢ በሆነ የኢኮኖሚ ሁኔታ ውስጥ ትቷታል። ይህም የ1789 የፈረንሳይ አብዮት አፋፍሟል፣ የአንሲየን አገዛዝን ገልብጦ የሰው መብቶች መግለጫን አዘጋጅቶ እስከ ዛሬ ድረስ የአገሪቱን እሳቤዎች ይገልፃል።ፈረንሳይ በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ በናፖሊዮን ቦናፓርት ስር በፖለቲካ እና በወታደራዊ ደረጃ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሳ አብዛኛው አህጉራዊ አውሮፓን በመግዛት የመጀመሪያውን የፈረንሳይ ኢምፓየር መሰረተች። የፈረንሳይ አብዮታዊ እና የናፖሊዮን ጦርነቶች የአውሮፓ እና የአለም ታሪክን ሂደት ቀርፀዋል። የግዛቱ ውድቀት በ1870 በፍራንኮ ፕሩሺያን ጦርነት ወቅት የፈረንሳይ ሶስተኛ ሪፐብሊክ እስኪመሰረት ድረስ ብዙ መንግስታትን ያሳለፈችበት አንፃራዊ ውድቀት የጀመረበት ወቅት ነበር። በቀጣዮቹ አሥርተ ዓመታት ብሩህ ተስፋ፣ የባህልና ሳይንሳዊ እድገት አሳይቷል። , እንዲሁም ቤሌ ኤፖክ በመባል የሚታወቀው ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና. ፈረንሣይ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ትልቅ ተሳታፊ ከነበሩት መካከል አንዷ ነበረች፣ ከዚም ትልቅ የሰውና የኢኮኖሚ ውድመት አስከፍላለች። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ከተባበሩት መንግስታት መካከል ነበረች ፣ ግን ብዙም ሳይቆይ በ 1940 በአክሲስ ተያዘ ። በ 1944 ነፃ ከወጣች በኋላ ፣ ለአጭር ጊዜ የቆየው አራተኛው ሪፐብሊክ ተመሠረተ እና በኋላም በአልጄሪያ ጦርነት ሂደት ፈረሰች። የአሁኑ አምስተኛው ሪፐብሊክ በ 1958 በቻርለስ ደ ጎል ተመሠረተ። አልጄሪያ እና አብዛኛው የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች በ1960ዎቹ ነጻ ወጡ፣ አብዛኛዎቹ ከፈረንሳይ ጋር የጠበቀ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ግንኙነት ነበራቸው። ፈረንሳይ እንደ ዓለም አቀፋዊ የሥነ ጥበብ፣ የሳይንስ እና የፍልስፍና ማዕከል ለዘመናት የዘለቀውን ደረጃዋን እንደያዘች ቆይታለች። በ2018 ከ89 ሚሊዮን በላይ የውጭ ሀገር ጎብኝዎችን በመቀበል በአለም ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ነች። ፈረንሳይ በስም በአለም ሰባተኛ ኢኮኖሚ ያላት እና ዘጠነኛዋ በፒ.ፒ.ፒ. ; ከአጠቃላይ የቤት ሀብት አንፃር በዓለም አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ፈረንሳይ በአለም አቀፍ የትምህርት፣ የጤና እንክብካቤ፣ የህይወት ዘመን እና የሰው ልጅ እድገት ደረጃዎች ጥሩ ትሰራለች። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ከአምስቱ ቋሚ አባላት እና ይፋዊ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ሀገር በመሆኗ በአለም አቀፍ ጉዳዮች ታላቅ ሃይል ሆና ቆይታለች። ፈረንሳይ የአውሮፓ ህብረት እና የዩሮ ዞን መስራች እና ግንባር ቀደም አባል ነች እንዲሁም የቡድን ሰባት ፣ የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ፣ የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ድርጅት () እና ላ ፍራንኮፎኒ ቁልፍ አባል ነች። ሥርወ ቃል እና አነባበብ መጀመሪያ ላይ ለመላው የፍራንካውያን ግዛት የተተገበረው ፈረንሳይ የሚለው ስም የመጣው ከላቲን ፍራንሢያ ወይም "የፍራንካውያን ግዛት" ነው። የአሁኗ ፈረንሳይ ዛሬም ፍራንሲያ በጣሊያንኛ እና በስፓኒሽ እየተሰየመች ስትጠራ በጀርመን ፍራንክሪች፣ ፍራንክሪክ በኔዘርላንድስ እና በስዊድን ፍራንክሪክ ሁሉም ትርጉማቸው "የፍራንካውያን ምድር/ግዛት" ማለት ነው። የፍራንካውያን ስም ፍራንክ ከሚለው የእንግሊዝኛ ቃል ጋር ይዛመዳል ("ነጻ")፡ የኋለኛው ግን ከድሮው የፈረንሳይ ፍራንክ ("ነጻ፣ ክቡር፣ ቅን")፣ በመጨረሻም ከመካከለኛውቫል ላቲን ፍራንከስ ("ነጻ፣ ከአገልግሎት ነፃ፣ ነፃ ሰው") , ፍራንክ")፣ የጎሳ ስም ጠቅለል ያለ የላቲን መበደር እንደገና የተገነባውን የፍራንካውያን ኢንዶኒም * ፍራንክ። “ነጻ” የሚለው ፍቺ ተቀባይነት ያገኘው ከጎል ወረራ በኋላ ፍራንካውያን ብቻ ከቀረጥ ነፃ ስለነበሩ ወይም በአጠቃላይ ከአገልጋዮች ወይም ከባሪያዎች በተቃራኒ የነጻነት ደረጃ ስለነበራቸው ነው። የ*ፍራንክ ሥርወ-ቃል እርግጠኛ አይደለም። በተለምዶ የተወሰደው *ፍራንኮን ከሚለው ፕሮቶ-ጀርመንኛ ቃል ሲሆን እሱም "ጃቪሊን" ወይም "ላንስ" ተብሎ ይተረጎማል (የፍራንካውያን መወርወሪያ መጥረቢያ ፍራንሲስካ ተብሎ ይጠራ ነበር) ምንም እንኳን እነዚህ የጦር መሳሪያዎች በስም የተጠሩበት ምክንያት በ ፍራንኮች, በተቃራኒው አይደለም. በእንግሊዘኛ 'ፈረንሳይ' በአሜሪካ እንግሊዝኛ / እና / ወይም / በብሪቲሽ እንግሊዝኛ ይጠራሉ። ከ // ጋር ያለው አነጋገር በአብዛኛው የተመካው እንደ የተቀበለው አጠራር ባሉ የወጥመዱ መታጠቢያ ክፍልፋዮች ላይ ነው፣ ምንም እንኳን በሌሎች እንደ ካርዲፍ እንግሊዝኛ ባሉ ቀበሌኛዎችም ሊሰማ ይችላል፣ ይህም // ከ// ጋር በነጻ የሚለዋወጥ ነው። . በ 4 ኛው እና በ 3 ኛው ሺህ ዓመታት መካከል ከጠንካራ የስነ-ሕዝብ እና የግብርና ልማት በኋላ ፣ ሜታሎሎጂ በ 3 ኛው ሺህ ዓመት መጨረሻ ላይ ታየ ፣ መጀመሪያ ላይ ወርቅ ፣ መዳብ እና ነሐስ እንዲሁም በኋላ ብረት ይሠራል። ፈረንሳይ ከኒዮሊቲክ ዘመን ጀምሮ በርካታ ቦታዎች አሏት፣ ልዩ የሆነ ጥቅጥቅ ያለ የካርናክ ድንጋይ ቦታ (በግምት 3,300 ዓክልበ. ግድም)። ጥንታዊነት (ከክርስቶስ ልደት በፊት 6 - 5 ኛ ክፍለ ዘመን ዓ.ም.) በ600 ዓክልበ. በሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ላይ፣ የፎኬያ አዮኒያውያን ግሪኮች የማሳሊያ (የአሁኗ ማርሴይ) ቅኝ ግዛት መሰረቱ። ይህም የፈረንሳይ ጥንታዊ ከተማ ያደርጋታል። በተመሳሳይ ጊዜ፣ አንዳንድ የጋሊክ ሴልቲክ ጎሳዎች የምስራቅ እና ሰሜናዊ ፈረንሳይን ክፍሎች ዘልቀው ገቡ፣ ቀስ በቀስ በቀሪው የሀገሪቱ ክፍል በ5ኛው እና በ3ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. የጎል ጽንሰ-ሀሳብ የወጣው በዚህ ወቅት ሲሆን በራይን ፣ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ፣ በፒሬኒስ እና በሜዲትራኒያን መካከል ካሉት የሴልቲክ ሰፈራ ግዛቶች ጋር ይዛመዳል። የዘመናዊቷ ፈረንሳይ ድንበሮች በሴልቲክ ጋውልስ ይኖሩ ከነበረው ከጥንት ጋውል ጋር ይመሳሰላል። ጎል ያኔ የበለጸገች አገር ነበረች፣ ከዚም ውስጥ ደቡባዊው ክፍል ለግሪክ እና ሮማውያን ባህላዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጽእኖዎች በጣም ተገዥ ነበር።በ390 ዓክልበ. አካባቢ፣ የጋሊካዊው አለቃ ብሬኑስ እና ወታደሮቹ በአልፕስ ተራሮች በኩል ወደ ኢጣሊያ አቀኑ፣ ሮማውያንን በአሊያ ጦርነት አሸንፈው ሮምን ከበቡ እና ገዙ። የጋሊክስ ወረራ ሮም እንዲዳከም አድርጎታል፣ እና ጋውልስ እስከ 345 ዓክልበ. ከሮም ጋር መደበኛ የሰላም ስምምነት ሲያደርጉ አካባቢውን ማዋከብ ቀጠሉ። ነገር ግን ሮማውያን እና ጋውልቶች ለቀጣዮቹ መቶ ዘመናት ባላንጣ ሆነው ይቆያሉ, እናም ጋልስ በጣሊያን ውስጥ ስጋት ሆነው ይቀጥላሉ. በ125 ዓክልበ. አካባቢ፣ የጎል ደቡብ በሮማውያን ተቆጣጠረ፣ ይህንን ክልል ፕሮቪንሺያ ኖስታራ ("የእኛ ግዛት") ብለው ይጠሩታል፣ እሱም ከጊዜ በኋላ በፈረንሳይኛ ፕሮቨንስ ወደሚለው ስም ተለወጠ። ጁሊየስ ቄሳር የጎል ቀሪዎችን ድል አደረገ እና በ 52 ዓክልበ. በጋሊክ አለቃ ቬርሲንቶሪክስ የተካሄደውን አመጽ አሸንፏል። ጋውል በአውግስጦስ ተከፍሎ ወደ ሮማውያን ግዛቶች ተከፋፍሏል። ብዙ ከተሞች የተመሰረቱት በጋሎ-ሮማን ዘመን ሲሆን እነዚህም ሉግዱኑም (የአሁኗ ሊዮን) የጋልስ ዋና ከተማ እንደሆነች ተደርጋለች።እነዚህ ከተሞች የተገነቡት በባህላዊ የሮማውያን ዘይቤ፣ መድረክ፣ ቲያትር፣ ሰርከስ፣ አምፊቲያትር ነው። እና የሙቀት መታጠቢያዎች. ጋውልስ ከሮማውያን ሰፋሪዎች ጋር በመደባለቅ የሮማን ባህል እና የሮማን ንግግር (ላቲን፣ የፈረንሳይ ቋንቋ የተፈጠረበት) ወሰዱ። የሮማውያን ፖሊቲዝም ከጋሊካዊ ጣዖት አምልኮ ጋር ወደ ተመሳሳይ ተመሳሳይነት ተቀላቀለ። ከ 250 ዎቹ እስከ 280 ዎቹ ዓ.ም.፣ ሮማን ጋውል የተመሸጉ ድንበሯን በተለያዩ አጋጣሚዎች በአረመኔዎች ጥቃት በመፈፀሙ ከባድ ችግር አጋጠመው። ቢሆንም, ሁኔታው ​​በ 4 ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ ተሻሽሏል, እሱም ለሮማን ጎል የመነቃቃት እና የብልጽግና ጊዜ ነበር. በ 312 ንጉሠ ነገሥት ቆስጠንጢኖስ 1ኛ ወደ ክርስትና ተለወጠ. በመቀጠልም እስከዚያ ድረስ ስደት ሲደርስባቸው የነበሩት ክርስቲያኖች በመላው የሮም ግዛት በፍጥነት ጨመሩ። ነገር ግን ከ 5 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ጀምሮ የባርባሪያን ወረራዎች እንደገና ጀመሩ ። የቴውቶኒክ ጎሳዎች ክልሉን ከዛሬ ጀርመን ወረሩ ፣ ቪሲጎቶች በደቡብ ምዕራብ ፣ በርገንዲያን በራይን ወንዝ ሸለቆ አጠገብ ፣ እና ፍራንኮች (ፈረንሳዮች የወሰዱት) ስማቸው) በሰሜን የመካከለኛው ዘመን መጀመሪያ (5 ኛ-10 ኛ ክፍለ ዘመን) በጥንታዊው ዘመን መገባደጃ ላይ፣ የጥንት ጎል ወደ በርካታ የጀርመን መንግስታት እና የቀረው የጋሎ-ሮማን ግዛት ተከፋፍሎ ነበር፣ እሱም የሲያግሪየስ መንግሥት በመባል ይታወቃል። በተመሳሳይ የሴልቲክ ብሪታኖች ከብሪታንያ የአንግሎ-ሳክሰን ሰፈር ሸሽተው የርሞሪካን ምዕራባዊ ክፍል ሰፈሩ። በውጤቱም፣ የአርሞሪካን ባሕረ ገብ መሬት ብሪትኒ ተብሎ ተሰየመ፣ የሴልቲክ ባህል ታድሷል እና በዚህ ክልል ውስጥ ገለልተኛ ትናንሽ መንግስታት ተነሱ። ራሱን በሁሉም የፍራንካውያን ንጉሥ ያደረገው የመጀመሪያው መሪ ክሎቪስ ቀዳማዊ ሲሆን በ481 ንግሥናውን የጀመረው በ486 የሮማውያን ገዥዎችን የመጨረሻውን ጦር በመምራት ግዛቱን የጀመረው በ486 ነው። በቪሲጎቶች ላይ ድል ለጦርነቱ ዋስትና ነበር ተብሎ ይነገርለታል። ክሎቪስ ከቪሲጎቶች ወደ ደቡብ ምዕራብ ተመለሰ፣ በ508 ተጠመቀ እና ራሱን አሁን ምዕራብ ጀርመን የሚባለውን ግዛት ዋና አድርጎ ሠራ። ክሎቪስ 1ኛ ከአሪያኒዝም ይልቅ ወደ ካቶሊክ ክርስትና የተሸጋገረ ከሮማ ግዛት ውድቀት በኋላ የመጀመሪያው ጀርመናዊ ድል አድራጊ ነበር። ስለዚህም ፈረንሳይ በጳጳሱ “የቤተ ክርስቲያን ትልቋ ሴት ልጅ” ( ፈረንሣይኛ፡ ላ ፊሌ አይነኤ ደ ላግሊዝ ) የሚል ማዕረግ ተሰጥቷታል፣ የፈረንሣይ ነገሥታት ደግሞ “የፈረንሳይ የክርስቲያን ነገሥታት ሁሉ” (ሬክስ ክርስቲያንሲመስ) ይባላሉ።ፍራንካውያን የክርስቲያኑን የጋሎ-ሮማን ባህል ተቀብለው የጥንት ጎል በመጨረሻ ፍራንሲያ (የፍራንካውያን ምድር) ተባለ። ጀርመናዊው ፍራንካውያን የሮማን ቋንቋዎችን ተቀበሉ፣ ከሰሜን ጎል በስተቀር የሮማውያን ሰፈሮች ብዙም ያልበዙበት እና የጀርመን ቋንቋዎች ብቅ ካሉበት። ክሎቪስ ዋና ከተማው ፓሪስ አደረገ እና የሜሮቪንጊን ሥርወ መንግሥት አቋቋመ ፣ ግን መንግሥቱ ከሞቱ በሕይወት ሊተርፍ አልቻለም። ፍራንካውያን መሬትን እንደ ግል ይዞታ በመመልከት ለወራሾቻቸው ከፋፍለው ስለነበር ከክሎቪስ ፓሪስ፣ ኦርሌንስ፣ ሶይስሰንስ እና ሬይምስ አራት መንግሥታት መጡ። የመጨረሻዎቹ የሜሮቪንግያን ነገሥታት በቤተ መንግሥት ከንቲባዎቻቸው (የቤተሰብ አስተዳዳሪ) ሥልጣናቸውን አጥተዋል። አንደኛው የቤተ መንግሥቱ ከንቲባ ቻርለስ ማርቴል በቱሪስ ጦርነት የጋውልን እስላማዊ ወረራ በማሸነፍ በፍራንካውያን መንግስታት ውስጥ ክብር እና ስልጣንን አግኝቷል። ልጁ ፔፒን ዘ ሾርት፣ ከተዳከሙት ሜሮቪንግያውያን የፍራንሢያን ዘውድ ነጥቆ የካሮሊንያን ሥርወ መንግሥት መሠረተ። የፔፒን ልጅ ሻርለማኝ የፍራንካውያንን መንግስታት አገናኘ እና በምዕራብ እና መካከለኛው አውሮፓ ሰፊ ግዛት ገነባ። በሊቀ ጳጳስ ሊዮ ሳልሳዊ የቅዱስ ሮማ ንጉሠ ነገሥት ተብሎ የተነገረው እና የፈረንሳይ መንግሥት ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጋር የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ትስስርን በቅንነት በማቋቋም ሻርለማኝ የምዕራቡን ሮማን ግዛት እና የባህል ታላቅነቱን ለማደስ ሞክሯል። የቻርለማኝ ልጅ፣ ሉዊስ 1 (ንጉሠ ነገሥት 814–840)፣ ግዛቱን አንድ አድርጎ ጠበቀ። ሆኖም፣ ይህ የካሮሊንግ ግዛት ከሞቱ አይተርፍም። እ.ኤ.አ. በ 843 ፣ በቨርዱን ስምምነት ፣ ኢምፓየር በሉዊስ ሶስት ልጆች ተከፈለ ፣ ምስራቅ ፍራንሢያ ወደ ጀርመናዊው ሉዊስ ፣ መካከለኛው ፍራንሢያ ወደ ሎተየር 1 ፣ እና ምዕራብ ፍራንሢያ ወደ ቻርለስ ዘ ባልድ። ምዕራብ ፍራንሢያ የተያዘውን አካባቢ ገምግሟል - እና የዘመናዊቷ ፈረንሳይ ቀዳሚ ነበር። በ9ኛው እና በ10ኛው መቶ ክፍለ ዘመን፣ በቫይኪንግ ወረራ ያለማቋረጥ ስጋት ውስጥ ገብታ፣ ፈረንሳይ በጣም ያልተማከለ መንግስት ሆነች፡ የመኳንንቱ የማዕረግ ስሞች እና መሬቶች በዘር የሚተላለፍ ሆኑ፣ እናም የንጉሱ ስልጣን ከዓለማዊው ይልቅ ሃይማኖተኛ እየሆነ ስለመጣ ውጤታማነቱ አናሳ እና በኃያላን መኳንንት የማያቋርጥ ፈተና ነበር። . ስለዚህ ፊውዳሊዝም በፈረንሳይ ተቋቋመ። ከጊዜ በኋላ አንዳንድ የንጉሥ ሎሌዎች በጣም ኃይለኛ ስለሚሆኑ ብዙ ጊዜ ንጉሡን አስጊ ሆኑ። ለምሳሌ፣ በ1066 ከሄስቲንግስ ጦርነት በኋላ፣ ዊልያም አሸናፊው “የእንግሊዝ ንጉስ”ን በማዕረጉ ላይ ጨምሯል። ተደጋጋሚ ጭንቀቶችን መፍጠር. ከፍተኛ እና ዘግይቶ መካከለኛው ዘመን (10-15 ኛው ክፍለ ዘመን) የ ሥርወ መንግሥት እስከ 987 ድረስ ፈረንሳይን ይገዛ ነበር፣ የፈረንሣይ መስፍን እና የፓሪስ ቆጠራው ሁው ካፔት የፍራንካውያን ንጉሥ ዘውድ እስከ ተቀበሉበት ጊዜ ድረስ። ዘሮቹ - የኬፕቲያውያን፣ የቫሎይስ ቤት እና የቡርቦን ቤት - በጦርነት እና በሥርወ-መንግሥት ርስት አገሪቱን በሂደት አንድ አድርገው ወደ ፈረንሣይ መንግሥት ገቡ፣ ይህም በ 1190 በፈረንሳዩ ፊሊፕ (ፊሊፕ ኦገስት) ሙሉ በሙሉ የታወጀው። የኋለኞቹ ነገሥታት በ15ኛው ክፍለ ዘመን አብዛኛው ሰሜናዊ፣ መሃል እና ምዕራብ ፈረንሳይን ጨምሮ ከዘመናዊው አህጉር ፈረንሳይ ከግማሽ በላይ የሚሸፍነውን ንጉሣዊ ሥልጣናቸውን ያስፋፋሉ። በዚህ ሂደት ውስጥ፣ የንጉሣዊው ሥልጣን በተዋረድ የተፀነሰውን ባላባቶችን፣ ቀሳውስትን እና ተራዎችን የሚለይ ማኅበረሰብ ላይ ያተኮረ ቆራጥ እየሆነ መጣ። የፈረንሣይ መኳንንት የክርስቲያኖች ወደ ቅድስት ሀገር መዳረሻ ለመመለስ በአብዛኛዎቹ የመስቀል ጦርነት ጉልህ ሚና ተጫውተዋል። በሁለት መቶ ዓመታት የመስቀል ጦርነት ጊዜ ውስጥ ከቋሚው የማጠናከሪያ ፍሰት ትልቁን የፈረንሣይ ባላባት የሠሩት በዚህ ዓይነት መልኩ አረቦች የመስቀል ጦሩን በአንድ ወጥ በሆነ መንገድ ፍራንጅ ብለው ይጠሩዋቸው ነበር፤ በእርግጥ ከፈረንሳይ የመጡ ናቸው አይመጡም። የፈረንሣይ ክሩሴደሮችም የፈረንሳይ ቋንቋን ወደ ሌቫንት በማስመጣት ፈረንሳይኛ የመስቀል ደርድር ግዛቶች የቋንቋ ፍራንካ መሠረት አድርጎታል። በሆስፒታሉም ሆነ በቤተመቅደሱ ትእዛዝ ውስጥ የፈረንሣይ ባላባቶች በብዛት ይገኙ ነበር። ፊልጶስ አራተኛ በ1307 ትእዛዙን እስኪያጠፋ ድረስ በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የፈረንሳይ ዘውድ ዋና ባንኮች ነበሩ።የአልቢጀንሲያን ክሩሴድ በ1209 በደቡብ ምዕራብ አካባቢ ያሉትን መናፍቃን ካታርስ ለማጥፋት ተጀመረ። የዘመናዊቷ ፈረንሳይ. በመጨረሻ፣ ካታርስ ተደምስሰው የቱሉዝ አውራጃ የራስ ገዝ አስተዳደር ወደ ፈረንሳይ ዘውድ ምድር ተቀላቀለ። ከ 11 ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የፕላንታገነት ቤት ፣ የአንጁ ካውንቲ ገዥዎች በሜይን እና ቱሬይን አውራጃዎች ላይ ግዛቱን በማቋቋም ቀስ በቀስ ከእንግሊዝ እስከ ፒሬኒስ ድረስ የሚሸፍን እና ግማሹን የሚሸፍን “ኢምፓየር” ገነባ። ዘመናዊ ፈረንሳይ. በ1202 እና 1214 የፈረንሳዩ ዳግማዊ ፊሊፕ እስኪያሸንፍ ድረስ በፈረንሣይ መንግሥት እና በፕላንታገነት ግዛት መካከል ያለው ውጥረት ለመቶ ዓመታት የሚቆይ ሲሆን ከ1202 እስከ 1214 ባለው ጊዜ ውስጥ አብዛኞቹን የግዛቱ አህጉራዊ ንብረቶች እንግሊዝን እና አኲቴይንን ወደ ፕላንታጄኔቶች በመተው። የቡቪንስ ጦርነትን ተከትሎ። ቻርለስ ትርኢቱ ያለ ወራሽ በ 1328 ሞተ ። በሳሊክ ህግ ህጎች የፈረንሳይ ዘውድ ወደ ሴት ሊተላለፍ አይችልም ፣ የንግሥና መስመር በሴት መስመር ውስጥ ማለፍ አይችልም። በዚህ መሠረት ዘውዱ በሴት መስመር በኩል ወደ ፕላንታገነት ኤድዋርድ ከመሄድ ይልቅ በቅርቡ የእንግሊዙ ኤድዋርድ ሳልሳዊ ይሆናል። በቫሎይስ ፊሊፕ የግዛት ዘመን የፈረንሳይ ንጉሳዊ አገዛዝ የመካከለኛው ዘመን ስልጣኑን ከፍታ ላይ ደርሷል. ሆኖም የፊሊፕ ዙፋን ላይ የተቀመጠው በ1337 በእንግሊዙ ኤድዋርድ ሳልሳዊ ተወዳድሮ ነበር፣ እና እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ከመቶ አመት በፊት ጦርነት ውስጥ ገቡ። ትክክለኛው ድንበሮች በጊዜ ሂደት በጣም ተለውጠዋል፣ ነገር ግን በፈረንሳይ ውስጥ በእንግሊዝ ነገሥታት የተያዙ የመሬት ይዞታዎች ለአሥርተ ዓመታት ሰፊ ሆነው ቆይተዋል። እንደ ጆአን ኦፍ አርክ እና ላ ሂር ካሉ የካሪዝማቲክ መሪዎች ጋር ጠንካራ የፈረንሳይ መልሶ ማጥቃት አብዛኛዎቹን የእንግሊዝ አህጉራዊ ግዛቶች አሸንፈዋል። ልክ እንደሌሎች አውሮፓውያን ፈረንሳይ በጥቁር ሞት ተመታ; ከ17 ሚሊዮን የፈረንሳይ ህዝብ ግማሹ ሞቷል። ቀደምት ዘመናዊ ጊዜ (15 ኛው ክፍለ ዘመን-1789) - አውሮፓውያን የፈረንሣይ ህዳሴ አስደናቂ የባህል እድገት እና የፈረንሳይ ቋንቋ የመጀመሪያ ደረጃ ታይቷል ፣ እሱም የፈረንሳይ ኦፊሴላዊ ቋንቋ እና የአውሮፓ መኳንንት ቋንቋ ይሆናል። በፈረንሳይ እና በሃብስበርግ ቤት መካከል የጣሊያን ጦርነቶች በመባል የሚታወቁት ረጅም ጦርነቶችን ታይቷል። እንደ ዣክ ካርቲር ወይም ሳሙኤል ዴ ቻምፕሊን ያሉ የፈረንሣይ አሳሾች ለፈረንሣይ አሜሪካን ምድር ይገባሉ፣ ይህም ለመጀመሪያው የፈረንሳይ ቅኝ ግዛት መስፋፋት መንገዱን ጠርጓል። በአውሮፓ የፕሮቴስታንት እምነት መጨመር ፈረንሳይን የፈረንሳይ የሃይማኖት ጦርነቶች ወደሚባል የእርስ በርስ ጦርነት አመራ።በ1572 በሴንት ባርቶሎሜዎስ ቀን በተካሄደው የቅዱስ ባርቶሎሜዎስ ቀን እልቂት በሺዎች የሚቆጠሩ ሁጉኖቶች ተገድለዋል።የሃይማኖት ጦርነቶች አብቅተዋል። ለሂጉኖቶች የተወሰነ የሃይማኖት ነፃነት የሰጠው የናንቴስ የሄንሪ አራተኛ አዋጅ። የስፔን ወታደሮች፣ የምእራብ አውሮፓ ሽብር፣ በ1589-1594 በሃይማኖት ጦርነት ወቅት የካቶሊክን ወገን ረድተው በ1597 ሰሜናዊ ፈረንሳይን ወረሩ። በ1620ዎቹ እና 1630ዎቹ ከተወሰኑ ግጭቶች በኋላ ስፔንና ፈረንሳይ ከ1635 እስከ 1659 ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ ሁለገብ ጦርነት ተመለሱ። ጦርነቱ ፈረንሳይን 300,000 ቆስሏል። በሉዊ ዘመን፣ ብርቱው ካርዲናል ሪቼሊዩ በ1620ዎቹ የሀገር ውስጥ ሃይል ባለቤቶችን ትጥቅ በማስፈታት የመንግስትን ማእከላዊነት በማስተዋወቅ የንጉሳዊ ሃይሉን አጠናከረ። የጌቶችን ግንብ ስልታዊ በሆነ መንገድ አፈራርሷል እና የግል ጥቃትን (ማደብዘዝ፣ መሳሪያ መያዝ እና የግል ጦር ማቆየትን) አውግዟል። እ.ኤ.አ. በ1620ዎቹ መገባደጃ ላይ ሪቼሌዩ እንደ አስተምህሮው “የኃይል ንጉሣዊ ሞኖፖሊ” አቋቋመ። በሉዊ አሥራ አራተኛ አናሳ እና በንግስት አን እና በካርዲናል ማዛሪን የግዛት ዘመን፣ ፍሮንዴ ተብሎ የሚጠራው የችግር ጊዜ በፈረንሳይ ተከስቷል። ይህ አመጽ በፈረንሣይ የንጉሣዊ ፍፁም ሥልጣን መነሳት ምላሽ ሆኖ በታላላቅ ፊውዳል ገዥዎች እና ሉዓላዊ ፍርድ ቤቶች ተንቀሳቅሷል።ንጉሣዊው ሥርዓት ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰው በ17ኛው ክፍለ ዘመን እና በሉዊ አሥራ አራተኛ የግዛት ዘመን ነው። በቬርሳይ ቤተ መንግሥት ኃያላን ፊውዳል ገዥዎችን ወደ ቤተ መንግሥት በመቀየር የሉዊ አሥራ አራተኛ ግላዊ ሥልጣን አልተገዳደረም። ባደረጋቸው በርካታ ጦርነቶች ሲታወስ፣ ፈረንሳይን የአውሮፓ መሪ አድርጓታል። ፈረንሳይ በአውሮፓ ውስጥ በሕዝብ ብዛት የምትገኝ አገር ሆና በአውሮፓ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ እና ባህል ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳደረች። ፈረንሳይኛ በዲፕሎማሲ፣ በሳይንስ፣ በሥነ ጽሑፍ እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች በብዛት ጥቅም ላይ የዋለ ቋንቋ ሆኖ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ቆይቷል። ፈረንሳይ በአሜሪካ፣ በአፍሪካ እና በእስያ ብዙ የባህር ማዶ ሀብት አግኝታለች። ሉዊ አሥራ አራተኛም የናንተስን አዋጅ በመሻር በሺዎች የሚቆጠሩ ሁጉኖቶች በግዞት እንዲሰደዱ አስገደዳቸው። በሉዊስ ጦርነት (አር. 1715–1774) ፈረንሳይ በሰባት አመት ጦርነት ከተሸነፈች በኋላ አዲሲቷን ፈረንሳይ እና አብዛኛዎቹ የህንድ ንብረቶቿን አጥታለች። እንደ ሎሬይን እና ኮርሲካ ባሉ ታዋቂ ግዢዎች የአውሮፓ ግዛቷ እያደገ ሄደ። በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው ንጉሥ፣ የሉዊስ 15ኛው ደካማ አገዛዝ፣ ያልተማከረው የገንዘብ፣ የፖለቲካ እና የወታደራዊ ውሳኔዎች እንዲሁም የቤተ መንግሥት መዘባረቅ ንጉሣዊውን ሥርዓት አጣጥለውታል፣ ይህም ከሞተ ከ15 ዓመታት በኋላ ለፈረንሣይ አብዮት መንገድ ጠርጓል። ሉዊስ 16ኛ (አር. 1774–1793)፣ አሜሪካውያንን በገንዘብ፣ መርከቦች እና ጦር ኃይሎች በንቃት በመደገፍ ከታላቋ ብሪታንያ ነፃነታቸውን እንዲያሸንፉ ረድቷቸዋል። ፈረንሳይ የበቀል እርምጃ ወሰደች ነገር ግን ብዙ ወጪ በማውጣት መንግስት ለኪሳራ ተዳረገ።ይህም ለፈረንሳይ አብዮት አስተዋጽኦ አድርጓል። አብዛኛው መገለጥ በፈረንሣይ ምሁራዊ ክበቦች ውስጥ የተከሰተ ሲሆን ዋና ዋና ሳይንሳዊ ግኝቶች እና ግኝቶች እንደ ኦክሲጅን እና ተሳፋሪዎችን የሚጭን የመጀመሪያው የአየር ፊኛ ያሉ በፈረንሣይ ሳይንቲስቶች የተገኙ ናቸው። እንደ ቡገንቪል እና ላፔሮሴ ያሉ የፈረንሣይ አሳሾች በዓለም ዙሪያ በተደረጉ የባህር ጉዞዎች በሳይንሳዊ ፍለጋ ጉዞዎች ተሳትፈዋል። የእውቀት () ፍልስፍና እንደ ቀዳሚ የሕጋዊነት ምንጭ ሆኖ የሚመከርበት፣ የንጉሣዊውን ሥርዓት ኃይል እና ድጋፍ ያጎድፋል እንዲሁም ለፈረንሣይ አብዮት ምክንያት ነበር። አብዮታዊ ፈረንሳይ - አውሮፓ የፋይናንስ ችግር እያጋጠመው፣ ንጉስ ሉዊስ 16ኛ ለመንግስት የመፍትሄ ሃሳቦችን ለማቅረብ በሜይ 1789 የስቴት ጄኔራልን (የግዛቱን ሶስት ግዛቶች መሰብሰብ) ጠራ። ችግር ውስጥ በመግባቱ የሶስተኛው እስቴት ተወካዮች የፈረንሳይ አብዮት መፈንዳቱን የሚያመላክት ብሔራዊ ምክር ቤት አቋቋሙ። ንጉሱ አዲስ የተፈጠረውን ብሄራዊ ምክር ቤት ያፍነዋል ብለው በመፍራት ጁላይ 14 ቀን 1789 ዓ.ም አማፂዎች ባስቲልን ወረሩ፣ ይህ ቀን የፈረንሳይ ብሄራዊ ቀን ይሆናል። እ.ኤ.አ. በነሀሴ 1789 መጀመሪያ ላይ የብሔራዊ ሕገ-መንግሥታዊ ምክር ቤት የመኳንንቱን መብቶች እንደ ግላዊ ሰርፍም እና ልዩ የአደን መብቶችን አጠፋ። የሰው እና የዜጎች መብቶች መግለጫ (ነሐሴ 27 ቀን 1789) ፈረንሳይ ለወንዶች መሠረታዊ መብቶችን አቋቋመች። መግለጫው "የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ እና የማይገለጽ መብቶች" "ነፃነት, ንብረት, ደህንነት እና ጭቆናን የመቋቋም" ያረጋግጣል. የመናገር እና የፕሬስ ነፃነት የታወጀ ሲሆን በዘፈቀደ እስራት በህግ የተከለከለ ነው። ባላባታዊ መብቶች እንዲወድሙና ነፃነትና ለሁሉም እኩል መብት እንዲከበር፣ እንዲሁም ከመወለድ ይልቅ በችሎታ ላይ የተመሰረተ የመንግሥት አገልግሎት ማግኘት እንዳለበት አሳውቋል። በኖቬምበር 1789 ጉባኤው በሀገሪቱ ውስጥ ትልቁ የመሬት ባለቤት የሆነውን የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንን ንብረት በሙሉ ለመሸጥ እና ለመሸጥ ወሰነ። በጁላይ 1790 የቄስ ሲቪል ሕገ መንግሥት የፈረንሳይ ካቶሊክ ቤተክርስቲያንን እንደገና በማደራጀት የቤተክርስቲያኑ ግብር የመጣል ስልጣንን በመሰረዝ ወዘተ. ይህ በአንዳንድ የፈረንሳይ ክፍሎች ብዙ ብስጭት እንዲፈጠር አድርጓል፣ ይህ ደግሞ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ለሚቀጣጠለው የእርስ በርስ ጦርነት አስተዋጽኦ አድርጓል። ንጉስ ሉዊስ 16ኛ አሁንም በህዝቡ ዘንድ ተወዳጅነት እያገኘ ባለበት ወቅት፣ ወደ ቫሬንስ (ሰኔ 1791) ያደረገው አስከፊ በረራ የፖለቲካ ድነት ተስፋውን ከውጭ ወረራ ተስፋ ጋር ያቆራኘው ይመስላል። የእሱ ተአማኒነት በጥልቅ በመናድ የንጉሣዊው ሥርዓት መጥፋት እና ሪፐብሊክ መመስረት እድሉ እየጨመረ መጣ። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 1791 የኦስትሪያ ንጉሠ ነገሥት እና የፕሩሺያ ንጉሥ በፒልኒትዝ መግለጫ አብዮተኛ ፈረንሳይ የፈረንሳይን ፍፁም ንጉሣዊ አገዛዝ ለመመለስ በትጥቅ ኃይል ጣልቃ እንድትገባ አስፈራሩ። በሴፕቴምበር 1791 የብሔራዊ ሕገ-መንግሥታዊ ጉባኤ ንጉሥ ሉዊስ 16ኛ የ1791 የፈረንሳይ ሕገ መንግሥት እንዲቀበል አስገድዶታል፣ በዚህም የፈረንሳይን ፍፁም ንጉሣዊ አገዛዝ ወደ ሕገ መንግሥታዊ ንጉሣዊ አገዛዝ ለወጠው። አዲስ በተቋቋመው የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት (እ.ኤ.አ. ጥቅምት 1791) በቡድን መካከል ጠላትነት ተፈጥሯል እና እየከረረ ሄዶ ከኦስትሪያ እና ከፕሩሺያ ጋር ጦርነትን በመረጡት 'ጂሮንዲንስ' እና በኋላም 'ሞንታኛርድ' ወይም 'ጃኮቢንስ' የተሰኘው ቡድን እንዲህ ያለውን ተቃውሞ በመቃወም ጦርነት ። እ.ኤ.አ. በ 1792 ብዙ የጉባኤው አባላት ከኦስትሪያ እና ከፕሩሺያ ጋር የተደረገ ጦርነት የአብዮታዊ መንግስትን ተወዳጅነት ለማሳደግ እድል አድርገው ይመለከቱት እና ፈረንሳይ በተሰበሰቡት ነገስታት ላይ ጦርነት ታሸንፋለች ብለው አሰቡ ። እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 20 ቀን 1792 በኦስትሪያ ላይ ጦርነት አወጁ።እ.ኤ.አ. ነሐሴ 10 ቀን 1792 የተናደዱ ሰዎች በሕግ ​​አውጪው ምክር ቤት የተጠለሉትን የንጉሥ ሉዊስ 16ኛ ቤተ መንግሥት አስፈራሩ። በነሐሴ 1792 የፕሩሺያን ጦር ፈረንሳይን ወረረ። በሴፕቴምበር መጀመሪያ ላይ የፓሪስያውያን ጦር ቬርዱን በምዕራብ ፈረንሳይ በወሰደው ፀረ-አብዮታዊ ዓመጽ የተበሳጩት የፓሪስ እስረኞች የፓሪስን እስር ቤቶችን በመዝለፍ ከ1,000 እስከ 1,500 የሚደርሱ እስረኞችን ገደሉ። ጉባኤው እና የፓሪስ ከተማ ምክር ቤት ያንን ደም መፋሰስ ማቆም ያቃታቸው ይመስላል። በመጀመሪያዎቹ ምርጫዎች በወንዶች ሁለንተናዊ ምርጫ የተመረጠው ብሔራዊ ኮንቬንሽን እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 20 ቀን 1792 የሕግ አውጪውን ምክር ቤት ተክቶ መስከረም 21 ቀን የፈረንሳይ የመጀመሪያ ሪፐብሊክን በማወጅ ንጉሣዊውን ሥርዓት አጠፋ። በጥር 1793 የቀድሞ ንጉስ ሉዊስ 16ኛ በሀገር ክህደት እና በወንጀል ተፈርዶበታል። ፈረንሳይ በታላቋ ብሪታንያ እና በኔዘርላንድ ሪፐብሊክ ላይ በህዳር 1792 ጦርነት አውጀች እና በማርች 1793 በስፔን ላይም እንዲሁ አደረገች። በ 1793 የጸደይ ወቅት ኦስትሪያ እና ፕሩሺያ ፈረንሳይን ወረሩ; በመጋቢት ወር ፈረንሳይ በ "ሜይንዝ ሪፐብሊክ" ውስጥ "የእህት ሪፐብሊክ" ፈጠረች እና በቁጥጥር ስር አዋለች. እንዲሁም በመጋቢት 1793 የቬንዳው የእርስ በርስ ጦርነት በፓሪስ ላይ ተጀመረ, በሁለቱም የ 1790 ቀሳውስት የሲቪል ሕገ መንግሥት እና በ 1793 መጀመሪያ ላይ በመላው አገሪቱ የጦር ሰራዊት ግዳጅ ተቀስቅሷል. በፈረንሳይ ሌላ ቦታም አመጽ እየተቀጣጠለ ነበር። ከጥቅምት 1791 ጀምሮ በብሔራዊ ኮንቬንሽኑ ውስጥ የነበረው የቡድናዊ ጠብ፣ ከ'ጂሮንዲንስ' ቡድን ጋር በጁን 2 1793 ስልጣን ለመልቀቅ እና ስብሰባውን ለቆ እንዲወጣ ተገደዱ። በመጋቢት 1793 በቬንዳው የጀመረው ፀረ አብዮት በጁላይ ወር ወደ ብሪትኒ፣ ኖርማንዲ፣ ቦርዶ፣ ማርሴይ፣ ቱሎን እና ሊዮን ተዛምቷል። በጥቅምት እና ታኅሣሥ 1793 መካከል የፓሪስ ኮንቬንሽን መንግሥት በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ሕይወትን የከፈሉትን አብዛኞቹን የውስጥ አመጾች በአረመኔ እርምጃዎች ለማሸነፍ ችሏል። አንዳንድ የታሪክ ተመራማሪዎች የእርስ በርስ ጦርነት እስከ 1796 ድረስ የዘለቀ እና ምናልባትም የ450,000 ሰዎች ህይወት እንዳለፈ ይገነዘባሉ። በ1793 መገባደጃ ላይ አጋሮቹ ከፈረንሳይ ተባረሩ። ፈረንሳይ እ.ኤ.አ. ከጥቅምት 1793 እስከ ሐምሌ 1794 በተደረገው ብሔራዊ ኮንቬንሽን የፖለቲካ አለመግባባቶች እና ጠላትነት ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ላይ በመድረስ በደርዘን የሚቆጠሩ የኮንቬንሽኑ አባላት የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በ1794 የፈረንሳይ የውጪ ጦርነቶች እየበለፀጉ ነበር ለምሳሌ በቤልጂየም። እ.ኤ.አ. በ 1795 ፣ መንግስት (የካቶሊክ) የሃይማኖት ነፃነት እና ፍትሃዊ የምግብ ስርጭትን በተመለከተ የታችኛው ክፍል ፍላጎቶች እና ፍላጎቶች ወደ ግዴለሽነት የተመለሰ ይመስላል። እ.ኤ.አ. እስከ 1799 ድረስ ፖለቲከኞች አዲስ የፓርላሜንታሪ ስርዓት (‹መመሪያ›) ከመፍጠራቸው በቀር ህዝቡን ከካቶሊክ እምነት እና ከዘውዳዊ አገዛዝ በማሳጣት ተጠምደዋል። ናፖሊዮን እና 19 ኛው ክፍለ ዘመን ናፖሊዮን ቦናፓርት በ1799 ሪፐብሊኩን ተቆጣጠረ የመጀመሪያ ቆንስል እና በኋላም የፈረንሳይ ግዛት ንጉሠ ነገሥት ሆነ። በፈረንሣይ ሪፐብሊክ ላይ በአውሮፓ ንጉሠ ነገሥታት የቀሰቀሱት ጦርነቶች እንደቀጠለ፣ የአውሮፓ ኅብረት ስብስቦች ለውጥ በናፖሊዮን ኢምፓየር ላይ ጦርነት አውጀዋል። ሠራዊቱ አብዛኛውን አህጉራዊ አውሮፓን እንደ ጄና-ኦየርስታድት ወይም አውስተርሊትዝ ባሉ ፈጣን ድሎች አሸንፏል። የቦናፓርት ቤተሰብ አባላት በአንዳንድ አዲስ በተቋቋሙት መንግስታት እንደ ንጉስ ተሹመዋል። እነዚህ ድሎች እንደ ሜትሪክ ሲስተም፣ ናፖሊዮን ኮድ እና የሰው መብቶች መግለጫ ያሉ የፈረንሳይ አብዮታዊ እሳቤዎችን እና ማሻሻያዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲስፋፋ ምክንያት ሆነዋል። ሰኔ 1812 ናፖሊዮን ሩሲያን በማጥቃት ሞስኮ ደረሰ። ከዚያ በኋላ ሠራዊቱ በአቅርቦት ችግር፣ በበሽታ፣ በሩሲያ ጥቃቶች እና በመጨረሻ በክረምት ተበታተነ። ከአሰቃቂው የሩስያ ዘመቻ በኋላ እና በግዛቱ ላይ ከተነሳው የአውሮፓ ንጉሳዊ አገዛዝ በኋላ ናፖሊዮን ተሸነፈ እና የቡርቦን ንጉሳዊ አገዛዝ እንደገና ተመለሰ. በናፖሊዮን ጦርነት ወቅት ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ፈረንሳውያን ሞቱ። ከስደት ለአጭር ጊዜ ከተመለሰ በኋላ ናፖሊዮን በመጨረሻ በ 1815 በዋተርሉ ጦርነት ተሸነፈ ፣ ንጉሳዊው ስርዓት እንደገና ተመሠረተ ፣ በአዲስ ህገ-መንግስታዊ ገደቦች። ተቀባይነት ያጣው የቡርቦን ሥርወ መንግሥት በ1830 በሐምሌ አብዮት ተወገደ፣ እሱም ሕገ መንግሥታዊውን የሐምሌ ንጉሣዊ ሥርዓትን አቋቋመ። በዚያ ዓመት የፈረንሳይ ወታደሮች አልጄሪያን ድል አድርገው በ1798 ናፖሊዮን ግብፅን ከወረረ በኋላ በአፍሪካ ውስጥ የመጀመሪያውን የቅኝ ግዛት ግዛት አቋቋሙ። በፈረንሣይ አብዮት ጊዜ ለአጭር ጊዜ የወጣው የወንድ ንጉሠ ነገሥት ባርነት እና ሁለንተናዊ ምርጫ በ1848 እንደገና ተወገደ። ሁለተኛው ኢምፓየር እንደ ናፖሊዮን . በውጭ አገር በተለይም በክራይሚያ፣ በሜክሲኮ እና በጣሊያን የፈረንሳይን ጣልቃገብነት በማባዛት የዱቺ ኦፍ ሳቮይ እና የኒስ ካውንቲ፣ ያኔ የሰርዲኒያ ግዛት አካል ሆነ። እ.ኤ.አ. በ1870 በፍራንኮ-ፕራሻ ጦርነት ሽንፈትን ተከትሎ ናፖሊዮን ሳልሳዊ ተቀምጦ ነበር እና አገዛዙ በሶስተኛው ሪፐብሊክ ተተካ። እ.ኤ.አ. በ 1875 ፈረንሣይ የአልጄሪያን ወረራ ያጠናቀቀ ሲሆን በዚህ ምክንያት ወደ 825,000 የሚጠጉ አልጄሪያውያን ተገድለዋል ።ፈረንሳይ ከ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ጀምሮ በተለያየ መልኩ የቅኝ ግዛት ይዞታዎች ነበሯት ነገር ግን በ19ኛው እና በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አለም አቀፋዊ የባህር ማዶ የቅኝ ግዛት ግዛቷ በእጅጉ በመስፋፋት ከብሪቲሽ ኢምፓየር ቀጥሎ በአለም ሁለተኛዋ ትልቅ ሆናለች። ሜትሮፖሊታን ፈረንሳይን ጨምሮ፣ በ1920ዎቹ እና 1930ዎቹ ውስጥ ያለው አጠቃላይ የመሬት ስፋት በፈረንሳይ ሉዓላዊነት ወደ 13 ሚሊዮን ስኩዌር ኪሎ ሜትር ሊደርስ ተቃርቧል፣ ይህም ከአለም መሬት 8.6% ነው። ቤሌ ኤፖክ በመባል የሚታወቀው፣ የክፍለ ዘመኑ መባቻ በብሩህ ተስፋ፣ በክልላዊ ሰላም፣ በኢኮኖሚ ብልጽግና እና በቴክኖሎጂ፣ ሳይንሳዊ እና ባህላዊ ፈጠራዎች የሚታወቅበት ወቅት ነበር። በ1905 ዓ.ም.የመንግስት ሴኩላሪዝም በይፋ ተመሠረተ። ዘመናዊ ጊዜ (1914-አሁን) ፈረንሳይ በጀርመን የተወረረች ሲሆን በታላቋ ብሪታንያ ተከላካለች፤ አንደኛው የዓለም ጦርነት በነሐሴ 1914 እንዲጀምር ነበር። በሰሜናዊ ምሥራቅ የሚገኝ የበለጸገ የኢንዱስትሪ አካባቢ ተያዘ። ፈረንሣይ እና አጋሮቹ በማዕከላዊ ኃያላን ላይ እጅግ ከፍተኛ በሆነ የሰው እና ቁሳዊ ዋጋ አሸንፈው ወጡ። አንደኛው የዓለም ጦርነት 1.4 ሚሊዮን የፈረንሣይ ወታደሮችን ለሞት ዳርጓል ይህም ከሕዝቧ 4% ነው። ከ 1912 እስከ 1915 ከተመዘገቡት ከ 27 እስከ 30% ወታደሮች ተገድለዋል. የኢንተር ቤልም አመታት በጠንካራ አለም አቀፍ ውጥረቶች እና በህዝባዊ ግንባር መንግስት በተለያዩ ማህበራዊ ማሻሻያዎች (የዓመት እረፍት፣ የስምንት ሰአት የስራ ቀናት፣ ሴቶች በመንግስት ውስጥ) ይታወቃሉ። እ.ኤ.አ. በ 1940 ፈረንሳይ በናዚ ጀርመን ወረራ በፍጥነት ተሸነፈች። ፈረንሣይ በሰሜን በጀርመን የቅሬታ ዞን፣ በደቡብ ምስራቅ የኢጣሊያ የወረራ ዞን እና ያልተያዘ ክልል፣ የተቀረው የፈረንሳይ ግዛት፣ የደቡብ ፈረንሳይ ዋና ከተማ ግዛት (ከጦርነት በፊት ሁለት አምስተኛ ሜትሮፖሊታን ፈረንሳይ) እና እ.ኤ.አ. የፈረንሳይ ቱኒዚያ እና የፈረንሣይ ሞሮኮ እና የፈረንሣይ አልጄሪያን ሁለቱን ጠባቂዎች ያካተተ የፈረንሳይ ግዛት; የቪቺ መንግሥት፣ አዲስ የተቋቋመው አምባገነናዊ አገዛዝ ከጀርመን ጋር በመተባበር፣ ያልተያዘውን ግዛት ገዛ። በቻርለስ ደጎል የሚመራው የስደት መንግስት ነፃ ፈረንሳይ የተቋቋመው በለንደን ነው። እ.ኤ.አ. ከ1942 እስከ 1944 ወደ 160,000 የሚጠጉ የፈረንሣይ ዜጎች ወደ 75,000 የሚጠጉ አይሁዶች ወደ ጀርመን የሞት ካምፖች እና ማጎሪያ ካምፖች ተወስደው ፖላንድን ተቆጣጠሩ። በሴፕቴምበር 1943 ኮርሲካ እራሷን ከአክሲስ ነፃ ያወጣች የመጀመሪያዋ የፈረንሳይ ከተማ ግዛት ነበረች። ሰኔ 6 1944 አጋሮቹ ኖርማንዲን ወረሩ እና በነሐሴ ወር ፕሮቨንስን ወረሩ። በተከታዩ አመት አጋሮቹ እና የፈረንሳይ ተቃውሞ በአክሲስ ሀይሎች ላይ ድል ተቀዳጅተዋል እና የፈረንሳይ ሉዓላዊነት የፈረንሳይ ሪፐብሊክ ጊዜያዊ መንግስት () በመመስረት ተመልሷል። በዲ ጎል የተቋቋመው ይህ ጊዜያዊ መንግስት በጀርመን ላይ ጦርነት መክፈቱን ለመቀጠል እና ተባባሪዎችን ከቢሮ ለማፅዳት አላማ ነበረው። እንዲሁም በርካታ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን አድርጓል (ለሴቶች የተዘረጋው ምርጫ፣ የማህበራዊ ዋስትና ስርዓት መፍጠር)።ጂፒአርኤፍ ለአዲሱ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት መሠረት ጥሏል አራተኛው ሪፐብሊክ አስደናቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ያስመዘገበችው (ሌስ ትሬንቴ ግሎሪየስ)። ፈረንሳይ የኔቶ መስራች አባላት አንዷ ነበረች። ፈረንሳይ የፈረንሳይ ኢንዶቺናን ለመቆጣጠር ሞከረች ነገር ግን በ1954 በዲን ቢየን ፉ ጦርነት በቬትናም ተሸነፈች። ከወራት በኋላ ፈረንሳይ በአልጄሪያ ሌላ ፀረ-ቅኝ ግዛት ግጭት ገጠማት። ስልታዊ ስቃይ እና ጭቆና እንዲሁም አልጄሪያን ለመቆጣጠር የተፈፀመው ከህግ-ወጥ ግድያ በኋላ እንደ ፈረንሳይ ዋና አካል እና ከአንድ ሚሊዮን በላይ አውሮፓውያን ሰፋሪዎች መኖሪያ ተደርጎ በመታየት ሀገሪቱን አመሰቃቅሎ ወደ መፈንቅለ መንግስት እና የእርስ በርስ ጦርነት ሊመራ ተቃርቧል። . እ.ኤ.አ. በ1958፣ ደካማ እና ያልተረጋጋው አራተኛው ሪፐብሊክ ለአምስተኛው ሪፐብሊክ መንገድ ሰጠ፣ እሱም የተጠናከረ ፕሬዚደንትን ያካትታል። በኋለኛው ሚና ቻርለስ ደ ጎል የአልጄሪያን ጦርነት ለማቆም እርምጃዎችን ሲወስድ ሀገሪቱን አንድ ላይ ማቆየት ችሏል። ጦርነቱ የተጠናቀቀው በ 1962 የአልጄሪያን ነፃነት ባደረገው የኤቪያን ስምምነት ነው። የአልጄሪያ ነፃነት ብዙ ዋጋ አስከፍሎበታል፡- በአልጄሪያ ሕዝብ ላይ ያደረሰው ከፍተኛ ጉዳት። ከግማሽ ሚሊዮን እስከ አንድ ሚሊዮን ሞት እና ከ 2 ሚሊዮን በላይ አልጄሪያውያን ተፈናቅለዋል ። የቅኝ ግዛት ግዛት የፈረንሳይ የባህር ማዶ መምሪያዎች እና ግዛቶች ናቸው።ከቀዝቃዛው ጦርነት አንፃር፣ ደ ጎል ወደ ምዕራባዊ እና ምስራቃዊ ቡድኖች “የብሔራዊ ነፃነት” ፖሊሲን ቀጠለ። ለዚህም ከኔቶ ወታደራዊ የተቀናጀ ዕዝ (በራሱ በኔቶ ጥምረት ውስጥ እያለ) የኒውክሌር ልማት መርሃ ግብር ከፍቶ ፈረንሳይን አራተኛው የኒውክሌር ኃይል አደረጋት። በአሜሪካ እና በሶቪየት ተጽእኖ ዘርፎች መካከል የአውሮፓን ሚዛን ለመፍጠር የፍራንኮ-ጀርመን ግንኙነቶችን መልሷል። ሆኖም፣ የሉዓላዊ አገሮችን አውሮፓን በመደገፍ የበላይ የሆነችውን አውሮፓን ማንኛውንም ልማት ተቃወመ። እ.ኤ.አ. በ1968 ከተደረጉት ተከታታይ አለም አቀፍ ተቃውሞዎች በኋላ፣ የግንቦት 1968 ዓመጽ ከፍተኛ ማህበራዊ ተፅእኖ ነበረው። በፈረንሳይ፣ ወግ አጥባቂ የሆነ የሞራል ሃሳብ (ሀይማኖት፣ ሀገር ወዳድነት፣ ስልጣንን መከባበር) ወደ የበለጠ ሊበራል የሞራል ሃሳብ (ሴኩላሪዝም፣ ግለሰባዊነት፣ ጾታዊ አብዮት) የተሸጋገረበት የውሀ ተፋሰስ ጊዜ ነበር። ምንም እንኳን አመፁ የፖለቲካ ውድቀት ቢሆንም (የጎልስት ፓርቲ ከበፊቱ የበለጠ ጠንካራ ሆኖ ብቅ እያለ) በፈረንሳይ ህዝብ እና በዲ ጎል መካከል መከፋፈል መፈጠሩን አስታውቋል። በድህረ-ጎልሊስት ዘመን፣ ፈረንሳይ በአለም ላይ ካሉት በጣም የበለፀጉ ኢኮኖሚዎች አንዷ ሆና ቆይታለች፣ ነገር ግን በርካታ የኢኮኖሚ ቀውሶች ገጥሟት ነበር ይህም ከፍተኛ የስራ አጥነት መጠን እና የህዝብ ዕዳ መጨመር ምክንያት ሆኗል። በ 20 ኛው እና በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ፈረንሳይ በ 1992 የማስተርችት ስምምነትን (የአውሮጳ ህብረትን የፈጠረውን) በመፈረም ፣ በ 1999 ዩሮ ዞን በመመስረት እና የሊዝበን ስምምነትን በመፈረም ፈረንሳይ በአውሮፓ ህብረት ልማት ግንባር ቀደም ነች ። 2007. ፈረንሳይ ቀስ በቀስ ግን ሙሉ በሙሉ ወደ ኔቶ ተመልሳለች እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በአብዛኛዎቹ የኔቶ ስፖንሰር ጦርነቶች ውስጥ ተሳትፋለችከ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ፈረንሳይ ብዙ ስደተኞችን ተቀብላለች። እነዚህ ባብዛኛው ከአውሮፓ ካቶሊካዊ አገሮች የመጡ ወንድ የውጭ አገር ሠራተኞች ሲሆኑ በአጠቃላይ ሳይቀጠሩ ወደ አገራቸው የተመለሱ ናቸው። እ.ኤ.አ. በ1970ዎቹ ፈረንሳይ የኢኮኖሚ ቀውስ ገጥሟት አዲስ ስደተኞች (በአብዛኛው ከማግሬብ የመጡ) በቋሚነት ከቤተሰቦቻቸው ጋር በፈረንሳይ እንዲሰፍሩ እና የፈረንሳይ ዜግነት እንዲኖራቸው ፈቅዳለች። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች (በተለይ በትልልቅ ከተሞች) በድጎማ በሚደረግ የህዝብ መኖሪያ ቤት ውስጥ እንዲኖሩ እና በጣም ከፍተኛ በሆነ የስራ አጥነት ችግር እንዲሰቃዩ አድርጓል። በተመሳሳይ ጊዜ ፈረንሳይ የስደተኞችን ውህደት ትታ የፈረንሳይ ባህላዊ እሴቶችን እና ባህላዊ ደንቦችን ያከብራሉ ተብሎ ይጠበቃል። ልዩ የሆኑ ባህሎቻቸውን እና ወጎችን እንዲቀጥሉ ተበረታተዋል እናም መዋሃድ ብቻ ይጠበቅባቸዋል። እ.ኤ.አ. ከ1995 የፓሪስ ሜትሮ እና የቦምብ ጥቃቶች ጀምሮ ፈረንሳይ አልፎ አልፎ በኢስላማዊ ድርጅቶች ኢላማ ሆና ቆይታለች ፣በተለይ እ.ኤ.አ. በጥር 2015 በቻርሊ ሄብዶ በፈረንሣይ ታሪክ ትልቁን ሕዝባዊ ስብሰባ ያስቀሰቀሰ ፣ 4.4 ሚሊዮን ሰዎችን የሰበሰበ ፣ በኖቬምበር 2015 የፓሪስ ጥቃት በ130 ምክንያት ሞት፣ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ በፈረንሳይ ምድር ላይ የደረሰው እጅግ አስከፊው ጥቃት እና በ2004 ከማድሪድ የባቡር ቦምብ ጥቃት በኋላ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ የተፈፀመው አስከፊው ጥቃት፣ እንዲሁም እ.ኤ.አ. በ2016 የባስቲል ቀን አከባበር ላይ 87 ሰዎችን የገደለው የኒስ የጭነት መኪና ጥቃት። ኦፔሬሽን ቻማል፣ ፈረንሳይ ን ለመቆጣጠር ባደረገችው ጥረት ከ1,000 በላይ የአይኤስ ወታደሮችን በ2014 እና 2015 ገድሏል። የመሬት አቀማመጥ ፈረንሳይ ከብራዚል እና ሱሪናም ጋር በፈረንሳይ ጊያና እና ከኔዘርላንድስ መንግሥት ጋር በሴንት ማርቲን የፈረንሳይ ክፍል በኩል የመሬት ድንበር አላት። ሜትሮፖሊታን ፈረንሳይ 551,500 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (212,935 ካሬ ማይል) ይሸፍናል፣ ከአውሮፓ ህብረት አባላት መካከል ትልቁ። የፈረንሳይ አጠቃላይ የመሬት ስፋት፣ ከባህር ማዶ መምሪያዎች እና ግዛቶች ጋር (ከአዴሊ መሬት በስተቀር) 643,801 2 (248,573 ካሬ ማይል) ነው፣ ይህም በምድር ላይ ካለው አጠቃላይ ስፋት 0.45% ነው። ፈረንሣይ በሰሜን እና በምዕራብ ካሉ የባህር ዳርቻ ሜዳማዎች እስከ ደቡብ ምስራቅ የአልፕስ ተራሮች ፣ ማሲፍ ሴንትራል በደቡብ ማዕከላዊ እና በደቡብ ምዕራብ ፒሬኒስ የተለያዩ መልክዓ ምድሮች አላት ። በፕላኔቷ ላይ በተበተኑ በርካታ የባህር ማዶ መምሪያዎች እና ግዛቶች ምክንያት ፈረንሳይ በአለም ላይ ሁለተኛውን ትልቁ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን () ይዛለች፣ 11,035,000 2 (4,261,000 ስኩዌር ማይል) የሚሸፍን ሲሆን ይህም ከዩናይትድ ስቴትስ በስተጀርባ ሲሆን ይህም 11,351,000000 2 (4,383,000 ስኩዌር ማይል)፣ ነገር ግን 8,148,250 2 (3,146,000 ስኩዌር ማይል) የሚሸፍነው ከአውስትራሊያ በፊት። የእሱ ከጠቅላላው የዓለም ኢኢኢዜዎች አጠቃላይ ገጽ 8 በመቶውን ይሸፍናል።ሜትሮፖሊታን ፈረንሳይ ብዙ አይነት መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ እና የተፈጥሮ መልክአ ምድሮች አሏት። በአሁኑ የፈረንሳይ ግዛት ውስጥ ትላልቅ ክፍሎች የተነሱት በፓሌኦዞይክ ዘመን ውስጥ እንደ ሄርሲኒያን ከፍ ከፍ ባሉ በርካታ የቴክቶኒክ ክፍሎች ውስጥ ሲሆን በዚህ ወቅት የአርሞሪክ ማሲፍ ፣ ማሲፍ ማዕከላዊ ፣ ሞርቫን ፣ ቮስጌስ እና አርደንነስ ክልሎች እና የኮርሲካ ደሴት ተመስርተዋል። እነዚህ ግዙፍ ቦታዎች እንደ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘውን አኲታይን ተፋሰስ እና በሰሜን የፓሪስ ተፋሰስ ያሉ በርካታ ደለል ተፋሰሶችን ይገልፃሉ፣ የኋለኛው ደግሞ በተለይ ለም መሬት በርካታ አካባቢዎችን ለምሳሌ እንደ የቢውስ እና የብሪዬ ደለል አልጋዎች ያሉ። እንደ ሮን ሸለቆ ያሉ የተለያዩ የተፈጥሮ መተላለፊያ መንገዶች ቀላል ግንኙነትን ይፈቅዳሉ። የአልፓይን ፣ የፒሬኔያን እና የጁራ ተራሮች በጣም ትንሽ ናቸው እና ብዙም ያልተሸረሸሩ ቅርጾች አሏቸው። ከባህር ጠለል በላይ 4,810.45 ሜትር (15,782 ጫማ) ላይ፣ በፈረንሳይ እና በጣሊያን ድንበር ላይ በአልፕስ ተራሮች ላይ የሚገኘው ሞንት ብላንክ በምዕራብ አውሮፓ ከፍተኛው ቦታ ነው። ምንም እንኳን 60 በመቶው ማዘጋጃ ቤቶች የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች ተብለው ቢከፋፈሉም, እነዚህ አደጋዎች መካከለኛ ናቸው.የባህር ዳርቻዎች ተቃራኒ መልክአ ምድሮችን ይሰጣሉ፡ በፈረንሳይ ሪቪዬራ የሚገኙ የተራራ ሰንሰለቶች፣ እንደ ኮት ዲ አልበትር ያሉ የባህር ዳርቻ ቋጥኞች እና በላንጌዶክ ውስጥ ሰፊ አሸዋማ ሜዳዎች። ኮርሲካ በሜዲትራኒያን የባህር ዳርቻ ላይ ይገኛል. ፈረንሳይ አራት ዋና ዋና ወንዞችን ሴይን፣ ሎየር፣ ጋሮንኔ፣ ሮን እና ገባር ወንዞቻቸውን ያቀፈ ሰፊ የወንዝ ስርዓት አላት፣ ጥምር ተፋሰሱ ከ62% በላይ የሚሆነውን የሜትሮፖሊታን ግዛት ያካትታል። ሮን ማሲፍ ሴንትራልን ከአልፕስ ተራሮች በመከፋፈል በካማርግ ወደ ሜዲትራኒያን ባህር ይፈስሳል። ጋሮን ከቦርዶ በኋላ ከዶርዶኝ ጋር ተገናኘ ፣ በምዕራብ አውሮፓ ውስጥ ትልቁ የጂሮንድ ኢስትውሪ ፣ በግምት 100 ኪ.ሜ (62 ማይል) ካለፈ በኋላ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ የሚያልፍ። ሌሎች የውሃ ኮርሶች በሰሜን-ምስራቅ ድንበሮች በኩል ወደ እና ይጎርፋሉ። ፈረንሳይ 11 ሚሊየን ስኩዌር ኪሎ ሜትር (4.2×106 ካሬ ማይል) የባህር ውሃ በግዛቷ ስር ባሉት ሶስት ውቅያኖሶች ውስጥ ያላት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 97 በመቶው ባህር ማዶ ናቸው። መንግስት እና ፖለቲካ ፈረንሳይ እንደ አሃዳዊ፣ ከፊል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ የተደራጀ ተወካይ ዲሞክራሲ ናት። የዘመናዊው ዓለም ቀደምት ሪፐብሊካኖች አንዱ እንደመሆኖ፣ ዲሞክራሲያዊ ወጎች እና እሴቶች በፈረንሳይ ባህል፣ ማንነት እና ፖለቲካ ውስጥ ሥር የሰደዱ ናቸው። የአምስተኛው ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት በሴፕቴምበር 28 ቀን 1958 በህዝበ ውሳኔ ጸድቋል, የአስፈጻሚ, የሕግ አውጪ እና የፍትህ አካላትን ያቀፈ ማዕቀፍ አቋቋመ. የሶስተኛው እና አራተኛው ሪፐብሊኮች አለመረጋጋት የፓርላማ እና የፕሬዚዳንታዊ ስርዓቶች አካላትን በማጣመር ከህግ አውጭው ጋር በተዛመደ የአስፈፃሚውን ስልጣን በከፍተኛ ደረጃ በማጠናከር ለመፍታት ሞክሯል. አስፈፃሚ አካል ሁለት መሪዎች አሉት። የሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት በአሁኑ ጊዜ ኢማኑኤል ማክሮን የሀገር መሪ ናቸው, በአለም አቀፍ የአዋቂዎች ምርጫ ለአምስት ዓመታት በቀጥታ ተመርጠዋል. ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአሁኑ ወቅት ዣን ካስቴክስ የፈረንሳይ መንግስትን እንዲመሩ በሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት የተሾሙ የመንግስት መሪ ናቸው። ፕሬዝዳንቱ ፓርላማውን የመበተን ወይም በቀጥታ ለህዝብ ህዝበ ውሳኔ በማቅረብ ፓርላማውን የመዝጋት ስልጣን አላቸው። ፕሬዚዳንቱ ዳኞችን እና ሲቪል ሰርቫንቶችን ይሾማሉ፣ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ይደራደራሉ እና ያፀድቃሉ እንዲሁም የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ሆነው ያገለግላሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህዝብ ፖሊሲን ይወስናል እና ሲቪል ሰርቪሱን ይቆጣጠራል, በአገር ውስጥ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል. የሕግ አውጭው የፈረንሳይ ፓርላማን ያቀፈ የሁለት ምክር ቤት የታችኛው ምክር ቤት፣ ብሔራዊ ምክር ቤት (የጉባኤ ብሄራዊ ምክር ቤት) እና ከፍተኛ ምክር ቤት ሴኔትን ያቀፈ ነው። በብሔራዊ ምክር ቤት ውስጥ ያሉ የሕግ አውጭዎች ዲፑቴስ በመባል የሚታወቁት የአካባቢ ምርጫዎችን ይወክላሉ እና ለአምስት በቀጥታ ይመረጣሉ። - ዓመት ውሎች. ምክር ቤቱ መንግስትን በአብላጫ ድምጽ የማሰናበት ስልጣን አለው። ሴናተሮች የሚመረጡት በምርጫ ኮሌጅ ለስድስት ዓመታት ሲሆን ግማሹ መቀመጫ በየሦስት ዓመቱ ለምርጫ ይቀርባል። የሴኔቱ የህግ አውጭ ስልጣኖች ውስን ናቸው; በሁለቱ ምክር ቤቶች መካከል አለመግባባት ሲፈጠር የብሔራዊ ምክር ቤቱ የመጨረሻ ውሳኔ ይኖረዋል። ፓርላማው አብዛኛዎቹን የህግ ዘርፎች፣ የፖለቲካ ምህረት እና የፊስካል ፖሊሲን የሚመለከቱ ህጎችን እና መርሆዎችን የመወሰን ሃላፊነት አለበት። ይሁን እንጂ መንግሥት አብዛኞቹን ሕጎች በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮችን ሊያዘጋጅ ይችላል። እስከ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ድረስ ራዲካልስ በፈረንሳይ ውስጥ በሪፐብሊካን፣ ራዲካል እና ራዲካል-ሶሻሊስት ፓርቲ የተዋቀረ ጠንካራ የፖለቲካ ኃይል የሶስተኛው ሪፐብሊክ ዋና አካል ነበር። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ፣ የፈረንሳይ ፖለቲካ በሁለት የፖለቲካ ተቃዋሚ ቡድኖች ተለይቶ ሲታወቅ፣ አንደኛው የግራ ክንፍ፣ የፈረንሣይ የሠራተኞች ዓለም አቀፍ ክፍል እና ተተኪውን የሶሻሊስት ፓርቲ (ከ1969 ዓ.ም.) እና ሌላኛው የቀኝ ክንፍ፣ በጋሊስት ፓርቲ ላይ ያተኮረ፣ ስሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ የፈረንሳይ ህዝቦች ፣ የዴሞክራቶች ህብረት ለሪፐብሊኩ ፣ ለሪፐብሊኩ ፣ እ.ኤ.አ. ህብረት ለታዋቂ ንቅናቄ እና ሪፐብሊካኖች (ከ2015 ጀምሮ)። እ.ኤ.አ. በ 2017 ፕሬዚዳንታዊ እና የሕግ አውጪ ምርጫዎች ፣ አክራሪ ማዕከላዊ ፓርቲ ኤን ማርቼ! ሶሻሊስቶችን እና ሪፐብሊካኖችን በማለፍ የበላይ ኃይል ሆነ። መራጩ ህዝብ በፓርላማ የተላለፉ ማሻሻያዎችን እና በፕሬዚዳንቱ የሚቀርቡ ረቂቅ ህጎች ላይ ድምጽ የመስጠት ህገ መንግስታዊ ስልጣን ተሰጥቶታል። ሪፈረንደም የፈረንሳይ ፖለቲካን እና የውጭ ፖሊሲን በመቅረጽ ረገድ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል; መራጮች እንደ አልጄሪያ ነፃነት፣ በሕዝብ ድምፅ የፕሬዚዳንቱ ምርጫ፣ የአውሮፓ ኅብረት ምስረታ እና የፕሬዚዳንት ጊዜ ገደብ መቀነስ በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ወስነዋል። በ2019 ህዝቡ የግዴታ ድምጽ መስጠትን እንደ መፍትሄ እንደሚደግፍ ተዘግቧል። ነገር ግን ቢያንስ እ.ኤ.አ. በ2017 የመራጮች ተሳትፎ በቅርብ ምርጫዎች 75 በመቶ ነበር ይህም ከ አማካኝ 68 በመቶ ይበልጣል። ፈረንሳይ የሲቪል ህጋዊ ስርዓትን ትጠቀማለች, በዚህ ውስጥ ህግ በዋነኛነት ከተፃፉ ህጎች ይነሳል; ዳኞች ሕግ ማውጣት ሳይሆን መተርጎም ብቻ ነው (ምንም እንኳን በአንዳንድ አካባቢዎች ያለው የዳኝነት ትርጉም መጠን በኮመን ሎው ሥርዓት ውስጥ ካለው የክስ ሕግ ጋር እኩል ያደርገዋል)። የሕግ የበላይነት መሰረታዊ መርሆች በናፖሊዮን ኮድ ውስጥ ተቀምጠዋል (ይህም በተራው, በሉዊ አሥራ አራተኛው ሥር በተቀመጠው የንጉሣዊ ሕግ ላይ የተመሰረተ ነው). የሰው እና የዜጎች መብቶች መግለጫ መርሆዎች ጋር በመስማማት ህጉ ማህበረሰቡን የሚጎዱ ድርጊቶችን ብቻ መከልከል አለበት። የሰበር ሰሚ ችሎት የመጀመሪያ ፕሬዝደንት ጋይ ካኒቬት ስለ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ሲፅፉ፡- “ነፃነት ህግ ነው፣ ገደቡም የተለየ ነው፣ ማንኛውም የነፃነት ገደብ በህግ የተደነገገ መሆን አለበት እና የግድ አስፈላጊ እና መሰረታዊ መርሆችን መከተል አለበት። ተመጣጣኝነት" ይኸውም ሕጉ ክልከላዎችን የሚያስቀምጥ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ብቻ ሲሆን በዚህ ክልከላ ምክንያት የሚፈጠሩት ችግሮች ክልከላው ሊስተካከል ከሚገባው ጉዳቱ ያልበለጠ ከሆነ ነው። የፈረንሳይ ህግ በሁለት ዋና ዋና ቦታዎች ይከፈላል፡ የግል ህግ እና የህዝብ ህግ። የግል ህግ በተለይም የፍትሐ ብሔር ህግ እና የወንጀል ህግን ያጠቃልላል። የህዝብ ህግ በተለይ የአስተዳደር ህግ እና ህገመንግስታዊ ህግን ያጠቃልላል። ነገር ግን፣ በተግባራዊ አገላለጽ፣ የፈረንሳይ ሕግ ሦስት ዋና ዋና የሕግ ዘርፎችን ያካትታል፡ የፍትሐ ብሔር ህግ፣ የወንጀል ህግ እና የአስተዳደር ህግ። የወንጀለኛ መቅጫ ህጎች የወደፊቱን ብቻ እንጂ ያለፈውን አይደለም (የወንጀለኛ መቅጫ ህጎች የተከለከሉ ናቸው)። የአስተዳደር ሕግ በብዙ አገሮች የፍትሐ ብሔር ሕግ ንዑስ ምድብ ሆኖ ሳለ፣ በፈረንሳይ ሙሉ በሙሉ ተለያይቷል እና እያንዳንዱ የሕግ አካል የሚመራው በልዩ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው፡ ተራ ፍርድ ቤቶች (የወንጀል እና የፍትሐ ብሔር ክርክርን የሚመለከቱ) በሰበር ሰሚ ችሎት ይመራሉ እና የአስተዳደር ፍርድ ቤቶች በመንግስት ምክር ቤት ይመራሉ. ተፈፃሚ ለመሆን፣ እያንዳንዱ ህግ በጆርናል ውስጥ በይፋ መታተም አለበት። ፈረንሣይ የሃይማኖት ህግን እንደ ክልከላዎች ማነሳሳት አትቀበልም; የስድብ ህጎችን እና የሰዶማውያን ህጎችን (የኋለኛው በ1791) ሽሮ ቆይቷል። ነገር ግን "በህዝባዊ ጨዋነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች" () ወይም ህዝባዊ ጸጥታን የሚረብሹ (ችግር ) የግብረ ሰዶምን ወይም የጎዳና ላይ ዝሙት አዳሪነትን በአደባባይ ለማፈን ጥቅም ላይ ውለዋል። ከ 1999 ጀምሮ የግብረ ሰዶማውያን ጥንዶች የሲቪል ማህበራት ይፈቀዳሉ እና ከ 2013 ጀምሮ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ እና ኤልጂቢቲ ጉዲፈቻ ህጋዊ ናቸው። በፕሬስ ውስጥ አድሎአዊ ንግግርን የሚከለክሉት ሕጎች በ1881 ዓ.ም. የቆዩ ናቸው። አንዳንዶች በፈረንሳይ የጥላቻ ንግግር ሕጎች በጣም ሰፊ ወይም ከባድ እንደሆኑ አድርገው ይመለከቱታል፣ የመናገር ነፃነትን የሚገታ። ፈረንሣይ ዘረኝነትን እና ፀረ-ሴማዊነትን የሚቃወሙ ሕጎች ያሏት ሲሆን በ1990 የወጣው የጋይሶት ሕግ ግን የሆሎኮስትን መካድ ይከለክላል። የሃይማኖት ነፃነት በ1789 በወጣው የሰው እና የዜጎች መብቶች መግለጫ ሕገ መንግሥታዊ ዋስትና ተሰጥቶታል። እ.ኤ.አ. በ 1905 የወጣው የፈረንሣይ የአብያተ ክርስቲያናት እና የመንግስት መለያየት ህግ ለ (መንግስታዊ ሴኩላሪዝም) መሠረት ነው፡ መንግስት ከአልሳስ ሞሴል በስተቀር የትኛውንም ሃይማኖት በይፋ አይቀበልም። ቢሆንም፣ የሃይማኖት ማኅበራትን እውቅና ይሰጣል። ፓርላማው ከ 1995 ጀምሮ ብዙ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎችን እንደ አደገኛ የአምልኮ ሥርዓቶች ዘርዝሯል ፣ እና ከ 2004 ጀምሮ በትምህርት ቤቶች ውስጥ ጉልህ የሆኑ ሃይማኖታዊ ምልክቶችን መልበስ አግዷል ። እ.ኤ.አ. እንደ አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂዩማን ራይትስ ዎች ያሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ህጉን ለሙስሊሞች አድሎአዊ መሆኑን ገልፀውታል። ይሁን እንጂ በአብዛኛው ሕዝብ ይደገፋል. የውጭ ግንኙነት እና ጥምረት ፈረንሳይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መስራች አባል ስትሆን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት የቬቶ መብት ካላቸው ቋሚ አባላት አንዷ ሆና ታገለግላለች። እ.ኤ.አ. በ 2015 ከማንኛውም ሀገር በበለጠ በአለም አቀፍ ተቋማት ውስጥ በአባልነት ምክንያት "በአለም ላይ ምርጥ የአውታረ መረብ መንግስት" ተብሎ ተገልጿል; እነዚህም 7፣ የዓለም ንግድ ድርጅት ()፣ የፓሲፊክ ማህበረሰብ () እና የሕንድ ውቅያኖስ ኮሚሽን () ያካትታሉ። የካሪቢያን ግዛቶች ማህበር (ኤሲኤስ) ተባባሪ አባል እና የ84 ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ሀገራት የድርጅቱ ) አባል ነው። ፈረንሳይ ለዓለም አቀፍ ግንኙነት ጉልህ ስፍራ እንደመሆኗ በሕዝብ ብዛት ከቻይና እና ከዩናይትድ ስቴትስ ቀጥላ ሦስተኛው ትልቁ የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች ጉባኤ አላት። እንዲሁም ፣ ዩኔስኮ፣ ኢንተርፖል፣ የአለም አቀፍ የክብደት እና መለኪያዎች ቢሮ እና ኦአይኤፍን ጨምሮ የበርካታ አለም አቀፍ ድርጅቶች ዋና መሥሪያ ቤትን ያስተናግዳል። ከጦርነቱ በኋላ የፈረንሳይ የውጭ ፖሊሲ በአብዛኛው የተቀረፀው በአውሮፓ ህብረት አባልነት ነው ፣ እሱም መስራች አባል ነበር። እ.ኤ.አ. ከ1960ዎቹ ጀምሮ ፈረንሣይ ከጀርመን ከተዋሀደችው የአውሮፓ ኅብረት ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪ ኃይል ለመሆን የጠበቀ ግንኙነት መሥርታለች። እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ ፈረንሣይ በአህጉር አውሮፓ የራሷን አቋም ለመገንባት ብሪታንያዎችን ከአውሮፓ ውህደት ሂደት ለማግለል ፈለገች። ይሁን እንጂ ከ1904 ዓ.ም ጀምሮ ፈረንሳይ ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር “” ጠብቃ ቆይታለች፣ እናም በአገሮቹ መካከል በተለይም በወታደራዊ ኃይል መካከል ያለው ግንኙነት እየጠነከረ መጥቷል። ፈረንሳይ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) አባል ስትሆን በፕሬዚዳንት ደ ጎል ግን በዩናይትድ ስቴትስ እና በብሪታንያ መካከል ያለውን ልዩ ግንኙነት በመቃወም እና የፈረንሳይን የውጭ እና የጸጥታ ነፃነት ለማስጠበቅ ከጋራ ወታደራዊ እዝ ራሷን አገለለች። ፖሊሲዎች. በኒኮላስ ሳርኮዚ ዘመን፣ ፈረንሳይ በኤፕሪል 4 ቀን 2009 የኔቶ የጋራ ወታደራዊ እዝ እንደገና ተቀላቅላለች። እ.ኤ.አ. በ 1990 ዎቹ መጀመሪያ ላይ ሀገሪቱ በፈረንሳይ ፖሊኔዥያ በድብቅ የኒውክሌር ሙከራ ስታደርግ ከሌሎች ሀገራት ከፍተኛ ትችት አቀረበች። ፈረንሳይ እ.ኤ.አ. በ2003 የኢራቅን ወረራ አጥብቃ ተቃወመች፣ ከዩናይትድ ስቴትስ እና ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነት አሻከረ። ፈረንሳይ በቀድሞው የአፍሪካ ቅኝ ግዛቶቿ (ፍራንቻሪክ) ጠንካራ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖ ያላት ሲሆን ለአይቮሪ ኮስት እና ቻድ የሰላም ማስከበር ተልእኮዎች የኢኮኖሚ እርዳታ እና ወታደሮችን አቅርባለች። በቅርቡ በቱዋሬግ ኤምኤንኤልኤ የሰሜን ማሊ የነፃነት አዋጅ በአንድ ወገን ነፃ መውጣቱን ካወጀ በኋላ እና በመቀጠልም ክልላዊ የሰሜን ማሊ ከአንሳርዲን እና ን ጨምሮ ከበርካታ እስላማዊ ቡድኖች ጋር ግጭት ከተፈጠረ በኋላ፣ ፈረንሳይ እና ሌሎች የአፍሪካ መንግስታት የማሊ ጦር እንደገና ለመቆጣጠር እንዲረዳቸው ጣልቃ ገብተዋል። እ.ኤ.አ. በ2017 ፈረንሳይ ከዩናይትድ ስቴትስ፣ ከጀርመን እና ዩናይትድ ኪንግደም ቀጥላ በፍፁም የዓለም አራተኛዋ ትልቅ የልማት ዕርዳታ ለጋሽ ነበረች። ይህ የ 0.43% ይወክላል፣ ከ 12ኛ ከፍተኛ ነው። ዕርዳታ የሚሰጠው ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት በዋናነት ሰብአዊ ፕሮጄክቶችን በሚሸፍነው የመንግስት የፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ ሲሆን “መሠረተ ልማትን ማጎልበት፣ የጤና እንክብካቤ እና የትምህርት ተደራሽነት፣ ተገቢ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን ተግባራዊ ማድረግ እና የህግ የበላይነትን ማጠናከር ላይ ትኩረት በማድረግ ነው። እና ዲሞክራሲ" የፈረንሳይ ጦር ኃይሎች (የፈረንሳይ የጦር ኃይሎች) በሪፐብሊኩ ፕሬዝደንት እንደ የበላይ አዛዥ ሆነው የፈረንሣይ ወታደራዊ እና ወታደራዊ ኃይል ናቸው። እነሱም የፈረንሳይ ጦር (አርሜይ ዴ ቴሬ)፣ የፈረንሳይ ባህር ኃይል (ማሪን ናሽናል፣ ቀደም ሲል አርሜይ ደ ሜር ይባላሉ)፣ የፈረንሳይ አየር እና ስፔስ ሃይል (የአየር እና የጠፈር ኃይል) እና ብሄራዊ የሚባል ወታደራዊ ፖሊስን ያቀፉ ናቸው። ጀንደርሜሪ (ብሔራዊ ጄንዳርሜሪ) በፈረንሳይ ገጠራማ አካባቢዎች የሲቪል ፖሊስ ግዴታዎችን የሚፈጽም ነው። አንድ ላይ ሆነው በዓለም ላይ ካሉት ታላላቅ የታጠቁ ኃይሎች እና በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ካሉት ትልቁ ናቸው። እ.ኤ.አ. በ 2018 በክሬዲት ስዊስ የተደረገ ጥናት የፈረንሳይ ጦር ኃይሎች ከሩሲያ ቀጥሎ በስድስተኛ ደረጃ እና በአውሮፓ ውስጥ በጣም ሀይለኛ ወታደራዊ ደረጃን አግኝተዋል ። ጄንዳርሜሪ የፈረንሳይ ጦር ኃይሎች ዋና አካል ቢሆንም (ጀንደሮች የሙያ ወታደር ናቸው) እና ስለዚህ በጦር ኃይሎች ሚኒስቴር ቁጥጥር ስር ሆኖ ከሲቪል ፖሊስ ተግባራቱ ጋር እስከ ተወካዩ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር ተያይዟል ። ያሳስበዋል። ጄንዳርሜሪ እንደ አጠቃላይ የፖሊስ ሃይል ሆኖ ሲሰራ የብሄራዊ ጀንዳርሜሪ የፓራሹት ጣልቃ ገብነት ክፍለ ጦር (የብሔራዊ ጄንዳርሜሪ ጣልቃ ገብነት ፓራትሮፐር ስኳድሮን።) የብሄራዊ የጀንዳርሜይ ጣልቃ ገብነት ቡድን (ቡድንየብሔራዊ ጄንዳርሜሪ ጣልቃገብነት) የሽብርተኛ ክፍሎችን ያጠቃልላል። ለወንጀል ጥያቄዎች ኃላፊነት ያለው የብሔራዊ ጄንዳርሜሪ (ክፍል ደ ሬቸርቼ ዴ ላ ጄንዳርሜሪ ናሽናል) የፍለጋ ክፍሎች እና የብሔራዊ ጂንዳርሜሪ ሞባይል ብርጌዶች ( የብሔራዊ ጄንዳርሜሪ ተንቀሳቃሽ ብርጌዶች ወይም በአጭሩ ጀንደርሜሪ ሞባይል) ተግባር ያላቸው የህዝብን ሰላም ለማስጠበቅ። የሚከተሉት ልዩ ክፍሎች የጄንዳርሜሪ አካል ናቸው፡ ዋና ዋና የፈረንሳይ ተቋማትን የሚያስተናግዱ የህዝብ ሕንፃዎችን የሚከላከለው የሪፐብሊካን ዘበኛ (ጋርዴ ሬፑብሊካይን)፣ የባህር ዳርቻ ጠባቂ (የጄንዳርሜሪ ባህር) እንደ የባህር ዳርቻ ጠባቂ፣ የፕሮቮስት አገልግሎት ()፣ እንደ ወታደራዊ ሆኖ ያገለግላል። የጄንዳርሜሪ ፖሊስ ቅርንጫፍ።የፈረንሳይ የስለላ ክፍሎችን በተመለከተ የውጭ ደህንነት ዳይሬክቶሬት ጄኔራል () በመከላከያ ሚኒስቴር ሥልጣን ስር የጦር ኃይሎች አካል ተደርጎ ይቆጠራል. ሌላው፣ የውስጥ ኢንተለጀንስ ማዕከላዊ ዳይሬክቶሬት () የብሔራዊ ፖሊስ ኃይል ክፍል ነው () ስለዚህ በቀጥታ ለውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሪፖርት ያደርጋል። ከ 1997 (አውሮፓውያን) ጀምሮ ምንም አይነት ብሄራዊ የውትድርና ምዝገባ የለም. ፈረንሳይ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባል እና ከ 1960 ጀምሮ እውቅና ያለው የኒውክሌር መንግስት ነች። ፈረንሳይ አጠቃላይ የኑክሌር-ሙከራ-ክልከላ ስምምነትን (ሲቲቢቲ) ፈርማ አፅድቃ የኑክሌር-መስፋፋት-አልባ ስምምነትን ተቀበለች። እ.ኤ.አ. በ2018 የፈረንሣይ አመታዊ ወታደራዊ ወጪ 63.8 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ውስጥ 2.3% ሲሆን ይህም ከአሜሪካ፣ ቻይና፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ህንድ ቀጥላ አምስተኛዋ ወታደራዊ ወጪ አስመዝግቧል። የፈረንሳይ የኑክሌር መከላከያ (የቀድሞው "" በመባል የሚታወቀው) በፍፁም ነፃነት ላይ የተመሰረተ ነው. የአሁኑ የፈረንሳይ የኒውክሌር ኃይል አራት ትሪምፋንት ክፍል ሰርጓጅ መርከቦችን ያቀፈ ሲሆን በባህር ሰርጓጅ የተወነጨፉ ባለስቲክ ሚሳኤሎች የታጠቁ ናቸው። ከባህር ሰርጓጅ መርከቦች በተጨማሪ፣ ፈረንሳይ ወደ 60 የሚጠጉ ከመካከለኛ ርቀት አየር ወደ መሬት ሚሳኤሎች ከኒውክሌር ጦር ጭንቅላት ጋር እንዳላት ይገመታል፣ ከነዚህም ውስጥ 50 ያህሉ በአየር እና ህዋ ሃይል ሚራጅ 2000 የረዥም ርቀት የኑክሌር ጥቃትን በመጠቀም የተሰማሩ ናቸው። አውሮፕላኖች፣ ወደ 10 የሚጠጉት በፈረንሳይ የባህር ኃይል ሱፐር ኤቴንዳርድ ሞዳኒሴ (ኤስኤም) ጥቃት አውሮፕላኖች በኑክሌር ኃይል ከሚሰራው ቻርለስ ደ ጎል የሚንቀሳቀሱ ናቸው። አዲሱ 3 አውሮፕላን ቀስ በቀስ ሁሉንም እና በኒውክሌር አድማ ሚና በተሻሻለ ሚሳይል በኑክሌር ጦር መሪ ይተካል። ፈረንሳይ በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ የኤሮስፔስ ኢንዱስትሪዎች አንዱ ያለው ዋና ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች አሏት። የእሱ ኢንዱስትሪዎች እንደ ራፋሌ ተዋጊ ፣ ቻርለስ ደ ጎል አውሮፕላን ተሸካሚ ፣ ኤክሶኬት ሚሳይል እና ሌክለር ታንክ እና ሌሎች መሳሪያዎችን አምርተዋል። ፈረንሳይ ከዩሮ ተዋጊ ፕሮጄክት ብታወጣም በአውሮፓ የጋራ ፕሮጀክቶች ላይ እንደ ዩሮኮፕተር ነብር ፣ ሁለገብ ፍሪጌት ፣ የ ማሳያ እና ኤርባስ በንቃት ኢንቨስት እያደረገች ነው። ፈረንሣይ የጦር መሣሪያ ሻጭ ግንባር ቀደም ስትሆን፣ አብዛኛዎቹ የጦር መሣሪያዎቿ ዲዛይኖች ከኒውክሌር ኃይል ማመንጫ መሳሪያዎች በስተቀር ለወጪ ገበያ ዝግጁ ናቸው። ፈረንሣይ የሳይበር ደህንነት አቅሟን ያለማቋረጥ በማዳበር ላይ ነች፣ይህም በመደበኛነት ከየትኛውም የዓለም ሀገር በጣም ጠንካራ ከሚባሉት ውስጥ ይመደባል። በየጁላይ 14 በፓሪስ የሚካሄደው የባስቲል ቀን ወታደራዊ ሰልፍ በእንግሊዘኛ ተናጋሪ አገሮች የባስቲል ቀን ተብሎ የሚጠራው (በፈረንሳይ ፊቴ ብሄራዊ ተብሎ የሚጠራው) በአውሮፓ ውስጥ እጅግ ጥንታዊ እና ትልቁ መደበኛ ወታደራዊ ሰልፍ ነው። ሌሎች ትናንሽ ሰልፎች በመላ አገሪቱ ተደራጅተዋል። ፈረንሳይ የዳበረ፣ ከፍተኛ ገቢ ያለው ቅይጥ ኢኮኖሚ አላት፣ በመንግስት ተሳትፎ፣ በኢኮኖሚ ልዩነት፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል እና ከፍተኛ ፈጠራ። ለሁለት ምዕተ ዓመታት ያህል፣ የፈረንሳይ ኢኮኖሚ በተከታታይ በዓለም አቀፍ ደረጃ አሥር ካሉት ትላልቅ ደረጃዎች ውስጥ አስቀምጧል። በአሁኑ ጊዜ የኃይል እኩልነትን በመግዛት ከዓለም ዘጠነኛ-ትልቁ ላይ ተቀምጧል፣ በስመ ሰባተኛ-ትልቁ፣ እና በአውሮፓ ህብረት በሁለቱም መለኪያዎች ሁለተኛ-ትልቅ ነው። በኢንዱስትሪ የበለጸጉ አገሮች ቡድን ሰባት፣ የኤኮኖሚ ትብብርና ልማት ድርጅት () እና የሃያ ታላላቅ ኢኮኖሚዎች ቡድን አባል በመሆን ፈረንሳይ የኤኮኖሚ ኃይል ነች። የፈረንሳይ ኢኮኖሚ በጣም የተለያየ ነው; አገልግሎቶች ከሁለቱም የሰው ኃይል እና የሀገር ውስጥ ምርት ውስጥ ሁለት ሶስተኛውን የሚወክሉ ሲሆን የኢንዱስትሪው ዘርፍ ደግሞ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እና ተመሳሳይ የስራ ድርሻ አምስተኛውን ይይዛል። ፈረንሳይ በአውሮፓ በሶስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ የአምራችነት ሀገር ስትሆን ከጀርመን እና ከጣሊያን በመቀጠል ከአለም አቀፍ የማኑፋክቸሪንግ ምርት በ1.9 በመቶ ከአለም ስምንተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት () ከ2 በመቶ በታች የሚሆነው በአንደኛ ደረጃ ዘርፍ ማለትም በግብርና ነው። ሆኖም የፈረንሣይ የግብርና ዘርፍ በዋጋ ትልቅ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ሲሆን በአጠቃላይ የምርት ደረጃ የአውሮፓ ህብረትን ይመራል። እ.ኤ.አ. በ 2018 ፈረንሳይ በአለም አምስተኛዋ ትልቅ የንግድ ሀገር እና በአውሮፓ ውስጥ ሁለተኛዋ ነበረች ፣ ወደ ውጭ የሚላከው እሴት ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት አምስተኛውን ይወክላል። በዩሮ ዞን እና በሰፊው የአውሮፓ ነጠላ ገበያ አባልነቱ የካፒታል፣ የሸቀጦች፣ አገልግሎቶች እና የሰለጠነ የሰው ሃይል ተደራሽነትን ያመቻቻል። በአንዳንድ ኢንዱስትሪዎች ላይ በተለይም በግብርና ላይ የጥበቃ አቀንቃኝ ፖሊሲዎች ቢኖሩም ፈረንሳይ በአጠቃላይ ኢኮኖሚዋን ለማሳደግ በአውሮፓ ነፃ ንግድን እና የንግድ ውህደትን በማጎልበት ግንባር ቀደም ሚና ተጫውታለች። እ.ኤ.አ. በ 2019 በአውሮፓ አንደኛ እና ከአለም 13 ኛ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ፣ የአውሮፓ ሀገራት እና ዩናይትድ ስቴትስ ምንጮች ግንባር ቀደም ሆነዋል ። የፈረንሳይ ባንክ እንደገለጸው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በቀዳሚነት የተቀበሉት ማኑፋክቸሪንግ፣ ሪል ስቴት፣ ፋይናንስ እና ኢንሹራንስ ናቸው። የፓሪስ ክልል በአውሮፓ ውስጥ ከፍተኛው የብዝሃ-ዓለም ኩባንያዎች ስብስብ አለው። በዲሪጊዝም አስተምህሮ መንግስት በታሪክ በኢኮኖሚው ውስጥ ትልቅ ሚና ተጫውቷል; እንደ አመላካች እቅድ እና ሀገር አቀፍ ፖሊሲዎች ለሶስት አስርት አመታት ታይቶ ማይታወቅ ከጦርነቱ በኋላ የኢኮኖሚ እድገት ትሬንቴ ግሎሪየስ በመባል ይታወቃል። እ.ኤ.አ. በ 1982 ከፍተኛ ደረጃ ላይ በነበረበት ጊዜ የመንግስት ሴክተር አንድ አምስተኛውን የኢንዱስትሪ ሥራ እና ከአራት-አምስተኛው የብድር ገበያን ይይዛል። ከ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ጀምሮ ፈረንሳይ ደንቦችን እና በኢኮኖሚው ውስጥ የመንግስት ተሳትፎን ፈታች ፣ አብዛኛዎቹ መሪ ኩባንያዎች አሁን በግል ባለቤትነት ተያዙ ። የመንግስት ባለቤትነት አሁን የሚቆጣጠረው በትራንስፖርት፣ በመከላከያ እና በስርጭት ብቻ ነው። ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን እና ፕራይቬታይዜሽንን ለማስፋፋት የታቀዱ ፖሊሲዎች የፈረንሳይን ኢኮኖሚ በአለም አቀፍ ደረጃ አሻሽለዋል፡ በ2020 ብሉምበርግ ፈጠራ ኢንዴክስ ከአለም 10 በጣም ፈጠራ ካላቸው ሀገራት አንዷ ነች እና 15ኛው በጣም ፉክክር ውስጥ ትገኛለች። የ2019 ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ሪፖርት (ከ2018 ጀምሮ ሁለት ቦታዎች)። እንደ አይኤምኤፍ ዘገባ፣ ፈረንሳይ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ 30ኛ ሆናለች፣ በአንድ ነዋሪ ወደ 45,000 ዶላር ገደማ ይዛለች። በሰው ልጅ ልማት መረጃ ጠቋሚ ውስጥ 23 ኛ ደረጃን አስቀምጧል, ይህም በጣም ከፍተኛ የሰው ልጅ እድገትን ያሳያል. የሙስና ግንዛቤዎች ጠቋሚ እ.ኤ.አ. በ 2012 ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ፈረንሳይ በተከታታይ ከ 30 ዝቅተኛ ሙስና ሀገራት ተርታ የምትመድበው የህዝብ ሙስና ከአለም ዝቅተኛው ነው። በ2021 22ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፣ ካለፈው አመት አንድ ደረጃ ከፍ ብሏል። ፈረንሣይ በአውሮፓ ሁለተኛዋ በምርምር እና በልማት ወጪ ከ2 በመቶ በላይ የሆነች ሀገር ነች። በአለም አቀፍ ደረጃ 12 ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል. የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ባንክ እና ኢንሹራንስ የኢኮኖሚው አስፈላጊ አካል ናቸው። በ2020 ባንኪንግ ባልሆኑ ንብረቶች የአለም ሁለተኛው ትልቁ የኢንሹራንስ ኩባንያ ነው። ከ2011 ጀምሮ በደንበኞቻቸው በትብብር ባለቤትነት የተያዙት ሦስቱ ትላልቅ የፋይናንስ ተቋማት ፈረንሣይ ነበሩ፡ ክሬዲት አግሪኮል፣ ግሩፕ ካይሴ ዲ ኢፓርግ እና ግሩፕ ካይሴ ዲኢፓርኝ። በ2020 በኤስ& ግሎባል ገበያ ኢንተለጀንች ባወጣው ሪፖርት መሠረት የፈረንሳይ ግንባር ቀደም ባንኮች ቢኤንፒ ፓሪባስ እና ክሬዲት አግሪኮል በንብረት ከዓለም 10 ታላላቅ ባንኮች መካከል ሲሆኑ ሶሺየት ጄኔራል እና ግሩፕ ቢፒሲኢ በዓለም አቀፍ ደረጃ 17ኛ እና 19ኛ ደረጃን ይዘዋል። የፓሪስ የአክሲዮን ልውውጥ (ፈረንሳይኛ: ላ ዴ ፓሪስ) በ 1724 በሉዊስ የተፈጠረ በዓለም ላይ ካሉት እጅግ ጥንታዊ ከሆኑት አንዱ ነው ። በ 2000 ከአምስተርዳም እና ከብራሰልስ አጋሮች ጋር ተቀላቅሎ ፈጠረ ፣ በ 2007 ከአዲሱ ጋር ተቀላቅሏል ። ዮርክ የአክሲዮን ልውውጥ ለመመስረት, በዓለም ትልቁ የአክሲዮን ልውውጥ. ዩሮኔክስት ፓሪስ፣ የ የፈረንሳይ ቅርንጫፍ፣ ከለንደን ስቶክ ልውውጥ ቀጥሎ በአውሮፓ ሁለተኛው ትልቅ የስቶክ ልውውጥ ገበያ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2018 (አውሮፓውያን) 89 ሚሊዮን ዓለም አቀፍ የቱሪስት መዳረሻ ያላት ፈረንሳይ ከስፔን (83 ሚሊዮን) እና ከዩናይትድ ስቴትስ (80 ሚሊዮን) በቀዳሚ የዓለማችን የቱሪስት መዳረሻ ነች። ነገር ግን በጉብኝት ጊዜ አጭር በመሆኑ ከቱሪዝም ከሚገኘው ገቢ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል። በጣም ታዋቂው የቱሪስት ድረ-ገጾች (ዓመታዊ ጎብኝዎች) ያካትታሉ፡- ኢፍል ታወር (6.2 ሚሊዮን)፣ ቻቶ ዴ ቬርሳይ (2.8 ሚሊዮን)፣ ሙዚየም ብሔራዊ (2 ሚሊዮን)፣ ፖንት ዱ ጋርድ (1.5 ሚሊዮን)፣ አርክ ደ ትሪምፌ ሚሊዮን)፣ ሞንት ሴንት ሚሼል (1 ሚሊዮን)፣ ሴንት-ቻፔል ፣ ቻቴው ዱ ሃውት-ኬኒግስቦርግ ፣ ፑይ ደ ዶሜ ፣ ሙሴ ፒካሶ እና ካርካሶንን። ፈረንሳይ እና በተለይም ፓሪስ በዓለም ላይ ለመሄድ እና ለመጎብኘት ብዙ የቱሪስት ቦታዎች አሏት። የኤፊሌ ግንብ የእንደዚህ አይነት ቦታ እና ታሪካዊ ሕንፃ ምሳሌ ነው።ፈረንሳይ፣ በተለይም ፓሪስ፣ በዓለም ላይ በብዛት የሚጎበኘውን የጥበብ ሙዚየም (5.7 ሚሊዮን) ሉቭርን ጨምሮ፣ ሙሴ ዲ ኦርሳይ (2.1 ሚሊዮን)፣ በአብዛኛው ለኢምፕሬሽኒዝም ያደሩ፣ የዓለማችን ትልልቅ እና ታዋቂ ሙዚየሞች አሏት። ሙሴ ደ (1.02 ሚሊዮን)፣ እሱም በክላውድ ሞኔት ስምንት ትላልቅ የውሃ ሊሊ ሥዕሎች፣ እንዲሁም ሴንተር ጆርጅስ ፖምፒዱ (1.2 ሚሊዮን)፣ ለዘመናዊ ሥነ ጥበብ የተዘጋጀ። ዲዝኒላንድ ፓሪስ በ2009 (አውሮፓውያን) ወደ ሪዞርቱ የዲስኒላንድ ፓርክ እና የዋልት ዲስኒ ስቱዲዮ ፓርክ 15 ሚሊዮን ጎብኝዎች ያሉት የአውሮፓ በጣም ታዋቂው የመዝናኛ ፓርክ ነው። ፈረንሣይ በታሪክ ከዓለም ዋና ዋና የግብርና ማዕከላት አንዷ ሆና “ዓለም አቀፍ የግብርና ኃይል” ሆና ቆይታለች። “የአሮጌው አህጉር ጎተራ” የሚል ቅጽል ስም ተሰጥቶታል፣ ከጠቅላላው የመሬት ስፋት ከግማሽ በላይ የሚሆነው የእርሻ መሬት ነው፣ ከዚህ ውስጥ 45 በመቶው እንደ እህል ላሉ ቋሚ የመስክ ሰብሎች ይውላል። የሀገሪቱ የተለያዩ የአየር ንብረት፣ ሰፊ የእርሻ መሬት፣ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ እና የአውሮፓ ህብረት ድጎማዎች በአውሮፓ ቀዳሚ ግብርና አምራችና ላኪ አድርጓታል። ከአውሮፓ ህብረት የግብርና ምርት አንድ አምስተኛውን ይይዛል፣ ይህም ከቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬዎች እና ወይን ውስጥ አንድ ሶስተኛውን ይጨምራል። እ.ኤ.አ. በ 2017 ፈረንሣይ በበሬ ሥጋ እና ጥራጥሬዎች በአውሮፓ ቀዳሚ ሆናለች ። በወተት እና በአክቫካልቸር ሁለተኛ; ሦስተኛው ደግሞ በዶሮ እርባታ፣ ፍራፍሬ፣ አትክልት፣ እና በተመረቱ የቸኮሌት ምርቶች። ፈረንሣይ ከ18-19 ሚሊዮን በአውሮፓ ህብረት ትልቁ የከብት መንጋ አላት። ፈረንሳይ ከ 7.4 ቢሊዮን ዩሮ በላይ የንግድ ትርፍ በማስገኘት ከዓለም ስድስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው የግብርና ምርት ነው። በቀዳሚነት ወደ ውጭ የሚላከው የግብርና ምርት ስንዴ፣ የዶሮ እርባታ፣ የወተት ሃብት፣ የበሬ ሥጋ፣ የአሳማ ሥጋ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑ ምርቶች በተለይም መጠጦች ናቸው። ፈረንሳይ ከቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ እና አሜሪካ በመቀጠል አምስተኛዋ ስንዴ አብቃይ ነች። የተፈጥሮ የምንጭ ውሃ፣ ተልባ፣ ብቅል እና ድንች ወደ ውጭ በመላክ በዓለም ቀዳሚ ነች። እ.ኤ.አ. በ 2020 ፈረንሳይ ከ 61 ቢሊዮን ዩሮ በላይ የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ ልካለች ፣ በ 2000 ከ 37 ቢሊዮን ዩሮ ጋር ሲነፃፀር ። ፈረንሳይ ቢያንስ በስድስተኛው መቶ ዘመን ዓ.ዓ. የጥንት የቪቪካልቸር ማዕከል ነበረች። እንደ ሻምፓኝ እና ቦርዶ ያሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑ ብዙ ዓይነት ዝርያዎች ያሉት ወይን በዓለም ሁለተኛው ትልቁ አምራች ነው። የቤት ውስጥ ፍጆታም ከፍተኛ ነው, በተለይም የሮሴ. ፈረንሳይ ሮምን በዋነኝነት የምታመርተው እንደ ማርቲኒክ፣ ጓዴሎፔ እና ላ ካሉ የባህር ማዶ ግዛቶች ነው። ከሌሎች የበለጸጉ አገሮች አንጻር ግብርና የፈረንሳይ ኢኮኖሚ አስፈላጊ ዘርፍ ነው፡ ከነቃ ሕዝብ 3.8% የሚሆነው በግብርና ሥራ ላይ የሚውል ሲሆን አጠቃላይ የአግሪ-ምግብ ኢንዱስትሪ ግን 4.2% የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ምርት በ2005 ነው። ፈረንሳይ የአውሮፓ ህብረት ትልቁ ተቀባይ ሆና ትቀጥላለች። ከ 2007 እስከ 2019 (አውሮፓዊ) አማካኝ 8 ቢሊዮን ዩሮ ዓመታዊ የግብርና ድጎማዎችን ይቀበላል። እ.ኤ.አ. በ2008 29,473 ኪሎ ሜትር (18,314 ማይል) የሚዘረጋው የፈረንሳይ የባቡር መስመር በምዕራብ አውሮፓ ከጀርመን ቀጥሎ ሁለተኛው ሰፊ ነው። የሚንቀሳቀሰው በ ሲሆን ከፍተኛ ፍጥነት ያላቸው ባቡሮች ታሊስ፣ ዩሮስታር እና ቲጂቪ በሰአት 320 ኪሜ (199 ማይል በሰአት) ይጓዛሉ። ኤውሮስታር፣ ከዩሮታነል ሹትል ጋር፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር በቻናል ዋሻ በኩል ይገናኛል። የባቡር ትስስሮች ከአንዶራ በስተቀር በአውሮፓ ውስጥ ካሉ ሌሎች አጎራባች አገሮች ጋር አለ። የከተማ ውስጥ ግንኙነቶች እንዲሁ በደንብ የተገነቡ ናቸው ፣ አብዛኛዎቹ ዋና ዋና ከተሞች የምድር ውስጥ ወይም የትራምዌይ አገልግሎቶች የአውቶቡስ አገልግሎቶችን ያሟላሉ። በፈረንሳይ ወደ 1,027,183 ኪሎ ሜትር (638,262 ማይል) አገልግሎት የሚሰጥ የመንገድ መንገድ አለ፣ ይህም ከአውሮፓ አህጉር እጅግ ሰፊው አውታረ መረብ ነው። የፓሪስ ክልል ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ጋር በሚያገናኙት በጣም ጥቅጥቅ ባለ የመንገድ እና አውራ ጎዳናዎች መረብ የተሸፈነ ነው። የፈረንሳይ መንገዶች ከአጎራባች ቤልጂየም፣ ሉክሰምበርግ፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ጣሊያን፣ ስፔን፣ አንዶራ እና ሞናኮ ካሉ ከተሞች ጋር በማገናኘት ከፍተኛ የሆነ አለምአቀፍ ትራፊክን ያስተናግዳሉ። ምንም ዓመታዊ ክፍያ ወይም የመንገድ ግብር የለም; ነገር ግን፣ በአብዛኛው በግል ባለቤትነት የተያዙ አውራ ጎዳናዎች አጠቃቀም ከትላልቅ ኮምዩኖች አካባቢ በስተቀር በክፍያ ነው። አዲሱ የመኪና ገበያ እንደ ፣ እና ባሉ የሀገር ውስጥ ብራንዶች የተያዘ ነው። ፈረንሳይ የዓለማችን ረጅሙ ድልድይ ይዛለች እና እንደ ያሉ ብዙ ጠቃሚ ድልድዮችን ገንብታለች። በናፍጣ እና በቤንዚን የተቃጠሉ መኪናዎች እና የጭነት መኪናዎች የሀገሪቱን የአየር ብክለት እና የግሪንሀውስ ጋዝ ልቀትን ትልቅ ክፍል ያስከትላሉ.በፈረንሳይ 464 አውሮፕላን ማረፊያዎች አሉ።በፓሪስ አካባቢ የሚገኘው የቻርለስ ደ ጎል አውሮፕላን ማረፊያ በአገሪቱ ውስጥ ትልቁ እና በጣም በተጨናነቀ አየር ማረፊያ ነው ፣ብዙውን ታዋቂ እና የንግድ ትራፊክ የሚያስተናግድ እና ፓሪስን ከሁሉም የዓለም ዋና ዋና ከተሞች ጋር ያገናኛል። ምንም እንኳን ብዙ የግል አየር መንገድ ኩባንያዎች የሀገር ውስጥ እና የአለም አቀፍ የጉዞ አገልግሎቶችን ቢሰጡም ኤር ፈረንሳይ የብሔራዊ አየር መንገድ ነው። በፈረንሳይ ውስጥ አስር ዋና ዋና ወደቦች አሉ ፣ ትልቁ በማርሴይ ነው ፣ እሱም ደግሞ የሜዲትራኒያን ባህርን የሚያዋስነው ። 12,261 ኪሎ ሜትር (7,619 ማይል) የውሃ መንገዶች ፈረንሳይን ያቋርጣሉ ፣ የሜዲትራኒያን ባህርን ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር የሚያገናኘው ቦይ ዱ ሚዲ በጋሮን ወንዝ በኩል ውቅያኖስ. ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ከመካከለኛው ዘመን ጀምሮ ፈረንሳይ ለሳይንሳዊ እና ቴክኖሎጂ ስኬት ትልቅ አስተዋፅዖ አድርጋለች። በ 11 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ፈረንሳዊው የተወለዱት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሲልቬስተር ዳግማዊ የአባከስ እና የጦር ሰራዊት ሉል እንደገና አስተዋውቀዋል, እና የአረብ ቁጥሮችን እና ሰዓቶችን ለብዙ አውሮፓ አስተዋውቀዋል. በ 12 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ የተመሰረተው የፓሪስ ዩኒቨርሲቲ አሁንም እጅግ በጣም ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ነው. በምዕራቡ ዓለም ውስጥ አስፈላጊ የትምህርት ተቋማት. በ 17 ኛው ክፍለ ዘመን የሒሳብ ሊቅ ሬኔ ዴካርትስ ሳይንሳዊ እውቀትን ለመቅሰም ዘዴ ሆኖ ምክንያታዊነትን ፈር ቀዳጅ ሆኖ ሲያገለግል ብሌዝ ፓስካል በፕሮባቢሊቲ እና በፈሳሽ መካኒኮች ሥራው ታዋቂ ሆነ። ሁለቱም በዚህ ወቅት በአውሮፓ ውስጥ ያበበው የሳይንሳዊ አብዮት ቁልፍ ሰዎች ነበሩ። የፈረንሳይ ሳይንሳዊ ምርምርን ለማበረታታት እና ለመጠበቅ በ 17 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ በሉዊ አሥራ አራተኛ የተመሰረተው የፈረንሳይ የሳይንስ አካዳሚ በታሪክ ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ ብሔራዊ የሳይንስ ተቋማት አንዱ ነበር; በሚቀጥሉት ሁለት መቶ ዓመታት በአውሮፓ ውስጥ በሳይንሳዊ እድገቶች ግንባር ቀደም ነበር ። የኢንላይንመንት ዘመን በባዮሎጂስት ቡፎን ሥራ ተለይቶ ይታወቃል ፣ ሥነ-ምህዳራዊ ተተኪነትን ከተገነዘቡ የመጀመሪያዎቹ የተፈጥሮ ተመራማሪዎች አንዱ እና ኬሚስት ላቮይየር በቃጠሎ ውስጥ የኦክስጅንን ሚና ባወቀ። ዲዴሮት እና ዲአሌምበርት ኢንሳይክሎፔዲ አሳትመዋል ይህም ለህዝቡ በዕለት ተዕለት ኑሮው ላይ ሊተገበር የሚችል "ጠቃሚ እውቀት" እንዲያገኙ ለማድረግ ያለመ ነው. በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን የኢንዱስትሪ አብዮት በፈረንሳይ አስደናቂ የሳይንስ እድገቶችን ታይቷል, አውጉስቲን ፍሬስኔል ዘመናዊ ኦፕቲክስን በመመሥረት, ሳዲ ካርኖት የቴርሞዳይናሚክስ መሰረት በመጣል እና ሉዊ ፓስተር የማይክሮባዮሎጂ ፈር ቀዳጅ። በጊዜው የነበሩ ሌሎች ታዋቂ የፈረንሣይ ሳይንቲስቶች ስማቸው በአይፍል ግንብ ላይ ተጽፎ ነበር። የ 20 ኛው ክፍለ ዘመን ታዋቂ የፈረንሳይ ሳይንቲስቶች የሂሳብ ሊቅ እና የፊዚክስ ሊቅ ሄንሪ ፖይንካርሬ; የፊዚክስ ሊቃውንት ሄንሪ ቤኬሬል ፣ ፒየር እና ማሪ ኩሪ ፣ በሬዲዮአክቲቭ ሥራቸው ዝነኛ ሆነው ይቀጥላሉ ። የፊዚክስ ሊቅ ፖል ላንግቪን; እና የቫይሮሎጂስት ሉክ ሞንታግኒየር, የኤችአይቪ ኤድስ ተባባሪ. እ.ኤ.አ. በ1998 በሊዮን ውስጥ የእጅ ንቅለ ተከላ የተሰራው ዣን ሚሼል ዱበርናርድን ባካተተው አለም አቀፍ ቡድን ሲሆን በመቀጠልም የመጀመሪያውን የተሳካ ባለ ሁለት እጅ ንቅለ ተከላ አድርጓል። ቴሌ ቀዶ ጥገና ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው በዣክ ማሬስካውዝ በሚመሩ የፈረንሳይ የቀዶ ጥገና ሐኪሞች እ.ኤ.አ. ሴፕቴምበር 7 ቀን 2001 በአትላንቲክ ውቅያኖስ አቋርጦ ነበር። የፊት ንቅለ ተከላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው እ.ኤ.አ. ህዳር 27 ቀን 2005 በዶክተር በርናርድ ዴቫቼሌ ነበር። ፈረንሳይ የኒውክሌር አቅምን በማሳካት አራተኛዋ ሀገር ነበረች እና በዓለም ላይ በሦስተኛ ደረጃ ትልቁ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ አላት። በሲቪል ኑክሌር ቴክኖሎጂ ውስጥም መሪ ነው. ፈረንሳይ የራሷን የጠፈር ሳተላይት ያመጠቀች ከሶቪየት ዩኒየን እና ከዩናይትድ ስቴትስ ቀጥሎ ሶስተኛዋ ሀገር ነበረች እና የንግድ ማስጀመሪያ አገልግሎት ሰጪ አሪያንስፔስ የመጀመሪያዋ ነች። የፈረንሣይ ብሔራዊ የጠፈር ፕሮግራም፣ ሲኤንኤስ፣ በዓለም ላይ ሦስተኛው ጥንታዊ፣ እና በአውሮፓ ውስጥ እጅግ ጥንታዊ፣ ትልቁ እና በጣም ንቁ ነው። ፈረንሣይ የአውሮፓ የጠፈር ኤጀንሲ () መስራች አባል ነች፣ ከበጀቷ ከሩብ በላይ ለማዋጣት፣ ከማንኛውም አባል ሀገር የበለጠ። ኢዜአ ዋና መሥሪያ ቤቱን ፓሪስ ነው፣ ዋናው የጠፈር ወደብ በፈረንሳይ ጊያና አለው፣ እና በፈረንሳይ የተሰራውን አሪያን 5ን እንደ ዋና ማስጀመሪያ ተሽከርካሪ ይጠቀማል። ኤርባስ፣ ግንባር ቀደም የኤሮስፔስ ኩባንያ እና የዓለማችን ትልቁ የአየር መንገድ አምራች፣ የተቋቋመው በከፊል ከፈረንሳዩ ኩባንያ አኤሮፓቲያሌ ነው፤ ዋናው የንግድ አየር መንገድ ሥራ የሚካሄደው በፈረንሳይ ዲቪዚዮን ኤርባስ ኤስ.ኤ.ኤስ.ፈረንሳይ የአውሮፓ ሲንክሮሮን ራዲየሽን ተቋም፣ ኢንስቲትዩት ላው–ላንጌቪን እና ሚናቴክን ጨምሮ ዋና ዋና አለም አቀፍ የምርምር ተቋማትን ታስተናግዳለች። እንዲሁም በዓለም ላይ ትልቁን ቅንጣት ፊዚክስ ላብራቶሪ የሚያንቀሳቅሰው እና በሦስተኛ ደረጃ ትልቁን አስተዋፅዖ የሚያደርገው ዋና አባል ነው። ፈረንሳይ አቅኚ ሆና አስተናግዳለች ፣ የአለም ትልቁ ሜጋ ፕሮጄክት የሆነውን የኒውክሌር ፊውዥን ሃይልን ለማዳበር የሚደረግን ጥረት። በፈረንሳይ ብሔራዊ የባቡር ኩባንያ የተገነባው , ተከታታይ የዓለም የፍጥነት መዝገቦችን የያዘ ከፍተኛ ፍጥነት ያለው ባቡር ነው; እ.ኤ.አ. በ 2007 574.8 ኪሜ በሰዓት (357.2 ማይል በሰዓት) የፈጣኑ የንግድ ጎማ ያለው ባቡር ሆነ። እ.ኤ.አ. ከ 2021 ጀምሮ ፣ መግነጢሳዊ ሌቪቴሽን በሚጠቀሙ በማግሌቭ ሞዴሎች ብቻ የሚበልጠው በዓለም ላይ ሦስተኛው ፈጣን ባቡር ነው። ምዕራብ አውሮፓ አሁን በ መስመሮች አውታረመረብ አገልግሎት ይሰጣል. የስቴቱ የምርምር ኤጀንሲ ሴንተር ናሽናል ዴ ላ ሬቸርቼ ሳይንቲፊክ () በአውሮፓ ውስጥ ትልቁ የምርምር ተቋም እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ ከሆኑት መካከል አንዱ ነው ። እ.ኤ.አ. በ 2020 ተፈጥሮ ኢንዴክስ መሠረት በዓለም ዙሪያ በሳይንሳዊ መጽሔቶች ላይ በሚታተሙ መጣጥፎች አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ፣ በአጠቃላይ ፈረንሳይ ስድስተኛ-ከፍተኛውን ድርሻ ይዛለች። እ.ኤ.አ. በ2022 ፈረንሳይ በኖቤል ተሸላሚዎች ቁጥር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፣ 70 ፈረንሳውያን የኖቤል ተሸላሚ ሆነዋል። 12 የፈረንሣይ የሂሳብ ሊቃውንት የመስክ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል፣ በዘርፉ እጅግ የላቀ ሽልማት ተሰጥቷቸዋል፣ ከአጠቃላይ ተሸላሚዎች አንድ አምስተኛውን፣ እና ከዩናይትድ ስቴትስ ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል። በ2021 ግሎባል ኢኖቬሽን ኢንዴክስ ፈረንሳይ በ11ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፣ በ2020 12ኛ እና በ2019 16ኛ ጋር ስትነፃፀር፣(ሁሉም ጊዜ በአውሮፓ አጠቃላይ ዘገባ) የከተማ ገጽታ ፈረንሣይ ዘመናዊ ሕንፃዎች ያሏት አገር ስትሆን አሮጌ ሕንፃዎች አገሯ በሥነ ሕንፃ ከበለጸጉት አንዷ ነች። በፓሪስ ከተማ እና በመላ ሀገሪቱ ታሪካዊ ጽናት የሚታይበት ይህ ታሪካዊ ክምችት በጥሩ ሁኔታ የተገነባ ሲሆን ይህም የፈረንሳይ ባህል ከሌሎች አህጉራት ልዩ ያደርገዋል. ፈረንሳይ ለዘመናት የምዕራባውያን የባህል ልማት ማዕከል ሆና ቆይታለች። ብዙ የፈረንሳይ አርቲስቶች በጊዜያቸው በጣም ታዋቂ ከሆኑት መካከል ነበሩ; ፈረንሣይ አሁንም በዓለም ላይ በበለጸገ የባህል ወግ ትታወቃለች። ተከታታይ የፖለቲካ አገዛዞች ሁሌም ጥበባዊ ፈጠራን ያበረታታሉ። በ 1959 የባህል ሚኒስቴር መፈጠር የሀገሪቱን ባህላዊ ቅርሶች ተጠብቆ ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ ረድቷል. የባህል ሚኒስቴር ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ለአርቲስቶች ድጎማ በመስጠት፣ የፈረንሳይ ባህልን በአለም ላይ በማስተዋወቅ፣ በዓላትን እና ባህላዊ ዝግጅቶችን በመደገፍ፣ ታሪካዊ ሀውልቶችን በመጠበቅ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው። የፈረንሳይ መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ የተሰሩ የኦዲዮቪዥዋል ምርቶችን ለመከላከል የባህል ልዩ ሁኔታን በመጠበቅ ረገድም ተሳክቶለታል። ፈረንሳይ በዓመት ከፍተኛውን የቱሪስት ቁጥር ትቀበላለች።በዋነኛነት በግዛቱ ውስጥ ለተተከሉት በርካታ የባህል ተቋማት እና ታሪካዊ ሕንፃዎች ምስጋና ይግባው። በየዓመቱ ከ 50 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን የሚያስተናግዱ 1,200 ሙዚየሞችን ይቆጥራል. በጣም አስፈላጊዎቹ የባህል ቦታዎች የሚተዳደሩት በመንግስት ነው፣ ለምሳሌ በህዝብ ኤጀንሲ ሴንተር ዴስ ሀውልቶች ናሽዮክስ በኩል፣ ወደ 85 የሚጠጉ ብሄራዊ ታሪካዊ ሀውልቶች ተጠያቂ ነው። እንደ ታሪካዊ ሐውልቶች ጥበቃ የተደረገላቸው 43,180 ሕንፃዎች በዋናነት የመኖሪያ ቤቶች (ብዙ ቤተመንግሥቶች) እና ሃይማኖታዊ ሕንፃዎች (ካቴድራሎች፣ ባሲሊካዎች፣ አብያተ ክርስቲያናት)፣ ግን ሐውልቶች፣ መታሰቢያዎች እና የአትክልት ስፍራዎች ያካትታሉ። ዩኔስኮ በፈረንሳይ 45 ቦታዎችን በአለም ቅርስነት አስመዝግባለች። የድሮ አርክቴክቸር በመካከለኛው ዘመን፣ ሥልጣናቸውን ለመለየት በፊውዳል መኳንንት ብዙ የተመሸጉ ቤተመንግስቶች ተገንብተዋል። በሕይወት የተረፉት አንዳንድ የፈረንሳይ ቤተመንግስቶች ቺኖን፣ ቻቴው ዲ አንጀርስ፣ ግዙፉ ቻቴው ዴ ቪንሴንስ እና የካታር ቤተመንግስት የሚባሉት ናቸው። በዚህ ዘመን ፈረንሳይ እንደ አብዛኛው የምዕራብ አውሮፓ የሮማንስክ አርክቴክቸር ትጠቀም ነበር። በፈረንሳይ ከሚገኙት የሮማንስክ አብያተ ክርስቲያናት ታላላቅ ምሳሌዎች መካከል በቱሉዝ የሚገኘው የቅዱስ ሰርኒን ባሲሊካ፣ በአውሮፓ ትልቁ የሮማንስክ ቤተ ክርስቲያን እና የክሉኒ አቢ ቅሪቶች ናቸው። የጎቲክ አርክቴክቸር፣ በመጀመሪያ ስሙ ኦፐስ ፍራንሲጀነም ትርጉሙ “የፈረንሳይ ስራ” ማለት ነው፣ የተወለደው በ-ፈረንሳይ ሲሆን በመላው አውሮፓ የተቀዳ የመጀመሪያው የፈረንሳይ የስነ-ህንፃ ዘይቤ ነበር። ሰሜናዊ ፈረንሳይ የአንዳንድ በጣም አስፈላጊ የጎቲክ ካቴድራሎች እና ባሲሊካዎች መኖሪያ ነው ፣ ከእነዚህም ውስጥ የመጀመሪያው የቅዱስ ዴኒስ ባሲሊካ (እንደ ንጉሣዊ ኔክሮፖሊስ ጥቅም ላይ ይውላል)።ሌሎች ጠቃሚ የፈረንሳይ ጎቲክ ካቴድራሎች ኖትር-ዳም ደ ቻርትረስ እና ኖትር-ዳም ዲ አሚን ናቸው። ነገሥታቱ በሌላ ጠቃሚ የጎቲክ ቤተ ክርስቲያን ዘውድ ተቀዳጁ፡ ኖትር ዴም ደ ሬምስ። ከአብያተ ክርስቲያናት በተጨማሪ፣ የጎቲክ አርክቴክቸር ለብዙ ሃይማኖታዊ ቤተ መንግሥቶች ያገለግል ነበር፣ በጣም አስፈላጊው በአቪኞን የሚገኘው ፓሌይስ ዴስ ፓፔስ ነው። የመቶ አመት ጦርነት የመጨረሻው ድል በፈረንሳይ የስነ-ህንፃ ዝግመተ ለውጥ ውስጥ ወሳኝ ደረጃን አሳይቷል። የፈረንሳይ ህዳሴ ጊዜ ነበር እና ከጣሊያን የመጡ በርካታ አርቲስቶች ወደ የፈረንሳይ ፍርድ ቤት ተጋብዘዋል; ከ1450 ጀምሮ በሎየር ሸለቆ ውስጥ ብዙ የመኖሪያ ቤተ መንግሥቶች ተገንብተው ለመጀመሪያ ጊዜ ቻቶ ዴ ሞንሶሬው ናቸው። እንደነዚህ ያሉት መኖሪያ ቤቶች ቻቴው ዴ ቻምቦርድ፣ ቻቴው ዴ ቼኖንሴው ወይም ቻቴው ዲ አምቦይዝ ነበሩ። ህዳሴውን ተከትሎ እና የመካከለኛው ዘመን መጨረሻ, ባሮክ አርክቴክቸር ባህላዊውን የጎቲክ ዘይቤ ተክቷል. ይሁን እንጂ በፈረንሣይ የባሮክ አርክቴክቸር ከሃይማኖታዊ ሥርዓት ይልቅ በዓለማዊው ጎራ ውስጥ ትልቅ ስኬት አግኝቷል። በዓለማዊው ጎራ ውስጥ የቬርሳይ ቤተ መንግሥት ብዙ ባሮክ ባህሪያት አሉት. የቬርሳይን ማራዘሚያዎች ያዘጋጀው ጁልስ ሃርዱይን ማንሳርት በባሮክ ዘመን ውስጥ በጣም ተደማጭነት ከነበራቸው የፈረንሳይ አርክቴክቶች አንዱ ነበር; እሱ በ በጉልበቱ ታዋቂ ነው። በጣም ከሚያስደንቁ የክልል ባሮክ አርክቴክቸር አንዳንዶቹ ገና ፈረንሣይ ባልሆኑ ቦታዎች እንደ ፕላስ ስታኒስላስ በናንሲ ይገኛሉ። በወታደራዊ ሥነ ሕንፃ በኩል ቫባን በአውሮፓ ውስጥ በጣም ቀልጣፋ ምሽጎችን ነድፎ ተጽዕኖ ፈጣሪ ወታደራዊ አርክቴክት ሆነ። በውጤቱም, የእሱ ስራዎች መኮረጅ በመላው አውሮፓ, አሜሪካ, ሩሲያ እና ቱርክ ውስጥ ይገኛሉ. ከአብዮቱ በኋላ፣ ሪፐብሊካኖች ኒዮክላሲዝምን ደግፈዋል፣ ምንም እንኳን ከአብዮቱ በፊት በፈረንሣይ ውስጥ እንደ ፓሪስ ፓንተን ወይም ካፒቶል ደ ቱሉዝ ካሉ ሕንፃዎች ጋር አስተዋወቀ። በመጀመሪያው የፈረንሳይ ኢምፓየር ጊዜ የተገነባው አርክ ደ ትሪምፌ እና ሴንት ማሪ-ማድሊን የኢምፓየር ዘይቤ አርክቴክቸር ምርጥ ምሳሌን ይወክላሉ። ናፖሊዮን ስር, የከተማ እና የሕንፃ አዲስ ማዕበል ተወለደ; እንደ ኒዮ-ባሮክ ፓላይስ ጋርኒየር ያሉ እጅግ ግዙፍ ሕንፃዎች ተገንብተዋል። በወቅቱ የነበረው የከተማ ፕላን በጣም የተደራጀ እና ጥብቅ ነበር; በተለይም የሃውስማን የፓሪስ እድሳት። ከዚህ ዘመን ጋር የተያያዘው አርክቴክቸር በእንግሊዝኛ ሁለተኛ ኢምፓየር የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፣ ቃሉ ከሁለተኛው የፈረንሳይ ግዛት የተወሰደ ነው። በዚህ ጊዜ በአውሮፓ እና በፈረንሣይ ውስጥ ጠንካራ የጎቲክ ዳግም መነሳት ነበር; ተዛማጅ አርክቴክት ነበር። በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ጉስታቭ ኢፍል ብዙ ድልድዮችን እንደ ጋራቢት ቫያዳክት ቀርጾ በዘመኑ ከፍተኛ ተደማጭነት ከነበራቸው የድልድይ ዲዛይነሮች አንዱ ሆኖ ቆይቷል። በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን የፈረንሳይ-ስዊስ አርክቴክት ሌ ኮርቡሲየር በፈረንሳይ ውስጥ በርካታ ሕንፃዎችን ነድፏል. በቅርብ ጊዜ, የፈረንሳይ አርክቴክቶች ሁለቱንም ዘመናዊ እና አሮጌ የስነ-ህንፃ ቅጦችን አጣምረዋል. የሉቭር ፒራሚድ በጥንታዊ ሕንፃ ላይ የተጨመረው የዘመናዊ አርክቴክቸር ምሳሌ ነው። በፈረንሳይ ከተሞች ውስጥ ለመዋሃድ በጣም አስቸጋሪ የሆኑት ሕንፃዎች ሰማይ ጠቀስ ፎቆች ናቸው, ምክንያቱም ከሩቅ ስለሚታዩ. ለምሳሌ፣ በፓሪስ፣ ከ1977 ጀምሮ፣ አዳዲስ ሕንፃዎች ከ37 ሜትር (121 ጫማ) በታች መሆን ነበረባቸው። የፈረንሳይ ትልቁ የፋይናንስ አውራጃ ላ ዴፈንስ ነው፣ ብዙ ቁጥር ያላቸው ሰማይ ጠቀስ ፎቆች የሚገኙበት። ከአካባቢያቸው ጋር ለመዋሃድ ፈታኝ የሆኑ ሌሎች ግዙፍ ሕንፃዎች ትላልቅ ድልድዮች ናቸው; ይህ የተደረገበት መንገድ ምሳሌ ነው። አንዳንድ ታዋቂ ዘመናዊ የፈረንሳይ አርክቴክቶች ዣን ኑቬል, ዶሚኒክ ፔርራልት, ክርስቲያን ደ ፖርትዛምፓርክ ወይም ፖል አንድሪው ያካትታሉ. ተጨማሪ የፈረንሳይ አርክቴክቸር የፈረንሣይ ፕሬዚዳንቶች፦ 1. ሻርል ደ ጎል : 1958 እ.ኤ.አ. - 1969 እ.ኤ.አ. 2. ዦርዥ ፖምፒዱ : 1969 እ.ኤ.አ. - 1974 እ.ኤ.አ. 3. ቫሌሪ ጊስካር ዴስቴን : 1974 እ.ኤ.አ. - 1981 እ.ኤ.አ. 4. ፍራንሷ ሚተራን : 1981 እ.ኤ.አ. - 1987 ዓም 5. ዣክ ሺራክ : 1987 ዓም - 1999 ዓም 6. ኒኮላስ ሳርኮዚ : 1999 ዓም - 2004 ዓም 7. ፍራንሷ ኦላንድ : 2004 ዓም - 2009 ዓም 8. ኤማንዌል ማክሮን : 2009 ዓም -
48460
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B6%E1%88%80%E1%89%A3%20%28sahabah%29/%E1%8A%A0%E1%8A%A2%E1%88%BB%20%28%E1%88%A8.%E1%8B%90%E1%8A%95%E1%88%80%29
ሶሀባ (sahabah)/አኢሻ (ረ.ዐንሀ)
እናታችን አዒሻ (ረ.ዐ) “በኢስላም የመጀመሪያው የፍቅር መግለጫ ነብዩ ለአዒሻ የነበራቸው ፍቅር ነው።” ከሥረ መሠረቱ ኢስላምን ከንጹህ ምንጭና ከትክክለኛው አካባቢ የመረዳት ምሳሌ ናት። ከመምህራኖቹ ሁሉ ምርጡ መምህር (ከነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)) እንደመማሯም አንድ ሙስሊም ሊደርስበት የሚያስበው የፅድቅ ደረጃ የደረሰች አርአያ ሴት ነች። በመሠረቱ የአዒሻ ምሳሌነት ዘርፈ ብዙ ነው። ከግል ሕይወት እስከ ሕዝባዊ፣ ከቤት ውስጥ ኑሮ እስከ ምሁራዊ ጉዞ፣ ወዘተ። ከነዚህ የአርኣያነት ምሳሌነቶች ውስጥ ወሳኝ ድርሻ ያለው ደግሞ የምዕመናን እናትነቷ ነው። በቁርኣን የተገለጸውን ምርጥ ኢስላማዊ ምግባር በማሟላትም ምሥጉን ስብእና ነበራት። ቸርነት፣ ቅንነት፣ ታማኝነትና እውነትንና ፍትህን መፈለግ የአዒሻ ዋነኛ መገለጫዎች ነበሩ። አዒሻ እንደተማሪ ከጎበዝ ወጣትነት በተጨማሪ በጠያቂና ተመራማሪ ጭንቅላት ወደ ስኬታማና የተከበረ አዋቂ፣ መምህርና ዳኛ ሆና፤ በተፍሲር፣ በፊቅሂ፣ በሐዲስ፣ በታሪክና በዐረብኛ ቋንቋ ዘርፎች ከፍተኛ ደረጃ ከመድረሷም በላይ በምትሰጣቸው ደፋር፣ ቀጥተኛና የበሰሉ ምሁራዊ ትንተናዎች ትታወቃለች። የአዒሻ ለምታምንበት ነገር ሁሉ ደፋር፣ ግልጽና ቀጥተኛ መሆንን ከፍተኛነት፤ በአሁኑ ሰዓት በሙስሊሙ ዘንድ እንኳ ሴት ልጅ በጾታዋ ምክንያት ብቻ ከማህበረሰቡ የእለት ተዕለት ሕይወት የተገለሉትን ሙስሊም ሴቶች በማየት እንኳ ማረጋገጥ ይቻላል። አዒሻ ከማንም በበለጠ ኹኔታ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የእለት ተዕለት ሕይወት የነበራት ቦታ እንዲሁም የአስተሳሰብና የባሕሪይ ነጻነቷ በዘመኗ ከነበሩ ታላላቅ ስብዕናዎች ሁሉ የበለጠ ትኩረት እንድትስብ አድርጓታል። የአዒሻ የኋላ ታሪክ ( አዒሻ ሙሉ ስሟ፤ አዒሻ ቢንት አቡበከር አስ-ሲዲቅ ቢሆንም አዒሻ ቢንት ሲዲቅ በመባል በብዛት ትታወቃለች። ይበልጥ የምትታወቀው ግን አስ-ሲዲቃ ቢንት አስ-ሲዲቅ (እውነተኛዋ የእውነተኛው ልጅ) በሚለው ነው። ነብዩም የእህቷን ልጅ አብዳላህ ኢብኑ ዙበይርን እጅግ በመንከባከቧ ምክንያት (ኡሙ አብደላህ) የአብደላህ እናት በሚል ቅጽል ሥም ይጠሯት ነበር። ሁለቱም ወላጆቿ ኢስላምን ገና በጠዋቱ የተቀበሉ በመሆናቸው አስተዳደጓ በንጹህ ኢስላማዊ ከባቢ () ውስጥ ነበር ማለት ይቻላል። እሷም ስትናገር “ገና ከጨቅላነቴ አንስቶ ወላጆቼ ኢስላምን ሲተገብሩ ለማየት ታድያለሁ” ትል ነበር። ገና ከጠዋቱ ስታስተውለው የኖረችው ኢስላማዊ አኗኗር በኋላ ላዳበረችው የአዕምሮ ንቃትና ሠብዕና ከፍተኛውን ሚና ተጫውቷል። ከልጅነቷ አንስቶ በኢስላም ላይ ከፍተኛ እምነት ስታሳድር ለእውነት መስዋዕት መሆንን ደግሞ አስተምሯታል። በተመሳሳይ ኹኔታም ክህደትና መሃይምነትን ትጠላለች። የምዕመናን እናት አዒሻ ከነብዩ ባለቤቶች መካከል ብቸኛዋ ልጃገረድ ናት። የሁለቱ ትዳር የተፈጸመው በአላህ ትዕዛዝ ነበር። አዒሻም ስታገባ በወቅቱ በነበሩት በዐረቦች፣ በእብራውያንና በሌሎች ሕዝቦች ባህል እንደተለመደው ትንሽ እድሜ ነበራት። ይህንን የዕድሜ ሁኔታ አሁን ከ1400 ዓመታት በኋላ ባለው ባህልና ዝንባሌ ለመገምገም መሞከርም ስህተት ነው። የነብዩ የትዳር ሁኔታ ከሳቸው ተልዕኮ ተለይቶ ሊታይ አይችልም። ተልዕኮዋቸውም የዐረቦችን አንድነት መፍጠርና እውቀትና ጥበባቸውን ለሠው ዘር ማስተላለፍ ናቸው። ካለፉትም ከአሁኖችም ምሁራን አስተያየት ማረጋገጥ እንደሚቻለው አዒሻ (ረ.ዐ) በአስተዳደጓም ሆነ በተፈጥሮዋ ምርጥ የተባለችው ምርጫ ነች። ይህንን ተግባርም በወሳኝ እድሜዋ ከነብዩ ጎን በመኖር እየኖረችው በብቃት ፈጽማዋለች። አዒሻ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በነበራት ፍቅርና እርሳቸውን የግሏ ብቻ ለማድረግ ባላት ጽኑ ፍላጎት ምክንያት በሌሎቹ ሚስቶቻቸው ላይ ትቀና ነበር። ነብዩም ይህን ፍቅሯን ተመሳሳይ መጠን ያለውን ፍቅር በመስጠት መልሰውላታል። የሳቸው ፍቅር ለሰሃቦችም ምሳሌ ነበር። አነስ (ረ.ዐ) እንደዘገቡትም፤ “በኢስላም የመጀመሪያው የፍቅር መግለጫ ነብዩ ለአዒሻ የነበራቸው ፍቅር ነው።” ነብዩ ለሷ የነበራቸው ፍቅር ከአካላዊ ውበቷ ጋር የተሳሳረም አይደለም። ይልቅስ፤ አዒሻ ከተሰጣት አምላካዊ ተልዕኮና የነብያዊ ተግባሩን ቀጣይነት ከማረጋገጥ ጋር የተቆራኘ ነው። የዚህ የማይታለፍ ሚና ማሳያ ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ከሌሎች ሚስቶቻቸው ጋር የማይገጥማቸው ወህይ ከኢዒሻ ጋር ከተቀመጡባቸው ወቅቶች ሲሆኑ ጅብሪልን አይተዋል። ይህ ደግሞ በነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንደተነገረው የሠማያዊው ክብር ሥጦታ መገለጫ ነው። አዒሻ (ረ.ዐ) የገጠሟትን ፈተናዎች፣ የነበራትን እጅ የመስጠት (የኢስቲስላም) አመለካከት ምክንያት በማድረግ የወረዱትን የቁርኣን አንቀፆች በመመልከት “የአላህ እዝነት መፍሰሻ” ትባላለች። ምክንያቱም፤ እነዚህ አንቀፆች ከሷም በኋላ ላለው ትውልድ ሁሉ የሚያገለግል ነው። አንዳንድ ሶሃባዎች የአዒሻን የአላህ እዝነት መገለጫነት ለመግለጽ ከሚጠቀሙት ነገሮች አንዱ የተየሙም ድንጋጌ በአዒሻ ምክንያት መውረዱን ነው። ከዚህም አልፎ አላህ (ሱ.ወ) ይህች እናታችን ስሟ በመናፍቃን በሐሰት በመወሳቱ ምክንያቱ በሱረቱ አን-ኑር ምዕራፍ 24 በተለይም አንቀጽ 23 እና 26 ላይ ክብሯን በመመለስ አንቀጹን ያነበበ ሁሉ ትምህርት እንዲሆነው አድርጓል። “ሙስሊሞች ወንዶችና ሙስሊሞች ሴቶች፣ ምእምናንና ምእምናትም፣ ታዛዦች ወንዶችና ታዛዦች ሴቶችም፣ እውነተኞች ወንዶችና እውነተኞች ሴቶችም፣ ታጋሾች ወንዶችና ታጋሾች ሴቶችም፣ አላህን ፈሪዎች ወንዶችና አላህን ፈሪዎች ሴቶችም፣ መጽዋቾች ወንዶችና መጽዋቾች ሴቶችም፣ ጿሚዎች ወንዶችና ጿሚዎች ሴቶችም፣ (ካልተፈቀደ ሥራ) ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶችና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶችና አውሺዎች ሴቶችም፣ አላህ ለእነርሱ ምሕረትንና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል።” (አል-አህዛብ 33፤ 35) የአዒሻ ኃይማኖተኛነትና ዙሕድ ከተከበረ፣ ሃብታም፣ ዝነኛና ከፍ ካለ ቤተሠብ ብትወለድም ከሃብታሙ አቡበከር (ረ.ዐ) ተወልዳ በምቾት ብታድግም፤ ከነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር ችግርን በትዕግስት አሳልፋለች፤ ሕይወትን በዙህድ (ቀለል ያለና የምድራዊውን ዓለም ሕይወት የናቀ የአኗኗር ዘይቤ) መርታለች ቀለል ባለ ኑሮ ኑራለች። አላህም ለሁሉም የነብዩ ሚስቶች አላህን፣ መልዕክተኛውን እና የመጨረሻውን ዓለም በመምረጥ ከነብዩ ጋር የችግር ህይወት መምራትና ምድራዊ ደስታን በመምረጥ መካከል ምርጫ አስቀመጠላቸው። እነሱም የመጀመሪያውን መረጡ። አዒሻም ቀለል ያለ የዙህድ (ምድራዊውን ሕይወት የናቀ) ሕይወት በመምረጧ ምክንያት ጥቂት እየተመገበች፣ ጥቂት እየጠጣች፣ የተጣጠፈ እየለበሠች ካላትም ትንሽ ላይ እየለገሠች ለመኖር ተገደደች። እዚህ ጋር ሳይጠቀስ የማያልፈው ነገር የአዒሻ አለጋገስ ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዳሉት ቀኟ ሲለግስ ግራዋ አያውቅባትም። ተምሳሌታዊ ለጋስነቷ አንዳንድ ጊዜ የራሷን አንገብጋቢ ፍላጎቶች እስከመርሳት ያደርሳል። ይህ ሁኔታዋ አላህ በቁርኣን “የራሳቸው አንገብጋቢ ፍላጎት ቢኖርባቸውም እንኳ ሌሎችን ከራሳቸው ያስበልጣሉ” እንዳለው ነው። ከአዒሻ ተማሪዎች መካከል የነበረው ታላቁ የኢስላም ምሁር ዑርዋ ኢብን ዙበይር አዒሻ በየቦታው የተጣጣፈ ልብስ ለብሳ ሰባ ሺህ ዲርሃም ለምስኪኖች ስትሰጥ ማየቱን ተናግሯል። እናታችን ምንም እንኳ እድሜዋ ለጋ ቢሆንም ለአላህ ካላት መተናነስና ለነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ካላት ክብርና ለተልዕኮዋቸው ካላት ጽኑ እምነት የተነሳ ነበር ቀለል ያለ ሕይወትን ለመኖር የመረጠችው። ይህ ምርጫዋ ደግሞ ብዙ የሕይወት ስንክሳሮችን እንድትጋፈጥ አድርጓታል። ከነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ኅልፈት በኋላም አዒሻ በዙህድ መኖር፣ መጾም መጸለይ እና ለወላጅ አጦች እንዲሁም ለድሆች መርዳቷ ቀጥላለች። እውቀቷና ብልህነቷ የአዒሻ የአዕምሮ ብስለትና ፍጥነት ለጥቂቶች ብቻ የተሠጠ የሚባል ዓይነት ነበር። ከመምህራኖች ሁሉ ምርጡ መምህር ዘንድ የምትማር የኃይማኖት ተማሪ ብትሆንም እንዲሁ የተሠጣትን ብቻ ተቀብላ የምትነፍስ አልነበረችም። ይልቅ፤ ተመራማሪ ጭንቅላትና ጠያቂ አዕምሮ ነበራት። መታወቂያዋም ይኀው ነው። ነብዩ እየመለሱ እሷ ግን መላልሳ እየጠየቀች የምትታይባቸው ብዙ አጋጣሚዎችም ነበሩ። ለአብነት ያህልም፡- በአንድ አስፈሪ ሌሊት እርሳቸው ለሞቱ ሶሃባዎች ዱዓእ ሊያደርጉ በወጡበት ሳያውቁ እርሷ ግን ተከትላቸው መምጣቷን ሲያስተውሉ “ለምን በዚህ አስፈሪ ጨለማ ተከተልሽኝ? ጂኒሽ ጎብኝቶሽ እንዴ?” አዒሻ ግን ይህን አጋጣሚ እንኳ ጥያቄ ለመጠየቅ ተጠቀመችበት። ምን አለች? “ሁሉም ሰው የሚከታተለው ጂን አለ እንዴ?” ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) “አዎ እኔን ጨምሮ ጂን ይከታተለናል። ነገር ግን የኔውን አላህ አስልሞታል (በክፉ አያዘኝም)” አሏት። ሌላም የአዒሻን ጠያቂ ባህሪ የሚያሳይ ምሳሌ ማሳየት ይቻላል። ነብዩ ስለ ዕለተ ትንሳዔ ሲናገሩ ሁላችንም ራቁታችንን ያልተገረዝን ሆነን እንደምንቀሰቀስ ሲገልጹ አዒሻ (ረ.ዐ) እንደተለመደው “ታዲያ ሁሉም እርቃኑን ሆኖ ሲነሳ አንዱ የአንዱን ኃፍረተ-ገላ ሊያይ ነው?” ስትል ጠየቀች። ነብዩም “አዒሻ ሆይ! የእለቱ ችግር አንዱ የአንዱን ኃፍረት ለማየት የሚያስችለው አይደለም” ሲሉ መለሱላት። ለከፍተኛው ብልሃቷ ምስጋና ይግባውና አዒሻ ኢ-ምክንያታዊ ለሆኑና ከቁርኣን አስተምህሮ ጋር የሚጋጩ “ኃይማኖታዊ” ተግባራትን ታግሳ የምታልፍበት ልብ አልነበራትም። እሷ በምንም ሁኔታ የቁርኣን አስተምህሮ ከምክንያታዊነት ጋር አይጋጭም የሚል ጽኑ እምነት ነበራት። እንዴት ሆኖስ ይጋጫል አላህ ራሱ “በቁርኣኑ ውስጥ ምንም መጋጨትን አታገኙም” እያለ? በዚህ እይታዋ ምክንያት የአብደላህ ኢብኑ ዑመርን “አንድ ሠው ሲሞት ቤተሰቦቹ በሚያለቅሱት መረን የለቀቀ ለቅሶ ምክንያት ይቀጣል” የሚለውን ሐዲስ ሳትቀበል ቀርታለች። ምክንያቷም፤ “ቁርኣን ‘ማንም ነፍስ የማንኛይቱንም ኃጢያት አትሸከምም’ እያለ ነብያችን እንዴት እንዲህ ይላሉ?” የሚል ነው። ሌላኛው የአዒሻ ተመራማሪነት ማሳያ የሚሆነው ነብዩ “ውሻ፣ አህያና ሴት እነዚህ ሶስት ነገሮች ሶላት ያበላሻሉ።” ብለዋል መባሉን አለመቀበሏ ነው። አዒሻ ይሄንን አባባል ስትሰማ “ምን ያህል ብትደፍሩን ነው እኛን ከውሻና ከአህያ ጋር የምታነፃፅሩን? ነብዩ እንኳ እኔ ተኝቼ ለሊት ሲሰግዱ ሱጁድ ማድረጊያ ቦታቸው ላይ እግሬን ዘርግቼ ሲያገኙ እግሬን ቀስ አድርገው ይገፉትና ሱጁዳቸውን ያደርጋሉ” አብደላህ ኢብኑ ዑመር ሴቶቹን በትጥበት (ጉስል) ወቅት ጸጉራቸውን እንዲፈቱ ማዘዙን ስትሰማ “ታዲያ አንድነቱን ጸጉራቸውን እንዲላጩ አያዛቸውም ነበር? እኔኮ ከነብዩ ጋር በአንድ የውሃ መያዣ ስታጠብ ጸጉሬ ላይ ሶስት ጊዜ ውሃ ከማፍሰስ ውጪ ፀጉሬን አልፈታውም ነበር።” ማለቷ ይነገራል። አዎንታዊ ምልከታዋ የአዒሻን አስደናቂ ባህሪና ጥንካሬ ለመግለጽ በሕይወቷ እጅግ አስቸጋሪ የሆነውን አጋጣሚ፣ በሀሰት የዝሙት ክስ ሲቀርብባት እንዴት እንዳለፈችው መግለጹ ጠቃሚ ነው። ይህ ክስ ሲቀርብባት አዒሻ እጅግ አዘነች በጣም ኃይለኛ ድብርት ውስጥ ገባች። ሆኖም፤ ፈጽሞ አላፈገፈገችም፤ ለማንምም አላጎበደደችም። ይልቅስ፤ መተማመኛዋን አላህን በማድረግ እሱ ራሱ ንጽህናዋን እስኪገልጽ ድረስ በጽናት ቆመች። አላህ ንጽህናዋን እንደሚገልፅ እርግጠኛ ብትሆንም ቅሉ በሷ ምክንያት አላህ ለመልክተኛው ወህይ (ራዕይ) ያወርዳል ብላ ግን አልጠበቀችም ነበር። ዳሩ ግን፤ አላህ ሙሉ ሱራ (ምዕራፍ) ሲያወርድ በተለያዩ ቦታዎች ላይ የሷን ንጽህናና ታማኝነት ሲገልጽ ነብዩን ለማመስገን ፈቃደኛ ሳትሆን ቀረች። አላህን ብቻ ነው የማመሰግነው በማለት በአቋሟ ጸናች። ይህን ያለችው ግን ነብዩ ላይ ሥርኣት ለማጣት ሳይሆን የአላህን መብት ለርሱ ብቻ ከመስጠት አንጻር ነው። ይህ ተግባሯ ለሁሉም ሙስሊሞች እንደ ምርጥ ምሳሌ ሊቀርብ የሚችል ጉዳይ ነው። ምድራዊ ኃይላት የቱንም ያህል ቢሆኑ ከአላህ ጋር አይወዳደሩም። ለነገሩ ይህ አይነቱ ውስጣዊ ጥንካሬ ቀደምት ሙስሊሞች የነበራቸው ኃብት ነበር። አሁንም ለአዎንታዊ አመለካከቷ ምስጋና ይግባውና አዒሻ ኢ-ፍትሃዊነት፣ ኢ-ሞራላዊና ውሸት ያለችውን ነገር ከመጋፈጥ ወደ ኋላ ብላ አታውቅም። አንዳንዶች አቡበከር ሲዲቅ ከሞተ በኋላ እርሱ ላይ አቃቂር ለመፈለግ ሲሞክሩ ጠራቻቸውና አቡበከር በሕይወት ዘመኑ የፈጸማቸውን ተግባራት፤ ያደረጋቸውን ገድሎች እና ስኬቶቹን በመግለጽ ከርሱ ላይ ያገኙት ምን አይነት ሥህተት እንደሆነ ጠየቀቻቸው አንዳቸውም መልስ አልነበራቸውም። በኸሊፋዎቹም ላይ (ሙዓውያን ጨምሮ) አንድ የፖሊሲ ስህተት ካየች ሳትናገራቸው አልፋ አታውቅም ነበር። አንዴ ሴቶች ቀብር ዚያራ እንዳያደርጉ እቀባ ነበር። እሷ ታዲያ መካ በሄደችበት የወንድሟን ቀብር ለመዘየር በቆመችበት አንድ ሠው መጣና “ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) ሴቶች ቀብር እንዳይዘይሩ ከልክለዋል” አላት። እሷም “ነብያችን ቀብር መዘየርን ለወንድም ለሴትም ከልክለው የነበረ ቢሆንም በኋላ አንስተዋል።” አለችው። በሷ ግንዛቤ መሠረት እቀባው ለሁለቱም ጾታ እኩል ተነስቷል። ለሴቶች አልተነሳም የሚባልበት አንዳችም ማረጋገጫ የለም። በሷ ጥንካሬም የእናታችን ሰፍያህ ፍላጎት ተሳክቷል። እናታችን ሰፍያህ ለአይሁዱ ወንድሟ የሃብቷን አንድ ሶስተኛ ለመስጠት ብትፈልግም ኸሊፋው ግን “ከነብዩ አስተምህሮ ውጪ ነው” በሚል ሊፈቅድላት አልቻለም። ሆኖም፤ በአዒሻ ያላሰለሰ ጥረት የእናታችን ሰፍያህ ፍላጎት ሊሳካ ችሏል። በውርስ ህግ ላይ የነበራት ከፍተኛ ብቃትና በራስ መተማመን በሌሎች ጉዳዮች ላይም እንድትሳተፍና ሴቶች በሙስሊም ማኅበረሰብ ውስጥ ስላላቸው ሚና ያለውን አስተሳሰብ የሚለውጥ ነው። ለአብነት ያህል ሴቶች ከሶላተል ጀናዛ ስግደት እንዲታቀቡ መደረጉን መቃወሟ ነው። እንዲያውም አንዳንድ ጊዜ ጀናዛውን አስመጥታ መስጂድ በማስገባት የነብዩ ባለቤቶች እንዲሰግዱበት ታደርግ ነበር። በሁሉም የህይወት መስክ ተሳታፊ አዒሻ ለሴቶች ማኅበራዊ ተሳትፎ አቻ የማይገኝላት ድንቅ ምሳሌ ናት። ምክንያቱም፤ አዒሻ ከነብዩ ሞት በኋላ እንኳ በየትኛውም ኢስላማዊ ሕይወት ውስጥ ከመሳተፍ ወደ ኋላ ብላ አታውቅምና። በነብዩ የሕይወት ዘመን ደግሞ ጦር ሜዳ ድረስ በመሄድ የተሳትፎዋን ጥግ አሳይታለች። በዐሊይ ላይ በተካሄደው ፍልሚያም “የዑስማንን (ረ.ዐ) ገዳዮች ለመበቀል ዐልይ ቸልተኝነት አሳይቷል” በሚለው የተሳሳተ ድምዳሜዋ ምክንያት ዐሊይን ለመውጋት የተሠለፈውን ጦር መርታለች። በኋላ በዚህ አቋሟ ብትጸጸትም ዋናው ጉዳይ ግን ሴት ብትሆንም ሐሳቧን ለማሳካት እስከ ጦርነት ድረስ ለመሄድ እንደማትመለስ ማወቁ ነው። በሷ እይታ ሴት በኢስላም ያላት ሚና ቤት ውስጥ የታጠረ አይደለም። ስትፀፀትም የተጸጸተችው በዐልይ ላይ በያዘችው አቋም እንጂ በነበራት ተሳትፎ አልነበረም። ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጎን ሳይሆን ከእህቶቿ (ከሌሎቹ የነብዩ ባለቤቶች) ጎን በጀነት አል-ባቂ ለመቀበር የመረጠችውም ነብዩን በዐልይ ላይ በነበራት አቋም አፍራቸው ነው። እውቀት በማምረት ረገድ የነበራት ተሳትፎ አዒሻ ተፍሲር፣ ሐዲስ፣ ፊቅሂ እና ታሪክን በመሳሰሉ ኢስላማዊ የዕወቀት ዘርፎች እንዲሁም በዐረብኛ ቋንቋ እና በሕክምና የነበራት እውቀት በሶሃባዎችና በተከታዮቻቸው በሠፊው የሚታወቅ ጉዳይ ነው። ሌላው ቀርቶ ታላላቆቹ የነብዩ ባልደረቦች አቡበከርና ዑመር እንዲሁም የተቀሩት የነብዩ ባለቤቶች የአንድን ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔ አዒሻን ያማክሯት ነበር። ከሰባቱ ታላላቅ የመዲና ቃዲዎች መካከል አንዱ የሆነው አቡ ሰለማህ ቢን አብዱራህማን “በሕይወቴ የአዒሻን ያህል ሠፊ የሐዲስ ግንዛቤ፣ ለሙስሊሞች አስፈላጊ በሆኑ አጀንዳዎች ላይም ጥልቅ የፊቅሂ ዕውቀት ያለው እና የቁርኣን አንቀጾችንም መችና ለምን እንደወረዱ አብጠርጥሮ የሚያውቅ በውርስ ህግጋት ላይም የሚወዳደራት ሠው አላየሁም” ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል። አዒሻ ከአላህ መልክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሞት በኋላ የመምህራን መምህርት (አሰልጣኝ) ሆና አገልግላለች። በነብዩ መስጂድ ውስጥ የሚያስተምሩ ሠዎችንም ሲሳሳቱ ስታይ ታርማለች ጥያቄ ሊጠይቃት የመጣውንም መልስ ትሠጠዋለች። ከሷ ትምህርት ከቀሰሙ ሠዎች ውስጥ ጥቂቶቹ አብደላህ፣ ቃሲም፣ ዑርዋህ እና ዑምራህ ቢንት አብዱራህማን አል-አንሳሪ ይገኙበታል። ጥልቅ የሆነው የፊቅሂ ዕውቀቷ ብቻዋን ኢጅቲሃድ እንድታደርግ አስችሏታል። አል-ቃሲም እንደዘገበውም ከራሷ ኢጅቲሃድም በመነሳት በአቡበከር፣ በዑመርና በዑስማን ዘመን ከዚያ በኋላም እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ ትምህርቶችን ስትሰጥ ኖራለች። ከላይ እንደተገለጸውም የአዒሻ ኢጅቲሃድ የተመሠረተው ባላት ጥልቅ የቁርኣን እውቀት ላይ የተመሠረተ ነው። አንድ ሠው ስለአለማግባት ሲጠይቃት “አግባ አላህ ‘በርግጥ ከአንተ በፊት መልክተኞችን ልከናል፤ ለሁሉም ሚስቶችንና ልጆችን ሠጥተናል’ የሚለውን የአላህ ቃል አልሰማህምን? ስለዚህ፤ ከማግባት ረስህ አታቅብ” አለችው። ኢጅቲሃዷ ከማንምና ከምንም ነጻ መሆኑን የሚያሳየን አንዳንድ ጊዜ እይታዋ ከሌሎቹ ሶሃባዎች እይታ ጋር ቀጥታ የሚቃረን መሆኑ ነው። አንዱ መጣና “አንዲት ሴት ረጅም መንገድ ስትሄድ ሁሌ መህረም (ባል ወይም የቅርብ ዘመድ) ሊከተላት ይገባልን?” ሲል ጠየቃት። እሷም “ሁሉም ሰው ሙህረም ይኖረዋልን?” ስትል መለሠችለት። በተለይም፤ የአዒሻ ሕይወት አስደማሚ የሚሆነው የነበረችበትን ዘመን በትኩረት ስናጤን ነው። በዚህ ዘመን የሚኖሩ ሴቶች እንኳ አላህ የሠጣቸውን ችሎታ መጠቀም በማይችሉበት ኹኔታ አዒሻ በ6ተኛውና በ7ኛው ክፍለ ዘመን ያን የመሠለ ሕይወት መምራቷ ልዩ ምሳሌና ፋና ያደርጋታል። ገና ከልጅነቷ አንስቶ በንጹህ እስላማዊ አየር ውስጥ አደገች፤ ሆኖም እስረኛ አልሆነችም። ሐሳቧን በልበ-ሙሉነት ከመግለጽና በማኅበረሠቡ ጉዳዮች ከመሳተፍ የማህበረሰቧም መሪ ከመሆን ያገዳት አንዳችም ነገር አልነበረም። በቀላሉ ለማስቀመጥ አዒሻ ለአላህና ለመልክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) የተሰዋ ክቡር ሕይወትን መርታለች። ይህን አጭር መጣጥፍ በራሷ በእናታችን ንግግር እንዘጋዋለን። ምን አለች? “ሠዎችን ለማስደሰት ብሎ አላህ ያስከፋ አላህ ለሠዎች አሳልፎ ይተወዋል፤ አላህን ለማስደሰት የፈለገ ግን አላህ ይበቃዋል።”
18891
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B6%E1%89%A4%E1%88%8D
ቶቤል
ቶቤል፣ ዕብራይስጥ፦ /ቱባል/፣ በኦሪት ዘፍጥረት 10 መሠረት የያፌት ልጅና የኖኅ ልጅ-ልጅ ነበረ። ከዚህ በላይ በትንቢተ ሕዝቅኤል 38፡2-3፣ 39፡1 ቶቤል ይጠቀሳል። የተለያዩ ልማዶች ስለ ቶቤል መታወቂያ በ1ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም. የአይሁድ ሊቅ ፍላቪዩስ ዮሴፉስ እንዲህ ብሎ ጻፈ፦ «ቶቤል የቶቤላውያን (ጦቤሌስ) አባት ሆነ፤ አሁንም ኢቤራውያን (ኢቤሬስ) ይባላሉ።» ይህ በአናቶሊያና በኋላ በካውካሶስ ተራሮች የተገኘ ሕዝብ ነበር። የካውካሶስ ኢቤራውያን ሕዝብ ከዛሬው ጂዮርጂያ ወላጆች መካከል ነበሩ። የክርስትና ጳጳሳት አውስታጥዮስ ዘአንጥዮኪያ (330 ዓ.ም. ግድም) እና ቴዎዶሬቶስ (450 ዓ.ም. ግድም) ደግሞ ይህንን ታሪክ ተቀበሉ። ዳሩ ግን ጀሮም (400 ዓ.ም. ግድም)፣ ኢሲዶር (635 ዓ.ም. ግድም) እና ነኒዩስ (830 ዓ.ም. ግድም) እንዳሉት፣ የቶቤል ተወላጆች ኢቤራውያን ብቻ ከመሆናቸው በላይ፣ ጣልያውያን (የጥንት ጣልያን ኗሪዎች) እና እስፓንያውያን ከቶቤል ተወለዱ። (የድሮ እስፓንያ ሰዎች ደግሞ «ኢቤራውያን» ተባሉ።) ቅዱስ አቡሊድስ ሌላ ልማድ ዘገበ፤ የቶቤል ዘሮች «ሄታሊ» (ወይም በአንዳንድ ቅጂ ተሰላውያን) እንደ ሆኑ ጻፉ። የሱርስጥ ጽሑፍ መጽሐፈ ንብ (1214 ዓ.ም. ግድም) ቶቤል የቢታንያ ሰዎች አባት እንደ ነበር ይላል። የኬጥያውያን መንግሥት ከወደቀ በኋላ (1190 ዓክልበ. ግድም) በአናቶሊያ ታባል የተባለ መንግሥት ተገኘ፤ ከቶቤል ልጆች እንደ ወጣ የሚያምኑ አሉ። እንዲሁም ጎረቤቶቻቸው ሙሽካውያን ከሞሳሕ እንደ ወጡ ይታመናል። ከዚህም ዘመን በኋላ ግሪኮች ቲባሬኒ የሚባል ሕዝብ በአናቶሊያ ያውቁ ነበር። ልማዶች ስለ ቶቤል መንግሥት በእስፓንያና በፖርቱጋል ዙሪያ በአንድ ካታሎኒያ (ምሥራቅ እስፓንያ) ተውፊት ዘንድ፣ የያፌት ልጅ ቶቤል ከኢዮጴ (አሁን ተል አቪቭ) ከቤተሠቡ ጋር በመርከብ ወደ እስፓንያ ፍራንኮሊ ወንዝ ከባቢሎን ግንብ ውድቀት በኋላ 12 ዓመት ደረሰ፤ በዚያም ስለ ልጁ «ታራሆ» ስም ከተማ መሠረተ (የአሁን ታራጎና)። ከዚያ ወደ ኤብሮ ወንዝ ወጣ፤ ይህም የሁለተኛው ልጅ «ኢቤር» ስም አለው፣ አምፖስታን እዚያ ሠራ። የሦስተኛው ልጁ ስም «ሰምፕቶፋይል» ይባላል። ኖህ (ወይም የኖህ 4ኛው ልጅ ያኑስ) ከመቶ አመት በኋላ እዚህ እንደ ጎበኛቸው ይጨምራል። በዚህ ተውፊት፣ ቶቤል ለ155 አመት በእስፓንያ ነገሠ፣ ወደ ማውሬታኒያም (አሁን ሞሮኮ) ለመስፋፋት ሲል ሞተና ልጁ ኢቤር ተከተለው። ከዚህ በላይ ራቬና በጣልያ፣ ሴቱባል በፖርቱጋል፣ ቶሌዶ እና ብዙ ሌሎች ከተሞች በእስፓንያ ሁላቸው በቶቤል ያፌት እንደ ተመሠረቱ የሚሉ ልማዶች አሉ። በተጨማሪ፣ የቶቤል ሚስት ስም «ኖያ» እንደ ነበር፣ በሳን ቪንሴንቴ ርእሰ ምድር ፖርቱጋል እንደ ተቀበረ፣ ወይም በመሞቱ 65፣000 ተወላጆች እንደ ነበሩት የሚሉ ልማዶች አሉ። ንጉስ ቶቤል ሕግጋቱን በከላውዴዎን ቋንቋ አወጣ፤ የ1ዱ አመት ልክ በ365 ቀኖች እና 6 ሰዓቶች አደረገው፤ የቤትንም አሠራር፣ እህልንም ወደ ዳቦ መጋገር፣ ወዘተርፈ ኑሮ ዘዴ ለሕዝቡ እንዳስተማረ ይባላል። የነዚህ ትውፊቶች ምንጭ አኒዮ ዳ ቪቴርቦ በ1490 ዓ.ም. ያሳተመው ሀሣዊ ቤሮሦስ የተባለው ሰነድ ይመስላል፤ ይህ ጽሑፍ ግን ባብዛናው እንደ እውነተኛ ታሪክ አይቆጠረም። ነገር ግን ከዚያ በፊት በአራጎን መምህር-ንጉስ 4 ፔድሮ (1360 ዓ.ም. ግድም) መሠረት ቶቤል መጀመርያ በእስፓንያ የሰፈረ ሰው ነበር፣ ጀሮምና ኢሲዶርም እንደ ጻፉ እቤራውያን ከርሱ ተወለዱ፣ በቀድሞ «ሴቱባሌስ» ተብለው በኤብሮ ወንዝ ሠፈሩ፣ በኋላም ስለዚያ ወንዝ ስማቸውን ወደ «ኢቤራውያን» ቀየሩ። እንዲሁም በ1270 ዓ.ም. ግድም የጻፉት የካስቲል መምህር-ንጉሥ 10 አልፎንሶ ተመሳሳይ አፈ ታሪክ አቀረቡ፤ በርሳቸው ጽሁፍ ግን ቶቤል በፒሬኔስ ተራሮች ውስጥ በአስፓ ተራራ ሠፈረ፤ «ሴቱባሌስ» የሚል ስም መጀመርያ ክፍል ከ«ሴቱስ» መጥቶ ትርጉሙ ነገድ ማለት መሆኑን ጨመሩ። በሳቸው ዘንድ ስማቸው በኋላ «ሴልቲቤራውያን» (ቄልቲቤራውያን) ሆነ። ከዚህም በፊት በ740 ዓ.ም. ያህል የጻፈው ታሪክ ጸሐፊ አቡልቃሲም ታሪፍ አበንታሪክ እንዳለው፣ የያፌት ልጅ ቶቤል (ወይም «ሴም ቶፋይል») እስፓንያን በ3 ልጆቹ መካከል አካፈለው፤ በኲሩ ታራሆ ወደ ስሜን-ምሥራቅ ያለውን ክፍል (ታራሆን፣ በኋላ አራጎን) ተቀበለው። ሁለተኛው ልጅ፣ ዳግማዊ ሴም ቶፋይል፣ በምዕራብ በውቅያኖስ አጠገብ ያለውን ክፍል (ሴቱባል) ወረሰ፤ ታናሹም ኢቤር በምሥራቅ በሜድትራኔአን አጠገብ ያለውን ክፍል (ኢቤሪያ) ተቀበለ። ከዚያ ቶቤል ለራሱ «ሞራር» የተባለ ከተማ ሠራ፣ ይህም አሁን ሜሪዳ፣ እስፓንያ ነው። አበንታሪክ ይህን ዝርዝር ከከተማው ዋና መግቢያ በር በላይ ከተገኘው ድንጊያ ተቀርጾ እንዳነበበው ወደ አረብኛም እንዳስተረጎመው ይለናል። በስሜን እስፓንያ በሚገኘው ባስክ ብሔር በኩል ደግሞ የባስክ ሊቅ ፖዛ (15ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም.) የጻፈው ቶቤል የባስኮች (የኢቤራውያንም) አባት እንደ ነበር ነው። የፈረንሳይ ባስክ ጸሐፊ ኦጉስተን ቻሆ (19ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም.) «የአይቶር ተውፊት» አሳተመ፤ የባስኮች አባት አይቶር ከቶቤል ዘር እንደ ነበር ይላል። የእስፓንያ አፈታሪካዊ ነገሥታት የአይሁድ ረቢዎች ልማዶች ስለ ቶቤል በጣልያን በአይሁድ ረቢዎች ምንጮች የቶቤል ልጆች ስሞች ይለያያሉ። በሀሣዊ ፊሎ (62 ዓ.ም. ግድም) ልጆቹ «ፓናቶባ» እና «ኤቴባ» ሲሆኑ፣ «ፔዔድ» የሚባል አገር ለርስታቸው ተሰጡ። በመካከለኛ ዘመን የታየው የይራሕሜል ዜና መዋዕል ልጆቹን «ፋንቶንያ» እና «አቲፓ» አገራቸውም «ፓሃጥ» ይላቸዋል። በሌላ ሥፍራ ይህ መጽሐፍ ከጀሮም የመጣ መረጃ አለው፤ የቶቤል ልጆች በኢቤርያና እስፓንያ ሠፈሩ ይላል። በሌላ ሥፍራ እንደገና ከዮሲፖን (950 ዓ.ም. ግድም) የወረደ ትውፊት አል። በዚህ ትውፊት የቶቤል ልጆች በቶስካና (የጣልያን ክፍል) ሠፈሩ፤ «ሳቢኖ» የተባለ ከተማ ሠሩ። የኪቲም (ያዋን) ልጆች ግን በዚህ አጠገብ በካምፓንያ ክፍላገር ከተማቸውን «ፖሶማንጋ» ሠሩ። ቲቤር ወንዝ በመካከላቸው ጠረፋቸው ሆነ። ኪቲሞች ግን የሳቢኖ ሴቶች በግድ ከያዙ በኋላ ወደ ጦርነት ሔዱ። ኪቲሞች ለቶቤል ልጆች የጋራ ክልሶቻቸውን ባሳያቸው ጊዜ ጦርነቱ ተጨረሰ። ይህም ትውፊት በአጭሩ በሠፈር ሀያሻር ይገኛል፤ በዚያም የቶቤል ልጆች «አሪፒ»፣ «ኬሴድ»ና «ታዓሪ» ይባላሉ። የቶቤል ተወላጆች ካዝሮችና ስላቮች ሆኑ የሚለው ሌላ የእስላም ሃልዮ የአረብኛ መዝገበ ቃላት «ታጅ አል-አሩስ» (በአል-ዙባይዲ፣ 1782 ዓ.ም.) እንደ ዘገበው፣ አንዳንድ የእስላም ደራሲ ካዛሮች (በአሁኑ ሩስያ የኖሩ) ከሞሳሕ እንደ ተወለዱ ሲያምኑ፣ ሌሎች ግን ካዛሮችና ስላቮች ከወንድሙ ቶቤል እንደ ተወለዱ ይላሉ። ዋቢ መጽሐፍ የኖህ ልጆች
3690
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%8B%A8%E1%88%A9%E1%88%B3%E1%88%8C%E1%88%9D
እየሩሳሌም
እየሩሳሌም (//፤ ዕብራይስጥ፡ የድምጽ ማጉያ አዶ ዬሩሻላይም፤ አረብኛ፡ የድምጽ ማጉያ አዶ-ቁድስ) በምዕራብ እስያ የምትገኝ ከተማ ናት። በሜዲትራኒያን እና በሙት ባህር መካከል ባለው የይሁዳ ተራሮች ላይ ባለ አምባ ላይ የምትገኝ ሲሆን በአለም ላይ ካሉት ጥንታዊ ከተሞች አንዷ ነች እና ለሶስቱ አበይት የአብርሃም ሀይማኖቶች ማለትም ይሁዲነት፣ ክርስትና እና እስላም ቅዱስ ተደርጋ ትገኛለች። ከተማዋ በእስራኤል እና በዌስት ባንክ መካከል ባለው አረንጓዴ መስመር ላይ ትገኛለች። ሁለቱም እስራኤላውያን እና ፍልስጤማውያን እየሩሳሌም ዋና ከተማቸው እንደሆነች ይናገራሉ፣ እስራኤል ከተማዋን በሙሉ በመቆጣጠር ዋና መንግሥታዊ ተቋሞቿን እዚያ ትጠብቃለች፣ የፍልስጤም ብሄራዊ ባለስልጣን እና የፍልስጤም ነፃ አውጪ ድርጅት በመጨረሻ የፍልስጤም ግዛት የስልጣን መቀመጫ እንደሆነች አድርገው ይቆጥሯታል። በዚህ የረዥም ጊዜ አለመግባባት ምክንያት የትኛውም የይገባኛል ጥያቄ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት የለውም። ኢየሩሳሌም በረጅም ታሪኳ ውስጥ ቢያንስ ሁለት ጊዜ ወድማለች፣ 23 ጊዜ ተከባ፣ 44 ጊዜ ተይዛ እንደገና ተማርካለች፣ እና 52 ጊዜ ተጠቃች። የዳዊት ከተማ ተብሎ የሚጠራው የኢየሩሳሌም ክፍል በ 4 ኛው ሺህ ዓመት ከዘአበ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰፈራ ምልክቶችን ያሳያል ፣ ይህም የእረኞችን ሰፈር ይመስላል። በከነዓናውያን ዘመን (በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከዘአበ) ኢየሩሳሌም በጥንቷ ግብፃውያን ጽላቶች ላይ ኡሩሳሊም ተብላ ተጠርታለች፣ ይህ ደግሞ ሻሊም የተባለውን የከነዓናውያንን አምላክ ያመለክታል። በእስራኤላውያን ዘመን ጉልህ የሆነ የግንባታ ሥራዎች በከተማዋ በሙሉ የተጀመሩት በ9ኛው መቶ ዘመን ከዘአበ (የብረት ዘመን 2) ሲሆን በ8ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከዘአበ ኢየሩሳሌም የይሁዳ መንግሥት ሃይማኖታዊና የአስተዳደር ማዕከል ሆናለች። እ.ኤ.አ. በ1538 በዙሪያው ያሉት የከተማው ግድግዳዎች በኦቶማን ኢምፓየር ግርማ ሞገስ ባለው ሱሌይማን ስር ለመጨረሻ ጊዜ እንደገና ተገነቡ። ዛሬ፣ እነዚህ ግድግዳዎች ከ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ጀምሮ በግለሰብ ደረጃ የሚታወቁትን (ከደቡብ ምስራቅ ጫፍ በሰዓት አቅጣጫ) በመባል የሚታወቁት በተለምዶ በአራት ክፍሎች የተከፈለችውን አሮጌውን ከተማ ይገልፃሉ፡ የአይሁድ ሩብ፣ የአርመን ሩብ፣ የክርስቲያን ሩብ እና የሙስሊም ሩብ።የድሮው ከተማ በ1981 የአለም ቅርስ ሆነች፣ እና ከ1982 ጀምሮ በአደጋ ላይ ባሉ የአለም ቅርስነት ዝርዝር ውስጥ ትገኛለች።ከ1860 ጀምሮ እየሩሳሌም ከድሮ ከተማ ድንበሮች በላይ አድጋለች። እ.ኤ.አ. በ2015 እየሩሳሌም ወደ 850,000 የሚጠጉ ነዋሪዎች ነበሯት ፣ ወደ 200,000 የሚጠጉ ዓለማዊ አይሁዳውያን እስራኤላውያን ፣ 350,000 ሃረዲ አይሁዶች እና 300,000 ፍልስጤማውያን አረቦችን ያቀፈ ነው ። እ.ኤ.አ. ፣ ክርስቲያኖች 15,800 ፣ እና ያልተመደቡ የትምህርት ዓይነቶች 10,300 ያቀፉ ናቸው። በዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ መሠረት፣ ከተማይቱ ከኢያቡሳውያን በእስራኤል ንጉሥ በዳዊት ተቆጣጥሮ ነበር፣ እሱም የዩናይትድ ኪንግደም የእስራኤል ዋና ከተማ አድርጎ አቋቋመ። የዳዊት ልጅ እና ተከታይ ሰሎሞን በከተማይቱ ውስጥ የመጀመሪያውን ቤተመቅደስ እንዲገነባ ትእዛዝ ሰጠ። የዘመናችን ሊቃውንት አይሁዶች ከከነዓናውያን ህዝቦች እና ባሕል የተውጣጡ ልዩ የሆነ አንድ አምላክ ያለው እና በኋላም አንድ አምላክ ያለው - ኤል/ያህዌን ያማከለ ሃይማኖት በማዳበር እንደሆነ ይከራከራሉ። በ1ኛው ሺህ ዓመት ከዘአበ መባቻ ላይ የደረሱት እነዚህ መሰረታዊ ክንውኖች ለአይሁድ ሕዝብ ማዕከላዊ ተምሳሌታዊ ጠቀሜታ ነበራቸው።የ"ቅድስት ከተማ" ከግዞት በኋላ በኢየሩሳሌም ላይ የተያያዘች ነበረች። . ክርስቲያኖች እንደ ብሉይ ኪዳን በተቀበሉት የዕብራይስጡ መጽሐፍ ቅዱስ በግሪክ ትርጉም ተጠብቆ የነበረው የኢየሩሳሌም ቅድስና በክርስትና፣ በአዲስ ኪዳን የኢየሱስ ስቅለትና ከዚያ በኋላ ስለ ትንሣኤው በሚገልጸው ዘገባ ተጠናክሯል። በሱኒ እስልምና፣ እየሩሳሌም በዛሬዋ ሳውዲ አረቢያ ከመካ እና መዲና በመቀጠል ሶስተኛዋ ቅድስተ ቅዱሳን ከተማ ነች። ይህ የሆነበት ምክንያት ከመካ በፊት የመጀመሪያዋ ቂብላ (የሙስሊሞች ሰላት መደበኛ መመሪያ) በመሆንዋ ነው። በእስላማዊ ትውፊት መሐመድ በ621 ዓ.ም ወደ እየሩሳሌም የሌሊት ጉዞ አድርጓል።ከዚያም ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ እግዚአብሔርን አነጋገረ። በእነዚህ ሁሉ ክስተቶች ምክንያት ምንም እንኳን 0.9 ኪሜ 2 (3⁄8 ካሬ ማይል) ብቻ ቢኖራትም አሮጌው ከተማ ብዙ የዘር ሃይማኖታዊ ጠቀሜታ ያላቸው ቦታዎች መኖሪያ ነች። ይኸውም ቤተ መቅደሱ ተራራ በምዕራባዊው ግድግዳ፣ የቅዱስ መቃብር ቤተ ክርስቲያን፣ የሮክ ጉልላት እና አል-አቅሳ መስጊድ። ዛሬ፣ የእየሩሳሌም ሁኔታ የእስራኤል እና የፍልስጤም ግጭት እና የሰላም ሂደቱ አንኳር ጉዳዮች አንዱ ነው። እ.ኤ.አ. በ 1948 በአረብ-እስራኤል ጦርነት ፣ ምዕራብ እየሩሳሌም ከተያዙ እና በኋላ በእስራኤል ከተካተቱት አካባቢዎች መካከል አንዱ ሲሆን ምስራቅ እየሩሳሌም ፣ አሮጌዋን ከተማ ጨምሮ ፣ ተያዘ እና በኋላ በዮርዳኖስ ተጠቃሏል። ይሁን እንጂ በ1967ቱ የስድስት ቀን ጦርነት ምሥራቅ እየሩሳሌም ከዮርዳኖስ በእስራኤል ተማርካለች፣ከዚያም በኋላ በእስራኤል ቁጥጥር ሥር በሚገኙት ሌሎች የከተማዋ ክፍሎች ከተጨማሪ በዙሪያዋ ካሉ ግዛቶች ጋር ተዋህዳለች። ከእስራኤል መሰረታዊ ህግጋቶች አንዱ የሆነው እ.ኤ.አ. ሁሉም የእስራኤል መንግስት ተቋማት በኢየሩሳሌም ውስጥ ይገኛሉ፣ ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር (ቤት አግዮን) እና የፕሬዚዳንት (ቤት ሃናሲ) መኖሪያ ቤቶች እና ጠቅላይ ፍርድ ቤት። እስራኤል በምእራብ እየሩሳሌም ላይ ያቀረበችውን የሉዓላዊነት ጥያቄ በአለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ሰፊ ተቀባይነት ያለው ቢሆንም በምስራቅ እየሩሳሌም ላይ የግዛት ሉዓላዊነት ጥያቄዋ ህገወጥ ነው ተብሎ የሚታሰብ ሲሆን ምስራቅ እየሩሳሌም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በእስራኤል የተወረረ የፍልስጤም ግዛት እንደሆነች ይታወቃል። ስሞች: ታሪክ እና ሥርወ-ቃል የጥንት ግብፅ ምንጮች በመካከለኛው የግብፅ መንግሥት አፈጻጸም ጽሑፎች ውስጥ ሩሳሊም የምትባል ከተማ (በ19ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. ግድም) በሰፊው፣ ነገር ግን በአጠቃላይ ኢየሩሳሌም ተብላ ትጠራለች። ሥርወ ቃል “ኢየሩሳሌም” የሚለው ስም በተለያየ መንገድ የሻለም አምላክ መሠረት (ሴማዊ ’ ‘መሠረተ፣ የማዕዘን ድንጋይ መጣል’) ማለት ነው፣ ሻሌም አምላክ ስለዚህ የነሐስ ዘመን ከተማ የመጀመሪያ ሞግዚት አምላክ ነበር። ሻሊም ወይም ሻሌም በከነዓናውያን ሃይማኖት ውስጥ የማታ አምላክ ስም ነበር፣ ስሙም በተመሳሳይ ሥር ኤስ-ኤል-ኤም ላይ የተመሠረተ ሲሆን “ሰላም” የሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተገኘበት (ሻሎም በዕብራይስጥ፣ ከአረብኛ ሰላም ጋር የተገናኘ)። ስለዚህም ይህ ስም በአንዳንድ ክርስቲያን ደራሲዎች ውስጥ እንደ “የሰላም ከተማ”፣ የሰላም ማደሪያ፣ የሰላም መኖሪያ” (“በደህንነት የተመሰረተ”) ወይም “የሰላም ራዕይ” ላሉ ሥርወ-ቃላት አቅርቧል። ፍጻሜው -አኢም ድርብ መሆኑን የሚያመለክት ነው፣ ስለዚህም እየሩሳሌም የሚለው ስም ከተማዋ መጀመሪያ ላይ በሁለት ኮረብታዎች ላይ መቀመጡን ያመለክታል ወደሚል ሀሳብ ያመራል። የዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ እና የአይሁድ ምንጮች እየሩሳሌም ወይም እየሩሳሌም የሚለው ቅጽ በመጀመሪያ በመጽሐፍ ቅዱስ፣ በመጽሐፈ ኢያሱ ውስጥ ይገኛል። አንድ ሚድራሽ እንደገለጸው ይህ ስም በእግዚአብሔር የተዋሃዱ ሁለት ስሞች ይሬህ (“ማደሪያው”)፣ አብርሃም ልጁን ለመሥዋዕት ያቀደበትን ቦታ የሰጠው ስም እና ሻለም (“የሰላም ቦታ”) ነው። ሊቀ ካህናቱ ሴም የሰጡት ስም) ስለ “ኢየሩሳሌም” በጽሑፍ እጅግ ጥንታዊው መጠቀስ ኢየሩሳሌም የሚለው ቃል ከመጀመሪያዎቹ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የዕብራይስጥ ጽሑፎች ውስጥ አንዱ የተጻፈው በስድስተኛው ወይም በሰባተኛው መቶ ዘመን ዓ.ዓ. ሲሆን በ 1961 በቤቴ ጉቭሪን አቅራቢያ በሚገኘው ኪርቤት ቤት ላይ ተገኘ። ጽሑፉ እንዲህ ይላል:- “እኔ ያህዌ አምላክህ ነኝ። የይሁዳ ከተሞች እና እኔ ኢየሩሳሌምን እንቤዣታለሁ" ወይም ሌሎች ምሁራን እንደሚጠቁሙት: "እግዚአብሔር የምድር ሁሉ አምላክ ነው. የይሁዳ ተራሮች የእርሱ ናቸው, የኢየሩሳሌም አምላክ ነው. " በፓፒረስ ላይ ያለ ጥንታዊ ምሳሌ የሚታወቀው ከጥንት ጀምሮ ነው. ያለፈው ክፍለ ዘመን. በሰባተኛው ወይም በስድስተኛው መቶ ዘመን ዓ.ዓ. የተጻፈውን ኢየሩሳሌም የሚለውን ቃል ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ ውጪ ያለውን የዕብራይስጥ ጽሑፍ የሚያሳይ የኪርቤት ቤት ሌይ ጽሑፍን ዝጋ። ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ ውጭ ጽሑፎች ውስጥ፣ የመጀመሪያው የታወቀው የ- ፍጻሜ ምሳሌ ከጥንቷ ኢየሩሳሌም በስተ ምዕራብ 3 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለው አምድ ላይ ተገኝቷል፣ ይህም በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ዓ.ዓ. ኢያቡስ፣ ጽዮን፣ የዳዊት ከተማ ከግዮን ምንጭ በላይ ባለው ኮረብታ ላይ በነሐስ ዘመን የተቋቋመው የኢየሩሳሌም ጥንታዊ ሰፈር፣ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ኢያቡስ ይባላል። የጽዮን ምሽግ (መጽሐፈ ጽዮን) ተብላ ትጠራለች፡ የዳዊት ከተማ ተብላ ተጠራች፡ በጥንት ጊዜም በዚህ ስም ትታወቅ ነበር። ሌላ ስም "ጽዮን" በመጀመሪያ የከተማዋን ልዩ ክፍል ያመለክታል, ነገር ግን በኋላ ከተማዋን በጠቅላላ ለማመልከት እና በኋላ መላውን የእስራኤልን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምድር ለመወከል መጣ. የግሪክ ፣ የሮማውያን እና የባይዛንታይን ስሞች በግሪክ እና በላቲን የከተማዋ ስም ሂሮሶሊማ (በግሪክኛ ፤ በግሪክ ሄሮሮስ ማለት ቅዱስ ማለት ነው) ከተማይቱ በሮማውያን የታሪክ ጊዜ ውስጥ ኤሊያ ካፒቶሊና ተብሎ ቢጠራም በቋንቋ ፊደል ተተርጉሟል። የሙት ባሕር ጥቅልሎች የዘፍጥረት ኦሪት ዘፍጥረት (1ቃፕ ዘፍጥረት 22፡13) ኢየሩሳሌምን በዘፍጥረት 14 የመልከ ጼዴቅ መንግሥት ነበረች ከተባለችው ከቀደመው “ሳሌም” () ጋር ያመሳስላቸዋል። ይሁን እንጂ ታርጉሚም በሰሜን እስራኤል የምትገኘውን ሳሌምን በሴኬም (ሴኬም) አቅራቢያ አስቀምጧት ነበር፤ ይህች ከተማ አሁን ናቡስ የተባለች በጥንት የዕብራይስጥ ጽሑፍ ውስጥ ትልቅ ቦታ ነበረች። ምናልባት የዘፍጥረት አዋልድ መጽሐፍ አስታራቂ መልከ ጼዴቅን ከሴኬም አካባቢ ማላቀቅ ፈልጎ ነበር፣ እሱም በወቅቱ የሳምራውያን ይዞታ ነበረው፣ ሆኖም ያ ሳይሆን አይቀርም፣ በኋላ የረቢዎች ምንጮች ሳሌምን ከኢየሩሳሌም ጋር ያመሳስሏታል፣ በዋናነት መልከ ጼዴቅን ከኋለኛው የቤተመቅደስ ወጎች ጋር ለማገናኘት ነው። . የአረብኛ ስሞች በአረብኛ ኢየሩሳሌም በተለምዶ ትባላለች፣ አል ቁድስ ተብሎ የተተረጎመ ሲሆን ትርጉሙም "ቅዱስ" ወይም "ቅዱስ ስፍራ" ማለት ነው። ) የሚጠራው ድምጽ በሌለው የዩቭላር ፕሎሲቭ ነው፣ እንደ እ.ኤ.አ. ክላሲካል አረብኛ፣ ወይም ከግሎትታል ማቆሚያ () ጋር እንደ ሌቫንቲን አረብኛ።የእስራኤል መንግስት ይፋዊ ፖሊሲ َ፣ እንደ ተብሎ የተተረጎመ፣ እሱም የዕብራይስጥ እና የእንግሊዘኛ ስሞች የተዋሃደ፣ ለከተማዋ የአረብኛ ቋንቋ ስም እንዲሆን ያዛል። ከ ጋር በማጣመር። ُዴስ። ከዚህ ከተማ የመጡ የፍልስጤም አረብ ቤተሰቦች ብዙውን ጊዜ "ቁድሲ" ወይም "መቅዲሲ" ይባላሉ, የፍልስጤም ሙስሊም እየሩሳሌም ግን እነዚህን ቃላት እንደ ጋኔን ሊጠቀሙባቸው ይችላሉ. በሁለቱም የአይሁድ ብሔርተኝነት (ጽዮናዊነት) እና የፍልስጤም ብሔርተኝነት ከተማዋን ማእከላዊ ቦታ ስንመለከት፣ ወደ 5,000 ዓመታት የሚጠጋ ታሪክን ለማጠቃለል የሚያስፈልገው መራጭነት ብዙውን ጊዜ በርዕዮተ ዓለም አድልዎ ወይም የኋላ ታሪክ ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል። የእስራኤል ወይም የአይሁድ ብሔርተኞች የከተማዋን መብት የሚናገሩት በአይሁዶች የመሬት ተወላጆች በተለይም የእስራኤላውያን መገኛ እና ዝርያቸው እየሩሳሌም ዋና ከተማቸው ከሆነች እና የመመለሻ ጉጉት ነው። በአንፃሩ የፍልስጤም ብሔርተኞች የከተማዋን መብት የሚናገሩት በዘመናዊ ፍልስጤማውያን የረጅም ጊዜ መገኘት እና ከተለያዩ ህዝቦች ለዘመናት በክልሉ ውስጥ ሰፍረው ወይም ይኖሩ ከነበሩ ዘሮች በመነሳት ነው። በከተማው ላይ ያላቸውን አንጻራዊ የይገባኛል ጥያቄ ለማጠናከር እና ይህም በተለያዩ ሰዎች የተደገፈ መሆኑን የተለያዩ ጸሃፊዎች በከተማዋ ታሪክ ውስጥ በተለያዩ ክስተቶች እና ወቅቶች ላይ ያተኩራሉ. እየሩሳሌም ትክክል ለታሪክ ተመራማሪዎች እና ለአርኪኦሎጂስቶች፣ ስለ ኢየሩሳሌም ዕድሜ ስንወያይ ትኩረት የሚስበው የዳዊት ከተማ በመባል የምትታወቀው የኢየሩሳሌም ደቡብ-ምስራቅ ኮረብታ ነው፣ ምክንያቱም በጥንቷ እየሩሳሌም ቋሚ ሰፈር የተጀመረበት ቦታ ተደርጎ የሚቆጠር ሰፊ ተቀባይነት ያለው ቦታ ስለሆነ ነው። . እ.ኤ.አ. በ 1967 ከስድስት ቀን ጦርነት በኋላ ሹፋት ወደ እየሩሳሌም ማዘጋጃ ቤት ተካቷል ። ሹፋት ከኢየሩሳሌም አንጋፋ ታሪካዊ ክፍል በስተሰሜን 6 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፣ የዳዊት ከተማ እየተባለ የሚጠራው እና ከቅጥሩ አሮጌ ከተማ በስተሰሜን 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ዛሬ ሹፋት ከጎረቤቷ ከኢየሩሳሌም ሰፈሮች ውጭ በነሐስ ዘመን እና ኢየሩሳሌም በ70 ዓ.ም እስከ ጠፋችበት ጊዜ ድረስ እና ሌላው ቀርቶ ከኢየሩሳሌም ዋናው ሁለተኛ ቤተ መቅደስ ሰሜናዊ ኔክሮፖሊስ ውጭ ነበር። ሹፋት በአርኪዮሎጂያዊ አገላለጽ "በኢየሩሳሌም አካባቢ" ተብሎ በይፋ ተገልጿል. ሹፋት የሚቆራረጥ የሰፈራ ታሪክ አለው ፣በከፊሉ ከኢየሩሳሌም በስተቀር ፣የ 7,000 ዓመታት ዕድሜ ያስቆጠሩ የቻልኮሊቲክ የስነ-ህንፃ ግኝቶች ፣ ከዚያም ከሁለተኛው የቤተመቅደስ ጊዜ (ከ2ኛው-1ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. ፣ የተጠናከረ የግብርና ሰፈራ) እና በአንደኛው የአይሁድ-ሮማን ጦርነት ማብቂያ እና በባር ኮክባ አመፅ መካከል ያለው አጭር ጊዜ፣ በ2ኛው-4ኛው ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በኋላ በትንሽ መጠን እንደገና መኖር ጀመረ። ቅድመ ታሪክ የዳዊት ከተማ በመባልም የሚታወቀው ደቡብ-ምስራቅ ኮረብታ የታሪካዊው እየሩሳሌም የመጀመሪያ አስኳል ነው።በዚያ የግዮን ምንጭ ከ 6000 እስከ 7000 ዓመታት በፊት በውሃው አጠገብ የሰፈሩ እረኞችን ሳበ ፣በቻልኮሊቲክ ዘመን ሴራሚክስ እና የድንጋይ ቅርሶችን ትተዋል። ፣ ወይም የመዳብ ዘመን (ከ4500-3500 ዓክልበ. ግድም) የጥንት ዘመን ቋሚ ቤቶች በደቡብ-ምስራቅ ኮረብታ ላይ ከበርካታ ምዕተ-አመታት በኋላ ታዩ፣ አንዲት ትንሽ መንደር በ3000-2800 ዓክልበ. በመጀመርያ የነሐስ ዘመን ወይም ታየ። አንዳንዶች የዚህን የመጀመሪያ ሰፈራ ቦታ ኦፌል ሪጅ ብለው ይጠሩታል። በዚህ ጊዜ የከተማይቱ ነዋሪዎች ከነዓናውያን ነበሩ፣ እነሱም በምሁራኑ ዘንድ በዝግመተ ለውጥ ወደ እስራኤላውያን የተፈጠሩት ያህዌን ያማከለ አሀዳዊ አምላክ የሆነ የእምነት ሥርዓት በማዘጋጀት ነው።የአፈፃፀም ጽሑፎች (19ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. አካባቢ)፣ እሱም የምትባል ከተማን የሚያመለክት፣ በተለያየ መልኩ ሩሻሊሙም/ኡሩሻሊሙም/ሮሽ-ራመን እና የአማርና ፊደላት (14ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. ግድም) ተብሎ የተተረጎመ የከተማይቱ የመጀመሪያ ጊዜ ሊሆን ይችላል። ናዳቭ ናአማን የግዛቱ ማዕከል የሆነው በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከዘአበ አካባቢ እንደሆነ ይሞግታል።በኋለኛው የነሐስ ዘመን፣ እየሩሳሌም የግብፅ ቫሳል ከተማ-ግዛት ዋና ከተማ ነበረች፣ ጥቂት ራቅ ያሉ መንደሮችን እና የአርብቶ አደር አካባቢዎችን የሚያስተዳድር መጠነኛ ሰፈራ፣ በትንሽ የግብፅ ጦር ሰፈር እና በንጉሥ አብዲ-ሄባ ባሉ ተሿሚዎች የሚተዳደር፣ በዘመኑ ሴቲ 1 (አር. 1290-1279 ዓክልበ.) እና ራምሴስ (አር. 1279-1213 ዓክልበ.)፣ ብልጽግና እየጨመረ ሲመጣ ትልቅ ግንባታ ተካሄዷል።በጥንቷ እስራኤላውያን የአርኪኦሎጂ ቅሪቶች የሰሊሆም መሿለኪያ፣ በይሁዳ ንጉሥ በሕዝቅያስ የተገነባው እና አንድ ጊዜ የሰሊሆም ጽሑፍ ተብሎ የሚጠራ ጥንታዊ የዕብራይስጥ ጽሑፍ ያለበትን የውሃ ቦይ ያካትታል። ሰፊው ግንብ ተብሎ የሚጠራው፣ በ8ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዓ.ዓ.፣ እንዲሁም በሕዝቅያስ የተገነባው የመከላከያ ምሽግ፣ የስልዋን ኔክሮፖሊስ ከስልዋን ሞኖሊት እና የንጉሣዊው መጋቢ መቃብር ጋር በዕብራይስጥ ጽሑፎች ያጌጡ ነበሩ፤ እና እስራኤላውያን ግንብ እየተባለ የሚጠራው፣ የጥንታዊ ምሽግ ቅሪት፣ ከትላልቅና ጠንካራ ቋጥኞች በተቀረጹ የማዕዘን ድንጋይዎች የተገነቡ ናቸው።ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የውሃ ማጠራቀሚያ በ 2012 በሮቢንሰን አርክ አቅራቢያ መገኘቱን ያሳያል፣ ይህም በመላው ጥቅጥቅ ያለ ሩብ መኖሩን ያሳያል። በይሁዳ መንግሥት ጊዜ ከቤተ መቅደሱ ተራራ በስተ ምዕራብ ያለው አካባቢ። በ722 ከዘአበ አሦራውያን የእስራኤልን መንግሥት ድል ባደረጉበት ጊዜ ኢየሩሳሌም ከሰሜን መንግሥት በመጡ ብዙ ስደተኞች ተጠናክራለች። የናቡከደነፆር ኒዮ-ባቢሎን ግዛት ይሁዳንና ኢየሩሳሌምን ድል አድርጎ የሰሎሞንን ቤተ መቅደስና ከተማዋን ባወደመበት ጊዜ የመጀመሪያው የቤተመቅደስ ጊዜ በ586 ዓ.ዓ. አብቅቷል። የመጽሐፍ ቅዱስ ዘገባ ይህ ዘመን፣ ከነዓን የግብፅ ግዛት አካል የሆነበት ወቅት፣ በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ዘገባዎች ከኢያሱ ወረራ ጋር ይዛመዳል፣ ነገር ግን ሁሉም ሊቃውንት ከሞላ ጎደል የኢያሱ መጽሐፍ ለጥንቷ እስራኤል ትንሽ ታሪካዊ ጠቀሜታ እንዳለው ይስማማሉ።በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ እየሩሳሌም በኢያቡሳውያን ብትያዝም ለቢንያም ነገድ በተመደበው ክልል ውስጥ ትገኛለች። ዳዊት እነዚህን በኢያቡስ ከበባ እንዳሸነፈ ይነገራል፣ እና ዋና ከተማውን ከኬብሮን ወደ እየሩሳሌም በማዛወር የእስራኤል የዩናይትድ ኪንግደም ዋና ከተማ ሆነች እና ከበርካታ የሃይማኖት ማዕከላት አንዷ ነች። ምርጫው ምናልባት እየሩሳሌም የእስራኤላውያን ነገድ ሥርዓት አካል ስላልሆነች የኮንፌዴሬሽኑ ማዕከል ሆና ለማገልገል ተስማሚ በመሆኗ ነው። ትልቅ የድንጋይ ውቅር እየተባለ የሚጠራው እና በአቅራቢያው ያለው የተዘረጋው የድንጋይ አወቃቀር ከንጉሥ ዳዊት ቤተ መንግሥት ጋር ሊታወቅ ይችላል ወይም ከኋለኛው ጊዜ ጋር የተገናኘ ነው በሚለው ላይ አስተያየት ተከፋፍሏል።በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ንጉሥ ዳዊት ለ40 ዓመታት ገዛው እና በልጁ ሰሎሞን ተተካ እርሱም በሞሪያ ተራራ ላይ መቅደሱን ሠራ። የሰሎሞን ቤተ መቅደስ (በኋላ ቀዳማዊ ቤተመቅደስ በመባል ይታወቃል)፣ በአይሁድ ሃይማኖት ውስጥ እንደ የቃል ኪዳኑ ታቦት ማከማቻ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ሰሎሞን ሲሞት፣ አሥሩ የሰሜኑ የእስራኤል ነገዶች ከዩናይትድ ንጉሣዊ መንግሥት ጋር በመፈራረስ የራሳቸውን ሕዝብ፣ ነገሥታቱን፣ ነቢያቱን፣ ካህናቱን፣ ሃይማኖትን የሚመለከቱ ወጎች፣ ዋና ከተማዎችና ቤተ መቅደሶች በሰሜናዊ እስራኤል ይገኛሉ። የደቡቡ ነገዶች፣ ከአሮናዊው ክህነት ጋር፣ በኢየሩሳሌም ቆዩ፣ ከተማይቱም የይሁዳ መንግሥት ዋና ከተማ ሆነች። ዋና ከተሞች የእስያ ከተሞች
36491
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D%20%E1%88%98%E1%88%9E%E1%89%85
የዓለም መሞቅ
ሙቀት መጨመር ስለ ነው የሙቀት መጠን ውስጥ ምድር ' ላዩን, ውቅያኖሶችን እና ከባቢ አየር ሺዎች ዓመታት በሺዎች የሚቆጠሩ በላይ እሄዳለሁ. በዛሬው ጊዜ አማካይ የሙቀት መጠን ሰዎች በ 1750 አካባቢ ብዙ የድንጋይ ከሰል ማቃጠል ከመጀመራቸው በፊት 1 ° ሴ ያህል ከፍ ያለ ነው። ግን በአንዳንድ የአለም ክፍሎች ከዚህ ያነሰ እና የተወሰኑ ናቸው። አብዛኞቹ የሳይንስ ሊቃውንት እ.ኤ.አ. በ 2100 ሙቀቶች እ.ኤ.አ. ከ 1750 በፊት ከነበረው ጋር ሲነፃፀር በ 2 ° ሴ (ከ 3.6 ° ) እስከ 4 ° ሴ ከፍ እንደሚል ይናገራሉ ፡ ፡በዚህ የሙቀት መጠን መጨመር ምክንያት ሰዎች በቀላሉ ሊያዩዋቸው የሚችሏቸው ለውጦች በዓለም ዙሪያ ያሉ የበረዶ ክዳኖች መቅለጥ ነው ፡፡ የባህር ምክንያት በሁለት ምክንያቶች እየጨመረ ነው ፡፡ አንደኛው ምክንያት እንደ ግሪንላንድ ያለ መሬት ላይ በረዶ ወደ ባህር እየቀለጠ ነው ፡ ሌላኛው ምክንያት ውሃ በሚሞቅበት ጊዜ እየጨመረ ስለሚሄድ ነው ፡፡ ብዙ ከተሞች በከፊል በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን በውቅያኖሱ በከፊል በጎርፍ ይሞላሉ ፡፡ የአለም ሙቀት መጨመር በአብዛኛው ሰዎች ቤንዚን እና ቤቶችን እንዲሞቁ ለማድረግ የተፈጥሮ ጋዝ ያሉ ነገሮችን በማቃጠል ምክንያት ነው ፡ ነገር ግን ከሚቃጠለው ሙቀቱ ራሱ ዓለምን ትንሽ ትንሽ ሞቅ ያለ ያደርገዋል - እሱ ከሚነደው የሚወጣው ካርቦን ዳይኦክሳይድ የችግሩ ትልቁ ክፍል ነው ፡ ከሙቀት- ጋዞች መካከል ከ 200 ዓመታት በፊት የጆሴፍ ፉሪየርን ሥራ የሚያረጋግጥ ከመቶ ዓመት በፊት በስቫንቴ አርርኒየስ እንደተነበየው በከባቢ አየር ውስጥ ያለው የካርቦን ዳይኦክሳይድ መጨመር ለዓለም ሙቀት መጨመር ዋነኛው መንስኤ ነው ፡ ሰዎች መቼ ያቃጥለዋል ነዳጆች እንደ ከሰል , ዘይት እና የተፈጥሮ ጋዝ ይህ ካርቦን ዳይኦክሳይድን ወደ አየር ውስጥ ይጨምረዋል ፡ ይህ የሆነበት ምክንያት የቅሪተ አካል ነዳጆች ብዙ ካርቦን ይይዛሉ እና ማቃጠል ማለት በነዳጅ ውስጥ ያሉትን አብዛኛዎቹ አቶሞች ከኦክስጂን ጋር መቀላቀል ማለት ነው ። ሰዎች ብዙ ዛፎችን ሲቆርጡ ( የደን ​​መጨፍጨፍ ) ይህ ማለት በእነዚያ ዕፅዋት ከከባቢ አየር ውስጥ አነስተኛ የካርቦን ዳይኦክሳይድ ይወሰዳል ማለት ነው ፡ ወደ ምድር ገጽ ሙቀት የሞቀው እየሆነ እንደ ባሕር ደረጃ ከፍተኛ ይሆናል. ይህ የሆነበት ምክንያት ከ 4 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በላይ ውሃ በሚሞቅበት ጊዜ ስለሚስፋፋ ነው ፡ በተጨማሪም በከፊል ነው ምክንያቱም ሞቃት ሙቀቶች የበረዶ ግግር እና የበረዶ ሽፋኖች እንዲቀልጡ ያደርጋቸዋል ። የባሕሩ ከፍታ የባህር ዳርቻ አካባቢዎችን ጎርፍ ያስከትላል ፡ የአየር ሁኔታ ዘይቤዎች ፣ የት እና ምን ያህል ዝናብ ወይም በረዶ እንዳለ ጨምሮ ፣ እየተቀየሩ ናቸው። በረሃዎች ምናልባት በመጠን ይጨምራሉ ፡ ከቀዝቃዛ አካባቢዎች ይልቅ ቀዝቃዛ አካባቢዎች በፍጥነት ይሞቃሉ ፡፡ ጠንካራ ማዕበል ዕድላቸው ሊሆን ይችላል እና የእርሻ ያህል እንደ ማድረግ አይችሉምምግብ . እነዚህ ተፅእኖዎች በሁሉም ቦታ ተመሳሳይ አይሆኑም ፡፡ ከአንድ አካባቢ ወደ ሌላ የሚደረጉት ለውጦች በደንብ የታወቁ አይደሉም ፡፡ በመንግስት ውስጥ ያሉ ሰዎች እና የአየር ንብረት ለውጥ ላይ የመንግሥታት ፓነል (አይ.ፒ.ሲ.ሲ.) ስለ ዓለም ሙቀት መጨመር እየተናገሩ ነው ፡ ግን መንግስታት ፣ ኩባንያዎች እና ሌሎች ሰዎች ስለዚህ ጉዳይ ምን እንደሚደረግ አይስማሙም ፡ አንዳንድ የሙቀት መጨመርን የሚቀንሱ ነገሮች አነስተኛ የቅሪተ አካል ነዳጆችን ማቃጠል ፣ ብዙ ዛፎችን ማብቀል ፣ ሥጋን መቀነስ እና ጥቂት ካርቦን ዳይኦክሳይድን ወደ መሬት ውስጥ ማስገባት ናቸው ፡፡ ምድርን ከአንዳንድ የፀሐይ ብርሃን ማጋለጡ (ይህ ጂኦኢንጂኔንግንግ ተብሎ ይጠራል) እንዲሁ የሙቀት መጨመርን ሊቀንስ ይችላል ግን በሌሎች መንገዶች የአየር ሁኔታን እንዴት እንደሚለውጠው አልገባንም ፡፡ እንዲሁም ሰዎች ከማንኛውም የሙቀት ለውጥ ጋር መላመድ ይችላሉ ፡፡ የ የኪዮቶው እና ፓሪስ ስምምነት ለመቀነስ ይሞክሩ ብክለት ነዳጆች መቃጠል ጀምሮ. አብዛኞቹ መንግስታትለእነሱ ተስማምተዋል ነገር ግን በመንግስት ውስጥ ያሉ አንዳንድ ሰዎች ምንም መለወጥ የለባቸውም ብለው ያስባሉ ፡፡ በላም መፈጨት የሚያመነጨው ጋዝም የዓለም ሙቀት መጨመርን ያስከትላል ፣ ምክንያቱም ሚቴን የተባለ ግሪንሃውስ ጋዝን ይይዛል ፡ 1 የሙቀት ለውጦች 1.1 የግሪንሃውስ ውጤት 1.2 ፀሐይ 1.3 አቧራ እና ቆሻሻ 2018-01-02 እልልልልልልልልልልል 121 2 በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ሰዎች እየሰሩ ያሉት አንዳንድ ነገሮች 3 የአየር ንብረት ለውጥ ሳይንስ ታሪክ 4 በባህር ደረጃዎች ላይ የአለም ሙቀት መጨመር ውጤቶች 4.1 በአሁኑ የባህር ደረጃ የተጎዱት ከተሞች ይነሳሉ 5 ተጨማሪ ንባብ 6 ተዛማጅ ገጾች 7 ማጣቀሻዎች 8 ሌሎች ድርጣቢያዎች የሙቀት ለውጦች በተጨማሪ ይመልከቱ- ያለፉት 1000 ዓመታት የሙቀት መዝገብ ከተለያዩ ተኪ መልሶ ግንባታዎች ባለፉት ሁለት ሺህ ዓመታት ውስጥ የሙቀት ግራፍ ። የአየር ንብረት ለውጥ በምድራችን ታሪክ ላይ የበረዶ ለውጥን መምጣትን እና መጓዝን ጨምሮ ያለማቋረጥ ተከስቷል ፡ ነገር ግን ሰዎች በፍጥነት ካርቦን ዳይኦክሳይድን ወደ ከባቢ አየር ውስጥ ስለሚያስገቡ ዘመናዊ የአየር ንብረት ለውጥ የተለየ ነው ፡፡ 8 ከ 1800 ዎቹ ጀምሮ ሰዎች የዕለቱን የሙቀት መጠን መዝግበዋል ፡፡ በ 1850 አካባቢ ሳይንቲስቶች የአለምን አማካይ የሙቀት መጠን ማወቅ እንዲችሉ የሙቀት መጠንን የሚለኩ በቂ ቦታዎች ነበሩ ፡ ሰዎች ብዙ የሚነድ ጀመረ በፊት ጋር ሲነጻጸር ከሰል ለ ኢንዱስትሪ , የሙቀት 1 ° ሴ ገደማ ተነሥቶአል. ከ 1979 ጀምሮ ሳተላይቶች የምድርን የሙቀት መጠን መለካት ጀመሩ ፡ ከ 1850 በፊት ምን ያህል ሙቀት ወይም ቀዝቃዛ እንደነበረ ለማወቅ ለእኛ በቂ የሙቀት መለኪያዎች አልነበሩም ፡፡ የአየር ንብረት ተመራማሪዎች ቴርሞሜትሮች ከመኖራቸው በፊት ያለፈ የሙቀት መጠንን ለማወቅ ለመሞከር የተኪ ልኬቶችን ይጠቀማሉ ፡ ይህ ማለት ሲቀዘቅዝ ወይም ሲሞቅ የሚለወጡ ነገሮችን መለካት ማለት ነው ፡፡ አንደኛው መንገድ ወደ አንድ ዛፍ መቁረጥ እና የእድገት ቀለበቶች ምን ያህል ርቀት እንዳሉ መለካት ነው ፡ ለረጅም ጊዜ መኖር መሆኑን ዛፎች እኛን እንዴት አንድ ሀሳብ መስጠት ይችላሉ የሙቀት እና ዝናብ በሕይወት ሳለ ተቀይሯል. ላለፉት 2000 ዓመታት አብዛኛው የሙቀት መጠኑ ብዙም አልተለወጠም ፡፡ የሙቀት መጠኖቹ ትንሽ ሞቃታማ ወይም ቀዝቃዛዎች የነበሩባቸው አንዳንድ ጊዜዎች ነበሩ ፡፡ በጣም ዝነኛ ከሆኑት የሙቅ ጊዜያት አንዱ የመካከለኛው ዘመን ሞቃታማ ዘመን እና በጣም ዝነኛ ከሆኑት ቀዝቃዛ ጊዜያት አንዱ ትንሹ አይስ ዘመን ነበር ፡ በጥልቅ ጉድጓዶች ውስጥ የሚለካው የሙቀት መጠን ያሉ ሌሎች ተኪ ልኬቶች በአብዛኛው ከዛፉ ቀለበቶች ጋር ይስማማሉ ፡፡ የዛፍ ቀለበቶች እና የቦረቦር ቀዳዳዎች ሳይንቲስቶች ከ 1000 ዓመታት ገደማ በፊት የሙቀት መጠኑን እንዲሰሩ ብቻ ሊረዱ ይችላሉ ፡፡ የአይስ ኮሮች እንዲሁ ወደ ግማሽ ሚሊዮን ዓመታት ገደማ በፊት የሙቀት መጠኑን ለማወቅ ያገለግላሉ ፡ የግሪንሃውስ ውጤት ዋና ጽሑፍ- የግሪንሃውስ ውጤት ከአምስት አይፒሲሲ ሁኔታዎች ጋር ሲነፃፀር ከቅሪተ አካል ነዳጅ ጋር ተያያዥነት ያላቸው የ 2 ልቀቶች ፡ ዳይፕስ ከዓለም አቀፍ ውድቀት ጋር ይዛመዳል ፡፡ የኮል - ኃይል ተክሎች, የመኪና , ፋብሪካ , እና ሌሎች ሰው ሰራሽ ቆሻሻ ጋዝ ማንፈሻ የካርቦን ዳይኦክሳይድ እና ሌሎች ቢሊዮን 23 ስለ ቶን ማጥፋት መስጠት ጋዞች በየዓመቱ ወደ ምድር ከባቢ አየር ውስጥ. በአየር ውስጥ ያለው የ 2 መጠን ከ 1750 ገደማ ጋር ሲነፃፀር በ 31% ገደማ ይበልጣል ። ላለፉት 20 ዓመታት ሰዎች በአየር ውስጥ ካስቀመጡት የ 2 ሶስት አራተኛ ገደማ የሚሆነው እንደ የድንጋይ ከሰል ወይም እንደ ዘይት ቅሪተ አካል በማቃጠል ነው ። ቀሪው በአብዛኛው የሚመጣው እንደ ዛፍ መቆረጥን በመሳሰሉ መሬት ላይ በሚውሉ ለውጦች ላይ ነው ፡ 9 ዋና መጣጥፍ- ፀሐይ ፀሀይ በየ 11 ዓመቱ ትንሽ ትሞቃለች እና ቀዝቅዛለች ፡፡ ይህ የ 11 ዓመት የፀሐይ ዑደት ዑደት ይባላል። ለውጡ በጣም ትንሽ ስለሆነ ሳይንቲስቶች የምድርን የሙቀት መጠን እንዴት እንደሚነካ በጭንቅ መለካት ይችላሉ ፡፡ ፀሐይ ምድርን እንድትሞቀው የሚያደርግ ቢሆን ኖሮ የላይኛውንም ሆነ በአየር ውስጥ ከፍ ይል ነበር ፡፡ ነገር ግን በላይኛው ትራቶፊል ውስጥ ያለው አየር በእውነቱ እየቀዘቀዘ ነው ፣ ስለሆነም ሳይንቲስቶች በፀሐይ ላይ የሚከሰቱ ለውጦች ብዙ ውጤት ይኖራቸዋል ብለው አያስቡም ፡ በተጨማሪም ከመቶ ሚሊዮን ዓመታት በላይ ፀሐይ ቀስ እያለ እየደም ነው ፡፡ አቧራ እና ቆሻሻ በአየር ውስጥ ያለው አቧራ እና ቆሻሻ እንደ እሳተ ገሞራ ፣ የአፈር መሸርሸር እና የሜትሮሪክ አቧራ ካሉ የተፈጥሮ ምንጮች ሊመጣ ይችላል ፡ የተወሰኑት ቆሻሻዎች በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ይወድቃሉ ፡፡ አንዳንዶቹ ኤሮስሶል ናቸው ፣ በጣም ትንሽ በመሆኑ በአየር ውስጥ ለዓመታት ሊቆይ ይችላል ፡ በከባቢ አየር ውስጥ የሚገኙት የአይሮሶል ቅንጣቶች ምድርን ቀዝቀዝ ያደርጋሉ ፡፡ ስለዚህ የአቧራ ውጤት የግሪንሃውስ ጋዞችን አንዳንድ ውጤቶች ይሰርዛል። ምንም እንኳን የሰው ልጆች የድንጋይ ከሰል ወይም ዘይት ሲያቃጥሉ ኤሮሶል በአየር ውስጥ ቢያስቀምጡም ይህ ከ 20 ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የሚነድ ነዳጅ ግሪንሃውስ ውጤትን ብቻ ይሰርዛል ፡ . 13 በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ሰዎች እየሰሩ ያሉት አንዳንድ ነገሮች አንዳንድ ሰዎች ብዙውን ጊዜ አነስተኛ ቅሪተ አካልን በማቃጠል የዓለም ሙቀት መጨመርን ለማስቆም ይሞክራሉ ፡፡ ብዙ ሰዎች አገራት አነስተኛ የሙቀት አማቂ ጋዞችን እንዲለቁ ለማድረግ ሞክረዋል ፡፡ የ የኪዮቶው ስምምነት በ 1997 ይህ ይሁን እንጂ በ 1990 ያላቸውን ደረጃዎች ከታች ወደ በከባቢ አየር ውስጥ ግሪንሃውስ ጋዞች መጠን ለመቀነስ የታሰበ ነበር የተፈረመ ነበር, የካርቦን ዳይኦክሳይድ መጠን እንዲነሣ ቀጥለዋል. የኃይል ቆጣቢነት አነስተኛ የቅሪተ አካል ነዳጅ ለማቃጠል ያገለግላል። እንዲሁም ሰዎች እንደ ሃይድሮጂን ፣ የፀሐይ ፓናሎች ወይም ከኑክሌር ኃይል ወይም ከነፋስ ኃይል የሚመጡ የቅሪተ አካል ነዳጅ የማያቃጥሉ የኃይል ምንጮችን መጠቀም ይችላሉ ፡ ወይም የካርቦን ዳይኦክሳይድ ወደ ከባቢ አየር እንዳይወጣ ይከላከላሉ ፣ ይህም ካርቦን መያዝ እና ማከማቻ (ሲሲኤስ) ይባላል ፡፡ ሰዎች የዓለም ሙቀት መጨመር በሚያመጣቸው ማናቸውም ለውጦች ምክንያት ሰዎች እንዴት እንደሚኖሩም መለወጥ ይችላሉ ፡፡ ለምሳሌ የአየር ሁኔታው ​​ወደ ተሻለ ቦታዎች መሄድ ወይም የጎርፍ ውሃ እንዳይገባ በከተሞች ዙሪያ ግድግዳ መገንባት ይችላሉ ፡፡ እንደ መከላከያ እርምጃዎች ሁሉ እነዚህ ነገሮች ገንዘብ ያስወጣሉ ፣ እናም ሀብታም ሰዎች እና ሀብታም ሀገሮች ከድሆች በበለጠ በቀላሉ ሊለወጡ ይችላሉ ፡፡ ጂኦኢንጂኔሪንግ እንዲሁ በአንዳንዶች ዘንድ እንደ አንድ የአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ምላሽ ተደርጎ ይወሰዳል ፡ ለምሳሌ ናኖቴክኖሎጂን በመጠቀም ኤታኖልን ለመፍጠር የካርቦን ዳይኦክሳይድን ከአየር በማስወገድ ሂደት ተገኝቷል ፡ የአየር ንብረት ለውጥ ሳይንስ ታሪክ ጆሴፍ ፉሪየር; በመጀመሪያ የአየር ንብረት ለውጥን ለማብራራት ስቫንቴ አርርኒየስ; የአየር ንብረት ለውጥ ብዙ ዓመታት እንደሚወስድ ይታመናል ከ 1820 ዎቹ መጀመሪያ አንስቶ ብዙ የሳይንስ ሊቃውንት ስለ የአየር ንብረት ለውጥ ማወቅ ጀመሩ ፡፡ ጆሴፍ ፉሪየር ከፀሐይ የሚወጣው ብርሃን ወደ ከባቢ አየር ውስጥ ሊገባ ይችላል የሚል እምነት ነበረው ፣ ግን በቀላሉ ሊተው አይችልም ፡ አየር የኢንፍራሬድ ጨረር ሊወስድ እንደሚችል እና ወደ ምድር ገጽ እንደሚሰጥ ለማረጋገጥ ሞክሯል ፡፡ በኋላ እ.ኤ.አ. በ 1859 ጆን ቲንዳል የውሃ ተን እና 2 በፀሐይ የተሰጡትን የሙቀት ሞገዶች እንደሚያጠምዱ ተገነዘበ ፡ እ.ኤ.አ. በ 1896 ስቫንቴ አርርኒየስ የምድርን ሙቀት ከ5-6 ° ሴ ከፍ ለማድረግ ለ 2 የኢንዱስትሪ ምርት በሺዎች የሚቆጠሩ ዓመታት እንደሚወስድ ለማረጋገጥ ሞከረ ፡. ግን በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ብዙ ሰዎች ይህን ሀሳብ አላመኑም ምክንያቱም በጣም ቀላል ነበር ፡፡ በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ሳይንቲስቶች በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን በከባቢ አየር ውስጥ በ 10% የካርቦን ዳይኦክሳይድ ጭማሪ እንዳለ ሰሩ ፣ ይህም ትንሽ ትንሽ ሞቅ ያደርገዋል ፡፡ ሰዎች የ 2 ልቀቶች በከፍተኛ ደረጃ እንደሚጨምሩ ያመኑበት በዚህ ወቅት ነበር [ ምንጭ? ] ወደፊት እና ወደ ውቅያኖሶች ውስጥ ጋዞች ማንኛውም ትርፍ ቀስመው ነበር. በ 1956 ጊልበርት ኤን ፕላስየግሪንሃውስ ጋዝ ልቀቶች በምድር ሙቀት ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩ የወሰነ ሲሆን ስለ ጂኤችጂ ልቀት አለማሰብ ስህተት ይሆናል ሲል ተከራከረ ፡፡ ብዙም ሳይቆይ ሁሉንም የተለያዩ ሳይንስ ዓይነቶች የሚያጠኑ የሳይንስ ሊቃውንት የጂኤችጂ ልቀት ምስጢራዊነት እና ውጤቶቻቸውን ለማወቅ አብረው መሥራት ጀመሩ ፡፡ ቴክኖሎጂ እየገፋ ሲሄድ በ 2 ደረጃዎች የመጨመሩ ማረጋገጫ በ 1980 ዎቹ ውስጥ ነበር ፡ በቁፋሮ የተያዘ የበረዶ እምብርት የካርቦን ዳይኦክሳይድ መጠን ከፍ ማለቱን ግልፅ ማስረጃ አቅርቧል ፡፡ 17 የዓለም ሙቀት መጨመር በባህር ደረጃዎች ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ የዓለም ሙቀት መጨመር ማለት አንታርክቲካ እና ግሪንላንድ የበረዶ ንጣፎች እየቀለጡ እና ውቅያኖሶች እየሰፉ ናቸው ማለት ነው ፡ የቅርብ ጊዜ የአየር ንብረት ለውጥ አሁንም 6 ሜትር (20 ጫማ) እንኳን ባሕር-ደረጃ መነሳት ሊያስከትል ነበር ግሪንሃውስ ጋዝ ልቀት ውስጥ ሳይንሳዊ ወረቀት በ 2015 ቅናሽ ነበር ሳይንስ . 18] እንደ ባንግላዴሽ ፣ ፍሎሪዳ ፣ ኔዘርላንድስ እና ሌሎች አካባቢዎች ያሉ ዝቅተኛ ስፍራዎች ከፍተኛ የጎርፍ መጥለቅለቅ ይገጥማቸዋል ፡ 20] በአሁኑ የባህር ደረጃ የተጎዱት ከተሞች ጭማሪ በ 6 ሜትር (20 ጫማ) በባህር ከፍታ በጎርፍ የሚጥለቀለቁ ቦታዎች አሁን ያለው የባህር ደረጃ ከፍ ካለ ብዙ ከተሞች የባህር ወደቦች እና የጎርፍ አደጋዎች ናቸው ፡ እነዚህ እና ሌሎቹ ከተሞች እየጨመረ የመጣውን የባህር ከፍታ እና ተያያዥ የዝናብ ማዕበልን ለመቋቋም መሞከራቸውን ጀምረዋል ፣ ወይም በዚህ ላይ እየተወያዩ መሆናቸውን ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል ፡ ለንደን ኒው ዮርክ ሲቲ በአሜሪካ ውስጥ በሃምፕተን መንገዶች አካባቢ ኖርፎልክ ቨርጂኒያ ሳውዝሃምፕተን ክሪስፊልድ ፣ ሜሪላንድ ፣ አሜሪካ ቻርለስተን ፣ ሳውዝ ካሮላይና ማይሚ ፣ ፍሎሪዳ ከአውሎ ነፋሱ ጋር በተዛመደ የጎርፍ መጥለቅለቅ እና በባህር ደረጃ መጨመር በንብረት ላይ ጉዳት ሊያስከትል በሚችል ሁኔታ “በአለም ቁጥር እጅግ ተጋላጭ የሆነች ከተማ” ተብላ ተመዘገበች ፡ 32 ሴንት ፒተርስበርግ ሲድኒ ፣ አውስትራሊያ ጃካርታ እና ውስጥ, , ፓኪስታን ማሌ ፣ ማልዲቭስ ሙምባይ ፣ ቦነስ አይረስ ፣ ሎስ አንጀለስ ፣ ሪዮ ዴ ጄኔይሮ ደግሞም ሁሉም ሌሎች የባህር ዳርቻ ከተሞች አደጋ ላይ ናቸው ፡፡ ተጨማሪ ንባብ የአየር ንብረት ለውጥ ናሽናል ጂኦግራፊክ ልጆች ምንድነው? የአየር ንብረት ለውጥ ምንድነው? በእውነት ቀላል መመሪያ ቢቢሲ ተዛማጅ ገጾች የአየር ንብረት ለውጥ ጄምስ ሃንሰን ስተርን ክለሳ የአየር ንብረት ለውጥን በተመለከተ የመንግሥታት ፓነል ከባቢ አየር ችግር
52551
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A4%E1%8A%95%E1%8C%83%E1%88%9A%E1%8A%95%20%E1%8A%94%E1%89%B3%E1%8A%95%E1%8B%AB%E1%88%81
ቤንጃሚን ኔታንያሁ
ቤንጃሚን "ቢቢ" ኔታንያሁ ጥቅምት 21 ቀን 1949 የተወለደ) የእስራኤል ፖለቲከኛ ነው ከ1996 እስከ 1999 እና ከ2009 እስከ 2021 ዘጠነኛው የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ ያገለገለ። ኔታንያሁ በአሁኑ ጊዜ የተቃዋሚ መሪ እና የሊኩድ - ብሄራዊ ሊበራል ንቅናቄ ሊቀመንበር ሆነው ያገለግላሉ። በአጠቃላይ ለ15 አመታት በስልጣን ላይ ያገለገሉ ሲሆን ይህም በታሪክ ረጅሙ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር አድርገውታል። በእስራኤል የነጻነት መግለጫ ከወጣ በኋላ የተወለዱ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ። በቴል አቪቭ ከአለማዊ አይሁዳዊ ወላጆች የተወለዱት ኔታንያሁ ሁለቱም በኢየሩሳሌም እና ለተወሰነ ጊዜ በፊላደልፊያ፣ ፔንስልቬንያ በዩናይትድ ስቴትስ ያደጉ ናቸው። እ.ኤ.አ. በ1967 የእስራኤል መከላከያ ሰራዊትን ለመቀላቀል ወደ እስራኤል ተመለሰ። በሳይሬት ማትካል ልዩ ሃይል የቡድን መሪ ሆነ እና በተለያዩ ተልእኮዎች ተሳትፏል፣ በክብር ከመልቀቁ በፊት የካፒቴንነት ማዕረግ አግኝቷል። ኔታንያሁ ከማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ተቋም ከተመረቁ በኋላ የቦስተን አማካሪ ቡድን የኢኮኖሚ አማካሪ ሆነዋል። በ1978 ዮናታን ኔታንያሁ ፀረ-ሽብር ተቋምን ለማግኘት ወደ እስራኤል ተመለሰ። ከ1984-1988 ኔታንያሁ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእስራኤል ቋሚ ተወካይ ነበሩ። እ.ኤ.አ. በ 1993 የተቃዋሚዎች መሪ በመሆን የሊኩድ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል ። እ.ኤ.አ. በ1996 በተካሄደው ምርጫ የወቅቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺሞን ፔሬስን በማሸነፍ የእስራኤል ትንሹ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። አንድ ጊዜ ካገለገሉ በኋላ ኔታንያሁ እና ሊኩድ በ1999 በተካሄደው ምርጫ በናዖድ ባራቅ አንድ የእስራኤል ፓርቲ በከፍተኛ ሁኔታ ተሸንፈዋል። ኔታንያሁ ከፖለቲካው ሙሉ በሙሉ ጡረታ መውጣትን መርጠው ወደ ግሉ ዘርፍ ገቡ። ከበርካታ አመታት በኋላ፣ የተተኩት የሊኩድ ሊቀመንበር ኤሪያል ሻሮን ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑ በኋላ ኔታንያሁ ወደ ፖለቲካው ለመመለስ እርግጠኛ ሆነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የገንዘብ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል። ኔታንያሁ የገንዘብ ሚኒስትር እንደመሆናቸው መጠን የእስራኤልን ቀጣይ የኢኮኖሚ አፈጻጸም በእጅጉ እንዳሻሻሉ ተንታኞች የሚናገሩትን በእስራኤል ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ ማሻሻያ አድርጓል። ኔታንያሁ በኋላ ከሳሮን ጋር ተጋጭተዋል፣ በመጨረሻም የጋዛን የመልቀቅ እቅድን በተመለከተ በተፈጠረው አለመግባባት ስራቸውን ለቀቁ። ሻሮን ካዲማ አዲስ ፓርቲ ለመመስረት ናታንያሁ በታህሳስ 2005 ወደ ሊኩድ አመራር ተመለሰ። እ.ኤ.አ. ከ2006 እስከ 2009 የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ነበሩ። ምንም እንኳን በ2009 በካዲማ ምርጫ ሊኩድ ሁለተኛ ሆኖ ቢያጠናቅቅም ኔታንያሁ ከሌሎች የቀኝ ክንፍ ፓርቲዎች ጋር ጥምር መንግስት መመስረት በመቻሉ ለሁለተኛ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሃላ ፈጸሙ። እ.ኤ.አ. በ2013 እና 2015 ምርጫ ሊኩድን ወደ አሸናፊነት መርቷል። የኤፕሪል 2019 ምርጫ የትኛውም ፓርቲ መንግስት መመስረት ካልቻለ በኋላ፣ በ2019 ሁለተኛ ምርጫ ተካሂዷል። በሴፕቴምበር 2019 በተካሄደው ምርጫ፣ በቤኒ ጋንትዝ የሚመራው የማዕከላዊው ሰማያዊ እና ነጭ ጥምረት ከኔታንያሁ ሊኩድ ትንሽ ቀድሞ ወጣ። ሆኖም ኔታንያሁም ሆነ ጋንትዝ መንግሥት መመስረት አልቻሉም። ከቀጠለ የፖለቲካ አለመግባባት በኋላ፣ የ2020 ምርጫን ተከትሎ ሊኩድ እና ሰማያዊ እና ነጭ የጥምር ስምምነት ሲደርሱ ይህ ተፈቷል። በስምምነቱ መሰረት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኔታንያሁ እና ቤኒ ጋንትዝ መካከል ይሽከረከራሉ፣ በዚህም ጋንትዝ በኖቬምበር 2021 ናታንያሁ እንዲተኩ ታቅዶ ነበር። በታህሳስ 2020 ይህ ጥምረት ፈርሶ በማርች 2021 አዲስ ምርጫ ተካሄዷል። በመጨረሻው መንግስቱ ኔታንያሁ የእስራኤልን ምላሽ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና ለ2021 የእስራኤል-ፍልስጤም ቀውስ መርቷል። በጁን 2021 ናፍታሊ ቤኔት ከያይር ላፒድ ጋር መንግስት ከመሰረተ በኋላ ኔታንያሁ ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ተወግዶ ለሶስተኛ ጊዜ የተቃዋሚ መሪ ሆነ። ኔታንያሁ እ.ኤ.አ. ከ1980ዎቹ ጀምሮ የግል ጓደኛቸው ከነበሩት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ያላቸውን ቅርበት ፣ እ.ኤ.አ. ከ2016 ጀምሮ በእስራኤል ለነበራቸው የፖለቲካ ጥሪ ዋና ማዕከል አድርገው ነበር። የአብርሃም ስምምነት፣ በእስራኤል እና በተለያዩ የአረብ ሀገራት መካከል የተደረጉ ተከታታይ የመደበኛ ስምምነቶች። እ.ኤ.አ. ከታህሳስ 2016 ጀምሮ ኔታንያሁ በእስራኤል ፖሊስ እና አቃቤ ህግ የሙስና ወንጀል ምርመራ ሲደረግላቸው ቆይቷል። እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 21 ቀን 2019 እምነትን በመጣስ፣ በሙስና እና በማጭበርበር ወንጀል ተከሷል። በቀረበበት ክስ ምክንያት ኔታንያሁ ከስልጣናቸው ከመነሳታቸው በፊት ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ ውጭ ያሉትን ሁሉንም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ሃላፊነታቸውን እንዲለቁ በህጋዊ መንገድ ተጠይቀው ነበር። የመጀመሪያ ህይወት እና ወታደራዊ ስራ ኔታንያሁ በ1949 በቴል አቪቭ እስራኤል ከአይሁዳዊ ቤተሰብ ተወለደ። እናቱ ትዚላ ሰጋል የተወለደችው በኦቶማን ኢምፓየር የኢየሩሳሌም ሙታሳሪፌት ውስጥ በፔታህ ቲክቫ ሲሆን አባቱ ዋርሶ የተወለደው ቤንዚዮን ኔታንያሁ (ኒ ሚሌይኮውስኪ፣ 1910–2012) የአይሁዶች ወርቃማ ላይ ልዩ የታሪክ ምሁር ነበሩ። የስፔን ዕድሜ. የናታንያሁ አባታዊ አያት ናታን ሚሌይኮቭስኪ ረቢ እና የጽዮናውያን ጸሃፊ ነበሩ። የናታንያሁ አባት ወደ እስራኤል ሲሰደድ ስሙን ከ"ሚሌይኮቭስኪ" ወደ "ናታንያሁ" ማለትም "እግዚአብሔር ሰጠ" ብሎ ጠራ። ቤተሰቦቹ በብዛት አሽከናዚ ሲሆኑ፣ የ ምርመራ የሴፋርዲክ የዘር ግንድ እንዳለው እንዳረጋገጠለት ተናግሯል። ከቪልና ጋኦን ዘር ነው ይላል። ኔታንያሁ ከሶስት ልጆች ሁለተኛ ሰው ነበር። መጀመሪያ ያደገው እና ​​የተማረው በኢየሩሳሌም ሲሆን እዚያም ሄንሪታ ስዞልድ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቷል። ከ6ኛ ክፍል መምህሩ ሩት ሩበንስታይን ያገኘው የግምገማ ግልባጭ ኔታንያሁ ጨዋ፣ጨዋ እና አጋዥ እንደነበር አመልክቷል። ሥራው "ተጠያቂ እና በሰዓቱ" እንደነበረ; እና እሱ ተግባቢ፣ ተግሣጽ ያለው፣ ደስተኛ፣ ደፋር፣ ንቁ እና ታዛዥ ነበር። እ.ኤ.አ. በ1956 እና በ1958 መካከል እና ከ1963 እስከ 1967 ድረስ ቤተሰቦቹ በዩናይትድ ስቴትስ በቼልተንሃም ታውንሺፕ ፔንስልቬንያ በፊላደልፊያ ከተማ ዳርቻ ይኖሩ የነበረ ሲሆን አባ ቤንዚዮን ኔታንያሁ በድሮፕሲ ኮሌጅ አስተምረዋል። ቤንጃሚን ተከታትሎ ከቼልተንሃም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል እናም በክርክር ክለብ፣ በቼዝ ክለብ እና በእግር ኳስ ንቁ ተሳትፎ አድርጓል። እሱ እና ወንድሙ ዮናታን በአካባቢው ባጋጠሟቸው ላዩን የአኗኗር ዘይቤዎች እርካታ አጥተው ነበር፣ ይህም የወጣቶች ፀረ-ባህል እንቅስቃሴ፣ እና ቤተሰቡ በተገኙበት የተሃድሶ ምኩራብ ፣ የይሁዳ ቤተመቅደስ ፣ የሊበራል ስሜቶችን ጨምሮ። እ.ኤ.አ. በውጊያ ወታደርነት አሰልጥኖ ለአምስት ዓመታት በመከላከያ ሰራዊት ልዩ ሃይል ክፍል በሳይሬት ማትካል አገልግሏል። እ.ኤ.አ. በተለያዩ ጊዜያት በጦርነት ቆስሏል። እ.ኤ.አ. በ1968 እስራኤላውያን በሊባኖስ ላይ ያደረጉትን ወረራ እና በግንቦት 1972 የተጠለፈውን የሳቤና በረራ 571 መታደግን ጨምሮ በሌሎች በርካታ ተልዕኮዎች ውስጥ ተሳትፏል። እ.ኤ.አ. በ 1972 ከነቃ አገልግሎት ተባረረ ነገር ግን በሳይሬት ማትካል ክምችት ውስጥ ቆየ። ከተለቀቀ በኋላ፣ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለመማር ሄደ፣ ነገር ግን በዮም ኪፑር ጦርነት ለማገልገል በጥቅምት 1973 ተመለሰ። በሶሪያ ግዛት ውስጥ ጥልቅ የሆነ የኮማንዶ ጥቃትን ከመምራቱ በፊት በስዊዝ ካናል ላይ ልዩ ሃይል በግብፅ ሃይሎች ላይ ባደረገው ወረራ ተሳትፏል። ኔታንያሁ በ1972 መጨረሻ ላይ በማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ () የስነ-ህንፃ ጥናት ለመማር ወደ አሜሪካ ተመለሰ። በዮም ኪፑር ጦርነት ለመፋለም ወደ እስራኤል ለአጭር ጊዜ ከተመለሰ በኋላ ወደ አሜሪካ ተመለሰ እና ቤን ኒታይ በሚል ስያሜ በየካቲት 1975 የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በአርክቴክቸር አጠናቅቆ በሰኔ 1976 ከ አስተዳደር ትምህርት ቤት ሁለተኛ ዲግሪ አግኝቷል። በተመሳሳይ በኦፕሬሽን ኢንቴቤ ወንድሙ ሞት ትምህርቱ እስኪቋረጥ ድረስ በፖለቲካል ሳይንስ የዶክትሬት ዲግሪ እየተማረ ነበር። በ ኔታንያሁ በዮም ኪፑር ጦርነት ለመፋለም እረፍት ቢወስዱም የማስተርስ ዲግሪያቸውን (በተለምዶ አራት አመት የሚፈጅ) በሁለት አመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ባለ ሁለት ሎድ አጥንተዋል። በ ውስጥ ፕሮፌሰር ግሮሰር እንዲህ በማለት አስታውሰዋል፡- “በጣም ጥሩ አደረገ። በጣም ብሩህ ነበር፣ የተደራጀ፣ ጠንካራ፣ ኃይለኛ። ምን ማድረግ እንደሚፈልግ እና እንዴት ማድረግ እንዳለበት ያውቅ ነበር። በዚያን ጊዜ ስሙን ቢንያም "ቤን" ኒታይ ብሎ ለወጠው (ኒታይ፣ የኒታይ ተራራ እና የአርቤላ ስም ለሚታወቀው አይሁዳዊ ጠቢብ ኒታይ፣ አባቱ ብዙ ጊዜ ለጽሁፎች ይጠቀምበት የነበረው የብዕር ስም ነው።) ከአመታት በኋላ ኔታንያሁ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው ቃለ ምልልስ አሜሪካውያን ስሙን መጥራት እንዲችሉ ለማድረግ መወሰኑን አብራርተዋል። ይህ እውነታ በፖለቲካ ተቀናቃኞቹ የእስራኤል ብሄራዊ ማንነት እና ታማኝነት እጦት በተዘዋዋሪ እንዲከሷቸው አድርገውታል። በ1976 የኔታንያሁ ታላቅ ወንድም ዮናታን ኔታንያሁ ተገደለ። ዮናታን የቢንያም የቀድሞ ክፍል አዛዥ ሳይሬት ማትካል አዛዥ ሆኖ ሲያገለግል እና ሽብርተኝነትን ለመከላከል በተካሄደው ታጋቾች የማዳን ተልዕኮ ኦፕሬሽን ኢንቴቤ በተባለበት ወቅት በአሸባሪዎች የተነጠቁ ከ100 በላይ እስራኤላውያን ታጋቾችን በማዳን ወደ ዩጋንዳ ኢንቴቤ አየር ማረፊያ ተወስዷል። . እ.ኤ.አ. በ 1976 ኔታንያሁ በክፍላቸው ጫፍ አቅራቢያ በ የተመረቀ ሲሆን በቦስተን ፣ ማሳቹሴትስ ውስጥ ለቦስተን አማካሪ ቡድን ኢኮኖሚያዊ አማካሪ ሆኖ በ 1976 እና 1978 መካከል በኩባንያው ውስጥ ይሠራ ነበር ። በቦስተን ኮንሰልቲንግ ቡድን፣ እሱ የሚት ሮምኒ ባልደረባ ነበር፣ ከእሱ ጋር ዘላቂ ወዳጅነት መሰረተ። ሮምኒ በወቅቱ ኔታንያሁ፡- “አንድ የተለየ አመለካከት ያለው ጠንካራ ስብዕና ያለው” እንደነበር ያስታውሳሉ እና “[] በአጭሩ መናገር ይቻላል… [] የጋራ ልምዶችን ማካፈል እና እይታ እና ተመሳሳይ ነው ። ኔታንያሁ “ቀላል ግንኙነታቸው” የ. ምሁራዊ ጥብቅ ቡት ካምፕ ውጤት ነው ብለዋል።እ.ኤ.አ. በ 1978 ኔታንያሁ በቦስተን የአካባቢ ቴሌቪዥን ላይ በ "ቤን ኒታይ" ስም ቀርበው ተከራክረዋል: "የግጭቱ ዋና ዋና የአረቦች የእስራኤልን መንግስት ለመቀበል አለመታደል ነው ... ለ 20 ዓመታት አረቦች ነበሩ ። ሁለቱም ዌስት ባንክ እና የጋዛ ሰርጥ እና አሁን እንዳሉት የራስን እድል በራስ መወሰን የግጭቱ አስኳል ከሆነ በቀላሉ የፍልስጤም መንግስት መመስረት ይችሉ ነበር።በ1978 ኔታንያሁ ወደ እስራኤል ተመለሰ። እ.ኤ.አ. በ 1978 እና በ 1980 መካከል የጆናታን ኔታንያሁ ፀረ-ሽብር ተቋም, መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ለሽብርተኝነት ጥናት ያደረ; ተቋሙ በአለም አቀፍ የሽብርተኝነት ውይይት ላይ ያተኮሩ በርካታ አለም አቀፍ ጉባኤዎችን አካሂዷል። ከ1980 እስከ 1982 በኢየሩሳሌም የሚገኘው የሪም ኢንዱስትሪዎች የግብይት ዳይሬክተር ነበሩ። በዚህ ወቅት ኔታንያሁ ከበርካታ የእስራኤል ፖለቲከኞች ጋር የመጀመርያ ግኑኝነትን አድርጓል፣ ሚኒስትር ሞሼ አረንስን ጨምሮ፣ በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ምክትል ዋና ሃላፊ አድርገው የሾሙት አሬንስ በዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሲሆኑ፣ እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. እስከ 1984 ድረስ እ.ኤ.አ. በ1982 የሊባኖስ ጦርነት በሳይሬት ማትካል ለስራ ተጠባባቂ ተጠርቶ ከአገልግሎት እንዲለቀቅ ጠይቋል ፣በጦርነቱ ላይ በተሰነዘረባት ከባድ አለም አቀፍ ትችት አሜሪካ ውስጥ መቆየት እና የእስራኤል ቃል አቀባይ በመሆን ማገልገልን መርጧል። . በጦርነቱ ወቅት የእስራኤልን ጉዳይ ለመገናኛ ብዙኃን አቅርቧል እና በእስራኤል ኤምባሲ ውስጥ በጣም ቀልጣፋ የህዝብ ግንኙነት ስርዓት ዘርግቷል ። እ.ኤ.አ. በ 1984 እና 1988 መካከል ኔታንያሁ በተባበሩት መንግስታት የእስራኤል አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል ። ኔታንያሁ በ 1980 ዎቹ ውስጥ ግንኙነት የፈጠሩት በራቢ ሜናችም ኤም. ሽኔርሰን ተጽዕኖ ነበራቸው። ሽኔርሰንን “በዘመናችን በጣም ተደማጭነት ያለው ሰው” ሲል ጠርቶታል። እ.ኤ.አ. በ 1980 ዎቹ ውስጥ ፣ በዩኤን የእስራኤል አምባሳደር ሆነው ሲያገለግሉ ኔታንያሁ የወደፊቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አባት ከሆነው ፍሬድ ትራምፕ ጋር ጓደኛ ሆኑ ። የተቃዋሚዎች መሪ : አውሮፓዊ ከ1988ቱ የእስራኤል ህግ አውጪ ምርጫ በፊት ኔታንያሁ ወደ እስራኤል ተመልሶ ሊኩድ ፓርቲን ተቀላቅሏል። በሊኩድ የውስጥ ምርጫ ኔታንያሁ በፓርቲዎች ዝርዝር ውስጥ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በኋላም የ12ኛው ክኔሴት አባል ሆነው ተመርጠዋል፣ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሞሼ አሬንስ ምክትል ሆነው ተሾሙ፣ በኋላም ዴቪድ ሌቪ። ኔታንያሁ እና ሌቪ አልተባበሩም እናም በሁለቱ መካከል ያለው ፉክክር ከጊዜ በኋላ ተባብሷል። እ.ኤ.አ. በ1991 መጀመሪያ ላይ በባህረ ሰላጤው ጦርነት ወቅት እንግሊዛዊ አቀላጥፎ የነበረው ኔታንያሁ በ እና በሌሎች የዜና ማሰራጫዎች ላይ በሚዲያ ቃለ ምልልስ ላይ የእስራኤል ዋና ቃል አቀባይ ሆኖ ብቅ አለ። እ.ኤ.አ. በ 1991 የማድሪድ ኮንፈረንስ ኔታንያሁ በጠቅላይ ሚኒስትር ይዝሃክ ሻሚር የሚመራ የእስራኤል ልዑካን ቡድን አባል ነበሩ። ከማድሪድ ኮንፈረንስ በኋላ ኔታንያሁ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ምክትል ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። እ.ኤ.አ. (ሳሮን መጀመሪያ ላይ የሊኩድ ፓርቲ አመራርን ፈልጎ ነበር፣ ነገር ግን አነስተኛ ድጋፍ እንደሚስብ ሲታወቅ በፍጥነት ራሱን አገለለ)። ሻሚር በ1992 ምርጫ ሊኩድ ከተሸነፈ በኋላ ከፖለቲካው ጡረታ ወጥቷል። የይስሃቅ ራቢን መገደል ተከትሎ የሱ ጊዜያዊ ተተኪ ሺሞን ፔሬዝ መንግስት የሰላም ሂደቱን እንዲያራምድ ሥልጣን ለመስጠት ቀድሞ ምርጫ እንዲደረግ ወሰነ። ኔታንያሁ እ.ኤ.አ. ኔታንያሁ ዘመቻውን እንዲያካሂድ አሜሪካዊው ሪፐብሊካን ፖለቲከኛ አርተር ፊንከልስቴይን ቀጥሮ ነበር፣ ምንም እንኳን የአሜሪካው የድምጽ ንክሻ እና የሰላ ጥቃት ጠንከር ያለ ትችት ቢያመጣም ውጤታማ ሆኖ ተገኝቷል። እ.ኤ.አ. በ 1996 ምርጫ ኔታንያሁ ሲያሸንፉ ፣በቦታው ታሪክ ውስጥ ትንሹ እና በእስራኤል ግዛት የተወለዱ የመጀመሪያው የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር (ይትዛክ ራቢን የተወለደው በኢየሩሳሌም ፣ በብሪቲሽ ፍልስጤም ማኔጅመንት ስር ነበር ፣ 1948 የእስራኤል መንግሥት ምስረታ)። ኔታንያሁ በቅድመ ምርጫ ተወዳጁ ሺሞን ፔሬዝ ማሸነፋቸው ብዙዎችን አስገርሟል። የኋለኛው ውድቀት ውስጥ ዋና ቀስቃሽ ከምርጫው ጥቂት ቀደም ብሎ የአጥፍቶ ጠፊዎች ማዕበል ነበር; እ.ኤ.አ. በማርች 3 እና 4 ቀን 1996 ፍልስጤማውያን ሁለት የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቶችን ፈጽመዋል፣ 32 እስራኤላውያንን ገድለዋል፣ ፔሬስ ጥቃቱን ማስቆም ያልቻለ ይመስላል። በዘመቻው ወቅት ኔታንያሁ የሰላም ሂደቱ መሻሻል የፍልስጤም ብሄራዊ ባለስልጣን ግዴታውን በመወጣት ላይ የተመሰረተ እንደሚሆን አፅንዖት ሰጥተዋል-በተለይ ሽብርተኝነትን በመዋጋት - እና የሊኩድ ዘመቻ መፈክር "ናታኒያሁ - አስተማማኝ ሰላም መፍጠር" ነበር. ሆኖም ኔታንያሁ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት በተካሄደው ምርጫ ቢያሸንፉም የፔሬስ የእስራኤል ሌበር ፓርቲ በኬኔሴት ምርጫ ብዙ መቀመጫዎችን አግኝቷል። ኔታንያሁ መንግስት ለመመስረት ከኦርቶዶክስ-ኦርቶዶክስ ፓርቲዎች፣ ሻስ እና ዩቲጄ ጋር ጥምረት ላይ መተማመን ነበረበት። ጠቅላይ ሚኒስትር : አውሮፓዊ የመጀመሪያ ጊዜ ብዙ የአጥፍቶ ጠፊ ቦምቦች የሊኩድ የጸጥታ ቦታን አጠናከረ። ለአብዛኞቹ የቦምብ ጥቃቶች ሃማስ ሃላፊነቱን ወስዷል። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ስለ ብዙ የኦስሎ ስምምነት ማእከላዊ ግቢ ብዙ ጥያቄዎችን አንስቷል። ከዋና ዋና ነጥቦቹ አንዱ በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ እንደ እየሩሳሌም ሁኔታ እና የፍልስጤም ብሄራዊ ማሻሻያ በመሳሰሉት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ከማግኘቱ በፊት ለፍልስጤማውያን መስማማት አለበት የሚለው የኦስሎ መነሻ ሃሳብ ጋር አለመስማማት ነው። ቻርተር የኦስሎ ደጋፊዎች የባለብዙ መድረክ አካሄድ በፍልስጤማውያን መካከል በጎ ፈቃድ እንደሚፈጥር እና እነዚህ አበይት ጉዳዮች በኋለኞቹ ደረጃዎች ሲነሱ እርቅን እንዲፈልጉ ያነሳሳቸዋል ብለው ነበር። ኔታንያሁ እንደተናገሩት እነዚህ ቅናሾች በምላሹ ምንም ዓይነት ተጨባጭ ምልክቶችን ሳያገኙ ለአክራሪ አካላት ማበረታቻ ሰጥተዋል። ለእስራኤላውያን ቅናሾች በምላሹ የፍልስጤም በጎ ፈቃድ ተጨባጭ ምልክቶች እንዲታዩ ጠይቋል። ከኦስሎ ስምምነት ጋር ልዩነት ቢኖራቸውም፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ አፈጻጸማቸውን ቢቀጥሉም፣ ጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው ግን የሰላም ሂደቱ መቀዛቀዝ ታይቷል። እ.ኤ.አ. በ 1996 ኔታንያሁ እና የኢየሩሳሌም ከንቲባ ኢሁድ ኦልመርት ከጠቅላይ ሚኒስትር ሺሞን ፔሬዝ በፊት ለሰላም ሲባል እንዲቆይ ትእዛዝ ሰጥተውት የነበረውን የዌስተርን ግድግዳ ዋሻ በአረብ ሰፈር ውስጥ ለመክፈት ወሰኑ። ይህ በፍልስጤማውያን የሶስት ቀናት ብጥብጥ የቀሰቀሰ ሲሆን በዚህም ምክንያት በደርዘን የሚቆጠሩ እስራኤላውያን እና ፍልስጤማውያን ተገድለዋል። ኔታንያሁ የፍልስጤም ፕሬዝዳንት አራፋትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኙት በሴፕቴምበር 4 ቀን 1996 ነው። ከስብሰባው በፊት ሁለቱ መሪዎች በስልክ ተነጋገሩ። ስብሰባዎቹ እስከ መኸር 1996 ድረስ ይቀጥላሉ ። ኔታንያሁ በመጀመሪያ ስብሰባቸው ላይ እንዲህ ብለዋል: - “የሁለቱም ወገኖች ፍላጎቶች እና ፍላጎቶች በአጸፋዊነት እና በፀጥታ እና በጥሩ ሁኔታ ላይ በመመስረት የሁለቱም ወገኖች ፍላጎቶች ግምት ውስጥ ማስገባት እንዳለብን አፅንዖት መስጠት እፈልጋለሁ ። - የሁለቱም እስራኤላውያን እና ፍልስጤማውያን መሆን. አራፋት “ከሚስተር ኔታንያሁ እና ከመንግስታቸው ጋር ለመስራት ቆርጠን ተነስተናል።” ንግግሮቹ የተጠናቀቁት እ.ኤ.አ. ጥር 14 ቀን 1997 የኬብሮን ፕሮቶኮል ሲፈረም ነበር። የፍልስጤም አስተዳደር ጋር የሄብሮን ፕሮቶኮል መፈራረሙ የእስራኤል ጦር በኬብሮን እንደገና እንዲሰማራ እና የሲቪል ባለስልጣን አብዛኛው አካባቢ የፍልስጤም አስተዳደር እንዲቆጣጠር አድርጓል።ውሎ አድሮ የሰላሙ ሂደት መሻሻል አለማድረግ በ1998 የዋይ ወንዝ ማስታወሻን ያዘጋጀው አዲስ ድርድር በእስራኤል መንግስት እና በፍልስጤም አስተዳደር የ 1995 ቀደሞ ጊዜያዊ ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግ የሚወሰዱ እርምጃዎችን ዘርዝሯል። እና የ ሊቀመንበር ያሲር አራፋት፣ እና በኖቬምበር 17 1998፣ የእስራኤል 120 አባል ፓርላማ፣ ፣ የዋይ ወንዝ ማስታወሻን በ75–19 ድምጽ አጽድቋል። እ.ኤ.አ. በ1967 በካርቱም በተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ “ከጎላን ኮረብቶች መውጣት የለም፣ የኢየሩሳሌምን ጉዳይ አለመነጋገር፣ በማናቸውም ቅድመ ሁኔታዎች ድርድር የለም” የሚለውን ፖሊሲ “ሶስት የለም(ዎች)” የሚል ፖሊሲ ላይ አፅንዖት ሰጥተዋል። እ.ኤ.አ. በ1997 ኔታኒያሁ ሁለቱ ሀገራት የሰላም ስምምነት ከተፈራረሙ ከ3 ዓመታት በኋላ በዮርዳኖስ የሃማስ መሪ ካሊድ ማሻልን ለመግደል የሞሳድ ዘመቻ ፈቀደ። የሞሳድ ቡድን እንደ አምስት የካናዳ ቱሪስቶች በሴፕቴምበር 27 ቀን 1997 ወደ ዮርዳኖስ ገብቶ በአማን ጎዳና ላይ የማሻልን ጆሮ መርዝ ገባ። ሴራው የተጋለጠ ሲሆን ሁለት ወኪሎች በዮርዳኖስ ፖሊስ ተይዘው ሲታሰሩ ሌሎች ሶስት ሰዎች ደግሞ በእስራኤል ኤምባሲ ውስጥ ተደብቀው በወታደሮች ተከቧል። የተበሳጨው ንጉስ ሁሴን እስራኤል መድሃኒቱን እንድትሰጥ ጠየቀ እና የሰላም ስምምነቱን እንደሚያፈርስ ዝቷል። ኔታንያሁ የዩኤስ ፕሬዝዳንት ቢል ክሊንተን ግፊት ካደረጉ በኋላ ጥያቄውን ተቀብለው ሼክ አህመድ ያሲንን ጨምሮ 61 የዮርዳኖስና የፍልስጤም እስረኞች እንዲፈቱ ትእዛዝ ሰጥተዋል። ክስተቱ ገና የእስራኤል እና የዮርዳኖስ ግንኙነት እያሽቆለቆለ ሄደ። በስልጣን ዘመናቸው ኔታንያሁ ወደ ነፃ ገበያ ኢኮኖሚ የሚያመሩ እርምጃዎችን በመውሰድ የኢኮኖሚ ነፃነት ሂደትን ጀምሯል። በእሱ ክትትል፣ መንግስት በባንክ እና በመንግስት ዋና ዋና ኩባንያዎች ውስጥ ያለውን ድርሻ መሸጥ ጀመረ። በተጨማሪም ኔታንያሁ የእስራኤል ጥብቅ የውጭ ምንዛሪ ቁጥጥርን በእጅጉ በማቃለሉ እስራኤላውያን ያልተገደበ ገንዘብ ከሀገራቸው እንዲወጡ፣ የውጭ ባንክ አካውንቶችን እንዲከፍቱ፣ የውጭ ምንዛሪ እንዲይዙ እና በሌሎች ሀገራት በነፃነት ኢንቨስት እንዲያደርጉ አስችሏቸዋል።በስልጣን ዘመናቸው ሁሉ ኔታንያሁ በእስራኤል የፖለቲካ ግራ ክንፍ ሲቃወሙ እና በኬብሮን እና በሌሎች ቦታዎች ለፍልስጤማውያን ባደረጉት ስምምነት እና በአጠቃላይ ከአራፋት ጋር ባደረጉት ድርድር ከቀኝ በኩል ድጋፍ አጥተዋል። ኔታንያሁ በትዳራቸው እና በሙስና ክስ ከተመሰረተባቸው ረጅም ተከታታይ ቅሌቶች በኋላ በእስራኤል ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት አጥተዋል። እ.ኤ.አ. በ1997 ፖሊስ ኔታንያሁ በሙስና ወንጀል ክስ እንዲመሰረት ሐሳብ አቀረበ። ክሱን የሚቀንስ ጠቅላይ አቃቤ ህግ በመሾም ተከሷል ነገር ግን አቃቤ ህግ ለፍርድ ለመቅረብ በቂ ማስረጃ የለም በማለት ብይን ሰጥቷል። እ.ኤ.አ. በ 1999 ኔታንያሁ የእስራኤል ፖሊስ ከመንግስት ተቋራጭ ነፃ አገልግሎት በ100,000 ዶላር በሙስና ክስ እንዲመሰረትበት ሲያበረታታ ሌላ ቅሌት ገጠመው። የእስራኤል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በማስረጃ የተቸገሩትን በመጥቀስ ክስ አልመሰረተም። የምርጫ ሽንፈት እ.ኤ.አ. በ1999 በተካሄደው የጠቅላይ ሚኒስትርነት ምርጫ በናዖድ ባራቅ ከተሸነፈ በኋላ ኔታንያሁ ለጊዜው ከፖለቲካው ጡረታ ወጥቷል። በመቀጠልም ከእስራኤል የመገናኛ መሳሪያዎች አምራች ጋር ለሁለት አመታት በከፍተኛ አማካሪነት አገልግሏል። እ.ኤ.አ. በ2000 መገባደጃ ላይ የባርቅ መንግስት ወድቆ ኔታንያሁ ወደ ፖለቲካው የመመለስ ፍላጎት እንዳለው ገለፀ። በህጉ መሰረት የባራክ ስልጣን መልቀቅ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ ብቻ ምርጫ እንዲደረግ ታስቦ ነበር። ኔታንያሁ አጠቃላይ ምርጫ መካሄድ አለበት ሲሉ አጥብቀው የጠየቁ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን የተረጋጋ መንግስት ሊኖር አይችልም ብለዋል። ኔታንያሁ ውሎ አድሮ ለጠቅላይ ሚንስትርነት ቦታ ላለመወዳደር ወሰኑ፣ ይህ እርምጃ በወቅቱ ከኔታንያሁ ያነሰ ተወዳጅነት የጎደለው ይባል የነበረው ኤሪኤል ሻሮን ወደ ስልጣን እንዲወጣ አመቻችቷል። እ.ኤ.አ. በ 2002 የእስራኤል ሌበር ፓርቲ ከጥምረቱ ወጥቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነቱን ከለቀቁ በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤሪያል ሻሮን ኔታንያሁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አድርገው ሾሙ። ኔታንያሁ ሳሮንን ለሊኩድ ፓርቲ መሪነት ቢሞግቱትም ከስልጣን ሊያነሱት አልቻሉም። በሴፕቴምበር 9 ቀን 2002 ኔታንያሁ በሞንትሪያል ፣ ኩቤክ ፣ ካናዳ በሚገኘው ኮንኮርዲያ ዩኒቨርሲቲ ሊያደርጉት የታቀደው ንግግር በመቶዎች የሚቆጠሩ የፍልስጤም ደጋፊ ተቃዋሚዎች ደህንነታቸውን ካጨናነቁ እና በመስታወት መስኮት ከተሰባበሩ በኋላ ተሰርዟል። ኔታንያሁ በሞንትሪያል ሪትዝ ካርልተን ሆቴል ቆይታው ውስጥ በመቆየታቸው በተቃውሞው ላይ አልነበሩም። በኋላ አክቲቪስቶቹን ሽብርተኝነትን ይደግፋሉ እና “ያበደ ቅንዓት” ሲል ከሰዋል። ከሳምንታት በኋላ እ.ኤ.አ ኦክቶበር 1 2002 ወደ 200 የሚጠጉ ተቃዋሚዎች ከኔታንያሁ ጋር በፒትስበርግ ከሄይንዝ አዳራሽ መገኘት ውጭ ተገናኙ። ምንም እንኳን የፒትስበርግ ፖሊስ፣ የእስራኤል ደህንነት እና የፒትስበርግ ክፍል ንግግሮቹ መሃል ከተማውን በአዳራሹ እና በዱኪሴን ክለብ እንዲሁም በከተማ ዳርቻ ሮበርት ሞሪስ ዩኒቨርሲቲ እንዲቀጥሉ ፈቅደዋል። በሴፕቴምበር 12 ቀን 2002 ኔታንያሁ በኢራቅ ግዛት የተፈጠረውን የኒውክሌር ስጋት አስመልክቶ በዩኤስ የተወካዮች ምክር ቤት የቁጥጥር እና የመንግስት ማሻሻያ ኮሚቴ ፊት (እንደ የግል ዜጋ በመሐላ) መስክሯል፡- “ሳዳም እየፈለገ ያለው እና እየሠራ ያለው ምንም አይነት ጥያቄ የለም። እና ወደ ኑክሌር ጦር መሳሪያ ልማት እየገሰገሰ ነው - ምንም ጥያቄ የለውም "ብለዋል. "እና አንዴ ካገኘ በኋላ, ታሪክ ወዲያውኑ እንደሚቀያየር ምንም ጥርጥር የለውም." በምስክርነቱ፣ ኔታንያሁም “የሳዳምን አገዛዝ ሳዳምን ከወሰድክ፣ በአካባቢው ላይ ትልቅ አዎንታዊ አስተያየት እንደሚኖረው አረጋግጥልሃለሁ” ብሏል። የገንዘብ ሚኒስትር : አውሮፓውያን እ.ኤ.አ. ከ2003 የእስራኤል ህግ አውጪ ምርጫ በኋላ ፣ ብዙ ታዛቢዎች እንደ አስገራሚ እርምጃ የቆጠሩት ፣ ሳሮን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ለሲልቫን ሻሎም አቅርቦ ለናታንያሁ የፋይናንስ ሚኒስቴር አቀረበች። አንዳንድ ተመራማሪዎች ሻሮን ይህን እርምጃ የወሰደው ኔታንያሁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ባሳዩት ብቃት በፖለቲካዊ ስጋት በመቁጠራቸው እና በኢኮኖሚ እርግጠኛ ባልሆነበት ወቅት በፋይናንስ ሚኒስቴር ውስጥ በማስቀመጥ የኔታንያሁ ተወዳጅነት ሊቀንስ ይችላል ብለው ይገምታሉ። ኔታንያሁ አዲሱን ሹመት ተቀብለዋል። ሻሮን እና ኔታንያሁ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል ኔታንያሁ እንደ የገንዘብ ሚንስትርነት ሙሉ ነፃነት እንደሚኖራቸው እና ሻሮን ማሻሻያዎቻቸውን ሁሉ እንዲመልሱላቸው ኔታንያሁ በሳሮን የእስራኤል ወታደራዊ እና የውጭ ጉዳይ ጉዳዮች ላይ የሳሮን አስተዳደር ዝም በማለታቸው ነው። ኔታንያሁ የገንዘብ ሚኒስትር እንደመሆናቸው መጠን በሁለተኛው ኢንቲፋዳ ወቅት የእስራኤልን ኢኮኖሚ ከዝቅተኛ ደረጃው ለመመለስ የሚያስችል የኢኮኖሚ እቅድ አውጥተዋል። ኔታንያሁ የኢኮኖሚ እድገትን ለማደናቀፍ የተዳከመ የህዝብ ሴክተር እና ከልክ ያለፈ መመሪያዎች ናቸው ብለዋል ። ምንም እንኳን ተቺዎቹ ባይኖሩም የእሱ እቅድ ወደ ነፃ ወደሆኑ ገበያዎች መሄድን ያካትታል። ሰዎች ለሥራ ወይም ለሥልጠና እንዲያመለክቱ፣ የመንግሥት ሴክተርን መጠን እንዲቀንስ፣ የመንግሥት ወጪን ለሦስት ዓመታት እንዲታገድና የበጀት ጉድለቱን 1 በመቶ እንዲሸፍን በማድረግ የበጎ አድራጎት ጥገኝነትን ለማቆም የሚያስችል ፕሮግራም ዘረጋ። የግብር አከፋፈል ስርዓቱ ተስተካክሎ ታክስ እንዲቀንስ የተደረገ ሲሆን ከፍተኛ የግለሰብ ታክስ መጠን ከ64% ወደ 44% እና የድርጅት ታክስ ምጣኔ ከ36 በመቶ ወደ 18 በመቶ ዝቅ ብሏል። ብዙ ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የመንግስት ሀብት ወደ ግል ተዛውሯል ከነዚህም መካከል ባንኮች፣ ዘይት ማጣሪያዎች፣ ኤል አል ብሔራዊ አየር መንገድ እና ዚም የተቀናጀ የመርከብ አገልግሎት። ለወንዶችም ለሴቶችም የጡረታ ዕድሜ ጨምሯል, እና የገንዘብ ልውውጥ ህጎች የበለጠ ነፃ ሆነዋል. ንግድ ባንኮች የረዥም ጊዜ ቁጠባቸውን ለመተው ተገደዱ። በተጨማሪም ኔታንያሁ ፉክክርን ለመጨመር ሞኖፖሊዎችን እና ካርቴሎችን አጠቃ። የእስራኤል ኢኮኖሚ ማደግ ሲጀምር እና ስራ አጥነት በከፍተኛ ደረጃ እያሽቆለቆለ ሲሄድ ኔታንያሁ በስልጣን ዘመናቸው መጨረሻ 'ኢኮኖሚያዊ ተአምር' እንደሰሩ አስተያየት ሰጪዎች በሰፊው ይነገር ነበር። ነገር ግን፣ በሌበር ፓርቲ ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች (እና ጥቂቶቹ በእራሱ ሊኩድ ውስጥ) የናታንያሁ ፖሊሲዎች በተከበረው የእስራኤል የማህበራዊ ሴፍቲኔት መረብ ላይ እንደ “ታቸር” ጥቃት ይመለከቱ ነበር። በስተመጨረሻ፣ የኢኮኖሚ ዕድገቱ እየጨመረ በሄደበት ወቅት ሥራ አጥነት ቀንሷል፣ የዕዳ-ከ- ጥምርታ በዓለም ዝቅተኛ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ዝቅ ብሏል፣ እና የውጭ ኢንቨስትመንት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። ኔታንያሁ በ2004 የጋዛን የማስወገጃ እቅድ ህዝበ ውሳኔ እስካልተደረገ ድረስ ከስልጣናቸው እንደሚለቁ ዝተዋል። በኋላ ላይ ኡልቲማተም አሻሽሎ በኪነሴት ውስጥ ለፕሮግራሙ ድምጽ ሰጥቷል, ይህም ወዲያውኑ በ 14 ቀናት ውስጥ ህዝበ ውሳኔ ካልተደረገ በስተቀር ስልጣኑን እንደሚለቁ አመልክቷል. የእስራኤል ካቢኔ 17 ለ 5 ድምፅ ከመስጠቱ በፊት ከጋዛ የመውጣትን የመጀመሪያ ምዕራፍ ከማጽደቁ ጥቂት ቀደም ብሎ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 7 ቀን 2005 የመልቀቂያ ደብዳቤ አስገባ። የተቃዋሚዎች መሪ : አውሮፓዊ ሻሮን ከሊኩድ መውጣቱን ተከትሎ ኔታንያሁ ለሊኩድ አመራር ከተወዳደሩት በርካታ እጩዎች አንዱ ነበር። ከዚህ በፊት ያደረገው የቅርብ ጊዜ ሙከራ በሴፕቴምበር 2005 ለሊኩድ ፓርቲ መሪነት ቀደምት ቅድመ ምርጫዎችን ለማድረግ ሲሞክር ፓርቲው የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታን ሲይዝ - በዚህም አሪኤል ሻሮንን ከስልጣን እንዲወርድ ገፋፍቶታል። ፓርቲው ይህንን ተነሳሽነት አልተቀበለውም። ኔታንያሁ መሪነቱን በታህሳስ 20 ቀን 2005 እንደገና ተረከበ፣ በ 47% የመጀመሪያ ድምጽ፣ 32% ለሲልቫን ሻሎም እና 15% ለሞሼ ፌይሊን። እ.ኤ.አ. በማርች 2006 በኬኔሴት ምርጫ ሊኩድ ከካዲማ እና ሌበር ቀጥሎ ሶስተኛ ደረጃን የያዙ ሲሆን ኔታንያሁ ደግሞ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ. ኦገስት 14 ቀን 2007 ኔታንያሁ የሊኩድ ሊቀመንበር እና እጩው ለጠቅላይ ሚኒስትርነት 73% ድምጽ በማግኘት የቀኝ ቀኝ እጩ ሞሼ ፌይሊን እና የአለም ሊኩድ ሊቀመንበር ዳኒ ዳኖን በመቃወም በድጋሚ ተመረጡ። እ.ኤ.አ. በ2008 የተካሄደውን የእስራኤል–ሃማስ የተኩስ አቁም ተቃወመ፣ ልክ እንደሌሎች የ ተቃዋሚዎች። በተለይም ኔታንያሁ “ይህ ዘና ለማለት ሳይሆን የእስራኤል ሃማስን ለማስታጠቅ የተደረገ ስምምነት ነው... ለዚህ ምን እያገኘን ነው?” ብለዋል። እ.ኤ.አ. በ 2008 የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ ዶክተሮች ጤናማ ሆኖ የተገኘ አንድ ትንሽ የአንጀት ፖሊፕ አስወገዱ። የቲዚፒ ሊቪኒ ካዲማን እንዲመሩ መመረጣቸውን እና ኦልመርት ከጠቅላይ ሚኒስትርነት መልቀቃቸውን ተከትሎ ኔታንያሁ ሊቪኒ ጥምረት ለመቀላቀል ፈቃደኛ አልሆነም እና በየካቲት 2009 የተካሄደውን አዲስ ምርጫ ደግፏል። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. የሕዝብ አስተያየት መስጫዎች ሊኩድ በበላይነት እንደሚመሩ አሳይተዋል፣ ነገር ግን ከእስራኤል መራጮች መካከል አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት ውሳኔ ባለማግኘታቸው ነው። በምርጫው እራሱ ሊኩድ ሁለተኛውን ከፍተኛ ወንበር አሸንፏል። ለሊኩድ በአንፃራዊ ሁኔታ ደካማ ማሳያ ሊሆን የሚችለው አንዳንድ የሊኩድ ደጋፊዎች ወደ አቪግዶር ሊበርማን የእስራኤል ቤይቲኑ ፓርቲ መክደዳቸው ነው። ኔታንያሁ ግን የቀኝ ክንፍ ፓርቲዎች አብላጫ ድምፅ ማግኘታቸውን በመግለጽ አሸንፈው የካቲት 20 ቀን 2009 ኢሁድ ኦልመርትን በመተካት በጠቅላይ ሚኒስትርነት ኔታንያሁ በእስራኤሉ ፕሬዝዳንት ሺሞን ፔሬዝ ተሾሙ እና ድርድር ለመመስረት ድርድር ጀመረ። ጥምር መንግስት. የቀኝ ክንፍ ፓርቲዎች አብላጫውን 65 የኪነሴት መቀመጫዎች ቢያሸንፉም፣ ኔታንያሁ ሰፋ ያለ የመሀል አዋቂ ጥምረትን መርጠው የካዲማ ተቀናቃኞቻቸው ሆነው በቲዚፒ ሊቪኒ ሊቀመንበርነት ወደ መንግስታቸው ዞረዋል። በዚህ ጊዜ የሊቪኒ ተራ ነበር ለመቀላቀል ፈቃደኛ አለመሆን፣የሰላም ሂደቱን እንዴት ማስቀጠል እንደሚቻል ላይ ያለው የሃሳብ ልዩነት ማደናቀፉ ነው። ኔታንያሁ ትንንሾቹን ተቀናቃኝ በኤሁድ ባራክ የሚመራውን የሌበር ፓርቲ መንግስቱን እንዲቀላቀል በማማለል የተወሰነ መጠን ያለው የመሃል ቃና ሰጠው። ኔታንያሁ ካቢኔያቸውን ለኪነሴት አቅርበው መጋቢት 31 ቀን 2009 ዓ.ም. 32ኛው መንግስት በእለቱ በ69 ህግ አውጭዎች በአብላጫ ድምፅ 45 (በአምስት ድምፅ ተአቅቦ) ጸድቆ አባላቱ ቃለ መሃላ ፈፅመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር : አውሮፓዊ ሁለተኛ ቃል እ.ኤ.አ. በ 2009 የዩኤስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሂላሪ ክሊንተን የፍልስጤም መንግስት መመስረትን እንደሚደግፉ ገልጸዋል - ይህ መፍትሄ በጠቅላይ ሚኒስትር በተመረጡት ቤንጃሚን ኔታንያሁ ከዚህ ቀደም የዩናይትድ ስቴትስ ትብብር ለማድረግ ቃል ገብተዋል። የፕሬዚዳንት ኦባማ አስተዳደር ልዩ መልዕክተኛ ጆርጅ ሚቸል ሲደርሱ ኔታንያሁ ከፍልስጤማውያን ጋር የሚደረጉ ማናቸውም ተጨማሪ ድርድር ፍልስጤማውያን እስራኤልን እንደ አይሁዳዊት ሃገር እውቅና እንዲሰጡ ቅድመ ሁኔታ ነው ብለዋል። ሰኔ 4 ቀን 2009 ኦባማ ለሙስሊሙ ዓለም ንግግር ባደረጉበት የፕሬዚዳንት ኦባማ የካይሮ ንግግር ኦባማ ከሌሎች ነገሮች መካከል፣ “ዩናይትድ ስቴትስ ቀጣይ የእስራኤል ሰፈራ ህጋዊነትን አትቀበልም” ብለዋል። የኦባማን የካይሮ ንግግር ተከትሎ ኔታንያሁ ወዲያውኑ ልዩ የመንግስት ስብሰባ ጠራ። እ.ኤ.አ ሰኔ 14፣ የኦባማ የካይሮ ንግግር ከአስር ቀናት በኋላ፣ ኔታንያሁ በባር-ኢላን ዩኒቨርሲቲ ንግግር ያደረጉት “ከወታደራዊ ነፃ የሆነ የፍልስጤም መንግስት”ን የደገፈ ቢሆንም እየሩሳሌም የተዋሃደች የእስራኤል ዋና ከተማ ሆና መቀጠል አለባት። ኔታንያሁ እየሩሳሌም የእስራኤል የተባበሩት መንግስታት ዋና ከተማ ሆና ከቀጠለች ፍልስጤማውያን ጦር እንደሌላቸው እና ፍልስጤማውያን የመመለስ ጥያቄያቸውን እንደሚተዉ የፍልስጤምን መንግስት እንደሚቀበሉ አስታውቀዋል። በተጨማሪም በዌስት ባንክ ውስጥ ባሉ የአይሁድ ሰፈሮች ውስጥ "የተፈጥሮ እድገት" የማግኘት መብት እንዳላቸው ተከራክረዋል ቋሚ ደረጃቸው ለተጨማሪ ድርድር ነው. የፍልስጤም ከፍተኛ ባለስልጣን ሴሬብ ኤሬክት ንግግሩ "የቋሚነት ድርድርን በር ዘግቷል" ያሉት ኔታንያሁ በእየሩሳሌም ፣ ስደተኞች እና ሰፈራዎች ላይ ባወጡት መግለጫ ምክንያት ነው። የስልጣን ዘመናቸውን ከጀመሩ ከሶስት ወራት በኋላ ኔታንያሁ የካቢኔያቸው በርካታ ጉልህ ስኬቶችን ማስመዝገቡን ለምሳሌ የሚሰራ የብሄራዊ አንድነት መንግስት መመስረት እና “የሁለት መንግስታት መፍትሄ” ላይ ሰፊ መግባባት ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል። እ.ኤ.አ. በጁላይ 2009 በሃሬትዝ የተደረገ ጥናት እንደሚያመለክተው አብዛኞቹ እስራኤላውያን የኔታኒያሁ መንግስትን ይደግፋሉ፣ ይህም የግል ይሁንታ 49 በመቶ ያህል ሰጠው። ኔታንያሁ የመንቀሳቀስ ነፃነትን እና ወደ ሀገር ውስጥ የማስገባት ፍሰት እንዲኖር ለማድረግ በዌስት ባንክ ውስጥ የፍተሻ ኬላዎችን አንስቷል; በዌስት ባንክ ውስጥ የኢኮኖሚ እድገት ያስከተለ እርምጃ. እ.ኤ.አ. በ 2009 ኔታንያሁ የአረብ ሰላም ተነሳሽነትን (“የሳውዲ የሰላም ተነሳሽነት” በመባልም ይታወቃል) እና ከእስራኤል ጋር ያለውን ግንኙነት መደበኛ ለማድረግ የባህሬን ልዑል ሳልማን ቢን ሃማድ ቢን ኢሳ አል ካሊፋ ያደረጉትን ጥሪ አወድሰዋል። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 2009 የፍልስጤም አስተዳደር ሊቀ መንበር ማህሙድ አባስ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ጋር ለመገናኘት ፈቃደኛ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ድርድር ኔታንያሁ በእነዚህ ግንዛቤዎች ላይ ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደሚገኝ ተዘግቧል፣ እነዚህም ቀደም ሲል በዌስት ባንክ የተፈቀደውን ግንባታ በመቀጠል ሁሉንም ሰፈሮች ለማቀዝቀዝ እና በምስራቅ እየሩሳሌም ግንባታን ለመቀጠል በፍቃድ ላይ ስምምነትን እንደሚያካትቱ ተዘግቧል። በተመሳሳይ ጊዜ እዚያ የአረብ ነዋሪዎችን ቤቶች መፍረስ ማቆም. በሴፕቴምበር 4 ቀን 2009 ኔታንያሁ ተጨማሪ የሰፈራ ግንባታዎችን ለማጽደቅ ሰፋሪዎች ለሚያቀርቡት የፖለቲካ ጥያቄ መስማማት እንዳለበት ተዘግቧል። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ሮበርት ጊብስ በተወሰደው እርምጃ “ተጸጸተ” ብለዋል፤ ሆኖም አንድ የዩኤስ ባለስልጣን እርምጃው “ባቡሩን አያደናቅፍም” ብለዋል። ሴፕቴምበር 7 ቀን 2009 ኔታንያሁ ወዴት እንደሚያመሩ ሳይዘግቡ ከቢሮአቸው ወጡ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወታደራዊ ጸሃፊ ሜጀር ጄኔራል ሜየር ካሊፊ ኔታንያሁ በእስራኤል የሚገኘውን የጸጥታ ተቋም ጎብኝተዋል ሲሉ ዘግበዋል። የተለያዩ የዜና ወኪሎች የት እንዳሉ የተለያዩ ታሪኮችን ዘግበዋል። እ.ኤ.አ. ሴፕቴምበር 9 ቀን 2009 ዬዲዮት አህሮኖት እንደዘገበው የእስራኤሉ መሪ የኤስ-300 ፀረ-አውሮፕላን ሚሳኤል ስርዓቶችን ለኢራን እንዳይሸጥ የሩሲያ ባለስልጣናትን ለማሳመን ወደ ሞስኮ ሚስጥራዊ በረራ አድርጓል። ርዕሰ ዜናዎች ኔታንያሁ “ውሸታም” በማለት ጉዳዩን “ፊያስኮ” ብለውታል። በኋላም በጉዳዩ ምክንያት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወታደራዊ ጸሃፊ ከስራ ሊሰናበቱ እንደሚችሉ ተነግሯል። ሰንበት ታይምስ እንደዘገበው ጉዞው የተደረገው የኢራንን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ መርሃ ግብር እስራኤል ናቸው ብላ የምታምንባቸውን የሩሲያ ሳይንቲስቶች ስም ለመጋራት ነው። እ.ኤ.አ ሴፕቴምበር 24 ቀን 2009 በኒውዮርክ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባደረጉት ንግግር ኢራን ለአለም ሰላም ስጋት መሆኗን እና እስላማዊ ሪፐብሊክ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳታገኝ መከላከል የአለም አካል አለበት ብለዋል። ለአውሽዊትዝ የወጣውን ንድፍ በማውለብለብ እና በናዚዎች የተገደሉትን የገዛ ቤተሰቦቻቸውን መታሰቢያ በመጥራት ኔታንያሁ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ ስለ እልቂት እልቂት ጥያቄ ሲያቀርቡ "አታፍሩም?" በኖቬምበር 25 ቀን 2009 ኔታንያሁ ከፊል 10 ወር የሚፈጀውን የሰፈራ ግንባታ የማቆም እቅድ አውጀዋል ። የታወጀው ከፊል ቅዝቃዜ በእውነተኛ የሰፈራ ግንባታ ላይ ምንም አይነት ለውጥ አላመጣም ሲል በዋናው የእስራኤል ዕለታዊ ዕለታዊ ሃሬትዝ ትንታኔ። የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ መልዕክተኛ ጆርጅ ሚቼል እንዳሉት "ዩናይትድ ስቴትስ የእስራኤልን የእጅ ምልክት ውስንነት በተመለከተ የአረቦችን ስጋት ብታጋራም የእስራኤል መንግስት እስካሁን ካደረገው በላይ ነው" ብለዋል። ኔታንያሁ በሰጡት መግለጫ እርምጃውን “የሰላሙን ሂደት የሚያበረታታ አሳማሚ እርምጃ ነው” በማለት ፍልስጤማውያን ምላሽ እንዲሰጡ አሳስበዋል። ፍልስጤማውያን በቅርቡ በዌስት ባንክ በሺዎች የሚቆጠሩ የሰፈራ ህንጻዎች መገንባታቸውን እና በምስራቅ እየሩሳሌም ምንም አይነት የሰፈራ እንቅስቃሴ እንደማይኖር በመግለጽ ምልክቱ “ቀላል አይደለም” በማለት ጥሪውን ውድቅ አድርገዋል። እ.ኤ.አ. በመጋቢት 2010 የእስራኤል መንግስት በሰሜን ምስራቅ እየሩሳሌም ራማት ሽሎሞ ተብሎ በሚጠራው ትልቅ የአይሁዶች የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ላይ ተጨማሪ 1,600 አፓርትመንቶች እንዲገነቡ አፅድቋል። የእስራኤል መንግስት ይህን ያስታወቀው የዩኤስ ምክትል ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና የአሜሪካ መንግስት በጎበኙበት ወቅት ነው እቅዱን በጠንካራ ቃል አውግዘዋል። ኔታንያሁ በመቀጠል ሁሉም የቀድሞ የእስራኤል መንግስታት በአካባቢው እንዲገነቡ እንደፈቀዱ እና እንደ ራማት ሽሎሞ እና ጊሎ ያሉ አንዳንድ ሰፈሮች እስከ ዛሬ ድረስ በሁለቱም ወገኖች በቀረበው የመጨረሻ የስምምነት እቅድ ውስጥ ሁልጊዜ እንደ እስራኤል አካል ይካተታሉ ሲል መግለጫ አውጥቷል። . ኔታንያሁ ይህ ማስታወቂያ በወጣበት ወቅት ተጸጽቷል ነገር ግን "በኢየሩሳሌም ላይ ያለን ፖሊሲ ለ42 አመታት የእስራኤል መንግስታት ሲከተሉት የነበረው ፖሊሲ ተመሳሳይ ነው እና ምንም ለውጥ አላመጣም" ብለዋል። በሴፕቴምበር 2010 ኔታንያሁ በኦባማ አስተዳደር ሸምጋይነት ከፍልስጤማውያን ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ከረጅም ጊዜ በኋላ ቀጥታ ውይይት ለማድረግ ተስማሙ። የእነዚህ ቀጥተኛ ንግግሮች የመጨረሻ አላማ ለአይሁዶች እና ለፍልስጤም ህዝቦች የሁለት ሀገር መፍትሄ በማቋቋም ለእስራኤል እና ፍልስጤም ግጭት ይፋዊ የሆነ "የመጨረሻ ደረጃ እልባት" ማዕቀፍ መፍጠር ነው። በሴፕቴምበር 27፣ የ10-ወር ሰፈራው መረጋጋት አብቅቷል፣ እና የእስራኤል መንግስት ምስራቅ እየሩሳሌምን ጨምሮ በምእራብ ባንክ አዲስ ግንባታን አፀደቀ። እ.ኤ.አ. በጁላይ 2011 ከቢሮ በጡረታ ሲወጡ የቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስትር ሮበርት ጌትስ ኔታንያሁ ለዩናይትድ ስቴትስ ምስጋና ቢስ እንደሆኑ እና እስራኤልን አደጋ ላይ ይጥላሉ ብለዋል። ምላሽ የሰጡት የሊኩድ ፓርቲ ናታንያሁ አብዛኛው እስራኤላውያን ጠቅላይ ሚኒስትሩን እንደሚደግፉ እና በዩናይትድ ስቴትስ ሰፊ ድጋፍ እንዳላቸው በመግለጽ ተሟግቷል። እ.ኤ.አ. በ1987 ሚስጥራዊ የአሜሪካ ሰነዶችን ለእስራኤል በማውጣቱ የእድሜ ልክ እስራት የሚቀጣው አሜሪካዊው ጆናታን ፖላርድ እንዲፈታ ኔታንያሁ ሳይሳካለት ቀርቷል። በ1998 በዋይ ወንዝ ስብሰባ ላይ ጉዳዩን አንስተው የዩኤስ ፕሬዝዳንት ቢል ክሊንተንን በግሉ አድርገው ነበር በማለት ተናግሯል። ፖላርድን ለመልቀቅ ተስማማ። በ2002 ኔታንያሁ ፖላርድን በሰሜን ካሮላይና እስር ቤት ጎበኘ። የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ከፖላርድ ሚስት ጋር ግንኙነት ነበራቸው፣ እና የኦባማ አስተዳደር ፖላርድን እንዲፈታ ግፊት በማድረግ ላይ ነበሩ። እ.ኤ.አ. በ2011፣ በመላው እስራኤል የማህበራዊ ፍትህ ተቃውሞዎች ተቀሰቀሱ። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በመላው ሀገሪቱ የእስራኤልን የኑሮ ውድነት ተቃውመዋል። በምላሹ ኔታንያሁ ችግሮቹን መርምሮ የመፍትሄ ሃሳቦችን እንዲያቀርብ በፕሮፌሰር ማኑኤል ትራጅተንበርግ የሚመራውን ኮሚቴ ሾመ። ኮሚቴው በሴፕቴምበር 2011 ከፍተኛውን የኑሮ ውድነት ለመቀነስ የውሳኔ ሃሳቦችን አቅርቧል። ኔታንያሁ የቀረቡትን ማሻሻያዎች በካቢኔ በኩል በአንድ ጊዜ ለመግፋት ቃል ቢገቡም ፣በጥምረቱ ውስጥ ያሉ ልዩነቶች ማሻሻያዎቹ ቀስ በቀስ እንዲፀድቁ አድርጓል ። የናታንያሁ ካቢኔ በመላ ሀገሪቱ የፋይበር ኦፕቲክ ኬብል ኔትወርክን የመገንባት እቅድ አጽድቆ ርካሽ እና ፈጣን የፋይበር ኦፕቲክ የኢንተርኔት አገልግሎት በእያንዳንዱ ቤት እንዲደርስ አድርጓል። እ.ኤ.አ. በ 2012 ኔታንያሁ መጀመሪያ ላይ ቀደምት ምርጫዎችን ለመጥራት አቅዶ ነበር ፣ ነገር ግን እ.ኤ.አ. በ 2013 ብሔራዊ ምርጫ እስኪደረግ ድረስ እስራኤልን ለማየት አወዛጋቢ የብሔራዊ አንድነት መንግስት መፈጠሩን ተቆጣጠረ ። በግንቦት 2012 ኔታንያሁ ለፍልስጤማውያን መብት ለመጀመሪያ ጊዜ እውቅና ሰጥተዋል ። በይፋዊ ሰነድ ውስጥ የራሳቸው ግዛት አላቸው ፣ ለማህሙድ አባስ የፃፉት ደብዳቤ ፣ ምንም እንኳን ቀደም ሲል እንደገለፀው ከወታደራዊ ነፃ መሆን አለበት ። እ.ኤ.አ. ኦክቶበር 25 ቀን 2012 ኔታንያሁ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቪግዶር ሊበርማን የፖለቲካ ፓርቲያቸው ሊኩድ እና እስራኤል ቤይቴኑ ተዋህደው በአንድ ድምፅ በእስራኤል ጥር 22 ቀን 2013 አጠቃላይ ምርጫ እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል። ሦስተኛው ጊዜ እ.ኤ.አ. በ 2013 በተካሄደው ምርጫ የናታንያሁ ሊኩድ ባይተይኑ ጥምረት የሊኩድ እና የእስራኤል ቤይቴኑ ፓርቲዎች ጥምር ድምፅ ከነበራቸው በ11 ጥቂት መቀመጫዎች ተመልሷል። ቢሆንም፣ በኬኔሴት ውስጥ ትልቁ አንጃ ሆኖ የቀረው፣ የእስራኤል ፕሬዚዳንት ሺሞን ፔሬዝ ኔታንያሁ የእስራኤል ሠላሳ ሦስተኛውን መንግሥት የመመሥረት ኃላፊነት ከሰሱት። አዲሱ ጥምረት ዬሽ አቲድ፣ የአይሁድ ቤት እና የሐትኑዋ ፓርቲዎችን ያካተተ ሲሆን በዬሽ አቲድ እና ​​በአይሁድ ቤት አፅንኦት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ፓርቲዎችን አግልሏል። ኔታንያሁ በሦስተኛ ጊዜ የሥልጣን ዘመን፣ የኤኮኖሚ ሊበራላይዜሽን ፖሊሲያቸውን ቀጥለዋል። እ.ኤ.አ. በታህሳስ 2013 የእስራኤልን በጣም የተከማቸ ኢኮኖሚ የሸማቾችን ዋጋ ዝቅ ለማድረግ፣ የገቢ አለመመጣጠንን ለመቀነስ እና የኢኮኖሚ እድገትን ለመጨመር የሚያቅድ የንግድ ማጎሪያ ህግን አጽድቋል። ኔታንያሁ የማጎሪያ ኮሚቴውን እ.ኤ.አ. በ2010 ያቋቋመ ሲሆን በመንግስታቸው የተገፋው ረቂቅ ህግ ምክሮቹን ተግባራዊ አድርጓል። አዲሱ ህግ የባለብዙ ደረጃ ኮርፖሬት ይዞታ መዋቅሮችን ያገደ ሲሆን በዚህ ውስጥ የዋና ስራ አስፈፃሚ ቤተሰቦች ወይም ሌሎች ተዛማጅነት ያላቸው ግለሰቦች የህዝብ ኩባንያዎችን በመያዝ ሌሎች የመንግስት ኩባንያዎችን ይዘዋል እና በዚህም የዋጋ ንረት ላይ መሰማራት ችለዋል። በህጉ መሰረት ኮርፖሬሽኖች ከሁለት እርከኖች በላይ በይፋ የተዘረዘሩ ኩባንያዎችን እንዳይይዙ እና የገንዘብ እና የገንዘብ ያልሆኑ ድርጅቶችን እንዳይይዙ ታግደዋል. ሁሉም ኮንግሎሜቶች ትርፍ ይዞታዎችን ለመሸጥ ከአራት እስከ ስድስት ዓመታት ተሰጥቷቸዋል. ኔታንያሁ የሸማቾችን ዋጋ ዝቅ ለማድረግ እና የወጪ ንግድን ለመጨመር በእስራኤል ወደብ ባለስልጣን ሰራተኞች በሞኖፖል የተያዘ ነው ብለው የሚያዩትን ወደብ የፕራይቬታይዜሽን ዘመቻ ጀመሩ። በጁላይ 2013 በሃይፋ እና አሽዶድ ውስጥ የግል ወደቦችን ለመገንባት ጨረታ አውጥቷል ። ኔታንያሁ በኢንዱስትሪው ላይ ያለውን ጫና ለማቃለል ከመጠን ያለፈ ቢሮክራሲ እና ደንቦችን ለመግታት ቃል ገብተዋል።እ.ኤ.አ ኤፕሪል 2014 እና እንደገና በሰኔ ወር ኔታንያሁ ሃማስ እና የፍልስጤም አስተዳደር ተስማምተው የአንድነት መንግስት ሲመሰርቱ ያደረባቸውን ጥልቅ ስጋት ተናግረው እና የዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ መንግስታት ከፍልስጤም ጥምር መንግስት ጋር ለመስራት ያደረጉትን ውሳኔ ሁለቱንም ክፉኛ ተችተዋል። . እ.ኤ.አ ሰኔ 2014 ላይ ለሶስት እስራኤላውያን ታዳጊዎች አፈና እና ግድያ ሃማስን ተጠያቂ አድርጓል፣ እና በዌስት ባንክ ከፍተኛ ፍተሻ እና ማሰር በተለይም የሃማስ አባላትን ኢላማ አድርጓል እና በሚቀጥሉት ሳምንታት በጋዛ 60 ኢላማዎች ላይ ደርሷል። በ30 ሰኔ 2014 መንግስት ለመጠርጠር በቂ ምክንያት ስላላቸው የተገደሉት የታዳጊዎቹ አስከሬን ከተገኘ በኋላ በጋዛ ታጣቂዎች እና በመከላከያ ሰራዊት መካከል የሚሳኤል እና የሮኬት ልውውጥ ተባብሷል።በርካታ የሃማስ አባላት ከተገደሉ በኋላ ወይ በፍንዳታ ወይም በእስራኤል የቦምብ ጥቃት፣ ሃማስ ከጋዛ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል እንደሚመታ በይፋ አስታውቋል፣ እና እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ኦፕሬሽን መከላከያ ጠርዝን ጀምሯል፣ ይህም የኖቬምበር 2012 የተኩስ አቁም ስምምነትን በመደበኛነት አብቅቷል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በአሜሪካ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞችን ሰርተው ሃማስን የዘር ማጥፋት ወንጀል አሸባሪ ሲሉ ሲኤንኤን በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልፀዋል። በቀዶ ጥገናው በጋዛ ላይ የደረሰው ጉዳት ለሶስተኛ ጊዜ ኢንቲፋዳ ሊፈጥር ይችላል ወይ ተብሎ ሲጠየቅ ኔታንያሁ ሃማስ ወደዚያ ግብ እየሰራ መሆኑን መለሱ። እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2014 የኔታንያሁ መንግስት በመንግስት ኩባንያዎች ውስጥ ያለውን ሙስና እና ፖለቲካን ለመቀነስ እና የእስራኤልን የካፒታል ገበያ ለማጠናከር የሚያስችል የፕራይቬታይዜሽን እቅድ አጽድቋል። በእቅዱ መሰረት በመንግስት ባለቤትነት ስር ባሉ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ 49% የሚደርሱ አናሳዎች, የጦር መሳሪያ አምራቾች, ኢነርጂ, ፖስታ, ውሃ እና የባቡር ኩባንያዎች እንዲሁም የሃይፋ እና አሽዶድ ወደቦች ይገኙበታል. በዚያው ወር ኔታንያሁ በሰፈራ ላይ የሚሰነዘረውን ትችት “ከአሜሪካን እሴት ጋር የሚቃረን” ሲሉ የገለፁት ይህ አስተያየት ከዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬታሪ ጆሽ ኢርነስት የሰላ ተግሣጽ እንዳስገኘላቸው የአሜሪካ እሴቶች እስራኤል የማያቋርጥ የገንዘብ ድጋፍ ብቻ ሳይሆን የመከላከያ ቴክኖሎጂ እንድታገኝ እንዳደረገው ጠቁመዋል። እንደ ብረት ዶሜ. ኔታንያሁ አይሁዶች በሚኖሩበት ቦታ ላይ ገደቦችን እንደማይቀበል ገልፀው የኢየሩሳሌም አረቦች እና አይሁዶች በፈለጉት ቦታ ቤት መግዛት አለባቸው ብለዋል ። የአሜሪካው ውግዘት እንዳስገረመኝ ተናግሯል። "ይህ ከአሜሪካን እሴት ጋር የሚጋጭ ነው። ለሰላምም ጥሩ ውጤት አያመጣም። ይህን የዘር ማጥራት ለሰላም ቅድመ ሁኔታ እናደርጋለን የሚለው ሀሳብ ፀረ ሰላም ይመስለኛል።" ብዙም ሳይቆይ የአትላንቲክ ባልደረባው ጄፍሪ ጎልድበርግ በኔታንያሁ እና በዋይት ሀውስ መካከል ያለው ግንኙነት አዲስ ደረጃ ላይ መድረሱን የዘገበው የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር በእስራኤል የሰፈራ ፖሊሲ የተናደደ ሲሆን ኔታንያሁ ደግሞ የአሜሪካ አስተዳደር በመካከለኛው ምስራቅ ላይ ያለውን ንቀት ገልጸዋል። እ.ኤ.አ. ዲሴምበር 2 2014 ኔታንያሁ ሁለቱን ሚኒስትሮቻቸውን የፋይናንስ ሚኒስትሩ ያየር ላፒድን የመሃል ተቃዋሚውን የየሽ አቲድ ፓርቲ እና የፍትህ ሚኒስትር ቲዚፒ ሊቪኒን ሃትኑዋን ይመራሉ። ለውጦቹ መንግስት እንዲበተን ምክንያት ሆኗል፣ እ.ኤ.አ. ማርች 17 ቀን 2015 አዲስ ምርጫዎች ይጠበቃሉ። በጥር 2015 ኔታንያሁ በአሜሪካ ኮንግረስ ንግግር እንዲያደርጉ ተጋብዘው ነበር። ይህ ንግግር ኔታንያሁ ለኮንግረስ የጋራ ስብሰባ ያደረጉት ሶስተኛው ንግግር ነው። ታይም በኮንግሬስ ንግግር እንደሚያደርጉ ከማስታወቁ አንድ ቀን ቀደም ብሎ እንደዘገበው የዩኤስ የህግ ባለሙያዎች እና የሞሳድ መሪ ታሚር ፓርዶ በኢራን ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዳይጥሉ ለማስጠንቀቅ በማሰብ ያደረጉትን ስብሰባ ለማደናቀፍ ሞክሯል ይህ እርምጃ የኒውክሌር ድርድርን ሊያደናቅፍ ይችላል። ወደ ንግግሩ መሪነት እ.ኤ.አ. በማርች 3 2015 በዩናይትድ ስቴትስ የሚገኙ የእስራኤል ቆንስላ ጄኔራል “ከአሜሪካ የአይሁድ ማህበረሰቦች እና የእስራኤል አጋሮች ከባድ አሉታዊ ምላሽ ይጠብቃሉ። ተቃውሞዎች ከኦባማ አስተዳደር ድጋፍ እና ተሳትፎ ውጭ የንግግሩን ዝግጅት እና የእስራኤል መጋቢት 17 2015 ምርጫ ከመደረጉ በፊት የንግግሩን ጊዜ ያካትታል። ሰባት የአሜሪካ የአይሁድ ህግ አውጭዎች በአሜሪካ የእስራኤል አምባሳደር ሮን ዴርመርን አግኝተው ኔታንያሁ ከህግ አውጭዎች ጋር በግል እንዲገናኙ ምክረ ሃሳብ አቅርበዋል። ኔታንያሁ ንግግሩን ሲያደርጉ በዓለም ዙሪያ ያሉትን ሁሉንም አይሁዶች እንደሚናገሩ ተናግሯል ፣ይህ የይገባኛል ጥያቄ በሌሎች የአይሁድ ማህበረሰብ ውስጥ አከራካሪ ነው። የአይሁድ ቮይስ ፎር ፒስ ዋና ዳይሬክተር ሬቤካ ቪልኮመርሰን እንዳሉት “አሜሪካውያን አይሁዶች ኔታንያሁ ወይም ሌላ ማንኛውም የእስራኤል ፖለቲከኛ - እኛ ያልመረጥነው እና ለመወከል ያልመረጥነው - እናገራለሁ በሚለው አስተሳሰብ በጣም ተደናግጠዋል። እኛ" እ.ኤ.አ. በ2015 በእስራኤል ምርጫ የቅርብ ውድድር ነው ተብሎ በሚታሰበው የምርጫ ቀን የምርጫው ቀን ሲቃረብ ኔታንያሁ የፍልስጤም ግዛት በስልጣን ዘመናቸው አይመሰረትም ወይ ብለው ሲጠየቁ 'በእርግጥ' ሲሉ መለሱ። የፍልስጤም መንግስት መደገፍ አክራሪ እስላማዊ አሸባሪዎች በእስራኤል ላይ ጥቃት እንዲሰነዝሩበት ቦታ ከመስጠት ጋር እኩል እንደሆነ ተናግረዋል ። ይሁን እንጂ ኔታንያሁ በድጋሚ "የአንድ ሀገር መፍትሄ አልፈልግም። ሰላማዊና ዘላቂ የሁለት ሀገር መፍትሄ እፈልጋለሁ። ፖሊሲዬን አልቀየርኩም" አራተኛው ጊዜ እ.ኤ.አ. በ 2015 ምርጫ ኔታንያሁ ከፓርቲያቸው ሊኩድ ጋር በመሆን ምርጫውን 30 ስልጣን በመምራት የተመለሱ ሲሆን ይህም ለክኔሴት ከፍተኛው መቀመጫ አድርጎታል። ፕሬዝዳንት ሪቪሊን በመጀመሪያዎቹ አራት ሳምንታት ድርድሮች ውስጥ ሳይጠናቀቅ ሲቀር ጥምረት ለመፍጠር ለኔታንያሁ እስከ ሜይ 6 2015 እንዲራዘም ፈቀዱ። በግንቦት 6 ቀን እኩለ ሌሊት ላይ በሁለት ሰዓታት ውስጥ ጥምር መንግስት መሰረተ። የሱ ሊኩድ ፓርቲ ከአይሁድ ሆም፣ ዩናይትድ ቶራ አይሁዲዝም፣ ኩላኑ እና ሻስ ጋር ጥምረት መሰረተ። እ.ኤ.አ. ሜይ 28 ቀን 2015 ኔታንያሁ በሚቀጥለው አጠቃላይ ምርጫ ከዚህ ቀደም ታይቶ ለማያውቅ አምስተኛ የስልጣን ዘመን ለጠቅላይ ሚኒስትርነት እንደሚወዳደሩ እና የሊኩድ የ እጩዎችን የመምረጥ ሂደት እንደሚደግፉ አስታውቀዋል። እ.ኤ.አ. በነሀሴ 2015 የኔታኒያሁ መንግስት የግብርና ማሻሻያ እና የምግብ ዋጋን ለመቀነስ ከውጪ የሚገቡትን ቀረጥ ለመቀነስ፣የመኖሪያ ቤት ወጪን ለመቀነስ እና የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን ለማፋጠን እና በፋይናንሱ ዘርፍ ማሻሻያ ለማድረግ የሚያስችል የሁለት አመት በጀት አጽድቋል። ውድድርን ለመጨመር እና ለፋይናንስ አገልግሎቶች ክፍያዎችን ለመቀነስ. በመጨረሻም መንግስት አንዳንድ ቁልፍ የግብርና ማሻሻያዎችን በማስወገድ ለመደራደር ተገዷል። እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2015 ኔታንያሁ የኢየሩሳሌም ታላቅ ሙፍቲ ሀጅ አሚን አል-ሁሴኒ ለሁለተኛው የአለም ጦርነት ቀደም ባሉት ወራት ለአዶልፍ ሂትለር የጅምላ ጭፍጨፋ ሀሳብ ሰጡ በማለታቸው የናዚ መሪ አይሁዶችን ከማጥፋት ይልቅ እንዲያጠፋ በማሳመን ሰፊ ትችት ሰንዝሯል። ብቻ ከአውሮፓ አስወጣቸው። ይህ ሃሳብ በዋና ዋና የታሪክ ተመራማሪዎች ውድቅ የተደረገ ሲሆን አል-ሁሴኒ ከሂትለር ጋር የተደረገው ስብሰባ የተካሄደው የአይሁዶች የጅምላ ግድያ ከተጀመረ ከአምስት ወራት ገደማ በኋላ ነው። የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል የኔታንያሁ የይገባኛል ጥያቄ እንደማይቀበሉት ገልፀው በናዚ ዘመን የሀገራቸውን ወንጀሎች መቀበላቸውን ደግመዋል። ኔታንያሁ በኋላም “ዓላማቸው ሂትለርን ከተሸከመው ኃላፊነት ነፃ ማውጣት ሳይሆን በወቅቱ የፍልስጤም አባት ያለ ሀገር እና ከ‘ወረራ’ በፊት፣ ያለግዛቶች እና ሰፈራዎች መሆናቸውን ለማሳየት ነበር” ሲሉ አብራርተዋል። በአይሁዶች ላይ በስርዓታዊ ቅስቀሳ እንኳን ተመኙ። አንዳንድ በጣም ጠንካራ ትችት ከእስራኤል ምሁራን የመጡ ናቸው፡ ዩሁዳ ባወር የኔታኒያሁ የይገባኛል ጥያቄ “ፍፁም ደደብ ነው” ሲል ሞሼ ዚመርማን ግን “ከሂትለር ሸክሙን ወደሌሎች ለማሸጋገር የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ የሆሎኮስት ክህደት ነው” ሲል ተናግሯል። እ.ኤ.አ. በማርች 2016 የናታንያሁ ጥምረት በዌስተርን ዎል ላይ የኦርቶዶክስ ያልሆኑ የጸሎት ቦታዎችን ለመፍጠር መንግስት በወሰዳቸው እርምጃዎች እራሳቸውን ለቀው እንደሚወጡ በመዝታታቸው የናታንያሁ ጥምረት ከፍተኛ ቀውስ ገጥሞታል። መንግስት ለኮንሰርቫቲቭ እና ሪፎርም አይሁዲዝም ሌላ ይፋዊ የመንግስት እውቅና ከሰጠ ከጥምረቱ እንደሚወጡ አስታውቀዋል። እ.ኤ.አ. በታህሳስ 23 ቀን 2016 ዩናይትድ ስቴትስ በኦባማ አስተዳደር ከተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ 2334 ተአቅቦ እንዲወጣ ውጤታማ በሆነ መንገድ ፈቅዳለች። እ.ኤ.አ. በታህሳስ 28 የዩኤስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ እስራኤልን እና የሰፈራ ፖሊሲዎችን በንግግራቸው አጥብቀው ወቅሰዋል። ኔታንያሁ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ውሳኔ እና የኬሪ ንግግር ምላሽ በፅኑ ነቅፈዋል። እ.ኤ.አ. ጥር 6 ቀን 2017 የእስራኤል መንግስት ከድርጅቱ የሚያወጣውን አመታዊ መዋጮ በድምሩ 6 ሚሊዮን ዶላር በዩናይትድ ስቴትስ ዶላር ተወ። እ.ኤ.አ. ከባለቤቱ ሳራ ጋር አብሮ ነበር። የሶስት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት የቢዝነስ ተወካዮችን ያካተተ ሲሆን ኔታንያሁ እና የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ማልኮም ተርንቡል በርካታ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ሊፈራረሙ ነበር። በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ቤርሳቤህን ነፃ ያወጡት የአውስትራሊያ ቀላል ሆርስ ጦር ሰራዊት መሆናቸውን ያስታወሱት ኔታንያሁ ይህ በአገሮቹ መካከል የ100 ዓመታት ግንኙነት የጀመረው። እ.ኤ.አ. ኦክቶበር 12 2017 ዩናይትድ ስቴትስ ተመሳሳይ እርምጃ መውሰዷን ካወጀች በኋላ የናታንያሁ መንግስት በኤጀንሲው ጸረ እስራኤል ርምጃ እንደሆነ ባየው ምክንያት ከዩኔስኮ መውጣቱን አስታውቆ ውሳኔውን በታህሳስ 2017 ይፋ አድርጓል። የእስራኤል መንግስት በይፋ እ.ኤ.አ. በታህሳስ ወር 2017 መገባደጃ ላይ ለዩኔስኮ መልቀቂያውን አሳውቋል። በ 30 ኤፕሪል 2018 ኔታንያሁ ኢራን የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር መጠን የሚገልጹ ከ100,000 በላይ ሰነዶችን ካሼ ካቀረበች በኋላ የኢራንን የኒውክሌር ስምምነት እንዳላቆመች ከሰሷት። ኢራን የኔታንያሁ ንግግር “ፕሮፓጋንዳ” ብላ ወቅሳለች። ኔታንያሁ የ2018 የሰሜን ኮሪያ-ዩናይትድ ስቴትስን ስብሰባ አወድሰዋል። በመግለጫውም "የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን በሲንጋፖር ታሪካዊ ጉባኤ ላይ አመሰግነዋለሁ። ይህ የኮሪያ ልሳነ ምድርን ከኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለማጽዳት ለሚደረገው ጥረት ጠቃሚ እርምጃ ነው" ብለዋል። እ.ኤ.አ. ጁላይ 19 2018 ክኔሴት በኔታንያሁ ጥምር መንግስት የተደገፈ መሰረታዊ ህግ የሆነውን የብሄር-ግዛት ህግን አፀደቀ። ተንታኞች ህጉ የኔታኒያሁ ጥምረት የቀኝ ክንፍ አጀንዳን እንደሚያራምድ ምልክት አድርገው ይመለከቱት ነበር። ከኤፕሪል 2019 የእስራኤል ህግ አውጪ ምርጫ በፊት፣ ኔታንያሁ የቀኝ ክንፍ ፓርቲዎች ህብረትን ለመመስረት የአይሁድ ሆም ፓርቲን ከቀኝ አክራሪው ኦትማ ይሁዲት ፓርቲ ጋር አንድ የሚያደርግ ስምምነትን ረድተዋል። የስምምነቱ አነሳሽነት ለትናንሽ ፓርቲዎች የምርጫ ገደብን ለማሸነፍ ነበር. ስምምነቱ በመገናኛ ብዙኃን ተችቷል፣ ምክንያቱም ኦትስማ በሰፊው በዘረኝነት የሚታወቅ እና መነሻውን ከአክራሪ ካሃኒስት እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ ነው። የወንጀል ምርመራ እና ክስ ከጃንዋሪ 2017 ጀምሮ ኔታንያሁ በእስራኤል ፖሊስ በሁለት ጉዳዮች "ክስ 1000" እና "ጉዳይ 2000" ሲመረመሩ እና ሲጠየቁ ቆይቷል። ሁለቱ ጉዳዮች ተያይዘዋል. በክስ 1000 ኔታንያሁ ጄምስ ፓከር እና የሆሊውድ ፕሮዲዩሰር አርኖን ሚልቻንን ጨምሮ ከነጋዴዎች ተገቢ ያልሆነ ሞገስ አግኝተዋል ተብሎ ተጠርጥሯል። ጉዳይ 2000 ከየዲዮት አህሮኖት ጋዜጣ ቡድን አሳታሚ አርኖን ሞዝዝ ጋር የየዲዮት ዋና ተፎካካሪ የሆነውን እስራኤል ሃዮምን ለማዳከም ህግን ለማስተዋወቅ ከየዲዮት አህሮኖት ጋዜጣ ቡድን አሳታሚ ጋር ለመስማማት መሞከሮችን እና ስለ ኔታንያሁ የተሻለ ሽፋን ለመስጠት መሞከሩን ያካትታል። እ.ኤ.አ. ኦገስት 3 2017 የእስራኤል ፖሊስ ኔታንያሁ በ"1000" እና "2000" ጉዳዮች ላይ በማጭበርበር፣ እምነትን በመጣስ እና ጉቦ በፈጸሙ ወንጀሎች መጠርጠራቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ አረጋግጧል። በማግስቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀድሞ የስራ ሃላፊ አሪ ሀሮው በእነዚህ ጉዳዮች ላይ በኔታንያሁ ላይ ለመመስከር ከአቃቤ ህግ ጋር ስምምነት መፈራረማቸው ተሰማ።እ.ኤ.አ. የፖሊስ መግለጫ እንደሚያመለክተው በሁለቱ ክሶች ላይ በጉቦ፣ በማጭበርበር እና እምነትን በመጣስ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመክሰስ በቂ ማስረጃ አለ። ኔታንያሁ ክሱ መሠረተ ቢስ ነው ሲሉ በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል ። እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 25 ቀን 2018 የኢኮኖሚ ወንጀሎች ዲቪዥን ዳይሬክተር በሁለቱም ጉዳዮች ላይ ክስ መመስረቱን ተዘግቧል። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. ኔታንያሁ በህዳር 21 ቀን 2019 በይፋ ተከሷል። ኔታንያሁ ጥፋተኛ ተብሎ ከተፈረደበት እስከ 10 ዓመት የሚደርስ እስራት በጉቦ እና በማጭበርበር እና እምነት በመጣስ ቢበዛ ሶስት አመት ሊቀጣ ይችላል። በእስራኤል ታሪክ በወንጀል የተከሰሱ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ናቸው። እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 23 2019 ኔታንያሁ በ1993 የእስራኤል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባስቀመጠው ህጋዊ ቅድመ ሁኔታ መሰረት ግብርናውን፣ ጤናውን፣ ማህበራዊ ጉዳዮቹን እና የዲያስፖራ ጉዳዮችን ፖርትፎሊዮ እንደሚለቅ ታወቀ። በክስ ሰበብ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣን እንዲለቁ የማስገደዱ ጉዳይ እስካሁን በፍርድ ቤት አልታየም። ጥር 28 ቀን 2020 በይፋ ተከሷል። የናታንያሁ የወንጀል ችሎት በግንቦት 24 ቀን 2020 እንዲጀመር ተቀጥሯል፣ መጀመሪያ ለዛ አመት መጋቢት ተይዞ የነበረ ቢሆንም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ዘግይቷል። አምስተኛው ጊዜ እ.ኤ.አ. ሜይ 17 ቀን 2020 ኔታንያሁ ከቤኒ ጋንትዝ ጋር በመተባበር ለአምስተኛ ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ቃለ መሃላ ፈጸሙ። በእስራኤል በ -19 ወረርሽኝ እና በኔታንያሁ የወንጀል ክስ ዳራ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ መኖሪያ ፊት ለፊት በእርሱ ላይ ሰፊ ሰልፎች ተካሂደዋል። ይህን ተከትሎም ኔታንያሁ የ -19 ልዩ መመሪያዎችን በመጠቀም ሰልፎቹን በ20 ሰዎች በመገደብ እና ከቤታቸው በ1,000 ሜትሮች ርቀት ላይ እንዲበተን አዘዋል። ይሁን እንጂ ትክክለኛው ተቃራኒው ተገኝቷል; ሰልፎቹ ሰፋ አድርገው ከ1,000 በላይ ማዕከላት ተበትነዋል። እ.ኤ.አ. በማርች 2021 እስራኤል በኮቪድ-19 በአለም ላይ በነፍስ ወከፍ ከፍተኛ የተከተቡ ህዝቦች ያላት ሀገር ሆነች። እ.ኤ.አ. ከቀዶ ጥገናው በኋላ የእስራኤል ፖለቲከኛ እና የያሚና ጥምረት መሪ ናታሊ ቤኔት ከተቃዋሚው ያየር ላፒድ መሪ ጋር ናታንያሁ ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታቸው የሚያባርር የሽግግር መንግስት ለመመስረት መስማማታቸውን አስታውቀዋል። በጁን 2 2021 ቤኔት ከላፒድ ጋር የህብረት ስምምነት ተፈራረመ። እ.ኤ.አ. የተቃዋሚዎች መሪ (2021–አሁን)፡ አውሮፓዊ የሁለተኛው ፕሪሚየር ሥልጣናቸው ካበቃ በኋላ ኔታንያሁ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ በመሆን ሦስተኛ ጊዜውን ጀምሯል። ሊኩድ የ ትልቁ ፓርቲ ሆኖ ይቆያል የፖለቲካ አቋም ኢኮኖሚያዊ እይታዎች ኔታንያሁ "የነፃ ገበያ ጠበቃ" ተብሎ ተገልጿል. በመጀመርያው የስልጣን ዘመናቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው የባንክ ዘርፉን በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻያ የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ፣የመንግስትን የግዴታ የዋስትና ግዥ እና ቀጥተኛ ብድርን አስወግደዋል። የፋይናንስ ሚኒስትር ኔታንያሁ የእስራኤልን ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አስተዋውቀዋል። የዌልፌር ለሥራ ፕሮግራም አስተዋውቋል፣ የፕራይቬታይዜሽን ፕሮግራም መርቷል፣ የመንግሥት ሴክተርን መጠን ቀንሷል፣ የግብር አወጣጥ ሥርዓትን አሻሽሎና አስተካክሏል፣ ፉክክርን ለመጨመር ዓላማ በማድረግ በሞኖፖሊና በካርቴሎች ላይ ሕግ አውጥቷል። ኔታንያሁ ከኩባንያዎች ወደ ግለሰቦች የካፒታል ትርፍ ታክስን ያራዘመ ሲሆን ይህም የገቢ ታክስን በመቀነስ የታክስ መሰረቱን እንዲያሰፋ አስችሎታል. የእስራኤል ኢኮኖሚ ማደግ ሲጀምር እና ስራ አጥነት በከፍተኛ ደረጃ እያሽቆለቆለ ሲሄድ ኔታንያሁ በስልጣን ዘመናቸው ማብቂያ ላይ 'ኢኮኖሚያዊ ተአምር' እንደሰሩ አስተያየት ሰጪዎች በሰፊው ይነገር ነበር።] በእስራኤል ኢኮኖሚ ላይ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት በ380 በመቶ አድጓል። በሌላ በኩል ተቺዎቹ የኢኮኖሚ አመለካከቶቹን በማርጋሬት ታቸር ተነሳሽነት "ታዋቂ ካፒታሊዝም" ብለው ሰይመውታል። ኔታንያሁ ካፒታሊዝምን ሲተረጉም “ሸቀጥ እና አገልግሎቶችን በትርፍ ለማምረት በግል ተነሳሽነት እና ውድድር እንዲኖር ማድረግ ፣ነገር ግን ሌላ ሰው ተመሳሳይ ነገር ለማድረግ እንዳይሞክር ማድረግ” ሲል ገልፀዋል ። ለቦስተን ኮንሰልቲንግ ግሩፕ የኢኮኖሚ አማካሪ ሆኖ ሲሰራ የነበረው አመለካከቱ እንደዳበረ ተናግሯል፡ "የቦስተን አማካሪ ቡድን መንግስታትን ሲመለከት እና ለመንግስታት ሲሰራ ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር ለስዊድን መንግስት ስትራቴጂክ እቅድ ለመስራት ፈልገዋል" እኔ በዚህ ጉዳይ ላይ ነበርኩ እና ሌሎች መንግስታትን እመለከት ነበር ። ስለዚህ በ 1976 ወደ ሌሎች የአውሮፓ መንግስታት ዞርኩ እና ብሪታንያ እያየሁ ነበር ፣ ፈረንሳይን እያየሁ ነበር ፣ ሌሎች አገሮችን እያየሁ ነበር ፣ እናም እነሱ መሆናቸውን አየሁ ። ፉክክርን በሚከለክለው የስልጣን ክምችት ተንኮታኩተናል።እናም አሰብኩ፣፣ እነሱ መጥፎ ቢሆኑም፣የእኛ የከፋ ነበር ምክንያቱም እኛ በመንግስት ቁጥጥር ስር ወይም በማህበር ቁጥጥር ስር ያሉ ኩባንያዎች እስከነበረን ድረስ ለግሉ ዘርፍ ውድድር ቦታ ስለነበረን እና ስለዚህ በእውነቱ ውድድሩን ወይም እድገቱን አላገኙም… እና እኔ ፣ ደህና ፣ ዕድል ካጋጠመኝ ያንን እቀይራለሁ ። ስለ ፀረ-ሽብርተኝነት አመለካከት ኔታንያሁ የራሳቸው "በሁሉም አሸባሪዎች ላይ ጠንካራ አቋም" የመጣው በወንድማቸው ሞት ምክንያት ነው ብለዋል ። ዮኒ ኔታንያሁ የተገደለው በኦፕሬሽን ኢንቴቤ የታገቱትን የማዳን ተልዕኮ ሲመራ ነው። ኔታንያሁ በውትድርና ውስጥ በነበሩበት ወቅት በፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ ከመሳተፋቸው በተጨማሪ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ላይ ያተኮሩ ሦስት መጽሃፎችን አሳትመዋል። ሽብርተኝነትን እንደ አምባገነንነት ገልፆ፣ ‹‹የጥቃቱ ኢላማ በአሸባሪዎች ከተገለፀው ቅሬታ ጋር በተገናኘ በተወገደ ቁጥር ሽብርነቱ እየጨመረ ይሄዳል...አሁንም ሽብርተኝነት ምንም አይነት ተጽእኖ እንዲያሳድር በትክክል ነው። የግንኙነት እጥረት፣ አሸባሪዎች ለማጥቃት በሚፈልጉበት አላማ ውስጥ የተመረጡት ተጎጂዎች ምንም አይነት ተሳትፎ ወይም "ተጋድሎ" አለመኖራቸው የሚፈለገውን ፍርሃት ይፈጥራል። ማንም ሰው ተጎጂ ሊሆን ይችላል, እና ስለዚህ ማንም ሰው ደህና አይደለም ... በእውነቱ, ዘዴዎቹ በሁሉም የአሸባሪ ቡድኖች ውስጥ የሚደርሰውን አጠቃላይ ጫና ያሳያሉ ... የአሸባሪዎቹ መጨረሻዎች ጥፋቱን ለማረጋገጥ አለመሳካታቸው ብቻ አይደለም. የመረጡት ማለት ነው፣ ምርጫቸው እውነተኛ ዓላማቸው ምን እንደሆነ ይጠቁማል፣ የነጻነት ታጋዮች ከመሆን ርቀው፣ አሸባሪዎች የግፍ አገዛዝ ግንባር ቀደም ናቸው፣ አሸባሪዎች የአመጽ አገዛዝን ለማምጣት የአመጽ ማስገደድ ዘዴዎችን ይጠቀማሉ። ማስገደድ" ኔታንያሁ “በፀረ-ሽብር ተግባራት ላይ ችግር ፈጥሯል… ይህ ክትትል በሚደረግላቸው ሰዎች ህይወት ላይ ትልቅ ጣልቃ ገብነት መሆናቸው ነው” ሲል ያስጠነቅቃል። በዜጎች ነፃነት እና ደኅንነት መካከል ሚዛናዊነት እንዳለ ያምናል ይህም በአንድ ሀገር ውስጥ ቀጣይነት ያለው የሽብር ጥቃት ደረጃ ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት. ቀጣይነት ያለው ጥቃት በሚፈጸምበት ወቅት፣ “በአስፈሪው የግል መብት ጥሰት የሽብር ሰለባዎች እና ቤተሰቦቻቸው” ምክንያት ወደ ደህንነት መሸጋገር አለበት። ነገር ግን ይህ በመደበኛነት መከለስ ያለበት ሲሆን የትም እና መቼም የደህንነት ጉዳዮች በሚፈቅዱበት ጊዜ የዜጎችን ነፃነት እና የግለሰብን ግላዊነት መጠበቅ ላይ አፅንዖት በመስጠት፡ "በንፁሀን ዜጎች የመብት ጥሰት ምክንያት የሲቪል ነፃ አውጪዎች አሳሳቢነት በጥሩ ሁኔታ ተቀምጧል እና ሁሉም ተጨማሪ ሀይሎች ለደህንነት ጥበቃ ተሰጥተዋል ። አገልግሎቶች በህግ አውጭው አመታዊ እድሳት ሊጠይቁ ይገባል ፣ይህም በመስክ ላይ በሚወሰዱት እርምጃዎች ላይ ከፍትህ ቁጥጥር በተጨማሪ። ጥብቅ የኢሚግሬሽን ህጎችን ሽብርተኝነትን አስቀድሞ ለመከላከል እንደ አስፈላጊ መሳሪያ ይመክራል፡- "ይህ ለሁሉም ነፃ የሆነ የስደተኞች ዘመን ማብቃት አለበት። የኢሚግሬሽን ሁኔታን የመቆጣጠር አስፈላጊው ገጽታ ስደተኞች ሊሆኑ የሚችሉትን ጥብቅ የጀርባ ማረጋገጫዎች ፣ ተጣምሮ ከአገር የመባረር እድል ጋር። በተጨማሪም መንግስታት አሸባሪዎችን ከእነዚያ ህጋዊ የፖለቲካ ቡድኖች ጋር እንዳያጋጩ፣ ነገር ግን በክርክር እና በክርክር አቋማቸውን የሚያራምዱ መሆናቸውንም አስጠንቅቋል፡ “ዲሞክራሲያዊ መንግስታት የየራሳቸው ድርሻ ከስደተኛ ወይም ፀረ-ስደተኛ ወይም ፀረ-ስደተኛ ነው። -መቋቋሚያ ፓርቲዎች፣ እንዲሁም የጽንፈኛ ብሔርተኝነት ወይም አለማቀፋዊ አቀንቃኞች... [ት] ብዙውን ጊዜ በዴሞክራሲ ውስጥ እውነተኛ ተሳታፊ የሆኑ፣ መሠረታዊ ሕጎቹን ተቀብለው ማዕከላዊ መርሆቹን የሚጠብቁ ናቸው። የዲሞክራሲያዊ ማህበረሰብ ፍፁም ጠርዝ፣ ብዙ ተመሳሳይ ሃሳቦችን ሊደግፍ ይችላል፣ ነገር ግን ከዴሞክራሲያዊ ስርዓቱ ግርዶሽ ለመውጣት እንደ ምክንያት ይጠቀሙባቸው። በተለይም ሮናልድ ሬጋን ኔታንያሁ በፀረ ሽብርተኝነት ላይ የሚያደርጉትን ስራ አድናቂ ነበር እና ሬገን ለኔታንያሁ አሸባሪነት፡ የሚለውን መጽሃፍ በአስተዳደሩ ውስጥ ላሉት ከፍተኛ ባለስልጣናት መክረዋል። የሞት ፍርድ እ.ኤ.አ. በ2017 ኔታንያሁ የ2017 የሃላሚሽ የስለት ጥቃት ፈጻሚ ላይ የሞት ቅጣት እንዲጣል ጠይቀዋል። በሱ መንግስት ውስጥ ያሉ ተወካዮች በሽብርተኝነት ላይ የሞት ቅጣትን የሚፈቅደውን ህግ ለኬሴቶች አስተዋውቀዋል። እ.ኤ.አ. በጥር 2018 በተደረገ ቅድመ ድምፅ ከ120 የእስራኤል ፓርላማ አባላት 52ቱ ድጋፍ ሲሰጡ 49ኙ ተቃውመዋል። የወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ማሻሻያ ህግ ለመሆን ከተፈለገ አሁንም ሶስት ተጨማሪ ንባቦችን ይፈልጋል ኤልጂቢቲ ለእነሱ ተጨማሪ ህግ ይሰጣል ኔታንያሁ ለኤልጂቢቲ (ሌዝቢያን፣ ግብረ ሰዶማውያን፣ ቢሴክሹዋል እና ትራንስጀንደር) ሰዎች እኩል መብቶችን ይደግፋል። “እያንዳንዱ ሰው በሕግ ፊት እኩል ሆኖ እንዲታወቅ የሚደረገው ትግል ረጅም ትግል ነው፣ አሁንም ብዙ የሚቀረው ነገር አለ... እስራኤል በግንኙነት በዓለም ላይ በጣም ክፍት ከሆኑ አገሮች ተርታ መሰለፏ ኩራት ይሰማኛል። ለኤልጂቢቲ ማህበረሰብ ንግግር።” በኬኔሴት አመታዊ የማህበረሰብ መብት ቀን በተካሄደ ዝግጅት ላይ ኔታንያሁ እንደተናገሩት “በተጨናነቀ ጊዜዬ መሃል እዚህ እንድመጣ ተጠይቆኛል ለወንድ እና ሴት አባላት አንድ ነገር ለመናገር የኤልጂቢቲ ማህበረሰብ፡ እያንዳንዱ ሰው በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ ነው በሚለው እምነት መመራት አለብን። ነገር ግን በእርሳቸው ጥምር መንግስት ውስጥ ብዙዎቹ ጥምር መንግስት ፓርቲ አባላት የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ተቃውመዋል። የኢትዮጵያ አይሁዶች ውህደት እ.ኤ.አ. በ2015 ኢትዮጵያውያን አይሁዳውያን የፖሊስን ጭካኔ በመቃወም ተቃውሞአቸውን ካሰሙ በኋላ ኔታንያሁ “በሁሉም መንገድ እርስዎን ለመርዳት የሚያስችል አጠቃላይ እቅድ ለመንግስት እናመጣለን፣ በህብረተሰባችን ውስጥ ለዘረኝነት እና መድልዎ ቦታ የለም፣ አንዳቸውም ... እንመለሳለን ዘረኝነት ወደሚናቅ እና ወደሚጠላ ነገር” የሰላም ሂደት ኔታንያሁ የኦስሎ ስምምነቶችን ከመመስረታቸው ጀምሮ ተቃውመዋል። እ.ኤ.አ. በ 1993 የኦስሎ የሰላም ሂደትን ለመቃወም ፕላስ ኦፍ ኔሽንስ በተሰኘው መጽሃፉ "ትሮጃን ሆርስ" የተሰኘውን ምዕራፍ ሰጠ። አሚን አል-ሁሴኒ የጅምላ ጭፍጨፋ ፈጣሪ ከሆኑት መካከል አንዱ እንደነበር እና ያሲር አራፋት የቀድሞውን “አጥፍቷል የተባለው ናዚዝም” ወራሽ እንደሆነ ተናግሯል። እ.ኤ.አ. በ1990ዎቹ መገባደጃ ላይ ኔታንያሁ የጠቅላይ ሚንስትርነት ዘመናቸው የኦስሎ የሰላም ሂደት አካል በመሆን የቀድሞ የእስራኤል መንግስታት የገቡትን ቃል ኪዳን በመተው የአሜሪካው የሰላም መልዕክተኛ ዴኒስ ሮስ “ፕሬዚዳንት ክሊንተንም ሆነ ፀሐፊው [የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማዴሊን] አልብራይት አይደሉም። ቢቢ ሰላምን ለማስፈን ምንም ዓይነት ፍላጎት እንዳላት ያምን ነበር። እ.ኤ.አ. በ 2001 በተለቀቀው ቪዲዮ ላይ ኔታንያሁ እንደሚቀረፀው ሳያውቅ “ከምርጫው በፊት [የኦስሎ ስምምነትን] እንደማከብር ጠየቁኝ” ሲል ተናግሯል ፣ “አደርገዋለሁ አልኩ ፣ ግን ... እሄዳለሁ ስምምነቱን በ67ቱ ድንበሮች ላይ ያለውን መቃቃር እንዲያቆም በሚያስችል መንገድ ተርጉሞታል፣እንዴት አደረግን?ማንም ወታደራዊ ዞኖች ምን እንደሆኑ አልተናገረም።የተወሰኑ ወታደራዊ ዞኖች የጸጥታ ዞኖች ናቸው፤እኔ እስከ እኔ ድረስ። ያሳስበኛል፣ የዮርዳኖስ ሸለቆ በሙሉ የተወሰነ ወታደራዊ ቀጠና ነው። ሂዱ ተከራከሩ። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 9 ቀን 2009 ሳምንታዊ የካቢኔ ስብሰባው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት ኔታንያሁ የጋዛን የአንድ ወገን መገለል “ስህተት” ላለመድገም ቃል ገብተዋል ፣ “ይህን ስህተት አንደግም ። አዲስ ተፈናቃዮችን አንፈጥርም” ብለዋል ። "የአንድ ወገን መፈናቀል ሰላምም ሆነ ደህንነት አላመጣም. በተቃራኒው ", እና "ከሁለት ነገሮች ጋር ስምምነት እንፈልጋለን, የመጀመሪያው የእስራኤል የአይሁድ ህዝብ ብሔራዊ ግዛት እና [ሁለተኛው] እውቅና መስጠቱ ነው. የደህንነት እልባት. በጋዛ ሁኔታ, እነዚህ ሁለቱም ምክንያቶች አልነበሩም. በተጨማሪም "ከልክ በላይ ከሆኑ አጋሮች ጋር ወደ ሰላም መዞር ከጀመርን የእስራኤል መንግስት እውቅና እንዲሰጥ እና የወደፊቱን የፍልስጤም መንግስት ከወታደራዊ ፍርሀት ለማውረድ እንጸልያለን" ብለዋል። እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2014 ኔታንያሁ "ግዛታችንን አናስረክብም አይናችንን ጨፍነን ለበጎ ነገር ተስፋ እናደርጋለን። በሊባኖስ ያንን አደረግን እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሮኬቶችን አግኝተናል። ያንን በጋዛ አደረግን፣ ሃማስን እና 15,000 ሮኬቶችን አግኝተናል።" ስለዚህ ያንን ብቻ መድገም አንሆንም። ለአይሁዶች መንግስት እውነተኛ እውቅና እና ጠንካራ የጸጥታ ዝግጅቶችን መሬት ላይ መጣል እንፈልጋለን። ያ ነው የያዝኩት አቋም፣ እና የበለጠ እየጠነከረ መጥቷል። ኔታንያሁ ከዚህ ቀደም በዩናይትድ ስቴትስ የሚደገፉትን የሰላም ንግግሮች ጊዜ ማባከን ብለው ጠርተው ነበር፣ በተመሳሳይ ጊዜ እንደሌሎች የእስራኤል መሪዎች ተመሳሳይ የሁለት ሀገር መፍትሄ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም ፣ በሰኔ 2009 ንግግር እስከሚያደርጉ ድረስ ። "የኢኮኖሚ ሰላም" አካሄድ ማለትም በፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ላይ የማያቋርጥ ክርክር ሳይሆን በኢኮኖሚ ትብብር እና በጋራ ጥረት ላይ የተመሰረተ አካሄድ ማለት ነው። ይህ ከሰላም ሸለቆ እቅድ ብዙ ጠቃሚ ሀሳቦች ጋር የሚስማማ ነው። እነዚህን ሃሳቦች ያነሳው ከቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኮንዶሊዛ ራይስ ጋር ባደረጉት ውይይት ነው። የእስራኤል ምርጫ ሲቃረብ ኔታንያሁ እነዚህን ሃሳቦች ማበረታታቱን ቀጠለ። ኔታንያሁ እንዲህ ብለዋል፡- በአሁኑ ጊዜ የሰላም ድርድሩ በአንድ ነገር ላይ ብቻ የተመሰረተ ነው፣ በሰላማዊ ድርድር ላይ ብቻ ነው። በዚህ ነጥብ ላይ በጣም ኮንትራት ስላለው ጉዳይ ማውራት ምንም ትርጉም የለውም. እየሩሳሌም ወይም ጡጫ፣ ወይም የመመለሻ ወይም የጡት መብት ነው። ያ ውድቀትን አስከትሏል እና እንደገና ወደ ውድቀት ሊያመራ ይችላል ... ከፖለቲካዊ ሂደት ጎን ለጎን ኢኮኖሚያዊ ሰላም መፍጠር አለብን. ይህም ማለት በእነዚያ አካባቢዎች ፈጣን እድገትን በማስተላለፍ መጠነኛ የሆኑትን የፍልስጤም ኢኮኖሚ ክፍሎች ማጠናከር አለብን፣ ይህም ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ለተራ ፍልስጤማውያን የሰላም ድርሻ ይሰጣል። እ.ኤ.አ. በጥር 2009 ከየካቲት 2009 የእስራኤል ምርጫ በፊት ኔታንያሁ ለመካከለኛው ምስራቅ ልዑክ ቶኒ ብሌየር የአሪኤል ሻሮን እና ኢዩድ ኦልመርትን የእስራኤል መንግስታት ፖሊሲ በዌስት ባንክ ውስጥ ሰፈራ በማስፋፋት የመንገድ ካርታውን በሚጻረር መልኩ እንደሚቀጥል አሳውቀዋል። አዳዲሶችን አለመገንባት.እ.ኤ.አ. በ 2013 ኔታንያሁ መንግስታቸው በአረንጓዴ መስመር ላይ በመመስረት ለሰላም ድርድር እንደሚስማሙ የሚገልጹ ዘገባዎችን አስተባብለዋል። እ.ኤ.አ. በ 2014 በአረንጓዴው መስመር ላይ የተመሠረተውን የአሜሪካን ማዕቀፍ ተስማምቷል እና የአይሁድ ሰፋሪዎች በፍልስጤም አገዛዝ ስር በሰፈራቸው ውስጥ የመቆየት ምርጫ ሊፈቀድላቸው ይገባል ብለዋል ። እ.ኤ.አ. በ 2014 የፍልስጤም ተደራዳሪ ሳእብ ኤሬካት ኔታንያሁ “በርዕዮተ ዓለም ሙሰኛ” እና የጦር ወንጀለኛ ሲሉ ተችተዋል። እ.ኤ.አ. በጥር 2020 ኔታንያሁ የትራምፕን የእስራኤል-ፍልስጤም የሰላም እቅድ የፍልስጤም ግዛት ለመፍጠር በይፋ ደግፈዋል። የቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን እንዳሉት ኔታንያሁ በግንቦት 22 ቀን 2017 የፍልስጤሙ ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ ህጻናት እንዲገደሉ ሲጠይቁ የሚያሳይ የውሸት እና የተቀየረ ቪዲዮ ለዶናልድ ትራምፕ አሳይተዋል። ይህ የሆነው ትራምፕ እስራኤል የሰላም እንቅፋት መሆን አለመሆኗን ሲያስቡበት ወቅት ነበር። ኔታንያሁ በእስራኤል እና ፍልስጤም ግጭት ውስጥ ያላቸውን አቋም ለመቀየር የውሸት ቪዲዮውን ለትራምፕ አሳይተው ነበር።በዩናይትድ ስቴትስ የተደራጁት የአብርሃም ስምምነት በእስራኤል እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች (በእስራኤል-የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ መደበኛነት ስምምነት) እና በባህሬን (በባህሬን-እስራኤል መደበኛነት ስምምነት) መካከል ያለውን ግንኙነት ሙሉ ለሙሉ መደበኛ ለማድረግ ተስማምቷል። እ.ኤ.አ. በ1994 ከዮርዳኖስ ወዲህ የትኛውም አረብ ሀገር ከእስራኤል ጋር ያለውን ግንኙነት መደበኛ ሲያደርግ ይህ የመጀመሪያው ነው። ስምምነቱን የተፈራረሙት በባህሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ኔታኒያሁ ሴፕቴምበር 15 ቀን 2020 በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የዋይት ሀውስ ሳውዝ ላውን። እ.ኤ.አ. ጥቅምት 23 ቀን 2020 የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሱዳን ከእስራኤል ጋር ያላትን ግንኙነት መደበኛ ማድረግ እንደምትጀምር በትራምፕ አስተዳደር አብርሀም ስምምነት መሰረት ይህንን የምታደርግ ሶስተኛዋ የአረብ ሀገር እንድትሆን አስታውቀዋል። ሱዳን እ.ኤ.አ. ሙሉ በሙሉ ተነጥለን ወደ ፖለቲካ ሱናሚ እንደምንሄድ ነገሩን። እየሆነ ያለው ግን ፍጹም ተቃራኒ ነው። ይህን ተከትሎም ሞሮኮ በታህሳስ ወር ከእስራኤል ጋር ግንኙነት ፈጠረች። የባር-ኢላን ንግግር እ.ኤ.አ. ሰኔ 14 ቀን 2009 ኔታንያሁ በባር-ኢላን ዩኒቨርስቲ (የባር-ኢላን ንግግር በመባልም ይታወቃል) ፣ በቤጂን-ሳዳት የስትራቴጂካዊ ጥናቶች ማእከል ፣በእስራኤል እና በተለያዩ የአረብ ሀገራት በቀጥታ የተላለፈ ሴሚናል ንግግር አድርጓል። በእስራኤል እና ፍልስጤም የሰላም ሂደት ላይ። ከእስራኤል ጎን ለጎን የፍልስጤም መንግስት የሚለውን ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ አፅድቋል። የኔታኒያሁ ንግግር ኦባማ በሰኔ 4 በካይሮ ላደረጉት ንግግር በከፊል ምላሽ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ዬዲዮት አህሮኖት የኦባማ ቃል “በኢየሩሳሌም ኮሪደሮች በኩል ተስማምቷል” ብሏል። የሐሳቡ አንድ አካል የሆነው ኔታንያሁ፣ ጦር፣ ሮኬቶች፣ ሚሳኤሎች እና የአየር ክልሏን ሳይቆጣጠር፣ የታቀደውን ግዛት ሙሉ በሙሉ ከወታደራዊ ኃይል ነፃ እንድትወጣ ጠይቀዋል እና እየሩሳሌም ያልተከፋፈለ የእስራኤል ግዛት እንደምትሆን ተናግሯል። ፍልስጤማውያን እስራኤልን ያልተከፋፈለች እየሩሳሌም ያላት የአይሁዶች ብሄራዊ መንግስት እንደሆነች ሊገነዘቡት ይገባል ብሏል። “በእስራኤል ውስጥ የፍልስጤም ስደተኞችን መልሶ የማቋቋም ጥያቄ የእስራኤልን የአይሁድ ህዝብ ግዛትነት የሚጎዳ ነው” በማለት የፍልስጤም ስደተኞችን የመመለስ መብት አልተቀበለም። እ.ኤ.አ. በ 2003 በሮድ ካርታ የሰላም ሀሳብ መሰረት በዌስት ባንክ የሚገኘውን የሰፈራ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ማቆም እንዳልተቻለ እና የማስፋፊያ ግንባታው የሚገደበው የኢሚግሬሽንን ጨምሮ በህዝቡ "ተፈጥሯዊ እድገት" ላይ በመመስረት ነው ብለዋል ። አዲስ ግዛቶች ተወስደዋል። ቢሆንም፣ ኔታንያሁ የ ፕሮፖዛል መቀበሉን አረጋግጠዋል። ከሰላም ድርድር በኋላ ሰፈራዎቹ የእስራኤል አካል ስለመሆኑ ወይም ስለሌለባቸው አልተወያየቱም፣ “ጥያቄው ይብራራል” በማለት ብቻ ተናግሯል። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በካይሮ ንግግራቸው ለተናገሩት ምላሽ ኔታንያሁ በሰጡት ምላሽ “የእልቂት እልቂት ባይከሰት ኖሮ የእስራኤል መንግሥት በፍጹም አትመሠርትም የሚሉ አሉ። እኔ ግን የእስራኤል መንግሥት ቢሆን ኖሮ እላለሁ። ቀደም ብሎ ይቋቋም ነበር፣ እልቂቱ አይከሰትም ነበር። በተጨማሪም “ይህ የአይሁድ ሕዝብ መገኛ ነው፣ ማንነታችን የተጭበረበረበት ይህ ነው” ብሏል። በተለይም ሶሪያን፣ ሳዑዲ አረቢያን እና ሊባኖስን በማንሳት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከየትኛውም "የአረብ መሪ" ጋር ለመገናኘት ፈቃደኛ እንደሚሆን ገልጿል። በአጠቃላይ አድራሻው በሰላሙ ሂደት ላይ ለኔታኒያሁ መንግስት አዲስ አቋምን ይወክላል። አንዳንድ የናታንያሁ የአስተዳደር ጥምረት የቀኝ ክንፍ አባላት ሁሉም መሬት በእስራኤል ሉዓላዊነት ስር መሆን አለበት ብለው በማመን የፍልስጤም መንግስት ለመፍጠር የሰጡትን አስተያየት ተችተዋል። ሊኩድ ኤምኬ ዳኒ ዳኖን ኔታንያሁ “በሊኩድ መድረክ ላይ ሄደው ነበር” ሲል የሀባይት ሃይሁዲው ግን “አደገኛ አንድምታ አለው” ብሏል። የተቃዋሚ ፓርቲ ካዲማ መሪ ቲዚፒ ሊቪኒ ከአድራሻቸው በኋላ እንደተናገሩት ኔታንያሁ በሁለቱ መንግስታት መፍትሄ በጭራሽ አያምንም ብለው ያስባሉ ። ለአለም አቀፍ ጫና የይስሙላ ምላሽ ሆኖ ያደረገውን ብቻ የተናገረው መስሏት ነበር። ፒስ ናው ንግግሩን በመተቸት በቡድኑ አስተያየት ፍልስጤማውያንን የሰላም ሂደት እኩል አጋር አድርጎ እንዳልተናገረ አመልክቷል። የሰላም አሁኑ ዋና ጸሃፊ ያሪቭ ኦፔንሃይመር “የኔታንያሁ ከመጀመሪያው የስልጣን ዘመናቸው ድጋሚ የተደረገ ነው” ብለዋል። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 9 ቀን 2009 በመንግስት ስብሰባ መክፈቻ ላይ ኔታንያሁ ከፍልስጤማውያን የይገባኛል ጥያቄያቸውን ደግመዋል፡- “እኛ ከሁለት ነገሮች ጋር ስምምነት እንፈልጋለን፣ ከእነዚህም ውስጥ የመጀመሪያው እስራኤል የአይሁድ ህዝብ ብሔራዊ ግዛት እና ሁለተኛው ደግሞ) የጸጥታ ስምምነት ነው. የኔታኒያሁ "የባር-ኢላን ንግግር" ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ የተለያየ ምላሽ አስነስቷል። የፍልስጤም ብሄራዊ ባለስልጣን በኔታንያሁ የተሰጠውን የፍልስጤም መንግስት ቅድመ ሁኔታዎችን ውድቅ አደረገ። ከፍተኛ ባለስልጣን ሳእብ እረቃት "የናታንያሁ ንግግር ለቋሚ ደረጃ ድርድር በር ዘጋው" ብለዋል። የሃማስ ቃል አቀባይ ፋውዚ ባርሆም ይህ "ዘረኝነት እና ጽንፈኛ አስተሳሰብ" የሚያንፀባርቅ መሆኑን ገልፀው የአረብ ሀገራት "ጠንካራ ተቃዋሚዎች እንዲፈጥሩ ጥሪ አቅርበዋል" የፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ " አሳሳች " በማለት ሰይሞታል እና ልክ እንደ ሃማስ በእስራኤል ላይ ጠንካራ ተቃውሞ ከአረብ ሀገራት ጠየቀ. ዘ ጀሩሳሌም ፖስት እንደዘገበው፣ አንዳንድ መሪዎች ለንግግሩ ምላሽ ሦስተኛውን ኢንቲፋዳ ይደግፋሉ። የአረብ ሊግ አድራሻውን ውድቅ በማድረግ "አረቦች በእየሩሳሌም ጉዳይ እና በስደተኞች ጉዳይ ላይ ስምምነት እንደማይሰጡ" እና "ታሪኩን እና የመሸሽ ስልቱን እናውቃለን" ሲል በመግለጫው አስታውቋል, የአረብ ሊግ እስራኤልን እንደ አይሁዶች አይቀበልም. ሁኔታ. የግብፁ ፕሬዝዳንት ሆስኒ ሙባረክ ፍልስጤማውያን እስራኤልን የአይሁድ ህዝብ ግዛት አድርገው እንዲቀበሉት ኔታንያሁ ያቀረቡትን ጥያቄ በመጥቀስ፣ “በግብፅም ሆነ በሌላ ቦታ ያን ጥሪ የሚመልስ ማንም አታገኝም” ብለዋል። የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ብዙም ግልፅ ያልሆነ ምላሽ ሲሰጥ ንግግሩ "ያልተጠናቀቀ" እና ሌላ "የተለያየ የእስራኤል ሀሳብ በሁለቱ ሀገራት መፍትሄ ላይ የተመሰረተ ነው" የሚል ተስፋ አለኝ ብሏል።የሶሪያ መንግስት ሚዲያ ንግግሩን በማውገዝ "ናታንያሁ የጸጥታው ምክር ቤት አንጻራዊ ሰላም ለማስፈን በሚያደርጋቸው ውጥኖች እና ውሳኔዎች ላይ የአረብ የሰላም ተነሳሽነትን እንደማይቀበል አረጋግጠዋል" ሲል ጽፏል። የሊባኖሱ ፕሬዝዳንት ሚሼል ሱሌይማን የአረብ መሪዎች አንድነት እንዲኖራቸው ጥሪ አቅርበዋል "የአረብ መሪዎች የበለጠ አንድነት እንዲኖራቸው እና የሰላም ሂደቱን እና የፍልስጤም የስደተኞችን ጉዳይ በተመለከተ የእስራኤልን አቋም ለመጋፈጥ የተቃውሞ መንፈስን መጠበቅ አለባቸው." “እስራኤል አሁንም በሊባኖስ እና በጋዛ ሰርጥ ላይ በምታደርገው ጥቃት ሊረጋገጥ የሚችል ወታደራዊ ግጭት ፍላጐት አላት” ሲሉ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የእስራኤል መንግስት የአረብ የሰላም ኢኒሼቲቭን እንዲቀበል የበለጠ ጫና እንዲያደርግ ጠይቀዋል። የዮርዳኖስ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ እና የመንግስት ቃል አቀባይ ናቢል ሸሪፍ መግለጫ ሰጥተዋል "በኔታንያሁ የቀረቡት ሃሳቦች ፍትሃዊ እና ሁሉን አቀፍ ሰላምን ለማስፈን መነሻ በማድረግ በአለም አቀፍ ማህበረሰብ የተስማሙበትን መሰረት አላደረጉም። ክልል" የቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ ንግግሩን "መጥፎ ዜና" ብለውታል። ቼክ ሪፐብሊክ የኔታንያሁ አድራሻ አወድሷል። በንግግራቸው ወቅት ሀገራቸው የአውሮፓ ህብረት የስድስት ወር የፕሬዚዳንትነት ቦታን የያዘች የቼክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጃን ኩውት "በእኔ እይታ ይህ ትክክለኛ እርምጃ ነው። የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የፕሬስ ሴክሬታሪ ሮበርት ጊብስ ንግግሩ “ጠቃሚ እርምጃ ወደፊት” ነው ብለዋል። ፕሬዝዳንት ኦባማ "ይህ መፍትሄ ሁለቱንም የእስራኤልን ደህንነት እና የፍልስጤማውያንን ህጋዊ ምኞቶች ማረጋገጥ ይችላል እና አለበት" ብለዋል ። የስዊድን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካርል ቢልድት "ግዛት የሚለውን ቃል መናገሩ ትንሽ እመርታ ነው" ብለዋል። አክለውም "የጠቀሱት ነገር እንደ ሀገር ሊገለጽ ይችላል ወይ የሚለው ጉዳይ የተወሰነ ክርክር ነው" ፈረንሳይ ንግግሩን አድንቆ እስራኤል ግን በዌስት ባንክ ውስጥ የሰፈራ ግንባታ እንድታቆም ጠይቃለች። የፈረንሳዩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በርናርድ ኩችነር “በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር የተገለጸውን የፍልስጤም መንግሥት ተስፋ ብቻ ነው የምቀበለው” ብለዋል። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ንግግሩን "ለውይይት ዝግጁነት ምልክት ነው" ብሏል ነገር ግን "የእስራኤል እና የፍልስጤም ችግርን ለመፍታት መንገዱን አይከፍትም. በፍልስጤማውያን ላይ ያለው ሁኔታ ተቀባይነት የለውም."
1527
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB
ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ወይም በይፋ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢ.ፌ.ዲ.ሪ.) በአፍሪካ ቀንድ የምትገኝ የረጅም ዘመን ታሪክ ያላት ሀገር ናት። በአፍሪካ ነፃነቷን ጠብቃ የኖረች ብቸኛ ሀገር ነች። በህዝብ ብዛት ከአፍሪካ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ስትሆን ፣ በቆዳ ስፋት ደግሞ አስረኛ ናት። ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ናት። አብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገሮች ዕድሜያቸው ከአንድ ምዕተ-ዓመት የሚያንስ ሲሆን ፣ ኢትዮጵያ ግን ከጥንት ጊዜ ጀምሮ በንጉሠ-ነገሥታት እና ንግሥተ-ነግሥታት የተመራች ሀገር ናት። የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት የአመጣጡን ዘር እስከ አስረኛው ዓመተ-ዓለም ድረስ ይቆጥራል። ኢትዮጵያ የሰው ልጅ ከጥንት ጊዜ ጀምሮ የኖረባት ቦታ እንደሆነች ብዙ የሳይንሳዊ መረጃ ተግኝቷል። በበርሊን ጉባኤ በኩል የአውሮፓ ሀያላት ሀገሮች አፍሪካን ሲከፋፍሏት፣ ኢትዮጵያ ነፃነቷን ጠብቃለች። የሊግ ኦፍ ኔሽንስ () አባል ከነበሩት ሶስት የአፍሪካ ሀገሮች አንዷ ነበረች። ከአጭር የኢጣልያ ወረራ ጊዜ በኋላም ከየተባበሩት መንግሥታት መሥራቾች አንዷ ናት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ነፃነታቸውን ሲያገኙ፣ ሰንደቅ-አላማቸውን በኢትዮጵያ ቀለሞች ማለትም በአረንጓዴ ፣ ቢጫ እና ቀይ ላይ ነው የመሠረቱት። አዲስ አበባ ደግሞ ለየተለያዩ በአፍሪካ ላይ ላተኮሩ አለም አቀፍ ድርጅቶች መቀመጫ ሆነች። የዛሬዋ ኢትዮጵያ የትልቅ የግዛት ለውጥ ውጤት ናት። ከሰሜን ግዛቱዋ በጣም የተቀነሰ ሲሆን በደቡብ በኩል ደግሞ ተስፋፍቷል። በ ፲፱፻፷፯ ዓ.ም.፣ ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ከሥልጣን ሲወርዱ፣ የእርስ በርስ ጦርነት በሀገሩ ተባባሰ። ከዚህ ጊዜ በኋላ ኢትዮጵያ በተለያዩ የመንግሥት አይነቶች ተዳድራለች። ዛሬ አዲስ አበባ የአፍሪካ ሕብረት () እና የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚክ ኮሚሽን ለአፍሪካ መቀመጫ ናት። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ከአፍሪካ ኃያል ሠራዊቶች አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪቃ የእራሷ ጥንታዊ ፊደል ያላት ሀገርም ናት። ኢትዮጵያ ተፈጥሮ ያደላት ሀገር ናት። ከአፍሪካ ትላልቅ ተራራዎች እንዲሁም ከዓለም ከባህር ጠለል በታች በጣም ጥልቅ ከሆኑ ቦታዎች አንዳንዶቹ ይገኙባታል። ሶፍ ዑመር ከአፍሪካ ዋሻዎች ትልቁ ሲሆን ፣ ዳሎል ከዓለም በጣም ሙቅ ቦታዎች አንዱ ነው። ወደ ሰማንኒያ የሚቆጠሩ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ዛሬ በኢትዮጵያ ይገኛሉ። ከእነዚህም ኦሮሞና አምሀራ በብዛት ትልቆቹ ናቸው። ኢትዮጵያ በኣክሱም ሓውልት፣ ከአንድ ድንጋይ ተፈልፍለው በተሰሩ ቤተ-ክርስትያኖቹዋ እና በኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ አትሌቶቹዋ ትታወቃለች። የቡና ፍሬ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢትዮጵያ ሲሆን ሀገሪቱዋ በቡናና ማር አምራችነት በአፍሪካ ቅድሚያ ይዛለች። ኢትዮጵያ ከዓለም ሶስቱ ትላልቅ የአብርሃም ሀይማኖቶች ጋር ታሪካዊ ግንኙነት አላት። ክርስትናን በአራተኛው ምዕተ-ዓመት ተቀብላለች። ከሕዝቡ አንድ ሁለተኛው ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ነው። የመጀመሪያው የእስላም ሂጅራ ወደ ኢትዮጵያ ነው የተከናወነው። ነጋሽ በአፍሪካ የመጀመሪያው የእስላም መቀመጫ ናት። እስከ ፲፱፻፸ ዎቹ ድረስ ብዙ ቤተ-እስራኤሎች በኢትዮጵያ ይኖሩ ነበር። የራስ ተፈሪ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያን በትልቅ ክብር ነው የሚያያት። ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ከስልጣን ከወረዱ በኋላ ድህነት በኢትዮጵያ በጣም ተስፋፍቶ ነበር። ሰማኒያ አምስት ከመቶ በላይ የሚሆነው የአባይ ወንዝ ውሀ ከሀገሩ የሚመጣ ቢሆንም በ ፲፱፻፸ ዎቹ በተከሰቱ ድርቆች በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ሞተዋል። ያንን ካሳለፈች በኋላ ሀገሪቱዋ አዲስ መንገድ በመፈለግ ላይ ትገኛለች። “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃል ትርጉሙንና አመጣጡን ለመመርመር በ፲፱፻፹፩ (1987 እ.ኤ.አ.) በወጣው ሰምና ወርቅ በተባለው የምርምር መጽሔት ፪ኛ ዓመት፣ ቁጥር ፬ አጥር ያለ ጽሑፍ አቅርበን፣ አንዳንድ ምሁራን፤ “ኢትዮጵያ ማለት ከግሪክ ቋንቋ የመጣ ቃል፣ ‘ፊቱ በፀሓይ የተቃጠለ፣ የተጠበሰ፣ ያረረ’ ማለት ነው ...” የሚሉት ትክክል እንዳልሆነ ለማሳየት፤ ናይጀርያ የሚባል አገርና፣ () ኒጀር () የሚባሉ አገርና ወንዝ በአፍሪካ እንዳሉ ጠቅሰን፣ ኔግራ፣ ኔግሮ፣ ኒገር፣ ኔግሪትዩድ () ለሚሏቸው ቃላት ወደ ላቲን/እንግሊዝኛ ቋንቋ ለመግባት ምክንያት ሆኑ እንጂ፣ ከላቲን ቋንቋ ተወስዶ ለአፍሪካ አገሮችና ወንዝ የተሰጠ ስም አይደለም በማለት፣ ኢትዮጵያ የሚለውም ቃል እንዲሁ ጥንታዊ ምንጩ ከግሪክ ሳይሆን ከአገራችን የወጣ ቃል መሆኑን ለመግለጽ ሞክረን ነበር። አንድ-አንድ ቃላትን ስንመረምር በውስጣቸው የተደበቅ ምስጢር እናገኛለን። የተደበቀውን ምስጠር ለማግኘት ጥልቅ የታሪክና የቃላት ምርምርና ጥናት () ማድረግ ያስፈልጋል። በብዙ ምርምርና ጥናትም ምስጢሩ የሚገለጥበት ጊዜ አለ። ለምሳሌ በግዕዝ፣ በትግርኛና፣ አማርኛ ‘አነ’፣ ‘እኔ’ የሚሉ ቃላት ስናገኝ፣ በላቲን/በእንግሊዝኛ ደግሞ ‘አይ’ ( - እንግሊዝኛ)፣ ‘ኢዮ’ ( -ጣልያንኛ) አሏቸው። በግዕዝ፣ ትግርኛና፣ አማርኛ ‘ዓይን’ ‘ዓይኒ’ ለሚሉ ቃላት ደግሞ፣ በእንግሊዝኛ አይ () እናገኛለን። በአማርኛና ትግርኛ፤ ‘ያለቀለት ጉዳይ’ ለማለት ‘ሙት፣ የሞተ ነገር’፣ ስንል በእንግሊዝኛ ‘ሙት ኢሹ’ () ይላሉ። በግዕዝና፣ ትግርኛ፣ ‘መርዓ’ ስንል፣ በእንግሊዝኛ () ‘መረጅ’ ይላሉ። ፈርኦን () ከሚባል ጥንታዊ የግብፅ ንጉሥም ወደ ግዕዝ፣ ትግርኛና አማርኛ፣ እንዲሁም ወደ እንግሊዝኛ ቃላት፤ ‘ፈሪሃ’ ‘ፍርሓት’ ‘’ (ፊር) ለሚሏቸው ቃላት ምንጭ የሆነ ይመስላል። ንጉሡ ታላቅና የሚፈራ የነበረ ነው የሚመስል። እነዚህን ለምሳሌ አቀረብን እንጂ እንደዚህ ብዙ የቃላት መቀራረብ እናገኛለን። “ማን ከማን ወሰደ? ታሪካዊ አመጣጡና አወራረዱስ እንዴት ነው?” የሚሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ነው የቃላት ጥናትና ምርምር የሚያስፈልግ። አንድ-አንድ ቃላትም ከቋንቋችን ፈልቀው ይወጡና ዓለምን ዞረው ተመልሰው ሲመጡ ብርቅ አድርገን እንቀበላቸዋለን። ለምሳሌ በኃይለሥላሴ ዘመን ያኔ ልዕልት ፀሓይ ሲባል ከነበረው ሆስፒታል ጎን አዲስ የሕንፃ ኮሌጅ ተከፍቶ፣ ‘የመሃንድስ ኮሌጅ’ በመባል ይታወቅ ነበር። መሃንድስ ማለት ምን ማለት ነው? መሃንድስ ማለት መሃናስ/መሃንዳሰ ከሚል የዓረብኛ ቃል የመጣ ሲሆን፣ እርሱ ደግሞ ሃነፀ፣ ይሃንፅ፣ ማነፅ፣ ማሕፀን (ሕፃን የሚታነፅበት ቦታ) ... ወዘተ ከሚሉ የግዕዝ፣ የትግርኛና፣ የአማርኛም ቃላት ይዛመዳል። እንግዲያውስ ማነፅ ከሚለው ቃል መሃንዳስ ሆኖ ተጣመመና፣ ከዚያም መሃንድስ ተብሎ፣ ዞሮ ተመልሶ ብርቅ ቃል ሆኖብን ለሕንፃ ኮሌጀ መጠሪያ ሆነ። አሁንም ቢሆን ኢንጂኔር ለማለት መሃንድስ ሲባል እንሰማለን። ሌላም ቃል ፋጡማ/ፋጢማ የሚል ስም ስንመለከት፣ ከነብዩ ሙሓመድ ሴት ልጆች ለአንዷ የተሰጠ መጠሪያ ነበረ። በዓረብኛ አባባል ግን ጠ/ጸ የሚለው ሳይሆን ተ የሚለው ፊዴል ድምፅ ነው። ይህም ማለት፣ ቃሉ “ፈቲማ” ብለው ሲሉ፣ ትርጉሙም፡ ፍጽምት፣ () ማለት ነው። ስለዚህ ፈቲማ ማለት፣ ፈጺማ (ትግረኛ) ፈጸመች (አማርኛ) ማለት ነው። ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት ሰምና ወርቅ በተባለው የምርምር መጽሔት (1987 እ.ኤ.አ.) ያቀረብነው፣ “ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ትርጉሙ ምን ማለት ነው? ኢትዮጲስ የሚባለው ንጉሥስ ለምን ይህ ስም ተሰጠው ... ብለን በጠየቅንበት ጊዜ አጥጋቢ መልስ ባለማግኘታችን ቋንቋ ለሚመረምሩ () እንዲያተኩሩበት በዚሁ እንተወዋለን” በማለት ምርምሩን ደመደምነው።በዚህም ይህን መልስ አግኝተናል ኢትዮጲስ በመጽሐፈ አክሱም ዘንድ ኑቢያን የመሠረተው የካም ልጅ ኩሽ ልጅ ነበር። በዚህ መሠረት በኢትዮጵያ የሚኖሩት ኩሺቲክ ብሔሮች አባት በመሆኑ አገሩ 'ኢትዮጵያ' መባሉ እንደሚገባው ይታመናል። በተክለ ጻድቅ መኩሪያ የተጻፈው “የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ኑብያ፣ (ናፓታ-መርዌ)” በተባለው መጽሐፍ በገጽ19-22 የካም ወገን የሆኑ 22 ነገሥታ ን ስምጠቅሶ፣ 55 ዓመት ከገዛው ከአክናሁስ ወይም ሳባ ፪ኛ ከክርስቶስ ልደት በፊት አንስቶ የ29 ነገሥታትን ስም አስቅምጦ፤ “... ራማ የተባለ የህንድ ንጉሥ ወደ ኢትዮጵያ ዘምቶ ማሸነፉንና ሕዝቡን እንደ ባርያ ...” ይገዛው እንደ ጀመረ ያትታል። ከዚያ ግን ሦስት የዮቅጣን ልጆች ተባብረው ተነስተው እሸነፉት፥ ገድለውም፣ አግዓዝያን (ነፃ አውጭዎች) ተብለው መንግሥቱን እንደ ያዙ ገልጾ፣ ከዚያ ቀጥለው የነገሡትን የ52 የኢትዮጵያ ነገሥታት ስም ይዘረዝራል። ከፊተኞቹ 29 ነገሥታትም የመጀመሪያዎቹ 10 ነገሥታት የሚከተሉት ናቸው:- ከዚህም ዓምድ እንደሚታየው ኢትዮጲስ ፩ኛ ከ1856-1800 ከክርስቶስ ልደት በፊት፣ ለ56 ዓመት መንገሡ፣ ኢትዮጲስ ፪ኛው ደግሞ ከ1730-1700 ከክርስቶስ ልደት በፊት፣ ለ30 ዓመት ያህል መንገሡ በታሪክ ተጽፏል። ይህንን ያላነበቡ ምሁራኖቻችን ግን ኢትዮጵያ ማለት ከግሪክ ቋንቋ የመጣ ቃል፤ ‘ፊቱ በፀሓይ የተቃጠለ፣ የተጠበሰ፣ ያረረ ማለት ነው’ ይሉናል። ታላቁ የግሪክ ተራኪና ባለ ቅኔ፣ ሆመር የኖረው 800 - 700 ከክርስቶስ ልደት በፊት ሲሆን፣ የግሪክ ስልጣኔ ዘመን ወይም የሄሌኒስቲክ ኤጅ () ተብሎ የሚታወቀውም ከታላቁ እስክንድር ዘመን አንስቶ፣ ማለትም 300-30 ከክርስቶስ ልደት በፊት ድረስ ያለው ጊዜ ነው። ይህ ማለት ኢትዮጲስ ፩ኛ ከባለቅኔው ከሆመር በፊት አንድ ሺሕ ዓመት ቀድሞ የነገሠ ንጉሥ ነው። እንግዲያውስ ምሁራኖቻችን ኢትዮጵያ ማለት ከግሪክ ቋንቋ የመጣ፤ ‘ፊቱ በፀሓይ የተቃጠለ፣ የተጠበሰ፣ ያረረ ማለት ነው’ ሲሉን፣ ሊመልሷችው የማይችሉ ሁለት ጥያቄዎች አሉን፣ 1 - የጥንት የአገራችን ነገሥታት የግሪክን ቋንቋ ከሆመር መወለድ በፊት አንድ ሺሕ ዓመት አስቀድመው እንደምን ዐወቁት? ዘመኑ አቴናውያንና ስፓርታውያን የእርስ-በርስ ጦርነት ( 431-404 ከክርስቶስ ልደት በፊት) አንድ ሺሕ አራት መቶ ዓመት በፊት ነው። የግሪክ ቋንቋም በአካባቢው ከነበሩ መቄዶንያ፣ ማግያር፣ አናጦልያ ... ወዘተ ከመሳሰሉት ቋንቋዎች በምኑም ተለይቶ የሚታወቅ፣ ወይም የገነነ ልሳን አልነበረም። ስለዚህ እንዴት ተብሎ ይህንን ስም የአገራችን ነገሥታት ከግሪክ ቋንቋ ወሰዱት ማለት ይቻላል? 2 - ቋንቋውን ቢያውቁና ቃሉን ከግሪክ ወሰዱት ብንልም፣ እንዴት የአገራችን ነገሥታት ራሳቸውን፤ “ፊታችን በፀሓይ ያረረ፣ የተጠበሰ፣ የተቃጠለ ነውና ራሳችንን ኢትዮጲስ፤ ‘ፊታቸው በፀሓይ ያረረ፣ የተጠበሰ፣ የተቃጠለ’ ብለን እንጥራ ...” ብለው የራሳቸውን የንግሥ ስም አወጡ? ይህ ዓይነቱ አባባል ይታመናል? ፈጽሞ የማይመስል ወሬ ነው። ምሁራኖቻችን እነዚህን ሁለት ጥያቄዎች ሲጠየቁ፣ “አፋፍ-ላፋፍ ስትሄድ አግኝቸ ሚዳቋ፣ በጅራቷ ብይዛት ዓይኗ ፍጥጥ አለ ...” እንደሚሉት ዓይናቸውን ከማፍጠጠና ከመቅበዝበዝ በቀር ሌላ የሚያድርጉት ሆነ የሚሰጡት ምንም መልስ የላቸውም። በግሪክ ቋንቋ (አይትዮፕያ) ማለት ፊቱ በፀሓይ የተቃጠለ፣ የተጠበሰ፣ ያረረ ማለት ለመሆኑ አያጠያይቅም። ጥያቄው፤ የትኛው ቃል ከየትኛው መጣ? ነው። ግሪኮች የአገራችን ጥቁር ሰው አይተው ነው ቃሉን ወደ ቋንቋቸው ያስገቡት፣ ወይስ የአገራችን ነገሥታት ናቸው ስማቸውን ከግሪክ ቋንቋ ወስደው ለራሳቸው መጠሪያ ያደረጉት? ጥያቄው ይህ ነው! የዚህ ዓይነቱ የተዛባ አስተሳሰብ የተላበሰ አንድ የሃይማኖት መሪ፤ “... ድንቅና ተአምር የሆነ የእግዚአብሔር ጥበብ የሚገርም ነገር አለ፣ ዓይናችን፣ አፍንጫችንና፣ ጆሮአችን እንዴት ብሎ ለመነጽር እንደሚገጥም ሆኖ መፈጠሩ ዕጹብ አይደለም?” እያለ ሰብኳል ይባላል። ይህ ግን የትኛው ቀዳሚ፣ የትኛው ኋለኛ መሆኑን ባለማወቁ ነው። መነጽር ነው ለዓይን፣ ለአፍንጫና ለጆሮ እንዲገጥም ሆኖ የተሠራ እንጂ፣ ፊታችን ለመነጽር እንዲገጥም ሆኖ አልተፈጠረም። ጥልቀት የሌለው ዐውቃለሁ ባይነት ግን ለእንዲህ ዓይነቱ መዘላበድ ያጋልጣል። ፪ኛ የቃላትና የፊዴላት ምርምር ‘ፐ’ ‘ጰ’ ‘ጠ’ ‘ተ’ በመጀመሪያ () ‘አይትዮፕያ’‘ኢትዮጵያ’ የሚሉ ቃላት ለመሆኑ የአገራችን ቃላት ናቸው ወይ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። ለመሆኑ ከግዕዝ፣ ከአማርኛና፣ ከትግርኛ ቋንቋዎች “ጰ” ወይም “ፐ” የሚል ፊዴል ያላቸውን ቃላት ብንፈልግ ምን እናገኛለን? በግዕዝፅ በትግርኛና በአማርኛ ፖሊስ ከሚል ቃል ሌላ ‘ፐ’ ፊዴል ያለበት ምን ቃል አለ? ምንም ያለ አይመስለንም። የአገራችን ሰውም ፓሊስ ከማለት ‘ቦሊስ’ ማለት ነው የሚቀናው፥ ኢትዮጵያ ከማለትም ይጦብያ ማለት ይቀልለዋል። ‘ፐ’ እና ‘ጰ’ የሚባሉ ፊዴላትም ወደ አገራችን የፊዴል ሰነድ የገቡት በቅርብ ጊዜ ከመሆኑም በላይ፥ የውጭ ቃላትን ለመጻፍ እንዲያመቹ ተብሎ መሆኑ ግልጽ ነው። በፊደላት ሰንጠረጅም ከሁሉ በታች፣ ወይም ከመጨረሻ ቦታ መስፈራቸው ኋላ የመጡ ለመሆናቸው ተጨማሪ ማስረጃ ነው። ‘ጰ’ የሚል ፊዴል ያላቸውን ቃላት የአገራችን ቋንቋዎች ብንፈልግም፤ ጴጥሮስ፣ ጳውሎስ፣ ቆጵሮስ፣ ጠረጴዛ ወዘተ... እናገኛለን። ይሁንና እነዚህ ሁሉ የውጭ ቃላት፣ ከመካከለኛው ምስራቅና ከኤውሮጳ የገቡ እንጂ የአገራችን ቃላት አይደሉም። ‘ጠረጴዛ’ የሚል ቃልም ትራፔዞይድ () ከሚለው የላቲን/የእንግሊዝኛ ቋንቋ የተገኘ እንጂ በመሰረቱ የአማርኛ ቃል አይደለም። በጥንታዊ ግዕዝ ጽሑፍም ስንመለከት፤ ‘ክሊዎፓትራ፣ የፕቶሎሚ ልጅ’ ለማለት፤ “አከልኡበጥራ፣ ወለተ በጥሊሞስ” ይላታል። ይህ የሚያሳየው “ፐ” የሚባል ፊዴል በጥንታዊ የአገራችን ቋንቋዎች ፈጽሞ እንዳልነበረ ነው። ክሊዎፓትራና አባቷ ፕቶሎሚ ግን ዘራቸው ግሪክ፣ ታላቁ እስክንድር ግብፅን አሸንፎ ከዚያው በኋላ ተክሏቸው የሄደ የግሪክ ገዢዎች ስለሆኑ፣ ስማቸው የግሪክ ስም ነው። ‘ፐ’ የሚል ፊዴልም አለበት። ይህንን የፊዴላት ጥያቄ ያመጣነው ጥንታዊው የሁለቱ ነገሥታት ስም አጠራር ‘ኢትዮጲስ’ ወይም ‘ኢትዮፒስ’ ሊሆን እንደማይችል ለማስረዳት ነው። እንግዲያውስ ከዚህ የቃላት ምርምር የምናገኘው ነገር ካለ ይኽ ነው፤ በትክክለኛው ጥንታዊ አባባል ኢትዮጲስ፣ ኢይቶጲስ፣ ኢቶፒስ፣ አይቶፒስ... የሚሉ ስሞች ፈጽሞ የአገራችን ንገሥታት ስም ሊሆኑ እንደማይችሉ ነው። ስለ ‘ጠ’ ፊዴል ካነሳን ደግሞ በግሪክ ቋንቋና በሌሎችም የኤውሮጳ ቋንቋዎች ‘ጠ’ የሚል ድምፅ የላቸውምና ‘ጠ’ የሚለውን በ ‘ተ’ እና ‘ፐ’ በሚሉ ፊዴላት ይተኳቸዋል። እንግዲያው ትክክለኛው አባባል ‘ይቶፒስ’ ሳይሆን “ይጦብስ” መሆን ይገባዋል እንላለን። ግሪኮች ‘ጠ’ ማለት ስላልቻሉ ነው () ‘አይትዮፕያ’ ያሉት። እኛም ይኸው እስከ ዛሬ ኤውሮ‘ፓ’ ከማለት ኤውሮ‘ጳ’ እንደሚቀናን ማለት ነው። የውጭ ታሪክ ጸሓፊዎች እነ ዮሴፍ ሃለቪ ()፣ እኖ ሊትማን ()፣ ኤድዋርድ ግላሴር ()፣ ኮንቲ ሮሲኒ ()፣ ጂ. ሪክማንስ () የመሳሰሉትና ሌሎችም የውጭ አገር ሰዎች ያቀረቡት ጽሑፍ ይጦብያ ለማለት ስላልቻሉ ይቶፕያ፣ ኢቶፕያ፣ ሆኖ ወደ ቋንቋችን ሲተረጐም ‘ኢትዮጵያ’ ተብሎ ሊጸና ቻለ እንጂ ይህ ስም ትክክለኛ የአገራችን ይሁን የንጉሦቻችን ስም እንዳልሆነ ግልጽ ነው። በአገራችን ታሪክ የምናገኘው ሓቅ ደግሞ፣ “ይጦብያ”፣ “ይጦብስ” የሚል ስም ለሕዝብና ለአገር ቀርቶ ለተራ ንጉሥም የማይሰጥ እንደ ነበረ ነው። ሕዝቡ ነገደ አግዓዝያን፣ አገሩ ብሔረ አግዓዚ፣ ቋንቋው ልሳነ ግዕዝ ነበር። ነገሥታቱም በየክፍለ-ሃገሩ ስም፤ የትግራይ ንጉሥ፣ የወሎ ንጉሥ፣ የጎጃም ንጉሥ፣ የሸዋ ንጉሥ... ወዘተ፣ ይባሉ ነበር። “ይጦብያ” ተብሎ የሚታወቀው ሁሉን የጠቀለለ ንጉሠ-ነገሥቱ ብቻ ነበር። ይህም የጥንቱን የይጦብስ ንጉሥን ጠቅላይ ስም ወራሽነት መያዙ ለማሳየት ሆን ብሎ የተደረገ ብልሓት ይመስላል። ይጦብስ ማለትስ ምን ማለት ነው? በግዕዝ በትግርኛና በአማርኛም “መጥበስ” የሚል ቃል አለ። ቃሉም ሲራባ፤ ጠበሰ፣ ተጠበሰ፣ ይጠብስ፣ ትጠብስ፣ ጥቡስ፣... ወዘተ፣ እያለ ይራባል። እንግዲያውስ ይጦብስ ማለት ጥንታዊ ትርጉሙ፤ ይጠብሳል፣ ያቃጥላል፣ ኃይለኛ ንጉሥ ነው! ተብሎ ጠላቶችን ለማስፈራሪያ የወጣ ስም ይመስላል እንጂ ከግሪክ ቋንቋ ተወስዶ ለአገራችን ነገሥታት ‘ፊቱ የተጠበሰ፣ በፀሓይ የተቃጠለ’ ተብሎ የተሰጠ ስም ነው ማለት አይቻልም። ይህንን የምንለው ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ከግሪኮች የመጣ ነው ለሚሉት አጉል ምሁራን ስሕተታቸውን ለማሳየት ነው እንጂ፣ በየዘመናቱ ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ልዩ-ልዩ ትርጉሞች እንደ ተሰጡት አይጠረጠርም። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ማለት መልካም መዓዛ ያለው ዕጣን ነው የሚሉ አሉ። የለም፣ ታላቅና ጠቅላይ ማለት ነው የሚሉም አሉ። ከዘመናት ብዛትልዩ-ልዩ ትርጉሞች እንደተሰጡት አያጠራጥርም። የሚደንቀው ነገር ግን መሃነስ/መሃንደስ የሚል ቃል ዓለምን ዞሮ ወደኛ መሃንድስ ሆኖ ሲመለስ ህንፃ የሚለውን ትርጉሙን እንዳልሳተ፣ ‘ይጦብስ’ የሚለውም ቃል እንዲሁ የቃሉ አባባል ትንሽ ተወላግዶ በግሪኮች አነጋገር ‘ይቶፒስ’ ቢባልም የመቃጠልና የመጠበስ ትርጉሙን ሳይስት እንደ ተቀመጠ ለብዙ ዘመናት የቆየ ይመስላል። እዚህ ላይ ‘ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ?’ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። ምናልባት በይጦብስ ዘመን የአገራችን ተጓዦች ወይም ነጋዴዎች ከግሪክ ሰዎች ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ሲገናኙ፤ “እናንተ እነማንናችሁ?”ብለዋቸው ይሆናል። “የይጦብስ ሰዎች ነን”፣ብለው መልሰዋል። “ይጦብስ ማለትስ ምን ማለት ነው?” ብለው ሳይጠይቋቸው አልቀሩም። “የሚያሳርር፣ የሚያቃጥል፣ የሚጠብስ ኃይለኛ!” ማለት ነው ብለው አስረድተዋቸዋል። ከዚያ ወድያ ግሪኮችጠቆር ያለውን ሰው ባዩ ቁጥር () “ይጦብስ” እያሉ መጥራት ጀምረው፣ ቃሉም ወደ ቋንቋቸው ከመግባቱም በላይ፣ “ይጠብስ” የሚለውን ጥንታዊውን ትርጉም ሳይስት ለጥቁር አፍሪካዊ ሁሉ ‘ፊቱ የተጠበሰ፣ በፀሓይ የተቃጠለ’ () ‘ኢትዮጵያ’ የሚል መጠሪያ ለመሆን የበቃ ነው የሚመስል። ምርምራችን በዚህ ያበቃል። ቅድመ ታሪክ ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ የሰው ልጅ ከነበረባችው ቦታዎች አንዷ መሆኗ ትታወቃለች። የሰው ፍልሰት ጥናቶች ፣ የቅሪተ አካል ጥናቶችና ሌሎች የሳይንሳዊ ዘዴዎች ይህን ያረጋግጣሉ። ድንቅነሽ የምትባለው በአፋር ክልል ውስጥ የተገኘችው አጽም በአለም በዕድሜ ሁለተኛ ጥንታዊ ናት። ከ 3.2 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ እንደኖረች ይገመታል። ሌሎችም ታዋቂ አጽሞች በኢትዮጵያ ተገኝተዋል። ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ደሴት በመሆን የቆየች ታላቅ ሀገር ናት። የመጀመሪያዎቹ መንግስታት በ ፰፻ ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። ከአውሮፓ ጋር የታደሰ ግንኙነት በ ፲ ፭ኛው ምዕተ-ዓመት መጀመሪያ ኢትዮጵያ ከአክሱም ጊዜ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአውሮፓ ጋር ግንኙነት ጀመረች። ከእንግሊዝ ንጉሥ ሄነሪ አራተኛ () ወደ የአቢሲኒያ ንጉሠ-ነገሥት የተላከ ደብዳቤ እስከ ዛሬ ድረስ አለ። በ1428 እ.ኤ.አ. አፄ ይስሐቅ ወደ የአራጎን ንጉሥ አልፎንዞ አምስተኛ () ሁለት መልክተኞች ልከው ነበር። ግን የመጀመራያው ያልተቋረጠ ግንኙነት በአፄ ልብነ ድንግል ስር ከፖርቱጋል ጋር ከ1508 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ነው የተካሄደው። ኢትዮጵያ በአህመድ ግራኝ ስትጠቃ ፣ ፖርቱጋል አራት መቶ ወታደሮችና የጦር መሳሪያ በመላክ ኢትዮጵያን ረድታለች። አፄ ሱስንዮስ በፖርቱጋልና እስፓንያ ተጽዕኖ እና ተጨማሪ እርዳታ ከመፈለጋቸው የተነሳ ወደ የሮማ ካቶሊክ ክርስትና ተለወጡ ፤ የኢትዮጵያ ይፋ ሀይማኖትንም አደረገቱት። ይህ ውሳኔ ወደ ግዙፍ ተቃውሞና ጦርነት አመራ። በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ከሞቱ በኋላ ፣ የአፄ ሱስንዮስ ልጅ አፄ ፋሲለደስ በ 1632 እ.ኤ.አ. ኢትዮጵያ ወደ አርቶዶክስ ክርስትና መመለሷን አወጁ። አውሮፓውያኖቹንም ከኢትዮጵያ አስወጡ። ዘመነ መሳፍንት ከ ፲፯፻፶፭ እስከ ፲፰፻፶፭ እ. ኤ. አ. ኢትዮጵያ እንደገና ከአለም ጉዳዮች ተገላ ነበር። ይህ ጊዜ «ዘመነ-መሳፍንት» ይባላል ምክኒያቱም የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥቶች በራስ ሚካኬል ስሁል ፣ ራስ ወልደ ሥላሴ ፣ ራስ ጉግሳ እና በመሳሰሉት ቁጥጥር ስር ነበሩ። ራስ ጉግሳ በ፲፯ኛው ክፍለ ዘመን ጎንደርን በመምራታቸው የቤተ-መንግሥቱን ቋንቋ ከአማርኛ ወደ ኦሮምኛ ለውጠው ነበር። የኢትዮጵያ ግለልኘነት ያበቃው ከእንግሊዝ ጋር ግንኙነት ስትጀምር ነው። ኢትዮጵያ እንደገና የተዋሀደችው እንዲሁም የዘውዱ ስልጣን የተጠናከረው በ ፲፰፻፶፭ እ. ኤ. አ. በአፄ ቴዎድሮስ ምክኒያት ነው። የሰሜን አሮሞዎችና ትግሬዎች አመፅና የግብፆች ተደጋጋሚ ድንበር መጣስ የአፄ ቴዎድሮስ ስልጣን እንዲዳከም አደረጉት። በመጨረሻም ከእንግሊዝ ጋር በነበረው ጦርነት እስረኛ አልሆንም ብለው አፄ ቴዎድሮስ እራሳቸውን አጠፉ። በ ፲፰፻፷፰ እ. ኤ. አ. ኢትዮጵያና ግብፅ ጉራ በሚባለው ቦታ ተዋጉ። በአፄ ዮሐንስ አራተኛ የተመሩት የሰሜን ኢትዮጵያ ኃይሎች ድል ተቀናጁ። በ ፲፰፻፹፱ እና በ ፲፰፻፺ ዎቹ እ.ኤ.አ. መጀመሪያ ፣ የሸዋ ንጉሥ ሳህለ ሥላሴ ከዚያም ዳግማዊ አፄምኒልክ በራስ ጎበና እርዳታ አማካኝነት ሀገሯን ወደ ደቡብና ምሥራቅ ማስፋፋት ጀመሩ። ከአህመድ ግራኝ ወረራ በኋላ በኢትዮጵያ ቁጥጥር ስር ያልነበሩ ፣ ሌሎች ደግሞ በማንኛው ጊዜ በኢትዮጵይ ቁጥጥር ስር ያልነበሩ ቦታዎች በዳግማዊ አፄ ምኒልክ አገዛዝ ጊዜ በኢትዮጵያ ስር ሆኑ። ከዚህ ጊዜ በኋላ የኢትዮጵያ ድንበር ብዙ አልተለወጠም። ከ ፲፰፻፹፰ እስከ ፲፰፻፺፪ እ. ኤ. አ. ድረስ የነበረው የሰፋ ድርቅ ከኢትዮጵያ ህዝብ በአንድ ሶስተኛ የሚገመተውን ቀጥፎአል። የአውሮፓ ሽሚያ ለአፍሪካ በ ፲፰፻፹ ዎቹ እ. ኤ. አ. የአውሮፓ መንግሥቶች በበርሊን ጉባኤ ተስማምተው አፍሪካን በቅኝ ገዢነት መከፋፈል ጀመሩ። በኢትዮጵያ እና ጣልያን መካከል የነበሩ የዚያ ዘመን ውዝግቦች ወደ አድዋ ጦርነት በ ፲፰፻፹፰ ዓ. ም. አመሩ። በጦርነቱ የጣልያን ትልቅ ዘመናዊ ጦር በኢትዮጵያ ጦር ትልቅ ሽንፈት የደረሰበት መሆኑ ዓለምን አስደነቀ። የአድዋ ጦርነት በካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በአጼ ምኒልክ በተመራው የኢትዮጵያ ሠራዊትና ባህር አቋርጦ ከአውሮፓ ከመጣው የጣሊያን ሠራዊት ጋር የተካሄደው የዓድዋው ጦርነት በታሪክ ውስጥ ከሚጠቀሱ ጉልህ ክስተቶች መካከል አንዱ ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች የዓድዋ ድል ጣሊያን አፍረካ ውስጥ በተለይ ደግሞ በምሥራቁ የአህጉሪቱ አካባቢ ለማስፋፋት አቅዳ የተነሳችለትን የቅኝ ግዛት ዕቅድን ያጨናገፈ ከመሆኑ ባሻገር፤ በዘመኑ የአውሮፓዊያን ሠራዊት በአፍሪካዊያን ካበድ ሽንፈት ሲገጥመው የመጀመሪያ በመሆኑ ድንጋጤንም ፈጥሮ ነበር። ለዓደዋው ጦርነት ዋነኛ ምክንያት የሆነው በኢትዮጵያና በጣሊያን መንግሥታት መካከል የተፈረመው የውጫሌ ውል ነበር። በዚህ ውል አንቀጽ 17 ላይ በጣሊያንኛ የሰፈረው ጽሑፍ ኢትዮጵያ ከአውሮፓ መንግሥታት ጋር ማድረግ የምትፈልገውን ግንኙነት በጣሊያ በኩል መሆን እንዳለበት ሲያመለክት የአማርኛው ግን ግንኙነቱን በኢጣሊያ በኩል ማድረግ ትችላለች ይላል። የአድዋ ማዕከል የአዲስ አበባ እምብርት ላይ ሊሰራ ነው ጣልያን በተሸነፈችበት አድዋ ቆንስላዋን ለምን ከፈተች? መከፋፈል ያጠላበት ጉዞ አድዋ ይህ የትርጉም ልዩነት እንደታወቀ መጀመሪያ ላይ አጼ ምኒልክ የውሉን አንቀጽ አስራ ሰባት እንደማይቀበሉ ካሳወቁ በኋላ ቀጥሎም የውጫሌውን ውል ሙሉውን ውድቅ አደረጉት። ይህም ጣሊያን ጦሯን በማዝመት ወረራ እንድትፈጽም ሊያደርጋት እንደሚችል የተረዱት ንጉሡ ዝግጅት ማድረግ ጀምረው ነበር። የተፈራው አልቀረም የጣሊያን ሠራዊት ለወረራ እንቅስቃሴ ጀመረ። ከኢትዮጵያ በኩል የንጉሡን ጥሪ ተከትሎ ከመላዋ አገሪቱ የተሰባሰበው ሠራዊት አገሩን ከጣሊየን ወረራ ለመከላከል ያለውን መሳሪያ ይዞ ወደ ሰሜን አቀና። በአጼ ምኒልክ የተመራው ሠራዊት እስከ ሃያ ሺህ የሚደርሱ ፈረሰኞችን ጨምሮ ከአንድ መቶ እስከ መቶ ሃያ ሺህ የሚገመት አርበኛ ወደ አድዋ ሲተም መነሻው ከአዲስ አበባ ነበር። ሠራዊቱ ዓድዋ ለመድረስ አንድ ሺህ ኪሎ ሜትር አካባቢ በእግሩና በጋማ ከብት መጓዝ ነበረበት። ሠራዊቱ ዓድዋ ከደረሰ በኋላ ለፍልሚያ አመቺ ጊዜን ሲጠብቅ ቆይቶ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ከ17 ሺህ በላይ ወታደሮችን ካሰለፈው አውሮፓዊ ኃይል ጋር ጦርነት ገጠመ። ጦርነቱ በተጀመረ በግማሽ ቀን ውስጥ የኢትዮጵያ አርበኞች በሁሉም አቅጣጫ በጣሊያን ሠራዊት ላይ በሰነዘሩት ጥቃት ከባድ ጉዳት ስላደረሱበት በአንድ ላይ ተሰልፎ ኢትዮጵያዊያኑን ለመቋቋም ሳይችል ቀረ። በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። በዚህም መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያም ተማርኳል። በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄኔራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄኔራል ባራቴሪ ሸሽቶ አመለጠ። የግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን በ ፳ኛው ምእት ሁለተኛው ሩብ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኢትዮጵያን ከልጅ ኢያሱ በኋላ መምራት ጀመሩ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ለአፍሪካ ሕብረት መቋቋም ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። የኢትዮጵያ ነጻነት በጣልያን ወረራ ከ ፲፱፻፴፮ እስከ ፲፱፻፵፩ እ. ኤ. አ. ድረስ ቢጠቃም በጀግኖችዋ መከታ ተጠብቋል። በአዚህ ጥቃት ጊዜ ዓፄ ኃይለሥላሴ በ ፲፱፻፴፭ እ. ኤ. አ. በሊግ ኦፍ ኔሽንስ () ፊት የሚታወስ ንግግር በአማርኛ አደረጉ። ይህ ንግግር በዓለም ታዋቂ አደረጋቸው። እንዲሁም በ ፲፱፻፴፭ እ.ኤ.አ. በ ታይም () መጽሄት «የዓመቱ ሰው» አስባላቸው። ጣልያን ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ውስጥ መሳተፍ ስትጀምር ፣ እንግሊዝ ከኢትዮጵያዊ ተዋጊዎች ጋር ኢትዮጵያን ነጻ አወጣች። ግን እስከ ፲፱፻፵፫ እ. ኤ. አ. ድረስ አንዳንድ ጣልያኖች በደፈጣ ያለ ስኬት ይዋጉ ነበር። በ ፲፱፻፵፪ እ. ኤ. አ. ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ባርነት እንደ ተከለከለ አወጁ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ጀግና ሆነው ቢታዩም ፣ የ ፲፱፻፸፫ እ.ኤ.አ. ዓለም አቀፍ የነዳጅ ቀውስ ፣ የምግብ ዕጥረትና የድንበር ጦርነቶች ተቃውሞ አስነሱ። ከዚያም በ ፲፱፻፸፬ እ. ኤ. አ. በሶቪየት ሕብረት የተደገፈውና በመንግስቱ ኃይለ ማርያም የተመራው ደርግ (ደርግ ማለት ኮሚቴ ማለት ነው) ዓፄ ኃይለ ሥላሴን ከስልጣን አስወረደ። የተለያዩ መፈንቅለ መንግሥቶች ፣ የሰፋ ድርቀትና ስደተኞች የደርግ ሥርዓት ትልቅ ችግሮች ነበሩ። በ ፲፱፻፸፯ እ. ኤ. አ. ሶማሊያ ኦጋዴንን በመውረሯ የኦጋዴን ጦርነት ተነሳ። በሶቪየት ሕብረት ፣ ኩባ ፣ ደቡብ የመን ፣ ምስራቅ ጀርመንና ሰሜን ኮሪያ የመሳሪያ እርዳታ እንዲሁም ወደ ፲፭ ሺህ በሚቆጠሩ የኩባ ወታደሮች ድጋፍ አማካኝነት ደርግ ኦጋዴንን እንደገና መቆጣጠር ቻለ። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በቀይ ሽብር ፣ የግዴታ ስደት ፣ ወይም ረሀብ ሞተዋል። መንግስቱ ቀይ ሽብር ያካሄደው በተቀዋሚዎች በተፈጸመው ነጭ ሽብር መልስ እንደሆነ ጠቅሷል። በ ፳፻፮ እ. ኤ. አ. መንግስቱ ኃይለ ማርያም በሌሉበት የሞት ቅጣት ተፈርዶባቸዋል። በ ፲፱፻፹ ዎቹ መጀመሪያ የተከሰቱ ድርቀቶች ምክኒያት ስምንት ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ሲራብ ፣ አንድ ሚሊዮን ደግሞ ሞተዋል። ተቃውሞ በትግራይና ኤርትራ ክልሎች ተስፋፋ። በ ፲፱፻፹፱ እ. ኤ. አ. ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ከሌሎች እንቅስቃሴዎች ጋር በመቀናጀት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባርን መሠረተ። የሶቪየት ሕብረትም ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ መቀነስ ጀመረች። የኢኮኖሚ ችግሮች ተከሰቱ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ተዳከመ። በሜይ ፲፱፻፺፩ እ. ኤ. አ. የኢ. ህ. አ. ዴ. ግ. ጦር ወደ አዲስ አበባ አመራ። የመንግስት ኃይሎች ምንም አይነት የውጭ እርዳታ ስላላገኙ ፣ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ.ን ጥቃቶች መቋቋም አልቻሉም። መንግስቱ ኃይለ ማርያም ወደ ዚምባብዌ ሄደው እስከ ዛሬ ድረስ በዛችው ሀገር ይኖራሉ። ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ. ፹ ፯ አባላት ያሉት የሽግግር መንግሥት መሠረተ። በጁን ፲፱፻፺፪ እ. ኤ. አ. የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፣ እንዲሁም በማርች ፲፱፻፺፫ እ. ኤ. አ. የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት የሽግግር መንግሥቱን ለቀው ወጡ። በ ፲፱፻፺፬ እ. ኤ. አ. ሁለት የሕግ አውጪ ምክር ቤቶችንና የፍትሕ ስርዓትን የሚደነግግ አዲስ ሕገ መንግሥት ተፃፈ። የመጀመሪያው ምርጫ በሜይ ፲፱፻፺፭ እ.ኤ.አ. ተካሄደ። አቶ መለስ ዜናዊ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። በቅርብ ጊዜ በየተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ ኢትዮጵያና ኤርትራ በፌደሬሽን ተዋህደው ነበር። በ ፲፱፻፺፫ እ.ኤ.አ. በተካሄደውና የተባበሩት መንግሥታት በታዘበው ሕዝበ ድምፅ ፣ በወቅቱ ስልጣንን በጠመንጃ አፈሙዝ የያዙትና የኤርትራን መገንጠል በሚፈልጉት በህውአትና ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ አማካይነት ለኤርትራ ህዝብ ‹ባርነት› ወይንስ ‹ነፃነት› ተብሎ እንዲመርጡ ተገደው ማንም ባርነትን የሚመርጥ የለምና ነፃነትን መረጡ ተባሎ በረሃ ገብተው ሲታገሉለት የነበረውን አላማ ስልጣናቸውን በመጠቀም አስፈፅመው ከ ፺፱ ከመቶ በላይ የሚሆነው የኤርትራ ሕዝብና በውጭ ሀገር የነበሩ ኤርትራውያን ከኢትዮጵያ መገንጠልን መርጠዋል። በሜይ ፳፬ ፣ ፲፱፻፺፫ እ. ኤ. አ. ኤርትራ ከኢትዮጵያ ነፃነቷን አወጀች። በሜይ ፲፱፻፺፰ እ. ኤ. አ. የድንበር ውዝግብ እስከ ጁን ፳፻ እ. ኤ. አ. ወደ ቀጠለው የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አምርቶአል። ይህ ጦርነት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚን ጎድቶአል። በሜይ ፲፭ ፣ ፳፻፭ እ.ኤ.አ. አጠቃላይ ምርጫ ቢካሄድም ተቃዋሚዎች ማጭበርበር እንደነበረ ወንጅለዋል። በአጠቃላይ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከ ፪፻ በላይ የፓርላማ መቀመጫዎችን አሸንፈዋል። ግን አንዳንድ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አባሎች ከምርጫው በኋላ ከነበረው ረብሻ ጋር በተያያዘ ታስረው ነበር። በአሁኑ ጊዜ ያለው የፖለቲካ ስርአት በብሄር ላይ የተመሰረተ ፌደራላዊ ስርአት ነው፡፡ ኢትዮጵያ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ከ 3-14 ዲግሪ ሰሜን እና ከ 33-48 ዲግሪ ምሥራቅ የምትገኝ አገር ስትሆን የቆዳ ስፋቱዋም 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ. ነው። በሰሜን ከኤርትራ ፣ በምዕራብ ከሱዳንና ደቡብ ሱዳን ፣ በደቡብ ከኬኒያ ፣ እንዲሁም በምሥራቅ ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ ጋር ትዋሰናለች። የኢትዮጵያ አብዛኛው ግዛት በተራሮች እና አንባዎች የተሞላ ሲሆን ፣ ታላቁ የምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ እነዚህኑ ከፍተኛ ቦታዎች ከሰሜን ምሥራቅ ወደ ደቡብ ምዕራብ በመጋደም ለሁለት ይከፍላቸዋል። በስምጥ ሸለቆው ዙሪያም በረሃማ የሆኑ ዝቅተኛ ቦታዎች ይገኛሉ። ይሄን መሰሉ የመልክዓ-ምድር ልዩነት አገሪቷ የተለያዩ የአየር ንብረት ፣ የአፈር ፣ የዕፅዋት እና የሕዝብ አሰፋፈር ገጽታዎች እንዲኖሯት አስችሏታል። በከፍታና በመልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ የተነሣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ዓይነት የአየር-፡ ንብረት ክልሎች ይገኛሉ። እነሱም፦ ደጋ – ከፍታቸው ከባሕር ጠለል 2400 ሜትር የሚጀምር እና የሙቀት መጠናቸው ከ 16 ዲግሪ ሴ. ግ. የማይበልጥ ወይናደጋ – ከፍታቸው ከባሐር ጠለል ከ 1500 እስከ 2400 ሜትር ፣ ሙቀታቸውም ከ 16 ዲግሪ ሴ. ግ. እስከ 30 ዲግሪ ሴ. ግ. የሚደርስ ፣ እና ቆላ – ከባህር ጠለል በታች ጀምሮ እስከ 1500 ሜትር ከፍታ ያላቸው ፣ የሙቀት መጠናቸውም ከ 30 ዲግሪ ሴ. ግ. እስከ 50 ዲግሪ ሴ. ግ. የሚደርስ አካባቢዎች ናቸው። ዋናው የዝናብ ወቅት ከሰኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን ፣ ከሱ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚጥል የበልግ ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው። አስተዳደራዊ ክልሎች ከ ፲፱፻፺፮ እ.ኤ.አ. በፊት ኢትዮጵያ በ ፲፬ ክልሎች ተከፍላ ነበር። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጽያ ውስጥ ፱ አስተዳደራዊ ክልሎች ይገኛሉ። አወቃቀራቸውም በህገ-መንግስቱ በተደነገገው መሰረት «በህዝብ አሰፋፈር ፤ ቋንቋ ማንነት እና ፈቃድ ላይ» ተመስርቶ ሲሆን ክልሎቹም፦ የትግራይ ክልል የአፋር ክልል የአማራ ክልል የኦሮሚያ ክልል የሶማሌ ክልል የቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል 8. የጋምቤላ ሕዝቦች ክልል የሐረሪ ሕዝብ ክልል የሲዳማ ሕዝቦች ክልል ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሲሆኑ በተጨማሪም አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ እራሳቸውን የቻሉ የአስተዳደር አካባቢዎች ሆነው ተዋቅረዋል። ዋና ሰሪ ምዕራፍ ሰሎሞን አስተደዳራዊ ክልሎች የኢትዮጵያ ሕዘብ ቁጥር ከ ፼፼ በላይ ሲሆን እንዲሁም ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ ፣ቀቤንኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። እንደ ወላይትኛ ፣ [[ጋሞኛ]፣ ጎፍኛ ፣ ከፋኛ ፣ ሃመርኛ የመሳሰሉት የኦሞአዊ ቋንቋ ዘሮች ሲሆኑ አማርኛ ፣ ትግርኛ ፣ ጉራጊኛ ፣ ስልጢኛ ፣ ሀደሪኛ፣ አርጎብኛ፣ ጎፍኛ እና መሰል ቋንቋዎች ከሴማዊ ቋንቋዎች ይመደባሉ። ዘጋቢ በአወል ሙሀመድ ደራ የሴሚቲክ ምንጭ ያላቸው እንደ ትግርኛና አማርኛ ያሉት ቋንቋዎች የራሱ የሆነ የተለየ የፊደል ስርአት ያላቸው ሲሆን ይህም ኢትዮጵያን ከአፍሪቃ ብቸኛዋ ባለ ጥንት ፊደል ሀገር ያደርጋታል። እነኚህ የሴሚቲክ ምንጭ ያላችው ቋንቋዎች ግዕዝ የተባለ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስትያን ውጭ ለዕለት ተዕለት ግልጋሎት ላይ የማይውል ግንድ ዘር አላቸው። በኣሁኑ ጊዜ ግዕዝ በዩኒኮድ ዕውቅና ያገኙትን የቢለን፣ ቤንች፣ ምኢን፣ ሙርሲ፣ ሱሪ፣ ትግረ፣ ትግርኛ፣ ኣገው፣ ኣውንጂ፣ ኦሮሚፋ፣ ዓማርኛ፣ ዲዚ፣ ዳውሮ፣ ጉሙዝ፣ ጉራጌ፣ ጋሞ ጎፋ እና ግዕዝ ቋንቋዎች የሚጋሯቸውን ቀለሞችና ሌሎች ያጠቃልላል። በፊደሉ ከሚጠቀሙ ቋንቋዎች መካከል ሓረሪ ኣንዱ ነው። መጽሓፍ ቅዱስ ሙሉዉን ወይም በከፊል ከ፲፭፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ በግዕዝ ቀለሞች በማተሚያ ቤቶች ከታተሙባቸው ቋንቋዎች መካከል ሃዲያ፣ ሲዳሞ፣ ከምባታ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ እና ጌዴኦ ይገኙበታል። (ደግሞ ኣበራ ሞላ ይዩ።) በእጅ ጽሑፍና ማተሚያ ቤቶች ብቻ ይቀርብ የነበረው የግዕዝ ፊደል በ፲፱፻፹ ገደማ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ ኣጠቃቀሙ ወደ ኮምፕዩተር ዞሯል። ከእዚያም ወዲህ ፊደሉ የዩኒኮድ የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ ስለገባ እያንዳንዱ ቀለም የእራሱ ስፍራ ኣለው። ይህ የኣማርኛ ውክፔድያ ድረገጽም የቀረበው በእዚሁ ፊደል ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህም ፊደሉን በእጅ ስልክ መጠቀም ተችሏል። ለፊደሉ ኣጠቃቀም ኣስፈላጊ ሆነው የተፈጠሩ ኣዳዲስ የቴክኖሎጂ ዘዴዎችም የዩናይትድ እስቴትስ የባለቤትነት መታወቂያ ወይንም ፓተንት ማግኘት ጀምረዋል። ባህል እና ሃይማኖት የውጭ መያያዣዎች
49612
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%88%98%E1%88%AD%E1%89%86%E1%88%AC%E1%8B%8E%E1%88%B5
ቅዱስ መርቆሬዎስ
የመጀመሪያ ስሙ ፒሉፖዴር ይባል የነበር ሲሆን ትርጔሜውም የአብ ወዳጅ ማለት ነው፤በሁለተኛው ትርጓሜ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው። የክርስትና ስሙ መርቆሬዎስ ሙያውም ውትድርና ዜግነቱም ሮማዊ ነው ። ይህ ታማኝ ምስክርነት የሰጠ ሰማዕት ወላጆቹ ጣዖት የሚያመልኩ አረማውያን ነበሩ።ከጊዜ ወደ ጊዜ የክርስትና እምነት እየተስፋፋ ስለ ሄደ ቤተሰቦቹም ክርስቲያኖች ሆነዋል። እሱም ካደገ በኋላ ተምሮና አምኖ ተጠመቀ ስመ ጥምቀቱም መርቆሬዎስ ተባለ ። ጥንተ ነገሩ አባትና አያቱ ጣኦት በማምለክ ሲኖሩ ከእለታት በአንዲቱ እለት ለአደን ቢወጡ ገጸ ከለባት መጥተው የመርቆሬዎስን አያት ሲበሉ አባቱን ግን መልአከ እግዚአብሔር ታድጎታል ምክንያቱም ከሱ ባህርይ የሚወለድ ማር መርቆሬዎስ አለና። ከዚህም በኋላ እናቱና አባቱ የክርስትና ጥምቀትን ተጠምቀው ክርስቲያኖች ሆኑ በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ ተወለደና ስሙ ፒሉፓዴር ተባለ፡፡ እነዚያን ገጸ ከለባትም እግዚአብሔር ባህርያቸውን ገራም አድርጎላቸው የመርቆሬዎስ አባት አገልጋይ ሆነዋል። ኋላም ንጉሱ የገጸ ከለባቱን ኃይል ተመልክቶ የመርቆሬዎስን አባት የጦር አለቃ አድርጎታል፤ ገጸ ከለባቱም በጦርነት ጊዜ የቀደመ ባህርያቸው እየተመለሰ የመርቆሬዎስን አባት ይረዱት ነበር ማንምም አይችላቸውም ነበር። በአንድ ጦርነት ግን የቅዱስ መርቆሬዎስ አባት በእግዚአብሔር ፈቃድ በጦርነት ተማርኮ በሌላ ንጉስ እጅ ገባ ይህንን የሰማው ንጉስ የመርቆሬዎስን እናት አገባለው በማለቱ የመርቆሬዎስ እናትና ብጹእ መርቆሬዎስ ወደ ሌላ አገር ተሰደዱ። የመርቆሬዎስ አባት ግን በተማረከበት ንጉስ ዘንድ ክርስቲያን መሆኑ ሲሰማ ተወዳጅነትን አግኝቶ ሹመትን አገኘ ኋላም ከብጹእ መርቆሬዎስና ከእናቱ ጋር በእግዚአብሔር ቸርነት ተገናኙና በአንድነት ኖሩ። የመርቆሬዎስ እናትና አባትም በአረፉ ጊዜ መርቆሬዎስ የአባቱን ሹመት ተቀብሎ በመርዶሳውያን አገር ላይ ተሾመ። ያ ገጸ ከልብም ከእርሱ ጋር ነበርና በውጊያ ጊዜ ማንም ሊቋቋመው አይችልም ነበር። የበርበር ሰዎችም በዳኬዎስ ንጉስ ላይ በተነሱ ጊዜ ንጉሱ ፈራ መርቆሬዎስም እግዚአብሔር ያጠፋቸው ዘንድ በእጃችንም አሳልፎ ሊሰጣቸው አለውና አትፍራ አለው። ከዚህም በኋላም የእግዚአብሔር መላእክ በውጊያ ውስጥ የተሳለ ሰይፍ ሰጥቶት ጠላቶቹን ድል አደረገ። ሰነፍ የሆነ ዳኬዎስ ግን ከጦርነቱ በኋላም ድልን የሰጡህ ጣኦቶቼ ናቸውና ለአማልክት ሠዋ አለው። መርቆሬዎስ ግን ትጥቁንና ልብሱን ወረወረለትና ንጉሱን እንዲህ አለው። እኔ ክብር ይግባውና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም ለረከሱ ጣኦታትም አልሰግድም። ከዚህ በኋላም ሰነፉ ዳዴዎስ ተቆጥቶ በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃየው። በሽመል የሚደበድቡት ጊዜ አለ፣ በቆዳ ጅራፍም የገረፉትም ጊዜ ነበር። ከሁሉ በላይ ግን ከታች እሳት አንድደው በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ቢገርፉት ደሙ ተንጠባጥቦ እሳቱን አጠፋው። እንዲህ ባለ ስቃይ ለ፭ ዓመታት ተሰቃይቶ መጨረሻ ላይ ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ተጋድሎውን ፈጽሞ በመንግስተ ሰማያት የሕይወት አክሊልን ተቀበለ። ካልዕ ሊቀ ሰማዕትም ተባለ። ከእረፍቱ በኋላም ክርስቲያኖችን ይገድል፣ያሰቃይ የነበረውን፣ በጌታችን በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይም የስድብን ቃል የተናገረውን ኡልያኖስን ተበቅሎ የገደለ፤ ቅዱስ ባስልዮስንና ቅዱስ ጎርጎርዮስን የረዳቸው እርሱ ተአምረኛው ድንቅ አድራጊው መርቆሬዎስ ነው። ለምን መከራን ተቀበለ? 1 ስለመንግስተ ሰማያት ሐዋ14÷22 2 ሃይማኖትን ለመመስከር ማቴ10÷32 3 አርአያ ለመሆን 4 እውነትን በሐሰት መለወጥ ስላልፈለገ 2ተኛ ቆሮ 5÷13 ስለመርቆሬዎስ በአጭሩ መርቆሬዎስም ማለት የእየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ሲሆን ይህም ቋሚ መጠርያ ስሙ ሆኖ ቀረ ። በእንግሊዞች የተጻፈው ገድለ ቅዱሳን ባዮግራፊ ኦፍ ሴንትስ እንደሚለው ዜግነቱ ኢጣሊያዊ ሲሆን ስሙንም መርኮርዮ ብሎታል የእባቱንም ስም ሎሪዮ የእናቱንም ስም ክርስቲና እንደሆነ ገልጿል ። በያመቱ ኅዳር ፳፭ ቀን የሚነበበው መጽሐፈ ስንክሳር ደግሞ የአባቱን ስም ኖኅ የናቱን ስም ታቦት የራሱንም ስም መርቆሬዮስ እንደሆነ ይገልጻል ። በዚያም ዘመን ውትድርና የተወደደና የተከበረ ሙያ ስለነበር መርቆሬዎስም ዳክዮስ ለተባለ ንጉሥ ወታደር ሆነ ዕለት ከዕለት የሚያሳየው ወታደራዊ ሥነ ሥርዓትና በሚፈጽመው ጀብዱ ከሌሎች ወታደሮች ይልቅ ተወዳጅነትና ባለሟልነት አገኘ ፤ ዳክዮስ ጠላቱን ድል አድርጎ በተመለሰ ቁጥር ድል ያስገኘለትን እግዚአብሔርን ዘንግቶ ድል የሚያስገኝለት ጣዖት እየመሰለው ከጦርነት ሲመለስ ለጣዖት መሥዋዕት የማቅረብ ልማድ ነበረው ከዕለታት አንድ ቀን ዳክዮስ መርቆርዮስን አስከትሎ ዘመተና ጠላቱን ድል አድርጎ በተመለሰ ጊዜ እንደ ልማዱ ለማይሰማውና ለማይናገረው ጣዖት ከስግደትና ከጸሎት ጋር የምስጋና መሥዋት አቀረበ ከደስታው ብዛት የተነሣ ብዙ እንሰሳት በየዓይነቱ እየመረጠ ሠዋ። ሰማዕት የሆነበት ምክኒያት ቅዱስ መርቆሬዎስም ይህን በማየቱ ሰው ድል ለሰጠው ለእግዚአብሔር በመስገድና እሱንም በማመስገን ፈንታ እንዴት ሰው ለሠራው ጣዖት ይሰግዳል ? በማለት ቅር ስላለውና አረማዊነቱንም በግልጽ ስላወቀ በዚህ ተቀይሞ ወደተዘጋጀው የድል ግብዣ ሳይሄድ ቀረ በዚሁ ጊዜ አብረው የዘመቱ ሌሎች የሠራዊቱ አባሎች እኛ ለምታመልከው ጣዖት ስንሰግድና ባደረከው ታላቅ ግብዣ ትእዛዝህን አክብረን ስንገኝ ታማኝ ባለሟልህ መርቆርዎስ ትእዛዝህን በመናቅና አንተን ባለማክበር እነሆ አልተገኘም እንዲያውም ለጣዖትህ መስገድ የማይፈልግ ሳይሆን አይቀርም አስተያየት ስጥበት ብለው በንጉሡ መሾምና መወደድ የሚፈልጉ ሰዎች አሳጡት። ዳክዮስም በመርቆሬዎስ ላይ የቀረበውን ክስ ካዳመጠ በኋላ መርቆርዎስን አስጠርቶ ስለምን ለጣዖት እንዳልሰገደና መሥዋዕት እንዳላቀረበ እንዲሁም ወደ ግብር እንዳልመጣ ጠየቀው ። እሱም ሳይፈራ በድፍረት እንኳንስ እኔ ለጣዖትህ ልሰግድና መሥዋዕት ላቀርብ አንተም እንዲህ በማድረግህ አዝናለሁ ብሎ መለሰለት ፤ ነገር ግን እኔ እግዚአብሔርን አመልካለሁ ፤ ለሱም እሰግዳለሁ ይኸው መሣሪያህንና ትጥቅህን ተረከበኝ ብሎ አውልቆ ወረወረለት።ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ መስቀል መሸከሙንና ወንጌል ይዞ የክርስቶስ ወታደርነቱን በመግለጹ ዳክዮስ በጣም ተናደደ በግርፋትና በእስራት እንዲያሰቃዩትም አዘዘ ። በእስር ቤት ሲሰቃይ ሳለ የሮም ዜጋ ሆኖ በመታሰሩና በመሰቃየቱ የሮም ዜጋ መታሰሩንና መሰቃየቱን ያወቁ መገረፉንም የሰሙ እንደሆነ ሮማውያን ታላቅ ኃይል ያስከትሉብናል የሚነሣውንም ዐመፅ ለመቋቋም ስለማይቻል ግዛታችን ሰፊ ነውና በጽኑ እስራትና በግዞት እንዲሰቃይ ወደ ቂሣርያ እንላከው ሲሉ ተማከሩ ። ዳክዮስና አማካሪዎቹ በዚሁ በመስማማታቸው ታማኙ ሰማዕት ወደዚችው አገር ተላከ ቂሣርያም የምትገኘው በምድረእስራኤል ነው ። ማርቆሬዎስ በቄሣሪያ በቂሣርያም እስር ቤት ስቃዩንና መከራውን ተቋቋመ ወንጌል እየሰበከና እስረኞችን ከአረማዊነት ወደ ክርስትና እምነት እየለወጠ ስላስቸገራቸው ኅዳር ፳፭ ቀን ፫፻፲ ዓ/ም በሰይፍ ተከልሎ በሰማዕትነት ዐረፈ። እንደ ቅዱስ መርቆሬዎስ ስለ ታማኝ ምስክር ዮሐንስ በራእዩ በም:፫፥፲፪ እንዲህ ሲል ጽፎታል፡ "ድል የነሣውን በአምላኬ መቅደስ ዐምድ እንዲሆን አደርገዋለሁ ፤ ወደፊትም ከዚያ ከቶ አይወጣም የአምላኬን ከተማ ስም ማለት ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን አዲሲቱን ኢየሩሳሌም አዲሲቱን ስሜን በእርሱ ላይ እጽፋለሁ..."ብሏል።እርግጥም ቅዱስ መርቆሬዎስ ወደ አዲሲቱ ከተማ ወደ ኢየሩሳሌም ገብቷል።
9831
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%88%E1%8C%A5%20%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%8C%8A%E1%8B%AE%E1%88%AD%E1%8C%8A%E1%88%B5
የለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ
የለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፤ በከሰም ወረዳ ውስጥ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ነው። ማረጋገጫ ጽሑፍ ባይገኝም፤ አፈ ታሪኩ፣ የጊዮርጊስ ታቦት በቡልጋ የለጥ የተተከለው በዓጼ ዮሐንስ ዘመን ነው ይላል። እስከ ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. ድረስ የቤተ ክርስቲያኑ ሕንጻ ክብ የሳር ክዳን ሕንጻ እንደነበር ይነገራል። እስከ እዚያም ዘመን የሰማእቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦት ከድንግል ማርያም፣ ቅዱስ ፋሲለደስ እና መድሃኔ ዓለም ታቦታት ሌላ 13 ታቦታት እዚያው እሳር ክዳን ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ እንደነበሩ ይነገራል። በ ፲፱፻፵፫ ዓ.ም ንቦች ጣሪያው ውስጥ ሰፍረው ኖሮ ከሳር ክዳኑ ውስጥ ሲገቡ ሲወጡ ይታዩ ነበር። የጊዜውም ካህናት በምስጢር ይሸራረሩኩና ማሩን በድብቅ ለመቁረጥ ይስማማሉ፣ ከዕለታት አንድ ቀን በምሽት ፍም ይዘው ሳር ክዳኑ ላይ ይወጡና ማሩን ቆርጠው ይወርዳሉ፣ ያልተገነዘቡት ግን ፍሙ ለካ እጣራው ወራጅ ላይ ወድቆ ኖሮ አንድ ሳምንት ሙሉ ካፈጋ በኋላ ተያይዞ ቤተ ክርስቲያኑን ያቃጥለዋል። ቤቱ ሲቃጠል የዋንዛ ዋልታው እመንበሩ ላይ ይወድቃና ታቦቱን ሸፍኖ ቀብሮ ያድነዋል። በየለጥ አካባቢ ሀዘንና ትካዜ ሰፈረ፣ ሕዝቡ ታቦታቱን ሲፈልግ ሰንብቶ በዚያ ጊዜ ከነበሩት አሥራ ሰባት ታቦታት ውስጥ የጊዮርጊስ ታቦትና የማሪያም፣ የመድሃኔዓለም፤ የፋሲለደስ ታቦታት ብቻ ሳይቃጠሉ ድነው ተገኙ ይላሉ ቄስ ሰርጸወልድ ተሰማ። ይኸኔ ልዩ ስሟ ቡሄ አምባ በምትባለው የየለጥ መንደር በ ፲፱፻፯ ዓ.ም ተወልደው በአምስቱ የኢጣሊያ ዘመን በአርበኝነት ተሰማርተው ሀገራቸውን ያገለገሉት ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን ቤተ ክርስቲያኑን እንዲያሰሩላቸው ጠይቀዋቸው ደጃዝማች ኪዳኔም ቤተ ክርስቲያኑን አሰርተው ከጨረሱ በኋላ ሕንጻው አሰራሩ ቅሬታ ስላሰማቸው አስፈርሰው እንደገና አሰርተው ታቦቱን ሚያዝያ ፳፫ ቀን ፲፱፻፵፱) ዓ.ም አዲሱ ቤተ ክርስቲያን ሊያስገቡ ቻሉ። ይኼ ቤተ ክርስቲያን በዘማናዊ መልክ በአራት ማእዘን ተሰርቶ በአካባቢው ቡልጋ ውስጥ በቆርቆሮ የተሰራ የመጀመሪያው ሕንጻ ነበር። በ ፲፱፻፺፭ ዓ.ም ለሚያዝያ ጊዮርጊስ በዓል በተደረገው የሕንጻ ምርመራ ቤተ ክርስቲያኑ አርጅቶ ተሰናጣጥቆ፣ ተበላሽቶ ስለነበር ሕንጻውን አፍርሶ እንደገና በዘማናዊ መልክ ለማሠራት ተወሰነ። ለዚኽም ሥራ:- (ሀ) ገበሬው አሸዋ ከከሰም ወንዝና ከአማሪት ወንዝ፤ ድንጋይ ከልዩ ስሙ በር ከሚባለው ሠፈር ፈንቅለው በሰው ትከሻና በአህያ ሸክም (ለ) ሲሚንቶ፤ የሕንጻ ብረት፤ ግንበኞችና ሌላም የሕንጻ ሥራ ባለሙያዎች ከአዲስ አበባ እስከ ሐሙስ ገበያ (አንዳንዴም እስከ ኮረማሽ) ድረስ በጭነት መኪና ተጉዞ ከዚያ በታች በሰው ሸክምና በአህያ ጭነት እስከ ቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ይቀርባል። (ሐ) በዚህ ቆላ አካባቢ የውሐ እጥረት ስላለ ከቤተ ክርስቲያኑ በላይ አንድ ኪሎሜትር ርቀት ያለው ምንጭ ተገኝቶ ሦሥት ሜትር ተኩል በሁለት ሜትር ስፋት እና የ ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው ማቆሪያ ከተገነባ በኋላ የተጠራቀመውን ውሐ በ ፔትሮል ፐምፕ እየተሳበ በላስቲክ ቧንቧ ቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ድረስ ገብቶ ለሥራው አገልግሏል። አዲሱ ቤተ ክርስቲያን ባለ ስምንት ማእዘን ሕንጻ ሲሆን፤ የመሬቱን ገደላማነት በመጠቀም ግምጃ ቤትና ቢሮ የሚሆን ምድር ቤት ተሠርቶለታል። ሕንጻው ሙሉ በሙሉ በድንጋይ የተገነባ ሲሆን፤ ጣራውን በዘመናዊ ሸክላ መሰል ቆርቆሮ ተደፍኗል። ከአካባቢውም ጋር በቀለም እንዲዋሃድ አረንጓዴ ቀለም ተመርጧል። ደጃዝማች ኪዳኔ ያሠሩት ቤተ ክርስቲያን ተገጥመው የነበሩት የሙገሬ ጽድ መዝጊያና መስኮቶች ከታደሱ በኋላ አዲሱ ቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ተመልሰው ሊገጠሙ ችለዋል። ሥራው በሁለት ዓመት ተኩል ተጠናቆ ቅዳሜ ጥቅምት ፳፫ ቀን ፳፻ ዓ.ም ታቦታቱን አዲሱ ቤተ ክርስቲያን አስገብተናል። በዚህም ዕለት ጸበሉን አስባረክን። ኢትዮጵያዊ የገጠር ሕዝብ በአንድነት የጋራ ኃይማኖቱን፤ ባህሉንም ሆነ ሰብዓዊ ሕይወቱን የሚኖረው በኃይማኖቱ ማስተናገጃ ቤት ነው። እነሆ በጋራ የዚህን ገጠር ሕዝብ "የለጤ" እና ሕዝበ ክርስቲያን አስብሎ የሚያስጠራውን የየለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በቅድሚያ ተሠርቶለታል፤ ከዚህ በኋል ትምህርት ቤት፤ ክሊኒክ፤ ወዘተ. ሊከተል ይችላል። ይኼንንና የመሳሰሉትንም ተግባራት ለማስፈጸም እግዚአብሔር ፈቃዱ ይኹን። አብያተ ክርስቲያናት
2818
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B4%E1%8B%B2%20%E1%8A%A0%E1%8D%8D%E1%88%AE
ቴዲ አፍሮ
ቴዲ አፍሮ () ዕውነተኛ ስሙ: ቴዎድሮስ ካሳሁን ሲሆን ከዘመናችን ወጣት ኢትዮጵያውያን ዘፋኞችና አቀንቃኞች ሁሉ እጅግ ዝነኛ ነው። ቴዲ ለጃማይካዊው ሬጌ ኮከብ ቦብ ማርሊ የዘፈነለት የሬጌ ሙዚቃው በዓለም ዙሪያ እንዲታወቅ ያደረገው ሲሆን በተለይ ለኃይሌ ገብረ ሥላሴ ና ለሌላኛው የኦሊምፒክ ጀግና ቀነኒሳ በቀለ በኦሊምፒክስ ካሸነፉ በኋላ ያወጣቸው ወቅታዊ አልቡሞቹ ይበልጥ ታዋቂ አርገውታል። ቴዲ አፍሮን በጣም ታዋቂ ያደረግው 'ያስተሰርያል' የተባለው አልበሙ ሲሆን ስለ ፍቅር ፣ መቻቻል ፣ ህዝብ ስሜት እንዲሁም ስለመንግስታት እና ስለ ተቃዋሚዎች በፍቅር ለሃገር እድገት መስራት ዘፍኖአል። ዘፈኖቹ ብስል እና ጠንካራ ናቸው። ቴዎድሮስ ካሳሁን ከድምፃዊነትም በተረፈ የግጥምና ዜማም ደራሲ ሲሆን ከራሱ ስራዎች በተጨማሪ ለተለያዩ ድምፃዊያን የግጥም እና ዜማ ድረሰቶችን አበርክቷል። ቴዎድሮስ ካሳሁን ሐምሌ 7 1968 በአዲስ አበባ ተወለደ። የትምህርት ደረጃ 12+ ቴዎድሮስ ካሳሁን ለምን "ቴዲ አፍሮ" ተባለ? ቴዲ አፍሮ የ፲፪ ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ሰፊ ጊዜ ሥለነበረው ከመቸውም በተለየ ሁኔታ በዚያን ጊዜ ነበር በእግር በፈረስ ሥለ ሙዚቃ መጋለብ እና መሮጥ የጀመረው። ፲፱፻፺፩ አመተ ምህረት አካባቢ ከ ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ተመርቀው የወጡ ባለሙያዎች ላስታስ የተባለ የሙዚቃ ባንድ አቋቁመው ነበር:: በዚያን ጊዜ ቴዲ የራሱ የሆነ ባንድ እንዲኖረው ይፈልግ ሥለነበር ከሙያ ጉዋደኞቹ ጋር መመሆን በወቅቱ የነበሩትን ጥሩ ጥሩ የሙዚቃ መሳሪያዎች በመግዛት ላስታስ ከተባለው የሙዚቃ ባንድ ጋር አብሮ ለመሠራት ያላቸዉን ፍላጎት ለባንዱ አባላት ይገልፃሉ:: የባንዱ አባላትም በደስታ ይቀበሉዋቸዋል:: ብዙም ሳይቆዩ የባንዱ ስያሜ ከላስታስ ወደ አፍሮ ሳዉንድ ቀየሩት:: ባንዱንም በበላይነት በመቆጣጠር እና በመምራት ቴዲ ትልቅ ድርሻና ሃላፊነት ነበረው:: መሳሪያ ተጫዋቾቹ እንደሚሉት ከሆነ፣ ቴዎድሮስ ካሳሁን ፣ ሽዋንዳኝ ሃይሉ እና ግሩም መዝሙር የአፍሮ ሳውንድ ባለቤቶች ተብለው የሚጠቀሱ ሲሆን "ቴዲ ግን እንደ ባንዱ ባለቤት ብቻ ሣይሆን እንደ ቅርብ ጏደኛችን ነበር የምናየው" ይሉታል። እንግዲህ በዚሕ ጊዜ ነበር ቴዎድሮስ ካሣሁን የሚለው ስሙ በቴዲ አፍሮ ተተክቶ ዋነኛ መጠሪያ ስሙ ለመሆን የበቃው። መኪና አደጋ በመኪና አደጋ ሰው ገድሎ በማምለጥ ወንጀል ተከሶ የነበረ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት 6 ዐመት አና 18000 ብር አንዲከፍል ከተወሰነበት በኋላ በእስር ቤት ውስጥ ለ 1 አመት ያህል ቆይቷል። ከዚያም በተለያዩ ምክንያቶች (ይቅርታን ይጨምራል) ከእስር እንዲፈታ ተወስኖለታል። የፍርዱ ሁኔታ ፍርዱ ብዙውን ህዝብ አላሳመነም። ህዝቡ በተለያዩ አጋጣሚዎች የቴዲን መፈታት አስመልክቶ ጩሀቱን አሰምቶአል። የፍርድ ሂደቱ ግልጽ አልነበረም ከ ወንጀል ክስነት ይልቅ የፖለቲካ ትርጉም የያዘ ነበር። እና ሌሎችም ተቃውሞዎች በተለያዩ ጊዜያት ከህዝቡ ተሰምተዋል። ሲገጭ አይቻለሁ ብሎ የመሰከረበት ይርዳው ጤናው ነው። እስከማለት ነበር የህዝቡ ተቃውሞ። የተሰኘ ቻናሌ ላይ ገብታችሁ ሙሉ መረጃውን ማግኘት ትችላላችሁ ከእስር በኋላ ተዲ አፍሮ ከ እስር ከተፈታ በኋላ በተለያዩ ቦታዎች ትሪቶቹን አቅርቧል። በቀጣይም ሊያቀርባቸው ያሰባቸው ኮንሰርቶች እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል። አለምአቀፍ ስኬት ኢትዮጵያ የተሰኘው አልበሙ በ2009 ዓ.ም ለህዝብ በቀረበበት ወቅት በቢልቦርድ የአለም አቀፍ የሙዚቃ ሰንጠረዥ ላይ የአንደኛነት ደረጃን ተጎናፅፎ ነበር። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት [ባራክ ኦባማ] በየአመቱ ይፋ በሚያደርጉት የሙዚቃ ዝርዝር ውስጥም የቴዲ አፍሮ [አርማሽ ] የተሰኘውን ዜማ በ2021 እ.ኤአ ዝርዝር ውስጥ አካተው ነበር። አቡጊዳ (2001 እ.ኤ.አ.) ታሪክ ተሰራ (2004 እ.ኤ.አ.) ያስተሰርያል (፲፱፻፺፯ ዓ.ም.) ጥቁር ሰው (፳፻፬ ዓ.ም.) ኢትዮጵያ (2009 ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ዘፋኞች
3398
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%B2%E1%89%A2%E1%88%8A%E1%8A%95%20%E1%88%98%E1%8C%BB%E1%88%95%E1%8D%8D%E1%89%B5
የሲቢሊን መጻሕፍት
የሲቢሊን መጻሕፍት በግሪክ የተጻፉ የትንቢት ግጥሞች ክምችት ነበሩ። በአፈ ታሪክ የጥንታዊ ሮማ ንጉሥ ታርኲኒዩስ ሱፐርቡስ ከአንዲት ሲቢል (ሴት ነቢይ) ገዝተዋቸው በሮማ መንግሥት ታሪክ ታላቅ አደጋ በተከሠተበት ወቅት እኚህ ትንቢቶች ይማከሩ ነበር። የዛሬው ምሁሮች እኚህ መጻሕፍትና ዛሬ የታወቁት በክርስትና አባቶችም ከ2ኛ ክፍለዘመን እስከ 5ኛ ክፍለዘመን ድረስ በሰፊ የተጠቀሱት የሲቢሊን ራዕዮች አንድ አይደሉም ባዮች ናቸው። መጻሕፍቱ ደግሞ ለግሪኮች ታወቁ። መጀመርያ የታዩ በገርጊስ በደብረ ኢዳ (ለጥሮአስ ትንሹ እስያ ቅርብ የሆነ) በአፖሎ ቤተ መቅደስ በ7ኛው ክፍለዘመን ዓክልበ እንደ ነበር ይታመናል። ደራሲይቱ የሄሌስፖንት ሲቢል ተባለች። ከዚያ ክምችቱ ከገርጊስ ወደ ኤሩትራይ (በምሥራቅ ትንሹ እስያ) እንዳለፈ የኤሩትራይ ሲቢልም ሥራ እንደ ተባለ ይታመናል። ይኸውም ክምችት ከዚያ እስከ ኩማይ ጣልያ ከዚያም እስከ ሮማ ከተማ እንደ ተጓዘ ይመስላል። በአይኔይድ ደራሲ ቪርጂል ዘንድ አይኔያስ ወደ ሢኦል ሳይጓዝ የኩማይ ሲቢልን አማከሮ ነበር። ንጉሥ ታርኲንዮስ ከኩማይ ሲቡል እንዴት እንደ ገዟቸው ዝነኛም አፈ ታሪክ ነበር። እርሷ ዘጠኝ የትንቢት መጻሕፍት ክምችት ለታርኲን ለመሸጥ ብታስብ እሳቸው ውድ በመሆኑ እምቢ ብለው ሦስቱን እንዳቃጠለች ይተረታል። ከዚያ በኋላ ስድስቱን ቀሪዎች መጻሕፍት ለፊተኛው ዋጋ ለመሸጥ አሰበች። ሁለተኛ እምቢ ብለው ሌላ ሶስት አቃጠለች። በመጨረሻ ሶስቱን የተረፉ መጻሕፍት እንዳይጠፉ ለዚህ ዋጋ ገዙና በሮማ በዩፒተር ቤተ መቅደስ አኖሯቸው። መጻሕፍቱም ለ2 የሮማ ባለሥልጣናት አደራ ተሰጡ። ከ375 ዓክልበ. ጀምሮ አሥር ጠባቂዎች -- አምሥት ከባለሥልጣናት ወገንና አምሥት ከተራ ዜጎች ወገን -- ተሾሙላቸው። ከዚህ በኋላ (ምናልባት በሱላ ጊዜ 96-86 ዓክልበ.) ቁጥራቸው እስከ 15 ተጨመረ። የኚህ ጠባቂዎች ተግባር ከአስጊ ሁኔታዎች ለማለፍ ተገቢ ስርዓት ምን እንደ ሆነ ማማከር ነበር። ሆኖም ስርአቱን ብቻ እንጂ ምስጢራዊ ትንቢቱን እራሱን አልገለጹም ነበር። የመጻሕፍቱ ተጽእኖ የምሥራቅ አማልክትን ለምሳሌ አፖሎ፣ «ታላቂቱ እናት» ኩቤሌ እና ኬሬስ፣ እንዲሁም የግሪኮች አረመኔ እምነት ወደ ሮማ አረመኔ ሃይማኖት አስገባ። ግጥሞቹ በግሪክ ስለተጻፉ ጠባቂዎቹ ሁልጊዜ በሁለት የግሪክ አስተርጓሚዎች ይረዱ ነበር። የዩፒተር መቅደስ በ91 ዓክልበ. በተቃጠለበት ወቅት ግን ጠፉ። ስለዚህ የሮማ ላይኛ ምክር ቤት (ሴናት) በ84 ዓክልበ. ተልእኮዎች ተመሳሳይ ትንቢቶች አገኝተው እንዲተኩ ላኩዋቸው። በተለይም ትንቢቶች የተለቀሙ ከትሮይ ከኤሩትራይ ከሳሞስ ደሴት ከአፍሪካ (ማለት የዛሬ ቱኒዚያ) በጣልያም ከሲሲልያ ደሴትና ከቲቡር ነበር። አዲሱን ክምችት ወደ ሮማ ካመጡ በኋላ የሮማ ቄሶች እውነት የመሠላቸውን ለይተው ሌሎቹን ግን ከክምችቱ ጣሉ። የሮማ ንጉሠ ነገሥት አውግስጦስ በ20 ዓክልበ. ወደ አፖሎ መቅደስ አዛውሮአቸው ተመርምረው አዲስ ቅጂ ተደረገ። እዚያ እስከ 397 ዓ.ም. ቆዩ። በዚያን ጊዜ የአሪዮስ ክርስትና ትምህርት አራማጅ የሆነ ስቲሊኮ እንዳቃጠላቸው ይባላል። በ2ኛው ክፍለዘመን ደራሲ የትራሌስ ፍሌጎን መጽሐፍ የጉዶች መጽሐፍ ወይም መታሠቢያ ውስጥ ከሲቡላውያን መጻሕፍት 70 መስመሮች ተጠቀሱ። ይህ ጥቅስ ስለ አንድ ፍናፍንት ልደትና ስለ ጣኦቶች መሥዋዕት ሥርአት ይናገራል። በታሪክ ከተመዘገቡት ምክሮች መኻል ፦ ዓክልበ. 407: መጻሕፍቱ ከአንድ ጨነፈር የተነሣ ተማከሩና ሌክቲስቴርኒዩም የተባለው ሥነ ሥርዓት ለአማልክታቸው ጣኦት ተመሠረተ። ዓክልበ. 303: እንደገና ከጨነፈር በኋላ ደግሞ ብዙ ወታደሮች በመብራቅ ስለ ተመቱ መጻሕፍቱ ተማክረው አንድ ቤተ መቅደስ ተሠራ። ዓክልበ. 301: ከሌላ ጨነፈር ቀጥሎ ተማክረው መልሱ ጣኦቱን አይስኩላፒዩስ ወደ ሮማ ከኤፒዳውሮስ (በግሪክ) እንዲያመጡ ሆነ። ሆኖም የሮማ ሴናት በጦርነት ተይዞ ከአንድ ቀን ጸሎት በቀር ስለ አይስኩላፒዩስ ነገር ምንም አላደረገም። ዓክልበ. 246: «የአበባ ጨዋታዎች» () በመጻሕፍቱ ምክር ተመሠረቱ። ዓክልበ. 224: የካርታጌና አለቃ ሃኒባል የሮማ ጭፍራ በካናይ ፍልሚያ ሲያጠፋ፥ መጻሕፍቱ ተማክረው እንደ ምክራቸው ሁለት ግሪኮችና ሁለት ጋውሎች በሮማ ገበያ በሕይወታቸው ተቀበሩ። ዓክልበ. 212: በካርታጌና ጦርነት ጊዜ የሮማ አበጋዝ ስኪፒዮ አፍሪካኑስ ከመጻሕፍቱ ምክር የተነሣ የኩቤሌ ጣኦት ከፔሢኖስ አምጥቶ አምልኮቷን በሮማ አስገባ። ዓክልበ. 71: «በሮማ ሦስት ቆርኔሌዎሶች ሊገዙ ነው» ከሚል ከአንዱ ትንቢት የተነሣ ፑብሊዩስ ቆርኔሌዎስ ሌንቱሉስ ሱራ አንድ ሤራ አደረገ። ዓክልበ. 63: 12 በጥሊሞስ ወደ ግብጽ ዙፋን እንዲመለሱ ሮማውያን ሥራዊቱን መላካቸውን ሲማከሩ፣ መብራቅ በድንገት የዩፒተር ጣኦት መታ። ስለዚህ የሲቢሊን መጻሕፍት ተማክረው «ከግብጽ አንድ ንጉሥ መቸም እርዳታ ቢለምንሽ፣ ወዳጅነትሽ አይቀርለት እንጂ ጣርና አደጋ እንዳያገኙሽ ሥራዊት ከቶ አትሥጪው» የሚል ትንቢት በመገኘቱ ይህ ቃል የበጥሊሞስን መመለስ በጣም አቆየ። ዓክልበ. 52: «በጳርቴ ላይ ማሸነፍ የቻለው ንጉሥ ብቻ ይሆናል» ስለሚል ትንቢት ቄሣር በሮማ ሬፑብሊክ ላይ ንጉሥነትን በቶሎ እንደሚይዝ ያለ ጭምጭምታ ተፈጠረ። 7 ዓ.ም.: በርማ ንጉሠ ጢባርዮስ ቄሣር ዘመን (የክርስቶስ ልደት አካባቢ) የሮማ ቲቤር ወንዝ ሲጎርፍ አንዱ ቄስ መጻሕፍቱ እንዲማከሩ አስቦ ጢባርዮስ ምስጢራዊ ስለቆጠራቸው እምቢ አለ። 263 ዓ.ም.: ሮማውያን በፕላኬንቲያ ፍልሚያ በአላማኒ ጀርመኖች ከተሸነፉ በኋላ መጻሕፍቱ ተማከሩ። 304 ዓ.ም.: ከሚልቪያን ድልድይ ፍልሚያ አስቀድሞ የተቃዋሚ አለቆች ማክሰንቲያስና ቆስጠንጢኖስ ሲያዘጋጁ ማክሴንቲዩስ የሲቢሊን መጻሕፍት አማከሩና ቆስጠንጢኖስ እምነታቸውን ከአፖሎ ወደ ክርስቶስ አዛወሩ። በፊልሚያውም የማክሴንቲዩስ ድል መሆኑ ስመ ጥሩ ድርጊት ነው። 355 ዓ.ም.: የሮማ ንጉሥ ዩሊያኖስ ከሃዲ በጳርቴ ላይ ዘመቻ ሊያደርግ ሲል መጻሕፍቱን አማከረ። ከሮማ የደረሰውም መልስ በዛኛው አመት ጠረፍ መሻገሩን በግልጽ ደገፈው። የውጭ መያያዣ አንድ ጽሑፍ ስለ ሲቢሊን መጻሕፍት በእንግሊዝኛ የክርስትና ዘመን እውቅ የሆኑት 'ሲቢሊን ንግሮች' - ከግሪክ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎሙ
52408
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%AE%E1%88%9B%20%E1%8C%8D%E1%8B%9B%E1%89%B5
የሮማ ግዛት
የሮማን ኢምፓየር (ላቲን፡ ኢምፔሪየም ]፤ ግሪክ፡ ፣ . የጥንት የሮማውያን ባሲሊያ ቶን የፖስታ ዘመን ነበር)። እንደ ፖለቲካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አፍሪካ እና በምዕራብ እስያ በሜዲትራኒያን ባህር ዙሪያ ያሉ ትላልቅ ግዛቶችን ያጠቃልላል፣ በንጉሠ ነገሥት ይመራ ነበር። አውግስጦስ ቄሳር የመጀመሪያው የሮም ንጉሠ ነገሥት ከሆነበት ጊዜ አንስቶ እስከ 3ኛው ክፍለ ዘመን ወታደራዊ ሥርዓት አልበኝነት ድረስ ጣሊያን የግዛቶቿ ዋና ከተማ ስትሆን የሮም ከተማ ብቸኛዋ ዋና ከተማ የሆነች ዋና ከተማ ነበረች። በኋላ፣ ኢምፓየር በምዕራባዊው የሮማ ኢምፓየር እና በምስራቃዊው የሮማ ኢምፓየር ላይ ቁጥጥር በሚጋሩ ብዙ ንጉሠ ነገሥታት ተገዛ። ሮም እስከ 476 ዓ.ም ድረስ የሁለቱም ክፍሎች ዋና ዋና ከተማ ሆና ቆየች፣ የንጉሠ ነገሥቱ ምልክቶች ወደ ቁስጥንጥንያ የተላከው የምዕራባዊውን የራቨና ዋና ከተማ በጀርመናዊው አረመኔዎች በኦዶአሰር ሥር መያዙን እና በመቀጠልም ሮሙሉስ አውጉስቱሉስ መቀመጡን ተከትሎ ነው። በ380 ዓ.ም ክርስትና የሮማን ኢምፓየር መንግሥታዊ ቤተ ክርስቲያን አድርጎ መቀበሉ እና የምዕራቡ የሮማ ኢምፓየር በጀርመን ነገሥታት መውደቅ የጥንታዊ ጥንታዊነት ፍጻሜ እና የመካከለኛው ዘመን መጀመሪያ ነው። በነዚህ ክስተቶች ምክንያት፣ ከምስራቃዊው የሮም ግዛት ቀስ በቀስ ሔለንናይዜሽን ጋር፣ የታሪክ ተመራማሪዎች በምስራቅ አውራጃዎች ውስጥ የቀረውን የመካከለኛው ዘመን የሮማን ኢምፓየር የባይዛንታይን ግዛት ብለው ይለያሉ። ከክርስቶስ ልደት በፊት በ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሮምን ንጉሣዊ አገዛዝ የተካው የሮማን ሬፐብሊክ መንግሥት በተከታታይ የእርስ በርስ ጦርነቶች እና በፖለቲካዊ ግጭቶች ክፉኛ ተበላሽቶ ነበር። ከክርስቶስ ልደት በፊት በ1ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ጁሊየስ ቄሳር ዘላለማዊ አምባገነን ሆኖ ተሾመ ከዚያም በ44 ዓክልበ. ተገደለ። የእርስ በርስ ጦርነቶች እና እገዳዎች ቀጠሉ፣ በመጨረሻም በ31 ዓክልበ በአክቲየም ጦርነት በቄሳር የማደጎ ልጅ፣ በማርክ አንቶኒ እና በክሊዮፓትራ ላይ በኦክታቪያን ድል ተጠናቀቀ። በቀጣዩ አመት ኦክታቪያን በግብፅ የሚገኘውን የቶለማይክ መንግስት ድል በማድረግ በ4ኛው ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በታላቁ እስክንድር ወረራ የጀመረውን የሄለኒዝም ዘመን አበቃ። ከዚያም የኦክታቪያን ኃይል ሊታለፍ የማይችል ሆነ፣ እና በ27 ዓ.ዓ.፣ የሮማ ሴኔት በመደበኛነት የበላይ ሥልጣንን እና የአውግስጦስን አዲስ ማዕረግ ሰጠው፣ በውጤታማነት የመጀመሪያውን የሮም ንጉሠ ነገሥት አደረገው። ሰፊው የሮማውያን ግዛቶች የተደራጁት በሴናቶሪያል እና በንጉሠ ነገሥት አውራጃዎች ውስጥ ሲሆን ከጣሊያን በስተቀር እንደ ሜትሮፖል ማገልገሉን ቀጥሏል ። የሮማን ኢምፓየር የመጀመሪያዎቹ ሁለት መቶ ዓመታት ፓክስ ሮማና በመባል የሚታወቅ ታይቶ የማይታወቅ የመረጋጋት እና የብልጽግና ጊዜ ታይቷል። ሮም በትራጃን ዘመን (98-117 ዓ.ም.) ከፍተኛውን የግዛት መስፋፋት ላይ ደርሳ ነበር። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው ችግር እና ውድቀት የጀመረው በኮሞደስ የግዛት ዘመን ነው። በ 3 ኛው ክፍለ ዘመን, ኢምፓየር ሕልውናውን አደጋ ላይ የሚጥል ቀውስ ገጥሞታል, ምክንያቱም የጋሊክ ኢምፓየር እና የፓልሚሬን ኢምፓየር ከሮማን ግዛት በመውጣታቸው እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ ጊዜ የቆዩ ንጉሠ ነገሥቶች, ብዙውን ጊዜ ከሌጌዎንቶች, ኢምፓየርን ይመሩ ነበር. በኦሬሊያን (አር. 270-275) ስር እንደገና ተገናኘ። ለማረጋጋት ሲል ዲዮቅላጢያን በ286 በግሪክ ምሥራቅ እና በላቲን ምዕራብ ሁለት የተለያዩ የንጉሠ ነገሥት ፍርድ ቤቶችን አቋቋመ። ክርስቲያኖች በ 4 ኛው ክፍለ ዘመን የ 313 ሚላን አዋጅ ተከትሎ በ 4 ኛው ክፍለ ዘመን የስልጣን ቦታ ላይ ወጡ ። ብዙም ሳይቆይ ፣ የፍልሰት ጊዜ ፣ ​​በጀርመን ህዝቦች እና በአቲላ ሁንስ ትልቅ ወረራ ፣ የምእራብ ሮማን ኢምፓየር ውድቀት አስከትሏል። በራቬና በጀርመናዊው ሄሩሊያውያን መውደቅ እና ሮሙሉስ አውግስጦስ በ 476 ዓ.ም በኦዶሴር ከተቀበረ በኋላ የምዕራቡ የሮማ ኢምፓየር በመጨረሻ ፈራረሰ። የምስራቃዊው የሮም ንጉሠ ነገሥት ዘኖ በ480 ዓ.ም. በአንፃሩ ቁስጥንጥንያ በ1453 በኦቶማን ቱርኮች እጅ እስከወደቀ ድረስ የምስራቅ ሮማን ኢምፓየር ለሌላ ሺህ ዓመታት ቆየ።የሮማ ኢምፓየር ሰፊና ረጅም ጽናት በመኖሩ የሮም ተቋማት እና ባሕል በሚያስተዳድሩት ግዛት ውስጥ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በሥነ ጥበብ፣ በሥነ ሕንፃ፣ በሥነ ጽሑፍ፣ በፍልስፍና፣ በሕግ እና በአስተዳደር ዓይነቶች እድገት ላይ ከፍተኛ እና ዘላቂ ተጽእኖ ነበራቸው። ፣ እና ከዚያ በላይ። የሮማውያን የላቲን ቋንቋ በመካከለኛው ዘመን እና በዘመናዊው ዓለም ወደ ሮማንቲክ ቋንቋዎች ተለወጠ ፣ የመካከለኛው ዘመን ግሪክ የምስራቅ የሮማ ኢምፓየር ቋንቋ ሆነ። ኢምፓየር ክርስትናን መቀበሉ የመካከለኛው ዘመን ሕዝበ ክርስትና እንድትመሰረት አድርጓል። የሮማውያን እና የግሪክ ጥበብ በጣሊያን ህዳሴ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል. የሮማ የሥነ ሕንፃ ወግ ለሮማንስክ፣ ህዳሴ እና ኒዮክላሲካል አርክቴክቸር መሠረት ሆኖ አገልግሏል፣ እንዲሁም በእስላማዊ ሥነ ሕንፃ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል። በመካከለኛው ዘመን አውሮፓ የግሪክ እና የሮማውያን ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ (ለኢስላማዊ ሳይንስ መሠረት የሆነው) እንደገና መገኘት ወደ ሳይንሳዊ ህዳሴ እና ሳይንሳዊ አብዮት አመራ። የሮማውያን ሕግ አካል ዛሬ በብዙ የዓለም የሕግ ሥርዓቶች ዘሮች አሉት፣ ለምሳሌ የፈረንሳይ ናፖሊዮን ኮድ፣ የሮማ ሪፐብሊካኖች ተቋማት ግን ዘላቂ ቅርስ ትተዋል፣ በመካከለኛው ዘመን በጣሊያን ከተማ-ግዛት ሪፐብሊካኖች ላይ ተጽዕኖ ያሳድራሉ እንዲሁም ቀደምት ዩናይትድ ስቴትስ እና ሌሎች ዘመናዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊኮች.
10091
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A8%E1%8A%A4%E1%89%BD%C2%B7%E1%8A%A0%E1%8B%AD%C2%B7%E1%89%AA%20%E1%89%AB%E1%8B%AD%E1%88%A8%E1%88%B5%20%E1%8C%8B%E1%88%AD%20%E1%89%B0%E1%88%B5%E1%88%9B%E1%88%9D%E1%89%B6%20%E1%88%88%E1%88%98%E1%8A%96%E1%88%AD
ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር ተስማምቶ ለመኖር
ከኤች·አይ·ቪ ጋር መኖር ከኤች.አይ.ቪ ቫይረስ ጋር መኖር ማለት ቫይረሱ በደሙ ውስጥ እንዳለ የተረዳ ሰው ራሱን አረጋግቶና ችግሩን እንደማንኛዉም የጤና ችግር በማየት ቫይረሱ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነሰ እና ለመከላከል በሕክምና፣ በአመጋገብ፣ እንዲሁም በባህርይ ላይ አስፈላጊ የሆኑ ለውጦችን በማምጣት ጥሩ ሕይወት መኖር ማለት ነው። አንድ ሰው ኤች·አይ·ቪ አለበት ማለት አሁኑኑ ታሞ ይተኛል ወይም በቅርቡ ሕይወቱ ያልፋል ማለት አለመሆኑን ማወቅ ተገቢ ነው። ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች የእድሜ ማራዘሚያ መድሀኒቶችን (ፀረ-ኤችአይቪ መዳኒቶች) በመጠቀም ለረጅም ዓመታት ጤናማ ሆነው ለመኖር ይችላሉ። አንዳንድ ሰዎች የበሽታዉ ምልክት ጨርሶ ሳይታይባቸው ከ15 ዓመት በላይ ከቫይረሱ ጋር መኖር እንደሚችሉ አንዳንድ ጥናቶችም ያመለክታሉ። ኤች·አይ·ቪ ቫይረስ በደም ውስጥ በመኖሩ ምክንያት ሊሰማ የሚችለዉን ስሜት አውነታውን መቀበል መቻል በጣም አስፈላጊ ነው። ጥሩ ያልሆኑትን ስሜቶች ለማስወገድ የሚከተሉትን ምክሮች መቀበልና መተግበርም ተገቢ ነው። ሁኔታዎች እያደር የተሻሉ እንደሚሆኑ ተስፋ ማድረግ፦ ፈታኝ የሆነ ሰሜት ሲሰማ ሁኔታዎች ሁሉ ከጊዜ ጋር እየተሻሻሉ እንደሚሄዱ ማመን በጣም ጠቃሚ ነው። የተሻለ ሁኔታ እንደሚኖር ተስፋ የሚሰጡ ብዙ መንገዶች አሉ። ለምሳሌ የራስን ጤንነት መጠበቅና የቀድሞውን የተረጋጋ ህይወት እንደገና መጀመር አንዱ መንገድ ነው። ከኤች·አይ·ቪ ጋር ከሚኖሩ ሰዎች ጋር መመካከር፦ ማንኛውንም የሚሰማን ስሜት ወይም የህመም ምልክት፤ ሌሎችም ምናልባት ተመሳሳይ ስሜት እና ምልክት ሊኖራቸው ስለሚችል ከቫይረሱ ጋር ከሚኖሩ ሰዎች ጋር መመካከር ወይንም ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ወደመሠረቷቸው ማህበራት በመሄድ የምክር እርዳታ ማግኘት አስፈላጊ ነው። ሁሌም የሚያስደስቱን ነገሮች ከማድረግ አለመቆጠብ፦ አንድ ሰው ኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በደሙ ውስጥ መኖሩን ካወቀ በኋላ የደረሰበትን ድንጋጤ ለማስወገድ ቀደም ሲል ያደርጋቸው የነበሩትን አስደሳች ስራዎችን በመቀጠል አሁን የተፈጠሩበትን የኀዘንና የብስጭት ሰሜቶችን መርሳት መቻል ይገባዋል። ዘወትር ሲያደርገው ያስደስቱት የነበሩትን ሥራዎች በቀጣይነት ማድረግ ኀዘን ወይም ጭንቀት ላይ ብቻ እንዳያተኩር ይረዳል። አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ፦ ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖር ሰው ድካም ሊሰማዉና ሊጫጫነው ይችላል። በዚህ ጊዜ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ብርታትና ጥንካሬ ይሰጣል። ከፍተኛ የሰውነት እንቅስቃሴ ባይሆንም እንኳን ቀላል እርምጃዎችን ማዘውተር ለአእምሮና ለሰውነት ጤንነት በጣም አስፈላጊ ነው። ጎጂ የሆኑ ቅፅበታዊ ለውጦችን በህይወት ላይ አለማድረግ፦ ሥራን አለመተው፣ ዘመድ ወዳጆችን አለመራቅ፣ ንብረቶችን አለመሸጥ። በእርግጥ አንድ ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖር ሰው የወደፊት እቅዱን ሊለውጥ ይችላል፤ ይህ ለውጥ ጫና ያልበዛበትና ውጤቱም ጠቃሚ መሆኑን አስቀድሞ መለየት ያስፈልጋል። ባለሞያን ማማከር፦ ስለ ኤች·አይ·ቪ/ኤድስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በመኖሪያ አካባቢያችን እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ማህበራትን ወይም ድርጅቶችን ማወቅ ጠቃሚ ነው። አንድ ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖር ሰዉ የጭንቀት እና የመከፋት ስሜት ካለቀቀው የህክምና ባለሞያዎች ወይንም አማካሪዎችን በስልክም ሆነ በአካል ማግኘትና ማማከር ያስፈልገዋል። ያስታውሱ! ብቻዎን አይደሉም ፦ኢትዮጵያ ውስጥ ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ከአንድ ሚሊዮን ተኩል በላይ ሰዎች አሉ። በአሁኑ ጊዜ 12 በመቶ ገደማ የሚሆኑ ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ይኖራሉ። በመላው ኢትዮጵያ ውስጥ ዕድሜያቸው በ15 እና በ49 መካከል የሚገኙ ከ4 ከመቶ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ። አንድ ኤች·አይ·ቪ ቫይረስ በደሙ ውስጥ ያለበት ሰው በቫይረሱ ለመያዝ ሆን ብሎ የሰራው ስህተት ስለሌለ ራሱን መውቀስ እና መጨነቅ የለበትም። ማድረግ ያለበት ነገር ቢኖር ለሌሎች ተጓዳኝ በሽታዎች እንዳይጋለጥ ራሱን እንዲጠብቅ ትምህርት ማግኘት እና ከኤች.አይ.ቪ ነፃ የሆኑ ሰዎች ለቫይረሱ እንዳይጋለጡ ስብዓአዊነት ተስምቶት ቅድመ ጥንቃቄዎችን ማድረግና፣ ከተቻለም ማስተማር። ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸዉ አውቀው ከጥቂት ጊዜ በኋላ ያሉበትን የጤና ሁኔታ ተቀብለው ራሳቸውን በማረጋጋት ወደፊት በተሻለ መንገድ ለመኖር ምን ማድረግ እንዳለባቸው ማሰብ ይጀምራሉ። እራሰን አረጋግቶ ለመኖር ከዚ በታች የተጠቀሱት ጠቃሚ መመሪያዎች በዝርዝር ጠንቅቆ ማወቅ አጥጋቢ የሆነ የፀባይ እና የአኗኗር ለውጥ ለማምጣት ይረዳል፦ ኤች·አይ·ቪ ቫይረስ በደም ዉስጥ መኖሩን በታወቀበት ጊዜ ሊገጥም የሚችለውን የጭንቀት እና የፍርሃት ስሜት እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል፤ አጋጣሚን ጠብቀው የሚመጡ የበሽታ ስሜት/ምልክቶች በሰውነት ላይ ሲታዩ መወሰድ ያለባቸውን ህክምና እና ጥንቃቄ፤ የተመጣጠነ ምግብ መመገብ፣ የራስን ንፅህና መጠበቅ እና የሰውነት እንቅስቃሴ የማድረግ አስፈላጊነትን፤ ጥንቃቄ ስለተሞላበት የግብረ ሥጋ ግንኙነት እና ስለወሊድ። ተስፋ እና የወደፊት ህይወት ከኤች.አይ.ቪ ጋር ኑሮን በሠላም ለረጅም እድሜ መምራት እንደሚቻል መገንዘብ አስፈላጊ ነው። እንዲሁም ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ህጋዊ መብታቸውን የሚያከብሩ ህግጋት እንዲደነግጉ ድጋፍን በመስጠት የራስን አስተዋፅኦ በማድረግ ተስፋን እውን ማድረግ። በተጨማሪም የዕለት ዜናዎችን በመከታተል፣ባለሞያዎችን ወይንም አማካሪዎችን በመጠየቅ በኤች.አይ.ቪ ላይ ያሉ አዳዲስ የህክምና እና የመድሀኒት ግኝቶችን መከታተልና ማወቅ ተስፋን ይሰጣል። ስለ ኤች.አይ.ቪ ዕውቀትን ማዳበርና ይበልጥ ማወቅ ራስን በደንብ ለመንከባከብ ይረዳል። አንድ ከኤች.አይ.ቪ ጋር የሚኖር ሰው ልጆች ካሉት ህመም ሲጠና ልጆችን የሚንከባከብ ሰው ቀድሞ ማዘጋጀት ያስፈልጋል። ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ክትባት ወይም ፈዋሽ መድኀኒት ባይገኝለትም ምርምሩና ሙከራዉ እንደቀጠለ ነው። የዕድሜ ማራዘሚያ መድሃኒቶች (ፀረ-ኤችአይቪ መዳኒቶች) ቫይረሱ በደም ውስጥ የሚያደርገውን የስርጭት ፍጥነት ለመግታትና ለማስቆም የሚወሰዱ መድሃኒቶች ናቸው። በሰውነት ዉስጥ የሚገኘውን የኤች.አይ.ቪ ቁጥር መቀነስ ይችላሉ፤ መድሃኒቶቹ ቫይረሱን ከናካቴው ማጥፋት አይችሉም። መድሃኒቶቹን ያለ ህኪም ትዕዛዘና ፍቃድ መውሰድ በጤንነት ላይ ትልቅ ችግር ያስከትላል። የመድሃኒቶቹ ተጠቃሚ ሰው አንድ በቅርብ ሆኖ የሚከታተለው ብቃት ያለው የህክምና ባለሙያ ያስፈልገዋል። የተመጣጠነ ምግብ መመገብ ሰውነታችንን እና የሰውነት የመከላከያ አቅማችንን እንደሚያጠነክር ሁሉ በቀላሉ ለበሽታ እንዳንጋለጥም ይጠቅመናል። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ስዎች በምግብ እና ውኀ ውስጥ ለሚገኙ በሽታን ወይም ህመምን ሊያስከትሉ ለሚችሉ ጀርሞች በቀላሉ የተጋለጡ በመሆናቸዉ፤ በቤት ውስጥም ሆነ ከቤት ውጭ ሲመግቡ ንጽህናውን የጠበቀ የአመጋገብ ሥርዓት መከተልና የሚጠጣው ውሃ ንጹሀ መሆኑን ማረጋግጥም በጣም ጠቃሚ ነው። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ስዎች የተለያዩ ዓይነት ምግቦችን በመመገብ ያልተፈለገ የሰውነት ክብደት መቀነሰን ለመከላከል እና ጡንቻዎቻቸዉ እንደጠነከሩ እንዲቆዩ የሰውነት እንቅስቃሴ ማድረግ አለባቸው። ሁሉም የምግብ ዓይነቶች የተለያዩ ጥቅሞች አላቸዉ። የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች በሚከተለው መሰረታዊ ምድቦች ተከፋፍለው ሊታዩ ይችላሉ። ገንቢ ምግቦች፦ ባቄላ፤ አተር፣ ምስር፣ እንቁላል፣ ሥጋ፣ አሣ፣ ዶሮ፣ ወተት፣ አይብ እና ለውዝ ሰውነትን ለመገንባት የሚያስችሉ የምግብ ንጥረ ነገሮችን ይዘዋል። ኃይል ሰጪ ምግቦች፦ ለሰውነት የሚያስፈልገውን ኃይል ሁሉ የምናገኝባቸው የምግብ አይነቶች እንደ በቆሎ፣ እንጀራ፣ ዳቦ፣ ድንች፣ ፓስታ፣ ሩዝ፣ ስንዴ፣ አጃ፣ ዳጉሳ፣ ማሽላ፣ ስኳር፣ ማርማላት፣ ማርጋሪን፣ ዘይት፣ ሲሆኑ በተጨማሪም እንደ ለውዝ እና አቮካዶ የመሳሰሉ የቅባት ምግቦችንም ያጠቃልላል። የሰውነትን የመከላከል አቅም የሚያጎለብቱ ምግቦች፦ አትክልትና ፍራፍሬ መመገብ የሰውነታችንን አቅም በማጎልበት በሽታን በሚገባ ለመቋቋም ያስችላል፤ እንዲሁም እንደ ካሮት፣ ሰላጣ እና ጎመን የመሳሰሉ ምግቦችንም መመገብ ቫይታሚን ለማግኘት ይረዳናል። የሰዉነትን የመከላከል አቅም ለማጎልበት፦ የምግብን የመፍጨት ሂደት ሊያውኩ የሚችሉ እንደ ቃሪያ፣ በርበሬ ወይም ሚጥሚጣ የመሳሰሉ እና ሌሎች ቅመማ ቅመም የበዛባቸውን ምግቦች በብዛት አለመመገብ፣ ለስለስ ያሉ እንደ አልጫ ወጥ ያሉ ምግቦችን መመገብ፣ ከህይለኛ ቅመሞች ይልቅ የጥብስ ቅጠልን የመሳሰሉ የምግብ ማጣፈጫዎች መጠቀም ያስፈልጋል። ፍራፍሬ እና የአትክልት አመጋገባችንን መጨመር፣ እነዚህን የሰውነት የመከላከል አቅም የሚያጎለብቱ ምግቦች በቫይታሚንና በማዕድን የበለፀጉ በመሆናቸው ሰውነታችንን ከበሽታ ይከላከላሉ። በመሆኑም እንደ ቆስጣ እና ጎመን የመሳሰሉ በጣም አረንጓዴ የሆኑ የቅጠላቅጠል ምግቦችን፣ እንደ ዱባ፣ ብርቱካን፣ ሎሚ፣ ማንጎ እና የመሳሰሉ ፍራፍሬዎችን በየቀኑ መመገብ ያስፈልጋል። በተጨማሪም ከጤፍ፣ ከጥቁር ስንዴ፣ ገብስ የተዘጋጁ ዳቦዎችን እና ሌሎች ምግቦችን መመገብ። ዉኃ ለሰውነታቻን ከሚያሰፈልጉን ነገሮች አንዱ ነው። በየቀኑ ቢያንስ 8 ብርጭቆ ዉሃ መጠጣት ጠቃሚ ነው። የምንጠጣው ዉሃ ንፁህ መሆን አለበት። ከኤች. አይ.ቪ ጋር የሚኖር ሰው እንደ ተስቦ፣ ኮሌራ፣ ቢልሀርዚያ እና ጃርዲያ ለመሳሰሉት በተበከለ ውኃ አማካኝነት በሚተላለፉ በሽታዎች የተጋለጠ ስለሆነ በቀጥታ የህይቅ ወይም የምንጭ ውኃ ከመጠጣት ፈልቶ የቀዘቀዘ ውኃ መጠጣት በጣም አስፈላጊ ነው። ሰዉነታችንን በጤንነት ለማቆየትና ቫይረሱ በጤና ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ ቫይታሚን ኤ፣ ቢ6፣ ቢ12፣ ሲ፣ ዚንክ፣ አይረን፣ ኮፐር፣ ማንጋኒዝ፣ ማግኒዥየም እና ሴሊኒየም ጨዉ የመሳሰሉትን ሁሉ መመገብ ይጠቅማል። የሰዉነትን የተፈጥሮ በሽታን የመከላከል አቅም በማጎልበት ረገድ ቫይታሚን ኤ፣ ሲ፣ ኢ፣ እና ከማዕድናትም ዚንክ በጣም ጠቃሚዎች ናቸው። እነዚህ የምግብ ንጥረ-ነገሮች በተፈጥሮ ከተለያዪ ምግቦች ዉስጥ ይገኛሉ። አንዳንድ ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ ባለመመገባችን ምክንያት የሚከተለውን ክፍተት ለማካካስ በፋብሪካ የተዘጋጁ ቫይታሚኖችን እንወስድ ይሆናል። ቅድሚያ መስጠት የሚገባን የተመጣጠነ ምግብ በመመገብ ተፈላጊ የሆኑትን የምግብ ንጥረ ነገሮች ማግኘት ቢሆንም የቫይታሚን እንክብሎችን መውሰድ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ጊዜያት አሉ። በግምት ብዙ ቫይታሚኖችን መውሰድ ጤንነትን ስለሚያቃውስ የቫይታሚን እንክብ በሚወሰድበት ጊዜ በህክምና ባለሞያ ትዕዛዝ መሰረት መሆን አለበት። በምግብ አዘገጃጀት እና አመጋገብ ምክንያት ሊከሰቱ ከሚችሉ በሽታዎች ራስን መከላከል ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች በምግብ ምክንያት ለሚመጡ በሽታዎች የተጋለጡ ናቸዉ። አንዳንድ ጎጂ የሆኑ ጀርሞች ከጥሬ ስጋ፣ ምግቡን ከሚያዘጋጁ ሰዎች ወይም አብረዉ እንጀራ ከሚበሉ ሰዎች አፍና እጅ ንክኪ ሊሸጋገሩና የምንመገበውም ሊበከል ይችላል። ከኤች·አይ·ቪ ቫይረስ ጋር የሚኖር ሰው በምግብ መመረዝ ሲታመም ለማዳን በጣም ከባድ ከመሆኑ ሌላ በሽታው በተደጋጋሚ ሊመላለስበት ይችላል። እንደ ኮሶ፣ ወስፋት እና አሜባ የመሳሰሉት በሽታዎች ከፍተኛ የጤና ችግርን እንዲሁም ሞትን ሊያስከትሉ ይችላሉ። ከነዚ በሽታዎች አብዛኛዎቹ በቀጥታ በበሽታዎቹ ከተያዘ ሰው የሚተላለፉ ቢሆንም ባልበሰለ ወይም ንጽህናው ባልተጠበቀ ምግብ፣ በነፍሳት (ተባዮች) በተበከለ ምግብ፣ የምግብ አያያዝ ሥርዓትና ደንብን ባልተከተለ ሰው ተዘጋጅቶ በሚቀርብ ምግብ አማካይነት ሊተላለፉ ይችላሉ። ምግብን በደምብ ማብሰል ባክቴርያና ጀርሞች እንዲሞቱ ይረዳል። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ጥሬ ሥጋ ወይም ጥሬ ክትፎም ሆነ ለብለብ ክትፎ ባይመገቡ ይመረጣል። በተጨማሪም ከቤት ውጭ በሆቴሎችና ቡና ቤቶች ውስጥ መመገብ ምግቡ እንዴት እንደተዘጋጀ ስለማይታወቅ ለህመም ሊያጋልጥ ይችላል። ከተቻለ ከቤት ውጭ አለመመገብ፤ ካልሆነም ምግቡ እንዴት እንደተዘጋጀ እና ጥሬ የሆኑ የምግብ ውህዶች ማለትም ያልበሰለ ሥጋ፣ እንቁላል ወይም አትክልት የሌለበት መሆኑን ጠይቆ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ዕፅ እና አልኮል ዕፅም ሆነ አልኮል በብዛት መውሰድ የሰውነትን የተፈጥሮ በሽታን የመከላከል አቅም ያዳክማል። ጤናማ ሆኖ ለመኖርም ሆነ ጤንነትን ለመንከባከብ አልኮልንም ሆነ ዕፅን መጠቀምን እስከመጨረሻው መተው አማራጭ መንገድ ቢሆንም ይህንን ሁሉም ሰው በቀላሉ ሊያደርገው አይችልም። የሚወሰደው የሲጋራ፣ የዕፅ ወይም የአልኮል መጠንን በተቻለ መጠን መቀነስ ጤንነትን በተሻለ ሁኔታ ለመጠበቅም ይረዳል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ የተሻለ ጢና እንዲኖር ከመርዳቱ ሌላ የመጨነቅ፣ እና የድካም ስሜትን ይቀንሳል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴው ራስን ዘና የሚያደርግና የልብን ምት እንዲጪምር ተደርጎ መሠራት አለበት እንጂ እስኪደክሙ መሆን የለበትም። ተገቢውን የየአካል ብቃት እንቅስቃሴ መጠን ለማወቅ ቢቻል የስፖርት ባለሞያዎችን አስቀድሞ ማማከር የተሻለ ነው። በየቀኑ ከ30 እስከ 60 ደቂቃ ያህል በእግር መጓዝ የተሻለ ጤና እንዲኖረን ከሚረዱት የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች አንዱ ነው። ወሲብና ፍቅር አንድ ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖር ሰው ስለራሱ ጤና በተመለከተ መብቱ የተሰጠዉ ለራሱ በመሆኑ ለፈለገው ሰው መንገር፣ ካልፈለገ ደግሞ ያለመናገርም ውሳኔው በእጁ ነው። ነገር ግን ከዚህ ጋር በተያያዘ መዘንጋት የሌለበት ጉዳይ አለ። በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ላይ የሰፈረ ድንጋጌ አንድ ሰው የሌላውን ሰው ጤንነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሆን ብሎ ይሁን በቸልተኝነት የሚጎዳ ተግባር ከፈጸመ እንደሚቀጣ ያስረዳል። ስለዚህ ከወሲብ ጓደኛ ጋር በሚኖር ግንኙነት ቫይረሱ ወደዛ ጓደኛ እንዳይተላለፍ ኮንዶም መጠቀም ያስፈልጋል ። ይህ ከሆነ ከኤች·አይ·ቪ ነፃ የሆነውን ወዳጅ ከቫይረሱ ለመጠበቅ ይረዳል። ከኤች·አይ·ቪ ጋር ነዋሪ መሆንን ለወሲብ/ፍቅር ጓደኛዎ አንዳንድ ጊዜ በቀጥታ ሌላ ጊዜ ደግሞ በተዘዋዋሪ መናገር ይቻላል። ለምሳሌ ስለቅድመ ወሲብ ጥንቃቄ ወይም ስለ ኤች·አይ·ቪ እና መተላለፊያ መንገዶች በማንሳት መነጋገር ይቻላል። ወሊድ ( ኤችአይቪ ያለባት እናት) አንዲት ሴት ኤች·አይ·ቪ በደሟ ውስጥ ቢኖርም እንኳን ልጆች ማፍራት ትችላለች። ተገቢውን ጥንቃቄ እና የህክምና ክትትል ካደረገች ከኤች·አይ·ቪ ነፃ የሆነ ጤነኛ ልጅ ሊኖራት ይችላል። ይሁን እንጂ ለኤች·አይ·ቪ የሚጋለጥም ልጅ ሊኖር ይችላል። ልጅ ለመውለድ እቅድ ካለ የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ማለት እና የህክምና ባለሞያን ማማከር ያስፈልጋል የጤንነት ሁኔታ- በእርግዝና ወቅት በብዛትም ሆነ በጥራት የተሻለ የምግብ አቅርቦት መኖር አለበት። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖር ሰው ደግሞ ከፍ ያለ የምግብ መጠንና የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች ማግኘት ያስፈልገዋል። ፅንሱን ከቫይረሱ መከላከል- ኤች·አይ·ቪ በደም ውስጥ መኖሩን አውቆ ልጅን ከኤች·አይ·ቪ ለመታደግ አስፈላጊውን እቅድ ማዉጣትና ተገቢውን ህክምና መከታተል የልጅን በቫይረሱ የመያዝ አጋጣሚ ለመቀነስ ይረዳል። በደም ዉስጥ የኤች·አይ·ቪ መኖር- ወደፊት አንድ ወቅት ላይ የኤድስ ታማሚ ሊሆኑ እና አልጋ ላይ የመዋል አጋጣሚ ሊመጣ ይችላል። ስለዚህ ልጅዎ ያለ ተንከባካቢ እንዳይቀር ቀደም ብሎ ሁኔታዎችን ማመቻቸትም ያስፈልጋል። ኤች·አይ·ቪ እና ሰብአዊ መብት ከኤች·አይ·ቪ ጋር መኖር ከማንኛውም ሰብአዊ ፍጡር አያሳንሰም። ኤች·አይ·ቪ በደም ውስጥ በመኖሩ በሰብአዊ ፍጡርነት ሊኖር የሚገባውን መብት ሊያጓድል የሚችል አንድም ምክንያት የለም። ይህም ማለት ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖር ማንኛውም ሰው እንደሌሎች እንደማንኛውም ሰው ቫይረሱ በደሙ ያለበት ሰው የጤና አጠባበቅ አገልግሎት፣ ሥራ እና የትምህርት ዕድል የማግኘትና፣ በማህበራዊ ክንውኖች፣ ለምሳሌ፣ ዕድር፣ በዕምነት፣ በማህበራት ወይም የስፖርት ቡድን በመሳሰሉ ማህበራዊ ተቋማት አባል የመሆን መብት አለው። ከኤች·አይ·ቪ ጋር የሚኖር ሰው ቤት የመከራየት ወይም ባለንብረት ለመሆን፣ የጤና፣ የህይወት ወይም የንብረት መድን የመግባት መብት አለው። ከኤች·አይ·ቪ ጋር በሚኖሩ ሰዎች ላይ የሚደረግ መድልዎ ዋና ዋና መንስኤዎች አሉት፦ እነዚህም ስለ ኤች·አይ·ቪ ቫይረስ መተላለፊያ መንገዶች ዝቅተኛ ወይም የተሳሳተ መረጃ መኖር፤ በቂ ግንዛቤ ካለማግኘት ወይም ከተሳሳተ መረጃ ላይ በመመርኮዝ የሚመጣ ፍርሃት፤ ስለግብረ ስጋ ግንኙነት በግልጽ መነጋገር እንደ ነውር ስለሚቆጠር፤ በሥራ ቦታ ላይ ስለሚደርስ መድልዎ ማወቅ፦ አንድ ሰው ከኤች·አይ·ቪ ጋር በመኖሩ ምክንያት መገለል ወይም አድልዎ ከደረሰበት ከቀጣሪው ጋር በመነጋገር ወይም በፍርድ ቤት በመክሰስ ፍትህ የማግኘት መብት አለው። ሕግም ከለላና ጥበቃ ያደርግለታል። የኢፌዴሪ የኤች·አይ·ቪ/ኤድስ ፖሊሲ ማግለልና አድልዎን በግልጽ ይከለክላል። የውጭ መያያዣዎች 1. አበሻ ኬር 2. የእንግሊዘኛ ውክፔዲያ
50399
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8B%B2%E1%88%B5%20%E1%89%85%E1%8B%B3%E1%88%9D
አዲስ ቅዳም
አ/ቅዳም አ/ቅዳም በአማራ ክልል አዊ ዞን የ[ፋግታ ለኮማ] ወረዳ ዋና ከተማ ስትሆን አ/ቅዳም በምሥራቅ ጎጃም እና በምእራብ መሃል የምትገኝ ከተማ ነች። አዲስ ቅዳም በድሮው ጎጃም አጠቃላይ ግዛት አገው ምድር አውራጃ ፣በባንጃ ወረዳ፣በባንጃ ለኮማ ምክትል ወረዳነት ከ1936-1987 ዓ.ም የቆየች ስትሆን ከ1987 ዓ.ም ወዲህ አዊ ብሔረሰብ ዞን ራሱን ችሎ ሲቋቋም ወረዳዎች ውስጥ የፋግታ ለኮማ ወረዳ ዋና ከተማ ነች ፡፡ አንዳንድ አፈታሪኮች ለኮማ የባንጃ ልጅ ሲሆን ፋግታ ደግሞ የአንከሻ ልጅ ነው ይላሉ ፡፡ከተማዋ ከመዲናችን አዲስ አበባ 470 ኪ.ሜ ፣ከክልሉ ርዕሰ ከተማ ባህርዳር 104 ኪ.ሜ እንዲሁም ከብሔስብ ዞን ርዕሰ ከተማ እንጅባራ 18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከአዲስ አበባ -ጎንደር በሚወስደው አገር አቋራጭ መንገድ ግራና ቀኝ ደጋማ ቦታ ላይ የተመሰረተች ናት ፡፡ሰባቱ የአገው አባቶች ዛሬ አዲስ ቅዳም እየተባለ የሚጠራውን ቦታ በድሮ ጊዜ “አጂስ ክዳሜ” ብለው ሰይመውት ቅዳሜ ቀን ለመወያያትና ለገቢያ ማዕከልነት (ኩሰጝፂ፣ዙሚትጝፂ፣ እንክርጝፂ ኧኧኮ) ይጠቀሙበት እንደነበር የአካባቢው ቀደምት አባቶችና አፈ ታሪኮች ያስረዳሉ ፡፡ በ1903 ዓ.ም ጎጃም ገዥ የነበረው ንጉስ ተ/ሃይማኖት ሲሞት በጊዜው የነበሩት የኢትዮጵያ ንጉስ አፄ ምኒልክ ጎጃምን ምስራቅ ፣ዳሞትና አገው ምድር ብለው ሲከፋፍሉ ለእነዚህ ግዛቶችም አስተዳዳሪ/ገዢ/ ሲመርጡ ራስ መንገሻ አቲከም አገው ምድርንና ደሞትን ገዢ ሆነው ተሾሙ፡፡ ከዚያ በፊት የነሩበት አዛዥ ገዛኻኝ ከወሰኑት ቦታ ባንግ ታራራ (አመዳይ ደን) ላይ ሆነው የጥንቱን ገበያ ስባቱ አባቶች ካስቀመጡት አንስተው ወደ አቅራቢያቸው አዛማች ኪዳነ ምህረት ወደ “ጉቢቺሊ” በመውሰዳቸው በመሰራቾቹ ተቃውሞ ብዙም ሳይቆይ ተመልሶ አሁን ካለንበት ከጥንቱ ቦታ ገበያው ተቋቁሟል ፡፡ ወደ ቦታው ሲመለሱ ግን የድሮ መጠሪያ “አጂስ ቅዳሜ” በመቀየር አዲስ ቅዳም ተብሎ ተጠርቷል ፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው የአውጚ ቋንቋ በአማረኛ እየተወረስ በመሄዱ ነው ይላሉ አባቶች ፡፡ የአዲስ ቅዳም ጦርነት የኢጣሊያን ጦርነት ሽንፈት በኃላ በኢትዮጵያ አርበኞች ላይ ለመቀበል ከ40 አመታት በኋላ እደገትና ተነሳስተው ክብራቸውንም ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ ላይ በኦጋዴን አካባቢ ድንበር ጥስው በመግባት አደጋን አድርሰዋል ፡፡ምንም እንኳ ያስቡት ባይሳካለቸውም የኢትዮጵያ አርበኞች ተጋድሏቸውን በየጫካውና በየሽንተረሩ ተያይዘውታል ፡፡ ለአምስት አመታት ያህል ከተካሄዱ ጦርቶች መካከል በድሮው አገው ምድር አውራጃ በአሁኑ አዊ አስ/ዞን ውስጥ አንዱ በጦርነት የአዲስ ቅዳም ጦርነት ነበር፡፡ ይህ ጦርነት የተካሄደው የኢጣሊያን የዳፈጣ ጦር ግንቦት 24/1932 ዓ.ም በሁለት አቅጣጫ ማለትም የእንጅባራው በደቡብና የዳንግላው በስተ ሰሜን የእንጅባራው አድጓሚ ተራራ እንዲሁም የዳንግላው ከአ/ ቅዳም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ላይ መትረይስ በመቀየስ ለገበያ የመጣውን ህዝብ ለመጨፍጨፍ ሲዘጋጅ ጀግኖች የአገው ምድር አባት አርበኞች የተለመደ ሽንፈት አከናንበው መልሰውታል ፡፡ አዲሲቅዳም ከተማ ምንም አይነት ቤት ስላልነበረው ቅዳሜ ቀን ለገቢያ ብዙ ህዝብ ይሰብሰብ ነበር፡፡ይህን ህዝብ ለመጨፍጨፍ ነበር የጣሊያን ፋሽስት ጦር ቋምጦ የተነሳው በዕለቱም ህዝብ በቦታው የተለያዩ መሳሪያዎችን ለመሸጥና ለመግዛት የመጡ የአገውምድር አባትአርበኞች፣ራስ ቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ፣ ፊታውራሪ የኔው አባዲት፣ ፊትአውራሪ ደስታወርቄ፣ቀኝ አዝማች በቀለ ወንድምና ቀኝ አዝማች አባ ደስታ የተሳተፉ ሲሆን በተለይ እና ፊት አውራሪ የኔው አባዲና ከማሳው በመመስግ ፣ራስ ቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ ከኳሽኒ መሽገው የፋሺስት ነጭ ደጋአመድ አድርገዋል፡፡ ጦርነቱ ከዕለቱ በግምት 4 ስዓት የተጀመረው ቀኑን ሙሉ ውሎ ጽሀይ ግባት ላይ በአገውምድር አርበኞች ድልአድራጊት ተፈፅሟል፡፡ በዕለቱ በዱርገ ደሉ የነበሩ ሴቶች ፊታውራሪ ተብለው የተሸለሙ ሲሆን ከጣላትም ሆነ ከአባት አርበኞች የሞተ እንዳለ ሆኖ ብዙ መሳሪያዎችን ማለትም 500 ያህል አልቢን ምኒሽር ፣50 ሽጉጦች ፣8 የእጅ መትረይስ ከጠላት እጅ ተማርከዋል፡፡ በማለት በወቅቱ ተሳታፊ የነበሩት አባት አርበኞች በትውስት ይናገራሉ ፡፡ የከተማዋ ገበሬዎች የአዲስ ቅዳም ከተማን ጥንታዊ የገቢያ ማዕከልነት ሲገልፁት በጃን ሆይ ጊዜ አዲስ ቅዳሜ ቀን የገቢያ ማዕከል በመሆንዋ ሀይለኛ የሆነ የገቢያ ምርት የገቢያ ግብዓት ለነበራትየዳንግላ ገበያን ቅዳሜ ቀን በተመሳሳይ ይውል ስለነበር ዳንግላ የገበያ ግብአት በመቀነሱ ወደ ረዕቡ ቀን እንደቀየሩ በጊዜው የነበረው ታሪክ አዋቂ አውራጃ ገዥ ግራ አዝማች አየሁ ጀንበሬያስረዳሉ ሆኖም ግን የደርግ መንግስት ከገባ በኃላ የገብያተኛውን የስራ ቀን እንዲውል ማለትም ቅዳሜ በማህበረሰዱ ዘምድ ስንበት ውይምሀጥማኖታዊ በዓል ተብሎ ስለሚከበር ነው ፡፡ ይህ አዲስ ቅዳም የገበያ ማዕከል በትልቅ ሾላ ዛፍ ስራ ስለነበር በዚህ ጥላ በመጠለል ጠላ፣ አረቄ፣ዳቦና የተለያዩ ነገሮች በተጨማሪ ይሸጥበት እንደነበር ይነገራሉ ፡፡ ገበያው ሰፊና ጥንታዊ በመሆኑ እንስሳት፣ እህል፣ማር፣ቅቤ ፣ሸቀጣ ሸቀጥ ፣ቡናና ሌሎችም ይገበያዩበታል ፡፡ የከተማው አመሰራረት ከተማዋ የተመሰረተችው በሁለት አጥቢያ ዳኛ በሚተዳደር የሽንኩሪ ሚካኤል እና በዚምብሪ ኪዳነ ምህረት ባለአባቶች መሬት ሲሆን ይህቦታ 1936 በፊት የባለአባቶች መሬት እንጂ ምንም አይነት ቤቶች ያልነበሩበት ፣ለከማነትም ያልታቀደ አልፎ አልፎ ቆባ ዛፍ ያለበት እንዲሁም ገበያተኛው የሚገበያይበት ትልቅ የሾላ ዛፍ እንደነበር የቦታው ነዋሪ አባቶች ያስተውሳሉ፡፡ ከጣሊያን ሽንፈት ወረራ በኃላ ፣ጃንሆይ ከውጭ ሀገር ከተመለሱ በኃላ /ማለትም 1936 ዓ.ም/ የአዲስ ቅዳም ከተማ ለገበያ ቦታ ሰፋትና ድምቀት በማመን በወቅቱ የነበሩ አገው ምድር አውራጃ አስተዳዳሪ ደጅ አዝማች ያረጋል እረታ ሰብሳቢነት ፣ በባንጃ ወረዳ አስረዳዳሪ ቀኝ አዝማች ቸኮል ጀንበሬ ፣በለኮማ ባንጃ ምክትል አስተዳዳሪነት ፣በፊት አውራሪ ደስታ ወርቄ በተገኙበት ገበያ ቦታ በአካባቢው ህዝብና የመሬት ባለይዞታዎች ፈቃደኝነት የገቢያው ስፋት በመከለሉ ከዚያው በመነሳት ምክትል አስተዳደሩና ወረዳ ቤተ ክህነት እንዲሆነ ተወሰነ፡፡ በ1951 በገቢያው ዙሪያ በአካባቢው ቤት በሰረቱት ከተማዋ መቆርቆር ጀመረች ከዚያ በፊት ለምክትል ወረዳ እናቤተ ክህነት ቢሮ በስተቀር ምንም አይነት ቤት ያልነበረ ሲሆን ከ1951 ጀምሮ ግንወ/ ሮ የዝብነሽ ታመነ የተባለች ሴት የመሸታ መሸጫ የዳስ ጎጆ በጊዜው ከነበሩ መሬት ባለአባቶች ጠይቃ ስራች ፡፡ በኋላም እና ወ/ሮ ቦጌ ብዙነህ፣ነጋድራስ ቢረስ፣ አቶ አያሌው ፈንቴ እና ሌሎችም የመሬት ባለአባቶችና ሌላ አካባቢ የመጡ ከባለአባቶች መሬት እየገዙ የሳር ጎጆዎችን መስራት ጀመሩ፡፡ ነጋድራስ ቢረስ ወርቅነህ የከተማዋ ቆርቆሮ ነጋዴ ነበሩ ሲሆን ከአዲስ አበባ በበቅሎ በመጫን አምጥተው ከተማዋን ከሳር ቤት ወደ ቆርቆሮ ቤት በመቀየር ከተማዋም ከገጠር ወደ ከተማ በሚደረገው የነጋዴዎችና ሴተኛ አዳሪዎች ፍልሰት እየሰፋች መምጣቷን የከተማዋ ነዋሪዎች ያበስራሉ ፡፡ ወ/ሮ የዝብነሽ ታመነ የመጀመሪያ መሽታ ቤት/ጠላ እና አረቄ / ስትከፍት ወ/ሮ ቦጌ ብዙነሽ መጀመሪያ ከተማ ጠጅ ቤት እንደነበራቸው አባቶች ያወሳሉ ፡፡ መጀመሪያው ሰፈር የዶሮ ማነቂያ ሰፈር ይባላል ፡፡ ስያሜ የተሰጠውም ትንሽ አጣብቂኝ መንገድ ዛሬ ቴሌ ከመሰራቱ በፊት እንደነበር የሰፈሩ ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡
47496
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B0%E1%88%8A%E1%8A%93%20%E1%8C%8E%E1%88%98%E1%8B%9D
ሰሊና ጎመዝ
ሰልና ሜሪ ጎመዝ (ተወለደች ሀምሌ ፲፬፣ ፲፱፻፹፬) አሜሪካዊት ዘፋኝና ተዋናይት ናት። ሰልና፣ የትወና ህይወቷ ገና በልጅነቷ ሲጀምር ተሳትፋ ባርኒ ኤንድ ፍረንድስ የተለቭዥን ተከታታይ ላይ እና በዛው የእድሜ ክልል ውስጥ አለክስ ሩሶ የተባለ ገጸ ባህሪን በድዝኒ ቻነል የተለቭዥን ተከታታይ ውዘርድ ኦቭ ዌቭርሊ ፕሌስ ላይ ተጫውታ ወደ ዝናው መጣች እንደ ተዋናይት፤ እንደ አቀንቃኝት ከፖፕ ሮክ ቡድኗ ሰልና ጎመዝ & ዘ ሲንጋ እውቅና ብታገኝም የአሁን እሷነቷ በይበልጥ መገንባት የጀመረው በግል ባደረገችው ጉዞ ነው የመጀመሪያ አልበሟ እስታርዝ ዳንስ በ፳፻፭ ተለቀቀ የመጀመሪያ ምርጥ አስር ሙዚቃዋን የያዘው። እስከ ፳፻፱ ድረስ ሰልና ሽጣለች ከ፯ ሚልየን በላይ አልበሞች እና ከ፳፪ ሚልየን በላይ ነጠላዎች በአለምአቀፍ ይህ መረጃ ቢልቦርድን መሰረት አድርጎ። የተለያዩ ሽልማቶችን ስትወስድ ቢልቦርድ ሰይሟት ነበር "የአመቱ እንስት" በ፳፻፱። ማህበራዊ ድረገጾች ላይ አያሌ ክተላዎች ሲኖሯት በአንድ ወቅት ይበልጡን ተከታዮች በማፍራት ቀዳሚ ነበረች እንደ ግለሰብ፣ እንስትግራም ላይ። የሰልና ሌሎች የስራ ሙከራዎች ይካተታሉ፦ የመቀባቢያ፣ የአልባሳት፣ የሽቶ፣ እና የእጅ ቦርሳ ስራ ሙከራዎች። ሰልና ከብዙ ረጂ ተቋማትጋ አብራ የሰራች ሲሆን አገልግላለችም እንደ የዩንሰፍ አምባሳደር ከእድሜዋ ፲፯ ጀምሮ። የቀድሞ ህይወት ሰልና ተወለደች በ፲፱፻፹፬ ከአባቷ ርካርዶ ጆውል ጎመዝ እና ከመድረክ ተዋናይት እናቷ አማንዳ ዶውን ኮርንት። ስሟ የተሰየመው ከቲዠኖ አቀንቃኝቷ ሰልና ኩወንታኒላ በኋላ ነው። አባቷ የሜክሲኮ ዘር ሲኖረው እናቷ ደግሞ የተወሰነ የጣልያን። የህስፓንክ ማንነቷን አስመልክቶ ሰልና ብላለች እንደሆነች "የኩራት የሶስተኛ ትውልድ አሜሪካዊ፡ሜክሲኮአዊ" ፡ "ቤተሰቦቼ የኩንሲንረስ አከባበር አላቸው ፡ ወደ ኮምንየን ቤተ ክርስትያን እንሄዳለን፣ ካቶልክ የሆነ ምንም ነገር እናደርጋለን፣ ግን ባህላዊ ነገሮች ብዙም የሉንም መናፈሻ ሄዶ ባርብኪው ከማድረግ ውጪ እሁድ እሁድ ከቤተ ክርስትያን መልስ"። ሰልና የአባቷ ሀገር ቋንቋ የሜክሲኮ እስፓንሽን አቀላጥፋ መናገር ትችል ነበር እስከ እድሜ ሰባት ፡ በአምስት አመቷ ከእናቷጋ ብቻ ለመቅረት ሁኔታው አስገድዷት ነበር፦ የወላጆቿ መፋታት ፡ ሰልና ሁለት ታናናሽ ግማሽ እህቶች አሏት—አባትና እናቷ በፈጠረቱ ሌሎች የየብቻ ትዳሮች። ሰልና ተወለደች እናቷ የ፲፮ አመት ልጅ ሳለች ፡ ቤተሰቡ ገንዘብ ነክ ጉዳዮች ላይ ችግር ነበረበት በሰልና የልጅነት እድሜዎች ውስጥ ፡ ሰልና አንስታለች የአንድ ዶላር ሩብ መፈለግ እደነበረባቸው ለመኪና በንዚን ለማግኘት ብቻ ፡ "ፈርቼ ነበር ቤተሰቦቼ አንድ አልነበሩም፣ መቼም ብርሀን አይቼ አላውቅም ነበር በሸለቆው ጫፍ እናቴ ጠንክራ በምትሰራበት ለኔ የተሻለ ህይወት ለማቅረብ ፡ ምን ልሆን እንደምችል ሰግቼ ነበር እዛ (ቴክሳስ) ምቆይ የነበረ ቢሆን"። "እናቴ ጠንካ ነበረች በዙሪያዬ፣ እኔን በአስራ ስድስት አመቷ መውለዷ ትልቅ ሀላፊነት ነው፤ ሁሉን [ትታለች] ለኔ ብላ ሶስት መተዳደሪያ ስራዎችን ይዛለች፣ ደግፊኛለች፣ ህይወቷን መስዋዕት አድርጋልኛለች"። ሰልና በልጅነቷ ከአያቶቿ ጋ ቅርብ ግንኙነት የነበራት ሲሆን አሳልፋለች የተለያዩ የህዝብ በአላትን ከነሱጋ ከፍ ባለችበት ጊዜ ፤ ወላጆቿ ማስተማርን ሲጨርሱ ብዙ አነሱ አያቶቿ ነበር የሚንከባከቧት። ብላለች፦ "አሳድገውኛል" እስካገኘች ድረስ የስኬት ጅማሮን በትእይንት ፕሮግራሞች። የስራ ታሪክ ከትወና ሙያዋጋ እነዚ ፊልሞች (ተከታታዮች) ላይ ሰርታለች፦ አናዘር ስንደረላ እስቶሪ ፣ ፕርንሰስ ፕሮተክሽን ፕሮግራም ፣ ውዘረድ ኦቭ ዌቨርሊ ፕሌስ ፡ ዘ ሙቪ ፣ ርሞና ኤንድ ቢዙስ ፣ ሞንቴ ካርሎ ፣ እስፕሪንግ ብሬከርስ ፣ ጌት እዌይ ፣ ዘ ፋንድመንተልስ ኦቭ ኬሪይንግ ፣ ዘ ደድ ዶንት ዳይ ፣ ኧ ሬይኒ ዴይ ኢን ንው ዮርክ ፣ ኦንሊ መርደርዝ እን ዘ ቢውልዲንግ (፳፻፲፬-ሚቀጥል)፣ እና ሆተል ትራንስልቨንያ (፳፻፬-የቀጠለ)። በአስተዳዳሪነት አግዛለች የነት ፍለክስ ተከታታዮችን፦ 13 ሪዝንስ ዋይ እና ልቪንግ አንዶክመንትድ በአጋዥ፡ኩባንያዋ ስር። ለቃለች ፫ አልበሞች ከቡድኗ ሰልና ጎመዝ & ዘ ሲንጋ እና ሶስቱም አስር ውስጥ ገብተዋል ከቢልቦርድ ተመስክረዋልም የወርቅ በዘ ርኮርዲንግ ኢንደስትሪ አሶስዬሽን ኦቭ አሜሪካ፦ ኪስ & ተል ፣ ኧ ይር ውዝአውት ሬይን እና ወን ዘ ሰን ጎዝ ዳውን ። የግል ሶስት አልበሞቿ፦ እስታርዝ ዳንስ ፣ ርቫይቨል እና ሬር ሁሉም አንደኝነት ላይ የተቀመጡ። አስር ውስጥ የገቡላት ዘፈኖቿ፦ "ከም & ጌት እት"፣ "ዘ ሀርት ወንትስ ዋት እት ወንትስ"፣ "ጉድ ፎር ዩ"፣ "ሴም ኦልድ ሎቭ"፣ "ሀንድስ ቱ ማይሰልፍ"፣ "እት ኤንት ሚ"፣ እና የመጀመሪያ ቁጥር አንድ ዘፈኗ "ሉዝ ይው ቱ ሎቭ ሚ"። የሙዚቃ አይነት ሰልና የምትገለጸው እንደ ፖፕ አርቲስት ሲሆን ስራዎቿ ይከፋፈላሉ በአይነተ ሙዚቃዎች፦ ዳንስ፡ፖፕ እና ኢዲኤም፤ ሌሎች የሙዚቃ አይነቶችን መሞከሯ እንዳለ ሆኖ ፡ የመጀመሪያ አልበሟ ከቡድኗ ዘ ሲንጋ የለቀቀችው የኧለክትሮንክ ሮክ እና የፖፕ ሮክ ተጽእኖች ሲኖርበት አከታትላ ከዚ ቡድኗጋ የለቀቀቻቸው ዘፈኖች የዳንስ፡ፖፕ ድምጸ ምርጫ አለባቸው ፡ "ኧ ይር ዊዝአውት ሬይን" አልበም ታውቋል በስንት፡ፖፕ ባህሪያቶቹ፣ "ወን ዘ ሰን ጎዝ ዳውን" አልበም ደግሞ በይበልጥ ኧለክትሮፖፕ እና ድስኮፖፕ ዘውጎችን አካቷል። የግል የመጀመሪያ አልበሟ "እስታር ዳንስ" እጅጉን የኢዲኤም፡ፖፕ ተጽዕኖ የነበረበት ሲሆን የኧለክትሮንክ፣ ድስኮ፣ ተክኖ፣ እና የዳንስሆል ሙዚቃዊ ባህሪያቶች ነበሩበት። ዘፈኖቿ፦ "ዘ ሀርት ወንትስ ዋት እት ወንትስ" እና "ጉድ ፎር ዩ" በይበልጥ ጎልማ ፖፕን ነው ያስተዋወቁት በየክፍላቸው። ሰልና፣ ቀደም ባሉ ጊዜያት ብሩኖ ማርስን እንደ ተፅኖዋ ገልፃው ነበር፦ "የሙዚቃ አይነቱ በአጠቃላይ [ሁኔታው]፣ [በሙዚቃ] የሚቀርብበት መንገድ፣ እራሱን የሚይዝበት መንገድ" ብላለች። ክርስቲና አግወሌራ፣ ብርትኒ እስፒርስ፣ ቢዮንሴ፣ ሪሀናና ቴይለር እስዊፍትንም እንደ ተፀዕኖ ጠቅሳቸዋለች እነማ "እስታር ዳንስ" እና "ርቫይቨል" አልበሞቿ ላይ ተፅዕኖ ያሳደሩ የፖፕ ንጉሱ ማይክል ጃክሰን እህት ጃነት ጃክስን ተካታበት። የአሜሪካ ዘፋኞች የአሜሪካ የፊልም ተዋናዮች‎
17698
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8B%9D
መንዝ
መንዝ የሚለው ስያሜ የመጣው ከግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙና አመጣጡም መንዛት መርጨት ከሚለው ቃል የመጣ ሲኾን ሊቀ መልዐክቱ ቅዱስ ዑራኤል የጌታችንን ደም የረጨባት የምድር ማእከል ናት ፡፡ መንዝ ማለትም ደሙን የረጨበት ስለሆነ ነዝሃ መንዝ ተባለ ፡፡ ቅዱሱ ጽዋም እዚችው ምድር ሲገኝ ብዙ ምስጢራት ስላላት ከዚህ በላይ መናገር አልችለም ፡፡በጣምም ቅዱስ ስፍራ ነው ፡፡ መንዝ በሰሜናዊ ሸዋ የሚገኝ ክፍል ሲሆን በውስጡ ላሎ ምድርን በስተደቡብ፣ ጌራ ምድርን በስተሰሜንና ማማ ምድርን በመካከል ይዞ ይገኛል ። የመንዝ ድንበር በ3 ወንዞችና በአንድ ተራራ እንዲህ ይካለላል፦ ሞፋር ወንዝ (ደቡብ)፣ አዳባይ ወንዝና ወንጭት ወንዝ (ምዕራብ)፣ ቀጨኔ ወንዝ (በሰሜን) እንዲሁም በስተምስራቅ ከቆላው ኤፍራታ፣ ግድምና ቀወት የሚለየው የተራራ ሰንሰለት ናቸው ። ታሪክና ባህል መንዝ ለመጀመሪያ ጊዜ በታሪክ ተጠቅሶ የሚገኘው በቀዳማዊ አጼ አምደ ጽዮን ዜና መዋዕል ሲሆን በጊዜው መንዝሔል ይባል ነበር ። ቀጥሎም በአጼ በእደ ማርያም ዜና መዋዕል ተጠቅሶ ይገኛል ። መንዝ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ የያዘው በ17ኛው ክፍለ ዘመን መጠናቀቂያ፣ በነጋሲ ክርስቶስ ነበር። የመንዝ ተወላጁ ነጋሲ የአጋንጫ ኪዳነ ምህረትን ቤተክርስቲያን በመመሰረት ሲታወቅ የፍሩክታንም ደብር በማስፋፋት ይጠቀሳል። ነጋሲ ታላቁ እያሱን ለመጠየቅ በሄደበት በትክትክ በሽታ ሲያርፍ ልጁ ሰባስቲያኖስ ሸዋን ከመንዝ ሆኖ ያስተዳድር ነበር። ኋላ ላይ የተነሱት ንጉስ አብይ፣ ምንም እንኳ እናታቸው ከላሎ ምድር የመጣች ብትሆንም መስተዳድራቸውን ከመንዝ ወደ ሐር አምባ በማዛወራቸው የመንዝ ማዕከላዊነት ደበዘዘ። የሆኖ ሆኖ መንዝ ለሚቀጥሉት ዘመናት ታዋቂ መሪወችን በማፍራትና በማስተናገድ ትታወቃለች። ለምሳሌ የነጋሲ ዘር የሆነው መርድ አዝማች አስፋ ወሰን በ18ኛው ክ.ዘመን መጨረሻ ጠላቶቹ ሲያሳድዱት በፍሩክታ ኪዳነ ምህረት እንደተጠለለ ይነገራል። የንጉሥ ሣህለ ሥላሴ እናት ወይዘሮ ዘነበወርቅ፣ የነጋሲ ዘር ሲሆኑ ዋና ከተማቸውን በሰላ ድንጋይ፣ ላሎ ምድር መሥርተው ይኖሩ ነበር። እንዲሁም አቶ በዛብህ ("አባ ደቅር") የመንዝ ባላባት ሲሆኑ በዓፄ ቴዎድሮስ የአበጋዝ ሹም የነበሩና የአጠቃላይ ሸዋ አስተዳዳሪና ኋላ ላይ ከወደፊቱ ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሠራዊት ጋር በአምባ ዳየር ጦርነት አድርገው የተሸነፉ ናቸው። ቆይቶም ዓፄ ምንሊክ በአምባ አፍቃራ፣ መንዝ፣ ቤተ መንግሥትና የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤት ገንብተዋል። በኋላ በጣሊያን ወረራ ወቅት ለነበረው ትግል መንዝ ማዕከላዊ ሚናን ተጫውቷል። ባህላዊ መልክዓ ምድር መንዝ እጅግ ለም የሆነ መሬት የሚገኝበት ሲሆን ጥሩ ዝናብ ሲገኝ በአመት እስከ 3 ጊዜ እህል ማጨድ ይቻላል። የአየር ጸባዩም፣ ከከፍታው አንጻር ደጋማ ሲሆን በደቡቡ ማማ ምድር የሚገኘው የአየር ንብረት ወይና ደጋማ ነው። ይህ ሆኖ እያለ የመሬቱ ተራራማ አቀማመጥ ከሞላ ጎደል በዚህ አካባቢ የሚደረግን ግብርና ከባድ ያደርገዋል። በመንዝ የሚገኙ ቤቶች በባህር ዛፍ እና ጥድ የሚታጀቡ ሲሆን አቀማመጣቸውም ተሰባጥረው ነው። በሞላሌ የሚገኘው የቅዳሜ ገበያ እስከ 2000 ሰወችን ያስተናግዳል። ከከፍታው አንጻር፣ ብዙው የመንዝ አካባቢ ብርዳማ ስለሆነ ልብስ የሚሰራው ከሪዝ () ነው። ይህም ልብስ ባና ይባላል። እንጀራም ብዙ ጊዜ ከገብስ የሚጋገር ሲሆን የመንዝ ሰወች ውርጩንና ንፋሱን ለመከላከል ቤቶቻቸውን ከእንጨትና ጭቃ ይልቅ ከድንጋይ መሰራት ያዘወትራሉ። ከዚህ እና መሰል ባህላዊ ቅርሶች አንጻር በአካባቢው ሕዝብ ዘንድ መንዝ «የአማራ ምንጭ» በመባል ይታወቃል። በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንና ደብር ስብጥር የሚገኘው በመንዝ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ ምስራቃዊ ( የመንዝ ሃዋርያ) ለአካባቢው ህዝብ ክርስትናን እንደሰበከ ትውፊት አለ። እንደ ታሪክ ተመራማሪወች አባባል ይህ ሰው በአጼ አምደ ጽዮን ዘመን የነበረው ዮሐንስ ዘቀላት ሲሆን በአቡነ ያቆብና የደብረ ሊባኖሱ እጨጌ ፍሊጶስ ታዞ በ1322 ዓ.ም. ይተጋ የነበረ ሓዋርያ ነው። አብያተ ክርስቲያናት ፍሩክታ ኪዳነ ምህረት -- ጌራ ምድር የሚገኝ ደብር ሲሆን ሁለት ህንጻወችን ያካትታል። አንደኛው ከአጼ ዘርአ ያዕቆብ ዘመን የሚመነጭ ሲሆን ሁለተኛው ከልጅ እያሱ ዘመን ይጀምራል። አፍቀራ ኪዳነ ምህረት -- አምባ አፍቀራ ላይ የሚገኝ ቤ/ክርስቲያን ሲሆን በነጋሲ ክርስቶስ የተቋቋመ ነው። አፍቀራ ገብርኤል -- አምባ አፍቀራ ላይ የሚገኝ። አፍቀራ ሥላሴ -- በአቡነ ተክለሃይማኖት ዘመን የተቋቋመ. በምባ አፍቀራ ላይ የሚገኝ። ይልማ ገዳም -- በሰሜን ምዕራብ የመንዝ ጠረፍ የሚገኝ ሲሆን የባለ እጅ ገዳም በመባል ይታወቃል። በዚህ ገዳም፣ ወንዶችም ሆነ ሴቶች፣ የሸክላ ስራወችን ያመርታሉ ስለሆነም የባለ እጆች ገዳም ይባላል። አርበራ መድሃኔ አለም -- ከዋሻ አለት የተሰራና የተለያየዩ አጽዋማት የሚገኙበት ገዳም ጓሳ ሜዳ የጓሳ ሜዳ በመንዝ የሚገኝ፣ወደ 110 ኪሎ ሜተር ስኩየር የሚጠጋ ስፋት ያለው፣ ከኢትዮጵያም ሆነ አፍሪካ ትልቁ የአፍሮ አልፓይን ስርዓተ ህይወት ቅሪት ነው። በዚህ ሜዳ 26 ምንጮች ሲኖሩ ቦታው ሳይታረስ ለ400 አመታት የተለያዩ ብርቅ እንስሳት (ምሳሌ፡- ጭላዳ ዝንጀሮ (200 የሚጠጉ) ፣ ቀይ ቀበሮ (ከ20 እስከ 50 ብቻ የሚደርሱ) ፣ አጋዘን፣ ወዘተ...) መኖሪያ በመሆን አገልግሏል። የአካባቢው ሕዝብ የዚህን ጉዳይ መሰረት ሲያስረዱ፣ ከላይ የተጠቀሰው ጻዲቁ ዮሐንስ ምስራቃዊ በዚህ አካባቢ ሲኖር ሳለ አንዲት ሴት በውሸት አስረግዞኛል ብላ ከሰሰችው። የአካባቢውም ሕዝብ ይህን ክስ ከጻዲቁ ፊት እንድትደግም አደረጓት እርሷ ግን ክሱን መድገም ብቻ አይደለም "ከዋሸሁ ድንጋይ ያድርገኝ" ብላም ጨመረች። በዚህ መሰረት ንግግሯን ሳታቋርጥ ወደ ድንጋይ ተቀየረች። ጻዲቁም በማዘን ሜዳው ምንም እህል እንዳያበቅል ተራገመ። በዚህ መሰረት በጥሩ ጤፍ ምርቱ ይታወቅ የነበረው ጓሳ የተለያዩ አውሬዎች መኖሪያ ኾነ። በአኹኑ ወቅት በጓሳ ሜዳ 7 ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ አጥቢ እንስሳት ይገኛሉ - ይህም ከአጠቃላዩ ኢትዮጵያ ብቻ ከሚገኙት አጥቢ እንስሳት 22.6% ነው። 111 የወፍ አይነቶች በመንዝ ሲገኙ ሰባቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ ናቸው።
52003
https://am.wikipedia.org/wiki/Interrupt
Interrupt
በዲጂታል ኮምፒውተሮች ውስጥ፣ ኢንተራፕት ማለት ከሶፍትዌሩ ትኩረት የሚፈልግ ክስተት በሚኖርበት ወቅት ፕሮሰሰሩ የሚሰጠው ምላሽ ነው። የኢንተራፕት ሁነት ፕሮሰሰሩ በማሳወቅ፣ ሲፈቀድለት አሁን ላይ እየሰራ ያለን ኮድ ፕሮሰሰሩ እንዲያቋርጥ በማድረግ፣ ሁነቱ ጊዜውን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወን ያደርጋል። ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ፣ ፕሮሰሰሩ የአሁን ላይ ስራዎቹን በማስቆም መልስ ይሰጣል፣ ስቴቱን ያስቀምጣል፣ እና ኢንተራፕት ሃንድለር (ወይም የኢንተራፕት ሰርቪስ ሩቲን፣ አይ.ኤስ.አር () የሚል መተግበሪያን በመጠቀም ለሁነቱ ምላሽ ይሰጣል። ይህ መስተጓጎል ጊዜያዊ ነው፣ እናም ኢንተራፕቱ ከባድ ችግር እስካልጠቆመ ድረስ፣ ፕሮሰሰሩ መደበኛ ስራውን ይቀጥላል ኢንተራፕት ሃንድለሩ ሲጨርስ። ኢንተራፕቶች በመደበኛነት በሃርድዌር መገልገያዎች ጥቅም ላይ የሚውሉ ሲሆን የኤሌክትሮኒክ ወይም የአካላዊ ሁነት ለውጦች ትኩረት እንደሚያስፈልጋቸው ለመጠቆም ጥቅም ላይ ይውላሉ። በተጨማሪም ኢንተራፕቶች ኮፕፒውተር ብዙ ስራ በሚሰራበት ጊዜ፣ በተለይ በሪል ታይም የኮምፒውቲንግ ስራ ጊዜ ለመተግበር ነው። ኢንተራፕትን በእዚህ መልኩ የሚተገብሩ ሲስተሞች ኢንተራፕት-መራሽ ይባላሉ። የኢንተራፕት ምልክቶች በሃርድዌር ወይም ሶፍትዌት ለውጦች ሊሰጡ ይችላሉ። እነዚህም በቅደም ተከተል፣ የሃርድዌር እና የሶፍትዌር ኢንተራፕቶች ተብለው ይከፈላሉ። ለአንድ የተወሰነ ፕሮሰሰር፣ የኢንተራፕር አይነቶች ቁጥር በአርኪቴክቸሩ ይወሰናል። የሃርድዌር ኢንተራፕቶች የሃርድዌር ኢንተራፕት ከሃርድ ዌሩ ሁነት ጋር የሚገናኝ ሲሆን በውጪያዊ የሃርድዌር መገልገያ ምሳሌ የኢንተራፕት ጥያቄ () የኮፒውተር መስመር፣ ወይም በፕሮሰሰር ሎጂክ ወስጥ መካተታቸው የታወቁ መገልገያዎች (ምሳሌ የሲፒዩ ሰአት ያዥ በአይ.ቢ.ኤም. ሲስተም/370)፣ መገልገያው ከኦፕሬቲንግ ሲስተሙ (ኦ.ኤስ) ትኩረት እንደሚፈልግ ወይም፣ ኦ.ኤስ ከሌለም ሲ.ፒ.ዩውን ከሚያንቀሳቅሰው ከ”ቤር ሜታል” ፕሮግራም ትኩረት እንደሚፈልግ ማሳያ ነው። እንደዚህ አይነት የውጪ መገልገያዎች የኮምፒውተሩ አካል ሊሆኑ ይችላሉ (ምሳሌ፣ ዲስክ ኮንትሮለር)፣ ወይም ወጪያዊ ፔሪፈራልስ (ተቀጽላዎች)። ለምሳሌ፣ የኪቦርድ ቁልፍ መጫን ወይም በ/2 ቦታ የተሰካ ማውስ ማንቀሳቀስ የሃርድዌር ኢንተራፕቶቹን በማስነሳት ፕሮሰሰሩ የኪቦርድ መጫንን ወይም የማውስ ቦታን እንዲያውቅ ያደርጋል። የሃርድዌር ኢንተራፕቶች ከፕሮሰሰር ሰአቱ ጋር ሳይናበቡ ሊደርሱ ይችላሉ፣ እናም በትእዛዝ ማስፈጸም ጊዜ በየትኛውም ሰአት ሊመጡ ይችላሉ። በቀጣይነትም፣ ሁሉም የሃርድዌር መልእክቶች ከፕሮሰሰር ሰአቱ ጋር እንዲናበቡ በማድረግ እና ድንበራቸውን በጠበቀ ትእዛዝ መልኩ ይፈጸማሉ። በብዙ ሲስተሞች ውስጥ፣ እያንዳንዱ መገልገያ ከተወሰነ የ ሲግናል ጋር ይቆራኛል። ይህም የትኛው ሃርድዌር አገልግሎት እየጠየቀ እኝደሆነ በቀላሉ ለመለየት እናም ለእዛ መገልገያ አገልግሎት ማቅረቡን ለማፋጠን ይረዳል። በተወሰኑ የድሮ ሲስተሞች ውስጥ ሁሉም ኢንተራፕቶች ወደ አንድ ቦታ የሚላኩ ሲሆን ኦፕሬቲንግ ሲስተሙ ከፍተኛ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ያልተገለጡ ልዩ ትእዛዞችን ለመለየት ያስችላል። በአሁን ወቅት ያሉ ሲስተሞች ደግሞ፣ የተለየ የኢንተራፕት ሂደት ለእያንዳንዱ የኢንተራፕት አይነት ወይም ለእያንዳንዱ የኢንተራፕት ምንጭ፣ በብዛት እንደ አንድ ወይም ከእዚያ በላይ የቬክተር ቴብሎች ይተገበራል። ማስክ ማድረግ ፕሮሰሰሮች በአይነተኛነት ውስጣዊ የሆነ የኢንተራፕት ማስክ መመዝገቢያ አላቸው፣ ይህም እየመረጡ የሃርድዌር ኢንተራፕቶችን እንዲያበሩ ወይም እንዲያጠፉ ይረዳል። እያንዳንዱ የኢንተራፕት ሲግናል በማስክ ሬጂስተሩ ውስጥ የተያያዘ ነው፣ በተወሰኑ ሲስተሞች ውስጥ፣ ኢንተራፕቱ ቢቱ በሚዘጋጅበት ወቅት ይበራል እና ቤቱ ባዶ በሚሆንበት ወቅት ይጠፋል፣ በሌሎች ላይ ደግሞ ቀድሞ የተመደበ ቢት ኢንተራፕቱን ያጠፋዋል። ኢንተራፕቱ በሚጠፋበት ወቅት፣ የተገናኘው የኢንተራፕት ሲግናል በፕሮሰሰሩ ይታለፋል። በማስኩ ተጽእኖ የሚፈጠርባቸው ሲግናሎች ማስክ መደረግ የሚቻልባቸው ኢንተራፕቶች ይባላሉ። አንዳንድ የኢንተራፕት ሲግናሎች በኢንተራፕት ማስኩ ጫና አይደረግባቸውም ስለዚህም መጥፋት አይችሉም፣ እነዚህ ማስክ መደረግ የማይችሉ ኢንተራፕቶች ይባላሉ ()። በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ችላ ሊባሉ የማይገባቸውን ከፍትኛ ትኩረት የሚፈልጉ ሁነቶችን፣ እንደ ከዋችዶግ ጊዜ መያዣ የሚሰጡ የጊዜ አልፏል ማሳወቂያዎችን ይጠቁማሉ። አንድን ኢንተራፕት ማስክ ማድረግ ማለት ማጥፋት ሲሆን፣ ማስኩን ማስወገድ ማለት ማብራት ማለት ነው። አስመሳይ ኢንተራፕቶች የአስመሳይ (ስፑሪየስ) ኢንተራፕት ማለት የሃርድዌር ኢንተራፕት ሆኖ ምንም ምንጭ ሊገኝለት ያልቻለ ማለት ነው። “ፋንተም ኢንተራፕት” ወይም “ጎስት ኢንተራፕት” ይህንን ሁነት ለመጠቆም ይውላሉ። የአስመሳይ ኢንተራፕቶች ዋየርድ-ኦ.አር () ኢንተራፕት ሰርኪውት ለፕሮሰሰር መግቢያው የደረጃ-ሴንሴቲቭ ጋር ችግር ይሆናል። እንደዚህ አይነት ኢንተራፕቶች ሲስተሙ በሚያስቸግረበት ወቅት መለየት አስቸጋሪ ናቸው። በዋየርድ-ኦ.አር () ሰርኪውት ውስጥ፣ የፓራሲቲክ ካፓሲታንስ ቻርጅ ማድረግ/ዲስቻርጅ ማድረግ በኢንተራፕት መስመሩ ባያስ ሬዚስተር ፕሮሰሰሩ አውቆ የተወሰነ መዘግየት መኖሩን ከዛም የኢንተራፕት ምንጩ እስኪጸዳ ያደርጋል። ኢንተራፕት የሚያደርገው መገልገያ በጣም ቆይቶ ከጸዳ የኢንተራፕት ሰርቪስ ሩቲን ()፣ የአሁን እስኪመለስ የዝምታ ጊዜ ለማሳለፍ እና የኢንተራፕት ሰርኪውቱ እስኪመለስ በቂ ጊዜ አይኖርም። ውጤቱ የሚሆነው፣ ፕሮሰሰሩ ሌላ ኢንተራፕት ሊኣጋጥም ነው ብሎ ይገምታል፣ ምክኒያቱም የኢንተራፕት ጥያቄ በሚያቀርብበት ወቅት ቮልቴጁ በበቂ ሁኔታ ከፍ ብሎ የውስጣዊ ሎጂክ 1 ወይም ሎጂክ 0 ለምፍጠር አይበቃም። የሚታየው ኢንተራፕት የሚለይ ምንጭ አይኖረውም፣ ስለዚህም “አስመሳይ” ሞኒከር ይሆናል። የአስመሳይ ኢንተራፕት በተሳሳተ የሰርኪውት ዲዛይን፣ ከፍተኛ የድምጽ መጠኖች፣ ክሮስቶክ፣ የሰአት አተባበቅ ችግሮች የኤሌክትሪካል ስህተቶች ውጤት ሊሆንም ይችላል፣ ወይም በብዛት ባያጋጥምም፣ የመገልገያ ኢራታ ሊሆን ይችላል። አስመሳይ ኢንተራፕት የሲስተም መቆለፍ ወይም ሌላ ያልተገለጸ ኦፕሬሽን ሊያስከትል ይችላል የተሳሳተ ኢንተራፕት ሊያጋጥም ይችላል ብሎ ከግምት ውስጥ ካላስገባ። አስመሳይ ኢንተራፕቶች በብዛት የዋየርድ-ኦ.አር () ውጤት እንደመሆናቸው፣ በእነዚህ አይነት ሲስተሞች ውስጥ ጥሩ የፕሮግራሚንግ ስራ ለ ሁሉንም የኢንተራፕት ምንጮች እንዲያውቅ እና ምንም ውስኔ እንዳይወስድ (ከመመዝገብ ባላለፈ) የትኛውም ምንጮች ኢንተራፕት እያደረጉ ካልሆነ። የሶፍትዌር ኢንተራፕቶች የሶፍትዌት ኢንተራፕት የተወሰኑ ትእዛዞችን ወይም የተወሰኑ ሁኔታዎች በሚሟሉበት ጊዜ በፕሮሰሰሩ የሚጠየቅ ነው። እያንዳንዱ የሶፍትዌትር ኢንተራፕት ሲግናል ከተወሰነ የኢንተራፕት ሃንድለር ጋር የተገናኘ ነው። የሶፍትዌር ኢንተራፕት ልዩ የሆነ ትእዛዝን በመፈጸም አውቆ ሊፈጸም ይችላል፣ በዲዛይን፣ ሲፈጸም ኢንተራፕትን ያስከትላል። እንደነዚህ አይነት ትእዛዞች ከንኡስ-ሩቲን ጥሪዎች ጋር በተመሳሳይነት ይሰራሉ እና ለብዙ አይነት አገልግሎቶች ጥቅም ላይ ይውላሉ፣ እንደ የኦፕሬቲንግ ሲስተም አገልግሎቶች እና ከመገልገያ ድራይቨሮች ጋር አብሮ መስራት (ምሳሌ የሚቀመጥ ሚዲያን ማንበብ ወይም መጻፍ)። የሶፍትዌር ኢንተራፕቶች ባልተጠበቀ ሁኔታ በፕሮግራም ማስፈጸም ስህተቶች ምክኒያት ሊመጡ ይችላሉ። እነዚህ ኢንተራፕቶች በአይነተኝነት ትራፖች ወይም ኤክሰፕሽኖች ተብለው ይጠራሉ። ለምሳሌ፣ በዜሮ አካፍል የሚባል ኤክሲፕሽን “ይወገዳል” (የሶፍትዌር ኢንተራፕት ይጠየቃል) ፕሮሰሰሩ የማካፈል ትእዛዝ ተሰጥቶት አካፋዩ ዜሮ ከሆነ። በአይነተኝነት፣ ኦፕሬቲንግ ሲስተሙ እንደዚህ አይነት ኤክሰፕሽኖችን ይይዝና መልስ ይሰጣቸዋል።
48461
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B6%E1%88%80%E1%89%A3%20%28sahabah%29/%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%88%9B%20%E1%89%A2%E1%8A%95%E1%89%B5%20%E1%8A%A0%E1%89%A1%E1%89%A0%E1%8A%AD%E1%88%AD%28%E1%88%A8.%E1%8B%90%E1%8A%95%E1%88%81%E1%88%9B%29
ሶሀባ (sahabah)/አስማ ቢንት አቡበክር(ረ.ዐንሁማ)
🎀አስማ ቢንት አቡበክር ረዲየላሁ ዐንሃ📤 <<ከአክስቴ አዒሻና ከናቴ አስማ የበለጡ ርኀሩኀ ሴቶች እስካሁን አላየሁም>>(አብደላህ ኢብኑ ዙበይር ረዲደላሁ ዐንሁ) ✍አስማ ቢንት አቡበክር ረዲየላ ሁ ዐንሃ ከተከበረ ሙስሊም ቤተሰ ብ የተገኘች ሴት ስትሆን አባቷ-አ ቡበክር-የነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወ ሰለም የልብ ወዳጅና ወራሽ (ኸሊ ፋ)ነበሩ።እህቷ-አዒሻ ረዲየላሁ ዐን ሃ የነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሚስትና ከኡሙ ሙእሚኒን (የምእ መናን እናት)አንዷ ነበረች።ባለቤቷ ዙበይር ኢብን አል አዋም ረዲየላሁ ዐንሁ የነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰ ለም ልዩ አማካሪዎች ከነበሩት አን ዱ ሲሆን፥ልጇ አብዱላህ ኢብኑ ዙ በይር ረዲየላሁ ዐንሁ ለሐቅ በነበረ ዉ ቀናዒነትና ጥንካሬ እጅግ የታወ ቀ ሰዉ ነበር። ✍አስማ ረዲየላሁ ዐንሃ ኢስላምን ለመጀመሪያ ጊዜ ከተቀበሉት ሙስ ሊሞች ጋር ትመደባለች።ወደ ኢስላ ም በመግባት ወንዶችንና ሴቶችን ጨምሮ አስራ ሰባት ሰዎች ብቻ ና ቸዉ የሚቀድሟት።አስማ ረዲየላሁ ዐንሃ፥የነብዩን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰ ለም የመዲና ጉዞ ዕቅድ ሚስጥር በነበራቸዉ ዝግጅት ምክንያት የጉ ዞዉ ሚስጢራዊነት በከፍተኛ ጀረ ጃ የተጠበቀ ነበር።በስንብታቸዉ ምሽት አስማ ረዲየላሁ ዐንሃ በአን ድ አገልግል ምግብና በሁለት ከረ ጢቶች ዉኃ ሞላች።ለከረጢቶቹ መ ቋጠሪያ ገመድ በማጣቷም የወገ ቧን መቀነት (ኒታቅ)ፈታች።አባቷ አ ቡበክርም ረዲየላሁ ዐንሁ ለሁለት እንድትሰነጥቀዉ ነገሯት።ነብዩም ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተግባሯን አደነቁ።በዚህ ምግባሯ ነበር <<ባ ለሁለት መቀነቷ>>(ዛት አን-ኒታቀይ ን)በመባል የታወቀችዉ። ✍የመጨረሻዉ ሂጅራ በነብዩ ሰለ ላሁ ዐለይሂ ወሰለም መካን መልቀ ቅ ከተፈፀመ በኃላ አስማ ረዲየላ ሁ ዐንሃ አረገዘች።እንደሌሎቹ የነ ብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሶሃባ ዎች ሁሉ፥እርሷም ሆነች ባልተቤቷ ከነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስ ደት በኃላ በመካ የመኖር ፍላጎት አልነበራቸዉም።እርግዝናዋም ሆነ የመንገዱ እርቀት ሳይበግሯት ወደ መዲና ጉዞ ተነሳች።በመዲና ዳርቻ ላይ ከምትገኝ ቁባ ከምትባል ሥፍ ራ እንደደረሱ ፥አብደላህ የተባለ ወ ንድ ልጅ ወለጀች።የልጁ መወለድ ታራካዊነት ስለነበረዉ በሙስሊሞ ች ዘንድ በተክቢራና ተህሊል የገለ ፁትን ደስታ ፈጠረ። ✍አስማ በመልካም ሥነ-ምግባሯ ና በልበ ብርሃንነቷን በዘመኑ የታወ ቀች ሴት ነበረች።ርኀራኄዋን በተ መለከተ ልጇ አብዱላህ በአንድ ወ ቅት እንዲህ ሲል የአማኝነት ቃሉን ለግሷል።<<ከአክስቴ ከአዒሻና ከእ ናቴ ከአስማ የበለጡ ርኀሩኀ ሴቶች እስከአሁን ድረስ አላደሁም።የሁለ ቱ ሴቶች ርኀራሄ የተለያየ ገጽታ ነበ ረዉ።አክስቴ በቂ የመሰላትን ያህ ል ማጠራቀሟን ካረጋገጠች በኃላ ለችግረኞቹ ታከፋፍለዋለች።እናቴ በ በኩሏ ለነገ የሚል ሐሳብ የላትም። እጇ ላይ የገባዉን ሁሉ ወዲያዉኑ ለተቸገረ ትለግሳለች።>> ✍የአስማ ረዲየላሁ ዐንሃ ልባምነ ት እጅግ የሚደንቅ ነዉ።ለቤተሰባ ቸዉ አንዳች ነገር ላይተዉ ስድስት ሺህ ዲርሃም የሚቀልጥ ንብረታቸ ዉን ጠራርገዉ ነበር ወደ መዲና የ ተጓዙት።በዚያን ጊዜ ሙሽሪክ የነበ ሩት የአቡበከር አባት አቡ ቁሓፋህ የልጃቸዉን ወደ መዲና መጓዝ እን ደሰሙ ቤታቸዉ ድረስ በመሄድ ለአ ስማ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ አሏት፦ <<ካለ ገንዘብ ትቶሽ እንደሄደ እር ግጠኛ ነኝ።>>አስማም ረዲየላሁ ዐንሃ <<አይደለም፥አያቴ ሆይ፥(አባ ቴ)በቂ ገንዘብ ትቶልን ነዉ የሄደዉ ።>> ስትል መለሰችላቸዉ።ጥቂት ገንዘብ መሰል ጠጠሮችን በገንዘ ብ ማስቀመጫ ትንሽ ሳጥን ዉስ ጥ አኖረቻቸዉ።በጨርቅ ከሸፈነቻ ቸዉ በኃላ አይነ ስዉሩ አያቷ በእጃ ቸዉ እንዲሳስሱት በማድረግ <<አ የህ!ምን ያህል ገንዘብ አባቴ ትቶል ን እንደሄደ>> አለቻቸዉ። ✍አስማ ረዲየላሁ ወንሃ ይህንን ስልት የተጠቀመችዉ ሙሽሪኩ አ ያቷ ገንዘብ የላቸዉም በሚል ከኔ ዉሰዱ እንዳይሉ በመስጋቷ ሲሆን ከርሳቸዉ መዉሰዱን የጠላችበት ምክንያትም ምንም እንኳን አያቷ ቢሆኑ ከሙሽሪክ (አጋሪ)ሰዉ እርዳ ታ መቀበል ኢስላማዊ ሰብዕናዋን እንደማዋረድ ስለቆጠረችዉ ነዉ። ✍አስማ ረዲደላሁ ዐንሃ በእናቷ ም ላይ ተመሳሳይ አቋም ነበራት። ክብሯን እና ኢማኗን ለድርድር የማ ቅረብ ዝንባሌ በጭራሽ አልታየባት ም።በቅድመ ኢስላም ከአባቷ ጋር የተፋታችዉ እናቷ ቀቲለህ አንድ ወ ቅት በመዲና ሳለች ልትጎበኛት መ ጣች።ኢስላምን ያልተቀበለችዉ እና ቷ ወደርሷ ስትመጣ ደረቅ ኮምጣ ጤ፣የተጣራ ቅቤ...ይዛላት ነበር።አ ስማ ረዲደየላሁ ዐንሃ አስቀድማ ለ እናቷ የመግባት ፍቃድ አልሰጠች ም፥ያመጣችዉን ስጦታም አልተቀ በለችም።አንድ ሰዉ ወደ አዒሻህ ረ ዲየላሁ ዐንሃ በመላክ መዉሰድ ስ ለሚገባት ርምጃ ከነብዩ ሰለላሁ ዐ ለይሂ ወሰለም ጠይቆ እንዲመጣ አደረገች።ነብዩም ሰለላለሁ ዐለይ ሂ ወሰለም እናቷን ወደቤት እንድታ ስገባ፥ስጦታዋንም እንድትቀበል አ ዘዟት።በዚህን ጊዜም የሚከተለዉን የቁርኣን አንቀፅ ተደነገገ። ከነዚያ በሃይማኖት ካልተጋደሏች ሁ፥ከአገሮቻችሁም ካላወጡዋች ሁ (ከሓዲዎች)፥መልካም ብትዉሉ ላቸዉና ወደነርሱ ብታስተካክሉ አላ ህ አይከለክላችሁም፤አላህ ትክክለ ኞችን ይወዳልና።አላህ የሚከለክላ ችሁ፥ከነዚያ ከሃይማኖት ከተጋደሉ ዋችሁ፥ከቤቶቻችሁም ካወጡዋች ሁ፥እናንተንም በማዉጣት ላይ ከ ረዱት (ከሓዲዎች)፥እንዳትወዳጁ ዋቸዉ ብቻ ነዉ።>>[አል ሙምተ ✍ለአስማም ረዲየላሁ ዐንሃ ሆነ ለበርካታ ሙስሊሞች የመጀመሪያ ዉ የመዲና ኑሮ ቀላል አልነበረም። ባሏ ችግረኛ ነበር።ቀደም ሲል ከገ ዛዉ ፈረስ በስተቀር አንዳችም ሀብ ት አልነበረዉም።ያንን ጊዜ አስማ ረ ዲየላሁ ዐንሃ እንደሚከተለዉ ትገ ልፀዋለች፦ <<ለፈረሱ ድርቆሽና ዉ ሃ ከሰጠሁ በኃላ የሰዉነቱንም ጽዳ ት እጠብቅለታለሁ።ዱቄት ፈጭቼ ም እጋግራለሀ።ግና ጋግሬም የተ ዋጣ ስለማይሆንልኝ ብዙዉን ጊዜ የአንሷር ሴቶች ይጋግሩልኛል።በጣ ም ጥሩ ሴቶች ነበሩ።ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ለዙበይር ረዲየላ ሁ ዐንሁ እንዲያደርሰዉ ከወሰኑለ ት መሬት ላይም እህል በራሴ ተሸ ክሜ እመጣለሁ።ይህ የእርሻ ቦታ ከከተማ ወደ ፈርሰኽ (18 ኪ•ሜ ያህል ይርቃል)።>> ✍አስማ ረዲየላሁ ዐንሃ እጅግ ጥ ንቁቅና ታታሪ ሴት ነበረች።ችግራቸ ዉ ቀስ በቀስ እስኪወገድላቸዉ ድ ረስም ከባሏ ጋር ጠንክረዉ ሰሩ።ዙ በይር ረዲየላሁ ዐንሁ ቀስ በቀስ ከ ሶሃባዎች ሁሉ እጅግ የታወቀ ባለፀ ጋ ሆነ።ሀብት ማግኘታቸዉ አስማን ረዱየላሁ ዐንሃ ቅጥያጣ ኑሮ እንድ ትከተል አላረደጋትም።እንደወትሮ ዋ ሁሉ በኢማኗ ላይ የፀናች ሴት ነ በረች።አንድ ወቅት ልጇ ሙንዚር ዋጋዉ ዉድ ከሆነ ክር የተሰራ ድን ቅ ቀሚስ ከኢራቅ ላከሊት።በጊዜ ዉ አይነ ሥዉር የነበረችዉ አስማ ረዲየላሁ ዐንሃ ቀሚሱን ዳብሳ ድን ቅነቱን በተረዳች ጊዜ ከፍተኛ ሐዘን ተሰማት፤ለመልእክተኛዉም ሰለላ ሁ ዐለይሂ ወሰለም <<ይህ ለኔ የ ሚገባ አይደለምና ወደርሱ መልስ ለት።>> ስትል አዘዘችዉ።ሙንዚር በሁኔታዉ ተበሳጭቶ <<እማማ፥ሰ ዉነትን የሚያሳይ ቀሚስ አይደለም ።>>ሲል ገለፀላት። ✍እርሷንም በቁጣ <<የሰዉነትን መልክ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል፥ነ ገር ግን ጠባብ ስለሆነ የሰዉነትን ቅርፅ ያሳያል።>> ስትል መለሰችለ ት አልሙንዚር የእናቱን አለመስማ ማት እንዳረጋገጠ ከእርሷ ፈቃድ ጋ ር የሚሄድ ሌላ ቀሚስ ገዛላት። ✍የአስማን ረዲየላሁ ዐንሃ የኢማ ን ጥንካሬ የሚያሳይ ከላይ የጠቀ ስነዉ ገጠመኟ በቀላሉ ሊረሳ ይች ል ይሆናል።ነገር ግን ከልጇ ከአብ ደላህ ረዲየላሁ ዐንሁ ጋር ለመጨ ረሻ ጊዜ በተገናኙበት ወቅት ያሳየ ችዉ ጥልቅ አስተዋይነት፣ታጋሽነት ና የኢማን ጥንካሬ ከቀደምት ሙስ ሊሞች ታሪክ ዉስጥ የሚዘነጉ አይ ✍ከየዚድ ኢብን ሙዓዉያህ ሞት በኃላ የኸሊፋዉን ቢሮ የመራዉ አ ብደላህ ረዲየላሁ ዐንሁ ነበር።የሂ ጃዝ፣የምስር (ግብፅ)፣የኢራቅ፣የኹ ራሳን አብዛኛዉ የሶሪያ ህዝብ የር ሱ አፍቃሪ ስለነበሩ የኸሊፋነት ስል ጣኑ ለእርሱ እንዲረጋ ወሰኑ።ነገር ግን በኑ ኡመያዎች ድርጊቱን በመ ቃወምና ኸሊፋዉን በመንቀፍ አል-ሃጃጅ ኢብን ዩሱፍ በተባለዉ ሰዉ የሚመራ ትልቅ ሰራዊት አንቀሳቀ ሱ።በሁለቱም ወገኖች መካከል ጠ ንካራ ዉጊያ ተደረገ።በዚህም ፍል ሚያ አብዱላህ ኢብን ዙበይር ረዲ የላሁ ዐንሁ ብዙ የጀግንነት ተግባ ራትን አሳየ።ነገር ግን አብዛኞቹ አጋ ሮቹ የጦርነቱን ፈታኝነት መቋቋም ስለተሳናቸዉ ጥለዉት ሸሹ።በመ ጨረሻ እሱም ዉጊያዉን ትቶ መካ በሚገኘዉ ቅዱስ መስጊድ ለጥገ ኝነት ገባ። ✍ በዚያን ጊዜ ነበር እርጅና ተጭ ኗት አይነ ሥዉር የሆነች እናቱን ለ መጎብኘት ወደ አስማ ረዲየላሁ ዐ ንሁ ዘንድ የሄደዉ።ከዚያም እንደደ ረሰ፦ <<እማማ፥የአላህ ሰለም ርኀ ራሄና በረከት በአንቺ ላይ ይሀን>>( አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ)አላት።እርሷም <<በአ ንተም ላይ ሰላም ይሁን (ወአለይኩ ሙስሰላም)፥አብዱላህ ረዲየላሁ ዐንሁ>>ስትል መለሰችለት።፡<<የሃ ጃጅ ጦር ሃረም በሚገኘዉ ሠራዊ ትህ ላይ መዓት በሚያዘንበብትና የመካ ቤቶች በሚንቀጠቀጡበት በዚህ ቀዉጢ ሰዓት ወደዚህ ምን አመጣህ?>> ስትልም ጠየቀችዉ ።እርሱም <<ምክርሽን ፍለጋ መጣ ሁ ኡማ (እማየ)>>በማለት ለጥያቄ ዋ ምላሽ ሰጠ። 🔺 እርሷም በመደነቅ <<የኔን ም ክር ፍለጋ?ስለምንድነዉ የምመክ ርህ አብዱላህ ረዲየላሁ ዐንሁ?>> በማለት ጠየቀችዉ። •<<ከጎኔ ተሰልፎ የነበረዉ ሕዝብ አብዛኛዉ ሃጃጅን በመፍራት ወይ ም በሚሰጠዉ ወሮታ በመጭበር በር ጥሎኝ ሸሸ።ልጆቼና መላዉ ቤ ተሰቤ እንኳን ከእኔ ተገለሉ።አብረ ዉኝ የቀሩት በጣም ትንሽ ሰዎች ሲሆኑ፥እነርሱም ምንም ያህል ጠካራና ቆራጥ ቢሆኑም የጠላትን ኃይል ሊቋቋሙ የሚችሉት ለአንድ ሰዓት ግፋ ቢል ለሀለት ሰዓት ያህ ል ነዉ።በኑ ኡመያዎች ከኔ ጋር ለ መደራደር መልእክተኞቻቸዉን ልከ ዋል።የምሻዉን አለማዊ ፀጋ (አዱን ያ)ሁሉ ሊሰጡኝ ፈቃደኛ መሆናቸ ዉንም ገልጸዉልኛል።ነገር ግን ለዚ ህ ዉለታቸዉ ጦሬን ላስቀምጥና ከአብዱል መሊክ ኢብን መርዋን ጋር የትብብር ቃል እንድገባ መስማማት አለብኝ።ታዲያ ስለዚህ ጉ ዳይ ምን ታስቢያለሽ?>> ድምጿን ከፍ በማድረግ፥ <<አብ ዱላህ ይህ የአንተ ጉዳይ ነዉ፣ማን ነትህን ጠንቅቀህ የምታዉቅ ሰዉ ነህ።ትክክለኛና ለእዉነት የቆምኩ ነኝ ብለህ ካሰ ብክ፥ በባንዲራህ ስ ር በቆራጥነት ሲዋጉ እንደተገደሉ ት ጓደኞችህ ሁሉ በፅናትና በቆራ ጥነት ዉጊያህን ቀጥል።ይህን ትተ ህ አዱንያን ከመረጥክም ምንኛ አ ሳዛኝ ሰዉ ነህ! እራስህንም ሆነ ሰ ዎችህን እንደምታጠፋ ልብ በል። >>ስትል ምክሯን ለገሰችዉ። •<<ግን እማየ እንደዚያ ካደረግሁ፥ ዛሬ ሟች ነኝ፣ምንም ጥርጥር የለዉም።>> ለሃጃጅ በፈቃደኝነት እጅህን ሰጥ ተህ የበኑ ኡመያ አጫፋሪዎች መ ጫወቻ ከምትሆን፥የጀግንነት ሞት ለአንተ እጅጉን በላጭ ነዉ።>> •<<ሞቴን አልፈራሁም፤የኔ ፍርሃት ሥጋዬን ይበጣጥቁታል ብዬ ነዉ።>> <<የሰዉ ልጅ ከሞቱ በኃላ በአካ ሉ ላይ ስለሚፈፀመዉ ድርጊት ም ንም የሚያስፈራዉ ነገር የለም።የቆ ዳዉ መገፈፍ ምንም የሚያመጣ ዉ ህመም አይኖርም።>>አለችዉ። ✍አብደላህ ረዲየላሁ ዐንሁ ልብ የሚያጠነክረዉን የእናቱን ምክር እ ንደሰማ የሚከተለዉን እየተናገረ ፊ ቱ አንፀባረቀ። <<ምኝኛ የተባረክሽ እናት ነሽ(መ ልካሙ ባህሪይሽ የተባረከ ይሁን)በ ዚህ ቀዉጢ ሰዓት ወደአንቺ የመ ጣሁት በጆሮዬ ያንቆረ ቆርሽዉን ምክር ለመስማት ነበር።እንዳልደከ ምኩና ተስፋ እንዳልቆጠረጥኩ አ ላህ ያዉቅልኛል።ለአዱኛ ፍቅር እን ዳልተሰለፍኩም በኔ ላይ ምስክሬ ነ ዉ።ገደብ የለሽ ቁጣየ የአላህ ሕግ በመጣሱ ነዉ።እናቴ! አንቺን ደስ ወደሚያሰኝሽ ለመሄድ እነሆ ዝግ ጁ ነኝ።ብሞት አትዘኝብኝ፤በፀሎት ሽ ብቻ አስታዉሽኝ።>> •ቆራጧ አሮጊት አስማ ረዲየላሁ ዐ ንሁ <<ልጄ!የማዝንብህ ለማይረባ ዓላማ ተሰልፈህ ብትሞት ነዉ።>> <<እርግጠኛ ሁኚ እማየ ልጅሽ ህገወጥ ዓላማን አልደገፈም።ፀያ ፍ የሆነ ተግባርም አልከወነም። ሙስሊሞችንም ሆነ ሙስሊም ያል ሆኑ ዜጎች ፍትህ አላጓደለም።ለር ሱ ከኃያሉ ጌታ ዉዴታ የበለጠ አን ዳችም ነገር የለም።ይህን ያልኩት ንፅህናዬን በመግለፅ ለመመጻደቅ ሳይሆን ልብሽን ለማጠናከር ብቻ እ ንደተናገርኩ አላህ ያዉቅልኛል>>አ <<አላህ ሱብሃን ወተአላህ ለሚወ ደዉና እኔም የምመኝልህን እንድት ፈፅም ስለረዳህ ምስጋና ይግባዉ! ና ልጄ ግንኙነቻችን የመጨረሻ ሊ ሆን ይችላልና እስኪ ሰዉነትህን ላ ሽትተዉ፥ልዳስሰዉም።>> አለችዉ ና ከፊቷ ተንበ ረከከ።ወደ እርሷ አስ ጠጋችዉ፤ አንገቱን ፥ፊቱንና እራሱን በእናትነት ስሜት ተዉጣ እየዳበሰ ች ሳመችዉ።ጣቶቿ ሰዉነቱን መ ጭመቃቸዉን ቀጠሉ።በድንገት እ ጇን ከሰዉነቱ አላቃ፦ <<ይህ የለበ ስከዉ ምንድን ነዉ? >>አለችዉ።< <የጦር ልብስ ነዉ>>አላት።<<ይህ ፥ሰማዕታትን የሚከጅል ሰዉ የሚ ለብሰዉ ልብስ አይደለም።አዉልቀ ዉ፥እንቅስቃሴህን ይበልጥ ቀላልና ቀልጣፋ ያደርግ ልሃል።በዚህ ምት ክ ሱሪ ልበስ።ብትገደልም ሃፍረተ ሥጋህ አይጋለጥም>>አለችዉ። ✍አብደላህ ረዲየላሁ ዐንሁ የጦ ር ልብሱን አዉልቆ ሱሪ አጠለቀ።ፍ ልሚያዉን ለመቀላቀል <<ሐረም> >ሲለቅ፦ <<እናቴ ሆይ!ዱዓሽ አይለ የኝ>> አላት። ✍እጇን ወደ ሰማይ ዘርግታ ዱዓ አደረገች፦ <<ጌታዬ ሆይ!...ለአባቱ ና ለእናቱ የእርሱን መልካም ሰሪነት ባርክላቸዉ።እርሱን ለአንተ ጉዳይ አበርክቻለሁ።ለእርሱ የወሰንክለት ነገር ያስተስተኛል።ለኔም ጽኑና ታጋ ሽ የሆኑ ሰዎችን ምንዳ ለግሰኝ።>> 🌹ፀሐይ ስትጠልቅ አብደላል ረዲ የላሁ ዐንሁ ለዘልዓለም አንቀላፍቶ ነበር።ልክ ከአሥር ቀናት በኃላ እና ቱን ተከተለችዉ።የመቶ ዓመታት እ ድሜ ባለፀጋ ነበረች።እድሜ የአላ ማ ጽናቷን አልዘረፋትም፤የአእምሮ ብሩህነቷን አላደበዘዘዉም።
47304
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%A9%E1%88%B2%E1%8B%AB%20%E1%8C%8D%E1%8B%9B%E1%89%B5
የሩሲያ ግዛት
የራሽያ ኢምፓየር በተለምዶ ኢምፔሪያል ሩሲያ እየተባለ የሚጠራው ከ1721 ጀምሮ በዩራሺያ የተስፋፋ ታሪካዊ ኢምፓየር ሲሆን የሩስያ ዛርዶምን በመተካት ታላቁን የሰሜናዊ ጦርነት ያበቃውን የኒስታድ ስምምነትን ተከትሎ ነበር። ከየካቲት 1917 የየካቲት አብዮት በኋላ ስልጣን በተረከበው ጊዜያዊ መንግስት ሪፐብሊክ እስኪታወጅ ድረስ ኢምፓየር ቆይቷል። በታሪክ ሶስተኛው ትልቁ ግዛት፣ በአንድ ወቅት በሶስት አህጉራት ማለትም በአውሮፓ፣ በእስያ እና በሰሜን አሜሪካ የተዘረጋው የሩስያ ኢምፓየር ነበር። መጠኑ በብሪቲሽ እና በሞንጎሊያውያን ግዛቶች ብቻ ይበልጣል። የሩስያ ኢምፓየር መነሳት ከጎረቤት ተቀናቃኝ ሀይሎች ውድቀት ጋር ተገጣጠመ፡ የስዊድን ኢምፓየር፣ ፖላንድ - ሊትዌኒያ፣ ኦስትሪያ - ሀንጋሪ፣ ፋርስ፣ የኦቶማን ኢምፓየር እና ቺንግ ቻይና። ከ 10 ኛው እስከ 17 ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ መሬቱን የሚመራው በታላቅ መደብ ማለትም , ከነሱ በላይ ዛር ሲሆን በኋላም ንጉሠ ነገሥት ሆነ. በኋላ ላይ ለመጣው ኢምፓየር መሠረት ጥሏል። የግዛቱን ግዛት በሦስት እጥፍ አሳደገ፣ የወርቅ ሆርዴ የበላይነትን አብቅቷል፣ የሞስኮ ክሬምሊንን አድሷል፣ የሩሲያን መንግሥት መሠረት ጥሏል። የሮማኖቭ ቤት ከ 1721 ጀምሮ እስከ 1762 ድረስ የሩስያን ኢምፓየር ያስተዳድር ነበር ። ከ 1762 እስከ ግዛቱ ፍፃሜ ድረስ የገዛው የሆልስቴይን-ጎቶርፕ-ሮማኖቭ ቤት - ማትሪሊናል ቅርንጫፍ የሆነው የፓትሪሊናል ጀርመን ዝርያ ነው። በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ኢምፓየር በሰሜን ከአርክቲክ ውቅያኖስ ወደ ደቡብ ጥቁር ባህር ፣ በምዕራብ ከባልቲክ ባህር እስከ አላስካ እና በሰሜን ካሊፎርኒያ ፣ በሰሜን አሜሪካ ፣ በምስራቅ ተዘርግቷል ። በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ የመካከለኛው እስያ እና የሰሜን ምስራቅ እስያ ክፍሎችን ይይዛል. በ 125.6 ሚሊዮን ርዕሰ ጉዳዮች, በ 1897 የሕዝብ ቆጠራ መሰረት, በወቅቱ ከቺንግ ቻይና እና ህንድ ቀጥሎ በሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል. ልክ እንደ ሁሉም ኢምፓየሮች፣ ታላቅ ኢኮኖሚያዊ፣ ጎሳ፣ ቋንቋ እና ሃይማኖታዊ ልዩነቶችን አሳይቷል። ግዛቱ በፊውዳል አደረጃጀት ከመሬት ጋር የተቆራኘው ሰርፍ በመባል የሚታወቁት በሩሲያ ገበሬዎች ምርታማ ባልሆነ መንገድ በሚሰሩ ትላልቅ ግዛቶች ላይ የተመሰረተ የግብርና ኢኮኖሚ ነበራት። ሰርፎች በ1861 ነፃ ወጡ፣ ነገር ግን የመሬት ባለቤት የሆነው ባላባት ክፍል ተቆጣጥሮታል። በባቡር እና በፋብሪካዎች የውጭ ኢንቨስትመንቶች በመታገዝ ኢኮኖሚው ቀስ በቀስ ወደ ኢንደስትሪ አደገ። ብዙ ተቃዋሚ አካላት ለዘመናት ብዙ አመጽ እና ግድያዎችን ከፍተዋል። በ19ኛው መቶ ዘመን ተቃዋሚዎችን በንጉሠ ነገሥቱ ሚስጥራዊ ፖሊስ በቅርበት ይከታተሉ የነበረ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ወደ ሳይቤሪያ ተወሰዱ። ንጉሠ ነገሥት ፒተር 1 ብዙ ጦርነቶችን ተዋግተው ቀድሞውንም ሰፊ ግዛትን ወደ ትልቅ የአውሮፓ ኃይል አስፋፉ። ዋና ከተማዋን ከሞስኮ ወደ አዲሱ ሞዴል ከተማ ሴንት ፒተርስበርግ አዛውሯል, ይህም በአብዛኛው በምዕራቡ ዲዛይን መሰረት ነው. አንዳንድ ባህላዊ እና የመካከለኛው ዘመን ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በዘመናዊ፣ ሳይንሳዊ፣ ምዕራባዊ ተኮር እና ምክንያታዊ ስርዓት የተካ የባህል አብዮት መርቷል። እቴጌ ካትሪን ታላቋ ወርቃማ ዘመንን መርተዋል; በምዕራብ አውሮፓ መስመር የጴጥሮስ 1ን የዘመናዊነት ፖሊሲ በመቀጠል ግዛቱን በወረራ፣ በቅኝ ግዛት እና በዲፕሎማሲ አስፋፍታለች። ንጉሠ ነገሥት አሌክሳንደር 1ኛ የናፖሊዮንን አውሮፓን የመቆጣጠር ፍላጎት በማክሸፍ እንዲሁም የወግ አጥባቂ ንጉሣውያን ህብረትን በማቋቋም ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ሩሲያም ወደ ምዕራብ፣ ደቡብ እና ምስራቅ በመስፋፋት በጊዜው ከነበሩት ኃያላን የአውሮፓ ግዛቶች አንዷ ሆናለች። በራሶ-ቱርክ ጦርነቶች ያስመዘገበው ድል በክራይሚያ ጦርነት ሽንፈት የተፈተሸ ሲሆን ይህም የተሃድሶ ጊዜ እንዲፈጠር እና በመካከለኛው እስያ እንዲስፋፋ አድርጓል። ዳግማዊ ንጉሠ ነገሥት አሌክሳንደር ብዙ ማሻሻያዎችን አስጀምረዋል፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ በ1861 23 ሚልዮን ሰርፎች ነፃ መውጣታቸው ይታወሳል። እ.ኤ.አ. በ 1914 ሩሲያ ወደ አንደኛው የዓለም ጦርነት እንድትገባ ያደረጋት አንዱ ምክንያት ይህ ነበር ፣ ከመካከለኛው ኃያላን ጋር በተባበሩት መንግስታት በኩል ። የራሺያ ኢምፓየር በኦርቶዶክስ፣ በራስ አገዛዝ እና በብሔረሰብ ርዕዮተ ዓለም አስተምህሮ ላይ እንደ ፍፁም ንጉሣዊ አገዛዝ አገልግሏል እ.ኤ.አ. በ1905 አብዮት እስከ ተካሔደ ድረስ፣ የስም ከፊል ሕገ መንግሥት ንጉሣዊ አገዛዝ እስከተመሠረተበት ጊዜ ድረስ። በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ጥሩ ውጤት አላስገኘም, ይህም ወደ የካቲት አብዮት እና ንጉሠ ነገሥት ኒኮላስ ከስልጣን እንዲወገድ አድርጓል, ከዚያ በኋላ ንጉሣዊው አገዛዝ ተወገደ. በጥቅምት አብዮት ቦልሼቪኮች ሥልጣናቸውን በመያዝ ወደ ሩሲያ የእርስ በርስ ጦርነት አመሩ። የቦልሼቪኮች የንጉሠ ነገሥቱን ቤተሰብ እ.ኤ.አ.
4226
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8D%E1%88%AB%E1%8A%95%E1%8A%AD%E1%88%8A%E1%8A%95%20%E1%88%AE%E1%8B%98%E1%89%A8%E1%88%8D%E1%89%B5
ፍራንክሊን ሮዘቨልት
ፍራንክሊን ዴላኖ ሩዝቬልት (/ ; ጥር 30, 1882 - ኤፕሪል 12, 1945), ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል. በመጀመርያ ፊደላቸው አሜሪካዊ ፖለቲከኛ እና ጠበቃ ከ1933 እስከ እለተ ሞቱ በ1945 ድረስ የዩናይትድ ስቴትስ 32ኛው ፕሬዚደንት ሆነው ያገለገሉ ሲሆን የዴሞክራቲክ ፓርቲ አባል በመሆን ሪከርድ በሆነ አራት ፕሬዚዳንታዊ ምርጫዎች አሸንፈው የሀገሪቱ ማዕከላዊ ሰው ሆነዋል። በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ የዓለም ክስተቶች። ሩዝቬልት በዩኤስ ታሪክ ውስጥ ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስ ምላሽ በመስጠት የኒው ድርድርን የሀገር ውስጥ አጀንዳ በመተግበር በአብዛኛዎቹ የታላቁ የኢኮኖሚ ድቀት ወቅት የፌደራል መንግስትን መርቷል። የፓርቲያቸው ዋና መሪ እንደመሆናቸው መጠን በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ሶስተኛው በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ዘመናዊ ሊበራሊዝምን የሚገልጸውን አዲስ ስምምነት ጥምረት ገነቡ። ሦስተኛው እና አራተኛው የስልጣን ዘመን በ2ኛው የዓለም ጦርነት የተቆጣጠረው ሲሆን በስልጣን ላይ ከሞተ በኋላ ብዙም ሳይቆይ አብቅቷል። የተወለደው ከሮዝቬልት ቤተሰብ በሃይድ ፓርክ ፣ ኒው ዮርክ ፣ ከግሮተን ትምህርት ቤት እና ከሃርቫርድ ኮሌጅ የተመረቀ ሲሆን በኮሎምቢያ የሕግ ትምህርት ቤት ገብቷል ፣ በኒው ዮርክ ከተማ የሕግ ልምምድ ለማድረግ ባር ፈተናውን ካለፈ በኋላ ወጣ ። እ.ኤ.አ. በ 1905 አምስተኛውን የአጎቱን ልጅ ኤሌኖር ሩዝቬልትን አገባ። ስድስት ልጆችን የወለዱ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አምስቱ እስከ ጉልምስና ደርሰዋል። እ.ኤ.አ. በ 1910 ለኒውዮርክ ግዛት ሴኔት ምርጫ አሸንፈዋል ፣ እና በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በፕሬዝዳንት ውድሮው ዊልሰን ስር የባህር ኃይል ረዳት ፀሀፊ ሆኖ አገልግሏል ። ሩዝቬልት በዲሞክራቲክ ፓርቲ 1920 የብሔራዊ ትኬት የጄምስ ኤም ኮክስ ተወዳዳሪ ነበር ፣ ግን ኮክስ ተሸንፏል። በሪፐብሊካን ዋረን ጂ ሃርዲንግ. እ.ኤ.አ. በ 1921 ሩዝቬልት በፓራላይቲክ በሽታ ያዘ ፣ በወቅቱ ፖሊዮ ተብሎ የሚታመን ሲሆን እግሮቹም በቋሚነት ሽባ ሆነዋል። ሩዝቬልት ከህመሙ ለማገገም ሲሞክር በዋርም ስፕሪንግስ፣ ጆርጂያ የፖሊዮ ማገገሚያ ማዕከል አቋቋመ። በ1928 የኒውዮርክ ገዥ ሆኖ ከተመረጠ በኋላ ሩዝቬልት ሳይታደግ መራመድ ባይችልም ከ1929 እስከ 1933 በገዥነት አገልግሏል፣ በዩናይትድ ስቴትስ እየከበበ ያለውን የኢኮኖሚ ቀውስ ለመቋቋም ፕሮግራሞችን አቅርቧል። እ.ኤ.አ. በ 1932 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ሩዝቬልት በዩኤስ ታሪክ ውስጥ ከታዩት የመሬት መንሸራተት ድሎች በአንዱ የሪፐብሊካን ፓርቲ ስልጣንን ኸርበርት ሁቨርን አሸንፏል። የሩዝቬልት ፕሬዝደንት የጀመረው በታላቁ የኢኮኖሚ ድቀት መካከል ሲሆን በመጀመሪያዎቹ 100 ቀናት ውስጥ በ73ኛው የአሜሪካ ኮንግረስ ታይቶ የማይታወቅ የፌደራል ህግ አውጪ ምርታማነትን መርቷል። ሩዝቬልት እፎይታን፣ ማገገሚያ እና ማሻሻያ ለማድረግ የተነደፉ ፕሮግራሞችን እንዲፈጠር ጠይቋል። በመጀመሪያው አመት ውስጥ እነዚህን ፖሊሲዎች በተከታታይ በሚወጡ የአስፈፃሚ ትዕዛዞች እና አዲስ ስምምነት ተብሎ በሚጠራው የፌደራል ህግ መተግበር ጀመረ። ብዙ የአዲስ ስምምነት ፕሮግራሞች እንደ ብሔራዊ የማገገም አስተዳደር ላሉ ሥራ አጦች እፎይታ ሰጥተዋል። በርካታ የአዲስ ስምምነት ፕሮግራሞች እና የፌዴራል ህጎች እንደ የግብርና ማስተካከያ ህግ ለገበሬዎች እፎይታ ሰጥተዋል። ሩዝቬልት ከፋይናንስ፣ ግንኙነት እና ጉልበት ጋር የተያያዙ ዋና ዋና የቁጥጥር ማሻሻያዎችን አቋቋመ። ከኢኮኖሚው በተጨማሪ፣ ሩዝቬልት በክልከላ ምክንያት እየጨመረ የመጣውን ወንጀል ለመግታት ሞክሯል። ለመሻር በመድረክ ላይ ዘመቻ ካደረጉ በኋላ፣ ሩዝቬልት የ1933 የቢራ ፍቃድ ህግን ተግባራዊ በማድረግ 21ኛውን ማሻሻያ ተግባራዊ አደረገ። ከአልኮል ሽያጭ የሚሰበሰበው የታክስ ገቢ እንደ አዲስ ስምምነት አካል ለሕዝብ ሥራዎች ይሆናል። ሩዝቬልት በፕሬዚዳንትነት ዘመናቸው 30 "የፋየርሳይድ ቻት" የሬዲዮ አድራሻዎችን በመስጠት ለአሜሪካን ህዝብ በቀጥታ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ሬዲዮን ይጠቀም ነበር እና በቴሌቪዥን የተላለፈ የመጀመሪያው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነዋል። ከ1933 እስከ 1936 ባለው ጊዜ ውስጥ ኢኮኖሚው በፍጥነት ተሻሽሏል፣ እና ሩዝቬልት በ1936 እንደገና በምርጫ አሸንፏል። የኒው ድርድር ታዋቂነት ቢኖርም ብዙዎቹ የዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወግ አጥባቂ አቋም ይዘው የቆዩ ሲሆን አዲስ ስምምነትን በተደጋጋሚ ይገድሉ ነበር። በድጋሚ መመረጡን ተከትሎ፣ ሩዝቬልት በ1937 የፍትህ ሂደቶች ማሻሻያ ህግ (ወይም "የፍርድ ቤት ማሸግ እቅድ") በመጠየቅ ይህንን ለመቃወም ፈለገ፣ ይህም የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን መጠን ያሰፋ ነበር። ሂሳቡ አዲስ በተቋቋመው የሁለትዮሽ ወግ አጥባቂ ጥምረት ታግዶ የነበረ ሲሆን ይህም ተጨማሪ የአዲስ ስምምነት ህግን ለመከላከል ፈልጎ ነበር። በውጤቱም, ኢኮኖሚው ማሽቆልቆል ጀመረ, ይህም የ 1937-1938 ውድቀትን አስከተለ. በሮዝቬልት ስር የተተገበሩ ሌሎች ዋና ዋና የ1930ዎቹ ህግጋቶች እና ኤጀንሲዎች የሴኩሪቲስ እና ልውውጥ ኮሚሽን፣ የብሄራዊ የሰራተኛ ግንኙነት ህግ፣ የፌደራል የተቀማጭ ገንዘብ መድን ድርጅት፣ የማህበራዊ ዋስትና እና የፍትሃዊ የስራ ደረጃዎች ህግን ያካትታሉ። ሩዝቬልት እ.ኤ.አ. በ 1940 በድጋሚ ለሦስተኛ የስልጣን ዘመናቸው ተመረጡ፣ ከሁለት የምርጫ ዘመን በላይ ያገለገሉ ብቸኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት አድርገውታል። እ.ኤ.አ. በ 1939 ሌላ የዓለም ጦርነት በአድማስ ላይ ነበር ፣ ይህም ዩናይትድ ስቴትስ ገለልተኛነትን የሚያረጋግጡ ተከታታይ ህጎችን በማውጣት እና ጣልቃ ገብነትን ውድቅ በማድረግ ምላሽ እንድትሰጥ አነሳሳው። ይህም ሆኖ ፕሬዚዳንት ሩዝቬልት ለቻይና፣ ለእንግሊዝ እና በመጨረሻም ለሶቪየት ኅብረት ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ እና የገንዘብ ድጋፍ ሰጡ። እ.ኤ.አ. ታኅሣሥ 7 ቀን 1941 የጃፓን ጥቃት በፐርል ሃርበር ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ ሩዝቬልት በጃፓን ላይ የጦርነት አዋጅ ተናገረ። በታኅሣሥ 11 የጃፓን አጋሮች፣ ናዚ ጀርመን እና ፋሺስት ኢጣሊያ በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ጦርነት አውጀዋል። በምላሹ ዩኤስ ከአሊያንስ ጋር በመተባበር ወደ አውሮፓ ጦርነት ቲያትር ገባ። በከፍተኛ ረዳታቸው ሃሪ ሆፕኪንስ በመታገዝ እና በጠንካራ ሀገራዊ ድጋፍ ከእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዊንስተን ቸርችል፣ የሶቪየት ዋና ፀሀፊ ጆሴፍ ስታሊን እና ከቻይናው ጄኔራሊሲሞ ቺያንግ ካይ-ሼክ ጋር በቅርበት በመስራት የተባበሩት መንግስታትን በአክሲስ ሀይሎች ላይ በመምራት ላይ ናቸው። ሩዝቬልት የጦርነቱን ጥረት ለመደገፍ የአሜሪካን ኢኮኖሚ ማሰባሰብን በበላይነት በመቆጣጠር የአውሮፓን የመጀመሪያ ስትራቴጂ በመተግበር የብድር-ሊዝ ፕሮግራምን በማነሳሳት እና የጀርመንን ሽንፈት ከጃፓን የበለጠ ቅድሚያ ሰጥቷል። የእሱ አስተዳደር የፔንታጎንን ግንባታ በበላይነት ይቆጣጠር ነበር፣ በዓለም የመጀመሪያውን የአቶሚክ ቦምብ ልማት አነሳስቷል እና ከሌሎች የህብረት መሪዎች ጋር በመሆን ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ከጦርነቱ በኋላ ሌሎች ተቋማትን መሠረት ለመጣል። ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም መድረክ ልዕለ ኃያል የሆነችው በጦርነቱ መሪነት ነው። ሩዝቬልት እ.ኤ.አ. በ 1944 በተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ከጦርነቱ በኋላ ማገገሚያ መድረክ ላይ በድጋሚ ተወዳድሮ አሸንፏል። በኋለኞቹ የጦርነት ዓመታት አካላዊ ጤንነቱ ማሽቆልቆል ጀመረ እና ለአራተኛው የስልጣን ዘመን ከሶስት ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ ሩዝቬልት ኤፕሪል 12, 1945 ሞተ። ምክትል ፕሬዝዳንት ሃሪ ኤስ. ትሩማን በፕሬዚዳንትነት ስልጣን ያዙ እና በአክሲስ ሀይሎች እጅ መስጠትን በበላይነት ተቆጣጠሩ። እሱ ከሞተበት ጊዜ ጀምሮ፣ በርካታ የሩዝቬልት ድርጊቶች እንደ ጃፓን አሜሪካውያን በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ ወደ ሌላ ቦታ መዛወር እና መመልመል በመሳሰሉት ከፍተኛ ትችቶች ደርሰዋል። ቢሆንም፣ እሱ በተከታታይ በምሁራን፣ በፖለቲካ ሳይንቲስቶች እና በታሪክ ተመራማሪዎች በአሜሪካ ታሪክ ውስጥ ከታላላቅ ፕሬዚዳንቶች አንዱ ሆኖ ተመድቧል። የአሜሪካ መሪዎች
34421
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%80%E1%89%B2%20%28%E1%8A%A0%E1%89%85%E1%89%B6%E1%8B%AD%29
ቀቲ (አቅቶይ)
ቀቲ ወይም አቅቶይ በ9ኛው ሥርወ መንግሥት (ምናልባት 2350-2331 ዓክልበ. ግድም) የገዛ የግብጽ ፈርዖን ነበረ። ዋና ከተማው በሄራክሌውፖሊስ (ግብጽኛ፦ ኸነን-ነሱት) በስሜኑ ነበረ። የቀቲ (አቅቶይ) ስም በአንዳንድ ቅርስ ቢገኝም፣ ተወላጆቹ ሁሉ «ቀቲ» የሚል የቤተሠብ ስም ስለነበራቸው እነርሱን መለያየት አስቸጋሪ ነው፣ ሊቃውንትም ሁላቸው አይስማሙም። በ3ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. የኖረው ታሪክ ጸሐፊ ማኔቶን ስለዚሁ ሥርወ መንግሥት ብዙ አይልም። ነገር ግን ስለ መጀመርያው ቀቲ እንዲህ ብሎ ይመሰክራል። «አቅቶይስ ከርሱ በፊት ከነበሩት ሁሉ ይልቅ አስፈሪ ሆነ፤ በመላ ግብጽ በተገኙት ሰዎች ላይ ክፋትን አደረገ፤ በመጨረሻም አብዶ በአዞ ተበላ።» ይህ ቀቲ ደግሞ የመሪካሬ ትምህርት በተባለው ሰነድ ይጠቀሳል። ይኸው ሰነድ የአረመኔ ንጉሥ አገዛዝ ዘዴ የሚመክር ነው። የአቅቶይ ምክር ከመሪካሬ ትምህርት «ለግፈኛው ዝም ማለት መሥዋዕቱን ያፈርሳል፣ አምላክ በመቅደሱ ላይ ያመጸውን ይመታልና፣ እርሱ እንደሚያደርገው ሰዎች ይደርሱበታል፣ ለታቀደለት ወጥመድ ይጠግባል፣ በሚመጣው ዕለት ምንም ሞገስ አያገኝም። መሥዋዕቱን ጠብቅ፣ አምላኩን አምልክ፣ ያስቸግረኛል አትበል፣ ዕጆችህ አይፈቱ። አመጽ ያደረገብህስ፣ ይህ ሰማይን ማጥፋት ነው። ሐውልት ለዘመናት ይጸናል፤ ጠላት አዋቂ ከሆነ አያጠፋውም፣ እርሱ ያደረገውን በሚከተሉት እንዲከብር በመመኘት። ጠላት የሌለው የለም፣ የሁለቱ አገራት {የግብጽ} ገዢ ግን ጥበበኛ ነው ሎሌዎችም ያሉት ንጉሥ ደደብ ሊሆን አይችልም። ከልደቱ ጀምሮ ጠቢብ ነው፣ አምላክም ከአዕላፍ ሰዎች ይለየዋል። ንጉሥነት በጎ ሹመት ነው፣ ሐውልቶቹን የሚያጸናለት ልጅ ወይም ወንድም የለውም፣ እራሱ ሌላውን የሚጠብቅ ነው እንጂ። ሰው ለቀዳሚው ይሠራል፤ እርሱ ያደረገውን በሚከተሉት እንዲከብር በመመኘት። በኔ ዘመን ግፈኛ አድራጎት ተሠራ፤ የጢኒስ አቅራቢያ ተፈረሰ። በውነት ሆነ፤ በኔ በኩል ግን አልሆነም፣ ከተደረገ በኋላ ብቻ አወቅኩት። እነሆ፣ ውጤቱ እኔ ካደረግኩ በላይ በለጠ፤ የተጎዳው ፍርስራሽ ሆኛልና፣ ያፈረሰውንም ለሚያሳድሰው ምንም ጥቅም የለም፣ ወይም ያሠራውን ለሚያፍርስ፣ ያጠፋውንም ለሚያክብር፤ ከዚሁ እራቅ። መምታት በተመሳሳዩ ይከፈላል፤ ለሥራዎችም ሁሉ መልስ አለ። አንዱ ትውልድ ለሌላው ያልፋል፤ ባሕርይንም የሚያውቅ አምላክ ተደብቋል። ባለ እጅን የሚቃውም የለም፣ አይኖቹ ያዩትን ሁሉ ይመታል፤ ስለዚህ በመንገዱ ላይ አምላኩን አምልክ። ዕቃዎች ከዕንቁና ከመዳብ ይሠራሉ፣ ማዕበል በማዕበል ይተካል፤ እንዲሠወር የተፈጠረ ፈሳሽ የለም፣ የተሠወረበት ግድብ ይጠፋ ነበርና። ነፍስ ወደሚያውቀው ቦታ ይሔዳል፣ በትናንትናም መንገድ ላይ አይዘግይም። በምዕራብ {በሢኦል} ያለህን አዳራሽህን አሳምር፣ በመቃብር ያለህን ሥፍራ በቅንነትና በትክክል አጌጥ፤ ልቦቻቸው በዚያው ይደገፋሉና፤ የቅን ሰው ባሕርይ ከበደለኛው በሬ በላይ ይቀበላልና። አምላኩን {የጸሐይ ጣኦት ሬ} አገልግል፣ እርሱም ተመሳሳዩን ያደርግልሃል፣ በመሥዋዕትና በተቀረጸው ምስል አገልግለው፣ ያው ስምህን የሚያሳይ ነው፤ አምላኩም ያገለገለውን ሁሉ ያውቃል። ለሰዎች፣ ለአምላኩ ከብት፣ አቅርብላቸው፣ እርሱ ሰማይንና ምድርን ለነርሱ ፈጠረና። እርሱ የውኃዎቹን ሥሥት አቀነሰ፣ ለአፍንጮቻቸው የሕይወት እስትንፋስ ሰጠ፣ ከሥጋው የወጡ የርሱ አራያዎች ናቸውና። ለልቡናቸው ጥቅም በሰማይ ያብራል፤ ሊመግባቸው ዕጽ፣ ከብት፣ አዕዋፍና ዓሳ ሠርቷል። ጠላቶቹን ገድሏል፤ የራሱንም ልጆች አጥፍቷል አመጽ ለማድረግ ስላቀዱ። ለልቡናቸው ጥቅም መዓልትን ይሠራል፤ ያያቸውም ዘንድ በምኋሩ ይዞራል። በስተኋላቸው መቅደስ ሠርቷል፤ ሲያልቅሱም ይሰማል። ከዕንቁላል ጀምሮ ገዢዎች አደረገላችው፤ ከድካሙ ጀርባ ሸክሙን የሚያንሣ። የሚሆነውን ለመከልከል ጥንቆላን እንደ መሣርያ ሠራላቸው፤ በሌሊትም በቀንም ጠብቀው። የማይወዱትን እንዴት ገድሏል፣ አባባሌን ቸል አትበል፣ ስለንጉሡ ሕግጋት ቢሰጥም። እንደ ሰው ልጅ እንድትነሣ ያስተምራል፣ የዛኔ ከሳሽ ሳይኖርብህ ትደርሰኝ ዘንድ። የሚቅርብህን አትገድል፣ ሞገስን ስጠው፣ አማላክቱ ያውቁታልና። በምድር የሚከናውን ከነርሱ አንድ ነው፣ ንጉሱንም የሚያገልግሉ ሰዎች አማልክት ናቸው። ፍቅርህን በመላ ዓለም አሳድር፣ መልካም ባህርይ የሚስታወስ ነውና። {አንድ መስመር ጠፍቶ ሊነብ አይችልም} በአቅቶይም ቤት በሚከተሉት አፍ 'የችግሮች ዘመንን የጨረሰ' እንዲነገርልህ ስለ ዛሬውኑ ዘመን ሲያስቡ። እነሆ፣ ከሃሳቦቼ የተሻሉትን ነግሬሃለሁ፣ በፊትህ አኑራቸው።» የ1ኛው ጨለማ ዘመን ፈርዖኖች
52405
https://am.wikipedia.org/wiki/African%20Leadership%20Academy
African Leadership Academy
የአፍሪካ አመራር አካዳሚ በጆሃንስበርግ ፣ ደቡብ አፍሪካ ዳርቻ የሚገኝ ቅድመ-ዩኒቨርስቲ ሲሆን ከ16 እስከ 19 አመት ለሆኑ ከአፍሪካ እና ከተቀረው አለም የተመሰረተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከ46 ሀገራት የተውጣጡ የቀድሞ ተማሪዎች አሉት። እ.ኤ.አ. በ 2004 በፍሬድ ስዋኒከር ፣ ክሪስ ብራድፎርድ ፣ ፒተር ሞምቡር እና አቻ ሌክ የተመሰረተ ሲሆን በሴፕቴምበር 2008 በ97 ተማሪዎች ስራውን ጀምሯል። ቀጣዩን የአፍሪካ መሪዎችን በመለየት፣ በማዳበር እና በማገናኘት አፍሪካን ለመለወጥ ያልማል። ይህንን ግብ ለማሳካት፣ በአፍሪካ ጥናቶች ፣ በፅሁፍ እና በአነጋገር እና በስራ ፈጠራ አመራር እንዲሁም በተለመዱት የአካዳሚክ አንኳር ትምህርቶች የሁለት አመት ስርአተ ትምህርት አለው። የ መስራቾች፣ በ2004 አካባቢ ለ መቅድም የሚሆን ግሎባል ሊደርሺፕ አድቬንቸርስ የተባለ የበጋ ፕሮግራም ጀመሩ ። እ.ኤ.አ. በ 2006 ስዋኒከር እና ብራድፎርድ በዓለም ላይ ካሉት 15 ምርጥ ብቅ ያሉ ማህበራዊ ስራ በመባል እውቅና አግኝተዋል። እ.ኤ.አ. በ 2007 የመነሻ ካምፓስ የተረጋገጠ ሲሆን ክሪስቶፈር ካምባ የትምህርት ቤቱ የመጀመሪያ ዲን ሆኖ ሆኗኑዋል ፣ የአሁኑ ዲን ደግሞ ዲን ሀቲም ኤልታይብ ነው። ደቡብ አፍሪካ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ካምፓሱ ከጆሃንስበርግ ወጣ ብሎ ሃኒድሪው ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ተማሪዎች አብረው ይሚጋሩት መኖሪያ ፣ የስፖርት ሜዳ፣ 350 መቀመጫ አዳራሾች፣ የመማሪያ ክፍሎች እና የመመገቢያ አዳራሾችን ጨምሮ ዘመናዊ መገልገያዎች አሉዋችው። የአፍሪካ ሊደርሺፕ አካዳሚ በመጀመሪያው ዙር 400 የሚጠጉ የፍጻሜ ውድድር ላይ ለመሳተፍ በሚመረጡበት የመጀመሪያ ዙር በሺዎች የሚቆጠሩ ማመልከቻዎችን ይቀበላል። የመጨረሻ እጩዎች የመግቢያ ፈተናዎችን ይጽፋሉ, በቡድን እንቅስቃሴዎች ውስጥ ይሳተፋሉ እና ቃለ መጠይቅ ይደረግላቸዋል ከዛም 120 ተማሪዎች በአካዳሚው እንዲካፈሉ ይመረጣሉ የመግቢያ ውጠት በኤፕሪል አጋማሽ ላይ ይወጣል። የምርጫ መስፈርት የአፍሪካ አመራር አካዳሚ አምስት መስፈርቶችን ይጠቀማል፡- ያለፈ የትምህርት ስኬት የአመራር አቅም የኢንተርፕረነር መንፈስ ለሕዝብ አገልግሎት መሰጠት ለአፍሪካ ፍቅር ሥርዓተ ትምህርት የአካዳሚክ አስኳል በካምብሪጅ ኤ ደረጃዎች እና በ ልዩ ስርአተ-ትምህርት በኢንተርፕረነርሺያል አመራር፣ በአፍሪካ ጥናቶች እና በፅሁፍ እና በአነጋገር ላይ የተመሰረተ የሁለት አመት የቅድመ-ዩኒቨርስቲ ፕሮግራምን ያጣምራል። ደረጃ . የኢንተርፕረነርሺፕ አመራር እና የአፍሪካ ጥናቶች የ ኢንተርፕረነርሺፕ አመራር ሥርዓተ ትምህርት የተማሪው ልምድ የማዕዘን ድንጋይ ሲሆን በመምሰል እና በፕሮጀክት ላይ የተመሰረተ ትምህርት የመሪነት እና የስራ ፈጠራ ችሎታዎችን ለመለማመድ እድሎችን ይፈጥራል። ተማሪዎች በቡድን ግንባታ እና ኦሪጅናል አስተሳሰብ ላይ እንዲሰሩ ይበረታታሉ። በኢንተርዲሲፕሊናዊ የአፍሪካ ጥናቶች ሥርዓተ ትምህርት፣ ተማሪዎች ረሃብን ማጥፋትን፣ የጤና እንክብካቤ አቅርቦትን፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን እና የግጭት አፈታትን ያጠናሉ። የአካዳሚክ ስኬት የአፍሪካ አመራር አካዳሚ ዲን የመጀመርያው ዲን ክሪስቶፈር ሲቱማ ካምባ ቀደም ሲል በኬንያ ናይሮቢ ዳርቻ የሚገኘው የአሊያንስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ነበር። ካምባ የ ትምህርቱን ከናይሮቢ ኬንያታ ዩኒቨርሲቲ አግኝቷል። የአሁኑ ዲን ሀቲም ኤልታይብ ናቸው። ፋኩልቲ አባላት የፋኩልቲ አባላት ብዙ ቃለመጠይቆችን፣ የአካዳሚክ ዳራ ፍተሻዎችን፣ እና የግል እና ሙያዊ ማጣቀሻዎችን በማረጋገጥ ሂደት ውስጥ ያልፋሉ። ከመጀመሪያው ዙር ቃለመጠይቆች በኋላ የወደፊት አስተማሪው ተማሪዎች እና ሁለት መምህራን በተገኙበት የማስመሰያ ትምህርት ይሰጣል። ከዚህ በኋላ የመጨረሻው ዙር ቃለ-መጠይቆች ይከተላል. ሁሉም መምህራን ከዩኒቨርሲቲዎች የተመረቁ እና ቀደም ሲል በመሪ ተቋማት ያስተምራሉ. የተማሪ ህይወት ተማሪዎች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ እንዲሳተፉ ይበረታታሉ። ይሁን እንጂ ስፖርት የአካዳሚው ጠንካራ አካል አይደለም. አሁን ያሉት የውድድር ስፖርቶች እግር ኳስ፣ ቅርጫት ኳስ እና መረብ ኳስ ያካትታሉ። የተማሪ ክለቦች እና ድርጅቶች ተማሪዎች በተለያዩ ክለቦች ውስጥ ይሳተፋሉ፣ እና እያንዳንዱ ተማሪ “የተማሪ ኢንተርፕራይዝ”፣ “የመጀመሪያው ሀሳብ ለልማት” ወይም “የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክት” መፍጠር ወይም ማስኬድ ይጠበቅበታል። የተማሪ ኢንተርፕራይዝ ፕሮግራሞች በተማሪ የሚተዳደሩት ንግዶች የሚሠሩት በግቢው ውስጥ ብቻ ነው፣ እና የሚከተሉትን ያካትታሉ፡- ተመጣጣኝ መኖሪያ ቤት ለአፍሪካ - ይህ ኢንተርፕራይዝ ዓላማው ለዝቅተኛ መካከለኛ ደረጃ ቤተሰቦች በተመጣጣኝ ዋጋ መኖሪያ ቤቶችን ለመመርመር እና ለማዳበር ነው. አግሪኖቬሽን - ይህ ምርትን ለ ማህበረሰብ የሚሸጥ የኦርጋኒክ ማህበረሰብ እርሻ ነው እና ተጨማሪ የኦርጋኒክ ቆሻሻን በግቢው ውስጥ እንደገና ጥቅም ላይ በማዋል ላይ ተጨማሪ ፈጠራን በመፍጠር ሥነ-ምህዳሩን ይደግፋል። ትርኢት - ይህ ኢንተርፕራይዝ ለአፍሪካ አርቲስቶች እና ባለድርሻ አካላት የመስመር ላይ የግንኙነት መድረክን ለመፍጠር ይሰራል - ይህ ኢንተርፕራይዝ ለምርምር እና የኢኮ ባትሪ ኃይልን ለማዳበር ይተገበራል። ግሪንሊንክ - ይህ ድርጅት በ አካባቢን መሰረት ያደረጉ ፈጠራዎች፣ ፕሮጀክቶች፣ ዘመቻዎች እና/ወይም ክለቦችን በመፍጠር ላይ ያተኩራል። የእግር አሻራዎች - ሸቀጣ ሸቀጦች - ቲ-ሸሚዞች, የቡና መያዣዎች, ወዘተ. ዱካ ቦራ - ይህ ኢንተርፕራይዝ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የፍጆታ ዕቃዎችን ለምሳሌ መክሰስ፣መጠጥ፣የአየር ሰአትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለ ማህበረሰብ ለማቅረብ የሚፈልገውን የ ለትርፍ መጫዎቻ ሱቅ ያስተዳድራል። - ይህ ኢንተርፕራይዝ ከ15-17 አመት የሆናቸው ከደቡብ አፍሪካ ልጃገረዶች ጋር ይሰራል እና ጥሩ እውቀት ያለው ውሳኔ እንዲያደርጉ እንደ ስሜታዊ እውቀት እና የጊዜ አጠቃቀም ያሉ ክህሎቶችን ያስተምራቸዋል። - ይህ በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን ትምህርት ውስጥ ይህንን አዲስ አስደሳች ቦታ ለማሰስ ለሚፈልጉ የቴክኖሎጂ ተማሪዎቻችን ማዕከል ነው። - ኢንተርፕራይዙ የ ተማሪዎችን ልምድ፣ሀሳብ እና ተሰጥኦ ለቀሪው አለም የሚያሳይ የመፃፍ፣የምስል እና የፎቶግራፊ ከፍተኛ ጥራት ያለው የሚዲያ መድረክ ነው። - ይህ ድርጅት በአስፐን ውስጥ ለቤዞስ ሊቃውንት ፕሮግራም ለተመረጡ ተማሪዎች ብቻ የተገደበ ነው። ዓመታዊውን የደቡብ አፍሪካ ሃሳቦች ፌስቲቫል () ያስተናግዳሉ። - ይህ ኢንተርፕራይዞች ለ ኢኮኖሚ የምክር አገልግሎት ይሰጣል። አገልግሎቶቹ የሁሉም የተማሪ ኢንተርፕራይዞች ውስብስብ፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የኦዲት እና የፋይናንሺያል ትምህርት ድጋፍን ያጠቃልላል። ለልማት የመጀመሪያ ሀሳቦች ኦሪጅናል ሐሳቦች ለልማት ()፣ ሰፊ ወሰን ያላቸው እና ከተማሪዎቹ ጊዜ በላይ የሚሠሩ ፕሮጀክቶች ናቸው። የአሁኑ ኦአይዲዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፡- - ዓለም አቀፍ የአካታች ትምህርት ስትራቴጂ - አካል ጉዳተኛ ልጆች የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ መርዳት - የካንሰር ግንዛቤ ዘመቻ ባኦባብ - ባህላዊ ግንዛቤን ለመጠበቅ እና ለማመቻቸት የቃል ታሪኮችን በመስመር ላይ ማንሳት ግሪንዶርም - በግቢው ውስጥ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆነ ኑሮ (ውስጣዊ) አልማስ (የቀድሞው ኒኬ) - የውበት ክሬም በመጠቀም የፀረ-ወባ ክሬም ለመፍጠር እና ለማሰራጨት የገንዘብ ድጋፍ - የትምህርት የሂሳብ ዲቪዲዎች ማምረት ኦያማ - ለወጣት አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎች ብዙ ሕዝብ የሚፈጥር መድረክ የአፍሪካ ባካሎሬት - የአፍሪካ የራሷ የሥርዓተ ትምህርት ንድፍ ሳይካ - ስለ አፍሪካ አህጉር የተሳሳቱ ቅድመ-ግምቶችን ለማቃለል የማህበራዊ ትስስር መድረክ ራዲዮ - አንዳንድ የአህጉሪቱን አንገብጋቢ ጉዳዮች በመዳሰስ በአፍሪካ ወጣቶች መካከል የእውቀት ጥያቄን ለማነሳሳት የተዘጋጀ የራዲዮ ጣቢያ - ወጣት ልጃገረዶች ወጣት እና ንቁ ሴቶች እንዲሆኑ ለማድረግ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ክህሎት ያላቸው ልጃገረዶችን ለማስታጠቅ የሚፈልግ የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክት ነው። ክትትል የሚደረግባቸው ጉዞዎች ተማሪዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ፣ አፍሪካ እና አለምን ያስሳሉ፣ በሽርሽር ፕሮግራም ላይ በመሳተፍ። የውጪ አድናቂዎች ቅዳሜና እሁድ በድራከንስበርግ ተራሮች የእግር ጉዞ ጉዞዎች እና በበዓል ሰአታት ረጅም ጉዞዎች ላይ ይሳተፋሉ፣ ሳይንቲስቶች ደግሞ በአሜሪካ የሳይንስ እድገት ማኅበር ለመሳተፍ ማመልከት ይችላሉ። ዓለም አቀፍ ምሁራን ፕሮግራም የአለም ምሁራን ፕሮግራም የሶስት ሳምንት አለም አቀፋዊ የአመራር የክረምት ፕሮግራም ነው እድሜያቸው ከ13-19 ለሆኑ ታዳጊዎች። በአለም ዙሪያ ያሉ የሌሎች ሀገራት ተማሪዎች ወደ የመምጣት እድል ያገኛሉ እና ስለ አህጉሪቱ እንዲሁም ከአመራር እና ስራ ፈጣሪነት ጋር የተያያዙ ክህሎቶችን ይማራሉ. የካታሊስት ጊዜ ከዓለም ዙሪያ ላሉ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እንደ ማህበራዊ ፈጠራዎች ለማዳበር የውጭ አገር ጥናት። ተማሪዎች በ ውስጥ ሶስት ወር ወይም ሙሉ አመት ለመውሰድ መምረጥ ይችላሉ። ሞዴል የአፍሪካ ህብረት በዓለም ዙሪያ ከሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተሳታፊዎች በአህጉሪቱ በጣም ውስብስብ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የሚከራከሩበት እና የሚወያዩበት የአራት ቀናት ኮንፈረንስ ነው። በአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት እና የውጭ ፖሊሲ ባለሙያዎች ገለጻ ላይ ተሳታፊዎችም ይገኛሉ። አንዚሻ ሽልማት የአንዚሻ ሽልማት ለማህበራዊ ተግዳሮቶች ፈጠራ መፍትሄዎችን ያዳበሩ እና ተግባራዊ ያደረጉ ወይም በማህበረሰባቸው ውስጥ ስኬታማ የንግድ ሥራዎችን የጀመሩ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ለመሸለም ይፈልጋል። ከመላው አፍሪካ የተውጣጡ 15 የፍጻሜ እጩዎች በህይወት ዘመን ሁሉ የስራ ፈጠራ ስኬት መንገዳቸውን ለማፋጠን የሚረዳውን ቦታ አሸንፈዋል። በዚህ ጉዞ ውስጥ የመጀመሪያው እርምጃ በጆሃንስበርግ ወጣ ብሎ በሚገኘው የአፍሪካ ሊደርሺፕ አካዳሚ ካምፓስ ለአስር ቀናት የሚቆይ የስራ ፈጠራ አውደ ጥናት እና ኮንፈረንስ አካል ለመሆን ሁሉንም ወጪ የሚከፈልበት ጉዞ ወደ ደቡብ አፍሪካ ማሸነፋቸው ነው። ከእነዚህ የመጨረሻ እጩዎች የተመረጡት ታላቅ ሽልማት አሸናፊዎች የ100,000 ዶላር ዋጋ ያላቸውን ሽልማቶች ይጋራሉ። ህብረቱ በመቀጠል ይቀጥላል፣በስራዎቻቸው ውስጥ የእድገት አቅምን ለመክፈት፣ከአለምአቀፍ የመሪዎች አውታረ መረብ ጋር በማገናኘት፣የአለምአቀፍ የንግግር እድሎችን እና ሙያዊ እድገታቸውን የሚደግፉ የንግድ የማማከር አገልግሎቶችን ይሰጣል። ከ 100 000 ዶላር ውድድር በተጨማሪ የአንዚሻ ሽልማት በአፍሪካ ውስጥ የስራ ፈጣሪዎችን ቁጥር በመሠረታዊነት እና በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ይፈልጋል ። ይህን ለማድረግ ዋናው ነገር ከፍተኛ አቅም ያላቸውን ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች (ከ15 እስከ 22 ዓመት ዕድሜ ያላቸውን) ለመለየት፣ ለማሰልጠን እና ለማገናኘት ሞዴሎችን መፈተሽ፣ መተግበር እና ማጋራት ሲሆን ይህም በርካታ ድርጅቶች የቧንቧ ሥራ ፈጣሪዎችን በመፍጠር ረገድ የተሻለ የጋራ ስኬት እንዲኖራቸው ማድረግ ነው ብለው ያምናሉ። የመጠን ችሎታዎች ጋር. በጣም ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ያክብሩ እና ታሪኮቻቸውን በንቃት ያካፍሉ፣ ሌሎችም ስኬታቸውን ለመምሰል የሚመርጡበትን እድል ለመጨመር። (የእኛን የቅርብ ጊዜ የጋላ ሽልማት ድምቀቶች፣ የአንዚሻ ሽልማት ገላጭ ቪዲዮ ይመልከቱ እና የቅርብ ጊዜ መጽሄታችንን ያንብቡ) በጣም ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ማሰልጠን እና ማፋጠን፣ በዚህም የኢንተርፕረነር ትምህርት ሞዴሎችን እንድናዳብር እና እንድንካፈል እና ከታዳጊ ወጣቶች እና በጣም ወጣት ጎልማሶች ጋር ስኬታማ የመሆን እድላቸው ሰፊ ነው። (ስለ ህብረት ልምዳችን አንብብ እና ጓደኞቻችንን አግኝ) የኢንተርፕረነርሺፕ ትምህርትን (ሁለተኛ እና ከፍተኛ ደረጃ) ላይ ተጽእኖ ያሳድራሉ ብዙ ወጣት ስራ ፈጣሪዎችን እድል ለመጨመር ብቻ ሳይሆን ለሌሎች እንደ ምርጫ ርህራሄ እና ለስራ ፈጣሪነት ድጋፍ. (ስለ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ኢንተርፕራይዝ ፕሮግራም ቪዲዮ ይመልከቱ) አፍሪካ የሙያ አውታረ መረብ አፍሪካ የስራ አውታረ መረብ (ኤሲኤን) ወጣት አፍሪካዊ ተሰጥኦዎችን ከ እና ከማስተር ፋውንዴሽን ምሁራኖች ፕሮግራም ጋር በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ ከሚያሳድር የስራ ልምምድ እና የስራ እድሎች ጋር የሚያገናኝ መድረክ ነው። ዓለም አቀፍ አማካሪ ምክር ቤት እንዲሁም የአስተዳዳሪዎች ቦርድ ፣ የአካዳሚው ግሎባል አማካሪ ካውንስል በቢዝነስ፣ በአመራር ልማት፣ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና በማህበራዊ ስራ ፈጠራ ዘርፍ አፍሪካውያን እና አለም አቀፋዊ ምሁራንን ያቀፈ ነው። የአለምአቀፍ አማካሪ ካውንስል ለ አስተዳደር ቡድን ስልታዊ ግብአት እና መመሪያ ይሰጣል። የአፍሪካ አመራር ፋውንዴሽን የአፍሪካ አመራር አካዳሚ እና ቀጣዩን የአፍሪካ መሪዎችን የሚደግፍ ዩኤስኤ 501(ሐ) ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው። የአፍሪካ አመራር አካዳሚ ድረ-ገጽ የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ ፈተናዎች የደቡብ አፍሪካ ሚዲያ ክለብ አረንጓዴ በማስተጋባት ላይ የአልማዝ ማበረታቻ ፈንድ ኤምቪ ጋዜጣ ዓለም አቀፍ ለውጥ ፈጣሪዎች ዕለታዊ ትርኢት ሃፊንግተን ፖስት የመጀመርያው የአፍሪካ አመራር ኢንዳባ
11934
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%BB%E1%88%AD%E1%88%8D%20%E1%8B%B0%20%E1%8C%8E%E1%88%8D
ሻርል ደ ጎል
ቻርለስ አንድሬ ጆሴፍ ማሪ ደ ጎል (/ /፤ የፈረንሳይ አጠራር: []፤ ህዳር 22 ቀን 1890 - ህዳር 9 ቀን 1970) በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ነፃ ፈረንሳይን በናዚ ጀርመን ላይ የመራ የፈረንሳይ ጦር መኮንን እና የሀገር መሪ ነበር። በፈረንሳይ ዲሞክራሲን ለመመለስ ከ1944 እስከ 1946 የፈረንሳይ ሪፐብሊክ ጊዜያዊ መንግስትን በሊቀመንበርነት መርተዋል። እ.ኤ.አ. በ 1958 በፕሬዚዳንት ሬኔ ኮቲ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት (ጠቅላይ ሚኒስትር) ሲሾሙ ከጡረታ ወጡ ። በሪፈረንደም ከፀደቀ በኋላ የፈረንሳይን ሕገ መንግሥት እንደገና ፃፈ እና አምስተኛውን ሪፐብሊክ መሰረተ። እ.ኤ.አ. በ 1965 ድጋሚ የተመረጡበት እና በ 1969 ስልጣን እስከለቀቁበት ጊዜ ድረስ የቆዩበት የፈረንሣይ ፕሬዝደንትነት በዚያው ዓመት በኋላ ተመረጡ ። በሊል ተወልዶ በ1912 ከሴንት-ሲር ተመረቀ። የአንደኛው የዓለም ጦርነት ያጌጠ መኮንን ነበር፣ ብዙ ጊዜ ቆስሏል እና በኋላም በቬርደን ታሰረ። በጦርነቱ ወቅት፣ ተንቀሳቃሽ የታጠቁ ክፍሎችን ይደግፋል። እ.ኤ.አ. በግንቦት 1940 በጀርመን ወረራ ወቅት ወራሪዎችን የሚያጠቃ የታጠቀ ክፍል መርቷል ። ከዚያም ለጦርነት ምክትል ጸሐፊ ተሾመ. ደ ጎል ከጀርመን ጋር የሚያደርገውን መንግሥታዊ ጦር አልቀበልም በማለቱ ወደ እንግሊዝ ሸሽቶ ፈረንሳዮች ወረራውን እንዲቃወሙ እና ትግሉን እንዲቀጥሉ በጁን 18 አሳስቧል። የፍሪ ፈረንሣይ ጦርን መርቶ በኋላም የፈረንሳይ ብሔራዊ ነፃ አውጪ ኮሚቴን በአክሲው ላይ መርቷል። ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የቀዘቀዘ ግንኙነት ቢኖረውም፣ በአጠቃላይ የዊንስተን ቸርችል ድጋፍ አግኝቶ የማያከራክር የፍሪ ፈረንሳይ መሪ ሆኖ ብቅ አለ። እ.ኤ.አ. በሰኔ 1944 የፈረንሳይ ነፃ ከወጣች በኋላ ጊዜያዊ መንግስት የፈረንሳይ ሪፐብሊክ ጊዜያዊ መንግስት መሪ ሆነ። በ1944 መጀመሪያ ላይ ዴ ጎል ዲ. የአልጄሪያ ጦርነት ያልተረጋጋውን አራተኛውን ሪፐብሊክ ሲበጣጠስ፣ ብሄራዊ ምክር ቤቱ በግንቦት 1958 ቀውስ ውስጥ ወደ ስልጣን እንዲመለስ አደረገው። አምስተኛውን ሪፐብሊክን በጠንካራ ፕሬዚደንትነት መስርቷል፣ እናም በዚህ ተግባር እንዲቀጥል ተመረጠ። ጦርነቱን ለማቆም እርምጃዎችን ሲወስድ ፈረንሳይን አንድ ላይ ማቆየት ችሏል፣ ይህም የፒድስ-ኖየርስ (በአልጄሪያ የተወለዱት ፈረንሣይ ብሔር ተወላጆች) እና የታጠቁ ኃይሎችን አስቆጥቷል። ሁለቱም ቀደም ሲል ቅኝ ገዥነትን ለማስጠበቅ ወደ ስልጣን መመለሱን ደግፈዋል። ለአልጄሪያ ነፃነት ሰጠ እና ወደ ሌሎች የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ቀስ በቀስ እርምጃ ወሰደ። ከቀዝቃዛው ጦርነት አውድ አንፃር፣ ዴ ጎል ፈረንሳይ እንደ ዋና ሃይል በሌሎች አገሮች፣ እንደ አሜሪካ፣ ለብሔራዊ ደኅንነት እና ብልጽግናዋ መታመን እንደሌለባት በማስረግ “የታላቅ ፖለቲካውን” አነሳ። ለዚህም ከኔቶ የተቀናጀ ወታደራዊ እዝ እንዲወጣና ራሱን የቻለ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዲጀምር ያደረገውን “የአገራዊ ነፃነት” ፖሊሲ ተከተለ።የዓለም አምስተኛው የኑክሌር ኃይል. በጥር 22 ቀን 1963 የኤሊሴ ስምምነትን በመፈረም በአንግሎ አሜሪካ እና በሶቪየት ተፅእኖ መስኮች መካከል የአውሮፓ ሚዛን ለመፍጠር የፍራንኮ-ጀርመን ግንኙነቶችን መልሷል ። ዴ ጎል አውሮፓን የሉዓላዊ ሀገራት አህጉር አድርጎ በመደገፍ የበላይ የሆነ የአውሮፓን ማንኛውንም እድገት ተቃወመ። ዴ ጎል በቬትናም ውስጥ የዩናይትድ ስቴትስ ጣልቃ ገብነት እና የዩናይትድ ስቴትስ ዶላርን "የተጋነነ ልዩ መብት" በግልፅ ተችቷል. በኋለኞቹ ዓመታት፣ “” የሚለውን መፈክር መደገፉ እና ብሪታንያ ወደ አውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ እንድትገባ ያደረገው ሁለት ተቃውሞ በሰሜን አሜሪካ እና በአውሮፓ ከፍተኛ ውዝግብ አስነስቷል። እ.ኤ.አ. በ1965 ለፕሬዝዳንትነት በድጋሚ ቢመረጥም፣ በግንቦት 1968 በተማሪዎች እና በሰራተኞች ሰፊ ተቃውሞ ገጥሞት ነበር፣ ነገር ግን የሰራዊቱን ድጋፍ አግኝቶ በብሔራዊ ምክር ቤት አብላጫ ድምጽ በምርጫ አሸንፏል። ዴ ጎል እ.ኤ.አ ተጨማሪ ያልተማከለ. ከአንድ አመት በኋላ በኮሎምቤይ-ሌ-ዴክስ-ኤግሊሴስ በሚገኘው መኖሪያው ሞተ፣ የፕሬዚዳንታዊ ትዝታውንም ሳያጠናቅቅ ቀረ። ብዙ የፈረንሳይ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና መሪዎች የ ቅርስ ይላሉ; በፈረንሣይ ውስጥ ብዙ ጎዳናዎች እና ሀውልቶች ከሞቱ በኋላ ለመታሰቢያነቱ ተሰጥተዋል።. የመጀመሪያ ህይወት ልጅነት እና አመጣጥ ቻርለስ አንድሬ ጆሴፍ ማሪ ደ ጎል የተወለደው እ.ኤ.አ. ህዳር 22 ቀን 1890 በሊል በኖርድ ዲፓርትመንት ውስጥ ከአምስት ልጆች ሦስተኛው ነው። ያደገው አጥባቂ ካቶሊክ እና ባህላዊ ቤተሰብ ውስጥ ነው። አባቱ ሄንሪ ደ ጎል በአንድ የጄሰስ ኮሌጅ የታሪክ እና ስነ-ጽሁፍ ፕሮፌሰር ነበር እና በመጨረሻም የራሱን ትምህርት ቤት አቋቋመ። ደ ጎል በ1897፣ በ7 ዓመቱ ሄንሪ ደ ጎል ከኖርማንዲ እና ቡርገንዲ ከረዥም የፓርላሜንታሪ ጄኔራል መጣ።፡ 13–16 ይህ ስም መነሻው ደች እንደሆነ ይታሰባል እና ምናልባት ከቫን ደር ዋል ደ ዋል ("ከግምብ፣ ከመከላከያ ግንብ የተወሰደ ሊሆን ይችላል። ") ወይም "): 42 የዴ ጎል እናት ዣን (የተወለደው ማይሎት) ከሊል ሀብታም ሥራ ፈጣሪዎች ቤተሰብ የተገኘ ነው። እሷ ፈረንሳይኛ፣ አይሪሽ፣ ስኮትላንዳዊ እና የጀርመን ዝርያ ነበራት።፡- 13–16 የዴጎል አባት በልጆቻቸው መካከል በምግብ ሰዓት ታሪካዊ እና ፍልስፍናዊ ክርክርን ያበረታታ ነበር፣ እና በማበረታቻውም ዴ ጎል ከልጅነቱ ጀምሮ የፈረንሳይን ታሪክ ጠንቅቆ ያውቅ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1870 በሴዳን ፈረንሣይ ለጀርመኖች የፈረንሣይ ንግግር በሰማች ጊዜ በልጅነቷ እንዴት እንዳለቀሰች እናቱ በተናገሩት ታሪክ ተደንቆ ስለ ወታደራዊ ስትራቴጂ ከፍተኛ ፍላጎት አዳበረ። እሱ ደግሞ የዌልስ፣ ስኮትስ፣ አይሪሽ እና ብሬቶንስ ወደ አንድ ህዝብ መቀላቀልን የሚደግፉ መጽሃፎችን እና በራሪ ጽሑፎችን የጻፈ የታሪክ ምሁር እና ስሜታዊ ሴልቲክስት በሆነው ቻርለስ ደ ጎል በሚባለው አጎቱ ተጽዕኖ አሳድሯል። አያቱ ጁሊን-ፊሊፕም የታሪክ ምሁር ነበሩ፣ እና አያቱ ጆሴፊን-ማሪ የክርስትና እምነቱን የሚነኩ ግጥሞችን ጽፋለች። የትምህርት እና የአዕምሮ ተጽእኖዎች በአስር ዓመቱ የመካከለኛው ዘመን ታሪክን ያነብ ነበር። ደ ጎል መጻፍ የጀመረው ገና በጉርምስና ዕድሜው ነበር ፣ በተለይም ግጥም ፣ እና በኋላ ቤተሰቦቹ ለአንድ ተጓዥ በግጥም የተፃፈውን የአንድ ድርሰት ተውኔት በግል እንዲታተም ከፈለ። ጎበዝ አንባቢ ስለነበር እንደ በርግሰን፣ ፔጊ እና ባሬስ ባሉ ጸሃፊዎች የፍልስፍና ቶሞችን ይወድ ነበር። ከጀርመናዊው ፈላስፋዎች ኒቼ፣ ካንት እና ጎተ በተጨማሪ የጥንቶቹ ግሪኮች (በተለይ የፕላቶ) ስራዎች እና የሮማንቲስት ገጣሚው ቻቴውብሪያንድ ድርሰት አንብቧል። ደ ጎል በፓሪስ በኮሌጅ ስታኒስላስ የተማረ እና ለአጭር ጊዜ በቤልጂየም ከተማረ በኋላ ታሪክን የማንበብ እና የማጥናት ፍላጎቱን ማሳየቱን ቀጠለ እና ብዙ የሀገሩ ሰዎች በሀገራቸው ስኬት የተሰማቸውን ታላቅ ኩራት አጋርተዋል። በ1930 በጀርመን ላይ ድል እንዲቀዳጅ የፈረንሣይ ጦርን እየመራ “ጄኔራል ደ ጎል” የሚል ጽሁፍ አሥራ አምስት ጻፈ። በወጣትነቱ በ1870 የፈረንሣይ ሽንፈትን ለመበቀል ከጀርመን ጋር የሚደረገውን የማይቀር ጦርነት በተወሰነ የዋህነት ተስፋ ይጠባበቅ እንደነበር ጽፏል። ደ ጎል በ1908 ዓ.ም በዴ ጎል የጉርምስና ወቅት ፈረንሳይ የተከፋፈለ ማህበረሰብ ነበረች፣ ለዴ ጎል ቤተሰብ የማይመቹ ብዙ እድገቶች ነበሩት፡ የሶሻሊዝም እና የሲንዲካሊዝም እድገት፣ የቤተክርስቲያን እና የመንግስት ህጋዊ መለያየት በ1905 እና የውትድርና አገልግሎት ጊዜ ቀንሷል። በተመሳሳይ ዓመት ውስጥ ሁለት ዓመታት. የኢንቴንቴ ኮርዲያል ከብሪታንያ፣የመጀመሪያው የሞሮኮ ቀውስ እና ከሁሉም በላይ የድሬይፉስ ጉዳይ ያልተቀበሉ ነበሩ። ሄንሪ ዴ ጎል የድሬይፉስ ደጋፊ ለመሆን መጣ፣ ነገር ግን ሰራዊቱ በራሱ ላይ ካመጣው ውርደት ይልቅ ስለ ንፁህነቱ ብዙም አላሳሰበውም። በዚሁ ወቅት በወንጌላውያን ካቶሊካዊነት፣ የ ፣ መሰጠት እና የጆአን ኦፍ አርክ አምልኮ መነሳት እንደገና መነቃቃት ታይቷል።፡ 50–51 ዴ ጎል በአሥራዎቹ አጋማሽ ላይ እስከ አሥራዎቹ አጋማሽ ድረስ ጎበዝ ተማሪ አልነበረም፣ ነገር ግን ከሐምሌ 1906 ጀምሮ በወታደራዊ አካዳሚ ውስጥ የጦር መኮንን ሆኖ ለመሠልጠን ቦታ በማሸነፍ በትምህርት ቤት በትጋት ሠርቷል፣ ሴንት-ሲር ላኮቱር ደ ጎል እንደተቀላቀለ ይጠቁማል። ሠራዊቱ ምንም እንኳን በፀሐፊነት እና በታሪክ ምሁርነት ለሥራው የበለጠ ተስማሚ ቢሆንም በከፊል አባቱን ለማስደሰት እና በከፊል መላውን የፈረንሳይ ማህበረሰብ የሚወክሉ ጥቂት አንድነት ኃይሎች አንዱ ስለሆነ። በኋላ ላይ “ሠራዊት ውስጥ ስገባ በዓለም ላይ ካሉት ታላላቅ ነገሮች አንዱ ነበር” ሲል ጽፏል፡ 51 ላኩተር ያመለከተው የይገባኛል ጥያቄ በጥንቃቄ መታከም አለበት፡ በ1900ዎቹ መጀመሪያ ላይ የሰራዊቱ ስም ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ነበር። ከድሬይፉስ ጉዳይ በኋላ. አድማ ለመስበር በስፋት ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን በ1908 የቅዱስ ሲር አመልካቾች ከ700 ያነሱ ነበሩ፣ ይህም በክፍለ ዘመኑ መባቻ ላይ ከ2,000 ዝቅ ብሏል የመጀመሪያ ሥራ ኦፊሰር ካዴት እና ሌተናት በ1909 ደ ጎል በሴንት ሲር ቦታ አሸንፏል።የክፍሉ ደረጃ መካከለኛ ነበር (ከ221 ተመዝጋቢዎች 119ኛ) ግን በአንጻራዊ ወጣት ነበር እና ይህ የፈተናው የመጀመሪያ ሙከራው ነበር። እ.ኤ.አ. በማርች 21 ቀን 1905 ዓ.ም በወጣው ህግ መሰረት የሰራዊት መኮንኖች ወደ አካዳሚው ከመሄዳቸው በፊት በግላቸው እና እንደ ጊዜን ጨምሮ በማዕረግ አንድ አመት እንዲያገለግሉ ይጠበቅባቸው ነበር። በዚህ መሠረት በጥቅምት 1909 ዴ ጎል በ 33 ኛው እግረኛ ክፍለ ጦር የፈረንሣይ ጦር ሠራዊት ውስጥ በአራስ ላይ ተመዝግቧል (እንደአስፈላጊነቱ ለአራት ዓመታት ፣ እንደ አስፈላጊነቱ ፣ ለግዳጅ የሁለት ዓመት ጊዜ) ። ይህ ታሪካዊ ክፍለ ጦር ነው ። ከአውስተርሊትዝ፣ ዋግራም እና ቦሮዲኖ ጋር በጦርነት ክብሩ ውስጥ።[በሚያዝያ 1910 ወደ ኮርፖራልነት ከፍ ብሏል። የኩባንያው አዛዥ ለሰራተኛ መደበኛ ማዕረግ ሊያሳድገው ፍቃደኛ አልሆነም ፣ ወጣቱ ከፈረንሣይ ኮንስታብል ያነሰ ምንም ነገር እንደማይጠቅመው በግልፅ እንደተሰማው አስተያየት ሰጥቷል። በመጨረሻም በሴፕቴምበር 1910 ወደ ሳጅንነት ከፍ ብሏል። ደ ጎል በጥቅምት 1910 በሴንት ሲር ቦታውን ያዘ።በመጀመሪያው አመት መጨረሻ 45ኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። በቅዱስ ሲር ደ ጎል በቁመቱ (196 ሴ.ሜ ፣ 6'5) ፣ ግንባሩ እና አፍንጫው የተነሳ “ታላቁ አስፓራጉስ” የሚል ቅጽል ስም አግኝቷል። ስነምግባር፣ ብልህነት፣ ባህሪ፣ የውትድርና መንፈስ እና ድካምን መቋቋም በ1912 በክፍላቸው 13ኛ ተመረቀ እና ያለፈው ዘገባው እሱ ጥሩ መኮንን እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም ፣የወደፊቱ ማርሻል አልፎንዝ ጁን ተሰጥኦ ያለው ካዴት እንደነበር ገልጿል። ምንም እንኳን ሁለቱ በወቅቱ የቅርብ ጓደኛሞች ባይመስሉም በመጀመሪያ ክፍል ውስጥ ወጡ። ከሩቅ የባህር ማዶ ቅኝ ግዛቶች ይልቅ በፈረንሳይ ማገልገልን በመምረጡ፣ በጥቅምት 1912 33ኛውን እግረኛ ክፍለ ጦርን በሶስ-ሌተናንት (ሁለተኛው ሌተና) ተቀላቀለ። ክፍለ ጦር አሁን በኮሎኔል (እና በወደፊቱ ማርሻል) ፊሊፕ ፔታይን የታዘዘ ነበር፣ እሱም ደ ጎል ለሚቀጥሉት 15 አመታት ይከተላል። በኋላም በማስታወሻው ላይ “የመጀመሪያዬ ኮሎኔል ፔታይን የትእዛዝ ጥበብን አስተምሮኛል” በማለት ጽፏል። አንደኛው የዓለም ጦርነት በተጠናከረበት ወቅት ዴ ጎል ስለ ፈረሰኞች እና ስለ መትረየስ ሽጉጥ እና ሽቦ መትረየስ ዘመን ስለ ፈረሰኞች እና ስለ ባሕላዊ ዘዴዎች ከፔታይን ጋር እንደተስማማ እና ብዙ ጊዜ ታላላቅ ጦርነቶችን እና የትኛውም ውጤት ሊኖር እንደሚችል ይከራከር እንደነበር ይነገራል። ከአለቃው ጋር ጦርነት እየመጣ ነው። ላኮቱር ተጠራጣሪ ነው፣ ምንም እንኳን ፔቴይን በ1913 የመጀመሪያዎቹ ሁለት አራተኛ ላይ ስለ ዴ ጎል አስደናቂ ግምገማዎችን ቢፅፍም እሱ በትእዛዝ ስር ከነበሩት 19 ካፒቴኖች እና 32 ሻለቃዎች መካከል ጎልቶ አይታይም ማለት አይቻልም። ዴ ጎል በ 1913 አራስ ማኑዋቭስ ላይ ተገኝቶ ነበር ፣ በዚህ ጊዜ ፔታይን ጄኔራል ጋሌትን በፊቱ ተችቷል ፣ ግን በማስታወሻ ደብተሮቹ ውስጥ የፔይንን ቅጥ ያጣ ሀሳቦች በዋና አስተምህሮው ላይ አጽንዖት የሚሰጠውን የእሳት ኃይል አስፈላጊነት እንደተቀበለ የሚያሳይ ምንም ማስረጃ የለም ። አጸያፊ መንፈስ" ዴ ጎል ሞሪስ ዴ ሳክ የእሳተ ገሞራ እሳትን እንዴት እንደከለከለ፣ በናፖሊዮን ዘመን የነበሩት የፈረንሳይ ጦር በእግረኛ አምድ ጥቃት ላይ እንዴት እንደተደገፈ፣ እና የፈረንሳይ ወታደራዊ ሃይል እንዴት በአስራ ዘጠነኛው ክፍለ-ዘመን እንደቀነሰ አፅንዖት ሰጥቷል - በሚታሰበው - በእሳት ኃይል ላይ ከመጠን ያለፈ ትኩረትን (ለምሳሌ ቻሴፖት)። ጠመንጃ) ከኤላን ይልቅ። በቅርቡ ከሩስ-ጃፓን ጦርነት የተወሰደውን የወቅቱን ፋሽን ትምህርት የተቀበለው ይመስላል፣ የጃፓን እግረኛ ወታደሮች ባዮኔት ክስ በጠላት የእሳት ኃይል ፊት እንዴት እንደተሳካለት ይገልጻል። ደ ጎል በጥቅምት 1913 (አውሮፓዊ) ወደ መጀመሪያው ሌተናነት አደገ። የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት እ.ኤ.አ. በነሀሴ 1914 መጨረሻ ላይ በፈረንሳይ ጦርነት በተቀሰቀሰበት ወቅት፣ በፈረንሳይ ካሉት ምርጥ ተዋጊ ክፍሎች አንዱ የሆነው 33ኛው ክፍለ ጦር ጀርመናዊውን ግስጋሴ በዲናንት ለማየት ወዲያውኑ ተጣለ። ሆኖም የፈረንሣይ አምስተኛው ጦር አዛዥ ጄኔራል ቻርለስ ላንሬዛክ ከ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የውጊያ ስልቶች ጋር ትዳር መሥርተው ቆይተዋል፣ ክፍሎቹን ከጀርመን መድፍ ጋር የሚቃወሙ በትሮች እና ባለ ሙሉ ቀለሞች ትርጉም በሌለው የባዮኔት ክሶች ላይ በመወርወር ከባድ ኪሳራ አስከትሏል። እንደ ጦር አዛዥ፣ ደ ጎል ገና ከጅምሩ ከባድ ጦርነት ውስጥ ይሳተፍ ነበር። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 15 ቀን የእሳት ጥምቀትን የተቀበለው እና በመጀመሪያ ከቆሰሉት መካከል አንዱ ነበር ፣ በዲናንት ጦርነት በጉልበቱ ላይ ጥይት ተቀብሏል። የፈረንሳይ ጦር ጊዜ ያለፈበት ዘዴዎችን በመቃወም ከተጎዱ ሌሎች መኮንኖች ጋር. ይሁን እንጂ በዘመናዊው ጦርነት ውስጥ የመድፍን አስፈላጊነት እንደተረዳ የሚያሳይ ምንም ወቅታዊ ማስረጃ የለም. ይልቁንም በጊዜው በፃፈው ፅሁፍ፣ “ከመጠን በላይ” ያለውን ጥቃት፣ የፈረንሳይ ጄኔራሎች በቂ አለመሆን እና “የእንግሊዝ ወታደሮች ዘገምተኛነት” ሲሉ ተችተዋል። የ7ኛው ኩባንያ አዛዥ በመሆን በጥቅምት ወር ወደ ክፍለ ጦርነቱ ተቀላቀለ። ብዙዎቹ የቀድሞ ጓዶቹ ሞተዋል። በታኅሣሥ ወር የሬጅመንታል ረዳት ሆነ። የዴ ጎል ክፍል የጠላትን ንግግር ለማዳመጥ ወደ ማንም ሰው ምድር በተደጋጋሚ በመዝለቁ እውቅናን አግኝቷል እናም ተመልሶ የመጣው መረጃ በጣም ጠቃሚ ነበር በጥር 18 ቀን 1915 ክሮክስ ደ ጉሬርን ተቀበለ ። በፌብሩዋሪ 10 መጀመሪያ ላይ በሙከራ ላይ ወደ ካፒቴን ከፍ ብሏል። እ.ኤ.አ. ማርች 10 ቀን 1915 ዴ ጎል በግራ እጁ በጥይት ተመታ ፣ ይህ ቁስል መጀመሪያ ላይ ቀላል ቢመስልም በቫይረሱ ​​​​ተይዟል። ቁስሉ ለአራት ወራት ያህል አቅመ-ቢስ አድርጎታል እና በኋላም የጋብቻ ቀለበቱን በቀኝ እጁ እንዲለብስ አስገደደው።፡ 61 በነሐሴ ወር ወደ ሬጅመንታል ረዳትነት ከመመለሱ በፊት 10ኛውን ድርጅት አዘዘ። ሴፕቴምበር 3 ቀን 1915 የመቶ አለቃ ማዕረግ ቋሚ ሆነ። በጥቅምት ወር መጨረሻ, ከእረፍት ሲመለስ, እንደገና ወደ 10 ኛ ኩባንያ አዛዥነት ተመለሰ. እ.ኤ.አ. ማርች 2 1916 በዱዋሞንት (በቨርዱን ጦርነት ወቅት) የኩባንያ አዛዥ ሆኖ ፣ በጠላት ከተከበበ ቦታ ለመውጣት ክስ እየመራ ሳለ ፣ ግራ ከተጋባ በኋላ በግራ ጭኑ ላይ የባዮኔት ቁስል ደረሰበት ። በሼል እና ከመርዝ ጋዝ ተጽእኖዎች ካለፉ በኋላ ተይዟል. ከሻለቃው ከተረፉት ጥቂቶች አንዱ ነበር።፡ 63 በጀርመን ወታደሮች ከባዶ የሼል ጉድጓድ አውጥቶ እስረኛ ተወሰደ። ፀረ ጋውሊስቶች እሱ በእርግጥ እጅ ሰጠ የሚል ወሬ ሲያሰራጩ የተያዙበት ሁኔታ ከጊዜ በኋላ የክርክር ርዕሰ ጉዳይ ይሆናል ፣ ይህም የይገባኛል ጥያቄ ደ ጎል ያለ አግባብ ውድቅ አደረገው ። ደ ጎል 32 ወራትን በስድስት የተለያዩ እስረኛ ካምፖች አሳልፏል፣ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜውን ያሳለፈው በ ]፣: 40 ህክምናው አጥጋቢ በሆነበት ነው። በግዞት ውስጥ፣ ደ ጎል የጀርመን ጋዜጦችን አነበበ (በትምህርት ቤት ጀርመንኛ ተምሯል እና በጀርመን የክረምት ዕረፍትን አሳልፏል) እና ስለ ግጭቱ ሂደት ያለውን አመለካከት ለሌሎች እስረኞች ንግግር አድርጓል። የአርበኝነት ስሜቱ እና በአሸናፊነት ላይ ያለው እምነት አሁንም ሌላ ቅጽል ስም አስገኝቶለታል, ("ኮንስታብል"), የመካከለኛው ዘመን የፈረንሳይ ጦር ሰራዊት ዋና አዛዥ ማዕረግ. በኢንጎልስታድት ደግሞ ጋዜጠኛ ሬሚ ሩሬ በመጨረሻ የዴ ጎል የፖለቲካ አጋር እና ሚካሂል ቱካቼቭስኪ የቀይ ጦር የወደፊት አዛዥ ነበሩ። ደ ጎል እንደ ጦር ሃይል በነበረበት ወቅት ቱካቼቭስኪን በደንብ ያውቀዋል። በጦርነት እስረኛ በነበረበት ጊዜ ደ ጎል በጀርመን ኃይሎች መካከል ያለውን ችግርና መከፋፈል በመተንተን ዲኮርዴ ቼዝ ሊኔሚ () የተሰኘውን የመጀመሪያውን መጽሃፉን ጻፈ። መጽሐፉ የታተመው በ1924 ነው።፡ 83 ደ ጎል ለማምለጥ አምስት ሙከራዎችን አድርጓል፣ እና ከፍተኛ ጥበቃ ወደሚደረግበት ተቋም ተወስዶ ሲመለስ ለረጅም ጊዜ በብቸኝነት እንዲቆይ እና እንደ ጋዜጦች እና ትምባሆ ያሉ መብቶችን በማንሳት ተቀጥቷል። በልብስ ማጠቢያ ቅርጫት ውስጥ ተደብቆ፣ ዋሻ በመቆፈር፣ ግድግዳ ላይ ጉድጓድ በመቆፈር አልፎ ተርፎም ጠባቂዎቹን ለማሞኘት እንደ ነርስ በመምሰል ለማምለጥ ሞከረ። ለወላጆቹ በጻፈው ደብዳቤ ላይ ያለ እሱ ጦርነቱ መቀጠሉ የተሰማውን ብስጭት ደጋግሞ ተናግሮ ሁኔታውን “አሳፋሪ መጥፎ ዕድል” ብሎ በመጥራት እና ከመሳደብ ጋር አወዳድሮታል። ጦርነቱ ወደ ፍጻሜው ሲቃረብ በድሉ ላይ ምንም አይነት ሚና ባለመጫወቱ በጭንቀት ተውጦ ነበር፣ ነገር ግን ጥረቱን ቢያደርግም እስከ ጦር ሰራዊት ድረስ በግዞት ቆይቷል። በታኅሣሥ 1 1918፣ ከሶስት ሳምንታት በኋላ፣ ሁሉም በሠራዊቱ ውስጥ ካገለገሉት እና ከጦርነቱ የተረፉት ከሶስት ወንድሞቹ ጋር ለመገናኘት በዶርዶኝ ወደሚገኘው የአባቱ ቤት ተመለሰ። በጦርነቶች መካከል በ1920ዎቹ መጀመሪያ፡ ፖላንድ እና የሰራተኞች ኮሌጅ ከጦር ኃይሉ በኋላ፣ ደ ጎል ከኮሚኒስት ሩሲያ ጋር ባደረገው ጦርነት የፖላንድ እግረኛ ጦር አስተማሪ ሆኖ በፖላንድ ከሚገኘው የፈረንሣይ ወታደራዊ ተልዕኮ ሠራተኞች ጋር አገልግሏል። በፖላንድ ጦር የሜጀርነት ማዕረግ በዝብሩክዝ ወንዝ አቅራቢያ ባደረገው እንቅስቃሴ ራሱን ለይቷል እና የፖላንድ ከፍተኛ ወታደራዊ ማስዋቢያ የሆነውን ቪርቱቲ ሚሊታሪን አሸንፏል።፡ 71–74 ዴ ጎል በሁለተኛ ደረጃ የጦርነት ትምህርት ቤት፣ በ1922 እና 1924 መካከል ደ ጎል ወደ ፈረንሳይ ተመለሰ፣ እዚያም በሴንት ሲር የውትድርና ታሪክ መምህር ሆነ። የጦር እስረኛ ሆኖ ከተለማመደ በኋላ ቀድሞውንም ኃይለኛ ተናጋሪ ነበር። ከዚያም ከህዳር 1922 እስከ ኦክቶበር 1924 ድረስ በኤኮል ደ ጉሬ (የስታፍ ኮሌጅ) ተማረ። እዚህም ከአስተማሪው ኮሎኔል ሞይራንድ ጋር በመሠረተ ትምህርት ሳይሆን በሁኔታዎች ላይ በመሞገት እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ካደረገበት ልምምድ በኋላ ተጋጨ። አዛዡ ስለ አቅርቦቶች ጥያቄን ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆነም, "" ("መሪ እራሱን ስለ ትሪቪያ አይመለከትም") በማለት ሀላፊነቱን የሚወስደውን መኮንን ለሞይራንድ መልስ እንዲሰጥ ከማዘዙ በፊት. በብዙ ምዘናዎቹ 15 ወይም ከ20 ውስጥ ላቅ ያለ ውጤት አላመጣም። ሞይራንድ በመጨረሻው ዘገባው ላይ “ብልህ፣ ባህል ያለው እና ቁም ነገር ያለው መኮንን፣ ብልህ እና ተሰጥኦ ያለው ነው” ሲል ጽፏል፣ ነገር ግን ከኮርሱ ማግኘት የሚገባውን ያህል ጥቅም ባለማግኘቱ እና በትዕቢቱ፡ የሱ” ሲል ተችቶታል። ከመጠን በላይ በራስ መተማመን፣ የሌሎችን አስተያየት በጭካኔ ማሰናበት "እና በግዞት ያለ ንጉስ ያለውን አመለካከት" ከ129 33ኛ በመግባት በ52ኛ ደረጃ በአስሴዝ ባይን ("በቃ") ተመርቋል። እሱ ወደ ማይንትዝ ተለጠፈ ለፈረንሣይ ወረራ ጦር የምግብ እና የመሳሪያ አቅርቦቶችን ለመቆጣጠር እንዲረዳ።፡ 82 የዴ ጎል መፅሐፍ ላ ዲኮርዴ ቼዝ ሊኔሚ በመጋቢት 1924 ታየ። መጋቢት 1925 በሁኔታዎች መሰረት ዘዴዎችን ስለመጠቀም አንድ ድርሰት አሳተመ። በ1920ዎቹ አጋማሽ፡ የፔታይን መንፈስ ጸሐፊ የዴ ጎልን ስራ በፔታይን አድኖታል፣ እሱም የሰራተኞቻቸውን የኮሌጅ ውጤታቸውን በክፍል እንዲሻሻል አመቻችቷል ("ጥሩ" - ግን ለአጠቃላይ ሰራተኛ ለመለጠፍ የሚያስፈልግ "ምርጥ" አይደለም)።82–83 ከጁላይ 1 1925 ጀምሮ ለፔታይን (እንደ አካል) ሠርቷል፣ በተለይም እንደ “ብዕር መኮንን” ። ዴ ጎል በ 1925 ሞሮኮ ውስጥ ለማዘዝ ያደረገውን ውሳኔ አልተቀበለም (በኋላ ላይ "ማርሻል ፔታይን ታላቅ ሰው ነበር. በ 1925 ሞተ, ነገር ግን አላወቀም ነበር" በማለት ተናግሮ ነበር) እና እንደ ፍትወት ያያቸው ነገሮችን አልተቀበለም. ለፔታይን እና ለሚስቱ ለሕዝብ አድናቆት። እ.ኤ.አ. በ 1925 ዴ ጎል የመጀመሪያውን የፖለቲካ ደጋፊ የሆነውን ጆሴፍ ፖል-ቦንኮርን ማዳበር ጀመረ። በታህሳስ 1 ቀን 1925 “የፈረንሣይ ምሽጎች ታሪካዊ ሚና” ላይ አንድ ድርሰት አሳተመ። ይህ በጣም ተወዳጅ ርዕስ ነበር ምክንያቱም በወቅቱ በታቀደው ማጊኖት መስመር ምክንያት ፣ ግን ክርክሩ በጣም የተዛባ ነበር ፣ እሱ የምሽጎች ዓላማ ጠላትን ማዳከም እንጂ በመከላከል ላይ ኢኮኖሚ መፍጠር አይደለም ሲል ተከራክሯል። በደ ጎል እና በፔታይን መካከል በሌ ሶልዳት ላይ አለመግባባት ተፈጠረ፣ እሱ በመንፈስ የፃፈው የፈረንሣይ ወታደር ታሪክ እና ለዚህም ታላቅ የፅሁፍ ምስጋና ይፈልጋል። እሱ በዋነኝነት የጻፈው ታሪካዊ ቁሳቁሶችን ነበር፣ ግን ፔታይን የራሱን ሀሳብ የመጨረሻ ምዕራፍ ለመጨመር ፈልጎ ነበር። በ 1926 መገባደጃ ላይ ቢያንስ አንድ አውሎ ነፋሶች ስብሰባ ነበር ከዚያ በኋላ ዴ ጎል ከፔታይን ቢሮ በቁጣ ነጭ ሆኖ ብቅ ሲል ታየ። በጥቅምት 1926 ከራይን ጦር ሠራዊት ዋና መሥሪያ ቤት ጋር ወደ ሥራው ተመለሰ ። ደ ጎል እንደ አዛዥ ካልሆነ በቀር ወደ ኤኮል ደ ጉሬ እንደማይመለስ ምሎ ነበር፣ ነገር ግን በፔታይን ግብዣ እና በደጋፊው ወደ መድረክ አስተዋወቀ፣ በሚያዝያ 1927 እዚያ ሶስት ንግግሮችን አቀረበ፡ “በጦርነት ጊዜ መሪነት”፣ “ባህሪ” , እና "ክብር". እነዚህ በኋላም ለተሰኘው መጽሐፋቸው መሠረት ሆኑ። ብዙዎቹ ታዳሚዎቹ ከጥቂት አመታት በፊት ያስተማሩትና የመረመሩት አዛውንቶቹ ነበሩ። በ1920ዎቹ መጨረሻ፡ ትሪየር እና ቤሩት አሥራ ሁለት ዓመታትን በካፒቴንነት ካሳለፈ በኋላ፣ መደበኛ ጊዜ፣ ደ ጎል በሴፕቴምበር 25 ቀን 1927 አዛዥ (ሜጀር) ሆነ። በኅዳር 1927 የ 19 ኛው ቻሴርስ ኤ ፒድ (የሊቃውንት ሻለቃ ጦር) አዛዥ ሆኖ ለሁለት ዓመት መለጠፍ ጀመረ። ቀላል እግረኛ) በትሪየር (ትሬቭስ) ከወረራ ኃይሎች ጋር።፡ 94 ደ ጎል ሰዎቹን ጠንክሮ አሰልጥኖ ነበር (በሌሊት የቀዘቀዘውን የሞሴሌ ወንዝ የወንዝ መሻገሪያ ልምምድ በአዛዥ ጄኔራልነት ውድቅ ተደርጓል)። ወታደሩን ለምክትል (የፓርላማ አባል) ወደ ኩሺየር ክፍል እንዲዘዋወር ይግባኝ በማለቱ ወህኒ አስሮ እና ሲመረመር መጀመሪያ ላይ የሜይሶን ፔታይን አባልነቱን ለመጥራት ሞክሯል፣ በመጨረሻም ፒቴን ከሚደርስበት ተግሣጽ ራሱን እንዲጠብቅ ይግባኝ ብሏል። በወታደሩ የፖለቲካ መብቶች ውስጥ ጣልቃ መግባት. በዚህ ወቅት አንድ ታዛቢ ስለ ደ ጎል እንደፃፈው ወጣት መኮንኖችን ቢያበረታታም "የእሱ ኢጎ... ከሩቅ የከበረ"። እ.ኤ.አ. በ 1928-1929 ክረምት 30 ወታደሮች ("አናሜሴን ሳይቆጥሩ") "የጀርመን ጉንፋን" ተብሎ በሚጠራው በሽታ ሞቱ ፣ ከእነዚህም ውስጥ ሰባቱ ከደ ጎል ሻለቃ። ከምርመራ በኋላ በተካሄደው የፓርላማ ክርክር ልዩ ችሎታ ያለው አዛዥ በመሆን ለሙገሳ ተለይቷል እና ወላጅ አልባ ለሆነው የግል ወታደር የልቅሶ ባንድ እንዴት እንደለበሰ ሲጠቅስ ከጠቅላይ ሚኒስትር ሬይመንድ የአድናቆት መግለጫ አግኝቷል። በ1928 በሌ ሶልዳት የመንፈስ ጽሁፍ ላይ በዴ ጎል እና በፔታይን መካከል የተፈጠረው ጥሰት ተባብሶ ነበር። ፔቴን አዲስ የሙት መንፈስ ጸሐፊ ኮሎኔል ኦዴት አምጥቶ ስራውን ለመቀጠል ፈቃደኛ ያልሆነውን እና ለደ ጎል በአሳፋሪ ሁኔታ ስራውን እንዲረከብ ጻፈ። ፕሮጀክት. ፔቲን ስለ ጉዳዩ በጣም ተግባቢ ነበር ነገር ግን መጽሐፉን አላሳተመም። እ.ኤ.አ. በ 1929 ፒታይን በአካዳሚ ፍራንሴይስ ውስጥ መቀመጫውን ለሚያስበው ለሟቹ ፈርዲናንድ ፎች ላደረገው አድናቆት የዴ ጎልን ረቂቅ ጽሑፍ አልተጠቀመም። የራይንላንድ የተባበሩት መንግስታት ወረራ እያበቃ ነበር፣ እና የዴ ጎል ሻለቃ ሊበተን ነበር፣ ምንም እንኳን ውሳኔው በኋላ ወደ ቀጣዩ መለጠፍ ከሄደ በኋላ ተሰርዟል። ዴ ጎል በ 1929 ኤኮል ደ ጉሬር የማስተማር ቦታ ፈለገ። ፋካሊቲው በጅምላ የመልቀቂያ ስጋት ነበረው በዚያ ቦታ እንዲሾም ተደረገ። ወደ ኮርሲካ ወይም ሰሜን አፍሪካ ስለመለጠፍ ወሬ ነበር ነገር ግን በፔታይን ምክር ወደ ሊባኖስ እና ሶሪያ የሁለት አመት መለጠፍን ተቀበለ።፡ 93–94 በቤሩት የጄኔራል ሉዊስ ፖል 3ኛ ቢሮ (ወታደራዊ ኦፕሬሽን) ሃላፊ ነበር። - ፣ እሱም የሚያበራ ማጣቀሻ የጻፈው ለወደፊቱ ከፍተኛ ትእዛዝ እንዲሰጠው ይመክራል። 1930 ዎቹ: ሰራተኛ መኮንን እ.ኤ.አ. በ1931 የጸደይ ወቅት፣ በቤሩት የለጠፈው ልጥፍ ሊጠናቀቅ ሲቃረብ፣ ዴ ጎል ፒቲንን ለ እንዲልክ በድጋሚ ጠየቀ። ፔታይን እዚያ የታሪክ ፕሮፌሰር ሆኖ ቀጠሮ ለመያዝ ሞክሮ ነበር፣ ግን በድጋሚ ፋኩልቲው ሊፈልገው አልቻለም። ይልቁንስ ዴ ጎል እ.ኤ.አ. በ 1928 ለተቋሙ ማሻሻያ ያቀዳቸውን ዕቅዶች በመንደፍ ፔቲን “የጦርነት ሥነ ምግባር” ላይ ለሁለቱም ለኤኮል ደ ጉሬሬ እና ለ ሴንተር - የጄኔራሎች ከፍተኛ ሰራተኛ ኮሌጅ፣ "ትምህርት ቤት ለማርሻልስ" በመባል ይታወቃል)፣ እና እንዲሁም በ ላሉ ሲቪሎች እና ለሲቪል አገልጋዮች። ይልቁንስ ለጠቅላይ ጦር ካውንስል አጠቃላይ ጽሕፈት ቤት ( - የጠቅላይ ምኒስትሩ ዋና ፀሐፊ ሪፖርት) ለመለጠፍ እንዲያመለክት መከረው ፣ ምንም እንኳን በኋላ በ 1936 ወደ ጦርነት ሚኒስቴር ተዛወረ። ) በፓሪስ. ፔቲን ለቀጠሮው ጥሩ ልምድ እንደሚኖረው በማሰብ ሎቢ ለማድረግ ቃል ገባ። በህዳር 1931 ወደ ተለጠፈ፣ በመጀመሪያ እንደ “ረቂቅ መኮንን”።፡ 94 በዲሴምበር 1932 ወደ ሌተና ኮሎኔል ከፍ ከፍ እና የሶስተኛው ክፍል (ኦፕሬሽንስ) ኃላፊ ተሾመ። በ ያከናወነው አገልግሎት በ1940 የሚኒስትርነት ኃላፊነቱን እንዲወስድ በሠራዊቱ ዕቅድ እና መንግሥት መካከል ያለውን ግንኙነት የስድስት ዓመታት ልምድ ሰጠው።: 97 ዴ ጎል በዩኤስ፣ ጣሊያን እና ቤልጂየም ውስጥ ዝግጅቶችን ካጠና በኋላ በጦርነት ጊዜ አገሪቱን ለማቋቋም የሚያስችል ረቂቅ አዘጋጀ። ስለ ሂሳቡ ለ ገለጻ አድርጓል። ረቂቅ ህጉ የተወካዮች ምክር ቤቱን አልፏል ነገር ግን በሴኔት ውስጥ አልተሳካም በ1930ዎቹ መጀመሪያ፡ የታጠቀ ጦርነት ሀሳብ ከፔታይን በተቃራኒ ዴ ጎል ከትሬንች ጦርነት ይልቅ ታንኮችን እና ፈጣን መንቀሳቀስን ያምን ነበር። 108 ደ ጎል የኤሚሌ ማየር ደቀ መዝሙር ሆነ፣ ጡረታ የወጣ ሌተና ኮሎኔል (ስራው በድሬፉስ ጉዳይ ተጎድቷል) እና ወታደራዊ አሳቢ። ሜየር ምንም እንኳን ጦርነቶች አሁንም መከሰታቸው የማይቀር ቢሆንም፣ በሠለጠኑት አገሮች እንደቀደሙት መቶ ዓመታት እርስ በርስ መፈራረቅ ወይም ጦርነት መክፈት “ጊዜ ያለፈበት” እንደሆነ አሰበ። እሱ ስለ ፈረንሣይ ጄኔራሎች ጥራት ዝቅተኛ አመለካከት ነበረው ፣ እና የማጊኖት መስመርን ተቺ እና የሜካናይዝድ ጦርነት ደጋፊ ነበር። ሜየር በጠንካራው መሪ ሚስጥራዊ ላይ ካለው አባዜ ርቆ ለሪፐብሊካን ተቋማት ታማኝነት እና ወታደራዊ ማሻሻያ እንዲሆን የዴ ጎልን ሃሳቦች እንዳተኮረ ይጠቁማል። እ.ኤ.አ. በ 1934 ዴ ጎል ወደ ፕሮፌሽናል ጦር ሰራዊት ፃፈ። 100,000 ሰዎች እና 3,000 ታንኮች ባለው ከፍተኛ ኃይል ላይ ውጥረት በመፍጠር የእግረኛ ጦር ሜካናይዜሽን ሐሳብ አቀረበ። መፅሃፉ ታንኮች እንደ ፈረሰኞች በሀገሪቱ ሲሽከረከሩ አስቧል። የዴ ጎል አማካሪ ኤሚሌ ማየር ስለ አየር ኃይል በጦር ሜዳ ላይ ስላለው የወደፊት ጠቀሜታ ከመግለጽ ይልቅ በተወሰነ ደረጃ ትንቢታዊ ነበር። ይህ አይነቱ ጦር ሁለቱንም የፈረንሳይን የህዝብ እጥረት ማካካሻ እና አለም አቀፍ ህግን ለማስከበር ውጤታማ መሳሪያ ይሆናል በተለይም የቬርሳይ ስምምነት ጀርመንን እንዳታስታጥቅ ይከለክላል። እሱ ደግሞ ጥልቅ ሀገራዊ መልሶ ማደራጀት ቅድመ ሁኔታ እንደሚሆን አስቦ "አንድ ጌታ መልክውን ማሳየት አለበት ትዕዛዙን መቃወም የማይቻል - በሕዝብ አስተያየት የተከበረ ሰው" ሲል ጽፏል. በፈረንሳይ 700 ቅጂዎች ብቻ ተሸጡ; በጀርመን በሺዎች የሚቆጠሩ ቅጂዎች ተሸጡ የሚለው አባባል የተጋነነ ነው ተብሎ ይታሰባል። ደ ጎል መጽሐፉን በጋዜጠኞች መካከል ያለውን ግንኙነት ለማስፋት ተጠቅሞበታል፣ በተለይም ከ አዘጋጅ አንድሬ ፒሮንኔ ጋር። መጽሐፉ ለሪፐብሊካን የዜጎች ሰራዊት ሃሳብ ከቆሙት ግራ ከተጋባው በስተቀር በፖለቲካው ዘርፍ ምስጋናን ስቧል። የዴ ጎል አስተያየቶች የአስደናቂውን ፖለቲከኛ ፖል ሬይናድ ቀልብ ስቦ ነበር ፣እሱም ደጋግሞ ይፅፍለት ነበር ፣አንዳንድ ጊዜም በድብቅ ቃላት። ሬይናውድ በመጀመሪያ ዲሴምበር 5, 1934 እንዲገናኘው ጋበዘው። የዴ ጎል ቤተሰብ በጣም ግላዊ ነበሩ። ዴ ጎል በዚህ ጊዜ በሙያው ላይ በጥልቅ ያተኮረ ነበር። በፋሺዝም እንደተፈተነ የሚያሳይ ምንም መረጃ የለም፣ በ1934 እና 1936 ውስጥ በተከሰቱት የሀገር ውስጥ ውጣ ውረዶች ወይም በአስር አመታት ውስጥ በተከሰቱት በርካታ የውጭ ፖሊሲ ቀውሶች ላይ የእሱ አመለካከት ጥቂት ማስረጃዎች አሉ። በ1936 የታዋቂው ግንባር መንግስት የጀመረውን የትጥቅ ጉዞ አጽድቋል፣ ምንም እንኳን የፈረንሳይ ወታደራዊ አስተምህሮ ታንኮች በፔኒ ፓኬቶች ለእግረኛ ድጋፍ መዋል እንዳለባቸው ቢቆይም (የሚገርመው በ1940 የጀርመን ፓንዘር ክፍሎች በተመሳሳይ መንገድ ጥቅም ላይ ይውላሉ) ዴ ጎል የተናገረው ነገር)። በዴ ጎል የፖለቲካ አመለካከት ላይ ያልተለመደ ግንዛቤ እናቱ ከጀርመን ጋር ጦርነት ፈጥኖም ይሁን ዘግይቶ የማይቀር መሆኑን በማስጠንቀቅ እና በ1935 ፒየር ላቫል ከዩኤስኤስአር ጋር የገባው ቃል ኪዳን ለበጎ እንደሆነ የሚያረጋግጥላት እናቱ ፍራንሲስ 1 ከጀርመን ህብረት ጋር ካለው ጥምረት ጋር በማመሳሰል ያረጋግጥላታል። ቱርኮች ​​በንጉሠ ነገሥቱ ቻርልስ የፈረንሣይ ፕሬዚዳንት
49628
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%89%86%E1%88%B5%20%E1%8B%88%E1%8A%95%E1%8C%8C%E1%88%8D
የማርቆስ ወንጌል
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ቅዱስ ማርቆስ እንደ ጻፈው። ቅዱስ ማርቆስ ወንግልን ለመስበክ ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ወደ ሮም ተጉዞ ቀዳሚ የወንጌል ፀሐፊ ሆነ ። (፩ኛ ጴጥ ም፡፭ ቁ፡፲፪- ፲፫) ከጌታ የሰማውንና የተማረውን ጽፎአል። ወንጌልንም የጻፈበት ዘመን ጌታ ከዐረገ አሥራ አንደኛው ተፈፅሞ አሥራ ሁለተኛው ሲጀምር፣ ቀላውዴዎስ ቄሣር በነገሠ በአራተኛው ዓመት ሲሆን ወንጌል ተብሎ ይፋ የወጣበት ቋንቋ ሮማይስጥ ነው ማለት ቅዱስ ጴጥሮስ በሮማይስጥ አስተርጉሞ የሮማ ሰዎችን ለማስተማር ተጠቅሞበታል ። ወንጌሉም ቅዱስ ማርቆስ ካለፈ በኋላ በስሙ ተጠርቷል። ቀጥሎም በመንፈስ ቅዱስ''' መሪነት በግብፅ አገር ተልኮውን ማኪያሄድ እንዳለበት ተረድቶ እዚሁ አገር ላይ የአንበሳ ጣዖቶችን በማጥፋት የነገደ ይሁዳ የሆነውን አንበሳ ክርስቶስን በመስበክ ከዚያም የመጀመሪያው ጳጳስ ሆኖ በመናፍቃን ተገድሎ በሰማዕትነት ያለፈ ቅዱስ ነው። ይህ ክርስቲያናዊ ተጋድሎ ነው የአንበሳ ምልክት እንዲሰጠው ዋና ምክኒያት የሆነው። በተጨማሪ በራዕዪ ዮሐንስ ጌታች መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ አሸናፊ የይሁዳ አንበሳ ተብሎ ተሰይሟል ፣ በነብዩ በሆሴዕ አንበሳ ተብሎ መጠራቱን እናያለን ። የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ ፩ አርባ፡ቀን፡ሰነበተ፡ከአራዊትም፡ጋራ፡ነበረ፥ መላእክቱም፡አገለገሉት። ምዕራፍ ፪ ስለ፡ምን፡ታስባላችኹ፧ 9፤ሽባውን፦ኀጢአትኽ፡ተሰረየችልኽ፡ከማለት፡ወይስ 1 ተነሣ፡ዐልጋኽንም፡ተሸከምና፡ኺድ፡ከማለት፡ ምዕራፍ ፫ ምዕራፍ ፬ 38፤ርሱም፡በስተዃላዋ፡ትራስ፡ተንተርሶ፡ተኝቶነበር፤አንቅተውም፣ መምህርሆይ፥ስንጠፋ አይገድኽምን፡አሉት። 41፤ እጅግም ፈሩና፡እንግዲህ፡ነፋስም፡ባሕርም፡የሚታዘዙለት፡ይህ፡ማን፡ነው፧ተባባሉ። ምዕራፍ ፭ ምዕራፍ ፮ ነበር፤የልብሱንም፡ጫፍ፡እንኳ፡ሊዳስሱ፡ይለምኑት፡ነበር፡የዳሰሱትም፡ዅሉ፡ዳኑ። (ጣልያታ፡ወይም፡ጣሊታ፡ማለት=ሴት፡ልጅ፥ቈንዦ፥ገና፡አካለ፡መጠን፡ያልሞላች)። ምዕራፍ ፯ ምዕራፍ ፰ ምዕራፍ ፱ ምዕራፍ ፲ ምዕራፍ ፲፩ ምዕራፍ ፲፪ 1፤በምሳሌም ይነግራቸው ጀመር። አንድ ሰው የወይን አትክልት ተከለ፥ ቅጥርም ቀጠረለት፥ መጥመቂያም ማሰለት፥ ግንብም ሠራና ለገበሬዎች አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ። 2፤በጊዜውም ከወይን አትክልት ፍሬ ከገበሬዎቹ እንዲቀበል አንድ ባሪያ ወደ ገበሬዎቹ ላከ፤ 3፤ይዘውም ደበደቡት ባዶውንም ሰደዱት። 4፤ዳግመኛም ሌላውን ባሪያ ወደ እነርሱ ላከ እርሱንም ወግረው ራሱን አቈሰሉት አዋርደውም ሰደዱት። 5፤ሌላውንም ላከ፤ እርሱንም ገደሉት፥ ከሌሎችም ከብዙዎች አንዳንዱን ደበደቡ አንዳንዱንም ገደሉ። 6፤የሚወደው አንድ ልጅ ገና ነበረው፤ ልጄንስ ያፍሩታል ብሎ እርሱን ከሁሉ በኋላ ወደ እነርሱ ላከ። 7፤እነዚያ ገበሬዎች ግን እርስ በርሳቸው፦ ወራሹ ይህ ነው፤ ኑ፥ እንግደለው፥ ርስቱም ለኛ ይሆናል ተባባሉ። 8፤ይዘውም ገደሉት፥ ከወይኑም አትክልት ወደ ውጭ ጣሉት። 9፤እንግዲህ የወይኑ አትክልት ጌታ ምን ያደርጋል? ይመጣል ገበሬዎቹንም ያጠፋል፥ የወይኑንም አትክልት ለሌሎች ይሰጣል። 10-11፤ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው። የሚለውን ይህን መጽሐፍ አላነበባችሁምን? 12፤ምሳሌውንም ስለ እነርሱ እንደ ተናገረ አውቀዋልና ሊይዙት ፈለጉ፥ ነገር ግን ሕዝቡን ፈሩ። ትተውትም ሄዱ። 13፤በንግግርም ሊያጠምዱት ከፈሪሳውያንና ከሄሮድስ ወገን የሆኑትን ወደ እርሱ ላኩ። 14፤መጥተውም፦ መምህር ሆይ፥ የሰውን ፊት ሳትመለከት በእውነት የእግዚአብሔር መንገድ ታስተምራለህና እውነተኛ እንደ ሆንህ ለማንምም እንዳታደላ እናውቃለን፤ ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? እንስጥን ወይስ አንስጥ? አሉት። 15፤እርሱ ግን ግብዝነታቸውን አውቆ፦ ለምን ትፈትኑኛላችሁ? አየው ዘንድ አንድ ዲናር አምጡልኝ አላቸው። 16፤እነርሱም አመጡለት። ይህች መልክ ጽሕፈቲቱስ የማን ናት? አላቸው፤ እነርሱም፦ የቄሣር ናት አሉት። 17፤ኢየሱስም መልሶ፦ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ አላቸው። በእርሱም ተደነቁ። 18፤ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ መጥተው ጠየቁት እንዲህም አሉት፦ 19፤መምህር ሆይ፥ ሙሴ፦ የአንድ ሰው ወንድም ሚስቱን ትቶ ልጅ ሳያስቀር ቢሞት፥ ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካ ብሎ ጻፈልን። 20፤ሰባት ወንድማማቾች ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ዘር ሳያስቀር ሞተ፤ 21፤ሁለተኛውም አገባት፥ ዘርም ሳይተው ሞተ፤ ሦስተኛውም እንዲሁ፤ 22ሰባቱም አገቡአት፥ ዘርም አላስቀሩም። ከሁሉም በኋላ ሴቲቱ ደግሞ ሞተች። 23፤ሰባቱ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀን ሲነሡ ከእነርሱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች? 24፤ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ስለዚህ የምትስቱ አይደለምን? 25፤ከሙታንስ ሲነሡ በሰማያት እንዳሉ መላእክት ይሆናሉ እንጂ አያገቡም፥ አይጋቡምም። 26፤ስለ ሙታን ግን እንዲነሡ እግዚአብሔር፦ እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ እንዳለው በሙሴ መጽሐፍ በቍጥቋጦው ዘንድ የተጻፈውን አላነበባችሁምን? 27፤የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም። እንግዲህ እጅግ ትስታላችሁ። 28፤ከጻፎችም አንዱ ቀርቦ ሲከራከሩ ሰማና መልካም አድርጎ እንደ መለሰላቸው አስተውሎ፦ ከሁሉ ፊተኛይቱ ትእዛዝ ማናቸይቱ ናት? ብሎ ጠየቀው። 29፤ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፥ 30፤አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። 31፤ሁለተኛይቱም፦ ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትል እርስዋን የምትመስል ይህች ናት። ከእነዚህ የምትበልጥ ሌላ ትእዛዝ የለችም። 32፤ጻፊውም፦ መልካም ነው፥ መምህር ሆይ፤ አንድ ነው ከእርሱም በቀር ሌላ የለም ብለህ በእውነት ተናገርህ፤ 33፤በፍጹም ልብ በፍጹም አእምሮም በፍጹም ነፍስም በፍጹም ኃይልም እርሱን መውደድ፥ ባልንጀራንም እንደ ራስ መውደድ በሙሉ ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከሌላው መሥዋዕት ሁሉ የሚበልጥ ነው አለው። 34፤ኢየሱስም በአእምሮ እንደ መለሰ አይቶ፦ አንተ ከእግዚአብሔር መንግሥት የራቅህ አይደለህም አለው። ከዚህም በኋላ ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም። 35፤ኢየሱስም በመቅደስ ሲያስተምር መልሶ እንዲህ አለ፦ ጻፎች ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ነው እንዴት ይላሉ? 36፤ዳዊት ራሱ በመንፈስ ቅዱስ፦ ጌታ ጌታዬን፦ ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው አለ። 37፤ዳዊትም ራሱ ጌታ አለው፤ እንዴትስ ልጁ ይሆናል? ብዙ ሕዝብም በደስታ ይሰሙት ነበር። 38-39፤ሲያስተምርም እንዲህ አለ፦ ረጃጅም ልብስ ለብሰው መዞርን፥ በገበያም ሰላምታን፥ በምኵራብም የከበሬታን ወንበር፥ በግብርም የከበሬታን ስፍራ ከሚወዱ ከጻፎች ተጠበቁ፤ 40፤የመበለቶችን ቤት የሚበሉ ጸሎታቸውንም በማስረዘም የሚያመካኙ እነዚህ የባሰ ፍርድ ይቀበላሉ። 41፤ኢየሱስም በመዝገብ አንጻር ተቀምጦ ሕዝቡ በመዝገብ ውስጥ ገንዘብ እንዴት እንዲጥሉ ያይ ነበር፤ ብዙ ባለ ጠጎችም ብዙ ይጥሉ ነበር፤ 42፤አንዲትም ድሀ መበለት መጥታ አንድ ሳንቲም የሚያህሉ ሁለት ናስ ጣለች። 43፤ደቀ መዛሙርቱንም ጠርቶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ በመዝገብ ውስጥ ከሚጥሉት ሁሉ ይልቅ ይህች ድሀ መበለት አብልጣ ጣለች፤ 44፤ሁሉ ከትርፋቸው ጥለዋልና፥ ይህች ግን ከጕድለትዋ የነበራትን ሁሉ ትዳርዋን ሁሉ ጣለች አላቸው። ምዕራፍ ፲፫ እርሱም ከመቅደስ ሲወጣ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፦ መምህር ሆይ፥ እንዴት ያሉ ድንጋይዎችና እንዴት ያሉ ሕንጻዎች እንደ ሆኑ እይ አለው። ኢየሱስም መልሶ፦ እነዚህን ታላላቅ ሕንጻዎች ታያለህን? ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አለው።3 በመቅደስም ትይዩ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ጴጥሮስና ያዕቆብ ዮሐንስም እንድርያስም፦ ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ሁሉ ይፈጸም ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ለብቻቸው ጠየቁት። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ ይላቸው ጀመር፦ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ። ብዙዎች፦ እኔ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፥ ብዙዎችንም ያስታሉ። ጦርንም የጦርንም ወሬ በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና፥ ነገር ግን መጨረሻው ገና ነው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፤ በልዩ ልዩ ስፍራ የምድር መናወጥ ይሆናል፤ ራብ ይሆናል፤ እነዚህ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው። እናንተ ግን ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል በምኵራብም ትገረፋላችሁ ምስክርም ይሆንባቸው ዘንድ ስለ እኔ በገዥዎችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ። አስቀድሞም ወንጌል ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበክ ዘንድ ይገባል። ሲጐትቱአችሁና አሳልፈው ሲሰጡአችሁም ምን እንድትናገሩ አስቀድማችሁ አትጨነቁ፥ ዳሩ ግን በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ፤ የሚነግረው መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁምና። ወንድምም ወንድሙን አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ። ይገድሉአቸውማል፤ በሁሉም ዘንድ ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። ነገር ግን በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፥ በሰገነትም ያለ ወደ ቤት አይውረድ ከቤቱም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይግባ፥ በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ። በዚያን ወራትም ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው። ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤ በዚያን ወራት እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያልሆነ ደግሞም የማይሆን የመከራ ዓይነት ይሆናልና። ጌታስ ወራቶቹን ባያሳጥር፥ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም፤ ነገር ግን ስለ መረጣቸው ምርጦች ወራቶቹን አሳጠረ። በዚያን ጊዜም ማንም፦ እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፥ ወይም፦ እነሆ፥ ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ፤ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ ያስቱ ዘንድ ምልክትና ድንቅ ያደርጋሉ። እናንተ ግን ተጠንቀቁ፤ እነሆ፥ አስቀድሜ ሁሉን ነገርኋችሁ። በዚያን ወራት ግን ከዚያ መከራ በኋላ ፀሐይ ይጨልማል ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፥ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፥ የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በብዙ ኃይልና ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል። በዚያን ጊዜም መላእክትን ይልካል ከአራቱ ነፋሳትም ከምድር ዳርቻ እስከ ሰማይ ዳርቻ የተመረጡትን ይሰበስባቸዋል። ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤ እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህን ሁሉ መሆኑን ስታዩ ቀርቦ በደጅ እንደ ሆነ እወቁ። እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም። ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም። ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም። ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም። ቤቱን ትቶ ወደ ሌላ አገር እንደ ሄደ ሰው ነው፥ ለባሮቹም ሥልጣን ለእያንዳንዱም ሥራውን ሰጥቶ በረኛውን እንዲተጋ አዘዘ። እንግዲህ በማታ ቢሆን ወይም በእኩለ ሌሊት ወይም ዶሮ ሲጮኽ ወይም በማለዳ ቢሆን ባለቤቱ መቼ እንዲመጣ አታውቁምና ድንገት መጥቶ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ ስለዚህ ትጉ። ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ። ምዕራፍ ፲፬ ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካና የቂጣ በዓል ነበረ። የካህናት አለቆችም ጻፎችም እንዴት አድርገው በተንኰል እንደሚይዙትና እንደሚገድሉት ይፈልጉ ነበር። የሕዝብ ሁከት እንዳይሆን በበዓል አይሁን ይሉ ነበርና። እርሱም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት በነበረ ጊዜ፥ በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የከበረ ጥሩ ናርዶስ ሽቱ የመላበት የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ ይዛ መጣች፤ ቢልቃጡንም ሰብራ በራሱ ላይ አፈሰሰችው። አንዳንዶችም፦ ይህ የሽቱ ጥፋት ለምንድር ነው? ይህ ሽቱ ከሦስት መቶ ዲናር በሚበልጥ ዋጋ ተሽጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበርና ብለው በራሳቸው ይቈጡ ነበር፤ እርስዋንም ነቀፉአት። ኢየሱስ ግን እንዲህ አለ፦ ተዉአት፤ ስለ ምን ታደክሙአታላችሁ? መልካም ሥራ ሠርታልኛለች። ድሆች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ በማናቸውም በወደዳችሁት ጊዜ መልካም ልታደርጉላቸው ትችላላችሁ፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም። የተቻላትን አደረገች፤ አስቀድማ ለመቃብሬ ሥጋዬን ቀባችው። እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለሙ ሁሉ በሚሰበክበት በማናቸውም ስፍራ፥ እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ ሊሆን ይነገራል። ከአሥራ ሁለቱም አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ ሊሰጠው ወደ ካህናት አለቆች ሄደ። ሲሰሙም ደስ አላቸው ብርም ይሰጡት ዘንድ ተስፋ ሰጡት። በሚመች ጊዜም እንዴት አድርጎ አሳልፎ እንዲሰጠው ይፈልግ ነበር። ፋሲካን በሚያርዱበት በቂጣ በዓል መጀመሪያ ቀን ደቀ መዛሙርቱ፦ ፋሲካን ትበላ ዘንድ ወዴት ሄደን ልናሰናዳ ትወዳለህ? አሉት። ከደቀ መዛሙርቱም ሁለት ላከ እንዲህም አላቸው፦ ወደ ከተማ ሂዱ፥ ማድጋ ውኃ የተሸከመ ሰውም ይገናኛችኋል፤ ተከተሉት፥ የሚገባበትንም የቤቱን ጌታ፦ መምህሩ፦ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን የምበላበት የእንግዳ ቤት ወዴት ነው? ይላል በሉት። እርሱም በደርብ ላይ ያለውን የተሰናዳና የተነጠፈ ታላቅ አዳራሽ ያሳያችኋል፤ በዚያም አሰናዱልን። ደቀ መዛሙርቱም ወጡ ወደ ከተማም ሄደው እንዳላቸው አገኙ፥ ፋሲካንም አሰናዱ። በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ጋር መጣ። ተቀምጠውም ሲበሉ ኢየሱስ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ፥ እርሱም ከእኔ ጋር የሚበላው አሳልፎ ይሰጠኛል አለ። እነርሱም ያዝኑ፥ እያንዳንዳቸውም፦ እኔ እሆንን? ይሉት ጀመር። እርሱም መልሶ፦ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ከእኔ ጋር ወደ ወጭቱ እጁን የሚያጠልቀው ነው። የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይሄዳል፤ ነገር ግን የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት፤ ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር አላቸው። ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ሰጣቸውና፦ እንካችሁ፤ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው፥ ሁሉም ከእርሱ ጠጡ። እርሱም፦ ይህ ስለ ብዙዎች የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ነው። እውነት እላችኋለሁ፥ በእግዚአብሔር መንግሥት ከወይኑ ፍሬ አዲሱን እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ደግሞ አልጠጣውም አላቸው። መዝሙርም ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ። ኢየሱስም፦ በዚች ሌሊት ሁላችሁ በእኔ ትሰናከላላችሁ፤ እረኛዉን እመታለሁ በጎችም ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና። ነገር ግን ከተነሣሁ በኋላ ወደ ገሊላ እቀድማችኋለሁ አላቸው። ጴጥሮስም፦ ሁሉም ቢሰናከሉ እኔ ግን ከቶ አልሰናከልም አለው። ኢየሱስም፦ እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ በዚች ሌሊት ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮኽሦስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው። እርሱም ቃሉን አበርትቶ፦ ከአንተ ጋር የምሞት እንኳ ቢሆን ከቶ አልክድህም አለ። ሁሉም ደግሞ እንደዚሁ አሉ። ጌቴሴማኒ ወደምትባልም ስፍራ መጡ፥ ደቀ መዛሙርቱንም፦ ስጸልይ ሳለሁ፥ በዚህ ተቀመጡ አላቸው። ጴጥሮስንና ያዕቆብን ዮሐንስንም ከእርሱ ጋር ወሰደ፤ ሊደነግጥም ሊተክዝም ጀመረና። ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቈዩ ትጉም አላቸው። ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በምድርም ወድቆ፥ ይቻልስ ቢሆን ሰዓቲቱ ከእርሱ እንድታልፍ ጸለየና፦ አባ አባት ሆይ፥ ሁሉ ይቻልሃል፤ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን አንተ የምትወደው እንጂ እኔ የምወደው አይሁን አለ። መጣም ተኝተውም አገኛቸው፥ ጴጥሮስንም፦ ስምዖን ሆይ፥ ተኝተሃልን? አንዲት ሰዓት ስንኳ ልትተጋ አልቻልህምን? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉ ጸልዩም፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች፥ ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው። ደግሞም ሄዶ ያንኑ ቃል ጸለየ። ደግሞም መጥቶ ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው፥ የሚመልሱለትንም አላወቁም። ሦስተኛም መጥቶ፦ እንግዲህስ ተኙ ዕረፉም፤ ይበቃል፤ ሰዓቲቱ ደረሰች፤ እነሆ፥ የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ይሰጣል። ተነሡ፥ እንሂድ፤ እነሆ፥ አሳልፎ የሚሰጠኝ ቀርቦአል አላቸው። ወዲያውም ገና ሲናገር ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ መጣ፥ ከእርሱም ጋር ብዙ ሰዎች ሰይፍና ጐመድ ይዘው ከካህናት አለቆችና ከጻፎች ከሽማግሌዎችም ዘንድ መጡ። በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ይሰጣል። አሳልፎ የሚሰጠውም፦ የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት ተጠንቅቃችሁም ውሰዱት ብሎ ምልክት ሰጥቶአቸው ነበር። መጥቶም ወዲያው ወደ እርሱ ቀረበና፦ መምህር ሆይ፥ መምህር ሆይ፥ ብሎ ሳመው፤ እነርሱም እጃቸውን በእርሱ ላይ ጭነው ያዙት። በአጠገብ ከቆሙት ግን አንዱ ሰይፉን መዞ የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መታ ጆሮውንም ቈረጠ። ኢየሱስም መልሶ፦ ወንበዴ እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ልትይዙኝ መጣችሁን? በመቅደስ ዕለት ዕለት እያስተማርሁ ከእናንተ ጋር ስኖር አልያዛችሁኝም፤ ነገር ግን መጻሕፍት ይፈጸሙ ዘንድ ይህ ሆነ አላቸው። ሁሉም ትተውት ሸሹ። ዕርቃኑን በነጠላ የሸፈነ አንድ ጎበዝ ይከተለው ነበር፥ ጎበዛዝቱም ያዙት፤ እርሱ ግን ነጠላውን ትቶ ዕራቁቱን ሸሸ። ኢየሱስንም ወደ ሊቀ ካህናቱ ወሰዱት፥ የካህናት አለቆችም ሁሉ ሽማግሌዎችም ጻፎችም ተሰበሰቡ። ጴጥሮስም እስከ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ውስጥ በሩቁ ተከተለው፥ ከሎሌዎችም ጋር ተቀምጦ እሳት ይሞቅ ነበር። የካህናት አለቆችም ሸንጎውም ሁሉ እንዲገድሉት በኢየሱስ ላይ ምስክር ይፈልጉ ነበር፥ አላገኙምም፤ ብዙዎች በሐሰት ይመሰክሩበት ነበርና፥ ምስክርነታቸው ግን አልተሰማማም። ሰዎችም ተነሥተው፦ እኔ ይህን በእጅ የተሠራውን ቤተ መቅደስ አፈርሰዋለሁ በሦስት ቀንም ሌላውን በእጅ ያልተሠራውን እሠራለሁ ሲል ሰማነው ብለው በሐሰት መሰከሩበት። ምስክርነታቸውም እንዲሁ እንኳ አልተሰማማም። ሊቀ ካህናቱም በመካከላቸው ተነሥቶ፦ አንዳች አትመልስምን? እነዚህስ በአንተ ላይ የሚመሰክሩብህ ምንድር ነው? ብሎ ኢየሱስን ጠየቀው። እርሱ ግን ዝም አለ አንዳችም አልመለሰም። ደግሞ ሊቀ ካህናቱ ጠየቀውና፦ የቡሩክ ልጅ ክርስቶስ አንተ ነህን? አለው። ኢየሱስም፦ እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይም ደመና ሲመጣ ታያላችሁ አለ። ሊቀ ካህናቱም ልብሱን ቀደደና፦ ከእንግዲህ ወዲህ ምስክሮችን ምን ያስፈልገናል? ስድቡን ሰማችሁ፤ ምን ይመስላችኋል? አለ። እነርሱም ሁሉ፦ ሞት ይገባዋል ብለው ፈረዱበት። አንዳንዶችም ይተፉበት ፊቱንም ሸፍነው ይጐስሙትና፦ ትንቢት ተናገር ይሉት ጀመር፤ ሎሌዎችም በጥፊ እየመቱ ወሰዱት። ጴጥሮስም በግቢ ውስጥ ወደ ታች ሳለ ከሊቀ ካህናቱ ገረዶች አንዲቱ መጣች፥ ጴጥሮስም እሳት ሲሞቅ አይታ ተመለከተችውና፦ አንተ ደግሞ ከናዝሬቱ ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው። እርሱ ግን፦ የምትዪውን አላውቅም አላስተውልምም ብሎ ካደ። ወደ ውጭም ወደ ደጅ ወጣ፤ ዶሮም ጮኸ። ገረዲቱም አይታው በዚያ ለቆሙት፦ ይህም ከእነርሱ ወገን ነው ስትል ሁለተኛ ትነግራቸው ጀመር። እርሱም ደግሞ ካደ። ጥቂት ቈይተውም በዚያ የቆሙት ዳግመኛ ጴጥሮስን፦ የገሊላ ሰው ነህና ከእነርሱ ወገን በእውነት ነህ አሉት። እርሱ ግን፦ ይህን የምትሉትን ሰው አላውቀውም ብሎ ይረገምና ይምል ጀመር። ወዲያውም ዶሮ ሁለተኛ ጮኸ። ጴጥሮስንም ኢየሱስ፦ ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው ቃል ትዝ አለው፤ ነገሩንም አስቦ አለቀሰ። ምዕራፍ ፲፭ ምዕራፍ ፲፮ መጽሐፍ ቅዱስ
51692
https://am.wikipedia.org/wiki/Tadbaba%20Maryam
Tadbaba Maryam
ተድባበ ማርያም (በቀዳሚ ስሟ ተድባበ ጽዮን). በደቡብ ወሎ በቀድሞው ቦረናና ሳይንት አውራጃ የምትገኘኝ በኢትዮጵያ ከሁሉም ቀድማ የተመሰረተች ታሪካዊ አድባር ናት፡፡ ተድባበ ማርያም በኦሪት ዘመን በቤተመቅደስ (ምኩራብ) አምልኮተ እግዚአብሔርና ፣መስዋዕተ ኦሪት ከተሰዋባቸው ቀደምት አድባራት መካከል አንዷና ዋናዋ ናት።}}). የምስረታ ታሪክ ተድባበ ማርያም በ982 ዓመተ ዓለም (ከእየሱስ ልደት በፊት) የተመሰረተች ሲሆን መስራቹ ደግሞ የቤተልሔም ተወላጅና የአሚናዳብ ዘር የሆነው ሳቤቅ ነው። ሳቤቅ የቅዱስ ዳዊት የወንድም ልጅ ሲሆን፤ በአዛሪያስ መሪነት ከእስራኤል ወደ ኢትዮጵያ ታቦተ ጽዮንን ተከትለው ከመጡት 12,000 (አስራ ሁለት ሺህ) ነገደ እስራል መካከል አንዱ ነው። አዛሪያስ ደግሞ የተድባበ ማርያም የመጀመሪያው ፓትርያርክ ነው። በመጻህፍትም እንደተደነገገው ተድባበ ማርያም የፓትርያርክ መቀመጫ ነበረች። በመፅሐፈ ሱባኤ ዘአማኑኤል ካልእ ገጽ 2:6 ላይ እንደተጻፈው፤ ከሳቤቅ ጋር ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ አብረውት ከመጡት መካከል ሊቀ ካህን አዛርያስ፣ የዳዊት ልጅ ከአቢያጥ የተወለደው ጌዴዎን፣ የእሴይ ልጅ የሰሎሞን አጎት ኤልያብ፣ የዳዊት የልጅ ልጅ የአምኖን ልጅ ሔት፣ ኢዩኤል፣ ከነገደ ቢኒያም የተወለደው አብሔል፣ ከከነዓን የተወለደው በልዳድ፣ ከነገደ ይሁዳ የተወለደው አሴር፣ ከመሳፍንት ወገን የሆኑት ሱርባ እና ጉርባ ጥቂቶቹ ናቸው። ከሌዋዊያኑ ካህናት ጋር ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት መሣፍንት፣ መኳንንትና፣ ወይዛዝርት መካከል 1,500 (አንድ ሺህ አመስት መቶ) የሚሆኑት በተግባረ ዕድ የሰለጠኑ የወርቅና የብር፣ የብረትና የመዳብ፣ እንዲሁም የነሐስ አንጥረኞች አዋቂዎች ጠቢባን ፀበርተ ዕፀውና ወቀርተ አዕባን ናቸው፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡም በኋላ 2,500 (ሁለት ሺህ አመስት መቶ) የሚሆኑት የሌዋዊያን ካህናትና ነገደ እስራል ተከዜን ተሻግረው በየጁ በኩል አድርገው ተጉዘው በጥንቱ አጠራር አምሐራ ሳይንት የሚባለው አካባቢ ላይ ሰፍረዋል። አማራ ሳይንት፣ የአሁኗ ተድባበ ማርያም ካለችበት አምባ ላይ እንደደረሱ 12 በር ባለው ታቦር ተራራ ላይ ለእግዚብሔር ቤተ መቅደስ ሰርተው የአምልኮ ስርዓታቸውን ማከናወን ጀመሩ። ቦታዋንም በሀገሩ ስም ገሊላ ብሎ ጠራት፡፡ ፓትርያርክ አዛሪያስ ደስ አለውና ስሙን በቡራኬ አፀደቀለት፡፡ ቤተ መቅደሱን ሰርቶ ሲጨርስ ከሌዋውያኑም ከካህናቱም ከፍሎ መስዋተ ኦሪት የሚሰው ካህናትና ሌዋውያንንም ሾመ፡፡ መስፍኑ ሳቤቅ ቤተልሄማዊም በገፀ ንጉስ በወርቅ ወንበር የሚቀመጥ ነበር፡፡ በኋላም ሌዋዊያኑ ካህናት ግማሾቹ ደብር ደባብ እንበላት አሉ አዛርያስ እና የዳዊት የወንድም ልጆች ሳቤቅ ይህቺማ የኢየሩሳሌም የዳዊት መታሰቢያ ከተማ ትሆን ዘንድ ተድባበ ጽዮን እንበላት ብለው እንደሰየሟት ይነገራል፡፡ በኋላም በዘመነ ሐዲስ ክርስትና ሲስፋፋ አማሮች ተድባበ ጽዮን የሚለውን ስያሚ እንዲቀይሩ የአክሱም ነገስታት የነበሩት አብረሃ ወአጽበሃ አሰገደዷቸው፡፡ ነገስታቱም ተድባብ ጽዮንን ተድባበ ማርያም ብለው ሰየሙ፡፡ ትርጓሜውም ለእግዚአብሔር የተመረጠ ከፍተኛ ቦታ ማለት ነው፡፡ ተድባበ ማርያም የተመሰረተችበት ተራራ 12 በሮች ሲኖሩት፣ ወደ ተራራው መዝለቅ ወይም መግባት የሚቻለው ግን በሁለት የተፈጥሮ በር ብቻ ነው። እነዚህ 12 በሮችም ለነገደ እስራኤል መታሰቢያ ይሆኑ ዘንድ ሳቤቅ አገሮቹን አሻግሮ እያየ በሀገሩ ምሳሌ ሰይሟዋቸዋል፡፡ እነዚህም በሮች ገሊላ፣ደብረ ዘይት፣ ኬብሮን፣እያሪኮ፣ሎዛ፣ታቦር፤ ቦረና መግቢያ ላይ ሊባኖስ፣ ደማስቆ፣ አርሞንኤም፣ ደብር ፋራን፤ በሰሜን በኩል ደግሞ ኮሬብ ፣ቃዴስ ደብረ ፍጌህ፣ ቂሣርያ፣ ቢታኒያ፣ ጋዛ፣ ጎልጎታ፣ ፌልስጥኤም በመባል ይታወቃሉ፡፡ ሳቤቅ አማራ ሳይንትን ያስተዳድር እንደነበር ተጽፏል።ዙፋኑ፣ ዳታኑና፣ ወንበሩ የብረት ዙፋን በመባል ይታወቃል።/ያሬድ ግርማ ጎንደር ታሪክ 1999 ዓ.ም ርዕስ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም በብሉይ ኪዳን ስለመመስረቷ ምስክር የሚሆኑ አንዳንድ የኦሪት ሥረዓቶች ሲከናወኑ ይስተዋላሉ ታቦታቱ በበሚነግሱበት ወቅት በምስራቅ ያሉ ምዕመናን ነዋያተ ቅዱሳቱን ይዘው በምዕራብ ካህናት ተሰልፈው በሰሜን ያሉ ምዕመናን መጋረጃን ይዘው በደቡብ ያሉ ምዕመናን ጎራዴውንና ካሰማውን ይዘው መንቀሳቀሳቸው በኦሪት ዚሁልቁ ፪፣፫-፬ ያለውን የኦሪት ሥርዓት ያመለክታል። አጼ ይኩኖ አምላክ በ13ኛው ክ/ዘ ቤተመንግስታቸውን በታቦር ተራራ አድርገው በብሉይ ዘመን የፍርድ መስጫ የነበረውን አደባባይ (ጉላቴ) እንዳሉት ይነገራል። በተራራው በስተቀኝ በኩል በሚገኘው በዚህ አደባባይ በ1270 አጼ ይኩኖ አምላክ የአማርኛ ቋንቋን ብሄራዊ ቋንቋ እንዲሆን አውጀውበታል። በተጨማሪም በተጋር ተራራ ዮሐንስ ገብላዊ የቅኔ መድብል ያዘጋጁበት ብሉያተ ካህናት የተናገሩበት ጽዋተ ዜማ የተዘመረበት ቦታ ነው። የአፄ ይኩኖ አምላክ ቤተ-መንግስት ፍርስራሽ ይገኝበታል ተብሎ የሚታመነዉ በታቦር ተራራ ነው። ህንጻ ቤተክርስቲያን ተድባበ ማርያም ስትመሰረት በኦሪት ዘመን በነበረው ስርዓተ አምልኮተ ስለነበር አመሰራረቷ እንደ ቤተመቅደስ (ምኩራብ፣ አድባር) ነበር። በገድለ ገላውዲዎስ ላይ እንደተመለከተው ግን፣ ለዘመናት በድንኳን ውስጥ እንደነበረች ተገልጿል። የኋላ ኋላ በዘመነ ሃዲስ የክርስትና መስፋፋትን ተከትሎ ህንጻ ቤተክርስቲያን ተሰርቶላታል። የተድባበ ማርያምን የመጀመሪያ ህንጻ ቤተ ክርስቲያን ያሰሩት አጼ ገላውድዎስ ናቸው። በስማቸውም ጽላት ተቀርጾለቸው በየአመቱ ግንቦት 2 እየተከበረ ይገኛል። ህንጻ ቤተክርስቲያኑ በየዘመናቱ በተነሱ ነገስታት ሲሰራና ሲፈርስ ኖሮ አሁን ያለውና ከነሞገሱ የሚታየው ህንጻ ዘጠነኛው ህንጻ ሲሆን የተሰራው በንጉሥ ሚካኤል ነው፡፡ የሳር ጣሪያዋ ደግሞ በ1955 ዓ.ም. በእቴጌ መነን መልካም ፍቃድና ገንዘብ ቆርቆሮ እንዲለብስ ተደርጓል፡፡ አጼ ገላውድዎስ አባታቸውን አጼ ልብነ ድንግልን ተክተው አገራችን ኢትዮጵያ ከ1533 አስከ 1551 ዓ.ም ድረስ ለ19 አመታት አስተዳድረዋል ፡፡ አጼ ገላውድዎስ በልዩ ልዩ ስፍራዎች ከግራኝ አህመድ ጋር ጦርነት አካሂደዋል፡፡ በመጨረሻም አጼ ገላውድዎስ የተድባበ ማርያምን ጽላት በመያዝ ዘምተው በ1535 ዓ.ም በበጌምድር ግዛት ግራኝን ድል አድርገው አሸንፈዋል፡፡ ጽላቷን ይዘው ከአጼ ገላውዴዎስ ጎን የተሰለፉት በወቅቱ የተድባበ ማርያም ፓትርያርክ የነበሩት አባ ዮሐንስ ናቸው። ከዚያም አጼ ገላውድዎስ ዋና ከተማቸውን ተድባበ ማርያም ካስማ ከተባለ ቦታ ላይ አደረጉ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ተድባበ ማርያም በአካባቢው ህብረተሰብ ‹‹የግራኝ እመቤት›› እየተባለች ትጠራለች፡፡ ቤተክርስቲያኑ አራት በሮች (> 3 ሜትር ቁመት) እና 32 መስኮቶች (> 2 ሜትር ቁመት) በውጭ በኩል ክብ ክብ ነው። በንድፍ ፣ ቤተክርስቲያኑ በሦስት ክፍሎች በተሰበሰቡ ክበቦች ተደራጅቷል። በማዕከሉ ውስጥ ያለው አብዛኛው ክፍል ውስጠ ቅድስት (ቅድስተ ቅዱሳን) እና ዲያሜትር 24 ሜትር ያህል ነው። ታቦቱ በግልጽ ድንኳን ውስጥ (ድንኳን) ውስጥ እንደሚቀመጥ የታመነበት ይህ ነው። አሁን ባለችበት ሁኔታ ፣ ቤተክርስቲያኑ በአጠቃላይ ወደ 34 ሜትር ዲያሜትር ትለካለች። ሥርዓተ በዓላት በዘመነ አራት የቂጣ በዓል የአይሁድ ፋሲካ ይከበር ነበር፡፡ በዘመነ አብረሃ ወአጽብሃ ተድባበ ማርያምን አንጽው ካበቁ በኋላ ጥር 21 ቀን በአሏን ለማክበር ደንግገው ነበር፡፡ ይህም የበአል አከባበር እስከ ዐፄ ገላውዴዎስ ከቆየ በኋላ ዐፄ ገላውዴዎስ ግራኝ አህመድን ድል አድርጎ ሲመለስ ግንቦት ፩ ቀን ተድባበ ማርያም በመግባቱ የገባሁት በልደቷ እለቱ የእመቤታችን ልደቷ ነው በማለት የልደታን ጽላት አሰገብቶ የተድባበ ማርያምን በአል ግንቦት ፩ ቀን እንዲሆን አዋጅ አስነገረ፡፡ ከዚያን ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ግንቦት አንድ ቀን በደማቆ ሁኔታ ይከበራል፡፡ በማግስቱ ግንቦት ሁለት የገላውዴዎስ ልደት በመሆን ተከብሮ ይውላል፡፡ ከክብረ በአሏ በተጨማሪ ከዓመት እስከ ዓመት ሰብሀተ ነግህና ሠዓታት ቅዳሴና መዓልት ሰዓታት አይቋረጥባትም፡፡ አሁን በሌላው ደብር ዓመት እስከ ዓመት ይቀድስ ነበር፣ ሰብሀተ ነግህ ይቆምበት ነበር ተብሎ ይነገርበታል እንጀ ሲሆን አይታይም ተድባበ ማርያም ግን እስከ አሁን ድረስ ቅደዳሴና ስብሐተ ነግህ ሰዓታትና መዓልት ሰዓታት ዓመት እስከ ዓመት አይቋረጥም፡፡ ዋዜማው ከጧቱ ሦስት ሰአት ተጀምሮ ከቀኑ አስር ሰአት ያልቃል ማህሌቱ ማታ ሁለት ሰአት ተጀምሮ እስከ ቅዳሴ መግቢያ ይቀጥላል በማህሌት ሰርዓቱ ላይ የሚቆመው እንደሌላ ቦታ መልክዓ ማርያም ሳይሆን የራሷ ሌቃውንት የደረሱት መልከዓ ልደታ ነው፡፡ ለአብነት ያህል ሰላም ለህንብርትኪ ዘአርያሁ ሰሌዳ ወለ ማህጸንኪ ቤቴል ማህደረ ክርስቶስ እንግዳ በእንቲአኪ ይብሉ ማርያም ሠራዊተ ንጉስ ይሁዳ ዳዊት ዘመዳ ኤያቄም ወለዳ ኤያቄም ወለዳ ዳዊት ዘመዳ፡፡ እያሉ የራሷን ድርሰት ይቆማሉ ፡፡ ይህም በሌላ ቦታ አይባልም፡፡ ሊቀ ካህኑ ሁል ጊዜ የአይሁድ ዘሮች እንደሆኑ ከታመነ ከካህናት ክፍል ጎሳዎች ይመረጣሉ። በተጨማሪም ፣ ዲያቆኖች ፣ ዕድሜያቸው ከ 9 ዓመት በታች ብቻ ፣ አገልግሎት እንዲሰጡ ይፈቀድላቸዋል። በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉት አብዛኛዎቹ ቅርሶች እና መገልገያዎች ዕጣን ማቃጠያ (ማጣሪያ በሰንሰለት) ጨምሮ ከንፁህ ወርቅ የተሠሩ ናቸው። ወደ ቅድስተ ቅዱሳን በሚገቡበት ጊዜ ረዳቶች በአደጋ ጊዜ የሊቀ ካህናቱን አካል በደህና ከውስጣዊው ቅድስት ውስጥ እንዲወጡ ለማድረግ ከሊቀ ካህኑ ጋር ታስሯል። የኢ / ኦ / ተ / ቤ / ክ 3 ኛ ፓትርያርክ አቡነ ታክላ ሃይማኖት ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ለመግባት ሞክረው በገመድ ተጎትተው ቢወጡም ከአንድ ዓመት በኋላ በ 1988 ዓ.ም. በዓመታዊ በዓላት ወቅት በታቦቱ ፊት የመጥፎ አደጋን ተከትሎ መሬቱን ስለወረረ ወረርሽኝ አንድ ታሪክ ይነገራል። በኋላ የአገሩ ሰዎችም በእብጠት እና በበሽታ ተሠቃዩ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ታቦቱ ከድንኳኑ ውጭ ተሸክሞ ወይም በጉባኤ ወቅት ለሕዝቡ ታይቷል። የቅርስ ክምችት ተድባበ ማርያም እድሜ ጠገብና አያሌ ታሪክ ያስተናገደች እጅግ ጥንታዊ መካነ ቅርስ ናት፡፡ የሚታዩና፣ የማይታዩ፤ ብሎም የተሰወሩና፣ ያልተነገሩ አያሌ ድንቅ የኢትዮጵያ ታሪኮችና ቅርሶችን ጠብቃ ዘመን ያሻገረች ህያው ሙዚየም ናት፡፡ ነገሥታት ዘውዳቸውን አውልቀው የሰጧት፣ ካባቸውን የደረቡላት፣ ደስታቸውን በድንቅ ስጦታዎቻቸው የገለጹላት ስፍራ ናት፡፡ አፄ ገላውደወስ፣ አፄ ዘርአያእቆብ፣ አፄ በዕደማርያም፣ አፄ እስክንድርና፣ ንጉስ ሚካኤልና ሌሎች ነገስታትም ልብሰ መንግስታቸውን፣ እንቁ፣ አልማዝ፣ ወርቅ፣ ብርና፣ ሌሎች የከበሩ ማእድናትንም ለቤተክርስትያኗ አበርክተዋል። ተድባበ ማርያም እጅግ ብዙ ውድ ሀብቶች አሏት ፣ አንዳንዶቹም ከድሮው መጽሐፍ ቅዱስ (ኦሪት) ጀምሮ ናቸው። ክምችቶቹ አሁን በአብያተ ክርስቲያናት ግቢ ውስጥ ባለው ሙዚየም ውስጥ ይታያሉ። እጅግ ልዩ ከሆኑት ቅርሶች መካከልም የበግ ምስልና የተቁለመለመ የበግ ቀንድ ያለበት መስቀል በዚያ ይገኛል፡፡ የዚህ መስቀል ብርሀን የሚያስገርምና ዓይንን የሚያንፀባርቅ ሲሆን ከምን አይነት ማእድን እንደተሰራ አይታወቅም፡፡ ከጥንታዊያን ነገስታትም መካከል ዐፄ ካሌብ ወደ ደቡብ አረቢያ የናግራንን ክርስቲያኖች ለመርዳት ሲዘምቱ ፓትርያርክ ዘሙሴ እሱም የኦየሩሳሌምን ገዳም ያቀናና በመጨረሻም በአባ ጴንጠሌዎን ገዳም ገብቶ ያረፈ አባት ጋር ዘምተው ድል አድርገው ሲመለሱ ይዘው የሄዱትን ጋሻ በስዕለት ለተድባባ ማርያም አስገብተውት በቦታው ይገኛል፡፡ እንዲሁም የእብራይጥ ሲኖዶስና የአረማይክ ቅዳሴ እግዚእ በቦታው ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ገዳም ከ1000 ያላነሱ የብራና ጥንታዊያን መጸህፍት ይገኛሉ እነዚህም መጻህፍት ክፊሎቹ በጥንታዊት የአክሱም ዘመን መንግስት የተጻፈ ሲሆኑ ሌሎቹ ደግም በመካከለኛ ዘመን የተጻፉ ናቸው፡፡ ተድባበ ማርያም ለትውልድ ካቆየቻቸው ቅርሶች መካከልም የሚታዩትና የሚዳሰሱት በጥቂቱ ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል፡፡ 1. የበግ ምስልና እንደ ኮኮብ የሚያበራ የተቁለመለመ የበግ ቀንድ ያለበት መስቀል 2. ዐፄ ካሌብ ወደ ደቡብ አረቢያ የናግራንን (የመን) ክርስቲያኖች ለመርዳት ይዘውት የዘመቱት ጋሻ 3. የእብራይጥ ሲኖዶስና 4. የአረማይክ ቅዳሴ እግዚእ (ገበታ ቅዳሴ) 5. በአረማክ ቋንቋ የተጻፉ የስሌዳ መጻህፍት 6. 4. በአረበኛና በግእዝ የተጻፉ መጻህፍት 7. ወንጌል ዘወርቅ እየተባለ የሚጠራ ትልቅ የወርቅ ጉብጉብታ ያለበት ቅዱስ ወንጌል 8. የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ጳጳስ የቀደሰበት የእጅ መስቀል 9. የመጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ መስቀል 10. የዕጨጌ ዮሐንስ በትረ ሆሳዕና እና የእጅ መስቀል 11. የአቡነ አኖሪዎስ የእጅ መስቀል 12. የአቡነ ቄርሎስ የእጅ መስቀል 13. ስእርተ ሀና (የማርያም እናት፣ ቅድስት ሀና ጸጉር)፣ የተቀመጠበት የሽክላ ገንቦ ጥንታዊና በስነ-ጥበባዊ ይዘቱ የሚያስገርም ነው 14. ሄሮድስ የጨፈጨፋቸው ህጻናት ዓጽም በክፊል 15. የቅዱስ ጊዩርጊስ አወራ ጣት 16. 13. በአጠቃላይ የ28 ሰማእታት ዓጽም ይገኛል 17. የዐፄ ገላውዴዎስን ጨምሮ የስድስት ነገስታትና የአራት እጨጌዎች ዓጽም ይገኛል 18. የአጼ ዳዊት ዙፋን 19. የቅዱስ የሬድ ድጓ እና ጊዩርጊስ ወልደ አሚድ፣ ገድለ አዳም 20. ከ1000 የሚበልጡ ጥንታዊ የብራና መጻህፍት 21. ሉቃስ እንዳሳላት የሚነገርላት የቅድስት ድንግል ማርያም ስዕለ አድህኖ 22. በርካታ ጥንታዊ የእጅና የመጾር መስቀል 23. 20.ልዩ ልዩ ንዋየ ቅድሳት 24. የነገስታት ዘውዶች፣ወንበርና አልባሳት 25. ባለ 3 ተከፍች የገበታ ስእልና ጥንታዊና ስነ ጥበባዊ ቅርሶች ይገኛሉ ስነ-ፅሁፍና ኪነ-ጥበብ ርእስ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም የሐዲስ ኪዳን የስርዓት መነሻ የቅኔ ምንጭ የደጔ ምልክት ነቅ ደጔ ከጠፋ በኋላ የድጔን ምልክት በመፍጠር ለትወልድ ያሰተላልፉ አዛዢ ጌራንና አዛዢ ዘራጉኤልን ያፈራች ዙሪያዋን በታላቅ ገዳማት እና አድባራት የተከበበች የአማርኛ ቋንቋ መገኛ እንደሆነች የሚነገርላት የጎንደር የጎጃምና የሽዋ እንዲሁም የወሎ መገናኛ ማእከል የሆነች ለስነ ልሳን ተመራማሪዎች ትልቅ የቅርስ ስፍራ የሆነችው ርእስ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርይም የታቦር ተራራ የቅኔ መገኛ ሰማንያ ጋሻ መሬት የሸፈነ የደንቆር ብሔራዊ ፓርክ ክልል የሚገኝባት ስትሆን ለኢትዮጵያ ታላቅ የታሪክ ማህደር ናት፡፡ ለበርካታ ጊዜያት በተፈጠሩ ክስተቶችና ወረራዎች አያሌ የቤተክርስትያን ንዋያተ ቅድሳት፣ ቅርሶች፣ መጸህፍትና፣ ሌሎችም ተቃጥለዋል፣ ወድመዋልም። በነዚህም ወረራዎች በርካታ ገዳማትና አድባራት ሲቃጠሉና ሲመዘበሩ ተድባበ ማርያም ግን ምንም አይነት ቃጠሎና የቅርስ ዝርፊያ አልደረሰባትም፡፡ ለዐዋቂዎች ጥበብን እንናግራቸዋለን ነገር ግን የዚህን ዓለም ጥበብ ወይም ያልፉ ዘንድ ያላቸውን የዚህን ዓለም ሹመች ጥበብ አይደለም፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር አስቀድሞ ከዘመናት በፊት ለክብራችን የወሰነውን ተሰውሮም የነበረውን የእግዚአብሔርን ጥበብ በምስጢር እንናገራለን፡፡ የእመቤታችን የፅዮን ማርያም ቤተክርስቲያን የንጉስ ጉላውዴዎስ ዜና መዋዕል ፣ ሰለሞን ገብረየስ። ጎጃም ውስጥ ጉዞዎች-ቅዱስ ሉቃስ ኢኮንስ እና ብራንክሌዎን እንደገና ተገኙ። 41965874 እ.ኤ.አ. የወሎ ጠቅላይ ግዛት ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ታሪክ በኢትዮጵያ - 1769–1916። ምስጋናው ታደሰ መላኩ የኢትዮጵያ ታሪክ - ጥራዝ ) - ኑቢያ እና አቢሲኒያ ፣ ኢኤ ዎሊስ ቡጌ (ገጽ 346 ፤ 351 ፤ 350 ፤ 353)። ተድባበ ማርያም (ተድባበ ጽዮን ፣ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም) (ጽሑፍ እና ፎቶዎች)
4273
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%89%A0%E1%88%B3
አንበሳ
አንበሳ () ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ተብሎ የሚታወቀው ቤተሰብ አባል ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። ቀልብ የሚስብ አስደናቂ ፍጡር አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። ሲምባ*—በማኅበር የሚኖር እንስሳ አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)።” የግርጌ ማስታወሻ ሲምባ በስዋሂሊ “አንበሳ” ማለት ነው። የዱር አራዊት ታላላቅ ድመቶች የኢትዮጵያ አጥቢ እንስሳት
10298
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%83%E1%8B%AD%E1%88%88%E1%88%9B%E1%88%AA%E1%8B%AB%E1%88%9D%20%E1%8B%B0%E1%88%B3%E1%88%88%E1%8A%9D
ኃይለማሪያም ደሳለኝ
አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በወላይታ አውራጃ በቦሎሶ ወረዳተወለዱ። የ1ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአከባቢያቸው የአየርላንድ ካቶሊክ ሚሺን ባቋቋመው ት/ቤት እንደፈጸሙ የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወላይታ ሶዶ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፈጽመው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢንጂነሪንግ ከተመረቁ በኋላ በአርባምንጭ ውኃ ተቋም አስተማሪ ሆነው እያገለገሉ ሳሉ የማስትሬት ዲግሪያቸውን በፊንላንድ ተምፔ ዩኒቨርስቲ በጽዳት ወይም ሳኒቴሺን አጠናቀው አገር ቤት በመመለስ በአርባምንጭ ውኃ ቴክኖሎጂ ዲን ሆነው አገልግለዋል። ከዚያም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በም/ፕሬዚዳንት፣ በፕሬዚዳንትና የኢሕአዴግ ዋና ጸሃፊ ሆነው አገልግለዋል። ተማሪ በነበሩ ጊዜ የደርግ ደጋፊ የነበሩት አቶ ሃይለማርያም፣ የማስተርስ ትምህርታቸውን ጨርሰው ሲመለሱ የመንግስት ለውጥ ስለነበረ፣ እሳቸውም የአቁዋም ለውጥ አርገው የገዚው መንግስት ደጋፊ መሆን ጀመሩ። የስልጣን ጥማታቸውንም ለማርካት፣ ከፖፑ በላየ ካቶሊክ እንደሞባለው፣ እሳቸውም የዘር ፖለቲካውን ከወያኔ ባለስልጣኖች በላይ ማናቸስ ጀመሩ። ባለቤታቸው ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ ከአከባቢያቸው ከወላይታ ዞን ሲሆኑ በኢኮኖሚክስና በሥራ ሃላፊነት ሁለት የማስተርስ ዲግሪ ምሩቅ ሲሆኑ ባለቤታቸው ወደ አዲስ አበባ እስከመጡበት ድረስ የደቡብ ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ቢሮ /የባለቤታቸው/ ልዩ አማካሪና የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል። ወ/ሮ ሮማን ከሃይስኩል እስከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ድሕረ ምረቃ ድረስ ከባለቤታቸው ጋር አብረዋቸው በከፍተኛ ትምሕርት ዘልቀዋል። ወ/ሮ ሮማን ተስፋዬ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅት መሥርተው በኃላፊነት ከሰሩ በህዋላ ወደ ዩ.ኤን.ዲ.ፒ. ዓለም አቀፍ መሥሪያ ቤት ተዛውረው ሲሰሩ ቆይተው ከህዳር ወር ጀምሮ ሙሉ በሙሉ የቀዳሚ ወይዘሮ ቢሮ ተረክበዋል። በዚህም ሥራ መስክ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያ ና የጎጂ ልማዶችና ባህሎች ማስወገጃ ሰሚናሮች ላይ እየተገኙ ንግግር በማድረግና ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛሉ። አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የኢሕአዴግ መንግስትና የወላይታ ሕዝብ በቋንቋ ምክንያት በተፈጠረው ውዝግብ ጊዜ የ"ወጋጎዳ" ቋንቋ የወላይታ ልጆች ተገደው እንዲማሩ ጫና አርገዋል ተብለው በሌሎች የአከባቢያቸው ጎሳዎች ዘንድ አለመወደዳቸው ጥቁር ነጥብ በታሪካቸው ጥሎ እንዳለፈ ይነገራል። እንዲሁም በደቡብ ክልል የክልል ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩ ጊዜ በጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ትዕዛዝ የበላይ አለቃቸውና የክልሉን ፕሬዚዳንት የነበሩትን አቶ አባተ ኪሾን ከስልጣን የሚያስወግድ ደብዳቤ በገዛ እጃቸው የጻፉና በምትካቸው ራሳቸውን ተክተዋል እየተባሉም ይተቻሉ። ይሁን እንጂ በመንግሥት ሚዲያ በኋላ እንደተነገረው አቶ አባተ ኪሾ በሙስና ምክንያት ከስልጣን መወገዳቸው ተዘግቦአል። በዚህም የተነሳ በጊዜው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መስተዳድር አስተዳደራቸውና እውቅናቸው እይደበዘዘ ስለመጣ የአካከባቢው ተወላጆች በተደጋጋሚ በሚቀሰቅሱት ተቃውሞች ከሥልጣናቸው ተነስተው ወዲያውኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ አማካሪ ሆነው በታላቁ ቤተመንግሥት አከባቢ ቆይተው በ2003 በ8ኛው የኢሕአዴግ ጠቅላላ ስብሰባ ላይ የቀድሞውን ብሄረ አማር ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ መሪ አቶ አዲሱ አበበን በመተካት የኢሕአዴግ ምክትል ሊቀመንበር ለመሆን በቅተዋል። በተጨማሪም የደቡብ ክልላዊ መንግሥት የኢሕአዴግ ሊቀመንበር በመሆናቸው በፓርቲው ታሪክ የመጀመሪያው በትጥቅ ትግል ያልተሳተፉ ከፍተኛ ባለሥልጣን መሆን ብቻ ሳይሆን ከመለስ ዜናዊ ቀጥሎ ያለውን 2ኛውን ትልቅ ቦታ በጣም በአጭር ጊዜ ውስጥ ከመቆናጠጣቸውም በላይ የኢትዮጵያ 24ኛው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል። ይህም በመሆኑ፡ ከሶስት ትላልቅ ብሄሮች ውጪ ማለትም አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ ብሄር አባል ያልሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የደቡብ ተወላጅና ከኦርቶዶክስ እምነትተከታይ ውጪ ፕሮተስታንትየውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው እ.ኤ.አ ኦገስት 22 /2012 ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ አቶ ኃ/ማሪያም ወደ ተጠባባቂ ጠ/ሚኒስትርነት ማዕረግ ከፍ ብለው ለአንድ ወር ያህል ከቆዩ በኋላ የገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የፓርቲው ሊቀመንበርና ባለሙሉ ስም ጠ/ሚኒስትር እንዲሆኑ በመመረጣቸው እስከ 2015 ምርጫ ቀጣዩ የኢትዮጵያ መሪ በመሆን በኢትዮጵያ ታሪክ መዝገብ ላይ ስማቸውን አኑረዋል። የሚከተለው አስረጅ ከአይጋ ፎረም የተወሰደ ነው የ47 ዓመቱ አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ በአረካ ከተማ ነው የተወለዱት ። የወጣትነት ዘመናቸውንም በዚህ በተወለዱበት ሰፍራ ያሳለፉ ሲሆን ፥ በ1980 ዓመተ ምህረት የባችለር ድግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስና አግኝተዋል። ገና በወጣትነት ዘመናቸው የያኔውን የአርባምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የዛሬውን አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲን በመምህርነት አገልግለዋል ። በተቋሙ ቆይታቸው ባገኙት ነፃ የትምህርት እድልም ወደ ፊንላንድ በማቅናት ከታምፔሬ የቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በስነ ንፅህና ምህንድስና የማስተርስ ድግሪያቸውን ተከታትለዋል ። ከተመለሱም በኋላ የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዲን በመሆን ለ13 ዓመታት ያገለገሉ ሲሆን ፥ በነዚህ ጊዜያት ውስጥም ከአሜሪካው አዙሳ ፓስፊክ ዩኒቨርሲቲ በድርጅት አመራር የማስተርስ ድግሪ አግኝተዋል ። አቶ ሀይለማሪያመ ደሳለኝ በ1990ዎቹ መግቢያ ላይ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ አባል በመሆን በአገሪቱ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ መሳተፍ ጀምረዋል ። የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስትን በምክትል ርእሰ መስተዳደርነት ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ ሀይለማሪያም በ1998 ለአራት ዓመታት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሆነው ሰርተዋል ። በመቀጠልም አቶ ሀይለማሪያም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመሆን የተንቀሳቀሱ ሲሆን ፥ በምክር ቤቱ የመንግስት ጉዳዮች ተጠሪ ሚኒስትርም ነበሩ ። ከዚህ በተጓዳኝም በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አማካሪም ሆነው የሰሩ ሲሆን ፥ የጠቅላይ ሚኒሰትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች ፣ የህዝብ አደረጃጀትና ተሳትፎ ልዩ አማካሪም ሆነው የሰሩባቸው ጊዜያቶች ነበሩ ።ከ2002 አገር አቀፍ መርጫ በኋላም በድጋሚ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ሆነው የተመረጡ ሲሆን ፥ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ካቢኔ ውስጥም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነትና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ተሹመው በማገልገል ላይ ይግኛሉ ። በፓርቲያቸው ውስጥ ባላቸው እንቀስቃሴም የኢህአዴግ አባል በሆነው ድርጅታቸው በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ንቅናቄ / ደኢህዴን/ ሊቀመንበር በመሆን ከ10 ዓመት ለሚበልጥ ጊዜ እየሰሩ ይገኛሉ ። የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልም ሲሆኑ ፥ ከሁለት ዓመት በፊት የድርጅቱ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ምክትል ሊቀመንበር ሆነውም ተመርጠዋል ። ከወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ ጋር ትዳር መስርተውና ሶሳት ልጆች አፈርተው እየኖሩ የሚገኙት አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ዛሬ የኢህአዴግ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል። በፓርቲው አሰራርም መሰረት የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ያገለግላሉ። የኢትዮጵያ መሪዎች የኢትዮጵያ ካቢኔ አባላት
43663
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%88%AD%E1%8B%A8%E1%88%9D%20%E1%8B%A8%E1%8A%A5%E1%8B%A8%E1%88%B1%E1%88%B5%20%28%E1%8A%A0.%E1%88%B0%29%20%E1%8A%A5%E1%8A%93%E1%89%B5
መርየም የእየሱስ (አ.ሰ) እናት
{{|መርየም በኢስላም||መርየም የእየሱስ (አ.ሰ) እናት}} ሌሎች ስሞችዋ ሜሪያም|ማርያም|መርየም(ስም) | ስም = ድንግል መርየም ኢምራን | ርእስ = ድንግል, የተጣራች, የተወደሰች, የእየሱስ (አ.ሰ) እናት, ድንግልናዋን የጠበቀች, ቅድስት, የሰቶች ምሳሌ, የአማኞች ምሳሌ | የትዉልድ_ቀን = | የትዉልድ_ቦታ = እየሩሳሌም | የሞተችበት_ቀን = | የሞተችበት_ቦታ = እየሩሳሌም | የምትታወቀዉ_በ = ሁሉም እስልምና<እና>በሁሉም ክርስትና | አራያ = | አራያ = በሁሉም እስልምና እና ክርስትና ሴቶች. | ዋነኛ_ስራዎች= | እምነት = ሙስሊም በክርስትና እምነት ማርያም ( መርየም በ አረበኛ), በስልምና እምነት መርየም የ(ኢሳ),ለሙስሊም ሴቶች አራያ ለአማኞች ምሳሌ ነች መርየም በቁራን ልይ ስምዋ ከ ፴ (ሰላሳ)ጊዜ በላይ በተለያዩ የቁራን ቁጥሮች ሲጠቀስ በስምዋ የተሰየመላት ብቸኛ ሴት ነች እሱም ምእራፍ ፩፱ (አስራ ዘጠኝ) ሱረቱ መርየም የሚል ምእራፍ አላት. ይሀም ምእራፍ ስለ ሂወት ታሪክዋ የሚአወራ ሲሆን መርየም በቁራን ላይ በስማቸዉ ምእራፍ ከተሰየመላቸዉ ስምንት ሰዎች ዉስጥ አንዷ ነች. መርየም በተለይ ከቁራን ላይ የተጠቀሰችዉ ከአስያ ጎን ለጎን ነዉ. ለነዚያ ለአመኑትም የፈርዖንን ሴት አላህ ምስል አዴገ፤ ጌታዬ ሆይ! አንተ ዘንድ በገነት ውስጥ ለኔ ቤትን ግንባልኝ፤ ከፈርዖንና ከሥራውም አድነኝ፤ ከበደለኞቹ ሕዝቦች አድነኝ ባእች ጊዜ። የዒምራንን ልጅ መርየምንም ያቺን ብልቷን የጠበቀችውን (ምሳሌ አደረገ)፤ በርሱም ውስጥ ከመንፈሳችን ነፍፋን እጌታዋ ቃላትና በመጽሐፍቱም አረጋገጠች፤ ከታዛዦቹም ነበረች። መርየም በእስልምና ባህል (ህግ) በጣም ግዴታ የሆነ ህግን ነበር ያከበረችዉ (ክብርን መጠበቅ ከዝሙት መጠበቅ) በቁራን መራፍ ዘወትር የተወራላት በቤተ መቅደስ ዉስጥ (በ መስጅድዶች ዉስጥ)፣. በቁራን ላይ እንደተጠቀሰዉ ኢሳ በሙስሊሞች ጌታ አላህ ፍላጎት በተአምር ከአባት ዉጭ ወይንም ያለ ግብረ ስጋ ግንኙነት ነበር የተወለደዉ. መርየም አላህ በምድር ላይ አልቆ የመረጣት ሴት ስትሆን ከ አራት ምርጥ ሴቶቻችን ዉሥጥ አንድዋ ነች. መላእክትም ያሉትን (አስታዉስ) - መርየም ሆይ! አላህ በእርግጥ መረጠሽ፣ አነጻሽም፣ በዓለማት ሴቶችም ላይ መረጠሽ። (አስያ ኢምራን፣ አስያ ቢንት መህዙም፣ኽዲጃ ኹወይሊድ፣ ፋጢማ ሙሃመድ). መርየም በቁራን ላይ የኢምራን ቤት፣ ከ ኢምራን ዋቢ እንደተገለጸዉ ሙሳ (አ.ሰ) ሃሩን (አሮን) እና ሜሪያም, ከነዚህ የትውልድ ዘር ነች። መርየም «የኢምራን ልጅ» ትባላለች። ስሙ ከቁርአን ያልተጠቀሰዉ እዉነተኛ አባትዋ ተብሎ በ ክርስትና እምነት እንደሚነገረዉ ስሙ ኢያቄም ይባላል። መርየም በቁርአን መርየም በተደጋጋሚ በቁራን ላይ ተጠቅሳለች፣ እናም የስዋ ታሪክ የያዘዉ ምእራፍ የወረደዉ ከ መጨረሻዉ ምእራፍ ነዉ, የወረደዉ በመካ ነበር, የመጨረሻዉ ምእራፍ ደግሞ በመዲና. ነበር. የመርየም አወላለድ ከቁርአን ከአባትዋ ጋር የተተቀሰችዉ እናትዋ ቅድስት አኔ. የመርየም አባት ኢምራን ይባላል ኢምራን በ አረብኛ እና አኔ ሃናህ በአረብኛ ይባላሉ በኢስላም ታሪክ ኢምራን እና ባለቤቱ ሃና ሽማግሌ እና መካን ነበሩ. አንድ ቀን ዛፍ ላይ ተለቁን የሚመግብ ወፍ አየች ከዛም በራስዋ ሂወት ተረጎመችዉ አልላህበሰበብ አድርጎ የፈለጉትን እንደሚሰጥ አስታወሰች ክዛም ለአላህ ልጅን እንዲአሞላላት ተማጸነችዉ. አላህም ልመናዋን እቀበለ መርየምን ጸነሰቻት. የዒምራን ባለቤት (ሐና)- ጌታዬ ሆይ! እኔ በሆዴ ዉስጥ ያለዉን (ፅንስ ከሥራ) ነጻ የተደረገ ሲሆን ለአንተ ተሳልኩ፤ ከኔም ተቀበል፤ አንተ ሰሚዉ አዋቂዉ ነህና ባለች ጊዜ (አስታውስ) ከዛም ወንድ መስላት ስለነበር ለአላህ ቤት አገልጋይነት ተሳልቻት ነገር ገን ሰት ሁና ተወለደች ከዛም ለመርየም ዱአ አደረገችላት አላህ ከሰይጣን (ሸይጥዋን) እስዋንምዘርዋንም እንዲጠብቅላት. እናም በ እስልማና ሀዲስ, ላይ እንደሚብራራዉ መርየም ኢሳ (አ.ሰ) ወይንም እየሱስም ብቸኛ በ ሰይጣን ያልተነኩ ሁነዉ የተወለዱ ህጻናት ናቸዉ. .ቡሀሪ, አንብያ", 44; ሙስሊም, ፈዳኢል'', 146, 147 በወለደቻትም ጊዜ- ጌታዬ ሆይ እኔ ሴት ሆና ወለድኋት፤ አላህም የወለደችዉን ዐዋቂ ነዉ፤ ወንድም እንደ ሴት አይደለም፤ እኔም መርየም ብዬ ስም አወጣሁላት፣ እኔም እስዋንም ዘርያዋንምን ከተረገመዉ ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ አለች። ቀሪዎቹ አመታት ቁር አን ላይ እንደተጠሰዉ መርየም በመጸለያዉ ቤተ መቅደስ ዉስጥ አደገች.ከቤተ መቅደሱም የተለየ የማረፍያ ቦታ ነበራት. በዛን ሰአት ያሳድጋት እና ያግዛት የነበረዉም ነብዩ ዘካሪአስ (ካህን) ዘከርያ(አ.ሰ) ነበር. ይህነነም የሚገልጸዉ ቅር አን ጌታዋም በደህና አቀባበል ተቀበላት፤ በመልካም አስተዳደግም አፋፋት፤ ዘከሪያም አሳደጋት ዘከሪያ በርሷ ላይ በምኲራቧ በገባ ቊጥር እርስዋ ዘንድ ሲሳይን አገኘ፤ -- መርየም ሆይ ይህ ለአንቺ ከየት ነዉ? አላት፤ --እርሱ ከአላህ ዘንድ ነዉ፤ አላህ ለሚሻዉ ሰዉ ሲሳዩን ያለድካም ይሰጣል አላችዉ። የመርየም ብስራት በድንግልናዋ መርየም የተወለደዉ እየሱስ በስልማና በጣም አስፈላጊ ነዉ. ይሀዉም ከአልላህ ተአምራቶች ዉስጥ አንዱ ነዉ. የ እየሱስ አወላለድ በመጀመርያ የተጠቀሰዉበ ሱራ መርየም ቁጥር ፳ (ሃያ) ላይ ነዉ መርየም ለገብርኤል ቅዱስ መንፈስ በ(ኢስላም)ጂብሪል መጥቶ ለገን ትወልጃሽ ሲላት ያለ ወንድ እንዴት ስትል የጠየቀችዉ ፦ እኔ ንጹሕን ልጅ ለአንቺ ልሰጥሽ፣ የጌታሽ መልክተኛ ነኝ አላት። (በጋብቻ) ሰዉ ያልነካኝ ኾኜ፣ አመንዝራም ሳልኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል! አለች። ፦ አላት (ነገሩ) እንደዚህሽ ነው ፤ ጌታሽ ፦ እርሱ በእኔ ላይ ገር ነው፤ ለሰዎችም ታምር፣ ከኛም ችሮታ ልናደርገው (ይህንን ሠራን) የተፈረደም ነገር ነዉ አለ፤ (ነፋባትም)። ወዲያዉኑም አረገዘችዉ፤ በርሱም (በሆድዋ ይዛዉ) ወደ ሩቅ ስፍራ ገለል አለች። ምጡም ወደ ዘንባባይቱ ግንድ አስጠጋት፣ ዋ ምኞቴ! ምነው ከዚህ በፊት በሞትኩ፣ ተረስቼም የቀረሁ በኾንኩ፤ አለች። ፩፱ አስራ ዘጠኝ|ከአስራ ዘጠኝ እስከ ሃያ አምስት ፩፱-፪፭ ነገር ገን መርየም በቸገር ላይ ሁና ይሀን ብትልም ለዚህ እድልዋ ገን አልላህን አመስግናለች. የእየሱስ በድንግልና አወላለድ ከቁራን ላይ ስለ እይውሱስ አወላለድ ብዙ ግዘ ተጠቅስዋል። በ ምእራፍ አስራ ዘጠኝ ፩፱ ቁጥር ፩፯ አስራ ሰባት እስከ ፪፩ ሃያ አንድ ቅዱስ ቁርአን 19-17. የ እየሱስ አወላለድ በስልምና የሰዉ ልጅ አፈጣጠር ወይንም አወላለድ ተአምሮች ዉስጥ በ አራተኛ ደረጃ ልይ የሚገኝ ተአምር ነው። ፩ (አንደኛ) የአደም (አ.ሰ) (አዳም) አፈጣጠር ነዉ አምላካችን አላህ አደምን ያለ እናት አባት ከአፈር ነው። ይህም ከአፈጣጠር ታላቁ ተአምር ነዉ አልላህ ከምንም የሚአስገኝ መሆኑን ያሳየበት (አልባሪእ) ይሄ ከ ፱፱ ዘጠና ዘጠኝ የአላህ ስሞቹ ዉስጥ ከኢምንት አስገኝ የሚለዉ ስሙ ነው። ሁለተኛዉ አፈጣጠር ደግሞ የሃዋ (ሄዋን) አፈጣጠር ነው። ይሀዉም ያለ እናት ያለ ማህጸን ከወንድ ግራ ጎን ከአደም ነው። ሶስተኛዉ ደግሞ ከወንድ እና ከሴት በተፈጥሮአዊ አወላለድ ከአደም እና ከሃዋ እኛ መወለዳጭን ነው። አራተኛዉ እና ብዙ መንገዶችን ከከፈተዉ ብሎም ብዙ አማኝ ያልሆኑ ሕዝቦችን ያሳሳተበት ግና ለክ እንደ ሃዋ አይነት አወልለድ ይዘት ያለዉ የ እየሱስ (አ.ሰ) አወላለድ ነዉ እሱም ሃዋ ያለ እናት ማህጸን ከለለዉ ወንድ ገና ያለማህጽን ቢሆንም ከጎኑ ከአደም እንደወጣችዉ ኢሳም ያለ አባት ማህጸን ባላት ሴት በድንግልዋ መርየም (ማርያም) አማካኝነት አራተኛ ተአምር ሁኖ ተውለደ ይሀ አወላለድ ክርስትያኖች ፫ቱን ሶስቱን ተአምር እረስተዉ ይሀ እንደትልቅ ተአምር ታይቶ ከነብይነት ወጥቶ ወደ ጌትነት ማእረግ አሸጋግሮታል። እስከአሁንም ፫ተኛ ጌታ ሁኖ የአብ ልጅ ይባላል።
3358
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%80%E1%88%AD%E1%88%98%E1%8A%95
ጀርመን
ጀርመን ወይንም በይፋ ስሙ የጀርመን ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ በመካከለኛ አውሮፓ የሚገኝ ታሪካዊ አገር ነው። አገሩ 16 ክልሎች ሲኖሩት ዋናና ትልቁ ከተማውም በርሊን ነው። በ100 ዓም በፊት እነኚህ ጎሳዎች "ጀርመኒያ" የተባለች ትንሽዬ ግዛት እንዳቋቋሙ በታሪክ ይገለፃል። ጀርመን መካከለኛውን የአውሮፓ ክፍል ይዛ እንደ ሀገር መቋቋም የጀመረችው በቅዱስ ሮማን ግዛት በ10ኛው ክፍለ ዘመን ነበር። ይህ ግዛት የጀረመን "የመጀመሪያው ራይክ" ተብሎ ይጠራል። ይህ ግዛት ከፍራንኮች (ፈረንሳይ) ጋር ተደጋጋሚ ጦርነት ውስጥ በመግባት የቅዱስ ሮማን ግዛት በናፖሊያ ጦርነት በ1806 ዓም ሊፈርስ ችሏል። ከዛም በኋላ የጀርመን ኮንፌድሬሽን ጥቂት ግዛቶችን በመያዝ መቋቋም ጀመረ። በመካከለኛው ዘመን በሀይማኖት አስተምሮት ችግር ሳቢያ የፕሮቴስታንት እምነት ከካቶሊክ ተገንጥሎ መውጣት ጀመረ። በኢንላይትመንት ጊዜ፣ ጀርመኖች አዳዲስ ሀሳቦችን ማፍለቅ ጀመሩ፣ የካቶሊክ መንግስትን ለመገርሰስ ሲባል የኢሉሚናቲ ማህበር በ1776 ዓም ተመሰረተ። ይህም ማህበር በዚሁ ስራ ቢሳካለትም አላማው ደግሞም የአለምን ሀኔታ ለመቆጣጠር፣ የሀይማኖትን ህልውና ለማጠልሸት እና የኒው ወርልድ ኦርደር አምባገነናዊ የአለም መንግስት ለመመስረት ነበረ። በ1871 ዓም የጀርመን ግዛት ተቋቋመ። ይህም "ሁለተኛው ራይክ" ተብሎ ይጠራል። ይህ ግዛት ጀርመንን ቀኝ እንድትገዛ እና ጀርመናዊ/ኖርዲካዊ የወደቁት መልዐክት ለማስፋፋት ነበረ የታሰበው። ምስራቃዊ የአውሮፓ ግዛቷ ፕሩዥያ ኢምፓየር ይባላል። በአንደኛው የአለም ጦርነት በኋላ የጀርመን ግዛት ከኦስትሮ ሀንጋሪ፣ ከኦቶማን ኢምፓየርና ከቡልጋሪያ ጋር በመግጠም፣ በአላይድ ፓወር ተሸነፈች። ከ1918 እስከ 1919 ዓም በተደረገው አብዮት የጀረመን የዘውዳዊ ግዛት ወደ ፌድራላዊ ዌማር ሪፐብሊክ ከ1918 እስከ 1933 ዓም ስትመራ ነበር። ጀርመን ቀደም ሲል በአንደኛው የዓለም ጦርነት በገጠማት የድንበር መጥበብ ምክንያት ሰይጣናዊው አምባገነናዊው የናዚ መንግስት በአዶልፍ ሂትለር ተጀመረ። ይህም ጊዜ "ሶስተኛው ራይክ" ተብሎ ይጠራል። ናዚ ጀርመን፣ ፋሺስት ኢጣሊያ እና የጃፓን ስርወ መንግስት የአንድዮሽ አምባገነናዊ የአለም መንግስት መመስረት ፍላጎት ቢኖራቸው ነገር ግን የነሱ ተቃራኒ የሆኑት አላይድ ፓወሮች አንድ ላይ ተቀናጅተው ይህንን ስርአት ለመመስረት ያቀረቡትን ጥያቄ ስለተቃወሙት ነበር ወደ ጦርነት የገቡት። ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ሽንፈት፣ የጀርመን የጣሊያንና የጃፓን መንግስት ወደ ሊብራል ዴሞክራሲ ተለወጠ። ጀርመን ከ 1958 ጀምሮ የአውሮፓ ህብረት አባል ነው ፣ እና ከተቀረው የምእራብ ጂኦግራፊያዊ ጎን ለጎን ፈጠራን ቀጥሏል። በሴፕቴምበር 1973 ምዕራብ ጀርመን የተባበሩት መንግስታት አባል ሆኑ። እ.ኤ.አ. በ 1991 የሶቪየት ኅብረት ውድቀትን ተከትሎ ፣ ጀርመን እንደገና ከተገናኘች በኋላ በአውሮፓ ህብረት እና በአውሮፓ አህጉር ውስጥ በጣም የበለፀገች ሀገር ሆናለች። ባህልና ጠቅላላ መረጃ ጀርመን አንድ ይፋዊ ቋንቋ ብቻ አለው እርሱም ጀርመንኛ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ብዙ ልዩ ልዩ የጀርመንኛ ቀበሌኞች በአገሩ ይገኛሉ። ለአንዳንድ ሰዎች ጀርመን «የገጣሚዎችና የአሳቢዎች አገር» በመባል ታውቋል። በዓመታት ላይ በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብ፣ በፍልስፍና፣ በሙዚቃ፣ በሲኒማ፣ እና በሳይንስ ዘርፎች በርካታ አስተዋጽኦች በማቅረባቸው ጀርመናውያን በዓለም ዝነኛነት አገኝተዋል፤ እንዲሁም መኪና የሚባለውን ፈጠራ በማስለማት ፈር ቀዳጅ ሆኑ። ጀርመን ደግም ስለ ቋሊማና ቢራዎች ልዩነት ብዛት የገነነ ሆኗል። እግር ኳስ በጀርመን ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የራይን ወንዝ አቅራቢያ በጥንት ከሁሉ በፊት የተሰፈረው ሲሆን እዚያ አንዳንድ ጥንታዊ የሮሜ መንግሥት ድልድይ፣ አምባ፣ ወይም ፍርስራሽ ሊታይ ይችላል። የጀርመን ሕዝብ በብዛት ክርስቲያኖች ናቸው፤ በስደትም ወደ አገራቸው ለደረሱት ሰዎች በጠቅላላው ሰላምታ ሰጪዎች ናቸው። የበርሊን ግድግዳ በፈረሰበትና «የቅዝቃዛ ጦርነት» በጨረሰበት ወቅት የጀርመን ዳግመኛ መወሐድ ተከሠተ። በዚያ ሰዓት የቀድሞ አገራት ምሥራቅ ጀርመንና ምዕራብ ጀርመን አብረው የአሁኑን ጀርመን መንግሥት ፈጠሩ። ብዙ የጀርመን ሰዎች በዓለም ዙሪያ ስመ ጥሩ ናቸው። ይህም ደራሲዎች ያኮብ ግሪምና ወንድሙ ቭልሄልም ግሪም፣ ባለቅኔው ዮሐን ቩልፍጋንግ ቮን ጌጠ፣ የፕሮቴስታንት ንቅናቄ መሪ ማርቲን ሉጠር፣ ፈላስፋዎች ካንት፣ ኒሺና ሄገል፣ ሳይንቲስቱ አልቤርት አይንስታይን፣ ፈጠራ አፍላቂዎች ዳይምለር፣ ዲዝልና ካርል ቤንዝ፣ የሙዚቃ ቃኚዎች ዮሐን ሴባስትያን ባክ፣ ሉድቪግ ቫን ቤትሆቨን፣ ብራምዝ፣ ስትራውስ፣ ቫግነርና ብዙ ሌሎች ይከትታል። እጅግ ቁም ነገር የሆነ ጠቃሚ ፈጠራ ማሳተሚያ፤ ዮሐንስ ጉተንቤርግ በሚባል ሰው በ1431 ዓ.ም. ተጀመረ። ስለዚህ ተጓዦች ከውጭ አገር ሲመልሱ በአውሮፓ ያለው ሰው ሁሉ እርግጡን በቶሎ ያውቀው ነበር። አሁን ጀርመን «ዶይቸ ቨለ» በሚባል ራዲዮን ጣቢያ ላይ ዜና በእንግሊዝኛ ያሠራጫል። የጀርመን ሕዝብ ባማካኝ ከአውሮፓ ሁሉ ቴሌቪዥንን የሚወድዱ ሲሆኑ ፺ ከመቶ ሰዎች ወይም ሳተላይት ወይም ገመድ ቴሌቪዥን አላቸው።
10102
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%88%E1%89%83%20%E1%8A%A0%E1%8B%AB%E1%88%8C%E1%8B%8D%20%E1%89%B3%E1%88%9D%E1%88%A9
አለቃ አያሌው ታምሩ
አለቃ አያሌው ታምሩ ከአባታቸው ከአቶ ታምሩ የተመኝና ከእናታቸው ከወይዘሮ አሞኘሽ አምባዬ፤ በጎጃም ክፍለ ሀገር በብቸና አውራጃ በእነማይ ወረዳ በታላቁ ደብር ወገዳም በደብረ ድማኅ ቅዱስ ጊዮርጊስ ልዩ ስሙ ቤተ ንጉሥ በተባለ ቦታ መጋቢት ፳፫ ቀን ፲፱፻፲፭ ዓመተ ምሕረት በዕለተ ሆሣዕና ተወለዱ። ዕድሜአቸው ለትምህርት ሳይደርስ ገና የሦስት ዓመት ተኩል ሕፃን ሳሉ በፈንጣጣ ሕመም ምክንያት የዐይናቸውን ብርሃን አጥተዋል። የስምንት ዓመት ዕድሜ ልጅ ሳሉ በዓለ ተክለ አልፋን ለማክበር ከአባታቸው ጋር ወደ ዲማ እንደ ሄዱ በዚያው ትምህርታቸውን ለመቀጠል ቀሩ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በቅርብ ቤተ ዘመድ እየተረዱ ለአንድ ዓመት ያህል ሲማሩ ከቈዩ በኋላ አባታቸው ስላረፉ ኑሮአቸው በትምህርት ቤት ብቻ ስለ ተወሰነ ከቤተ ሰብእ ጋር የነበራቸው ግንኙነት እየቀነሰ መጣ። ይህም ሁኔታ የሚፈልጉትን ትምህርት በአንድ ልብ ለመቀጠል ግድ ሆኖባቸዋል። በዚሁ መሠረት በ፲፭ ዓመት ዕድሜአቸው የቅኔ መምህር ለመሆን በቅተዋል። ስለ ዐይናቸው ብርሃንና ስለ ትምህርታቸው፤ «ምልጃ ዕርቅና ሰላም፤» በተባለው መጽሐፋቸው ገጽ ፬ ላይ እንዲህ ሲሉ ገለጸዋል። «ይህ ሁሉ የተገኘው ገና በልጅነት ዕድሜዬ፤ በቅዱስ ሐዋርያ ያዕቆብ እንደ ተነገረው የምመራበት፣ የምኖረበት በወሰድከው በዐይኔ ፈንታ ዕውቀት ስጠኝ ብዬ የለመንኩት አምላኬ፤ «ለምኑ ይሰጣችኋል፤ ሹ ታገኛላችሁ፤ በር ምቱ ይከፈትላችኋል፤ ለሚወደኝ እኔ ራሴን እገልጥለታለሁ፤» ሲል በሰጠው ተስፋና በለገሰኝ የአእምሮ ምጽዋት መሆኑን ስለምረዳ ነው፤» ብለዋል። ክቡር አለቃ አያሌው ታምሩ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት፥ ትምህርት፥ ሥርዐትና አስተዳደር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተለወጠና እየተበላሸ መሄዱ በእጅጉ ያሳዝናቸው ስለ ነበር፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሊቃውንት ጉባኤ ዋና ሰብሳቢ እንደ መሆናቸው መጠን፤ ጥፋቱ እንዲታረም ብዙ አቤቱታና ተማጽኖ ጉዳዩ ወደሚመለከተው ወደ ቤተ ክርስቲያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስ፤ ሲኖዶሱን በመሠረተና በሚመራው በመንፈስ ቅዱስ ስም ተማጽነው ቢያቀርቡም ሲኖዶሱ ጉዳዩን ለማፈን ከመሞከር በስተቀር ምንም እርምጃ ሳይወስድ ቀርቷል። እሳቸውም ያቀረቡት ጥያቄ መፍትሔ ባለማግኘቱ ጉዳዩን ለሚመለከተው ለኢተዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን ለማሳወቅና፤ በቤተ ክርስቲያን ላይ ዐመፅ የሚፈጽሙትን ፓትርያርኩንና የእሳቸው ተባባሪ የሆኑ ጳጳሳትን ባላቸው ከፍተኛ ኀላፊነተና ሥልጣነ ክህነት በሥልጣነ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፥ በሥልጣነ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ለማውገዝ ተገደዋል። ከዚህም በተጨማሪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ የዐመፀኛውን ፓትርያርክ ስም እንዳይጠሩ ውግዘት አስተላልፈዋል። ምእመናንም ከዐመፀኞች ካህናት ምንም ዐይነት አገልገሎት ማገኘት የማይችሉ መሆናቸውን ተገንዝበው ሕይወታቸውን በጥንቃቄ እንዲመሩ አሳስበዋል። በዚህም ምክንያት ከ፶ ዓመት በላይ ካገለገሉበት የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በሐሰት ክስና የእምነት ክሕደት ቃላቸውን ባልሰጡበት ሁኔታ ያለ ምንም ጡረታ ከሥራ ገበታቸው ላይ በግፍ እንዲነሡ በመደረጉ ከሚያዝያ ወር ፲፱፻፹፰ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ እስከ ዕለተ ዕረፍታቸው በመኖሪያ ቤታቸው ተወስነው ኖረዋል። በነዚህ ዓመታትም በየዕለቱ ለጸሎት ባዘጋጇት አነስተኛ ክፍል በመገኘት ወደ ልዑል እግዚአብሔር በመጸለይና በማልቀስ ይተጉ ነበር። ምእመናንም በተኲላ እንዳይነጠቁ በተለያዩ ጋዜጦች ትምህርትና ማበረታቻ ሲሰጡ ኖረዋል። የክቡር አለቃ አያሌው ታምሩ የቀብር ሥነ ሥርዐት ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፱፻፺፱ ዓመተ ምሕረት ብዙ ዘመን ባገለገሉበት የአዲስ አበባው ደብረ አሚን ተክለ ኃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ብዙ ሕዝብ በተገኘበት ተፈጽሟል። ክቡር አለቃ አያሌው ታምሩ በቤተ ክርስቲያን ሥርዐት መሠረት በሥርዐተ ተክሊል ከወይዘሮ ርብቃ ልሳነ ወርቅ ጋር ሚያዝያ ፲፪ ቀን ፲፱፻፶ ዓመተ ምሕረት ጋብቻ ፈጽመው ፲፬ ልጆችና ፲፪ የልጅ ልጆች ለማፍራት ታድለዋል። መንፈሳዊ አገልግሎትና አስተዳደር። ወደ አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ዛሬ የክቡር ዐፅማቸው ማረፊያ በሆነው ደብረ አሚን ተክለ ኃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የቅኔ መምህርነት አገልግሎታቸውን በ፲፱፻፴፱ ዓመተ ምሕረት ጀመሩ። በመቀጠልም በዚሁ ደብር፤ መጀመሪያ የሊቀ ጠበብትነት ማዕረግ አግኝተው ያገለገሉ ሲሆን ኋላም የዚሁ ደብር አስተዳዳሪ በመሆን ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሊቃውንት ጉባኤ ተመርጠው ከሰኔ ወር ፲፱፻፵፰ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ የስብከተ ወንጌል ክፍል አባል ሆነው አገልግለዋል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ አባልና ዋና ሰብሳቢ ሆነው ሠርተዋል። በዚህም የሥራ ዘመናቸው፤ የቤተ ክርስቲያን የወንጌል ትምህርት በመሆኑ ይህ አገልግሎት ሳይበረዝና ሳይከለስ እምነቱም፣ ትምህርቱም፣ ሥርዐቱም ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ የሚያስችለውን መንገድ ለመቀየስ በተሰጣቸው ኀላፊነት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ሌት ተቀን ሠርተዋል። አልፎ አልፎም ከውስጥም ሆነ ከውጪ ለሚነሡት መናፍቃን መልስ በመስጠት፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ በየጊዜው የሚታተሙትን መጻሕፍት በማረምና ለኅትመት እንዲበቁ በማድረግ፤ ስለ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ስለ ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ለሚጠየቁ ጥያቄዎች መልስ በመስጠት፤ በበዓላትም ሆነ በሌሎች አጋጣሚዎች በራዲዮ፥ በቴሌቪዥን፥ በመጽሔቶችና በጋዜጦች ትምህርትና ምክር በማስተላለፍ ሀገራዊና ሃይማኖታዊ ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል። ሐዲስ ኪዳንን በግእዝና በአማርኛ ፥ መጽሐፈ ግጻዌ፥ ሃይማኖተ አበው የተባሉትን መጻሕፍት ከሌሎች የጉባኤው አባላት ጋር ተርጉመው እንዲታተሙ አድርገዋል። በቀዳማዊ ኀይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መንፈሳዊ ኰሌጅ ከ፲፱፻፶፬ እስከ ፲፱፻፷፬ ዓመተ ምሕረት፤ እንዲሁም በተግባረ እድ ትምህርት ቤትና በቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት መንፈሳዊ ትምህርት አስተምረዋል። ከኢትዮጵያ ዓይነ ሥውራን ማኅበር መሥራቾች አንዱ ሲሆኑ፤ መጀመሪያ የማኅበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት ኋላም የቦርድ ሊቀ መንበር በመሆን አገልግለዋል። የአለቃ አያሌው መጻሕፍት በመጽሐፍ ጥራዝ አዘጋጅተውና አሳትመው ለትውልድ ያስተላለፏቸው መጻሕፍት ዘጠኝ ሲሆኑ በይዘታቸው በሁለት የተከፈሉ ናቸው። በአንደኛው ክፍል ያሉት የቤተ ክርስቲያንንና የኢተዮጵያን ማንነት ለኢትዮጵያውያን ለማስተማር የተዘጋጁ ሲሆኑ፤ በሁለተኛው ክፍል ያሉት ደግሞ ከቤተ ክርስቲያን ውስጥም ሆነ ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ለተነሡና ለሚነሡ መናፍቃን መልስ በመስጠት የምእመናንን ልቦና ለማጽናት የሚያስችል መልእክት የሚያስተላልፉ ናቸው። ከነዚህ መጻሕፍት ውስጥ ዐምስቱ በቤተ ክህነት አገልገሎት ላይ የተዘጋጁ ሲሆኑ፤ አራቱ ደግሞ ከቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በግፍ ከታገዱበት ከ፲፱፻፹፰ ዓመተ ምሕረት በኋላ የተዘጋጁ ናቸው። በቤተ ክህነት አገልገሎት ላይ በነበሩበት ጊዜ ያዘጋጇቸው፤ «መች ተለመደና ከተኲላ ዝምድና»፥ «የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ሕግጋት»፥ «የኑሮ መሠረት ለሕፃናት»፥ «ወላዲተ አምላክ በኢትዮጵያ»፥ «የጽድቅ በር» የተባሉት መጻሕፍት ሲሆኑ፣ ከሥራ ገበታ ከታገዱ በኋላ በመኖሪያ ቤታቸው ሆነው ያዘጋጇቸው፤ «ምልጃ፥ ዕርቅና ሰላም»፥ «ተአምርና መጽሐፍ ቅዱስ»፥ «መልእክተ መንፈስ ቅዱስ»፥ «ዜና ሕይወት ዘቅድስተ ቅዱሳን እመ አምላክ» የተባሉት ናቸው። እባካችሁ "የኢትዮጵያ እምነት በሶስቱ ሕግጋት" የሚለውን መጽሐፍ ጫኑልን የኢትዮጵያ እምነት በሶስቱ ሕግጋት የኢትዮጵያ ሰዎች
14117
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%88%E1%88%8D%E1%8B%B0%20%E1%8C%8A%E1%8B%AE%E1%88%AD%E1%8C%8A%E1%88%B5%20%E1%8B%88%E1%88%8D%E1%8B%B0%20%E1%8B%AE%E1%88%90%E1%8A%95%E1%88%B5
ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ
ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ (፲፰፻፺፫ ዓ/ም - ፲፱፻፷፰ ዓ/ም) በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት በተላለያዩ ጊዜያት የፅሕፈት፤ የእርሻ፤ የአገር ግዛት እና ገንዘብ ሚኒስቴር እንዲሁም የጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ በመሆን አገልግለዋል። በትውልድ አገራቸው ቡልጋ ቤተ ክርስቲያን ያሠሩ ትልቅ ሁለ ገብ ሰው ነበሩ። ወደፊት የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት የሚደመድመው የስድሳ ስድስቱ አብዮት በተፋፋመበት ወቅት፣ እኚህ ሰው ለሕክምና ወደ ሎንዶን መጥተው ሲታከሙ ቆይተው ሐምሌ ፳ ቀን ፲፺፻፷፰ ዓ/ም እዚያው አርፈው ኬንሳል ግሪን (እንግሊዝኛ፦ ) በሚባል የመቃብር ሥፍራ ተቀበሩ። የወጣትነት ዘመናት ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ በሞረትና ጅሩ ወረዳ ጎበላ ሚካኤል በሚባል ስፍራ ከተወለዱት ከአባታቸው አቶ ወልደዮሐንስ ናዳቸው እና ከመንዝ ተወላጅዋ እናታቸው ወይዘሮ ወደርየለሽ ወልደገብሬል፣ አዲስ አበባ 'አባታችን ሠፈር'፣ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ በ፲፰፻፺፫ ዓ/ም ተወለዱ። በዘመኑ ስርዓት የግዕዝ እና አማርኛ ትምህርታቸውን በቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ በሚገኘው ትምህርት ቤት የአማርኛን ጽሕፈትና ንባብ አጠናቀቁ። ከዚያ ቀጥሎ መቼ፣ እንዴትና ለምን ለሚሉት ጥያቄዎች መረጃ ባይገኝም ሆኔም ቀሬ በንግሥተ ነገሥት ዘውዲቱ ዘመን መሆኑ ነው፣ አዲስ አበባ በዳግማዊ ምኒልክ ትምሕርት ቤት ፈረንሳይኛ ቋንቋ አጥንተዋል። በዚህም የቋንቋ ዕውቀት በአስተርጓሚነት ሲያገለግሉ ቆይተው ኢትዮጵያ የዓለም መንግሥታት ማኅበር አባል ስትሆን በ ፲፱፻፲፰ ዓ/ም ወደ ማኅበሩ ፅሕፈት ቤት ዠኔቭ ይላካሉ። ከዠኔቭ ሲመለሱ፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የ ጣልያን፣ ቤልጅግ እና ጀርመን ክፍል ኃላፊ ሆነው ሲሠሩ ከቆዩ በኋላ በ፲፱፻፳፫ ዓ/ም በዚያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዲሬክቶርነት ማዕርግ ለሦስት ዓመት አገልግለዋል። በ፲፱፻፳፮ ዓ/ም በፅሕፈት ሚኒስቴር ጠቅላይ ዲረክቶር ተብለው ለጥቀውም የንጉሠ ነገሥቱ የግል ፀሐፊ ሆነው እስከ ጠላት ወረራ ድረስ ሲያገለግሉ ቆዩ። ከንጉሠ ነገሥቱም ጋር የቅርብ ግንኙነታቸውና ወደፊት የሚይዙትም የ’ፈላጭ ቆራጭነት’ ሥልጣን የተመሠረተው በዚህ ጊዜ እንደሆነ ይገመታል። የጠላት ወረራና ያስከተለው ስደት የንጉሠ ነገሥቱ የግል ፀሐፊ አቶ ወልደ ጊዮርጊስ ፋሽሽት ኢጣልያ አገራችንን በወረረ ጊዜ ክንጉሠ ነገሥቱ ሳይለዩ፣ በማይጨው ዘመቻ ከአዲስ አበባ ወደደሴ አብረው ኅዳር ፲፰ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም ይጓዛሉ ። በኋላም ግንቦት ወር ፲፱፻፳፰ ዓ/ም በጂቡቲ እና በኢየሩሳሌም በኩል አድርገው ከሐይፋ ወደብ እስከ ጅብራልታር በእንግሊዝ የጦር መርከብ፣ ከጅብራልታር እስከ "ሳውዝሃምፕቶን" (እንግሊዝኛ ) የእንግሊዝ ወደብ በመንገደኛ መርከብ ተጉዘው የአምስት ዓመት የስደታቸውን ዘመን አብረው ተሳትፈዋል። በስደት ዘመን ንጉሠ ነገሥቱ ከቤተሰባቸው ጋር በባዝ ከተማ “ፌየርፊልድ ሃውስ” (እንግሊዝኛ )የስደት ዘመን እንዳሳለፉ ብዙ ተጽፏል። ከቤተ ሰቡም ጋር አብረው የነበሩ (ሠራተኞች፣ አገልጋዮች፣ መነኮሳት) ሌሎች ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደነበሩ ‘ሉትዝ ሄበር’ () “ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በባዝ ከ 1928 – 1932 ዓ.ም” በሚል ጽሑፉ በሰፊው አስፍሮታል። በዚያ የስደት ዘመን ግን ፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ የት እንደኖሩ መረጃ ማግኘት ባይቻልም የንጉሠ ነገሥቱ የግል ጸሐፊ ስለነበሩ እምብዛም እንድማይርቋቸው ይገመታል። ሆኔም ቀሬ በታኅሣሥ ፲፱፻፳፱ ዓ/ም የፈረንጆች ገና ዕለት ንጉሠ ነገሥቱ በቢቢሲ ራዲዮ ለአሜሪካውያን ደጋፊዎቻቸው መልዕክት ሲያስተላልፉ፣ በስደት የዲፕሎማሲ ትግል ሲያካሂዱና ከዓለም መንግሥታት ማኅበር ጋር ‘የአእምሯዊ ግብግብ’ በገጠሙበት ጊዜ አጠገባቸው ሆነው ከሚያማክሯቸው ሰዎች አንዱ አቶ ወልደ ጊዮርጊስ እንደነበሩ ንጉሥ ነገሥቱ “ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ - ፪ኛ መጽሐፍ” ላይ ጠቅሰውታል። ከድል እስከ ግዞት «የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሥልጣን በግዛቱ ውስጥ ያልተወሰነ ነው። ሥልጣኑ ሃይማኖታዊም ሆነ ሥጋዊ ጉዳዮችን ያጠቃልላል። በሥልጣኑ ይሾማል፣ ይሽራል መውሰድም፣ መስጠትም፤ ማሰርም፣ መፍታትም፤ መግደልም፣ መስቀልም ይችላል። ትንሹም ትልቁም ንጉሠ ነገሥቱ የእግዚአብሔር ተወካይ ነው ብሎ ስለሚያምን የእርሱን ትዕዛዝ ያለአንዳችም ሰበብ ወይም ማመካኘት በደስታ ይቀበላል።» “ዝክረ ነገር” ከ ብላቴን ጌታ ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል «በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የአስተዳደር ስልት፤ ለሥልጣን የብቃተ ቢስነት ወንጀል ወይም የማይካድ የሙስና ድርጊት ሲታይ የተለመደው ቅጣት ወደሌላ ሥራ መዛወር ሲሆን፤ ለንጉሠ ነገሥቱ ታማኝ አለመሆን ግን ያለምንም ጥርጣሬ በፈጣን ፍርድ በግዞት ዓለም መጥፋትን ያስከትላል።» ጆን ማርካኪስ ()፣ “ኢትዮጵያ፥ የባህላዊ ሽከታ ሥነ አካል” ()። እዚህ አስተያየት ላይ ደግሞ ‘የንጉሠ ነገሥቱን ስም እና ተወዳጅነት የሚሻማ/የሚያሳማ ዝናም ያተረፈ ‘ባለ ሥልጣን’ የሚጠብቀው እንዲሁ ተመሳሳይ ቅጣት ነበር’ ብንል ከእውነቱ አንርቅም። ስለፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ እምብዛም የተጻፈ ባይኖርም ያሉት ቅንጥብጣቢዎች ከሞላ ጎደል የሚያሳዩን በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ከላይ የሠፈሩትን ሁለቱንም ገጽታዎች መጀመሪያ በ”እንደራሴ” መልክ የተጠቀሙበትና በመጨረሻውም የግዞት ዓለምን የቀመሱባቸው ገጽታዎች መሆናቸውን ነው። ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር አብረው በስደት በነበሩባቸው ዘመናት በታማኝነታቸው የንጉሠ ነገሥቱን እምነት አስገኘላቸው። የግል ጸሐፊነታቸው በኋላም የጽሕፈት ሚኒስቴርነታቸው ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ከማንም የላቀ አቀራረብ (ስለዚህም ተሰሚነትን) ስለሰጣቸው እንዲሁም የራሳቸው የዱኛ ችሎታ ከንጉሠ ነገሥቱ ቀጥሎ ሌላ ማንም ያልነበረውን የሥልጣን መብት ሰጥቷቸዋል። (ባህሩ ዘውዴ - የዘመናዊ ኢትዮጵያ ታሪክ ከ 1847 እስከ 1983) ከስደት ሲመለሱ ‘ፀሐፌ ትዕዛዝ’ ተብለው የጽሕፈት ሚንስቴር ሆነው ይሾማሉ። በተለምዶው ስርዓት የጽሕፈት ሚኒስቴሩ የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥታዊ መዝገቦች ጸሐፊ እና ጠባቂ ሲሆን፣ ዐዋጆች፤ ትዕዛዛት እና መንግሥታዊ ሰነዶችም በዚሁ ሰው በኩል ያልፋሉ። ይሄ ማለት ደግሞ ከላይ እንደሠፈረው፣ ብላቴን ጌታ ማኅተመ ሥላሴ ወልደመስቀል በ”ዝክረ ነገር” ላይ “ትንሹም ትልቁም ንጉሠ ነገሥቱ የእግዚአብሔር ተወካይ ነው ብሎ ስለሚያምን የእርሱን (የንጉሠ ነገሥቱን) ትዕዛዝ ያለአንዳችም ሰበብ ወይም ማመካኘት በደስታ ይቀበላል።>> ብለው ያስረዱንን ስርዓት ለዚህ ማዕርግ የበቃ ሰው የቱን ያህል ሥልጣን እንደነበረውና ዝንባሌው የራሱን ሥልጣን የማዳበርም ከሆነ ይሀንን ዓይነት መሠረት ይዞ የዝንባሌውን ዓላማ ስኬታማ ማድረግ እንዴት ቀላል እንደሆነ ይገነዘቧል። በ፲፱፻፴፭ ዓ/ም ፣ ድል በተገኘ በሁለት ዓመቱ፣ ንጉሠ ነገሥቱ “የመንግሥታችንን ሚኒስቴሮች ሥልጣንና ግዴታዎች ለማብራራት” በሚል ዐዋጅ በራሳቸው ሰብሳቢነት የሚመራ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት እና “ቃለ መሐላ” የሰጡ ሚኒስቴሮች መሾማቸውን ሲይስታውቁ የምክር ቤቱ ጽሕፈት ቤት በፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ እንደሚመራና ምክር ቤቱም በኒሁ ሰው ‘ቁጥጥር’ ስር እንደሚሆን ታወጀ። እኒህ ሚኒስቴር በንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ውስጥ “ከማናቸውም ባለሥልጣን ጋር በቀጥታ የመገናኘት ሥልጣን” እንደተሰጣቸው ዐዋጁ ለጥቆ አስታወቀ። እንግዲህ በዚህ አዋጅ መሠረት ፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ በንጉሠ ነገሥቱ ፍላጎት እና ዐዋጅ የዘውዱን የበላይነት ለማስከበር ሙሉ ሥልጣን ‘እንደራሴ’ መሆናቸው ተረጋግጧል። በሌላ መልክ ሲተረጎም፤ ፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ በንጉሠ ነገሥቱ እውቀትም ይሁን ፍላጎት ‘በማስመሰል’ም ይሁን በትክክል የንጉሠ ነገሥት መንግሥቱን ዓላማ በማራመድ ኢትዮጵያን ለማልማት፤ በዘመናዊ መንገድ ለመምራት፤ ‘ለመፍለጥ ለመቁረጥ’፤ የራሳቸውን ባለሟሎች እና ወገኖች በማንኛውም ረገድ ለማዳበር፤ የራሳቸውን የሥልጣን መሠረት ለማስፋፍትም ሆነ የዘውድ ስርዓቱን ዘላለማዊ ለማድረግ ልዩና ቁልፋዊ ቦታ እንደነበራቸው እንገነዘባለን። ምስጢራዊና የሥልጣን አያያዝ፣ አጠቃቀም እና ‘ከመለኮት የተሠጠ’ መብታቸውን ከማንም ጋር መሻማት የማይፈልጉትስ ንጉሠ ነገሥት እንደዚህ ዓይነት ዐዋጅ ሲያስተላልፉ፣ ምን አስበው ኖሯል? በጊዜው አገራችንን ከፋሽሽት ጣልያን ለማላቀቅ አባቶቻችን እና እናቶቻችን የሚያደርጉትን ተጋድሎ ለመደገፍ ገብተው የነበሩት እንግሊዞች፤ ከድል በኋላ ኢትዮጵያን ቢያንስ በሥራቸው እንደቅኝ ግዛት ለማስተዳደር፤ ይሄ ባይሳካላቸው ደግሞ ሕዝቦቿንና ግዛቷን ከፋፍለው ለመበተን የሚጥሩበት ጊዜ ነበር። ታዲያ ለንጉሠ ነገሥቱ የዚህ አዋጅ መነሻ ምናልባት እንግሊዞች በዓላማቸው የቀናቸው እንደሆነ የሚያሳብቡበት () የዋህ ሰው ማዘጋጀታቸው ኖሯል? የፀሐፌ ትእዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ አነሳስ፣ እድገት፣ ይሄን ያህልም ሥልጣን እስከመያዝ መብቃትና በመጨረሻውም ውስጡ ከተበላ በኋላ እንደሚወረወር የሙዝ ልጣጭ መደረግ ብዙ ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በአንባቢ እና የኢትዮጵያን የቅርብ ታሪክ በሚያጠና ሰው ጭንቅላት ላይ ያስነሳሉ። በሥልጣን ዘመን በ፲፱፻፴፬ - ፴፭ ዓ/ም የ”አንግሎ-ኢትዮጵያ ስምምነት” (እንግሊዝኛ 1941-42) ድርድር ወሳኝና ቁልፍ የሆነ ሚና ተጫውተዋል። በተለይም በጊዜው ኦጋዴንን በእንግሊዝ መንግሥት ሥር ለማስተዳደር የሚካሄደውን ሴራ በመቃወም ያደረጉት ትግል በአንዳንድ የብሪታንያ ባለ ሥልጣናት አመለካከት እሳቸውን ያለአግባብ ‘ጸረ-ብሪታንያ’ እንዳስባላቸው ትልቁ የኢትዮጵያ ታሪክ ምሑር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ገልጾታል። ይሄንን በተመለከተ እሳቸው “እኔ ለኢትዮጵያ የቆምኩ እንጂ ጸረ ማንም አይደለሁም።” ብለዋል። በ ፲፱፻፴፭ ዓ/ም የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት በአውራጃዎቹና በጠቅላይ ግዛቶቹ ላይ ‘ለማጠንከር’ በወሰዱት እርምጃ የአገር ግዛት ሚኒስቴርነትን ሥልጣን ከጽሕፈት ሚኒስቴር ጋር በመለጠቅ ያዙ። ይሔ ሚኒስቴር በአገሪቱ አጠቃላይ የጸጥታን ጉዳይ የሚቆጣጠርም ስለነበር ፀሐፌ ትዕዛዝን የበለጠ አስከባሪና ተፈሪነትን አስገኝቶላቸዋል። ሆኖም የአገር ግዛት ሚኒስቴርን በ፲፱፻፵፩ ዓ/ም ለቀው የፍትሕ ሚኒስቴርነትን ያዙ። የራሳቸውን ባለሟሎችም በየሚኒስትሩና በየ መንግሥት መሥሪያ ቦታዎች አሠማሩ። የ ፲፱፻፵፰ ዓመተ ምሕረቱን የሕገ መንግሥት ረቂቅ ከሦስት አሜሪካውያን እና ከጊዜው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ ጋር አዘጋጅተዋል። በንጉሠ ነገሥቱ የሳቸው ልዩ እና አቻ የሌለው ተሰሚነት እንዲሁም የያዙት ቆራጣዊ ሥልጣን የሚያስፈራቸውና የሚያሳስባቸው መሳፍንት፣ መኳንንትና ባለ ሥልጣኖች ቁጥር እያደር እይጨመረ መምጣቱ አልቀረም። ለጊዜው በንጉሠ ነገሥቱ አመለካከት (እንደዚህ የተጠላ ባለ ሥልጣን በንጉሠ ነገሥቱ ላይ ለማመጽ አይፈልግም እንዲያውም ጥላቻን ከንጉሠ ነገሥቱ ላይ ይመክታል) እና ግምገማ የዚህ ዓይነት ጥላቻ ፀሐፌ ትዕዛዝን እስከነአካቴው ጠቀመቸው እንጂ አልጎዳቸውም። ሆኖም የውጭ ጋዜጠኖች ፀሐፌ ትዕዛዝን ‘የኢትዮጵያ አምባ ገነን’ ሲሉ ማንሳታቸው ለንጉሠ ነገሥቱ የሳቸው የዝና ተወዳዳሪ ሆኖ መታየት የፀሐፌ ትዕዛዝን ውድቀት ካስጀመሩት ምክንያቶች አንዱ ነው ተብሉ ይገመታል። ሌላው ደግሞ ምክንያት የኤርትራን እና የኢትዮጵያን ‘ማኅበራዊ’ መንግሥት ይመለከታል። አምባሳዶር ዘውዴ ረታ፣ “የኤርትራ ጉዳይ” በተባለው መጽሐፋቸው እንደገለጹልን በመጋቢት ወር ፲፱፻፵፩ ዓ/ም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤርትራን በተመለከተ ጉዳይ ክርክር ሲደረግ የእንግሊዙ ልዑክ ያቀረበውን የመከፋፈል ኃሳብ በመቃወም የጊዜው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ መልስ ሲሰጡ ይሄንን በመቃወም ስለተናገሩት ንግግርና የእንግሊዝን መንግሥት ‘አስቀይመው’ ከሆነ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ምን ዓይነት እርምጃ መውሰድ እንዳለበት ለመምከር ንጉሠ ነገሥቱ በሰበሰቡት ጉባዔ ላይ በጊዜው የግል ጸሐፊያቸው የነበሩት እና ዬንግሊዝ ደጋፊ የሚባሉት አቶ (በኋላ ፀሐፌ ትዕዛዝ) ተፈራ ወርቅ ኪዳነ ወልድ አክሊሉ ለብሪታንያ መንግሥት ልዑክ ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ደጋፊ ፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ደግሞ የአክሊሉ እርምጃ ትክክል መሆኑን እና ምንም ዓይነት ይቅርታ መደረግ እንደሌለበት ተከራከሩ። በዚሁ መጽሐፍ ላይ ኤርትራና ኢትዮጵያ በ’ኅብረት መንግሥት’ አስተዳደር () በተዋሃዱ ዓመት ባልሞላው ጊዜ በተነሳው የ’ኅብረት መንግሥት’ አለማስፈለግ ጉዳይ በ መስከረም ወር ፲፱፻፵፯ ዓ/ም በተደረገው የንጉሠ ነገሥቱ ውስጣዊ ጉባዔ ላይ ልዑል ራስ ካሳ በአንድ አገር ውስጥ ሁለት ዓይነት አመራር ሊኖር ስለማይችል በአንድ ሕጋዊ አስተዳደር ሁሉንም የኢትዮጵያ አካላት ማስተዳደር እንደሚያስፈልግ ሲያስረዱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ አክሊሉ ሀብተ ወልድ ደግሞ ኢትዮጵያ ወዳም ሆነ ጠልታ ይሄንን ዓይነት አስተዳደር በሕግ የተቀበለችው ስለሆነ ይሄንን በጥንቃቄ መተግበር ግዴታዋ እንደሆነና ኅብረታዊ መንግሥቱን መለወጥ ካስፈለገም ሕጋዊ በሆነ እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ታዛቢዎች የሚመሰከር የ’ውሳኔ ሕዝብ’ ድምጽ መሆን እንዳለበት ሲያስገነዝቡ፣ ፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ አክሊሉን በመደገፍ ‘ ኢትዮጵያ የኅብረታዊ መንግሥትን ለመደምሰስ እንዳልተዘጋጀችና እርምጃው የሚያስከትላቸውንም ክስተቶች በቅጡ ለማጥናት ጊዜ ያስፈልጋል።’ ብለው ካስረዱ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ይሄንን ግምገማ እሳቸው ያስጀመሩት እና የሚገፋፉት ጉዳይ ነው በሚል ተርጉመው ፀሐፌ ትዕዛዙን በመቆጣት ‘’ለ እንደራሴያችን ራስ አንዳርጌ ወይም ለምክትሉ ደጃዝማች አስፍሃ የኅብረት መንግሥቱን መውደቅ የሚያፋጥን ምንም ዓይነት ትዕዛዝ እንዳልሰጠን ከሁሉ የበለጠ አንተ ታውቃለህ።” በማለት ገሰጿቸው ይሉናል። እንግዲህ ባንድ በኩል ፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ ከንጉሠ ነገሥቱ በዐዋጅ በተሰጣቸው ሙሉ ሥልጣን ብዙ የሚፈሯቸውና የተከፉ መሳፍንት፣ መኳንንትና ባለሥልጣናት እንደጠሏቸውና የሳቸውን ከሥልጣን መውረድ በጉጉት ይጠባበቁ እንደነበር ተመልክተናል። ቀጥሎም የንጉሠ ነገሥቱ የግል ፀሐፊ (ማለትም ለንጉሠ ነገሥቱ ቅርብነትና ተሰሚነትን እያገኙ የመጡት) እንዲሁም የ’እንግሊዝ ደጋፊ’ ይባሉ የነበሩት ፀሐፌ ትዕዛዝ ተፈራ ወርቅ ኪዳነ ወልድ ከወልደ ጊዮርጊስ ጋር ያደርጉትን ሙግት ተመልክተን ምናልባት የጽሕፈት ሚኒስቴሩ ዘላቂና ኃይለኛ ባላጋራ አጋጥሟቸው ይሆን ለማለት እንችላለን። በሦስተና ደረጃ የኤርትራን የኅብረት መንግሥት በተመለከት የንጉሠ ነገሥቱ ተግሳጽ በሌሎች (ተቃዋሚዎቻቸው) ፊት ሲደርሳቸው ጆን ማርካኪስ “በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የአስተዳደር ስልት፤ ለሥልጣን የብቃተ ቢስነት ወንጀል ወይም የማይካድ የሙስና ድርጊት ሲታይ የተለመደው ቅጣት ወደሌላ ሥራ መዛወር ሲሆን፤ ለንጉሠ ነገሥቱ ታማኝ አለመሆን ግን ያለምንም ጥርጣሬ በፈጣን ፍርድ በግዞት ዓለም መጥፋትን ያስከትላል።” ያለን በፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ላይ እየተተገበረ መሆኑን እንገነዘባለን። ወዲያውኑ ፀሐፌ ትዕዛዝ ከጽሕፈት ሚኒስቴርነታቸው ተሽረው መጀመሪያ የአሩሲ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ ሆነው እስከ ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ከቆዩ በኋላ ወደ ገሙ ጎፋ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳድሪ ሆነው ተዛወሩ። የስድሳ ስድስቱ አብዮት ኃይለ ሥላሴን ከሥልጣን ከማውርዱ ከጥቂት ጊዜ ቀደም ብሎ ለሕክምና ወደ እንግሊዝ አገር ይሄዱና ሁለተኛውንና የመጨረሻውን የስደት ዘመን ጀምረው በተወለዱ በሰባ አምስት ዓመታቸው እዚያው እንግሊዝ አገር አርፈው ተቀበሩ። ፀሐፊ ትዕዛዝ ወልደጊዮርጊስ በአባታቸው የትውልድ አገር በቡልጋ ውስጥ የቅድስጌ ማርያምን ቤተ ክርስቲያን በግል አሠርተዋል። ዋቢ ምንጮች ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ፣ አንደኛ መጽሐፍ ዓ/ም የኢትዮጵያ ካቢኔ አባላት
48361
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%98%E1%88%98%E1%8A%90%20%E1%88%85%E1%8B%B3%E1%88%B4
ዘመነ ህዳሴ
ዘመነ ህዳሴ ( ረኔሳንስ ) በተለይ በአውሮፓ ታሪክ እንደሚወሰን ከ1445 እስከ 1640 ዓም ድረስ ያህል ያለው ጊዜ ነው። በተለይ በዚህ ዘመን የተከሠተው የሥነ ጥበብ ተሃድሶ ማለት ነው። ይህም ቁስጥንጥንያ ለኦቶማን ቱርኮች ከወደቀበት ዓመት ከ1445 ዓም ጀምሮ አካባቢ ይቆጠራል። በዚያን ጊዜ ቢዛንታይን መንግሥት ስለ ወደቀ የአውሮፓ ሥነ ጥበብ ማዕከል ወደ ጣልያን ሊዛወር ጀመረ። ከዚህም በኋላ የሥነ ጥበብ «ዘመነ ህዳሴ» ከጣልያን ወደ ሌሎቹ አውሮፓ አገራት ይስፋፋ ነበር። «የፕሮቴስታንት ተሃድሶ» ንቅናቄ () ደግሞ በዚህ ዘመን ያህል ውስጥ (ከ1509 እስከ 1640 ዓም ድረስ) ተከሠተ። በአውሮፓ ታሪክ ውስጥ ከመካከለኛው ዘመን ወደ ዘመናዊነት የተሸጋገረበት እና የ 15 ኛውን እና 16 ኛውን ክፍለ ዘመን የሚሸፍንበት ወቅት ነው ፣ እሱም የጥንታዊ ጥንታዊ ሀሳቦችን እና ግኝቶችን ለማነቃቃትና ለመብለጥ በሚደረገው ጥረት ይታወቃል። የተከሰተው ከመካከለኛው ዘመን መጨረሻ ቀውስ በኋላ እና ከትልቅ ማህበራዊ ለውጥ ጋር የተያያዘ ነው. ከመደበኛው ወቅታዊነት በተጨማሪ የ"ረዥም ህዳሴ" ደጋፊዎች በ 14 ኛው ክፍለ ዘመን እና መጨረሻውን በ 17 ኛው ክፍለ ዘመን ያስቀመጡት ይሆናል. ባህላዊው አመለካከት በይበልጥ የሚያተኩረው በህዳሴው ቀደምት ዘመናዊ ገፅታዎች ላይ ነው እና ካለፈው ጊዜ የራቀ ነው በማለት ይከራከራሉ፣ ነገር ግን ዛሬ ብዙ የታሪክ ተመራማሪዎች በመካከለኛው ዘመን ገፅታው ላይ ያተኩራሉ እና የመካከለኛው ዘመን ማራዘሚያ ነበር ብለው ይከራከራሉ። ሆኖም የዘመኑ ጅምር - የ15ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ህዳሴ እና የጣሊያን ፕሮቶ-ህዳሴ ከ1250 ወይም 1300 አካባቢ - ከኋለኛው መካከለኛው ዘመን፣ በተለምዶ እስከ ሲ. 1250-1500፣ እና የመካከለኛው ዘመን እራሳቸው እንደ ዘመናዊው ዘመን ባሉ ቀስ በቀስ ለውጦች የተሞላ ረጅም ጊዜ ነበሩ። እና በሁለቱም መካከል እንደ መሸጋገሪያ ጊዜ፣ ህዳሴ ከሁለቱም ጋር ተመሳሳይነት አለው፣ በተለይም የሁለቱም የመጨረሻ እና የመጀመሪያ ንዑስ ወቅቶች። የህዳሴው ምሁራዊ መሰረት ከሮማን ሰብአዊታስ ጽንሰ-ሀሳብ የተገኘ እና "ሰው የሁሉም ነገር መለኪያ ነው" ከሚለው እንደ ፕሮታጎራስ ያለ የጥንታዊ የግሪክ ፍልስፍና እንደገና የተገኘ የሰብአዊነት ስሪት ነው። ይህ አዲስ አስተሳሰብ በኪነጥበብ፣ በሥነ ሕንፃ፣ በፖለቲካ፣ በሳይንስ እና በሥነ ጽሑፍ ውስጥ ተገለጠ። ቀደምት ምሳሌዎች በዘይት ሥዕል ላይ የአመለካከት እድገት እና ኮንክሪት እንዴት መሥራት እንደሚቻል እንደገና መታደስ ናቸው። ምንም እንኳን የብረት ተንቀሳቃሽ ዓይነት መፈልሰፍ ከ 15 ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ ሀሳቦችን ለማሰራጨት ቢያፋጥንም ፣ የሕዳሴው ለውጦች በመላው አውሮፓ አንድ ወጥ አልነበሩም ። የመጀመሪያዎቹ ምልክቶች በጣሊያን በ 13 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ታይተዋል ፣ በተለይም በዳንቴ ጽሑፎች። እና የጊዮቶ ሥዕሎች። እንደ ባህላዊ እንቅስቃሴ ፣ ህዳሴው የላቲን እና የቋንቋ ሥነ-ጽሑፍ ፈጠራዎችን ያቀፈ ነበር ፣ በ 14 ኛው ክፍለ ዘመን በጥንታዊ ምንጮች ላይ የተመሠረተ የመማር ትንሳኤ ጀምሮ ፣ በዘመኑ የነበሩት ለፔትራች ይመሰክራሉ ። በሥዕል ውስጥ የበለጠ ተፈጥሯዊ እውነታን የመስመራዊ እይታ እና ሌሎች ዘዴዎችን ማዳበር; እና ቀስ በቀስ ግን ሰፊ የትምህርት ማሻሻያ። በፖለቲካ ውስጥ ህዳሴ ለዲፕሎማሲ ልማዶች እና ስምምነቶች እድገት አስተዋጽኦ አድርጓል ፣ በሳይንስ ደግሞ በታዛቢነት እና በመረጃ አመክንዮ ላይ የበለጠ ጥገኛ እንዲኖር አድርጓል። ምንም እንኳን ህዳሴ በብዙ ምሁራዊ እና ማህበራዊ ሳይንሳዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ አብዮቶች ቢያዩም ፣ እንዲሁም ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት እና የሂሳብ አያያዝ መስክ ፣ ምናልባት በሥነ-ጥበባዊ እድገቶቹ እና እንደ ሊዮናርዶ ዳ ቪንቺ እና ማይክል አንጄሎ ባሉ ፖሊማቶች አስተዋፅዎ ይታወቃል። "የህዳሴ ሰው" የሚለውን ቃል አነሳስቷል. ህዳሴ የጀመረው ከብዙዎቹ የኢጣሊያ ግዛቶች አንዷ በሆነችው በፍሎረንስ ነው። በጊዜው የፍሎረንስን ማህበራዊ እና ህዝባዊ ባህሪያትን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ላይ በማተኮር ስለ አመጣጡ እና ባህሪያቱ የተለያዩ ንድፈ ሀሳቦች ቀርበዋል-የፖለቲካ አወቃቀሯ ፣ የበላይ ቤተሰቡ ፣የሜዲቺ እና የግሪክ ፍልሰት። የቁስጥንጥንያ የኦቶማን ቱርኮች ውድቀትን ተከትሎ ወደ ኢጣሊያ የመጡ ምሁራን እና ጽሑፎቻቸው። ሌሎች ዋና ዋና ማዕከላት ቬኒስ፣ ጄኖዋ፣ ሚላን፣ ሮም በህዳሴው ፓፓሲ እና ኔፕልስ ነበሩ። ከጣሊያን ጀምሮ ህዳሴ በመላው አውሮፓ በፍላንደርዝ፣ ፈረንሳይ፣ ብሪታኒያ፣ አየርላንድ፣ ስፔን፣ ፖርቱጋል፣ ጀርመን፣ ፖላንድ፣ ሃንጋሪ (ከኔፕልስ ቢያትሪስ ጋር) እና ሌሎችም ተስፋፋ። የህዳሴው ዘመን ረጅምና ውስብስብ የሆነ የታሪክ አጻጻፍ አለው፤ ከአጠቃላይ የልዩነት ጊዜያዊ ጥርጣሬዎች ጋር ተያይዞ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የ‹‹ሕዳሴ›› ክብርና የግለሰብ የባህል ጀግኖች ‹‹የሕዳሴ ሰዎች›› በማለት ምላሽ በሚሰጡ የታሪክ ተመራማሪዎች መካከል ብዙ ክርክር ተካሂዷል። የህዳሴ ጥቅም እንደ ቃል እና እንደ ታሪካዊ መግለጫ። አንዳንድ ታዛቢዎች ህዳሴ ከመካከለኛው ዘመን ጀምሮ የተፈጠረ የባህል “ግስጋሴ” ነው ወይ የሚለውን ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ሲሆን ይልቁንም ዘመኑን ለጥንታዊው ዘመን አፍራሽነት እና ናፍቆት ያዩታል፣ የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የታሪክ ተመራማሪዎች በተለይም የሎንጌ ዱሬዬ በምትኩ ላይ ያተኩራሉ። በሁለቱ ዘመናት መካከል ያለው ቀጣይነት, ተያያዥነት ያላቸው, ፓንፍስኪ እንደተመለከተው, "በሺህ ትስስር". ሪናሲታ ('ዳግም መወለድ') የሚለው ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ በጆርጂዮ ቫሳሪ የአርቲስቶች ህይወት ላይ ታየ፣ በ1830ዎቹ ውስጥ እንደ ህዳሴ ተብሎ ተጠርቷል። ቃሉ እንደ ካሮሊንግያን ህዳሴ (8ኛው እና 9ኛው ክፍለ ዘመን)፣ የኦቶኒያ ህዳሴ (10ኛው እና 11ኛው ክፍለ ዘመን) እና የ12ኛው ክፍለ ዘመን ህዳሴ ላሉ ሌሎች ታሪካዊ እና ባህላዊ እንቅስቃሴዎችም ተዘርግቷል። የአውሮፓ ታሪክ
3621
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A4%E1%88%8B%E1%88%9D
ኤላም
ኤላም ጥንታዊ ሃገር ነበር። ዛሬ ደቡብ-ምዕራብ ፋርስ በሆነ አቅራቢያ ተገኘ። መነሻው በዋና ከተማው በሱስን (ሹሻን) እና በካሩን ወንዝ ሸለቆ ከታሪክ መዝገብ መጀመርያ ሲሆን እስከ 547 ክ.በ. ድረስ ቆየ። ከሱመር እና ከአካድ (የዛሬ ኢራቅ) ወደ ምስራቅ የሆነ አገር ነበር። የኤላም መንግሥት ለፋርስ ከወደቀ በኋላ ቢሆንም የኤላም ቋንቋ በፋርስ አሐይመንድ መንግሥት በመደብኝነት ቆይቶ ነበር። ይህ ቋንቋ የፋርስኛ ዘመድ ሳይሆን ምናልባት ለደቡብ ሕንድ ድራቪዲያን ቋንቋዎች የተዛመደ ይሆናል። እስከ ዛሬም ድረስ በፋርስ አገር ውስጥ ኢላም ክፍላገር ከጥንታዊው አገር ተሰይሞ ይገኛል። ኤላማውያን የራሳቸውን ሀገር ስም ሃልታምቲ ብለው ሰይመውት ሲሆን ለጎርቤቶቻቸው ለአካዳውያን «ኤላምቱ» በመባል ታወቁ። 'ኤላም' ማለት 'ደጋ' ሊሆን ይቻላል። ከዚህ በላይ በብሉይ ኪዳን (ዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ) አገሩ 'ኤላም' ተብሏል፤ ስሙም ከኖኅ ልጅ ሴም ልጅ ኤላም ነው። የኤላም ጥንታዊ ዘመን የኤላም መጀመርያ ከተማ ሱስን ወይም ሹሻን ነበር። አንዳንዴም የሱመር አለቆች ወርረው አገሩን ይገዙ ነበር። በሱመር ነገሥታት መዝገብ ዘንድ የኪሽ ንጉሥ ኤንመባራገሲ (2384 ዓክልበ. ግድም) እንዲሁም የላጋሽ ንጉሥ ኤአናቱም (2200 ዓክልበ.) እና የአዳብ ንጉሥ ሉጋል-አኔ-ሙንዱ (2150 ዓክልበ.) ኤላምን አሸነፉት። በሌሎች ጊዜያት ኤላማውያንም ከተሞች ለምሳሌ የሐማዚ ወይም የአዋን (አቫን) ነገስታት በፈንታቸው ሱመርን ይገዙ ነበር። በአዋን ነገሥታት ዘመን የአካድ ንጉሥ ታላቁ ሳርጎን ኤላምን አሸንፎ (2075 ዓክልበ.) ከመግዛቱ በላይ በኤላም ውስጥ አካድኛን ይፋዊ ቋንቋ አደረገበት። ሆኖም ከሻርካሊሻሪ ዘመን በኋላ በ2013 ዓክልበ ግድም የአካድ መንግሥት በጉታውያን ወረራ ተሰብሮ ኤላም እንደገና ነጻ ወጣና አካድኛን ተወ። የሹሻን አገረ ገዥ የሆነ ኩቲክ-ኢንሹሺናክ ያንጊዜ የአዋን ንጉሥ ሆነና አዲስ ኤላማዊ ጽሕፈት አገባ። ኩቲክ-ኢንሹሺናክ አንሻንንና ሲማሽኪን ወደ ግዛቱ ጨመረ፤ እንኳን በ1986 ዓክልበ. ግድም እርሱ የአካድን ቅሬታ ያዘ። ነገር ግን በ1979 ዓክልበ. ግድም የኡር ንጉሥ ኡር-ናሙ አሸነፈውና የሲማሽኪ ሥርወ መንግሥት በኤላም ተነሣ። በዚህ ወቅት ከመስጴጦምያ ጋር ሰላምና ጦርነት ተፈራረቀና እንኳን ገደማ የኡር ንጉሥ ሹ-ሲን ሴት ልጁን ለአንሻን መስፍን በትዳር ሰጠ። ነገር ግን የሱመር ኃይል ደክሞ ይጀምርና በ1879 ዓክልበ. ግድም፤ በሺማሽኪ ንጉስ በኪንዳታ መሪነት ኤላማውያን ከሹሻን ሕዝብ ጋር ኡር ከተማን አጠፉና ንጉሣቸውን የሹ-ሲን ልጅ ኢቢ-ሲንን ማረኩት። ከዚህ በኋላ ግን የኢሲን ከተማ ንጉሶች ኤላማውያን ከኡር አስወጥተው እንደገና ሰርተውት ኤላማውያን የበዘበዙትን ጣኦታቸውን ናና አስመለሱ። የሚከተለው መንግሥት 'ኤፓርቲ' ይባላል። ደግሞ ከነገስታት ማዕረግ 'ሱካልማህ' ይባላል። በ1858 ዓክልበ. ግድም የመሠረተው ንጉሥ 2 ኤፓርቲ ነበር። በዚህ ጊዜ ሹሻን በኤላም ስልጣን ብትሆንም የመስጴጦምያ ኃያላት እንደ ላርሳ ምንጊዜ ሊይዙት ሞከሩ። በ1745 ዓክልበ. ገደማ ከሹሻን ወደ ስሜን በሆነ ከተማ የነገሠ ሌላ ኤላማዊ ንጉሥ ኩዱር-ማቡግ ልጁን ዋራድ-ሲን በላርሳ ዙፋን ላይ አስቀመጠ። የዋራድ-ሲን ወንድም ሪም-ሲን ተከተለውና በብዛት መስጴጦምያን አሸነፈ። በዚህ ወቅት በኤፓርቲ መንግሥት ታዋቂ ከሆኑ ነገሥታት መኃል፤ ሺሩክዱቅ የባቢሎንን ሥልጣን ለመቃወም ከሌሎች አገሮች ጋር ስምምነት አደረገ። ሲዌ-ፓላር-ቁፓክ የመስጴጦምያ ነገሥታት እንደ ማሪ ንጉስ ዝምሪ-ሊም እንዲሁም የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ 'አባት' ብለው ይጠሩት ነበር። ኩዱር-ናሑንተ የአካድ መቅደሶች በዘበዘ። ነገር ግን የኤላም ተጽእኖ በመስጴጦምያ አልቆየም። በ1675 ዓክልበ. ገደማ ሃሙራቢ ኤላማውያን አስወጥቶ የላርሳ ንጉሥ ሪም-ሲን ገለበጠውና መስጴጦምያን በሙሉ ገዛ። ሃሙራቢ የዘፍጥረት 14 አምራፌል ሲሆን ዋራድ-ሲን ወይም ሪም-ሲን አርዮክ እንደ ነበር ቢታስብም ዛሬ ብዙ ሊቃውንት ይህን ሃሳብ አይቀብሉም። በዚህ ምዕራፍ የተጠቀሰው ኤላማዊ ንጉስ ኮሎዶጎምር (በግሪኩ 'ኮዶሎጎሞር') ግን እንኳን ትክክለኛ ኤላማዊ ስም ('ኩዱር-ላጋማር') እንዳለው ይመስላል፤ ላጋማር የአረመኔ እምነታቸው ጣኦት ስም ነበርና። ካሳውያን በ1507 ዓክልበ. ገደማ ባቢሎንን ካሸነፉ በኋላ ታሪካዊ ምንጮች አይበዙምና ስለ ኤፓርቲ መንግሥት መጨረሻ ዘመን ብዙ አይታወቅም። የኤላም መካከለኛው ዘመን ከክርስቶስ በፊት ከ1500 ዓመት ጀምሮ በአንሻን ከተማ ዙርያ አዳዲስ ሥርወ መንግሥታት ተነሡ። የንገስታት ማዕረግ 'የአንሻንና የሱስን ንጉሥ' ተብሎ ነበር። መጀመርያው 1500-1400 የኪዲኑ ሥርወ መንግሥት ሲሆን የሚከተለው 1400-1210 የኢጊሃልኪ ሥርወ መንግሥት ነበር። ከኢጊሃልኪ 10 ነገሥታት አንዳንዱ ካሣዊት ልዕልትን ያገባ ነበር። በ1330 ክ.በ. ገደማ የካሳውያን ንጉስ 2 ኩሪጋልዙ ለጊዜው ኤላምን ወረረ። ከዚያም በ1240 ክ.በ. ገደማ ሌላ ካሳዊ ንጉስ 4 ካሽቲሊያሽ ከኤላም ጋር ሲዋግ አላከናወነም። የኤላም ንጉሥ ኪዲን-ሑትራን በ1232 ክ.በ. የካሳውያን ንጉሥ ኤንሊል-ናዲን-ሹሚ አሸንፎ በ1230 ክ.በ. ደግሞ የካሳውያን ንጉስ አዳድ-ሹማ-ኢዲና አሸነፈ። የሚከተለው ሥርወ መንግሥት የሹትሩክ ነገሥታት 1210-1100 ያሕል ገዙ። 2ኛው የሹትሩክ ንጉስ ሹትሩክ-ናሑንተ በ1184 ክ.በ. ካሳውይያንን በባቢሎን ሲዋጋ የሃሙራቢ ሕገጋት የተጻፈበትን ድንጋይ ከመማረኩ በላይ የማርዱክና የማኒሽቱሹ ጣኦታትና የናራም-ሲን ሐውልት ወደ ሱስን ማረከባቸው። በ1166 ሹትሩክ-ናሑንተ ካሳውያንን በፍጹም ድል አደረጋቸው። ነገር ግን በ1130 ሱስን ለባቢሎን ንጉሥ ለ1 ናቡከደነጾር ወደቀና የኤላም ንጉሥ ሑተሉሽ-ኢንሹሺናክ ወደ አንሻን ሸሸ። ከሱ በኋላ የኤላም ታሪክ ለጥቂት መቶ ዘመን አይገኝም። የኤላም አዲስ ዘመንና ፍጻሜ ከዚህ ዘመን እስከ 800 ክ.በ. ድረስ ስለ ኤላም ብዙ አይታወቀም። ቢያንስ አንሻን የኤላም ከተማ ሆኖ ቀረ። ኤላም ከባቢሎን ጋር በአሦር ላይ ስምምነት ያደርግ ነበር። የባቢሎን ንጉሥ ማር-ቢቲ-አፕላ-ኡሹር ከኤላም ትውልድ እንደ ነበር ይታመናል። ኤላማውያን ከባቢሎን ንጉሥ ከማርዱክ-በላሱ-ኢቅቢ ጋራ ጦርነት በአሦር ንጉስ በ5ኛ ሻምሺ-አዳድ ላይ አደረጉ። በዚያን ጊዜ ገዳማ ከኤላም ወደ ስሜን የማዳይ (ሜዶን) ሕዝብ በስሜን ፋርስና ዘመዶቹ ፋርሳውያን በኡርምያህ ሐይቅ ዙሪያ ተነሡ። ንጉሥ ሑምባኒጋሽ ከባቢሎን ንጉሥ ከመሮዳክ ባልዳን ጋራ በአሦር ንጉስ በ2ኛ ሳርጎን ላይ ስምምነት እንዳደረገ ይታወቃል። ከሱ የተከተለው ንጉሥ 2ኛ ሹትሩክ-ናሑንተ በ718ና በ716 ክ.በ. በሳርጎን ሠራዊት እጅ ድል ሆነ። የሳርጎን ልጅ ሰናክሬም መሮዳክ-ባላዳንን ገልብጦ የራሱን ልጅ አሹር-ናዲን-ሹሚ በባቢሎን ዙፋን ላይ በ708 ክ.በ. ንጉስ አደረገው። ሹትሩክ-ናሑንተ በወንድሙ ሐሉሹ ተገድሎ ይህ ሐሉሻ አሹር-ናዲን-ሹሚንና ባቢሎን በ702 ክ.በ. ማረከው። ሐሉሻ ግን በኩትር-ናሑንተ እጅ ተገደለ። ኩትር-ናሑንተ ዙፋኑን ለቅቆ በኡ ፈንታ የነገሠ ሑማ-መናኑ እንደገና ከአሦር ጋር ተዋገ። ሰናክሬም ግን በ697 ክ.በ. ባቢሎንን አጠፋው። በሰናክሬም ልጅ በአስራዶን ዘመን አንድ ኤላማዊ አገረ ገዥ በደቡብ መስጴጦምያ አመፃ አድርጎ ወደ ኤላም ሸሽቶ የኤላም ንጉስ ግን ገደለው። የአስራዶን ልጅ አስናፈር በ661 ክ.በ. ሱስንን ድል አድርጎ ወረራት። በዚህ አመት ደግሞ እስኩታውያን ሜዶንን ስለወረሩ የፋርስ ነገዶች ከዚያ ወደ አንሻን ፈልሶ ንጉሳቸው ተይስፐስ ያንጊዜ አንሻንን ማረከው። ሆኖም ለጊዜው የኤላም ነገሥታት ማዕረግ 'የአንሻንና የሱስን ንጉስ' ተብሎ ቆየ። ከዚያ በአሦር ውስጥ የብሄራዊ ጦርነት ጊዜ ስለተከተለ እንዲሁም በኤላም የብሔራዊ ጦርነት ዘመን ተነሣ። በመጨረሻ ግን አስናፈር በ648 ክ.በ. ኤላምን በሙሉ ሲያጠፋ እንኳን እርሻቸውን በጨው ዘራ። ከዚያ በኋላ የኤላም ኅይል ደክሞ በብዙ ትንንሽ መንግሥታት ተከፋፈለ። በመጨረሻ የፋርሶች አሐይመኒድ ነገሥታት በ546 ክ.በ. ሱሳንን ያዙት። የኤላም መንግሥት ቢጠፋም ተጽእኖው በፋርስ መንግሥት ቀረ። ኤላምኛ ከፋርስ ሶስት ይፋዊ ቋንቋዎች አንዱ ነበር። ኤላምኛ ደግሞ የሐዋርያት ሥራ 2:9 እንደሚመስክር በ1ኛ ክፍለ ዘመን በጴንጤቆስጤ ከተሰሙት ልሳናት አንዱ ነበር። የኤላም ቋንቋ ኤላምኛ ለጎረቤቶቹ ለሰናዓርኛም ሆነ ለሕንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ወይም ለሴማዊ ቋንቋዎች ቤተሰቦች የተዛመደ አልነበረም። በኋለኛ ዘመን የተጻፈበት ከአካድኛ ባለ-ማዕዘን (ኩኔይፎርም) ጽሕፈት በተለመደ ጽሕፈት ሲሆን ከሁሉ ጥንታዊ የሆኑት ሰነዶች ግን ከዚህ በተለየ ማሥመርያ ኤላማዊ ጽሕፈት ነው የተቀረጹት። ባለፈው አመት ውስጥ ለዚህም ተመሳሳይ ጽሕፈት በጂሮፍት ፋርስ ተገኝቷል። ከዚህ በፊት ቅድመ-ኤላማዊ ጽሕፈት የሚባል የስዕል ጽሕፈት ነበረ። ይህ ግን ኤላምኛ ለመጻፍ መጠቀሙ እርግጠኛ አይደለም። አንዳንድ የቋንቋ ሊቃውንት እንደሚያምኑ ኤላምኛ የዛሬው ደቡብ ሕንድ ድራቪዲያን ቋንቋዎች (ታሚል ተሉጉ ወዘተ.) ዘመድ ይሆናል። በተጨማሪ በዛሬ ፓኪስታን የተገኘው ጥንታዊ የሕንዶስ ወንዝ ሥልጣኔ የሃራፓ ስዕል ጽሕፈት ስለነበረው ከኤላም ጋር ግንኙነት ሊኖር ይችላል ቢሉ፥ እስከ ዛሬ ድረስ ግን ለዚህ ጽሕፈት መፍትሔ ወይም ትርጉም ስላልተገኘም አጠያያቂ ሆኖ ቀርቷል። ታሪካዊ አገሮች የፋርስ ታሪክ
22422
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%80%E1%8B%B2%E1%8B%AB
ሀዲያ
ሀዲያ በአብዛኛው በደቡብ ኢትዮጵያ እና በሌሎችም አካባቢዎች በስፋት ከሚገኙ ብሄረሰቦች አንዱ ሲሆን የራሱ የሆነ ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ስነጥበብ፣ ወግና፣ የኑሮ ዘይቤ ያለው ህዝብ ነው። የሀዲያ ዋና ከተማ ዋቸሞ ተብላ ስትጠራ ይህች ከተማ በደርግ ዘመነ መንግስት በሸዋ ክፍለ ሃገር የሃዲያና ከምባታ አውራጃ ዋና ከተማ ነበረች። የዋቸሞ ከተማን የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች በአብዛኛው ሆሳዕና ብለው ይጠሯታል። ሆሳዕና የሚል ስያሜ ያገኘችው አውራጃዋን ይገዙ በነበሩት በራስ አባተ ቧያለው ዘመን ሲሆን ራስ አባተ ወደ ሥፍራው ሲደርሱ ዕለቱ የሆሣዕና በዓል በሚከበርበት ሳምንት በመሆኑ ነው ሆሣዕና ብለው የሰየሙት። ከዚያ በፊት ሦስት ስሞች ነበሯት፦ ዋቸሞ፣ ሴችዱና እና ሐገተ ትባል ነበር። (በተቻለ መጠን ታሪክን ሳናዛባ ብንጽፍ ይሻላል) አማርኛ ተናጋሪዎች ሳይሆኑ የወቅቱ መሪ ነው ስሟን ሆሳዕና ብሎ የቀየረው፤ ዋቸሞ የሚል ስያሜ የዞኑ ዋና ከተማ ሆኖ በኢህአዴግ ዘመን ለጥቂት ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ ዋለ እንጂ እንደ ዞን ዋና ከተማ ሆኖ አገልግሎት ላይ ውሎ አያወቅም። የደጋማው ምሥራቃዊ ኩሽ የቋንቋ ቤተሰብ የሆነው ‹‹ሀዲይኛ›› የሀዲያ ብሔረሰብ አፍ መፍቻ ቋንቋቸው ሲሆን በተጨማሪ ብዙዎቹ ከምባትኛን ፤ ኦሮምኛን ስልጢኛን ወላይትኛንና አማርኛ በሁለተኛ ቋንቋነት ይናገራሉ፡፡ ሀዲይኛ ከንግግር ቋንቋነት አልፎ የጽሑፍ ቋንቋ መሆን የጀመረው በ1920ዎቹ ዓለም አቀፍ የእንግሊዝ መጽሐፍ ቅዱስ ማኀበር መጽሐፍ ቅዱስን በሀዲይኛ ቋንቋ አስተርጉሞ ካሳተመበት ወቅት ጀምሮ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከ1967 እስከ 1968 ዓ.ም በነበረው የእድገት በኀብረትና የዕውቀት ዘመቻ ወቅት የሳባን ፊደላት በመጠቀም ለመሠረተ ትምህርት ማስተማሪያነት መዋል እንደተጀመረ ይነገራል፡፡ ከ1983 ዓ.ም ወዲህ ግን በሀገሪቱ የአንደኛ ደረጃ ትምህርትን በአፍ መፍቻ ቋንቋ ለማስተማር ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ከመስከረም 1986 ዓ.ም ጀምሮ በሀዲይኛ የአንደኛ ደረጃ የመጀመሪያ ሳይክል ከንድ እስከ አራት ሁሉም የትምህርት ዓይነቶች በሃዲይኛ በላቲን ፊደላት እየተሰጠ ይገኛል። በ2002/2003/ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትም ራሱን የቻለ ቋንቋ ሆኖ እስከ ዩንቬርስቲ ድረስ እንድገባ ተደርጓል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሀዲያ ዞን የሥራ ቋንቋ ሀዲይኛ ነው፡፡ ሕዝብ ቁጥር በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት መሠረት የብሔሰቡ ሕዝብ ብዛት 1 ሚሊዮን 284 ሺ 373 ነው፡፡ መልክዓ ምድር የሃዲያ ብሔረሰብ በዋነኛነት በሀዲያ ዞን በሚገኙ አስር ወረዳዎች ውስጥ የሚኖር ሲሆን፤ ከዞኑ ውጪ ደግሞ በወላይታ፣ በሲራሮ፣ በአርሲ፣ በባሌ፣ በአጄ፣ በወንጂ፣ በመተሐራ፣ በስልጤ፣ በቀቤና፣ በማረቆ በሀላባ፣ በሲዳማ፣ በየም፣ በሐረሪ፣ በአፋር፣ በኮፌሌና በከንባታ በብዛት እንደሚገኙ ይነገራል፡፡ የብሔረሰቡ አባላት በዋነኛነት የሚኖሩባቸው አሥራ ሁለት ወረዳዎችና አራት ከተማ አስተዳደር ሜዳማ፣ ተዳፋትና ወጣገባ የመሬት አቀማመጥ ሲኖራቸው የአየር ንብረቱም ደጋ፣ ወይናደጋና ቆላማ ነው፡፡ ሀዲያ ብሔረሰብ በደቡብ ክልል ከሚገኙት ብሔረሰቦች አንዱ ነው፡፡ የብሔረሰቡ መጠሪያ ስያሜውን ያገኘው ከአረብኛ ቋንቋ ነው፡፡ ትርጓሜውም ‹‹ስጦታ›› ማለት እንደሆነ መጃዎች ያስረዳሉ፡፡ የብሔረሰቡ ዋነኛ መተዳደሪያ እርሻ ሲሆን፤ከብት እርባታና ንግድ በተጓዳኝ በማከናወን ኑሮውን ይመራል፡፡ በብሔረሰቡ የበርካታ ከብት ባለቤት መሆን ማኀበራዊ ከበሬታ ይሰጥ ስለነበር ከአንድ መቶ እስከ አንድ ሺ ከብት የማስቆጠር ወይም የማስመረቅ ሥርዓት ይከናወናል፡፡ይህም አባባል በቋንቋ//ይባላል። በሀዲያ ብሔረሰብ ውስጥ አሥራ ሰባት ማኀበራዊ ቡድኖች ወይም ጐሳዎች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም ሌሞ (ኡቤኤ) ጋሞ፣ለሞሬ፣ ዑሱማኖ ምሮሬ፣ ሞቾሶ፣ ሶሮ (ዶጌኤ) ወይም ቦያሞ፣ ሀዴ፣ ሀባሮ፣ ሸካ፣ ቦሻ፣ ሻሼ፣ ኡሩሶ፣ ዳዳ፣ (ሶሌቾ) በርጋጌኤ፣ ሀበሎ፣ ሀዱሞ፣ ባደጐ፣ ሆጄኤ፣ ዋየቦ፣ ሀንቃላ፣ አጎር-ገሣ/ ሎካ፣ ዱግሞ መስመስ፣ ሳውካ፣ ገንዛ፣ ኤሬራ፣ መሳዋ፣ ባዳዋች፣ ደዋ-ዲጋላ ናቸው፡፡ እነዚህ ጐሳዎች የተለያየ ባህላዊ የአስተዳደር እርከኖችና መሪዎች ያላቸው ሲሆን፤ ይህም ከዝቅተኛው ወደ ከፍተኛው እንደሚከተለው ይገለጻል፡፡ (ቤተሰብ) ሲሆን የደረጃው መሪ ምዕኒዳና ይባላል (ጐጭ/ኦሊዳና) የጐጥ መሪ 3. ሱሎ (ነገድ/ሱኡሊዳና) የነገድ መሪ 4. ጊቾ (ጐማ/ጊቺዳና) የነገድ መሪ 5. ጊራ (ብሔረሰብ/ግዕሊዳና) የብሔረሰቡ መሪ የሀዲያ ባህላዊ አስተዳደሪዎች አመራረጥ መመዘኛው ግላዊ ብቃትና የኀብረተሰብ ሚዛን ናቸው፡፡ በግላዊ ብቃቱ የብሔረሰቡን ባህላዊ እሴቶች ጠንቅቆ የማወቅ፣አንደበተ ርዕቱነት፣ አስተዋይነት፣ ቀናነት፣ ቸርነት፣ ይቅርባይነት ሀብትና ወዘተ… ናቸው፡፡ በብሔረሰቡ ሁለት ዓይነት የተለዩ የቤት አሠራሮች አሉት፡፡ የመጀመሪያው ከላይ እስከታች ሣር የሚለብስ ጐጆ ሲሆን ‹‹ሀጉማኦ›› ይባላል፡፡ ሁለኛው ግድግዳውና ጣሪያው ተለይቶ ጣሪያው በሣር የሚከደንና ‹‹ፌንጋሞ›› በመባል የሚጠራው ነው፡፡ በቤት አሠራሩ ሂደት ውስጥ ዋና ተሳታፊዎች ወንዶች ሲሆኑ፤ በምርጊቱ ላይ የሚሳተፉት ሴቶች ናቸው፡፡ የሀዳያ ብሔረሰብ ከ45 በላይ ባህላዊ ምግቦችና የተለያዩ ባህላዊ መጠጦች እንዳሉት ይነገራል፡፡ ብሔረሰቡ በየዕለቱ ከሚመገባቸው የዘወትር ምግቦች መካከል ቆጮ፣ቂጣ፣ወተት (በየቀኑ ይጠጣል)እና የወተት ተዋጽኦ ቆሎ፣ቡና ድንችና ‹‹ቡሎ›› ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ነጭ ሽንኩርት (ቱማ) እና ጤና አዳም (ጫሮተ~ቅንትለማ) ከምግብነት በተጨማሪ ለባህላዊ መድኃኒትነት ሲያገለግሉ የኮሶ(ሱጦ) ዛፍም ለመድኃኒትነት ይጠቀማሉ፡፡ == ሀዲያ ብሔረሰብ ፌስቡክ ገጽ የሀዲያ ብሔረሰብ በደቡብ ከልል ከሚገኙት ብሔረሰቦች አንዱ ነው። የብሔረሰቡ መጠሪያ ስያሜውን ያገኘው ከአረብኛ ቋንቋ ነው። ትርጓሜውም «ስጦታ» ማለት እንደሆነ መረጃዎች ያስረዳሉ። ብሔረሰቡ በዋነኛነት በሀዲያ ዞን በሚገኙ አስር ወረዳዎች ውስጥ የሚኖር ሲሆን፤ ከዞኑ ውጪ ደግሞ በወላይታ፣ በሲራሮ፣ በአርሲ፣ በባሌ፣ በአጆ፣ በመንጂ፣ በመተሐራ፣ በስልጤ፣ በቀቤና፣ በማረቆ፣ በሀላባ፣ በሲዳማ፣ በየም፣ በሐረሪ፣ በአፋር፣ በኮፌሌና በከንባታ በብዛት እንደሚገኙ ይነገራል። የብሔረሰቡ አባላት በዋነኛነት የሚኖሩባቸው አሥሩ ወረዳዎች ሜዳማ፣ ተዳፋትና ወጣገባ የመሬት አቀማመጥ ሲኖራቸው የአየር ንብረቱም ደጋ፣ ወይናደጋና ቆላማ ነው። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት መሠረት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 1 ሚሊዮን 284 ሺ 373 ነው። የብሔረሰቡ ዋነኛ መተዳደሪያ እርሻ ሲሆን፤ ከብት እርባታና ንግድ በተጓዳኝ በማከናወን ኑሮውን ይመራል። በብሔረሰቡ የበርካታ ከብት ባለቤት መሆን ማኅበራዊ ከበሬታን ይሰጥ ስለነበር ከአንድ መቶ እስከ አንድ ሺ የማስቆጠር ወይም የማስመረቅ ሥርዓት ይከናወናል። የደጋማው ምሥራቃዊ ኩሽ የቋንቋ ቤተሰብ የሆነው «ሀዲይኛ» የሀዲያ ብሔረሰብ ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ ከምባታ፣ ኦሮምኛንና ስልጢኛ በሁለተኛ ቋንቋነት ይናገራሉ። ሀዲይኛ ከንግግር ቋንቋነት አልፎ የጽሑፍ ቋንቋ መሆን የጀመረው በ1920ዎቹ ዓለም አቀፍ የእንግሊዝ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር መጽሐፍ ቅዱስን በሀዲይኛ ቋንቋ አስተርጉሞ ካሳተመበት ወቅት ጀምሮ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከ1967 እስከ 1968 ዓ.ም በነበረው የእድገት በኅብረት ዘመቻ ወቅት የሳባን ፊደላት በመጠቀም ለመሠረተ ትምህርት ማስተማሪያነት ማዋል እንደጀመረ ይነገራል። ከ1983 ዓ.ም ወዲህ ግን በሀገሪቱ የአንደኛ ደረጃ ትምህርትን በአፍ መፍቻ ቋንቋ ለማስተማር ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ከመስከረም 1986 ዓ.ም ጀምሮ በሀዲይኛ የአንደኛ ደረጃ የመጀመሪያ ሳይክል ከአንድ እስከ አራት ሁሉንም የትምህርት ዓይነቶች እየተሰጡ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት የሀዲያ ዞን የሥራ ቋንቋ ሀዲይኛ ነው፡ በሀዲያ ብሔረሰብ ውስጥ አሥራ ሰባት ማኅበራዊ ቡድኖች ወይም ጐሳዎች ይገኛሉ። እነዚህም ሌሞ (ኡቤኤ)፣ ጋሞ፣ ላሞሬ፣ ሞቾሶ፣ ዶጌኤ (ሶሮ) ዑሱማኖ ወይም በያሞ፣ ሀዴ፣ ሀባሮ፣ ሻካሀ፣ ቦሻሀ፣ ሻሼ፣ ኡሩሶ፣ ዳዳ፣ (ሶሌቾ) በርጋጌኤ፣ ሀበሎ፣ ሀዱባ፣ ባደጐ፣ ሆጄኤ፣ ዋየቦ፣ ሀንቃላ፣ አጎር-ገሣ/ ሎካ፣ ዱግሞ፣ መስመስ፣ ሳውካ፣ ገንዛ፣ ኤሬራ፣ መሳዋ፣ ባዳዋች፣ ደዋ-ዲጋላ ናቸው። እነዚህ ጐሳዎች የተለያየ ባህላዊ የአስተዳደር እርከኖችና መሪዎች ያላቸው ሲሆን ፤ ይህም ከዝቅተኛው ወደ ከፍተኛው እንደሚከተለው ይገለጻል። 1. ምኔ (ቤተሰብ )ሲሆን የደረጃው መሪ ምኒዳና ይባላል 2. ሞሎኒ( ጐጥ/ ኦኦሊዳና) የጐጥ መሪ 3. ሱላአ ( ነገድ/ ሱኡሊዳና) የነገድ መሪ 4. ጊዕቾ( ጐማ/ ጊዕችዳና) የነገድ መሪ 5. ግራ( ሔረሰብ/ ግዕሊዳና) የብሔረሰቡ መሪ የሀዲያ ባህላዊ አስተዳዳሪዎች አመራረጥ መመዘኛው ግላዊ ብቃትና የኅብረተሰብ ሚዛን ናቸው። በግላዊ ብቃቱ የብሔረሰቡን ባህላዊ እሴቶች ጠንቅቆ የማወቅ፣ አንደበተ ርዕቱነት፣ አስተዋይነት፣ ቀናነት፣ ቸርነት፣ ይቅርባይነት፣ ሀብትና ወዘተ ናቸው። በብሔረሰቡ ሁለት ዓይነት የተለያዩ የቤት አሠራሮች አሉት። የመጀመሪያው ከላይ እስከታች ሣር የሚለብስ ጐጆ ሲሆን «ሁጉማኦ» ይባላል። ሁለተኛው ግድግዳውና ጣሪያው ተለይቶ ጣሪያው በሣር የሚከደንና «ፌንጋሞ» በመባል የሚጠራው ነው። በቤት አሠራሩ ሂደት ውስጥ ዋና ተሳታፊዎች ወንዶች ሲሆኑ፤ በምርጊቱ ላይ የሚሳተፉት ሴቶች ናቸው። የሀዲያ ብሔረሰብ ከ45 በላይ ባህላዊ ምግቦችና የተለያዩ ባህላዊ መጠጦች እንዳሉት ይነገራል። ብሔረሰቡ በየዕለቱ ከሚመገባቸው የዘወትር ምግቦች መካከል ቆጮ፣ ቂጣ፣ ወተት እና የወተት ተዋጽኦ፣ ቆሎ፣ ቡና፣ ድንችና «ቡሎ» ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው። ነጭ ሽንኩርት (ቱማ) እና ጤና አዳም (ቅንትለማ) ከምግብነት በተጨማሪ ለባህላዊ መድኃኒትነት ሲያገለግሉ የኮሶ ዛፍም ለመድኃኒትነት ይጠቀማሉ። ታዋቂ ሰዎች የኢትዮጵያ ብሔሮች
50474
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%8A%A5%E1%88%B5%E1%8C%A2%E1%8D%8B%E1%8A%96%E1%88%B5%20%E1%88%8A%E1%89%80%20%E1%8B%B2%E1%8B%AB%E1%89%86%E1%8A%93%E1%89%B5%20%E1%8B%88%E1%89%80%E1%8B%B3%E1%88%9C%20%E1%88%B0%E1%88%9B%E1%8B%95%E1%89%B5
ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት
እስጢፋኖስ (በግሪክ: ሲነበብ ፡ ስቴፋኖስ ፤ በዕብራይስጥ ፡ ፤ በእንግሊዘኛ ፡ ሲነበብ ፡ ስቴፈን) በሕገ ወንጌል (በክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው ። ቅዱሱ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር ። ይህም በወጣትነት ያለፈችው ሕይወቱ ስትሠራ የነበረው ታላቅ መንፈሳዊ ሥራ ይመሠክራል ። የመጀመሪያው ሕይወቱ በአጭሩ የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም ይባላሉ ። (ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ) ገና ከልጅነቱ ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ እድሜው ሲደርስ ወደ ት/ቤት ገባ ። የወቅቱ ታላቅ መምህር ገማልያል ይባል ነበር። ይህ ሰው በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፭፥፴፫ ላይ ተጠቅሷል ። በትውፊት ትምህርት ደግሞ ይህ ደግ (ትልቅ) ሰው በርካታ ቅዱሳንን (እስጢፋኖስን፣ ጳውሎስን ፣ ናትናኤልን፣ ኒቆዲሞስን...) አስተምሯል ። በጌታችን መዋዕለ ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ እየቀረበ ይጨዋወት ነበር ፤ በፍጻሜውም አምኗል ። ቅዱስ እስጢፋኖስም ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ ወጣ ። ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና በተስፋ ይጠባበቅ ነበር ። ከቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁ ጋር በወቅቱ ደግሞ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ ። ከእግዚአብሔር ሆኖ ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ። ለስድስት ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ ። ለስድስት ወራት ከቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በኋላ ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠመቀ ። በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ እስጢፋኖስ መምህሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው ጠየቀው ። "ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው ።" በሚል ላከው ። ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ እጅ ነስቶ ተማረ ። (ሉቃ. ፯፥፲፰) በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ ። ወንጌል ስለማጥናቱ ጌታም ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት ላከው ፤ አጋንንትም ተገዙለት ። (ሉቃ. ፲፥፲፯) ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን መድኃኔ ዓለም ከዋለበት እየዋለ ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ ፤ ምሥጢር አስተረጐመ ። ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ ከተነሳ በኋላ ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ ባርኳል ። በዚህ ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ ሐዋርያት ቅስናን (ጵጵስናን) ተሹሟል ። በበዓለ ሃምሳም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሰባ ሁለቱ አርድእት የእርሱን ያህል ልሳን የበዛለት፣ ምሥጢርም የተገለጠለት የለም ። በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን ይሰብክ ገባ ። በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ ሰባቱ ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር ። አልፎም የስድስቱ ዲያቆናት አለቃ እና የስምንት ሺው ማኅበር መሪ(አስተዳዳሪ) ሆኑዋል ። ስምንት ሺህ ሰውን ከአጋንንት መጠበቅ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ አባቶቻችን መጠየቅ ነው ። አንድን ሰው ተቆጣጥሮ ለደኅንነት ማብቃት እንኳን እጅግ ፈተና ነው ። መጸሐፍ እንደሚል ግን መንፈስ ቅዱስ የሞላበት ማኅደር እግዚአብሔር ነውና ለርሱ ተቻለው ። (ሐዋር፣ሥ፡፮ ቁ፡፭) አንዳንዶቻችን ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ሲባል እንደዘመኑ ይመስለን ይሆናል ። እርሱ በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው ። ዲቁና ለእርሱ " በራት ላይ ዳርጎት" እንጂ እንዲሁ ድቁና አይደለም ። ከጌታችን እርገት በኋላ ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በኋላ ለአንድ ዓመት ያህል ስምንት ሺውን ማኅበር እየመራ ወንጌልን እየሰበከ ቢጋደል ኦሪት "እጠፋ እጠፋ" አለች ። በዚህ ጊዜ "ክርስትናን ለማጥፋት መፍትሔው ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው " ብለው አይሁድ በማመናቸው አልቀረም ገደሉት ። እርሱ ግን ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው ። በመጨረሻውም ስለ እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት ። ደቀ መዝሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት ። ከአረፈ በኋላ ቅዱስ እስጢፋኖስ ከአረፈ ከሦስት መቶ ዓመት በኋላ በኢየሩሳሌም የሚኖር አንድ ደግ ሰው ነበረ ስሙም ሉኪያኖስ ይባላል ። በተደጋጋሚ በራዕዪ ቅዱሱ እየተገለጠለት "ሥጋዬን አውጣ" ይለው ነበርና ሒዶ ለጳጳሱ ነገረው ። ጳጳሱም ደስ ብሎት ካህናትና ምዕመናንን ሰብስቦ ወደ አፀደ ገማልያል ማለት ወደ መምህሩ ሄደ ። ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ ። መላዕክት ሲያጥኑም በጎ መዓዛ ሸተተ ። ዝማሬ መላዕክትም ተሰማ ። ሕዝቡና ጳጳሱም በቅዱስ እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው በታላቅ ዝማሬና በሐሴት ዐፅሙን ከዚያ አውጥተው በጽርሐ ጽዮን (በተቀደሰችው ቤት) አኖሩት ። እለ እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተክርስቲያን አነጸለት ወደዚያ አገቡት ። ከአምስት ዓመታት በኋላም እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጎን አኖሩት ። የእስክንድሮስ ባለቤት ግን ወደ ሀገሩዋ ቁስጥንጥኒያ ስትመለስ የባሏ ሥጋ መስሉዋት የእስጢፋኖስን ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው ። መንገድላይም ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው ። እጅግም ደስ አላት አምላክ ለዚህ አድሉዋታልና ። እርሷም ወስዳ ለታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጥንጢኖስ አስረከበችው ። በከተማው ታላቅ ሐሴት ተደረገ ። ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች ። በዚያም ላይ ትልቅ ቤተክርስቲያን ታንጾለታል ። ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲመቱ ጥቅምት ፲፯ ቀን ዕረፍቱ ጥር ፩ ቀን ፍልሰቱ መስከረም ፲፭ ቀን ነው ።
3360
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%88%B4
ደሴ
ደሴ በወሎ ክፍለ ሃገር የሚገኝ ከተማ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ የደቡብ ወሎ ዋና ከተማ ነው። የወይና ደጋ አየር ጸባይ ያለው ይህ ከተማ፣ በከተማነት ታዋቂ እየሆነ የመጣው በዓፄ ዮሐንስ ፬ኛ ዘመን እንደሆነ ይጠቀሳል። የአካባቢው መሬት ከእሳተ ጎሞራ ቅሪት የሚመነጭ ስለሆነ፣ በንጥረ ነገር የዳበርና ለምነት ስለሚያሳይ፣ ከተማው በ20ኛው ክፍለዘመን በፍጠነት እንዲያድግና በኋላም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እና ደርግ ዘመን ወሎ ተብሎ ለተሰየመው ክፍለ ሃገር ዋና ከተማ እንዲሆን ዋና አስተዋጽዖ አድርጓል። እንደ አርመን ኢምባሲ ታሪካዊ ሰነድ፣ የአርመን ክርስቲያኖች በ7ኛው ክፍለ ዘመን በአረቦች በተነሳባቸው ወከባ ምክንያት ብዙዎች ተሰደው በአሁኑ ደሴ ከተማ አካባቢ እንደሰፈሩና በኋላ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተሰኘውን ገዳም በሐይቅ እንደመሰረቱ ያትታል። በዚህ አካባቢ አርመኖች የመስፋፋትና የመጎልበት ሁኔታ እያሳዩ ስለመጡ አካባቢው የአርመን ደሴት እስከመባል እንደደረሰና በኋላ በ16ኛው ክፍለ ዘመን በግራኝ አህመድ ወረራ ምክንያት ካሉበት ተነቅለው በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች እንደተበተኑ ይሄው የኢምባሲ ሰነድ ያትታል። እ.ኤ.አ. በ 1882ዓ.ም. ነበር ን/ነገስት ዮሃንስ ጦራቸውን በዚሁ አካባቢ ሲያሰፍሩ ከአመት በፊት በአካባቢው የታየችውን ባለጭራ ኮከብ በማስታወስ " ይህን ቦታ ደሴ ብየዋለሁ" ብለው ከተማውን እንደቆረቆሩ ይጠቀሳል። የደሴ ከተማ የፖስታ አገልግሎት ያገኘችው እ.ኤ.አ. 1920 ነው። የስልክ አገልግሎትም ቢሆን በቅርቡ ማለትም እ.ኤ.አ. በ 1954 ነው ያገኘችው። ፤የደሴ ከተማ የ መብራት አገልግሎት ያገኘችው እ.ኤ.አ. በ 1963 ነው። ይህን የመብራት አገልግሎት ያገኘችው በጊዜው በመገንባት ላይ በነበረው በናፍጣ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ሃይል ነው። አጠቃላይ መረጃ ከአዲስ አበባ ተነስተን 401 ኪሎ ሜትር ወደ ሰሜን ስንጓዝ ከኮምቦልቻ ቀጥሎ የምናገኘዉ ከተማ የደሴ ከተማ ነው። ደሴ ጥንታዊ ስሙ ላኮመልዛ የሆነ የሰሜን-መሃል ኢትዮጵያ ከተማና ወረዳ ነው። ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ መስመር (መንገድ) ላይ በአማራ ክልል፤ ደቡብ ወሎ ዞን ሲገኝ በላቲቱድና ሎንግቱድ ላይ ነዉ። የብሔራዊ ስታትስቲክ ባለስልጣን በ1998 እንደመዘገበው፤ ከኢትዮጵያ ሰፊ ከትሞች አንዱ ሲሆን የ169,104 ሕዝብ መኖሪያ ከተማ ነው። ከነሱም መኻከል 86,167 ወንዶች 82,937 ሴቶች ናቸው ተብሎ ተገምቷል። ደሴ አሁን ስራ ቢያቆምም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያን ከጎረቤቱ ከኮምቦልቻ ከተማ ጋር ይጋራ ነበር። አዲስ አመት አካባቢ የጥቅምት ወር ሲገባ በጣም ታዋቂ እና ብዙ የተዘፈነለት የጦሳ ተራራ በቢጫ (አደይ) አበባ ተሸፍኖ ማየት ምን ያህል ለበአል ድምቀት የመንፈስ እርካታ እንደሚሰጥ መግለጽ ያዳግታል። ደሴ ለመስፋፋት ሰፊ እድል ያለዉ አይመስልም ምክንያቱም ዙሪያዉ በወግዲ የተከበበ በመሆኑ እና መሬቱ ዉሃ የሚበዛበት (ረግራጋማ ) ስለሆነ ነው። ከዚህም አንጻር በጣም ብዙ ህዝብ እንደሚኖርበት ይታወቃል። የውቦች ከተማ እንደሆነች የሚነገርላት ደሴ ከተማ በ ኪነ-ጥበቡ ረገድ በሃገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ካላቸው ከተሞች አንዷ ናት። በከተማይቱ መሃል ዕምብርት የሚገኙት ወሎ ባህል አምባ እና ምን ትዋብ አዳራሾች ለከተማዋ የኪነ ጥበብ እድገት ከፍተኛውን ድርሻ ይወስዳሉ። ደሴ የበፊቱ ሙዚየም የተቀየረው የደጃዝማች ዮሴፍ ብሩ መኖሪያ ቤት መቀመጫ ናት። የ አራቱም የሙዚቃ ቅኝቶች መፍለቂያ የሆነችው ደሴ ከተማ በ ሙዚቃው ዘርፍ በሃገሪቱ ከፍተኛ ድርሻ ካላቸው ከተሞች አንዷ ናት። ለዚህም ተጠቃሽ የሚሆነው ከከተማይቱ የሚዎጡ በርካታ ድምጻዊያንን መጥቀስ ይቻላል። በተጨማረም ከተማይቱን አስመልክቶ የተዘፈኑ ከ መቶ ሃያ በላይ የአማርኛ ዘፎኖች እንዳሉ ይነገራል። አብዛሃኛዎቹ ዘፈኖች በከተማዋ ስለሚገኙ ቆነጃጂቶች የተዜሙ ናቸው።ባህሩ ቃኘው፤ ማሪቱ ለገሰ፤ ዚነት ሙሃባ፤ መስፍን አበበን የመሳሰሉ ዘፋኞች የተገኙት ከደሴ ነው። ለኢትዮጵያ የቴአትር ጥበብ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ካደረጉትና በሀገር ውስጥ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ እና በሁንጋርያ ቡዳፔሽት ሥልጠናቸውን በጥበቡ ቀስመው የምጀመርያ ዲግሪያቸውን አግኝተው በሃገራቸው ትያትር ቤቶች በመሥራት የሕዝብ ፍቅርንና ሙያዊ ልዕልና ከተጎናፀፍትና፣ በዓለም አቀፍ የፊልም ሥራ በመካፈል ቀደምት ሥፍራን የያዙት የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱም የዚሁ የወሎ (ደሴ) ተወላጅ ናቸው። በከተማይቱ ውስጥ በ 1996 የተገነባ ግዙፍ የወጣቶች ማእከል ይገኛል። ይህ ማእከል ከፍተኛ አገልግሎት እየሰጠ ቢሆንም በቂ እንዳልሆነ ግን ይታመናል። የቤተሰብ መምሪያ እና የሰርከስ ደሴን ጨምሮ በርካታ መካከለኛ እና አነስተኛ የሙዚቃ ባንዶች ይገኛሉ። ከተገነባ በርካታ አመታትን ያሳለፈውና ተገቢውን እድሳት ያላገኘው የ ደሴ እታዲየም በከተማይቱ እምብርት ይገኛል። ይህ እታዲየም እስከቅርብ ጊዜ ድረስ የ ኮምቦልቻ ጨርቃ ጨርቅ የ እግር ኳስ ክለብ የመጫወቻ መዳ ሁኖ አገልግሏል። በዚህም በርካታ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን የማስተናገድ እድል አግኝቷል። መሰረተ ልማት ይህች ከተማ በመሰረተ ልማቱ ረገድ ተረስታ የቆየች ከተማ ናት ማለት ይቻላል። ለዚህም እንደ መንገድ ያሉ መሰረተ ልማቶችን ማንሳት ይቻላል። በቅርቡ ማለትም በ እ.ኤ.አ. 2006 ስራ የጀመረው ወሎ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም መምህር አካለ ወልድ፣ ወይዘሮ ስህን እና ሆጤ በመባል የሚጠሩት ሶስት ከፍተኛ ትምህርት ቤቶች በዚሁ ከተማ ይገኛሉ። ብዙ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶችም ይገኛሉ። ከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተማይቱ የበርካታ የግል ዩኒቨርስቲዎች እና ኮሌጆች መዳረሻ ሆናለች። በደሴ ከተማ ውስጥ ሁለት የመንግስት ሆስፒታሎች ማለትም የደሴ ሪፈራል ሆስፒታል እና ቦሩ ሆስፒታል ይግኛሉ። በግሉ የ ጤና ዘርፍም ሶስት ሆስፒታሎች ማለትም ሰላም ጠቅላላ ሆስፒታል፣ ባቲ ጠቅላላ ሆስፒታል እና ኢትዮ ጠቅላላ ሆስፒታሎችን ጨምሮ በርካታ የግል ክሊኒኮች አሉ። የ ደሴ ከተማ ትልቅ ችግር ተደርጎ ሊወሰድ የሚችለው ይህ ዘርፍ ነው። ከተማይቱ ምንም እንኳን በቅርቡ የከተማው ዋና መንገድ እና የውስጥ ለውስጥ መንገድ በመገንባት ላይ ቢሆንም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ደረጃውን ያልጠበቀና የተጎዳ ባለ አንድ መስመር አስፋልት መንገድ ብቻን ነበር የነበራት። አሁን የተጀመረውና እስከ ነሃሴ መጨረሻ 2002 አመተ ምህረት ይጠናቀቃል የተባለው መንገድ የከተማይቱን ዋና መንገድ ጨምሮ በተለያዩ የውስጥ ለውስጥ ክፍሎች የተዘረጋ ነው። መንገዱ የሚገነባው በ ሁለት አካላት ነው። አንደኛው የከተማይቱ መዘጋጃ ቤት ነው። ይህ ክፍል የሚያስገነባው ዋናውን የመሃል መስመር ሲሆን ይዘቱ ባለ ሁለት (መንታ) መንገድ ነው። ሁለተኛው አካል የሃገሪቱ የመንገድ ትራንስፖርት የሚያስገነባው ሲሆን የከተማይቱን የ ዳር ክፍሎችና ከ አዋሳኝ ከተሞች ጋር የሚያገናኙ መንገዶች ናቸው። የአየር ሁኔታደሴ'' ከተማ በአመዛኙ ቀዝቃዛማ የአየር ጸባይ ያላት ደጋማ ከተማ ናት። በተለይ በክረምት ወራት የሚጥለው ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ እና ውርጭ የተለመደ ነው። በከፍተኛ ቦታ ላይ መገኘቷ ለዚህ ምክንያት ሊሆን ይችላል። በተራራ የተከበበችው ደሴ ለበርካታ እንደ ገብስ፣ አጃ፣ ባቄላ እና ሌሎች የ አዝእርት አይነቶች መብቀያ ናት። በዚህም የደሴ ዙሪያ አከባቢ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ናቸው።
52684
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8C%E1%88%AA%E1%8B%AB%E1%88%8D%20%E1%88%83%E1%8D%8B%E1%8C%84
ፌሪያል ሃፋጄ
ፌሪያል ሃፋጄ (እ.ኤ.አ. የካቲት 20፣ 1967 ተወለደች) ደቡብ አፍሪካዊ ጋዜጠኛ ነች፣ በተከታታይ የፋይናንሺያል ሜይል ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ፣ ሜይል እና ጋርዲያን ፣ ከተማ ፕሬስ (ከጁላይ 2009 እስከ ሐምሌ 2016)፣ ሃፍፖስት ደቡብ አፍሪካ ደቡብ ከዚያም በዴይሊ ማቬሪክ ምክትል አዘጋጅ. አመጣጥ እና ጥናቶች ከህንድ ተወላጅ እና የሙስሊም ሀይማኖት ፣ የአህመድ እና የአየሻ ሃፋጄ ልጅ ፣ ፌሪያል ሃፋጄ ያደገችው በቦስሞንት ፣ በጆሃንስበርግ ባለ ቀለም ከተማ ፣ በዊትዋተርስራንድ ዩኒቨርሲቲ ተምራ በ1989 በኪነጥበብ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመረቀች ። ፌሪያል ከተመረቀች በኋላ በዊክሊ ሜይል በሰልጣኝ ጋዜጠኝነት ለሁለት አመታት ሰርታለች ከዚያም በ1991 የደቡብ አፍሪካ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ተቀላቅላ በቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት እስከ 1994 ድረስ ሰርታለች። እ.ኤ.አ. በ 1994 የፋይናንሺያል ሜይል መጽሔትን ተቀላቀለች እና ለፖለቲካው ክፍል ሀላፊነት ነበረች እና በ 1997 ውስጥ አርታኢ ሆነች ፣ እንደዚህ አይነት ቦታ በመያዝ የመጀመሪያዋ ነጭ ያልሆነች ሴት ነበረች ። እ.ኤ.አ. በ 2003 ሜይል እና ጋርዲያን (የቀድሞ ሳምንታዊ መልእክት) በምክትል አርታኢነት ተቀላቀለች እና ወረቀቱ በዚምባብዌ አሳታሚ ትሬቨር ንኩቤ ከተገዛ ከሁለት ዓመት በኋላ በመጨረሻም በ 2004 ወደ አርታኢ ከፍ ብላ ወጣች ፣ ። እ.ኤ.አ. በ 2006 ሀፋጄ ነቢዩ መሐመድን የሚያሳዩ አወዛጋቢ ካርቶኖችን እንደገና ካተመ በኋላ ዛቻ ደርሶባታል በ2009 የሲቲ ፕሬስ ዋና አዘጋጅ ሆነች። እ.ኤ.አ. በ 2012 ፣ በጃኮብ ዙማ የተሰሩ አስቂኝ ካርቶኖችን አሳትማለች ይህም በራሷ እና በሰራተኞቿ ላይ ጠንካራ ትችት እና ዛቻ ምላሽ እንድትሰጥ አድርጓታል። የመንግስት ሚኒስትር ምስሉን ከድረ-ገጹ ካላነሳው ጋዜጣው እንዲታገድ ጠየቀ። ሁኔታውን ለማቃለል ምስሉን ሰርዛለች, ነገር ግን ይህን በማድረግ በሌሎች ወገኖች ይህን በማድረጋቸው ተተችታለች. ካሰላሰለች በኋላ ለዙማ ደጋፊዎች ስጋት በመገዛቷ ትቆጫለች እና እራሷን እንደ “ ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መሰረታዊ ሰው” በማለት ትቃወማለች ። እ.ኤ.አ. በጥቅምት 2013 ሃፋጄ በአርትኦት ሰራተኞቿ ውስጥ በጥቁር ጋዜጠኞች በትዕቢት እና በዘረኝነት ተከሷታል ምክንያቱም የአርትኦት ክፍሏን በበቂ ሁኔታ ስለማታስተካክል ፣ነገር ግን በወቅቱ 8 ጋዜጠኞች ነበሯት ፣ይህም 5 ጥቁሮች ፣ 3 ነጮች ፣ 4 ሴቶች እና 4 ወንዶች በምላሹም ተቃዋሚዎቿን ጃኮብ ዙማን እንደምታይ አላስተናግድም ብለው የሚከሷት ተቃዋሚዎቿ ራሳቸው ዘረኞች ናቸው ስትል መለሰች። ከዚያም በሃፋጄ ላይ ቅሬታ አቅርበዋል በመጨረሻም አስተያየቱን አቋርጦ ይቅርታ ጠየቀች , ። እ.ኤ.አ. በ 2015 እሷም የደቡብ አፍሪካን ታሪክ እና አሁን ባለው ስሜት ቀስቃሽ ጥያቄን ስትመረምር ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነጮች ባይኖሩስ? ? ጥቁሮች ለተሻለ የሀብት ክፍፍል ምስጋና ይግባቸው (አይደለም ብላ ደመደመች) ሀብታሞች ወይም ድሆች ይሆኑ ነበር። መጽሐፉ ዓመት በኬፕ ታውን ዩኒቨርሲቲ የሴሲል ሮድስን ሐውልት በማፍረስ ረገድ ተሳክቶለታል ፣ የሀገሪቱን ተምሳሌታዊነት እና የአንግሎ-ሳክሰን ባህልን እንዲሁም ስምምነትን እና ሽግግሩን ድርድር ይጠይቃል ። በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ከአፓርታይድ መውጣት በተለይም ከአዲሱ የድህረ-አፓርታይድ ትውልድ ጋር እራሷን እንዳጣች ትናገራለች ብላ ታምናለች የነጭነት ፅንሰ-ሀሳብ የተጠናወተው የነጮች መብት እየተባለ የሚጠራውን ውግዘት እና ያለፈው ትውልድ ያመጣውን ስምምነት ውድቅ በማድረግ ነው። , , ። በደቡብ አፍሪካ ሃፊንግተን ፖስት ውስጥ ለሁለት አመታት አጭር ቆይታ ከቆየች በኋላ በ2018 ዴይሊ ማቬሪክን ተቀላቅላለች። ጁሊየስ ማሌማ ፕሬዚደንት ሲሪል ራማፎሳን ለመተቸት ማንም አልፈቀደም ያለው የጋዜጠኞች ስብስብ አካል አድርጎ ለይቷታል፣ ከራንጄኒ ሙኑሳሚ ፣ ማክስ ዱ ፕሬዝ እና ሌሎች ጥቂት ሰዎች ጋር በመጥቀስ ከዚያም እነሱን ለመመርመር እና ለማስፈራራት . የግል ሕይወት ፌሪያል ሃፋጄ ከፖል ስቶበር፣ አምደኛ እና የሜይል እና ጠባቂ ምክትል ዳይሬክተር ጋር አግብቷል። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነጮች ባይኖሩስ? ? ፣ ፓን ማክሚላን ኤስኤ ፣ 2015 ማስታወሻዎች እና ማጣቀሻዎች ፌሪያል ሀፋጄ ፣ደቡብአፍሪካ፣ሲፒጄ ጋዜጠኞች ሀፋጄን በዘረኝነት ከሰሷቸው፣ የፌሪያል ሀፋጄ የዘረኝነት ስም ማጥፋት ክስ ተጠናቀቀ፣ የስራ ቀን፣ 16 በኤስኤ ውስጥ ነጭ ሰዎች ባይኖሩስ? ፣ ህዳር 27፣ 2015 ሊን ፣ « ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነጭ ሰዎች ባይኖሩስ? »፣ ሱር 8 ዲሴምበር 2015) ዳን ሮድ፣ « ፡ ጸረ-ነጭ ደፋር አዎንታዊ እርምጃ ልዕልት»፣ ሱር (እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 11 ቀን 2021 ደርሷል) ፌሪያል ሀፋጄ ወደ 2018 ይሄዳል ለተቃዋሚዎች ተጠያቂ የሆኑትን የጥላቻ ጋዜጠኞች ማነሳሳትን አውግዟል, ድንበር የለሽ ዘጋቢዎች, ኖቬምበር 28, 2018 የህይወት ታሪክ ፣ በአጭሩ የህይወት ታሪክ የጌጥ አዶ ደቡብ አፍሪካ ፖርታል [[መደብ:የሲፒጄ አለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት ሽልማት አሸናፊዎች]] [[መደብ:1967 ልደት]] [[መደብ:ሕያዋን ሰዎች]] [[መደብ:ከጆሃንስበርግ የመጡ ሰዎች]] [[መደብ:የደቡብ አፍሪካ ጋዜጠኞች]] [[መደብ:የደቡብ አፍሪካ ጋዜጣ አዘጋጆች]] [[መደብ:የደቡብ አፍሪካ ጸሐፊዎች]] [[መደብ:የዊትዋተርስራንድ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች]]
48354
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%B8%E1%88%90%E1%8D%8C%20%E1%89%B5%E1%8B%95%E1%8B%9B%E1%8B%9D%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A8%20%E1%88%A5%E1%88%8B%E1%88%B4%20%E1%8B%88%E1%88%8D%E1%8B%B0%20%E1%8A%A0%E1%88%A8%E1%8C%8B%E1%8B%8A
ጸሐፌ ትዕዛዝ ገብረ ሥላሴ ወልደ አረጋዊ
ጸሐፌ ትዕዛዝ ገብረ ሥላሴ ወልደ አረጋዊ በ፩፰፻፴፯ ዓ.ም. ከአቶ ወልደ አረጋዊና ከወይዘሮ ወለተ ጊዮርጊስ በደብረ ብርሃን አካባቢ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ሲፈቅድላቸውም በአንኮበር ከተማ አስቀድመው የንባብ፤ ቀጥሎ የዜማ፤ የቅኔና የትርጓሜ ሐዲሳት ትምህርታችውን ተራ በተራ ተማሩ።በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን፤ ከኢትዮጵያ መንግሥት የጽሕፈት ሚኒስተርነት መዓርግ ጋር የአዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ንቡረ ዕድነት ሹመት ተሰጥቶአቸዋል። በቅኔና በሥነ ጽሑፍ ሞያቸውም እጅግ የሚመሰገኑ ታላቅ ሊቅ ስለበሩ፡ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የኢትዮጵያ ሊቃውንትን ቅኔ አሰባስበው እንዲያሳትሙ ያነቃቁአቸውና ያበረታቱአቸው እንደነበር የታሪክ ዘገባዎች ያረጋግጣሉ። በዚሁም በታተመው የቅኔ መጽሐፍ ውስጥ በራሳቸው የተቀነባበሩት ልዩ ልዩ ቅኔዎች በከፍተኛ ሊቅነት መድረክ ላይ የቆሙ ለመሆናቸው ማረጋገጫዎች ናቸው። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ በቤተ ክህነትም ሆነ ቤተ መንግሥት የክበረ አገልግሎት ለማበርከት በነበራቸው ፈላጎት መሠረት፤ በመጀመሪያ የንጉሥ ምኒልክ ባለቤት ለነበሩት ለወይዘሮ ባፈና ልዩ ጸሕፊ በመሆን በቅንነትና መታማኝነት አገልግሎታቸውን ጀመሩ። በኋላም አለቃ ወልደ መድኅን ይባሉ የነበሩት የዳግማዊ ምኒልክ ጸሐፌ ትእዛዝ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፡ በ፩፰፻፷፬ ዓ.ም. "ጸሐፌ ትእዛዝ" ተብለው ተሾሙና የቤተ ክርስቲያንን ሊቃውንት ወደ ቤተ መንግሥት ለማቅረብና ቁልፍ ቁልፍ ይሆኑትንም ከፍተኛ ቦታዎች ለማስያዝ የመሸጋገሪያ ደልድይ ምክንያት ሆኑ። ይኽውም በዚያን ጊዜ የኢትዮጵያ መንግሥት ሥራ አብዛኛውን የሚካሄደው በኢትዮጵያ ሊቃውንት ስለነበር ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የትምህርት ሚኒስቴር በመሆን በመላ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ትምህርት እንዲሰጥ በተጨማሪም የፍርድ ሚኒስቴርነቱንም ሥልጣን በሥራ በመተርጎም በከፍተኛ የነፍስ ግዳይ ወንጀል ላይ እንዃ ሳይቀር “ለሞት የሚያበቃ ወንጀል ነው ወይስ አያበቃውም” ብላ የመጨረሻውን ፍርድ እንዲጸድቅ በማድረግ ለኢትዮጵያ መንግሥት ታላቅ የሥራ ድርሻ በይበልጥ ለማበርከት የቻለችው በጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ የሥራ ዘመን እንደሆነ ይነገራል። ጸሐፌ ትእዛዝ የተማረና የተመራመረ፤ በአስተያየቱ የበሰለ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ካጋጠማቸው ለዚያ ምሁር ቀለብ ወይም ተገቢውን ሹመት ሳይሰጡ በፍጹም እንቅልፍ አይወስዳቸውም ነበር የሚሉ ብዙዎች ናቸው፡ ይሁን እንጂ ለሹመት የሚያጩትን እያንዳንዱን የኢትዮጵያ ሊቅ በጠባይ ይዘቱ በኩል ምን ዓይነት አቋም እንዳለው የማጥናቱና የመከታተሉን ጉዳይ ቅድሚያ ይሰጡት እንደነበልም ይነገራል። ያኽውም ዛሬ ሾሞ ነገ መሻሩን እየተሳቀቁና እንደ ነዉርም እየቆጠሩት መሆኑ ይተረካል። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ በጸሐፌ ትዛዝነቱ መዓርግ ለሠላሳ ስድስት ዓመት ያህል በትጋት በቅንነትና በታማኝነት ሲሰሩ ከኖሩ በኋላ ያበረከቱት የአገልግሎት አስተዋጻኦ ተገምግሞ፤ በ፩፱፻ ዓመተ ምሕረት ለመጀመሪያ ጊዜ በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን የሚኒስትርነት ሹመት ሲጀመር በዚያው አስቀድሞ ይዘውት የነበረው ሥራቸው ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት የጽሕፈት ሚኒስቴር ሚኒስትር በመባል ከፍተኛ መዓረግ አገኙ። በዚህም ወቅት በተጨማሪ የእንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤልን እንዲያስተዳድሩ ተሾመዋል። ከዚህም ቀደም ብሎ በ፩፰፻፺፬ ዓ.ም ዳግማዊ ምኒልክ የአዲስ ዓለም ዳግማዊት ጽዮንን ቤተ ክርስቲያን በሚገባ አሳንፀው ሥርዓቷንም ሆን መዓርጓን እንደ አክሱም ተመሳሳይ የሆነ የንቡረ ዕድነቱን ሹመት ለማን እንደሚሰጡት አሳስቦአቸው ነበርና፤ መኳንንቱን ሊቃውንቱ ለዚህ ሹመት ተገቢ የሆነውን ሰው በስብሰባ መርጠው እንዲያቀቡላቸው ትእዛዝ ሰጡ። ለሚመረጠው ሰው ባለሟልነትን ከሊቅነት ጋር አጣምሮ የያዘ መሆን እንደሚገባው መመሪያ ሰጡ፤ ይህም ያስፈለገበት ምክንያት፤ “በባለሟልነቱ ይህ ቀረ ያ ጎደለ እንዲህ እንዲህ ያለው ያስፈልጋል ብሎ ደፍሮ እንዲያስታውሰኝ፤ በትምህርቱ ካህናቱንም ሆነ ምእመናኑን በእውቀት በምርምር እንዲያንፅ፤ መናፍቃንን እንዲገስጽ ነው” አሉ። ይኽንኑ መመሪያ የተቀበሉት መኳንንትና ሊቃውንትም የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤልን፤ አሁን መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ የተባለውን የቀድሞውን መካነ ሥላሴን አድባራት፤ በየተራ የተሾሙትን ታላቁን ሊቅ አለቃ ወልደ ማሪያምን በተባበረ ድምፅ መርጠው አሳባቸውን አቀረቡ። ዳግማዊ ምኒልክ በባለሙዋልነትም ሆነ በትምህርት የተሟላ ይዘት ያላቸው አለቃ ወልደ ማርያምን ለአዲሱ ዓለም ደብር ተሿሚ የራስ ወርቅ፤ የወርቅ ጫማ፤ የወርቅ ላንቃ ካባ፤ የወርቅ መቋሚያ፤ የወርቅ ጸናጽልና የወርቅ ወንበር በአስቸኳይ ተዘጋጅቶ ንቡረ ዕድነቱ አንዲሰጣቸው አዘዙ። በዚህም ወቅት ዳግማዊ ምኒልክ አንድ ነገር ትዝ አላቸው፤ ይኸውም የቤተ ክህነቱን ሥርዓት በሚገባ ጠንቅቀው የሚያውቁትና በሀሳብ አቅራቢነት ችሎታቸውም ተደማጭነት የነበራቸው የአፈ ንጉሥ እስጢፋኖስ በጉባኤው አለመገኘት ነበር። በመሆኑም አፈ ንጉሡን ወዲያውኑ አስጠርተው የጥናቱንና የውሳኔውን ሁኔታ ቢያስረዱአቸው፤ የሊቁን ተፈላጊነት እንደሚያምኑበትና የቀረበውንም የውሳኔ ሀሳብ እንድሚስማሙበት አረጋገጡ። “ብቻ” እሱ አፈ ንጉሥ እስጢፋኖስ “ንቡረ ዕዱ በታላላቅ በዓላት የወርቅ ጫማ መጫማት አለበት፤ ስለዚህ የሊቁ አንድ እግራቸው በሽተኛ ነውና፤ የወርቅ ጫማ ለማድረግ ያስቸግር የመስለለኛል” አሉ። በዚህም ወቅት በአዲስ ዓለም ዳግማዊት ጽዮን ደብር ምንም ዓይነት ነቀፌታን ያስከተለ ነጥብ እንዲገኝ የማይፈልጉት ዳግማዊ ምኒልክ ከቀሩት መማከርት ያመለጠው ሀሳብ ከአፈ ንጉሥ በመገኘቱ እጅግ አድርገው አደነቁና የአለቃ ወልደ ማርያምን ሹመት በዚሁ ብቻ ውድቅ አድርገው “የተደከመበትን ሀሳብና ጥናት ማፍረስ ብቻ ሳይሆን እንደገና ሌላ አዲስ ሕንፃ ማነፅ ያስፈልግሃልና አንተ በበኩልህ ማን ቢሆን ይሻላል ትላለህ ብለው አፈ ንጉሡን ቢጠይቁአቸው፤ እንደ እኔማ ቢሆን በአንድ በኩል ደግሞ በቅርብ የሚያውቁትና ጠባዮን የመረመሩት ጸሐፊ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ስለሆነ በዚሁ በያዘው ሹመት ላይ ንብረ ዕድነቱ ቢፈቀድለት ደስ ይለኛል” ሲሉ ሀሳብ አቀረቡ። በዚህ ሀሳብ ላይ ምንም ዓይነት ተቃውሞ ለመሰንዘር ያልፈለጉ ዳግማዊ ምኒልክ፤ ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ የክብር ልብሱን ለብሰው፤ የወርቁን ጫማ ተጫምተውንና የራስ ወርቁን ደፍተው እንዲቀርቡ፤ መዃንንቱና ሊቃውንቱም እንዲሰበሰቡ ውዲያው አዘዙ። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ እንደሚሾሙ ተነግሯቸው፡ የክብር ልብስ ለብሰው እጅ ለመንሣት ሲቀርቡ ዳግማዊ ምኒልክ “ገብረሥላሴ!! የመረጡህ ታማኝነትህና አገልግሎትህ ተባብረው ነው፤ እኔ አሰተናባሪና አዳይ እንጂ፤ ሰጪው እግዚአብሔር ነው” ስለ አሉዋቸው በዚህ አነጋገር ልባቸው የተነካ ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ እያለቀሱ “ከትቢያ ላይ አንስተው ሰው ቢያደርጉኝ፤ ሰው ሆንኩ እንጂ ለርስዎ ስጦታ የኔ ታማኝነትና አገልግሎት ምን ይመጥነዋል” በማለት ዕንባቸው አልታገድ አለ። በዚህ ወቅት ፈሊጠኛው አፈ ንጉሥ እስጢፋኖስ “ሲሾሙህ ያለቀስክ ቢሽሩህ ምን ልትል ነው” ? ብለው ሁኑንም ስለ አሳቁት የጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ኃዘን በቀልድ ተለውጦ፤ በቤት መንግሥቱ እንዲሁም በተሿሚው መኖሪያ ቤት ደስታ ሆነ። የዳግማዊ ምኒልክ ጸሐፌ ትእዛዝ፤ ንቡረዕድ ገብረ ሥላሴም ከጥቂት ቀናት በኋላ በብዙዎች ሊቃውንትን መዃንንት ታጅበው በዘመኑ የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጥ በነበረው ሠረገላ ከባለቤታቸው ጋር ሆነው በአዲስ ዓለም ዳገማዊት ደብረ ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ሲደርሱ፤ ጥንግ ድርብ፡ ባለ ወርቅ ካባና ቀሚስ ለብሰው የብር መቋሚያና ጽናጽል ይዘው የሚጠባበቁት ካህናት በይባቤ ተቀበሉዋቸው። የባለቤታቸውም ስም “ወይዘሮ ዕሤተ” ስለነበር ሊቃውንቱ ይኽንኑ ሁኔታ በማስመልከትና ምሥጢሩን ከምሥጢር በማስተባበር “ዘዕሤቱ ምሰሌሁ ወምግባሩ ቅድመ ገጹ ገብረ ሥላሴ ጸሐፌ ትእዛዙ ለዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ጸዮን ጻድቅ ወየዋህ ምኒልክ” የሚል ግሥ ገሥሠው እንደወረቡና በዚሁም በጣም እንደተመሰገኑበት ይነገራል። በዚህም ወቅት አዲስ ዓለም እንደ ስሟ በእውነቱ አዲስ ዓለም ሆነች፤ የመጀመሪያው ንቡረ ዕድ ገብረ ሥላሴ ፤ የብሉያት፤ የሐዲሳት፤ የሊቃውነት ትርጓሜ፤ የዜማና የቅኔ መምህራን ሊቃውንትን፤ እጥፍ እየሆኑ በአዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ጉባዔ ዘርግተው እንዲያስተምሩ አደረጉ። በዚህ ጊዜ ነበር ታዋቂ የሐዲስ የነበሩት ሊቁ ወልደ ሚካኤል በአዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ጉባዔ ዘርግተው ትርጓሜ ሐዲሳትን ሲያስተምሩ የነበረው። የብሉዩና የቅኔው መምህር ስመ ጥሩው አለቃ ተጠምቆም በዚሁ ደብር ጉባዔ ዘርግተው ያስተምሩ ነበር። ጸሐፌ ትእዛዝ በትምህርትና በመልካም ጠባይ የተማመኑባቸውን ሊቃውንት በተከታታይ በአዲስ ዓለም፤ በእንጦጦ ራጉኤል፤ በሌሎቹም ታላላቅ አድባአት ሁሉ በመመደባቸው ይልቁንም በጎንደር፤ በጎንደር፤ በጎጃም፤ በሸዋ የሚገኙትን ሊቃውንት ደጅ ሳይጠኑ ራሳቸው ካሉበት እያስፈለጉ በገዳማትንና በአድባራት እንዲሾሙና የተወሰነ መተዳደሪያ እየተሰጣቸው እንዲያስተምሩ በማድረጋቸው ከፍ ያለውን መንፈሳዊ ዝና ለማትረፍ ቻሉ። በአዲስ ዓለም የግል ቤታቸውን ከቤተልሔም ላስመጧቸው፤ ለመዝገብ ድጓው መምህር ለሊቀ ቴዎድሮስ ሰጡ፤ የመኖሪያ ቤታቸው ማዕድ በሊቃውንት ብቻ የተከበበ በመሆኑ፤ ምግብ ተጀምሮ ከፍ እስኪል ድረስ ከሊቃውንቱ ጋር ስለ ትርጓሜ መጻሕፍት ምሥጢር ከመነጋገርና ሀሳብ ለሀሳብ ከመለዋወጥ በቀር ሌላ ዓለማዊ ነገር አይነገርም ነበር እየተባለ ይተረካል። ንቡረዕድ ገብረ ሥላሴ ሠርቶ በማሰራት፤ የሥራን ክቡርነትም አውቆ በማሳወቅ፤ በጣም የተመሰገኑ እንደ ነበሩ ታሪክ ያረጋግጣል። ለምሳሌ አንድ የግል ጸሐፊያቸው ሆኖ በቤታቸው የሚኖር ሠራተኛ ለሥራ እየፈለጉት ሊያገኙት ስለ አልቻሉ ከመገሠጽም ሆነ በገንዘብ ከመቅጣት የተሻለ መስሎ የታያቸውን ልዩ ዘዴ መረጡ፤ የኸውም ቀጥሎ የትመለከተው ነው፤ አንድ ባዶ የሆነ ኤንቬሎፕ አሽገው ጧት ከቤታቸው ወደ ቤተ መንግሥት በበቅሎ ሲሔዱ የኸንን ከዚያው ከግቢ ስደርስ ትሰጠኛለህና የዘህ ተከተለኝ ብለውት ከቤተ መንግሥት ደርሰው ከበቅሎ ሲወርዱ ቢሰጣቸው ወደ ቤት ስንመለስ ትሰጠኛለህ አሉት። በዚህም ዓይነት ከቤት ሊሰጣቸው ከቤተ መንግሥት፤ ከቤት መንግሥት ሲሰጣቸው ከቤት እያሉ ለአሥራ አምስት ቀናት ያህል እንዳይለያቸው አደረጉ፤ ከዚያ በኋላ ግን እየወተወተ ስለ አስቸገራቸው ለልዩ ጸሐፊያቸው እንዲሰጥ አዘዙት። ልዩ ጽሐፊውም ተቀብሎ ቢከፍተው ባዶ ኤንቬኖፕ ሆኖ ስለ አገኘው "የሰጡህም ጽሑፍ ከሥራህ ላይ እየታጣህ ስለ አስቸገርክ በዘዴ ትምህርት ሊሰጡህ ነውና ለወደፊቱ ተጠንቀቅ" ብሎ መክረው። ጸሐፊውም ሁኔታውን ስለ ተረዳው የሥራን ክቡርነት ዐውቆ ጠባዩን ሊያሻሻል እንደቻለ ይነገራል። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ "የታሪክ ዘመን ዘዳግማዊ ምኒልክ" ተብሎ በ፩፱፻፶፱ ዓ.ም የታተመውን መጽሐፍ ቀደም ብለው ረቂቁን አዘጋጅተው፤ በአንዳንድ ገዳማትና አድባራት እንዲቀመጥ አድርገው እንደ ነበር የኸው መጽሐፍ ያስረዳል። ስለዚህ የዳግማዊ ምኒልክ ጸሐፌ ትእዛዝ የነበሩት፤ ንቡረ ዕድ ገብረ ሥላሴ ከዚህ በላይ በተዘረዘረው የሥራ ፍሬአቸው፤ ለኢትዮጵያ ቤተ መንግሥትና ቤተ ክህነት ባለውለታ ናቸው ለማለት ይቻላል። ይኸንንና ይኸንን በመሳሰለው ሁኔታ ሕይወታቸውን በታሪክና በሥራ ሲያስጌጡ ከኖሩ በኋላ ጥቅምት ፪፯ ቀን ፩፱፻፭ ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተው ባቀኑት፤ ባፀኑትና ባስተዳደሩት በእንጦጦ ራጉኤል ደብር የቀብራቸው ሥነ ሥርዓት ተፈጽሟል።
9388
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%AB%E1%89%B2%E1%8A%AB%E1%8A%95%20%E1%8A%A8%E1%89%B0%E1%88%9B
ቫቲካን ከተማ
ቫቲካን ሲቲ (/ /፣ በይፋ የቫቲካን ከተማ ግዛት (ጣሊያን፡ ስታቶ ዴላ ሲትታ ዴል ቫቲካኖ፤ [] ላቲን፡ ስታተስ ሲቪታቲስ ቫቲካንኤ) በሮም፣ ጣሊያን ውስጥ የሚገኝ ራሱን የቻለ የከተማ-ግዛት እና መገኛ ነው። የቫቲካን ከተማ ግዛት፣ በቀላሉ ቫቲካን በመባልም የምትታወቀው፣ ከጣሊያን በላተራን ስምምነት ነጻ ሆነች፣ እና በቅድስት መንበር “ሙሉ ባለቤትነት፣ ብቸኛ ግዛት እና ሉዓላዊ ሥልጣን እና ሥልጣን” ስር ያለ የተለየ ግዛት ነው፣ እራሷ የአለም አቀፍ ሉዓላዊ አካል ነች። የከተማውን ግዛት ጊዜያዊ፣ዲፕሎማሲያዊ እና መንፈሳዊ ነፃነትን የሚጠብቅ ህግ፣49 ሄክታር (121 ኤከር) የቆዳ ስፋት እና 825 አካባቢ ህዝብ ያላት፣ በአካባቢው እና በህዝብ ብዛት በአለም ላይ ትንሹ ግዛት ነች። ቅድስት መንበር፣ የቫቲካን ከተማ መንግሥት የቤተክርስቲያን ወይም የሳሰርዶታል-ንጉሣዊ መንግሥት (የቲኦክራሲ ዓይነት) በሮማ ሊቀ ጳጳስ እና በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ራስ የሚመራ ሊቀ ጳጳስ ነው። ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ሁሉም የቫሪዮ የካቶሊክ ቀሳውስት ናቸው። የኛ ብሄራዊ አመጣጥ። ከአቪኞን ፓፓሲ በኋላ ጳጳሳቱ በአሁኑ ጊዜ በቫቲካን ከተማ ውስጥ በሚገኘው ሐዋርያዊ ቤተ መንግሥት ውስጥ ይኖራሉ ፣ ምንም እንኳን አንዳንድ ጊዜ በሮም ወይም በሌላ ቦታ በኲሪናል ቤተ መንግሥት ይኖሩ ነበር። ቅድስት መንበር የጀመረችው ከጥንት ክርስትና ጀምሮ ሲሆን በዓለም ዙሪያ 1.329 ቢሊዮን የተጠመቁ የካቶሊክ ክርስቲያኖችን በ2018 በላቲን ቤተክርስቲያን እና በ23 የምስራቅ ካቶሊኮች አብያተ ክርስቲያናት ያላት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ዋና ኤጲስ ቆጶሳት ነው። በሌላ በኩል የቫቲካን ከተማ ነፃ መንግሥት በየካቲት 11 ቀን 1929 በቅድስት መንበር እና በኢጣሊያ መካከል በተደረገው የላተራን ስምምነት የተቋቋመ ሲሆን ይህም እንደ አዲስ ፍጥረት ነው እንጂ በጣም ትልቅ ለሆኑት የጳጳሳት ግዛቶች መገለጫ አይደለም ፣ እሱም ቀደም ሲል ማዕከላዊ ጣሊያንን ያቀፈ ነበር። በቫቲካን ከተማ ውስጥ እንደ የቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን፣ የሲስቲን ቤተ ክርስቲያን እና የቫቲካን ሙዚየሞች ያሉ ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ቦታዎች አሉ። በዓለም ላይ በጣም ታዋቂ የሆኑ ሥዕሎችንና ቅርጻ ቅርጾችን ያሳያሉ። የቫቲካን ከተማ ልዩ ኢኮኖሚ የሚደገፈው ከምእመናን በሚሰጡ መዋጮዎች፣ በፖስታ ቴምብሮች እና በመታሰቢያ ዕቃዎች ሽያጭ፣ ወደ ሙዚየሞች የመግባት ክፍያዎች እና የሕትመት ሽያጭ ነው። "ቫቲካን" የሚለው ስም ቀደም ሲል በሮማ ሪፐብሊክ ዘመን ለኤጀር ቫቲካነስ፣ ከሮማ ከተማ ማዶ በቲቤር ምዕራብ ዳርቻ ላይ ረግረጋማ አካባቢ ፣ በጃኒኩለም ፣ በቫቲካን ሂል እና በሞንቴ ማሪዮ መካከል ይገኛል ። ወደ አቬንቲኔ ኮረብታ እና እስከ ክሪሜራ ክሪክ መገናኛ ድረስ. የኢትሩስካውያን ከተማ ቬኢ (ሌላኛው የአገር ቫቲካኑስ መጠሪያ ሪፓ ቬየንታና ወይም ሪፓ ኢትሩስካ) እና በቲቤር ጎርፍ ስለተፈፀመባት ሮማውያን ይህ በመጀመሪያ ሰው የማይኖርበትን የሮማን ከተማ ቬኢ ከሚባለው አካባቢ በመጣችበት ምክንያት እና አስጸያፊ. በተለይ ዝቅተኛ ጥራት ያለው የቫቲካን ወይን፣ አካባቢው ከተስተካከለ በኋላም ቢሆን፣ ገጣሚው ማርሻል (40 - በ102 እና 104 ዓ.ም. መካከል) ላይ አስተያየት ሰጥቷል። ታሲተስ በ69 ዓ.ም የአራቱ ንጉሠ ነገሥታት ዘመን፣ እ.ኤ.አ. ቪቴሊየስን ወደ ስልጣን ያመጣው የሰሜኑ ጦር ሮም ደረሰ፣ “ብዙ ቁጥር ያለው ክፍል ጤናማ ባልሆኑ የቫቲካን አውራጃዎች ውስጥ ሰፈረ፣ ይህም በተለመደው ወታደር መካከል ብዙ ሞትን አስከትሏል፣ እና ቲበር በአቅራቢያው ስለነበር ጋውል እና ጀርመኖች መሸከም አልቻሉም። ከጅረት የጠጡት ሙቀትና ስግብግብነት አስቀድሞ ለበሽታ ቀላል የሆነውን ሰውነታቸውን አዳክሟል። አጀር ቫቲካነስ የሚለው ስም የተመሰከረለት እስከ 1ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዓ.ም ድረስ ነው፡ ከዚያ በኋላ ሌላ ከፍተኛ ስም ታየ፣ ቫቲካነስ፣ ይህም በጣም የተከለከለ አካባቢን የሚያመለክት ነው፡ የቫቲካን ኮረብታ፣ የዛሬው የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ እና ምናልባትም የዛሬው በቪያ ዴላ ኮንሲልያዚዮን።በሮማ ኢምፓየር ስር፣ ብዙ ቪላዎች እዚያ ተገንብተው ነበር፣ ከክርስቶስ ልደት በፊት 14-18 ኦክቶበር 33) አካባቢውን ካሟጠጠ በኋላ የአትክልት ስፍራዎቿን በ1ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ዘርግታለች። በ40 ዓ.ም ልጇ ንጉሠ ነገሥት ካሊጉላ (31 ኦገስት 12-24 ጃንዋሪ 41፣ አር. 37–41) በአትክልቶቿ ውስጥ ሰርከስ ለሠረገላ አሽከርካሪዎች (40 ዓ.ም) ሠራ በኋላ በኔሮ የተጠናቀቀው ሰርከስ ጋይ እና ኔሮኒስ , በተለምዶ ፣ በቀላሉ ፣ የሰርከስ ኦፍ ኔሮ ተብሎ ይጠራል። የቫቲካን ሀውልት በመጀመሪያ በካሊጉላ የተወሰደው የሰርከሱን አከርካሪ ለማስጌጥ ከግብፅ ሄሊዮፖሊስ የተወሰደ ሲሆን በዚህም ምክንያት የመጨረሻው የሚታየው ቅሪት ነው። ይህ አካባቢ በ64 ዓ.ም ከታላቁ የሮም እሳት በኋላ የብዙ ክርስቲያኖች የሰማዕትነት ቦታ ሆነ።የጥንት ትውፊት እንደሚለው በዚህ ሰርከስ ቅዱስ ጴጥሮስ ተገልብጦ የተሰቀለው። ከሰርከሱ ተቃራኒ በቪያ ኮርኔሊያ የተነጠለ የመቃብር ቦታ ነበር። የቀብር ሐውልቶች እና መካነ መቃብሮች እንዲሁም ትናንሽ መቃብሮች እንዲሁም የጣዖት አምላኪዎች መሠዊያዎች በ 4 ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ የቅዱስ ጴጥሮስ ቆስጠንጢኖስ ቤተመቅደስ ከመገንባቱ በፊት የቆዩ ነበሩ ። ለፍርግያ አምላክ ሲቤል እና አጋሯ አቲስ የተሰጠ መቅደስ የጥንት የቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ መቅደስ በአቅራቢያው ከተሰራ ከረጅም ጊዜ በኋላ ንቁ ሆኖ ቆይቷል። የዚህ ጥንታዊ ኔክሮፖሊስ ቅሪቶች በዘመናት ውስጥ በተለያዩ ሊቃነ ጳጳሳት እድሳት ላይ አልፎ አልፎ ታይተዋል ፣ በህዳሴው ዘመን ድግግሞሹ እየጨመረ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፒዮስ 12ኛ ትእዛዝ ከ1939 እስከ 1941 ድረስ ቁፋሮ እስኪያገኝ ድረስ የቁስጥንጥንያ ቤተ ክርስቲያን በ326 ተገንብቷል በዚያ መቃብር የተቀበረው የቅዱስ ጴጥሮስ መቃብር እንደሆነ ይታመን ነበር።ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ከባዚሊካ እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ አካባቢው በይበልጥ የሚበዛበት ሆነ። በጳጳስ ሲምማከስ ሊቀ ጳጳስ (498-514 የነገሠ) በ5ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ቤተ መንግሥት ተሠራ። የመሬት አቀማመጥ "ቫቲካን" የሚለው ስም ቀደም ሲል በሮማ ሪፐብሊክ ዘመን ለኤጀር ቫቲካነስ፣ ከሮማ ከተማ ማዶ በቲቤር ምዕራብ ዳርቻ ላይ ረግረጋማ አካባቢ ፣ በጃኒኩለም ፣ በቫቲካን ሂል እና በሞንቴ ማሪዮ መካከል ይገኛል ። ወደ አቬንቲኔ ኮረብታ እና እስከ ክሪሜራ ክሪክ መገናኛ ድረስ. የቫቲካን ከተማ ግዛት የቫቲካን ኮረብታ አካል ነው, እና በአቅራቢያው ያለው የቀድሞ የቫቲካን መስኮች. የቅዱስ ጴጥሮስ ባሲሊካ፣ ሐዋርያዊ ቤተ መንግሥት፣ ሲስቲን ቤተ ክርስቲያን፣ ቤተ መዘክሮች ከተለያዩ ሕንፃዎች ጋር የተገነቡት በዚህ ክልል ነው። አካባቢው እስከ 1929 ድረስ የቦርጎ የሮማውያን ሪዮን አካል ነበር። ከከተማይቱ ተነጥሎ በቲቤር ወንዝ በስተ ምዕራብ ዳርቻ ላይ፣ አካባቢው በሊዮ አራተኛ ቅጥር ውስጥ በመካተት ከከተማው ወጣ ብሎ ነበር ። -855)፣ እና በኋላ በጳውሎስ ፣ በፒየስ አራተኛ እና የከተማ ስምንተኛ በተገነቡት አሁን ባለው የማጠናከሪያ ግድግዳዎች ተዘርግተዋል።የ1929 የላተራን ስምምነት ለግዛቱ ቅርፁን የሰጠው ሲዘጋጅ፣ የታቀደው የግዛት ወሰን አብዛኛው በዚህ ሉፕ የታሸገ በመሆኑ ተጽዕኖ አሳድሯል። ለአንዳንድ የድንበሩ ትራክቶች ምንም ግድግዳ አልነበረም, ነገር ግን የአንዳንድ ሕንፃዎች መስመር የድንበሩን ክፍል ያሟላል, እና ለትንሽ የድንበሩ ክፍል ዘመናዊ ግድግዳ ተሠርቷል. ግዛቱ ፒያሳ ፒዮ 12ኛ የሚነካው ከጣሊያን ግዛት በነጭ መስመር ብቻ የሚለየው የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይን ያጠቃልላል። የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ከቲቤር አቅራቢያ ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ በሚወስደው በቪያ ዴላ ኮንሲልያዚዮን በኩል ይደርሳል። ይህ ታላቅ አቀራረብ በቤኒቶ ሙሶሎኒ የተገነባው የላተራን ስምምነት ከተጠናቀቀ በኋላ ነው። በላተራን ስምምነት መሠረት፣ በጣሊያን ግዛት ውስጥ የሚገኙ የቅድስት መንበር አንዳንድ ንብረቶች በተለይም የካስቴል ጋንዶልፎ ጳጳስ ቤተ መንግሥት እና ዋና ዋና ባሲሊካዎች ከውጭ አገር ኤምባሲዎች ጋር ተመሳሳይነት አላቸው። እነዚህ ንብረቶች በመላው ሮም እና ኢጣሊያ ተበታትነው የሚገኙት ለቅድስት መንበር ባህሪ እና ተልእኮ አስፈላጊ የሆኑ ቢሮዎችን እና ተቋማትን አኖሩ። ካስቴል ጋንዶልፎ እና ስማቸው ባሲሊካዎች የሚጠበቁት በቫቲካን ግዛት በፖሊስ ወኪሎች እንጂ በጣሊያን ፖሊስ አይደለም። በላተራን ስምምነት (አንቀጽ 3) የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ወደ ባሲሊካ የሚወስዱትን ደረጃዎች ሳይጨምር በመደበኛነት በጣሊያን ፖሊሶች ቁጥጥር ይደረግበታል። ከአካባቢው የጣሊያን ግዛት ወደ ቫቲካን ከተማ ለሚገቡ ጎብኚዎች የፓስፖርት ቁጥጥሮች የሉም። ወደ ሴንት ፒተር አደባባይ እና ባሲሊካ እና ጳጳስ አጠቃላይ ታዳሚዎች በተገኙበት ወደሚገኝበት አዳራሽ ነፃ የህዝብ መዳረሻ አለ። ለእነዚህ ታዳሚዎች እና በሴንት ፒተር ባዚሊካ እና አደባባይ ላሉ ዋና ዋና ሥርዓቶች ትኬቶችን አስቀድመው ማግኘት አለባቸው። የሲስቲን ቻፕልን የሚያካትተው የቫቲካን ሙዚየሞች አብዛኛውን ጊዜ የመግቢያ ክፍያ ያስከፍላሉ። የአትክልት ስፍራው አጠቃላይ የህዝብ መዳረሻ የለም ፣ ግን ለትንንሽ ቡድኖች የሚመሩ ጉብኝቶች በባሲሊካ ስር ወደ አትክልቶች እና ቁፋሮዎች ሊዘጋጁ ይችላሉ ። ሌሎች ቦታዎች ክፍት የሆኑት እዚያ ለመገበያየት የንግድ ሥራ ላላቸው ግለሰቦች ብቻ ነው። የአውሮፓ አገራት
2628
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%85%E1%8A%95%E1%8B%B5
ህንድ
ህንድ፣ በይፋ የህንድ ሪፐብሊክ (ሂንዲ፡ ብሃራት ጋናራጃ)፣ በደቡብ እስያ የሚገኝ አገር ነው። በአካባቢው በሰባተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ፣ በሕዝብ ብዛት ሁለተኛዋ አገር፣ እና በዓለም ላይ በሕዝብ ብዛቷ ዲሞክራሲ ናት። በደቡብ በህንድ ውቅያኖስ፣ በደቡብ ምዕራብ የአረብ ባህር፣ በደቡብ ምስራቅ የቤንጋል የባህር ወሽመጥ የተከበበ ሲሆን በምዕራብ ከፓኪስታን ጋር የመሬት ድንበሮችን ይጋራል። ቻይና, ኔፓል እና ቡታን በሰሜን; እና ባንግላዴሽ እና ምያንማር በምስራቅ። በህንድ ውቅያኖስ ውስጥ ህንድ በስሪ ላንካ እና በማልዲቭስ አካባቢ ነው; የአንዳማን እና የኒኮባር ደሴቶች ከታይላንድ፣ ከማያንማር እና ከኢንዶኔዢያ ጋር የባህር ድንበር ይጋራሉ። የዘመናችን ሰዎች ከ55,000 ዓመታት በፊት ከአፍሪካ ወደ ህንድ ክፍለ አህጉር ደርሰዋል። የረዥም ጊዜ ሥራቸው፣ መጀመሪያ ላይ እንደ አዳኝ ሰብሳቢነት በተለያየ መልኩ፣ አካባቢውን በጣም የተለያየ አድርጎታል፣ በሰዎች የዘረመል ልዩነት ከአፍሪካ በመቀጠል። ከ9,000 ዓመታት በፊት በኢንዱስ ወንዝ ተፋሰስ ምዕራባዊ ዳርቻ ላይ የሰፈረ ሕይወት በክፍለ አህጉሩ ታየ፣ ቀስ በቀስ ወደ ኢንደስ ሸለቆ ሥልጣኔ በሦስተኛው ሺህ ዓመት ዓክልበ. በ1200 ዓ.ዓ.፣ ጥንታዊ የሳንስክሪት ዓይነት፣ ኢንዶ-አውሮፓዊ ቋንቋ፣ ከሰሜን ምዕራብ ወደ ህንድ ተሰራጭቶ፣ የሪግቬዳ ቋንቋ ሆኖ ተከፈተ፣ እና በህንድ ውስጥ የሂንዱይዝም ጎህ መጀመሩን መዝግቧል። የህንድ ድራቪዲያን ቋንቋዎች በሰሜናዊ እና ምዕራባዊ ክልሎች ተተክተዋል። እ.ኤ.አ. በ 400 ዓክልበ, በዘር መከፋፈል እና ማግለል በሂንዱይዝም ውስጥ ብቅ አለ, እና ቡዲዝም እና ጄኒዝም ከዘር ውርስ ጋር ያልተገናኙ ማህበራዊ ትዕዛዞችን አውጀዋል. ቀደምት የፖለቲካ ማጠናከሪያዎች በጋንጀስ ተፋሰስ ላይ የተመሰረቱትን የሞርያ እና የጉፕታ ኢምፓየር ሹራብ ፈጠሩ። የጋራ ዘመናቸው ሰፊ በሆነ የፈጠራ ችሎታ የታሸገ ነበር ነገር ግን የሴቶች ደረጃ እያሽቆለቆለ በመሄድ እና ያለመነካካትን ወደ የተደራጀ የእምነት ስርዓት መቀላቀልም ጭምር ነው። በደቡብ ህንድ የመካከለኛው መንግስታት የድራቪዲያን ቋንቋ ጽሑፎችን እና ሃይማኖታዊ ባህሎችን ወደ ደቡብ ምስራቅ እስያ መንግስታት ላከ። በመካከለኛው ዘመን መጀመሪያ ላይ ክርስትና፣ እስልምና፣ ይሁዲነት እና ዞራስትሪኒዝም በህንድ ደቡባዊ እና ምዕራባዊ የባህር ዳርቻዎች ላይ ስር ሰደዱ። ከመካከለኛው እስያ የመጡ የሙስሊም ወታደሮች የሕንድ ሰሜናዊ ሜዳዎችን አልፎ አልፎ ወረሩ፣ በመጨረሻም የዴሊ ሱልጣኔትን መስርተዋል፣ እና ሰሜናዊ ህንድን ወደ መካከለኛው ዘመን እስላም አጽናፈ ሰማይ አውጥተዋል። በ 15 ኛው ክፍለ ዘመን የቪጃያናራ ኢምፓየር በደቡብ ሕንድ ውስጥ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ የተዋሃደ የሂንዱ ባህል ፈጠረ. በፑንጃብ፣ ተቋማዊ ሃይማኖትን በመቃወም ሲኪዝም ብቅ አለ። በ1526 የሙጋል ኢምፓየር ለሁለት መቶ ዓመታት አንጻራዊ ሰላም አስገኝቷል፤ ይህም የብርሃን አርክቴክቸር ትቶ ነበር። ቀስ በቀስ እየሰፋ የመጣው የብሪቲሽ ኢስት ህንድ ኩባንያ አገዛዝ ተከትሎ፣ ህንድን ወደ ቅኝ ገዥ ኢኮኖሚ ለወጠው፣ ነገር ግን ሉዓላዊነቷን አጠናክራለች። የብሪቲሽ ዘውድ አገዛዝ በ 1858 ተጀመረ. ለህንዶች ቃል የተገባላቸው መብቶች ቀስ በቀስ ተሰጥተዋል, ነገር ግን የቴክኖሎጂ ለውጦች መጡ, እና የትምህርት, የዘመናዊነት እና የህዝብ ህይወት ሀሳቦች ስር ሰደዱ. ፈር ቀዳጅ እና ተደማጭነት ያለው የብሄረተኛ ንቅናቄ ተፈጠረ፣ እሱም በሰላማዊ ተቃውሞ የሚታወቅ እና የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ለማቆም ዋና ምክንያት ሆነ። እ.ኤ.አ. በ1947 የብሪቲሽ ህንድ ኢምፓየር በከፍተኛ የህይወት መጥፋት እና ታይቶ በማይታወቅ ፍልሰት ውስጥ በሁለት ገለልተኛ ግዛቶች ተከፈለ። ህንድ ከ1950 ጀምሮ በዲሞክራሲያዊ ፓርላሜንታሪ ስርዓት የምትመራ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ነች። የብዝሃነት፣ የቋንቋ እና የብዙ ብሄር ማህበረሰብ ነው። የህንድ ህዝብ በ1951 ከነበረበት 361 ሚሊየን በ2011 ወደ 1.211 ቢሊዮን አድጓል።በዚሁ ጊዜ የነፍስ ወከፍ ገቢዋ ከ64 የአሜሪካ ዶላር በዓመት ወደ 1,498 የአሜሪካ ዶላር ከፍ ብሏል፣ እና ማንበብና መጻፍ ከ16.6% ወደ 74% አድጓል። እ.ኤ.አ. በ 1951 በአንፃራዊ ሁኔታ ድሃ ሀገር ከመሆኗ አንፃር ህንድ ፈጣን እድገት እያስመዘገበች ያለች ትልቅ ኢኮኖሚ እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎት ማዕከል ሆናለች፣ መካከለኛ መደብ እየሰፋ ነው። በርካታ የታቀዱ ወይም የተጠናቀቁ ከመሬት በላይ ተልእኮዎችን የሚያካትት የጠፈር ፕሮግራም አለው። የህንድ ፊልሞች፣ ሙዚቃዎች እና መንፈሳዊ ትምህርቶች በአለምአቀፍ ባህል ውስጥ ሚናቸው እየጨመረ ነው። ህንድ የድህነት መጠኑን በእጅጉ ቀንሳለች፣ ምንም እንኳን ኢኮኖሚያዊ እኩልነትን ከፍ ለማድረግ ብትሞክርም። ህንድ በወታደራዊ ወጪ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ሀገር ነች። ከ 20 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በካሽሚር ከጎረቤቶቿ ፓኪስታን እና ቻይና ጋር አለመግባባት አለባት። ህንድ ካጋጠሟት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች መካከል የፆታ እኩልነት ፣የህጻናት የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እና የአየር ብክለት ደረጃ መጨመር ይገኙበታል። የህንድ መሬት ሜጋ ዳይቨርስ ነው፣ አራት የብዝሃ ሕይወት ቦታዎች አሉት። የደን ​​ሽፋን ከአካባቢው 21.7% ይይዛል። በህንድ ባህል በተለምዶ በመቻቻል ይታይ የነበረው የህንድ የዱር አራዊት በእነዚህ ደኖች እና በሌሎችም ስፍራዎች በተጠበቁ መኖሪያዎች ውስጥ ይደገፋል። ሥርወ ቃል እንደ ኦክስፎርድ ኢንግሊሽ መዝገበ ቃላት (እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በሦስተኛው እትም) “ህንድ” የሚለው ስም የመጣው ከጥንታዊው የላቲን ህንድ ፣ የደቡብ እስያ ማጣቀሻ እና በምስራቅ በኩል እርግጠኛ ያልሆነ ክልል ነው ። እና በምላሹ ከ: ሄለናዊ ግሪክ ሕንድ (); የጥንት ግሪክ ኢንዶስ (); የድሮው የፋርስ ሂንዱሽ፣ የአካሜኒድ ግዛት ምስራቃዊ ግዛት; እና በመጨረሻም የተዋሃደው፣ ሳንስክሪት ሲንዱ፣ ወይም “ወንዝ”፣ በተለይም የኢንዱስ ወንዝ እና፣ በተዘዋዋሪም፣ በደንብ የሰፈረው ደቡባዊ ተፋሰስ። የጥንት ግሪኮች ሕንዶችን ኢንዶይ () ብለው ይጠሯቸው ነበር፣ እሱም “የኢንዱስ ሰዎች” ተብሎ ይተረጎማል። ብሃራት የሚለው ቃል በህንድ ግጥሞች እና በህንድ ህገ መንግስት ውስጥ የተጠቀሰው ባሃራት (ብሃራት ፣ ይጠራ በብዙ የህንድ ቋንቋዎች በተለዋዋጭነቱ ጥቅም ላይ ይውላል። ባራታቫርሻ የሚለው የታሪካዊ ስም ዘመናዊ አተረጓጎም ፣ እሱም በመጀመሪያ በሰሜን ህንድ ፣ ባራት ተሰራ። ከ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ የህንድ የአፍ መፍቻ ስም ሆኖ ጨምሯል። ሂንዱስታን ህንድ የመካከለኛው ፋርስ ስም ነው፣ በሙጋል ኢምፓየር ጊዜ አስተዋወቀ እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በሰፊው ጥቅም ላይ ውሏል። ትርጉሙ የተለያየ ነው፣ የዛሬውን ሰሜናዊ ህንድ እና ፓኪስታንን ወይም በአጠቃላይ ህንድን የሚያጠቃልለውን ክልል ያመለክታል። ጥንታዊ ሕንድ ከ6500 ዓ.ዓ በኋላ የምግብ ሰብሎችንና እንስሳትን ለማዳረስ፣ ቋሚ የግንባታ ግንባታ እና የግብርና ተረፈ ምርቶችን ለማከማቸት ማስረጃዎች በሜርጋርህ እና ሌሎች ቦታዎች በአሁኑ ባሎቺስታን፣ ፓኪስታን ውስጥ ታዩ። እነዚህም በ2500-1900 ዓክልበ. በአሁን ፓኪስታን እና ምእራብ ህንድ ውስጥ የበለፀገው በደቡብ እስያ የመጀመሪያው የከተማ ባህል ወደ ኢንደስ ሸለቆ ስልጣኔ አደጉ። እንደ ሞሄንጆ-ዳሮ፣ ሃራፓ፣ ዶላቪራ እና ካሊባንጋን በመሳሰሉ ከተሞች ዙሪያ ያተኮረው እና በተለያዩ የኑሮ ዘይቤዎች ላይ የተመሰረተው ስልጣኔ በእደ ጥበብ ውጤቶች እና ሰፊ ንግድ ላይ ተሰማርቷል። ከ2000-500 ከዘአበ ባለው ጊዜ ውስጥ ብዙ የክፍለ አህጉሩ ክልሎች ከቻልኮሊቲክ ባህሎች ወደ ብረት ዘመን ተሸጋገሩ። ቬዳስ፣ ከሂንዱይዝም ጋር የተያያዙ ጥንታዊ ቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉት በዚህ ወቅት ነው፣ እናም የታሪክ ተመራማሪዎች የቬዲክ ባህልን ለማመልከት እነዚህን ተንትነዋል። በፑንጃብ ክልል እና በላይኛው የጋንግቲክ ሜዳ። አብዛኞቹ የታሪክ ተመራማሪዎችም ይህ ወቅት ከሰሜን-ምዕራብ ወደ ክፍለ አህጉር በርካታ የኢንዶ-አሪያን ፍልሰት ማዕበሎችን ያቀፈ እንደሆነ አድርገው ይቆጥሩታል። የካህናት፣ የጦረኞች እና የነጻ ገበሬዎች ተዋረድ የፈጠረው፣ ነገር ግን ተወላጆችን ሥራቸውን ርኩስ አድርጎ በመፈረጅ ያገለላቸው የዘውድ ሥርዓት የተነሳው በዚህ ወቅት ነው። በዲካን ፕላቶ ላይ፣ ከዚህ ጊዜ የተገኙ የአርኪኦሎጂ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የፖለቲካ ድርጅት ዋና ደረጃ መኖሩን ያሳያል። በደቡብ ህንድ፣ ወደ ተቀናቃኝ ህይወት መሸጋገሩን ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በተፈጠሩት በርካታ የሜጋሊቲክ ሀውልቶች፣ እንዲሁም በአቅራቢያው ባሉ የግብርና፣ የመስኖ ታንኮች እና የዕደ-ጥበብ ወጎች። በቬዲክ መገባደጃ ላይ፣ በ6ኛው ክፍለ ዘመን ከዘአበ አካባቢ፣ የጋንግስ ሜዳ ትንንሽ ግዛቶች እና አለቆች እና የሰሜን-ምዕራብ ክልሎች ወደ 16 ዋና ዋና ኦሊጋርቺስ እና ንጉሳዊ መንግስታት ማሃጃናፓዳዎች ተብለው ይጠሩ ነበር። የከተሞች መስፋፋት የቬዲክ ያልሆኑ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆኗል፣ ከእነዚህም ውስጥ ሁለቱ ራሳቸውን የቻሉ ሃይማኖቶች ሆነዋል። ጄኒዝም ታዋቂነት ያገኘው በአርአያነቱ መሃቪራ በነበረበት ወቅት ነው። በጋውታማ ቡድሃ አስተምህሮ ላይ የተመሰረተ ቡድሂዝም ከመካከለኛው መደብ በስተቀር ከሁሉም ማህበራዊ ክፍሎች የመጡ ተከታዮችን ስቧል; በህንድ ውስጥ ለተመዘገቡት የታሪክ ጅማሬዎች የቡድሃን ሕይወት መዝግቦ መዝግቦ መዝግቦ ነበር። የከተማ ሀብት እየጨመረ በሄደበት ዘመን ሁለቱም ሃይማኖቶች ክህደትን እንደ አንድ ጥሩ ነገር አድርገው ነበር, እና ሁለቱም ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ገዳማዊ ወጎችን አቋቋሙ. በፖለቲካዊ መልኩ፣ በ 3 ኛው ክፍለ ዘመን ከዘአበ፣ የማጋዳ መንግሥት ሌሎች ግዛቶችን ጠቅልሎ ወይም ቀንሶ እንደ ሞሪያን ኢምፓየር ብቅ አለ። ግዛቱ በአንድ ወቅት ከሩቅ ደቡብ በስተቀር አብዛኛው ክፍለ-አህጉርን ይቆጣጠር ነበር ተብሎ ይታሰብ ነበር፣ ነገር ግን ዋናዎቹ ክልሎች አሁን በትላልቅ የራስ ገዝ አካባቢዎች ተለያይተዋል ተብሎ ይታሰባል። የሞሪያን ነገሥታት በግዛት ግንባታ እና በቆራጥነት በሕዝብ ሕይወት አስተዳደር ይታወቃሉ፣ አሾካ ወታደራዊነትን በመካድ እና የቡዲስት ደምማ የራቀ ጥብቅና መቆም። የታሚል ቋንቋ የሳንጋም ሥነ ጽሑፍ እንደሚያሳየው ከ200 ከዘአበ እስከ 200 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ደቡባዊው ባሕረ ገብ መሬት በቼራስ፣ ቾላስ እና ፓንዲያስ ሥር ይገዛ ነበር፣ ሥርወ መንግሥት ከሮማ ኢምፓየር እና ከምዕራብ እና ደቡብ-ምስራቅ እስያ ጋር ብዙ ይነግዱ ነበር። በሰሜን ሕንድ ሂንዱይዝም በቤተሰብ ውስጥ የአባቶች ቁጥጥርን በማረጋገጡ የሴቶችን የበታችነት መጨመር አስከትሏል. በ 4 ኛው እና በ 5 ኛው ክፍለ ዘመን የጉፕታ ኢምፓየር በትልቁ ጋንግስ ሜዳ ውስጥ ውስብስብ የአስተዳደር እና የግብር ስርዓት ፈጠረ; ይህ ስርዓት ለኋለኞቹ የህንድ መንግስታት ሞዴል ሆነ። በጉፕታስ ስር፣ የአምልኮ ሥርዓትን ከማስተዳደር ይልቅ በአምልኮ ላይ የተመሰረተ የታደሰ ሂንዱዝም እራሱን ማረጋገጥ ጀመረ። ይህ እድሳት በከተማ ልሂቃን መካከል ደጋፊዎችን ባገኘው የቅርጻቅርፃ እና የስነ-ህንፃ አበባ ላይ ተንጸባርቋል። ክላሲካል የሳንስክሪት ሥነ ጽሑፍም አብቧል፣ የሕንድ ሳይንስ፣ አስትሮኖሚ፣ ሕክምና እና ሒሳብ ከፍተኛ እድገቶችን አድርገዋል። የመካከለኛው ዘመን ህንድ የሕንድ የመካከለኛው ዘመን ዘመን፣ ከ600 እስከ 1200 ዓ.ም.፣ በክልል መንግሥታት እና በባህል ልዩነት ይገለጻል። ከ606 እስከ 647 እዘአ አብዛኛው የኢንዶ-ጋንግቲክ ሜዳ ያስተዳደረው የቃናውጅ ሀርሻ ወደ ደቡብ ለመስፋፋት ሲሞክር በዴካን ቻሉክያ ገዥ ተሸነፈ። ተተኪው ወደ ምስራቅ ለመስፋፋት ሲሞክር በቤንጋል ፓላ ንጉስ ተሸነፈ። ቻሉኪያስ ወደ ደቡብ ለመዘርጋት ሲሞክሩ ከሩቅ ደቡብ በፓላቫስ ተሸነፉ፣ እነሱም በተራው በፓንዲያስ እና ቾላስ ከደቡብ ሩቅ ሆነው ተቃወሙ። የትኛውም የዚህ ዘመን ገዥ ኢምፓየር መፍጠር እና ከዋና ክልላቸው በላይ ብዙ መሬቶችን በቋሚነት መቆጣጠር አልቻለም። በዚህ ወቅት፣ መሬታቸው ለግብርና ኢኮኖሚ ምቹ እንዲሆን የተነደፈ አርብቶ አደር ሕዝቦች፣ በነጠላ ማህበረሰብ ውስጥ፣ እንደ አዲስ ባህላዊ ያልሆኑ ገዥ መደቦች ይስተናገዳሉ። የዘውድ ሥርዓት በዚህ ምክንያት የክልል ልዩነቶችን ማሳየት ጀመረ። በ6ኛው እና በ7ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያዎቹ የአምልኮ መዝሙሮች በታሚል ቋንቋ ተፈጠሩ። በመላው ህንድ ውስጥ ተመስለዋል እናም ለሁለቱም የሂንዱዝም ትንሳኤ እና የክፍለ አህጉሩ ዘመናዊ ቋንቋዎች በሙሉ እንዲዳብሩ አድርጓቸዋል. የሕንድ ንጉሣውያን፣ ትልቅም ሆኑ ትናንሽ፣ እና እነርሱን ያስተዳድሩ የነበሩት ቤተመቅደሶች ዜጐች ብዙ ቁጥር ወደ ዋና ከተማዎቹ እንዲሳቡ አድርጓቸዋል፣ ይህም የኢኮኖሚ ማዕከልም ሆኑ። ህንድ ሌላ የከተማ መስፋፋት በጀመረችበት ወቅት የተለያየ መጠን ያላቸው የቤተመቅደስ ከተሞች በየቦታው መታየት ጀመሩ። በ8ኛው እና በ9ኛው ክፍለ ዘመን በደቡብ-ምስራቅ እስያ ደቡብ ህንድ ባህል እና የፖለቲካ ስርአቶች የዘመናዊቷ ምያንማር፣ ታይላንድ፣ ላኦስ፣ ካምቦዲያ፣ ቬትናም፣ ፊሊፒንስ፣ ማሌዥያ እና አካል ወደሆኑ አገሮች በመላኩ ውጤቱ ተሰምቷል። ጃቫ የሕንድ ነጋዴዎች, ምሁራን እና አንዳንድ ጊዜ ወታደሮች በዚህ ስርጭት ውስጥ ይሳተፋሉ; ደቡብ-ምስራቅ እስያውያንም ተነሳሽነቱን ወስደዋል፣ ብዙዎች በህንድ ሴሚናሪ ውስጥ በመገኘት የቡድሂስት እና የሂንዱ ጽሑፎችን ወደ ቋንቋቸው ሲተረጉሙ ነበር። ከ10ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኋላ የሙስሊም መካከለኛው እስያ ዘላኖች ጎሳዎች ፈጣን ፈረስ ፈረሰኞችን በመጠቀም እና በጎሳ እና በሃይማኖት የተዋሃደ ሰፊ ሰራዊት በማፍራት የደቡብ እስያ ሰሜናዊ ምዕራብ ሜዳዎችን ደጋግመው በማሸነፍ በመጨረሻ እ.ኤ.አ. በ 1206 ኢስላሚክ ዴሊ ሱልጣኔት እንዲመሰረት አድርጓል ። ሱልጣኔት አብዛኛው የሰሜን ህንድ ክፍል ለመቆጣጠር እና ወደ ደቡብ ህንድ ብዙ ጉዞዎችን ለማድረግ ነበር። ምንም እንኳን በመጀመሪያ የህንድ ልሂቃን ረብሻ ቢፈጥርም ሱልጣኔቱ ሙስሊም ያልሆነውን ሰፊ ​​ህዝብ ለራሱ ህጎች እና ልማዶች ትቷል። ሱልጣኔቱ በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሞንጎሊያውያን ዘራፊዎችን ደጋግሞ በመቃወም ህንድን በምእራብ እና በመካከለኛው እስያ ከተጎበኘው ውድመት ታድጓል ፣ይህም ለዘመናት ሸሽተው የሚሸሹ ወታደሮች፣ ምሁራን፣ ምሑራን፣ ነጋዴዎች፣ አርቲስቶች እና የእጅ ጥበብ ባለሙያዎች ከዚያ ክልል ወደሚገኙበት ቦታ ፈጥሯል። ንዑስ አህጉር, በዚህም በሰሜን ውስጥ የተመሳሰለ ኢንዶ-እስላማዊ ባህል መፍጠር. የሱልጣኔቱ ወረራ እና የደቡብ ህንድ ክልላዊ መንግስታት መዳከም ለቪጃያናጋራ ተወላጅ ኢምፓየር መንገድ ጠርጓል። ጠንካራ የሻይቪት ባህልን በመቀበል እና በሱልጣኔቱ ወታደራዊ ቴክኖሎጂ ላይ በመገንባት፣ ኢምፓየር ብዙ ልሳነ ምድርን ህንድ ለመቆጣጠር መጣ እና በደቡብ ህንድ ማህበረሰብ ላይ ለረጅም ጊዜ ተፅእኖ መፍጠር ነበረበት። የጥንት ዘመናዊ ህንድ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ሰሜናዊ ህንድ፣ ያኔ በዋነኛነት በሙስሊም ገዥዎች ስር፣ እንደገና በመካከለኛው እስያ ተዋጊ አዲስ ትውልድ የላቀ ተንቀሳቃሽነት እና የእሳት ኃይል ወደቀ። ያስከተለው የሙጋል ኢምፓየር እየገዛ የመጣውን የአካባቢ ማህበረሰቦችን አላጠፋም። ይልቁንም በአዳዲስ አስተዳደራዊ አሰራሮች እና የተለያዩ እና ሁሉንም ባሳተፈ የገዢ ልሂቃን አማካይነት ሚዛናዊና ሰላም እንዲሰፍን አድርጓል፤ ይህም ወደ ስልታዊ፣ የተማከለ እና ወጥ የሆነ አገዛዝ እንዲመራ አድርጓል። የጎሳ ትስስርን እና ኢስላማዊ ማንነትን በተለይም በአክባር ስር፣ ሙጋላዎች የራቁትን ግዛቶቻቸውን በፋርስ ባህል በመግለጽ በታማኝነት አንድ አደረጉ። የሙጋል ስቴት የኢኮኖሚ ፖሊሲ ከግብርና የሚገኘውን አብዛኛው ገቢ የሚያገኘው እና ታክስ በደንብ በተያዘው የብር ምንዛሪ እንዲከፈል በማዘዝ ገበሬዎች እና የእጅ ባለሞያዎች ወደ ትላልቅ ገበያዎች እንዲገቡ አድርጓል። በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በግዛቱ የነበረው አንጻራዊ ሰላም የህንድ ኢኮኖሚ መስፋፋት ምክንያት ሲሆን ይህም በሥዕል፣ በሥነ ጽሑፍ፣ በጨርቃጨርቅ እና በሥነ ሕንፃ ግንባታ የላቀ ድጋፍ አስገኝቷል። በሰሜን እና በምእራብ ህንድ እንደ ማራታስ፣ራጅፑትስ እና ሲክ ያሉ አዲስ ወጥነት ያላቸው ማህበረሰባዊ ቡድኖች ወታደራዊ እና የአስተዳደር ምኞቶችን በሙጋል አገዛዝ ጊዜ አግኝተዋል፣ይህም በትብብር ወይም በችግር፣ እውቅና እና ወታደራዊ ልምድ ሰጥቷቸዋል። በሙጋል አገዛዝ ወቅት የንግድ ልውውጥ መስፋፋት በደቡብ እና በምስራቅ ህንድ የባህር ዳርቻዎች ላይ አዲስ የህንድ የንግድ እና የፖለቲካ ልሂቃን ፈጠረ። ግዛቱ ሲበታተን፣ ከእነዚህ ልሂቃን መካከል ብዙዎቹ የራሳቸውን ጉዳይ መፈለግ እና መቆጣጠር ችለዋል።በ 18 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ፣ በንግድ እና በፖለቲካዊ የበላይነት መካከል ያለው መስመሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየደበዘዙ በመጡ ፣ የእንግሊዝ ምስራቅ ህንድ ኩባንያን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ የንግድ ኩባንያዎች የባህር ዳርቻዎች ምሽጎችን አቋቁመዋል። የምስራቅ ህንድ ካምፓኒ የባህር ቁጥጥር፣ ከፍተኛ ሀብቶች እና የላቀ ወታደራዊ ስልጠና እና ቴክኖሎጂ ወታደራዊ ጥንካሬውን እንዲያረጋግጥ እና የህንድ ልሂቃን ክፍል እንዲስብ አድርጎታል። እነዚህ ምክንያቶች ኩባንያው በ 1765 የቤንጋልን ክልል እንዲቆጣጠር እና ሌሎች የአውሮፓ ኩባንያዎችን ወደ ጎን እንዲተው ለመፍቀድ ወሳኝ ነበሩ። የቤንጋልን ሀብት የበለጠ ማግኘት እና የሰራዊቱ ጥንካሬ እና መጠን መጨመር በ 1820 ዎቹ ህንድ አብዛኛው ክፍል እንድትቀላቀል ወይም እንድትገዛ አስችሎታል። ህንድ ያኔ የተመረተ ምርትን ለረጅም ጊዜ ወደ ውጭ መላክ ቀርቶ በምትኩ ለብሪቲሽ ኢምፓየር በጥሬ ዕቃ ታቀርብ ነበር። ብዙ የታሪክ ተመራማሪዎች ይህንን የሕንድ የቅኝ ግዛት ዘመን መጀመሪያ አድርገው ይመለከቱታል። በዚህ ጊዜ፣ በእንግሊዝ ፓርላማ የኢኮኖሚ ኃይሉ በከፍተኛ ሁኔታ ተገድቦ እና በብቃት የብሪታንያ አስተዳደር ክንድ ሆኖ፣ ኩባንያው እንደ ትምህርት፣ ማህበራዊ ማሻሻያ እና ባህል ባሉ ኢኮኖሚያዊ ያልሆኑ መድረኮች በንቃት መግባት ጀመረ። ዘመናዊ ህንድ የታሪክ ተመራማሪዎች የሕንድ ዘመናዊ ዘመን ከ1848 እስከ 1885 ባለው ጊዜ ውስጥ እንደጀመረ አድርገው ይቆጥሩታል። በ1848 የሎርድ ዳልሁዚ የምስራቅ ህንድ ኩባንያ ገዥ ጄኔራል ሆኖ መሾሙ ለዘመናዊ መንግስት አስፈላጊ ለውጦችን ደረጃ አድርጓል። እነዚህም የሉዓላዊነትን ማጠናከር እና ማካለል፣ የህዝቡን ክትትል እና የዜጎችን ትምህርት ያካትታሉ። የቴክኖሎጂ ለውጦች-ከነሱ መካከል የባቡር መስመሮች፣ ቦዮች እና ቴሌግራፍ - በአውሮፓ ከገቡ ብዙም ሳይቆይ አስተዋውቀዋል። ሆኖም ከኩባንያው ጋር ያለው አለመስማማት በዚህ ጊዜ ውስጥ ጨመረ እና በ 1857 የህንድ ዓመፅን አስነሳ ። በተለያዩ ቂሞች እና አመለካከቶች ፣ ወራሪ የብሪታንያ መሰል ማህበራዊ ማሻሻያዎችን ፣ ከባድ የመሬት ታክስን እና የአንዳንድ ሀብታም የመሬት ባለቤቶችን እና መኳንንቶች ማጠቃለያ ፣ በህንድ ሰሜናዊ እና መካከለኛው አካባቢ ብዙ ክልሎችን አናወጠ እና የኩባንያውን አገዛዝ መሰረት አናጋው። በ1858 ዓመፁ ቢታፈንም የምስራቅ ህንድ ካምፓኒ እንዲፈርስ እና የህንድ ቀጥተኛ አስተዳደር በእንግሊዝ መንግስት እንዲመራ አድርጓል። አሃዳዊ መንግስት እና ቀስ በቀስ ግን የተገደበ የብሪታኒያ አይነት የፓርላማ ስርዓት በማወጅ፣ አዲሶቹ ገዥዎች መኳንንትን እና መሬት ላይ ያሉ ሰዎችን ከወደፊቱ ብጥብጥ ለመከላከል እንደ ፊውዳል ጥበቃ አድርገው ነበር። በቀጣዮቹ አሥርተ ዓመታት ውስጥ፣ የሕዝብ ሕይወት ቀስ በቀስ በመላው ሕንድ ታየ፣ በመጨረሻም በ 1885 የሕንድ ብሔራዊ ኮንግረስ ምስረታ ላይ ደርሷል። በ19ኛው ክፍለ ዘመን ሁለተኛ አጋማሽ ላይ የቴክኖሎጂው ጥድፊያ እና የግብርና ንግድ ሥራ በኢኮኖሚ ውድቀቶች የተስተዋለ ሲሆን ብዙ ትናንሽ ገበሬዎች በሩቅ ገበያዎች ፍላጎት ላይ ጥገኛ ሆነዋል። መጠነ ሰፊ የሆነ ረሃብ ጨምሯል፣ እና ምንም እንኳን የህንድ ግብር ከፋዮች የሚሸከሙት የመሠረተ ልማት ዝርጋታ አደጋዎች ቢኖሩም፣ ለህንዶች አነስተኛ የኢንዱስትሪ ሥራ አልተፈጠረም። የጨዋማ ውጤቶችም ነበሩ፡ የንግድ ሰብል በተለይም አዲስ በተሸፈነው ፑንጃብ ውስጥ ለውስጣዊ ፍጆታ የሚሆን የምግብ ምርት እንዲጨምር አድርጓል። የባቡር ኔትዎርክ ወሳኝ የሆነ የረሃብ እፎይታ አቅርቧል፣በተለይም የሸቀጦችን ማጓጓዝ ወጪን በመቀነሱ እና ገና በህንድ የተያዙ ኢንዱስትሪዎችን ረድቷል።ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ሕንዶች ያገለገሉበት ከአንደኛው የዓለም ጦርነት በኋላ አዲስ ጊዜ ተጀመረ። በብሪቲሽ ማሻሻያዎች ነገር ግን አፋኝ ህግ፣ በይበልጥ ጠንከር ባሉ የህንድ እራስን በራስ የማስተዳደር ጥሪዎች እና የትብብር-አልባ እንቅስቃሴ ጅምር ሲሆን ሞሃንዳስ ካራምቻንድ ጋንዲ መሪ እና ዘላቂ ምልክት ይሆናል። እ.ኤ.አ. በ 1930 ዎቹ ውስጥ ፣ ዘገምተኛ የሕግ ማሻሻያ በብሪቲሽ ተደነገገ ። በተካሄደው ምርጫ የህንድ ብሄራዊ ኮንግረስ ድሎችን አሸንፏል። የሚቀጥሉት አስርት አመታት በቀውሶች ተከባ ነበር፡ የህንድ በሁለተኛው የአለም ጦርነት ተሳትፎ፣ የኮንግረሱ የመጨረሻ የትብብር አላማ እና የሙስሊም ብሄርተኝነት መነሳት። ሁሉም በ1947 የነፃነት መምጣት ተዘግተዋል፣ነገር ግን ህንድ ወደ ሁለት ግዛቶች በመከፈሏ ህንድ እና ፓኪስታን። ህንድ እንደ ነጻ ሀገር ለመምሰል አስፈላጊ የሆነው እ.ኤ.አ. በ1950 የተጠናቀቀው ሕገ መንግሥት ዓለማዊ እና ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክን ያቋቋመ ሕገ መንግሥት ነበር። የዜጎች ነፃነት፣ የነቃ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ብዙ ነፃ ፕሬስ ያለው ዲሞክራሲያዊት ሆኖ ቆይቷል። እ.ኤ.አ. በ1990ዎቹ የጀመረው የኤኮኖሚ ሊበራላይዜሽን ትልቅ የከተማ መካከለኛ መደብ ፈጥሯል ፣ ህንድን በዓለም ፈጣን ኢኮኖሚ እያደጉ ካሉ ሀገራት ተርታ እንድትሰለፍ አድርጓታል ፣ እና ጂኦፖለቲካዊ ዝናዋን አሳድጋለች። የህንድ ፊልሞች፣ ሙዚቃ እና መንፈሳዊ ትምህርቶች በአለምአቀፍ ባህል ውስጥ ሚናቸው እየጨመረ ነው። ገና፣ ህንድ በገጠርም በከተማም የማይበገር በሚመስል ድህነት ነው የተቀረፀችው። በሃይማኖታዊ እና ጎሳ-ተኮር ጥቃት; በማኦኢስት አነሳሽነት ናክሳላይት ዓመፅ; እና በጃሙ እና ካሽሚር እና በሰሜን ምስራቅ ህንድ ውስጥ በመለያየት። ከቻይና እና ከፓኪስታን ጋር ያልተፈታ የግዛት ውዝግብ አላት። የሕንድ ቀጣይነት ያለው የዲሞክራሲ ነፃነቶች ከዓለም አዲስ አገሮች መካከል ልዩ ናቸው; ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያስመዘገበው ኢኮኖሚያዊ ስኬት፣ የተቸገረ ሕዝቧን ከችግር ነፃ ማድረግ ገና ሊደረስበት ያልቻለ ግብ ነው።
48468
https://am.wikipedia.org/wiki/Sahabah%20story%28%E1%88%B6%E1%88%80%E1%89%A3%29
Sahabah story(ሶሀባ)
እናታችን አዒሻ (ረ.ዐ) “በኢስላም የመጀመሪያው የፍቅር መግለጫ ነብዩ ለአዒሻ የነበራቸው ፍቅር ነው።” ከሥረ መሠረቱ ኢስላምን ከንጹህ ምንጭና ከትክክለኛው አካባቢ የመረዳት ምሳሌ ናት። ከመምህራኖቹ ሁሉ ምርጡ መምህር (ከነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)) እንደመማሯም አንድ ሙስሊም ሊደርስበት የሚያስበው የፅድቅ ደረጃ የደረሰች አርአያ ሴት ነች። በመሠረቱ የአዒሻ ምሳሌነት ዘርፈ ብዙ ነው። ከግል ሕይወት እስከ ሕዝባዊ፣ ከቤት ውስጥ ኑሮ እስከ ምሁራዊ ጉዞ፣ ወዘተ። ከነዚህ የአርኣያነት ምሳሌነቶች ውስጥ ወሳኝ ድርሻ ያለው ደግሞ የምዕመናን እናትነቷ ነው። በቁርኣን የተገለጸውን ምርጥ ኢስላማዊ ምግባር በማሟላትም ምሥጉን ስብእና ነበራት። ቸርነት፣ ቅንነት፣ ታማኝነትና እውነትንና ፍትህን መፈለግ የአዒሻ ዋነኛ መገለጫዎች ነበሩ። አዒሻ እንደተማሪ ከጎበዝ ወጣትነት በተጨማሪ በጠያቂና ተመራማሪ ጭንቅላት ወደ ስኬታማና የተከበረ አዋቂ፣ መምህርና ዳኛ ሆና፤ በተፍሲር፣ በፊቅሂ፣ በሐዲስ፣ በታሪክና በዐረብኛ ቋንቋ ዘርፎች ከፍተኛ ደረጃ ከመድረሷም በላይ በምትሰጣቸው ደፋር፣ ቀጥተኛና የበሰሉ ምሁራዊ ትንተናዎች ትታወቃለች። የአዒሻ ለምታምንበት ነገር ሁሉ ደፋር፣ ግልጽና ቀጥተኛ መሆንን ከፍተኛነት፤ በአሁኑ ሰዓት በሙስሊሙ ዘንድ እንኳ ሴት ልጅ በጾታዋ ምክንያት ብቻ ከማህበረሰቡ የእለት ተዕለት ሕይወት የተገለሉትን ሙስሊም ሴቶች በማየት እንኳ ማረጋገጥ ይቻላል። አዒሻ ከማንም በበለጠ ኹኔታ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) የእለት ተዕለት ሕይወት የነበራት ቦታ እንዲሁም የአስተሳሰብና የባሕሪይ ነጻነቷ በዘመኗ ከነበሩ ታላላቅ ስብዕናዎች ሁሉ የበለጠ ትኩረት እንድትስብ አድርጓታል። የአዒሻ የኋላ ታሪክ ( አዒሻ ሙሉ ስሟ፤ አዒሻ ቢንት አቡበከር አስ-ሲዲቅ ቢሆንም አዒሻ ቢንት ሲዲቅ በመባል በብዛት ትታወቃለች። ይበልጥ የምትታወቀው ግን አስ-ሲዲቃ ቢንት አስ-ሲዲቅ (እውነተኛዋ የእውነተኛው ልጅ) በሚለው ነው። ነብዩም የእህቷን ልጅ አብዳላህ ኢብኑ ዙበይርን እጅግ በመንከባከቧ ምክንያት (ኡሙ አብደላህ) የአብደላህ እናት በሚል ቅጽል ሥም ይጠሯት ነበር። ሁለቱም ወላጆቿ ኢስላምን ገና በጠዋቱ የተቀበሉ በመሆናቸው አስተዳደጓ በንጹህ ኢስላማዊ ከባቢ () ውስጥ ነበር ማለት ይቻላል። እሷም ስትናገር “ገና ከጨቅላነቴ አንስቶ ወላጆቼ ኢስላምን ሲተገብሩ ለማየት ታድያለሁ” ትል ነበር። ገና ከጠዋቱ ስታስተውለው የኖረችው ኢስላማዊ አኗኗር በኋላ ላዳበረችው የአዕምሮ ንቃትና ሠብዕና ከፍተኛውን ሚና ተጫውቷል። ከልጅነቷ አንስቶ በኢስላም ላይ ከፍተኛ እምነት ስታሳድር ለእውነት መስዋዕት መሆንን ደግሞ አስተምሯታል። በተመሳሳይ ኹኔታም ክህደትና መሃይምነትን ትጠላለች። የምዕመናን እናት አዒሻ ከነብዩ ባለቤቶች መካከል ብቸኛዋ ልጃገረድ ናት። የሁለቱ ትዳር የተፈጸመው በአላህ ትዕዛዝ ነበር። አዒሻም ስታገባ በወቅቱ በነበሩት በዐረቦች፣ በእብራውያንና በሌሎች ሕዝቦች ባህል እንደተለመደው ትንሽ እድሜ ነበራት። ይህንን የዕድሜ ሁኔታ አሁን ከ1400 ዓመታት በኋላ ባለው ባህልና ዝንባሌ ለመገምገም መሞከርም ስህተት ነው። የነብዩ የትዳር ሁኔታ ከሳቸው ተልዕኮ ተለይቶ ሊታይ አይችልም። ተልዕኮዋቸውም የዐረቦችን አንድነት መፍጠርና እውቀትና ጥበባቸውን ለሠው ዘር ማስተላለፍ ናቸው። ካለፉትም ከአሁኖችም ምሁራን አስተያየት ማረጋገጥ እንደሚቻለው አዒሻ (ረ.ዐ) በአስተዳደጓም ሆነ በተፈጥሮዋ ምርጥ የተባለችው ምርጫ ነች። ይህንን ተግባርም በወሳኝ እድሜዋ ከነብዩ ጎን በመኖር እየኖረችው በብቃት ፈጽማዋለች። አዒሻ ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በነበራት ፍቅርና እርሳቸውን የግሏ ብቻ ለማድረግ ባላት ጽኑ ፍላጎት ምክንያት በሌሎቹ ሚስቶቻቸው ላይ ትቀና ነበር። ነብዩም ይህን ፍቅሯን ተመሳሳይ መጠን ያለውን ፍቅር በመስጠት መልሰውላታል። የሳቸው ፍቅር ለሰሃቦችም ምሳሌ ነበር። አነስ (ረ.ዐ) እንደዘገቡትም፤ “በኢስላም የመጀመሪያው የፍቅር መግለጫ ነብዩ ለአዒሻ የነበራቸው ፍቅር ነው።” ነብዩ ለሷ የነበራቸው ፍቅር ከአካላዊ ውበቷ ጋር የተሳሳረም አይደለም። ይልቅስ፤ አዒሻ ከተሰጣት አምላካዊ ተልዕኮና የነብያዊ ተግባሩን ቀጣይነት ከማረጋገጥ ጋር የተቆራኘ ነው። የዚህ የማይታለፍ ሚና ማሳያ ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ከሌሎች ሚስቶቻቸው ጋር የማይገጥማቸው ወህይ ከኢዒሻ ጋር ከተቀመጡባቸው ወቅቶች ሲሆኑ ጅብሪልን አይተዋል። ይህ ደግሞ በነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንደተነገረው የሠማያዊው ክብር ሥጦታ መገለጫ ነው። አዒሻ (ረ.ዐ) የገጠሟትን ፈተናዎች፣ የነበራትን እጅ የመስጠት (የኢስቲስላም) አመለካከት ምክንያት በማድረግ የወረዱትን የቁርኣን አንቀፆች በመመልከት “የአላህ እዝነት መፍሰሻ” ትባላለች። ምክንያቱም፤ እነዚህ አንቀፆች ከሷም በኋላ ላለው ትውልድ ሁሉ የሚያገለግል ነው። አንዳንድ ሶሃባዎች የአዒሻን የአላህ እዝነት መገለጫነት ለመግለጽ ከሚጠቀሙት ነገሮች አንዱ የተየሙም ድንጋጌ በአዒሻ ምክንያት መውረዱን ነው። ከዚህም አልፎ አላህ (ሱ.ወ) ይህች እናታችን ስሟ በመናፍቃን በሐሰት በመወሳቱ ምክንያቱ በሱረቱ አን-ኑር ምዕራፍ 24 በተለይም አንቀጽ 23 እና 26 ላይ ክብሯን በመመለስ አንቀጹን ያነበበ ሁሉ ትምህርት እንዲሆነው አድርጓል። “ሙስሊሞች ወንዶችና ሙስሊሞች ሴቶች፣ ምእምናንና ምእምናትም፣ ታዛዦች ወንዶችና ታዛዦች ሴቶችም፣ እውነተኞች ወንዶችና እውነተኞች ሴቶችም፣ ታጋሾች ወንዶችና ታጋሾች ሴቶችም፣ አላህን ፈሪዎች ወንዶችና አላህን ፈሪዎች ሴቶችም፣ መጽዋቾች ወንዶችና መጽዋቾች ሴቶችም፣ ጿሚዎች ወንዶችና ጿሚዎች ሴቶችም፣ (ካልተፈቀደ ሥራ) ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶችና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶችና አውሺዎች ሴቶችም፣ አላህ ለእነርሱ ምሕረትንና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል።” (አል-አህዛብ 33፤ 35) የአዒሻ ኃይማኖተኛነትና ዙሕድ ከተከበረ፣ ሃብታም፣ ዝነኛና ከፍ ካለ ቤተሠብ ብትወለድም ከሃብታሙ አቡበከር (ረ.ዐ) ተወልዳ በምቾት ብታድግም፤ ከነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር ችግርን በትዕግስት አሳልፋለች፤ ሕይወትን በዙህድ (ቀለል ያለና የምድራዊውን ዓለም ሕይወት የናቀ የአኗኗር ዘይቤ) መርታለች ቀለል ባለ ኑሮ ኑራለች። አላህም ለሁሉም የነብዩ ሚስቶች አላህን፣ መልዕክተኛውን እና የመጨረሻውን ዓለም በመምረጥ ከነብዩ ጋር የችግር ህይወት መምራትና ምድራዊ ደስታን በመምረጥ መካከል ምርጫ አስቀመጠላቸው። እነሱም የመጀመሪያውን መረጡ። አዒሻም ቀለል ያለ የዙህድ (ምድራዊውን ሕይወት የናቀ) ሕይወት በመምረጧ ምክንያት ጥቂት እየተመገበች፣ ጥቂት እየጠጣች፣ የተጣጠፈ እየለበሠች ካላትም ትንሽ ላይ እየለገሠች ለመኖር ተገደደች። እዚህ ጋር ሳይጠቀስ የማያልፈው ነገር የአዒሻ አለጋገስ ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዳሉት ቀኟ ሲለግስ ግራዋ አያውቅባትም። ተምሳሌታዊ ለጋስነቷ አንዳንድ ጊዜ የራሷን አንገብጋቢ ፍላጎቶች እስከመርሳት ያደርሳል። ይህ ሁኔታዋ አላህ በቁርኣን “የራሳቸው አንገብጋቢ ፍላጎት ቢኖርባቸውም እንኳ ሌሎችን ከራሳቸው ያስበልጣሉ” እንዳለው ነው። ከአዒሻ ተማሪዎች መካከል የነበረው ታላቁ የኢስላም ምሁር ዑርዋ ኢብን ዙበይር አዒሻ በየቦታው የተጣጣፈ ልብስ ለብሳ ሰባ ሺህ ዲርሃም ለምስኪኖች ስትሰጥ ማየቱን ተናግሯል። እናታችን ምንም እንኳ እድሜዋ ለጋ ቢሆንም ለአላህ ካላት መተናነስና ለነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ካላት ክብርና ለተልዕኮዋቸው ካላት ጽኑ እምነት የተነሳ ነበር ቀለል ያለ ሕይወትን ለመኖር የመረጠችው። ይህ ምርጫዋ ደግሞ ብዙ የሕይወት ስንክሳሮችን እንድትጋፈጥ አድርጓታል። ከነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ኅልፈት በኋላም አዒሻ በዙህድ መኖር፣ መጾም መጸለይ እና ለወላጅ አጦች እንዲሁም ለድሆች መርዳቷ ቀጥላለች። እውቀቷና ብልህነቷ፣የአዒሻ የአዕምሮ ብስለትና ፍጥነት ለጥቂቶች ብቻ የተሠጠ የሚባል ዓይነት ነበር። ከመምህራኖች ሁሉ ምርጡ መምህር ዘንድ የምትማር የኃይማኖት ተማሪ ብትሆንም እንዲሁ የተሠጣትን ብቻ ተቀብላ የምትነፍስ አልነበረችም። ይልቅ፤ ተመራማሪ ጭንቅላትና ጠያቂ አዕምሮ ነበራት። መታወቂያዋም ይኀው ነው። ነብዩ እየመለሱ እሷ ግን መላልሳ እየጠየቀች የምትታይባቸው ብዙ አጋጣሚዎችም ነበሩ። ለአብነት ያህልም፡- በአንድ አስፈሪ ሌሊት እርሳቸው ለሞቱ ሶሃባዎች ዱዓእ ሊያደርጉ በወጡበት ሳያውቁ እርሷ ግን ተከትላቸው መምጣቷን ሲያስተውሉ “ለምን በዚህ አስፈሪ ጨለማ ተከተልሽኝ? ጂኒሽ ጎብኝቶሽ እንዴ?” አዒሻ ግን ይህን አጋጣሚ እንኳ ጥያቄ ለመጠየቅ ተጠቀመችበት። ምን አለች? “ሁሉም ሰው የሚከታተለው ጂን አለ እንዴ?” ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) “አዎ እኔን ጨምሮ ጂን ይከታተለናል። ነገር ግን የኔውን አላህ አስልሞታል (በክፉ አያዘኝም)” አሏት። ሌላም የአዒሻን ጠያቂ ባህሪ የሚያሳይ ምሳሌ ማሳየት ይቻላል። ነብዩ ስለ ዕለተ ትንሳዔ ሲናገሩ ሁላችንም ራቁታችንን ያልተገረዝን ሆነን እንደምንቀሰቀስ ሲገልጹ አዒሻ (ረ.ዐ) እንደተለመደው “ታዲያ ሁሉም እርቃኑን ሆኖ ሲነሳ አንዱ የአንዱን ኃፍረተ-ገላ ሊያይ ነው?” ስትል ጠየቀች። ነብዩም “አዒሻ ሆይ! የእለቱ ችግር አንዱ የአንዱን ኃፍረት ለማየት የሚያስችለው አይደለም” ሲሉ መለሱላት። ለከፍተኛው ብልሃቷ ምስጋና ይግባውና አዒሻ ኢ-ምክንያታዊ ለሆኑና ከቁርኣን አስተምህሮ ጋር የሚጋጩ “ኃይማኖታዊ” ተግባራትን ታግሳ የምታልፍበት ልብ አልነበራትም። እሷ በምንም ሁኔታ የቁርኣን አስተምህሮ ከምክንያታዊነት ጋር አይጋጭም የሚል ጽኑ እምነት ነበራት። እንዴት ሆኖስ ይጋጫል አላህ ራሱ “በቁርኣኑ ውስጥ ምንም መጋጨትን አታገኙም” እያለ? በዚህ እይታዋ ምክንያት የአብደላህ ኢብኑ ዑመርን “አንድ ሠው ሲሞት ቤተሰቦቹ በሚያለቅሱት መረን የለቀቀ ለቅሶ ምክንያት ይቀጣል” የሚለውን ሐዲስ ሳትቀበል ቀርታለች። ምክንያቷም፤ “ቁርኣን ‘ማንም ነፍስ የማንኛይቱንም ኃጢያት አትሸከምም’ እያለ ነብያችን እንዴት እንዲህ ይላሉ?” የሚል ነው። ሌላኛው የአዒሻ ተመራማሪነት ማሳያ የሚሆነው ነብዩ “ውሻ፣ አህያና ሴት እነዚህ ሶስት ነገሮች ሶላት ያበላሻሉ።” ብለዋል መባሉን አለመቀበሏ ነው። አዒሻ ይሄንን አባባል ስትሰማ “ምን ያህል ብትደፍሩን ነው እኛን ከውሻና ከአህያ ጋር የምታነፃፅሩን? ነብዩ እንኳ እኔ ተኝቼ ለሊት ሲሰግዱ ሱጁድ ማድረጊያ ቦታቸው ላይ እግሬን ዘርግቼ ሲያገኙ እግሬን ቀስ አድርገው ይገፉትና ሱጁዳቸውን ያደርጋሉ” አብደላህ ኢብኑ ዑመር ሴቶቹን በትጥበት (ጉስል) ወቅት ጸጉራቸውን እንዲፈቱ ማዘዙን ስትሰማ “ታዲያ አንድነቱን ጸጉራቸውን እንዲላጩ አያዛቸውም ነበር? እኔኮ ከነብዩ ጋር በአንድ የውሃ መያዣ ስታጠብ ጸጉሬ ላይ ሶስት ጊዜ ውሃ ከማፍሰስ ውጪ ፀጉሬን አልፈታውም ነበር።” ማለቷ ይነገራል። አዎንታዊ ምልከታዋ የአዒሻን አስደናቂ ባህሪና ጥንካሬ ለመግለጽ በሕይወቷ እጅግ አስቸጋሪ የሆነውን አጋጣሚ፣ በሀሰት የዝሙት ክስ ሲቀርብባት እንዴት እንዳለፈችው መግለጹ ጠቃሚ ነው። ይህ ክስ ሲቀርብባት አዒሻ እጅግ አዘነች በጣም ኃይለኛ ድብርት ውስጥ ገባች። ሆኖም፤ ፈጽሞ አላፈገፈገችም፤ ለማንምም አላጎበደደችም። ይልቅስ፤ መተማመኛዋን አላህን በማድረግ እሱ ራሱ ንጽህናዋን እስኪገልጽ ድረስ በጽናት ቆመች። አላህ ንጽህናዋን እንደሚገልፅ እርግጠኛ ብትሆንም ቅሉ በሷ ምክንያት አላህ ለመልክተኛው ወህይ (ራዕይ) ያወርዳል ብላ ግን አልጠበቀችም ነበር። ዳሩ ግን፤ አላህ ሙሉ ሱራ (ምዕራፍ) ሲያወርድ በተለያዩ ቦታዎች ላይ የሷን ንጽህናና ታማኝነት ሲገልጽ ነብዩን ለማመስገን ፈቃደኛ ሳትሆን ቀረች። አላህን ብቻ ነው የማመሰግነው በማለት በአቋሟ ጸናች። ይህን ያለችው ግን ነብዩ ላይ ሥርኣት ለማጣት ሳይሆን የአላህን መብት ለርሱ ብቻ ከመስጠት አንጻር ነው። ይህ ተግባሯ ለሁሉም ሙስሊሞች እንደ ምርጥ ምሳሌ ሊቀርብ የሚችል ጉዳይ ነው። ምድራዊ ኃይላት የቱንም ያህል ቢሆኑ ከአላህ ጋር አይወዳደሩም። ለነገሩ ይህ አይነቱ ውስጣዊ ጥንካሬ ቀደምት ሙስሊሞች የነበራቸው ኃብት ነበር። አሁንም ለአዎንታዊ አመለካከቷ ምስጋና ይግባውና አዒሻ ኢ-ፍትሃዊነት፣ ኢ-ሞራላዊና ውሸት ያለችውን ነገር ከመጋፈጥ ወደ ኋላ ብላ አታውቅም። አንዳንዶች አቡበከር ሲዲቅ ከሞተ በኋላ እርሱ ላይ አቃቂር ለመፈለግ ሲሞክሩ ጠራቻቸውና አቡበከር በሕይወት ዘመኑ የፈጸማቸውን ተግባራት፤ ያደረጋቸውን ገድሎች እና ስኬቶቹን በመግለጽ ከርሱ ላይ ያገኙት ምን አይነት ሥህተት እንደሆነ ጠየቀቻቸው አንዳቸውም መልስ አልነበራቸውም። በኸሊፋዎቹም ላይ (ሙዓውያን ጨምሮ) አንድ የፖሊሲ ስህተት ካየች ሳትናገራቸው አልፋ አታውቅም ነበር። አንዴ ሴቶች ቀብር ዚያራ እንዳያደርጉ እቀባ ነበር። እሷ ታዲያ መካ በሄደችበት የወንድሟን ቀብር ለመዘየር በቆመችበት አንድ ሠው መጣና “ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) ሴቶች ቀብር እንዳይዘይሩ ከልክለዋል” አላት። እሷም “ነብያችን ቀብር መዘየርን ለወንድም ለሴትም ከልክለው የነበረ ቢሆንም በኋላ አንስተዋል።” አለችው። በሷ ግንዛቤ መሠረት እቀባው ለሁለቱም ጾታ እኩል ተነስቷል። ለሴቶች አልተነሳም የሚባልበት አንዳችም ማረጋገጫ የለም። በሷ ጥንካሬም የእናታችን ሰፍያህ ፍላጎት ተሳክቷል። እናታችን ሰፍያህ ለአይሁዱ ወንድሟ የሃብቷን አንድ ሶስተኛ ለመስጠት ብትፈልግም ኸሊፋው ግን “ከነብዩ አስተምህሮ ውጪ ነው” በሚል ሊፈቅድላት አልቻለም። ሆኖም፤ በአዒሻ ያላሰለሰ ጥረት የእናታችን ሰፍያህ ፍላጎት ሊሳካ ችሏል። በውርስ ህግ ላይ የነበራት ከፍተኛ ብቃትና በራስ መተማመን በሌሎች ጉዳዮች ላይም እንድትሳተፍና ሴቶች በሙስሊም ማኅበረሰብ ውስጥ ስላላቸው ሚና ያለውን አስተሳሰብ የሚለውጥ ነው። ለአብነት ያህል ሴቶች ከሶላተል ጀናዛ ስግደት እንዲታቀቡ መደረጉን መቃወሟ ነው። እንዲያውም አንዳንድ ጊዜ ጀናዛውን አስመጥታ መስጂድ በማስገባት የነብዩ ባለቤቶች እንዲሰግዱበት ታደርግ ነበር። በሁሉም የህይወት መስክ ተሳታፊ አዒሻ ለሴቶች ማኅበራዊ ተሳትፎ አቻ የማይገኝላት ድንቅ ምሳሌ ናት። ምክንያቱም፤ አዒሻ ከነብዩ ሞት በኋላ እንኳ በየትኛውም ኢስላማዊ ሕይወት ውስጥ ከመሳተፍ ወደ ኋላ ብላ አታውቅምና። በነብዩ የሕይወት ዘመን ደግሞ ጦር ሜዳ ድረስ በመሄድ የተሳትፎዋን ጥግ አሳይታለች። በዐሊይ ላይ በተካሄደው ፍልሚያም “የዑስማንን (ረ.ዐ) ገዳዮች ለመበቀል ዐልይ ቸልተኝነት አሳይቷል” በሚለው የተሳሳተ ድምዳሜዋ ምክንያት ዐሊይን ለመውጋት የተሠለፈውን ጦር መርታለች። በኋላ በዚህ አቋሟ ብትጸጸትም ዋናው ጉዳይ ግን ሴት ብትሆንም ሐሳቧን ለማሳካት እስከ ጦርነት ድረስ ለመሄድ እንደማትመለስ ማወቁ ነው። በሷ እይታ ሴት በኢስላም ያላት ሚና ቤት ውስጥ የታጠረ አይደለም። ስትፀፀትም የተጸጸተችው በዐልይ ላይ በያዘችው አቋም እንጂ በነበራት ተሳትፎ አልነበረም። ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጎን ሳይሆን ከእህቶቿ (ከሌሎቹ የነብዩ ባለቤቶች) ጎን በጀነት አል-ባቂ ለመቀበር የመረጠችውም ነብዩን በዐልይ ላይ በነበራት አቋም አፍራቸው ነው። እውቀት በማምረት ረገድ የነበራት ተሳትፎ አዒሻ ተፍሲር፣ ሐዲስ፣ ፊቅሂ እና ታሪክን በመሳሰሉ ኢስላማዊ የዕወቀት ዘርፎች እንዲሁም በዐረብኛ ቋንቋ እና በሕክምና የነበራት እውቀት በሶሃባዎችና በተከታዮቻቸው በሠፊው የሚታወቅ ጉዳይ ነው። ሌላው ቀርቶ ታላላቆቹ የነብዩ ባልደረቦች አቡበከርና ዑመር እንዲሁም የተቀሩት የነብዩ ባለቤቶች የአንድን ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔ አዒሻን ያማክሯት ነበር። ከሰባቱ ታላላቅ የመዲና ቃዲዎች መካከል አንዱ የሆነው አቡ ሰለማህ ቢን አብዱራህማን “በሕይወቴ የአዒሻን ያህል ሠፊ የሐዲስ ግንዛቤ፣ ለሙስሊሞች አስፈላጊ በሆኑ አጀንዳዎች ላይም ጥልቅ የፊቅሂ ዕውቀት ያለው እና የቁርኣን አንቀጾችንም መችና ለምን እንደወረዱ አብጠርጥሮ የሚያውቅ በውርስ ህግጋት ላይም የሚወዳደራት ሠው አላየሁም” ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል። አዒሻ ከአላህ መልክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሞት በኋላ የመምህራን መምህርት (አሰልጣኝ) ሆና አገልግላለች። በነብዩ መስጂድ ውስጥ የሚያስተምሩ ሠዎችንም ሲሳሳቱ ስታይ ታርማለች ጥያቄ ሊጠይቃት የመጣውንም መልስ ትሠጠዋለች። ከሷ ትምህርት ከቀሰሙ ሠዎች ውስጥ ጥቂቶቹ አብደላህ፣ ቃሲም፣ ዑርዋህ እና ዑምራህ ቢንት አብዱራህማን አል-አንሳሪ ይገኙበታል። ጥልቅ የሆነው የፊቅሂ ዕውቀቷ ብቻዋን ኢጅቲሃድ እንድታደርግ አስችሏታል። አል-ቃሲም እንደዘገበውም ከራሷ ኢጅቲሃድም በመነሳት በአቡበከር፣ በዑመርና በዑስማን ዘመን ከዚያ በኋላም እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ ትምህርቶችን ስትሰጥ ኖራለች። ከላይ እንደተገለጸውም የአዒሻ ኢጅቲሃድ የተመሠረተው ባላት ጥልቅ የቁርኣን እውቀት ላይ የተመሠረተ ነው። አንድ ሠው ስለአለማግባት ሲጠይቃት “አግባ አላህ ‘በርግጥ ከአንተ በፊት መልክተኞችን ልከናል፤ ለሁሉም ሚስቶችንና ልጆችን ሠጥተናል’ የሚለውን የአላህ ቃል አልሰማህምን? ስለዚህ፤ ከማግባት ረስህ አታቅብ” አለችው። ኢጅቲሃዷ ከማንምና ከምንም ነጻ መሆኑን የሚያሳየን አንዳንድ ጊዜ እይታዋ ከሌሎቹ ሶሃባዎች እይታ ጋር ቀጥታ የሚቃረን መሆኑ ነው። አንዱ መጣና “አንዲት ሴት ረጅም መንገድ ስትሄድ ሁሌ መህረም (ባል ወይም የቅርብ ዘመድ) ሊከተላት ይገባልን?” ሲል ጠየቃት። እሷም “ሁሉም ሰው ሙህረም ይኖረዋልን?” ስትል መለሠችለት። በተለይም፤ የአዒሻ ሕይወት አስደማሚ የሚሆነው የነበረችበትን ዘመን በትኩረት ስናጤን ነው። በዚህ ዘመን የሚኖሩ ሴቶች እንኳ አላህ የሠጣቸውን ችሎታ መጠቀም በማይችሉበት ኹኔታ አዒሻ በ6ተኛውና በ7ኛው ክፍለ ዘመን ያን የመሠለ ሕይወት መምራቷ ልዩ ምሳሌና ፋና ያደርጋታል። ገና ከልጅነቷ አንስቶ በንጹህ እስላማዊ አየር ውስጥ አደገች፤ ሆኖም እስረኛ አልሆነችም። ሐሳቧን በልበ-ሙሉነት ከመግለጽና በማኅበረሠቡ ጉዳዮች ከመሳተፍ የማህበረሰቧም መሪ ከመሆን ያገዳት አንዳችም ነገር አልነበረም። በቀላሉ ለማስቀመጥ አዒሻ ለአላህና ለመልክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) የተሰዋ ክቡር ሕይወትን መርታለች። ይህን አጭር መጣጥፍ በራሷ በእናታችን ንግግር እንዘጋዋለን። ምን አለች? “ሠዎችን ለማስደሰት ብሎ አላህ ያስከፋ አላህ ለሠዎች አሳልፎ ይተወዋል፤ አላህን ለማስደሰት የፈለገ ግን አላህ ይበቃዋል።” 2. አቡበክር አስ-ሲዲቅ ዐብደላህ ቢን አቡ ቁሐፋህ ኡስማን ቢን ዓሚር አል-ቁረይሽይ አት-ተሚሚይ ሲሆን የዝሆኑ ክስተት እውን በሆነ በሁለት አመት ከስድሰት ወሩ ተወለዱ። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በነብይነት ከመላካቸው በፊት አቡበክር ባልንጀራቸው ነበሩ። ከነብይነት በኋላም ቀድመው ሰለሙ። በመካው የዳዕዋ ዘመን አብረዋቸው ሆኑ። ወደ መዲና ሲሰደዱ፣ በዋሻው ታሪክና ከዚያ በኋላ እስኪሞቱ ድረስ ከርሳቸው አልተለዩም። በተቡክ ዘመቻ የሙሰሊሞችን አርማ ተሸካሚ ነበሩ። በዘጠነኛው ዓመተ ሂጅራ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በሕይወት እያሉ የሐጅ ሥርዓትን መርተዋል። ከርሳቸው ሞት በኋላም እርሳቸውን ተክተው የሙስሊሞች ኸሊፋ ሆነዋል። የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ምትክ (ኸሊፊቱ ረሱሊላህ) የሚል ማእረግም በሙስሊሞች አግኝተዋል። ኢብን ኢስሐቅ “ሲረቱል ኩብራ” በተሰኘ መጽሐፋቸው እንዳወሱት አቡበክር (ረ.ዐ) በወገኖቻቸው ዘንድ ተወዳጅ እና ተግባቢ ሰው ነበሩ። በቁረይሽ የዘር ሐረግና ታሪክ እውቀትም አቻ አይገኝላቸውም። ጸባየ መልካም ነጋዴ ነበሩ። ሰዎች የርሳቸውን እውቀት፣ ተሞክሮና መልካም ባህሪ በመሻት በጣም ይቀርቧቸው ነበር። ከርሳቸው ጋር መቀማመጥንም ይወዱ ነበር። አቡበክር ይበልጥ የሚቀርቧቸውንና የሚያምኗቸውን ሰዎች ወደ እስልምና ጋበዙ። በርሳቸው እጅ፣ ዑስማን፣ ጦልሐ፣ ዙበይር፣ ሰዕድ እና ዐብዱረህማን ኢቢን አውፍ ሰለሙ። የዕቁብ ኢቢን ሱፍያን በታሪክ ዘገባቸው እንዳወሱት፣ አቡበክር ሲሰልሙ አርባ ሺህ (የወርቅ ሳንቲሞች) ነበሯቸው። ወዲያውኑ በአላህ መንገድ መጸወቱት። ለአላህ ሲሉ ስቃይና መከራ ያስተናገዱ ሰባት ባሪያዎችን ገዝተው ነጻ ለቀቁ። እነርሱም ቢላል፣ ዓሚር ኢቢን ፋሀይራህ፣ ዚኒራህ፣ ነህዲያህንና ልጇን፣ የበኒ ሙእመል እንስት አልጋይና ኡምሙ ዓቢስ ናቸው። ኡሳማ ኢቢን ዘይድ አባታቸውን ጠቅሰው እንዳስተላለፉት “አቡበክር እውቅ ነጋዴ ነበሩ። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በነብይነት ሲላኩ አቡበክር አርባ ሺህ የወርቅ ሳንቲሞች ነበሯቸው። ባሪያዎችን እየገዙ በመልቀቅና የተቸገሩ ሙስሊሞችን በመርዳት ሐብታቸውን ወጭ አደረጉ። ወደ መዲና ሲሰደዱ 5 ሺህ (የወርቅ ሳንቲሞች) ብቻ ቀራቸው። እርሱንም መዲና ውስጥ መጸወቱት።” ቡኻሪ እንደዘገቡት ዐምር ኢቢን አል-ዓስ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፡- “የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ከርስዎ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጅ ሰው ማን ነው? በማለት ጠየቅኳቸው። ‘ዓኢሻ’ አሉኝ። ‘ከወንድስ?’ አልኳቸው። ‘አባቷ’ አሉኝ። ቀጥሎም ሌሎች ሰዎችን አወሱ።” ዐብደላህ ኢቢን ጃእፈር (ረ.ዐ) እንዲህ ብለዋል፡- “ወዳጃችን አቡበክር፣ መልካም፣ እጅግ ሩህሩህና አዛኝ ኸሊፋችን ናቸው።” ኢብራሂም አን-ነኸዒ እንዲህ ብለዋል፡- “አቡበክር በጣም አዛኝ ስለነበሩ ‘አውዋህ’ ተብለው ተጠሩ።” በ 11ኛው ዓመተ ሂጅራ በወርሃ ጀማዱል ኡላ ሰኞ ቀን በ63 ዓመት እድሜያቸው ይህችን ዓለም በሞት ተሰናበቱ። ባህሪያቸውና ስብእናቸው በጃሂልያ ዘመን ከቁረይሾች መሐል በዘር ሐረግና በታሪክ እውቀት ወደር አይገኝላቸውም። ውጤታማ ነጋዴም ነበሩ። በመልካም ባህሪና በችሮታ ይታወቃሉ። ወገኖቻቸው ይወዷቸዋል። አስካሪ መጠጥ አይጠጡም፣ ጣኦት አያመልኩም። ስብእናቸውን የሚያጎድፍ አንዳች ድርጊት ሲፈጽሙ አልተስተዋሉም። ቆዳቸው ነጭና አካላቸው ሸንቃጣ፣ የፊታቸው ስጋ መጠነኛ ነበር። ዓይኖቻቸው ገባ፣ ግንባራቸው ወጣ ያሉ ነበሩ። ጸጉረ ብዙ፣ የተስተካከለ ቁመና ባለቤት ነበሩ። ሰዎች በጃሂልያ ዘመን የአቡበክርን መልካም ስብእና እና ታማኝነት በማወቃቸው “አስ-ሲዲቅ” (እውነተኛው) በሚል ቅጽል ስም ጠሯቸው። በታማኝነታቸው ቁረይሾችን በመወከል ይፈጣጠሙ ነበር። ቁረይሾች እርሳቸው ያጸደቁትን ያጸድቃሉ። ሌላ ሰው ያጸደቀውን ግን ተቀብለው ለመተግበር ያንገራግራሉ። ኢስላምን መቀበላቸው ከነብይነት በፊት የመልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) ባልደረባ ነበሩ። አላህ ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) በመልእክተኝንት ሲያልቃቸው ወደ እስልምና መጀመሪያ የጋበዙት አቡበክርን ነበር። እርሳቸውም ሳያመነቱ እስልምናን ተቀበሉ። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ይህን በማስመልከት ሲናገሩ፡- “የትኛውም ሰው ወደ እስልምና ስጋብዘው ይከብደዋል። ለመቀበልም ያመነታል። አቡበክር ሲቀር። እርሱ ግን ወዲያውኑ እንደጠራሁት ሳያመነታ ተቀበለኝ።” (ሲረት ኢቢን ሂሻም) በተለያዩ የዳዕዋው እርከኖች ውስጥ ከአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሳይነጠሉ፣ አስፈላጊውን ሁሉ እገዛ እያደረጉላቸው፣ ለአምላክና ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ጥሩና አማኝ፣ ለሐይማኖታቸው ቀናኢ ሆነው ኖረዋል። በዚህ ሂደትም የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የስደት ጉዞ ተጋሪ፣ የዋሻ ውስጥ ባልደረባ እንዲሆኑ ያስቻሏቸውን በርካታ መከራዎች አስተናግደዋል። ገንዘባቸውን ሁሉ ለእስልምና ዳዕዋ ሳይሰስቱ ችረዋል። ከአላህ መልእክተኛም (ሰ.ዐ.ወ) “የአቡበክር ገንዘብ የጠቀመኝን ያህል በማንም ገንዘብ አልጠቀመኝም።” የሚል ምስክርነትአግኝተዋል። (አህመድ፣ አቡ ሐቲምና ኢቢን ማጃህ) የዚህ ሁኔታ የአላህን መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እስከ እለተ ሞታቸው ድረስ ደግፈው ለቀልባቸውም ይበልጥ ቅርብና ለኸሊፋነትም ይበልጥ ብቁ ሶሐባ ለመሆን ታደሉ። በዚህ ረገድ ታላቁ ነቢይ (ሰ.ዐ.ወ) የሰጡት ምስክርነት ከበቂ በላይ ነው። እንዲህ ብለዋል፡- “በባልደረባነትና በገንዘብ ከማንም በላይ የደገፈኝ አቡበክር ነው። ከአምላኬ ውጭ የመጨረሻውን ፍጹማዊ ፍቅር የምለግሰው ሰው ቢኖር ኖሮ ያ ሰው አቡበክር ይሆን ነበር። ቢሆንም የእስልምና ወንድማማችነት እና ፍቅር አስተሳስሮናል።” (ቡኻሪ፣ ሙስሊምና ቲርሚዚ ዘግበውታል) ልቅናቸውን የሚገልጹ ምስክርነቶች የአቡበክርን ልቅና ከሚያሳዩ ዘገባዎች መካከል አቡ ሰዒድ (ረ.ዐ) ያስተላለፉት ይገኝበታል። እንዲህ ብለዋል፡- “ከእለታት አንድ ቀን የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)፡- ‘አላህ አንድን ባሪያውን ከዚህች ዓለም ሕይወትና ከርሱ ዘንድ ካለው ጸጋ ሲያስመርጠው ከአላህ ዘንድ ያለውን መረጠ።’ በማለት ሲናገሩ አቡበክር አለቀሱ። ለቅሷቸው አስገረመን። ለካስ ምርጫ የተሰጣቸው መልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) ኖረዋል። አቡበክርም ከማንኛችንም ቀድመው ይህን ተረድተዋል:: መልእክተኛውም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‘በባልደረባነትና በገንዘብ ከማንም በላይ የደገፈኝ አቡበክር ነው። ከአምላኬ ውጭ የመጨረሻውን ፍጹማዊ ፍቅር የምለግሰው ሰው ቢኖር ኖሮ ያ ሰው አቡበክር ይሆን ነበር። ቢሆንም የእስልምና ወንድማማችነት እና ፍቅር አስተሳስሮናል። የአቡበክር በር ሲቀር ሁሉም የመስጂዱ በሮች ይዘጋሉ’። ” (ቡኻሪ፣ ሙስሊምና ቲርሚዚ ዘግበውታል) በሌላ ዘገባ እንደተወሳው እንዲህ ብለዋል፡- “ከአምላኬ ውጭ ፍጹማዊ ፍቅር የምለግሰው ሰው ቢኖር ኖሮ ያ ሰው አቡበክር ይሆን ነበር። ይህም ሆኖ ወንድሜና ባልደረባዬ ነው። አላህ ባልደረባችሁን ፍጹማዊ ወዳጁ (ኸሊል) አድርጎታል።” (ቡኻሪ፣ ሙስሊምና ቲርሚዚ ዘግበውታል) በአላህና በመልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) ማመን አቡበክር የመጀመሪያው ሙስሊም እንዲሆኑና የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) የሚናገሩትን ሁሉ ቅንጣት ሳይጠራጠሩና ሳያመነቱ እንዲቀበሉ የረዳቸው ይህ እምነታቸው ነው። በኢስራእ እና ሚዕራጅ ሐዲስ ውስጥ ያሳዩትን እጅግ አንጸባራቂ አቋም አስተውል። የአላህ መልእክተኛ ለባልደረቦቻቸውና ለቁረይሾች በዚያች ሌሊት ያጋጠማቸውን ክስተት ባጫወቷቸው ጊዜ እምነተ ደካሞች ከእስልምና እስከ መውጣት ደረሱ። ቁረይሾችም በአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ተሳለቁ። አቡበክር ስለዚህ እንግዳ ክስተት የሚኖራቸውን አቋም ለማወቅም አቡ ጀህል ወደርሳቸው ሄደ። ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የተናገሩትንም አጫወታቸው። እርሳቸውም በፍጹም መተማመንና በእርጋታ፡- “በእርግጥ ይህን ተናግረዋልን?” በማለት ጠየቁ። አቡ ጀህልም “አዎ” ሲል መለሰ። እርሳቸውም፡- “ሙሐመድ ይህን ከተናገረ እውነቱን ነው” አሉ። አቡ ጀህልና አብረውት የነበሩት ባልደረቦቹም፡- “በአንድ ቀን ሌሊት ወደ በይተል መቅዲስ ሄጄ ሳይነጋ በፊት ተመለስኩ ማለቱን አምነህ ትቀበላለህን?” አሏቸው። አቡበክር የሚከተለውን አስገራሚ መልስ ሰጡ፡- “ከዚህ ይበልጥ እንግዳ የሆነ ነገር ተናግሮ አምኘዋለሁ። ጧት ማታ ከሰማይ መልእክት እንደሚወርድለት ነግሮኝ ተቀብየዋለሁ” አሉ። ወደ ነቢዩ (ሶ.ወ.ወ) በመሄድም የኢስራእን ታሪክ ሰሙ። “አንተ የአላህ መልክተኛ መሆንህን እምሰክራለሁ።” በማለትም የሰሙትን ሳያመነቱ መቀበላቸውን አረጋገጡ። (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል) የመጨረሻውን የምጥቀት ጫፍ የደረሰ ኢማን፣ የዚህ እምነት ባለቤት የኢስላም ታላላቅ ሰዎች ፈርጥ ቢሆኑ ምኑ ያስገርማል! አቡበክር ነፍሳቸዉንና ገንዘባቸውን ለእስልምና ዳዕዋ መሰዋታቸው የጽኑ እምነታቸው አይቀሬ ውጤት ነው። ኢማን ወደ ቀልብ ሲገባ ለመስዋእትነት ያነሳሳል። እንደ አቡበክር አይነት እጅግ ጽኑና ጥልቅ እምነት ከሆነስ?! አቡበክር ራሳቸውን ለመስዋእትነት አቅርበው የአላህን መልእክተኛ የታደጉባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው። አንድ ቀን ቁረይሾች ከካዕባ መስክ ላይ የአላህን መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ለማነቅ ሙከራ ሲያደርጉ አቡበክር ተከላከሉላቸው። በዚህ ጊዜ ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ትተው ከርሳቸው ላይ በመረባረባቸው ራሳቸውን ስተው እስኪወድቁ ድረስ ደበደቧቸው። አፍንጫቸውን ከዓይናቸው ወይም ከጉንጫቸው መለየት እስኪያዳግት ድረስ ክፉኛ ቆሰሉ። ሰዎች አንስተው ወደቤታቸው ወሰዷቸው። ራሳቸውን ሲያውቁ መጀመሪያ ያቀረቡት ጥያቄ፡- “የአላህ መልእክተኛ በምን ሁኔታ ውስጥ ናቸው?” የሚል ነበር። (ሲረቱ አን-ነበዊያህ ዘይኒ ደህላን፡፡) ከመልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ወደ መዲና በተሰደዱ ጊዜም ተመሳሳይ መስዋእትነት ከፍለዋል። ቁረይሾች አግኝተው ሊገድሏቸው ብርቱ ጥረት አድርገዋል። በዚህ ጊዜ የአቡበክር አቋም እጅግ አስገራሚ ነበር። ቁረይሾች ከዋሻው በር ላይ ቆመው በነበረ ጊዜ የተናገሩትን ድንቅ ቃል እንመልከት። “የአላህ መልእክተኛ ሆይ! አንደኛቸው ወደ እግሩ ስር ቢያይ ይመለከተናል።” መልእክተኛው ግን ባልደረባቸውን እንዴት እንደሚያጸኑ ያውቁ ነበር። እንዲህ አሉ፡- “አቡበክር ሆይ! አላህ አብሯቸው ባለ ሁለት ሰዎች ስጋት አይግባህ።” አቡበክር ገንዘባቸውን ሁሉ ለእስልምና ዳዕዋ መስዋእት አደረጉ። ዓኢሻ እንዲህ ብለዋል፡- “አቡበክር 40 ሺህ (የወርቅ ፍራንክ) ለዳዕዋ መጸወቱ። የአላህ መልእክተኛ ለአስቸጋሪው የተቡክ ዘመቻ ጦርነት ትጥቅና ስንቅ እንዲዘጋጅ ባልደረቦቻቸውን በጠየቁ ጊዜ ሶሐቦች ገንዘቦቻቸውን እየያዙ መጡ። ኡስማን ብዙ ገንዘብ አመጣ። ዑመር ግማሽ ሐብታቸውን መጸወቱ። አቡበክር ደግሞ ሙሉ ገንዘባቸውን ሰጡ። የአላህ መልእክተኛም (ሰ.ዐ.ወ)፡- ‘አቡበክር ሆይ! ለቤተሰቦችህ ምን አስቀረህ?’ ሲሏቸው። ‘አላህንና መልእክተኛውን’ ሲሉ መለሱ።” (ቲርሚዚ ዘግበውታል) ብልህነትና ቆራጥነት በጃሂልያ ዘመን ወገኖቻቸው ጣኦት ለማምለክ ሲጋፉ እርሳቸው አንድም ጊዜ እንኳ ለጣኦታት ለመስገድ ካለመፍቀዳቸው፣ ወገኖቻቸው በአስካሪ መጠጥ ሲነከሩ እርሳቸው ግን ኢምንት እንኳ ካለመጎንጨታቸው የበለጠ ብልህና አስተዋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ነገር የለም። ጣኦት አምልኮ ቂልነት እና ጥመት፣ አስካሪ መጠጥ መጠጣትም ውድቀትና ውርደት መሆኑን በብሩህ አእምሯቸው ተረድተዋል። ምን ያህል ጀግናና ቆራጥ እንደሆኑ ለማሳየት የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በሞቱና ከፊል ዐረቦች በኢስላማዊው ስርዓት ላይ ባመጹ ጊዜ ያሳዩአቸው አስደናቂ የጀግንነት አቋሞች በቂ ናቸው። ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በሞቱ ጊዜ ሶሐቦች እጅግ ከማዘናቸው የተነሳ ከፊሎቹ አንደበታቸው ተሳሰረ። ሌሎችም ከተቀመጡበት መነሳት ተሳናቸው። ዑመርም (ረ.ዐ) “ነብዩ አልሞቱም። ይመለሳሉ።” እስከማለት ደረሱ። አቡበክር ግን ሌሎች ሰዎች እንደሚሞቱት መልእክተኛውም መሞታቸውን አወጁ። የዑመርን ንግግር ሐየሱ። ሶሐቦችን አረጋጉ። የሚከተለውን የአላህ ቃልም አስታወሱ፡- “ሙሐመድም ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡” (ኣሊ-ዒምራን 3፤144) ሪዳህን ክስተትን የተቆጣጠሩበት ሁኔታም በወሳኝና ፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ የሚላበሱትን ፍጹም ጀግንነት ያሳያል። ያኔ አላህ የአቡበክርን ቀልብ በሐቅ ላይ ባያጸና እና የጽኑ ነብያትን ቆራጥነት ባያላብሳቸው ኖሮ ተከስቶ የነበረው ፈተና ገና ለጋ የነበረውን የእስልምና ሕንጻና መንግስቱን ባወደመው ነበር። ይህም ስለሆነ ነው አቡበክር ከአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በኋላ ሁለተኛው የእስልምና መንግስት መስራች ተብለው የሚወደሱት። ትህትናና ቁጥብነት እንደ አቡበክር ያለ ታላቅ ስብእና ስልጣን አያታልለውም። ከኢስላማዊው አደብና ስነምግባር አያወጣውም። እናም በኸሊፋነት ዘመናቸው ልክ እንደ ቀድሞው ለስላሳና አዛኝ፣ ለሕዝባቸው ጉዳይም ቀናኢ ሆነው ቀጠሉ። ተከታዩ ታሪክ አቡበክር በኸሊፋነት ዘመን የነበራቸውን ትህትና ለማሳየት ጥሩ ምስክር ነው፡- አቡበክር ለአዛውንትና ረዳት አልባ እንስቶች ዘወትር ጠዋት ፍየል ያልቡ ነበር። ኸሊፋ በሆኑ ጊዜ አንዲት የመንደራቸው እንስት፡- “ከእንግዲህ አቡበክር ፍየሎቻችንን አያልብልንም” አለች። አቡበክር ይህን ማለቷን ሲሰሙ፡- “በአላህ እምላለሁ፣ እንደወትሮው ሁሉ ማለቤን እቀጥላለሁ። የኖርኩበትን መልካም ባህሪ አላህ እንደማይቀይርብኝ ተስፋ አደርጋለሁ።” አሉ። የዓለማችን ታላላቆች ለክብራቸው እንዲያጎበድዱ የሚያደርግ አንጸባራቂ አቋም ነው።፡ ከስጋዊ ስሜቶችና ዝንባሌዎች በላይ በመምጠቅ የኡምማውን መብትና አስፈልጎት የማስታወስ፣ ክብሩንና ገንዘቡን የሚጠብቅለት ታላቅነት ነው። የአቡበክር ዙህድ የአቡበክርን ዙህድ (ለዓለማዊ ጸጋና ድሎት አለመጓጓት) ከሚያሳዩ ክስተቶች መሐል ኢማም አህመድ፣ አኢሻን ጠቅሰው የዘገቡት ታሪክ ይገኝበታል። እንዲህ ብላለች፡- “አቡበክር ሲሞቱ አንዲት ዲናር ወይም ዲርሃም አልተውም። ከመሞታቸው በፊት ገንዘባቸውን በሙሉ ወደ በይተል ማል (የሙስሊሞች የገንዘብ ግምጃ ቤት) አስገብተውት ኖሯል።” ዑርወት እንዳስተላለፉት አቡበክር ኸሊፋ በተደረጉ ጊዜ ያላቸውን እያንዳንዷን ዲርሃምና ዲናራቸውን ወደ ሙስሊሞች በይተል ማል አስገቡ። “በዚህ ገንዘብ እነግድ ነበር። አሁን ግን ኸሊፋቸው ሲያደርጉኝ መነገድ አልቻልኩም።” አሉም። አጧእ ቢን ሳኢብን በመጥቀስ ቢን ሰእድ እንደዘገቡት አቡበክር ኸሊፋ በተደረጉ ማግስት ጠዋቱኑ በርካታ ኩታ በትከሻቸው ተሸክመው ሲሄዱ ዑመር ተመለከቷቸው። “የት እየሄድክ ነው?” ሲሉም ጠየቋቸው። “ወደ ገበያ” በማለት መለሱ። “የሙስሊሞች ሐላፊ ተደርገህ እያለ ኃላፊነትህን ትተህ ገበያ ውስጥ ምን ትሰራለህ?” ሲሉም ጠየቋቸው። “ቤተሰቦቼን ምን ላበላ ነው?” አሉ አቡበክር። “አቡ ዑደይዳህ ቀለብ ይወስንልሃል” አሏቸው። ተያይዘው ወደ አቡ ዑበይዳህ ዘንድ ሄዱ። እርሳቸውም፡- “አንድ ሙሃጅር የሚበቃውን ቀለብ፣ ሳይበዛም ሳያንስም፣ እቆርጥልሃለሁ። ለክረምትና ለበጋ የሚሆን ልብስም እገዛልሃለሁ። እርሱ ሲነትብ ትመልሰውና በልዋጩ ሌላ ትወስዳለህ” አሉ። በየቀኑ ግማሽ ፍየል ወሰኑላቸው። ገላቸውን የሚሸፍኑበት እራፊ ጨርቅም ሰጧቸው! በበጎ ነገሮች ሁሉ ቀዳሚ አቡ ሁረይራ እንዳስትላለፉት ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ)፡- “ከናንተ ውስጥ ጾም ይዞ ያነጋ ማን ነው? በማለት ጠየቁ። አቡበክርም፡- ‘እኔ’ አሉ። ከናንተ ውስጥ ጀናዛን የሸኘ ማን ነው? ሲሉም ጠየቁ። አቡበክርም፡- ‘እኔ’ አሉ። ዛሬ ምስኪንን ያበላ ማን ነው? አሉም። አቡበክርም፡- ‘እኔ’ አሉ። በሽተኛ የጠየቀስ ማን ነው? ሲሉ፣ አቡበክር ‘እኔ’ አሉ። የአላህ መልእክተኛም፡- እነዚህ በጎ ድርጊቶች በአንድ ሰው ላይ አይሰባሰቡም፣ ያ ሰው ጀነት የገባ ቢሆን እንጅ አሉ።” (ሙስሊም ዘግበውታል) “ጅብሪል መጣና እጄን ይዞ ተከታዮቼ የሚገቡበትን የጀነት በር አሳየኝ። አሉ። አቡበክርም፡- ‘ከርስዎ ጋር ሆኜ ባየው እወድ ነበር’ አሏቸው። ነቢዩም፡- አቡበክር ሆይ! ከኡመቴ (ሕዝቦቼ) ውስጥ መጀመሪያ ጀነት የምትገባው አንተ ነህ አሏቸው።” (አቡ ዳውድ ዘግበውታል) የአላህ ፍራቻ እና ጥንቃቄ አቡበክር አንድ ባሪያ ነበራቸው። ዘወትር ጠዋት እየወጣ ስራ በመስራት ገንዘብ ያገኛል። አንድ ቀን ምግብ ይዞ መጣ። አቡበክርም አንድ ጉራሽ ተመገቡለት። ባሪያውም በመሐይምነት ዘመን ለፈጸመው የጥንቆላ ተግባር ከተሰጠው ክፍያ ያገኘው ምግብ እንደሆነ ነገራቸው። አቡበክርም፡- “ልታጠፋኝ ተቃርበህ ነበር።” አሉና ጣታቸውን ወደ ጉሮሯቸው በመላክ እንዲያስመልሳቸው ሞከሩ። አልወጣ ብሎ አስቸገራቸው። “በውሃ እንጅ አይወጣም” ሲሏቸው በሳህን ውሃ እንዲቀርብላቸው አደረጉና እርሱን እየጠጡ የበሉትን ሁሉ አስመለሱ። “አላህ ይዘንልዎት። ለአንዲት ጉርሻ ይህን ያህል ራስዎን ያንገላታሉን?” ተባሉ። “ነፍሴ ከአካሌ ካልተነጠለች ይህች ጉርሻ የማትወጣ ቢሆንም እንኳ ነፍሴን ከማውጣት ወደኋላ አልልም። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)፡- ‘በሐራም ምግብ የበቀለ ስጋ እሳት ለርሱ ይበልጥ የተገባ፣ ነው’ ሲሉ በመስማቴ በዚህ ጉርሻ አማካይነት ከአካሌ አንዳች ነገር እንዳይበቅል ስለፈራሁ ነው” አሉ። (በይሐቂ እንደዘገቡት አል ሒልያህ 2/31) የአምላካቸውን ከለላነት መምረጣቸው ቡኻሪ እንደዘገቡት ዓኢሻ (ረ.ዐ) የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ወላጆቼ ሙስሊም ሆነው እንጅ አላውቃቸውም። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ጠዋትና ማታ ከኛ ዘንድ የሚመጡ ሆነው እንጅ አንድም ቀን አላለፈም።” ሙስሊሞች መካ ውስጥ እንግልት ሲበዛባቸው አቡበክር ወደ ሐበሻ ለመሰደድ መካን ጥለው ወጡ። “በርከል ገማድ” ከተባለ ቦታ ሲደርሱ ኢብን ዱግነህ አገኛቸው። የጎሣ አለቃ ነው። “የት እየሄድክ ነው?” ሲልም ጠየቃቸው። “ወገኖቼ ከሀገር አስወጡኝ፤ ሀገር ላገር እየተዘዋወርኩ አምላኬን ማምለክ እፈልጋለሁ” ሲሉ መለሱ። ኢብን ዱግነህም፡- “አቡበክር ሆይ! አንተን የመሰለ ሰው ሀገር ጥሎ አይወጣም። እንዲወጣም አይደረግም። አንተ ችግረኛን የምትረዳ፣ ዝምድናን የምትቀጥል፣ ችግርን የምትጋራ፣ እንግዳ የምታስተናግድ፣ ከባለመብት ጎን የምትቆም ሰው ነህ። ስለዚህ እኔ ከለላ እሆንሃለሁ። ተመለስና እዚያው ሀገርህ ውስጥ ጌታህን አምልክ” አላቸው። ወደ መካ ተመለሱ። ኢቢን ዱግነህም አብሯቸው ሄደ። ማታ ላይ የቁረይሽ ባላባቶችን በየቤታቸው እየዞረ፡- “አቡበክር ከሀገር የሚወጣ ወይም እንዲወጣ የሚደረግ ሰው አይደለም። ችግረኛን የሚታደግን፣ ዝምድናን የሚቀጥልን፣ ችግርን የሚጋራን፣ እንግዳ የሚንከባከብንና ከተበዳይ ጎን የሚቆምን ሰው ከሀገር ታስወጣላችሁን?” ሲል ወቀሳቸው። ቁረይሾች ለአቡበክር ከለላ መሆኑን ተቀበሉ። ግና እንዲህ ሲሉ አስጠነቀቁት፡- “ለአቡበክር አምላክን ቤቱ ውስጥ ብቻ እንዲያመልክና እንዲሰግድ ንገረው። በቤቱ ውስጥ ያሻውን ነገር ያንብብ። እኛን እያወከን ግን፣ እነዚህን ነገሮች በይፋ ከፈጸመ ሴቶቻችንና ልጆቻችን እንዳይፈተኑ እንሰጋለን።” ኢብን ዱግነህ ለአቡበክር ይህንኑ ነገራቸው። አቡበክር ጌታቸውን በቤታቸው ውስጥ ማምለካቸውን ቀጠሉ። ሶላት በይፋ አይሰግዱም፤ ቁርአንም ከቤታቸው ውጭ አይቀሩም። በኋላ ግን ከካዕባ ግቢ ውስጥ የመስገድ ሐሳብ መጣላቸው። ይህንኑ አደረጉ። ከርሱ ውስጥም መስገድና ቁርአን መቅራት ጀመሩ። የጣኦታውያን እንስቶችና ሕጻናትም በአግራሞት ይመለከቷቸው ጀመር። አቡበክር አልቃሽ ሰው ነበሩ። ቁርአን ሲቀሩ በለቅሶ ይንፈቀፈቃሉ። ይህ ድርጊታቸው የቁረይሽ ባላባቶችን አስደነገጠ። ለኢቢን ዱግነህም እንዲህ የሚል መልእክት ላኩ፡- “አቡበክር አምላኩን ከቤቱ ውጭ ላያመልክ ቃል አስገብተን ከለላ ትሆን ዘንድ ፈቅደን ነበር። እርሱ ግን ቃሉን ጥሶ በካዕባ ግቢ ውስጥ መስገድ እና መቅራት ጀምሯል። ሴቶቻችንና ልጆቻችን እንዲፈተኑ ስለማንሻ ከልክለው። ቤቱ ውስጥ ብቻ ማምለክ ከፈለገ ይችላል። አምልኮውን ይፋ ማድረግ የሚፈልግ ከሆነ ግን ከለላነትህን መልስለት፤ የሰጠንህን ቃል ማፍረስ አንሻም። በይፋ እንዲያመልክም አንፈቅድለትም።” ዓኢሻ እንዳስተላለፉት ኢቢን ዱግነህ ወደ አቡበክር ዘንድ መጣና፡- “እኔና አንተ የተጋባነውን ቃል ታውቃለህ። ስለዚህም በቃልህ መሠረት ቤትህ ውስጥ ብቻ አምልክ፤ ካልሆነ ከለላነቴን መልስልኝ። ከለላዬ እንዲጣስና ዐረቦችም ይህን ጉድ እንዲሰሙ አልሻም” አለ። አቡበክርም፡- “ከለላነትህን መልሸልሃለሁ። ከእንግዲህ የአላህን ከለላነት ብቻ እሻለሁ።” አሉ። ከአቡበክር ሌላ ይህን የጀግንነት አድራጎት ማን ሊፈጽም ይችላል። በዚህ ድንቅ አቋም ሊዋብ የሚችለው የአቡበክር ስብእና ብቻ ነው። በአላህ ላይ የነበራቸው እምነት ይህን ያህል ጽኑና ጠንካራ ነበር። የክህደት ሐይሎች ዙሪያውን ከበው ሊያጠፏቸው ባሰፈሰፉበት ወቅት አላህ ከየትኛውም ፍጡር የላቀ፣ ከለላው የሚከጀል፣ ተስፋ የሚጣልበት ብቸኛ ሐይል መሆኑን፣ አላህ የረዳውን የሚያሸንፈው እንደሌለ በጥልቅ ተረዱ። በኸሊፋነት ዘመን አቡበክር ኸሊፋ የሆኑት ሙስሊሞች በነብያቸው (ሰ.ዐ.ወ) ሞት ምክንያት ግራ በተጋቡበት አስፈሪ ወቅት ነው። በወቅቱ ከፊል ዐረቦች ከኢስላም አፈንግጠዋል። ሌሎች ከመልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) በኋላ ለማንም ላለማደር ወስነዋል። ሮሞች ሂጃዝን ለመውረር በዝግጅት ላይ ናቸው። የሮሞችን ጥቃት ለመመለስ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ያዘጋጁት የኡሳማ ኢቢን ዘይድ (ረ.ዐ) ጦር ጉዞውን ለመቀጠል ከመዲና አፋፍ ላይ ሆኖ ትእዛዝ ይጠባበቃል። በዚህ ሁሉ ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ ኸሊፋ የተደረጉት አቡበክር ሐላፊነታቸውን በሚገባ ተወጡ። አፈንጋጮችን (አል-ሙርተዲን) አደብ (ሥርዓት) ለማስያዝ ቆራጥ ውሳኔ ወሰኑ። ሌሎች ሶሐቦች የጦርነቱን ሐሳብ ባይደግፉም እርሳቸው ግን በዚሁ ሐሳባቸው ጸኑ። በኋላ ላይ ግን ሶሐቦች የርሳቸውን ሐሳብ ደገፉ። በአላህ በረከትም እስልምናን በዐረቢያ ውስጥ እንደ አዲስ ለማጽናት ተመሙ። አላህ የለገሳቸው ድል ታላቅ ነበር። የአመጽ እንቅስቃሴውን በእንጭጩ ቀጩት። የኡሳማንም ጦር የአላህ መልእክተኛ ወዳሰማሩት ግንባር አዘመቱ። ይህ ጦር እስልምናን ለማስፋፋትና ሕዝቦችን ነጻ ለማውጣት የተገኙ ድሎች ሁሉ መነሻ ሆነ። የአስተዳደር ፖሊሲያቸው ኸሊፋ በተደረጉ ጊዜ ያሰሙት ተከታዩ ታሪካዊ ንግግር ነበር፡- “እኔ በናንተ ላይ ተሹሚያለሁ። ይህ ማለት ግን ከናንተ ብልጫ አለኝ ማለት አይደለም፤ በጎ ከሰራሁ አግዙኝ። ክፉ ከሰራሁ አስተካክሉኝ። እውነት መናገር አደራን መጠበቅ ሲሆን፣ መዋሸት ደግሞ ክህደት ነው። ከናንተ መካከል ደካማው መብቱን እስካሟላለት ድረስ ከኔ ዘንድ ጠንካራ ነው። ከናንተ ዘንድ ጠንካራው ግዴታውን እንዲወጣ እስካደርገው ድረስ ከኔ ዘንድ ደካማ ነው። ሰዎች በአላህ መንገድ መፋለምን ሲተው አላህ ውርደትን ያከናንባቸዋል። በአንድ ሕዝብ ውስጥ ዝሙት ከተስፋፋ አላህ ሁሉንም በቅጣቱ ያጠቃልላቸዋል። አላህንና መልእክተኛውን እስከታዘዝኩ ድረስ ታዘዙኝ። የአላህን እና የመልእክተኛውን ፈቃድ ስጥስ ግን ልትታዘዙኝ አይገባም።” አቡበክር የአስተዋይ ልቦና፣ የሩቅ አሳቢ አእምሮ ባለቤት ነበሩ። በዘመናቸው ያሉ ሁኔታዎችን በጥንቃቄ ከማየት፣ በጥልቀት ከማስተዋል የመነጨ ንግግራቸው የልብ ብርታትን፣ ፍጹም መተማመንና ጽኑነትን የተላበሰ ነው። የኸሊፋነት ዘመናቸው ጥቂት ቢሆኑም እጅግ አስደናቂና ታላላቅ በሆኑ ስኬቶች የተሞሉ ናቸው። የአቡበክር ብልህነት በበርካታ አጋጣሚዎች ተስተውሏል። በተለይም እጅግ ፈታኝ በሆኑ ሁኔታዎች። ታላቅ ሰው ታላላቅ አቋሞችን ያስመዘግባል። ቁርኣንን የመሰብሰብ ድንቅ ተግባር በየማማህ ጦርነት ወቅት በርካታ የቁርአን አዋቂዎች የመገደላቸውን ዜና አቡበክር በሰሙ ጊዜ ዑመር አብረዋቸው ነበሩ። በዚህ ጦርነት በርካታ የቁርአን አዋቂዎች ተገድለዋል። “በሌሎች ጦርነቶችም ተመሳሳይ ሁኔታ ተፈጥሮ አዋቂዎቻችን እንዳያልቁ እሰጋለሁ። ስለዚህም በነቢዩ ዘመን የተጻፉ የቁርኣን ጽሑፎች እንዲሰበሰቡ ብታደርግ መልካም ይመስለኛል” አቡበክርም፡- “የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ያላደረጉትን ነገር እንዴት እኔ አደርገዋለሁ?” ሲሉ ጠየቁ። ዑመርም፡- “በአላህ እምላለሁ! ይህን ብታደርግ መልካም ነው” አሉ። ዑመር አቡበክርን ደጋግመው ጎተጎቱ። በመጨረሻም አቡበክር በሐሳቡ ተስማሙ። ዘይድ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል አቡበክር እንዲህ አሉኝ፡- “አንተ አስተዋይ ወጣት ነህ በመጥፎ ነገር አንጠረጥርህም። ለአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ቁርኣን ሲወርድላቸው እየተከታተልክ ትጽፍ ነበር። ስለዚህም የተጻፉ የቁርኣን መልእክቶችን በአንድ አሰባስብ” አሉኝ። በአላህ እምላለሁ! ይህን ሐላፊነት ከሚያሸክሙኝ ተራራ እንድገፋ ቢያዙኝ እመርጥ ነበር። “የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ያላደረጉትን እንዴት እናንተ ታደርጋላችሁ?” አልኳቸው። አቡበክርም “በአላህ እምላለሁ! በጎ ነገር ይመስለኛል” አሉኝ። ደጋግመውም ጎተጎቱኝ። በመጨረሻ በሐሳባቸው ተስማማሁ። በተለያዩ ቁሳቁሶች ላይ ተጽፎ የነበረውን ቁርአን ከያለበት ተከታትዬ ሰበሰብኩት። የአት-ተውባህን የመጨረሻ አናቅጽም ከኹዘይማህ ቢን ሳቢት ዘንድ አገኘሁት። “ከጎሳችሁ የሆነ ችግራችሁ በእርሱ ላይ ጽኑ የሆነ፣ በእናንተ (እምነት) ላይ የሚጓጓ፣ በምእምናን (ላይ) ርኅሩኅ አዛኝ የኾነ መልክተኛ በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ ቢያፈገፍጉም አላህ በቂዬ ነው፡፡ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ በእርሱ ላይ ተጠጋሁ እርሱም የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው በላቸው፡፡” (አል-ተውባህ 9፤ 128-129) (ሐዲስ ሐሰኑን ሶሂህ) ዘመን ተሻጋሪ መልእክቶቻቸው። “ሰዎች ሆይ! በአላህ እምላለሁ! ጠላቶቻችሁ ቢበዙ፣ ወዳጆቻችሁ ቢያንሱና ሰይጣን በሙሉ ኃይሉ ቢዘምትባችሁም እንኳ አላህ ይህን ሐይማኖት የሐይማኖቶች ሁሉ የበላይ ያደርገዋል። ጣኦታውያን ይህን ቢጠሉም። ንግግሩ እውነት፣ ቃል ኪዳኑም የማይታብል ቅል ነው። አህባሽ ማን ነው የሀበሺ (አህባሽ) መንገድ የጀመረው አብደላ አል-ሐረሪ የተባለ ግለሰብ ነበር፡፡ ግለሰቡ ሐረር የተወለደ ሲሆን የሀይለ ስላሴ መንግስት ቀኝ እጅ ነበር፡፡ ከሃይለስላሴ አማች አንደርጌ ጋር ሆኖ ዓሊሞችን ሲያሳስር፣ መብትና እኩልነትን የሚሉትን ሲያጠቃ እና ሲሰልል ቆየ፡፡እ.ኤ.አ በ1940 (1367 ሂጅራ) ላይ በሐረር የቁርኣን ሂፍዝ ማዕከል መምህራንን አሳስሮ አስዘጋ፡፡ የመርከዙን ዳይሬክተር ሼህ ኢብራሁም ሀሰንን አሳስሮ 23 ዓመታት አስረፈደባቸው፡፡ አብደላ አል-ሐረሪ የፈጠረው ፊትና ‹‹ፊትነተልኩሉብ›› ተብሎ ይታወቃል፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሀደሬ ሰፈር ሙስሊሙን ሲያጋጭ ቆይቶ በ1948 ወደ እስራኤል ተጓዘ፡፡ ለዓመት በዚያ ቆይቶ በ1949 ወደ ሶሪያ ገባ፡፡ ከዚያም በ1950 ወደ ሊባኖስ ተጓዘ፡፡ በሊባኖስ በማቅራት ህፃናትን ማሳደን ቀጠለ፡፡ ቀስ እያለ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪች አፈራ፡፡ ከአገር ከወጣ በኋላ ከየሁዳዎች ጋር በሚስጢር ይገናኝ ጀመር። ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦለት እ.አ.አ በ1982 የሊባኖስ የርስ በርሱ ጦርነት ጊዜ ድምፁን ሀይሉን አጠናከረ፡፡ ከዚያ በ1980ዎች እስራኤል ሊባኖስ ስትወርና ስታጠቃ የሙስሊሞች ጀመዓ ስትወጋ አህባሾችን ግን ተወቻቸው፡፡ ምክንያቱም የርሷ ወዳጅ ናቸውና ነው፡፡ በ1990 አህባሾች በእስራኤል ተረድተው ወደ ፖለቲካ ገቡ፡፡ በ1992 የሊባኖስ ጥቂት ወንበር አሸንፈው ፓርላማ ገቡ፡፡ ቀስ በቀስ የራሳቸውን ሚሊሻ ጦር መለመሉ፡፡ ሙስሊሙን ማበጣበጡን ገፍተው ቀጠሉ፡፡ ከነርሱ ውጭ ያለውን ሁሉ ‹‹ካፊር›› እያሉ መፈረጁ ተያያዙት፡፡ ለመንግስትና ለእስራኤል መረጃ እየሰጡ ሙስሊሙን ማስመታት ጀመሩ፡፡ ራሳቸውን በውሸት ‹‹የሻፊዒ መዝሀብ እንከተላለን›› እያሉ ያስወራሉ፡፡ አህለል ሱንና ነው። አሻዓሪና ማቶረዲ ነን ይላሉ፡፡ ሱፊያም ነን ይላሉ። ሆኖም የሶፊያ ዓሊሞች በሊባኖስ በሌሎች ሀገራትም መጀመሪያ እውነት ሱፊያ ናቸው ብለው ተሸደውደው ነበር። ሆኖም በሗላ በዝርዝር ሲያውቋቸው አጋልጠው ምላሽ ጻፉባቸው። ሰዉም እንዲያውቃቸውን እና አስጠነቀቁ።እውነታው ግን እነርሱ የእስራኤል ቀኝ እጅ ናቸው፡፡ ቀሰ በቀስ አል-ሀበሺ የሱንና መንገድ እየበከለ ሺዓ፣ ሪፋኢ፣ ሙርጂአ፣ተክፊር፣ሱፊ፣አል-ጀበሪ፣ ቃዲሪያና ጃህሚያ ወዘተ መንገዶችን ቀይጦ(ስፕሪስሪስ) አድርጎ የራሱን አዲስ መንገድ ፈጠረ፡፡ የዓለም ሙስሊሞችን ማክፈር ያዘ፡፡ አብደላ አል-ሐረሪ ‹‹ሳዑዲ እንዴት ከፈረች?›› ብሎ ሁሉ መጽሀፍ ጽፏል፡፡ (ሶ.አ.ወ) አገር መካና መዲና የካፊር አገር ብሎ ጽፏል፡፡ ይህ ብቻ የየሁዳ መሳሪያ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ አቋማቸው ምንድነው? ቀጥሎ ጥቂቶችን ብቻ እናያለን፡- 1. ከካፊር ጋር ቁማር መጫወት፣ የካፊርን (ክርስቲያን) መስረቅና ማጭበርበር ይቻላል ብሎ ያስተምራል።ዋናው እንዳይነቃ በድብቅ ማድረግና ዋናው መጠንቀቅ ነው ብሎ ያስተምራል፡፡ (መጽሐፉ ሰሪህ አል-በያን፣ገጽ 133) 2. ሰሀቦችን ይሳደባል፡፡ አንዳንዶቹን ሰሀቦች ካፊር ናቸው የጀሀነም ናቸው ብሎ ጽፏል፡፡ ለምሳሌ ታላቁን የነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ሆሃባ ሙአዊያ ኢብኑ አቢሱፍያን ካፊር የጀሀነም ሲል ገልጿል፡፡ የነብያችን (ሶ.ዐ.ወ) ባለቤት አዒሻን ተሳድቧል፡፡ 3. በነጃሳ መስገድ ይፈቀዳል ይላል፡፡(መጽሐፉ ቡግየቱ 4. ዘካ የለም ይላል፡፡ ዘካ ከእስልምና ማዕዘናት አንዱ ነው፡፡ አህባሾች ግን ሰው ዘካ እንዳያወጣ ከወረቀቱ ብር(ኖት) ላይ ዘካ የለበትም ይላሉ፡፡ ይህ ማለት በባንክም ይሁን በቤትዎ ቢሊዮን ብር እንኳ ካለዎ ዘካ አይስጡ ብሎ 5. ሪባ (ወለድ) መውሰድን ያበረታታሉ፡፡ ባንክ ገንዝ አስቀምጠው ባንኩ የካፊሮች(ወይም ስራ አስኪያጁ ካፊር(ክርስቲያን) ከሆነ ጠላታችን ስለሆኑ ወለዱን መውሰድ ይቻላል ብለው ያስተምራሉ። 6. ሴቶቻቸው ሻሽ ብቻ አድርገው ሱሪ ማድረግ ይችላሉ ይላሉ። ጂንስና ፋሽንንም ያበረታታሉ፡፡ 7. በሊባኖስ አገር የሙዚቃ ባንድ አላቸው ይህ ባንዳቸው ‹‹›› ይባላል፡፡ ዓመታዊ የሙዚቃ ድግስ ያደርጋሉ:: በዛ ላይ ሴቶችና ወንዶች በጋራ 8. የአጅነቢ ሴትን ፎቶ፣ ቪዲዮ አልያም በመስታወት ውስጥ ራቁቷን እንኳ ብትሆን በስሜትም ቢሆን ማየት ይቻላል:: ከቁርአንና ሱና ተቃራኒ ሆነው የተከለከለው በዓይን በቀጥታ ማየት ብቻ ነው ብለው ያስተምራሉ፡፡ ‹‹ሪፋዒ›› የተሰኘ ጦሪቃን ያስፋፋሉ:: በኢትዮጵያ ጀምረዋል ይህ ጦሪቃ ከሺዓ ጋር የሚያመሳስለው ብዙ እምነት አለው፡፡ የኢትዮጵያ ሙስሊም ግን ሱኒ ነው፡፡ 10. እምነት በልብ ነው ባይሰግዱም ኢባዳ ባይሰራም አንዴ አመንኩ ማለት በቂ ነው ብለው ያስተምራሉ:: (መጽሀፍ አ-ደሊል አልቀዊም፣ ገጽ 7) 11. ተከታዮቻቸው በአሜሪካና ካናዳ የቂብላ አቅጣጫ ካልተቀየረ ብለው ረብሻ ፈጥረዋል፡፡ በመጨረሻም ከመስጊድ ሲባረሩ የራሳቸው መስጊድ በተለየ ቂብላ ላይ ሰሩ። አሁን ከሙስሊሙ በተለየ ቂብላ ነው መስጊዳቸው፡፡ 12. ድግምትን አይቃወሙም። ራሳቸውም ይፈፅማሉ፡፡ ለሲህር የሚጠቀሙበት ‹‹ሁቡብ አል-አሀብ›› ብለው የሚጠሩት ነገር አላቸው፡፡ 13. ቁርኣን የጂብሪል ቃል እንጂ የአላህ ቃል አይደለም ብለዋል። የአላህ ቃል አይፃፍም ይላሉ፡፡ 14. የሚገርመው ይህን ሁሉ የጥመት መንገድ እየተከተሉ ሱፊያ ነን፣ ሻፊዒ መዝሀብ ተከታይ ነን ይላሉ፡፡ 15. ከነርሱ እምነት ዉጭ ያሉ ዓሊሞችን እንደያስተምሩ ሆን ብለው ያስተጓጉላሉ፣ ይደበድባሉ፣ ያሳስራሉ፣ ያውካሉ፣ በአንድ ወቅት በሊባኖስ ይህ ችግር በስፋት ፈጥረው ‹‹ሸሪዓ መጽሔት›› በቁጥር 574 እትሙ ‹‹ሊባኖስ ጦርነት በመስጂዱ ውስጥ›› በሚል ርዕስ ጽሑፍ አስነበቦ ነበር፡፡ 16. ዓመታዊ የሴቶቻቸው የሂጃብ ፋሺን ሾው አላቸው፡፡ በዚያ ላይ ሂጃብ ከሚለብሱት ሴቶች ጋር በጋራ ይጨፍራሉ፡፡ ስውር አጀንዳዎች የአህባሽ ጉዳይ በኢትየጲያችን አነጋጋሪ አጀንዳ ከሆነ ሰንበትበት ብሏል ። በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃንም ስለዚህ ጀመዓ ብዙ ብዙ ተብሏል ። አነጋጋሪነቱም ያለምክኒያት አይደለም ። ከአስተሣሠብ እስከ ሥነምግባር ፤ ከእምነት እስከ ማህበራዊ ኑሮ ግንኙነት በእጅጉ የወረደ አመለካከትና አስተምህሮ ያለው አህባሽ በህዝቡ መካከል ማረፊያ ቢያገኝ ሊያደርሰው የሚችለው ጥፋት ከፍተኛ ይሆናል የሚለው የብዙዎች ስጋት ነው ። አህባሽ እንከኖቹ ብዙ ናቸው ። ትኩረቱና መሠረቱ ከተውሂድ ይልቅ ወደ ሽርክ ( በአላህ ማጋራት ) እና ወደ ሸርክ የሚያደርሱ መንገዶች ያዘነበለ ነው ፤ ጥርት ካለው የቁርኣንና የሀዲስ ትምህርት በበለጠ ወደ ፍልስፍና እና መሠረት አልባ ቂሣዎች (ትረካዎች) ያደላል ፤ ከፍቅርና ከመደጋገፍ ይልቅ በማህበረሰቡ መካከል ጥላቻን ፣ ምቀኝነትንና ውጥረትን ያራምዳል ፤ ከሱ ውጭ ያሉትን ሁሉ የማክፈር (ከእስልምና የማስወጣት) ፖሊሲውና ‘ ለመቻቻል ወኔ የከዳው ስብስብ ’ መሆኑ ሲታሰብ ደግሞ የአህባሽ ጀመዓን አደገኛነትና የአስተሣሣቡን መርዛማነት አጉልቶ ያሣያል ። በመሆኑም ይህ ጉዳይ እጅግ አሣሣቢ ነው ስላመንበት በዛሬው የአጀንዳ አምዳችን የተለያዩ መረጃዎችን በማገላበጥ ስለዚህ ጀመዓ ምንነት በሚከተለው መልኩ አጠናቅረናልና ተከተሉን ። የኋላ ታሪክ ዛሬ የምናነሣት የዐብደላህ አልሀረሪ (አልሀበሺ) ጀመዓ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው ያላት ። በምድር ላይ የሃምሣ አመት እድሜ እንኳን አልሞላትም ። የተመረሠተችው በሊባኖስ ሲሆን መሥራቹም የኛው ሰው ናቸው ። ሙሉ ሥማቸው ዐብደላህ ኢብኑ ሙሀመድ አልሀረሪ (አልሀበሺ) ይባላል ። በሀረር ከተማ ከአደሬ ብሄረሰብ ነው የተወለዱት ። አልሀበሺ የዘር ሀረጋቸው ከቁረይሽ ጎሣዎች አንዷ ከሆነችው ከበኒ ሸይባህ እንደሚመዘዝ ይነገራል ። ተከታዮቻቸው እሣቸው ይዘው የመጡትን ዐቂዳ / እምነት / ታላቅነት ለማመልከት የዘራቸውን ታላቅነት ይጠቅሣሉ ። በሌላ በኩል ግን ይህንን ጉዳይ የማይጋሩ በርካቶች ናቸው ። ናቸው ቢባል እንኳ ከተከበረ ዘር መሆንንና መልካምነትን የሚያገናኛቸው ነገር አለመኖሩን በርካታ ምሣሌዎችን በመጥቀስ ማስረዳት ይቻላል ። የዚህ ኡመት ፈርዖውን በመባል የሚታወቀውና በነቢያችን ሰለላሁ ዐለይህ ወሠለም ዘመን ዋና የኢስላም ጠላት የነበረው አቡጀህል ከቁረይሽ ጎሣ መሆኑን ልብ ይሏል ። በቁርኣን ከባድ እርግማን የወረደበት አቡለሀብም ቢሆን የነቢያችን ሰላላሁ ዐለይህ ወሠለም አጎት የነበረ ስለመሆኑ አንዘንጋ ። ዐብደላህ አልሀበሺ በልጅነታቸው በሀረር ገጠራማ አካባቢዎች የዐረብኛ ቋንቋና የሻፊዒይን ፍቅሂ ተምረዋል ። ሌሎች ሃይማኖታዊ ትምህርቶችንም ከተለያዩ መሻኢኮች ቀስመዋል የማይጨበጠው አቋማቸው ዐብደላህ አልሀበሺ ከወጣትነት እስከ ሽምግልና በዘለቀው የህይወት ዘመናቸው አንድ አይነት አቋም ይዘው ሲጓዙ አልተስተዋሉም ። ለበርካታ ጊዜያት በሱፊያ አመለካከቶችና መንገዶች ውስጥ ሲወጡና ሲገቡ ቆይተዋል ። ሀረር እያሉ ቃዲሪያ የሚባል ጠሪቃ መንገድ ተከታይ ነበሩ ። ወደ ጅማ ሲሄዱ ደግሞ ቅልጥ ያሉ ቲጃኒ እንደነበሩ ይነገራል ። ከዚህም በተጨማሪ በየጊዜው የሚፈፅሟቸው ድርጊቶች ለብዙዎች ግራ የሚያጋቡ ነበሩ ። ሼክ አህመድ አድደውለዊ ስለሣቸው ያዩትን ሲናገሩ ‘ይህ ሰው በአንድ ወቅት ጅማ ሄዶ ሲመለስ በቲጃኒ ጠሪቃ ላይ ተመስርቶ አላህን የሚያወሣበት መስገጃው ላይ ተቀምጦ በዙሪያው ስድስት ሲጃዳዎች አንጥፎ አየሁት ። ስለዚህ ሁኔታ ተጠይቆም አንደኛዋ ሲጃዳ ለነቢዩ ናት ፤ ሁለተኛዋ ደግሞ ለኢማም አህመድ አትቲጃኒ ስትሆን የቀሩት አራቱ ደግሞ አውራዱ (አላህን ማውሣቱ) ላይ ይገኛሉ ተብለው ለሚጠበቁት ለአራቱ ኸሊፋዎች እንደሆኑ ተናግሯል ። አልሀበሺ ሀረር ተመልሰው ጥቂት እንደቆዩ ግን ይህን ጠሪቃ ተው ። ቲጃኒዎችንም ማክፈር ጀመሩ ። ወደ ሊባኖስ ሲሻገሩ ደግሞ የሪፋዒ ጠሪቃ ተከታይ እንደሆኑና ከሌሎች የሚሻለውም ይሀው መንገድ እንደሆነ ያስተምሩ ነበር ። በሊባኖስ ቆይታቸው ጥመትና አልባሌ ነገሮች ከሞላባቸው ከተለያዩ የፍልስፍና መንገዶች የተለያዩ አመለካከቶች መቅዳትና መገልበጥ ያዙ ። ውርሣቸውም ይህን ይመስላል – በኢማን / እምነት/ ጉዳይ ላይ ከኸዋርጆች (አፈንጋጮች) ጋር በማበር ሙስሊሞችን ማክፈር ጀመሩ ። ጀህሚያ እና ሙዕተዚላ ከሚባሉ ጀመዓዎች ደግሞ ደግሞ የአላህን መልካም ሥሞችና ባህሪዎች በመቁረጥ አሊያም በመቀጠል ለቁርኣን አንቀፆች ያልሆነ ትርጉም መስጠትን ወረሡ ። ከሺኣዎች ደግሞ እነ ሙዓዊያን እና ዐምር ኢብኑልዓስን ጨምሮ ታላላቅ ሰሃቦችን የመስደብ ትልቅ ወንጀል ተጋሩ ። ከአህለልኪታቦች ደግሞ በተወሱል ሰበብ መቃብር ለመቃብር አማላጅ ፍለጋ መንከራተትን በትምህርታቸው ውስጥ አካተቱ ። ሸኹ እንዲህ የተሠባጠረ አካሄድ የሚከተሉ ከመሆናቸው የተነሣ የሣቸው መንገድ ይህ ነው ብሎ በግልፅ ለማስቀመጥ ይቸግራል ። ሸኽ ዐብደላህ አልሀበሺ ከትንሽነታቸው ጀምሮ በባህሪያቸው አስቸጋሪ ሰው እንደነበሩ ይነገርላቸዋል ። ትክክል ነኝ ብለው ባመኑበት ነገር ከሸኾቻቸውና አስተማሪዎቻቸው ጋር ክርክር በመውደድ ይታወቃሉ ። በዚህም የተነሣ በየጊዜው ከሚያስተምሩዋቸው ሸኾች ጋር ውዝግብ ውስጥ ይገቡ ነበር ። ሰላትን ማንንም ተከትሎ ለመስገድ ፈቃደኛ አይደሉም ። ከሰዎች ጋር ላለመስገድ ሲልም ሰላታቸውን ያዘገዩ ነበር ። ከዚህም በላይ ሰዎች በሰላትና በቂርኣት በጥንቃቄ እንዲጨናነቁ ያስገድዳሉ ። የገዛ ሸኻቸውን ጭምር ተከትለው የማይሰግዱ ሲሆን ክስተቱም አንድን ሙስሊም ለማነወርና ለማክፈር ዳርዳርታውን የጀመሩበት ወቅት ነበር ። ላለመስገድ እንደምክኒያትነት ያቀርቡ የነበረውም ኢማማቸው በዐረቢኛ የፊደል አወጣጥ (መኻሪጀልሁሩፍ ) ላይ ችግር አለባቸው የሚል ነበር ። በወቅቱ ከተማሪያቸው ይህን ያስተዋሉት ሸህም ‘ ይህ ሰው ወደፊት የፊትና ሰው ( ሰዎች በሱ የተነሣ የሚወዛገቡበት ) ነው የሚሆነው ።’ እስከማለት ደርሰዋል ። ዘግይቶም ቢሆን የሸኹ ትንበያ የሠመረ ይመስላል ። ዛሬ ዓለማችን እሣቸው ባመጡትና ከአራቱም መዝሀብ ውጭ በሆነው አዲስ አመለካከት ችግር ውስጥ የገባች ስትሆን በዋናነት ደግሞ ያደጉባት ሀገር ሊባኖስ ትልቅ ፈተና ውስጥ ናት ። ሸሁ የዛሬ ሁለት አመት አካባቢ ይህችን ዓለም በሞት ቢሰናበቱም የለኮሱት ፊትና ግን ዛሬም ከሀገር ሀገር እየዘለለ ነው ። ሸኹና ተከታዮቻቸው ብዙ ክርስቲያኖች ሺዓዎችና የተለያዩ አልባሌ እምነት ተከታዮች በሚገኙባት በዚህች ሀገር እግራቸውን ሊያቆሙ የቻሉት ለሱና ሰዎች ባላቸው ጥላቻ የተነሣ ከምእራባውያን ፣ ከሺዓዎችም ሆነ ከሌሎች የኢስላም ጠላቶች ከፍተኛ ድጋፍ ስለሚደረግላቸው ነው ይባላል ። ማክፈር … ትልቁ መፈክር ዐብደላህ አልሀበሺ ለማንኛውም ‘ ይቃወመኛል አሊያም አመለካከቴን አይጋራም ’ ብለው ባመኑት ሰው ላይ ረጅም ምላሣቸውን ለመልቀቅ ወደኋላ አይሉም ። እሣቸውም ሆኑ ተከታዮቻቸው አንድን ሰው ለማክፈር እጅግ ሲበዛ ችኩሎች ናቸው ። በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ ሱፊዮች እስከዛሬ ድረስ ሰውን ሲያከፍሩ አልተስተዋለም ። አሁን የአህባሽ አመለካከት ከመጣ ወዲህ ግን እነሱም ወደማክፈር ገብተዋል ። ዐብደላህ አልሀበሺ ‘ አትተዓዉን ዐላ ነህይ ወልሙንከር ’ ( በመጥፎ ነገር ላይ መረዳዳት ) በሚለው ኪታባቸው ላይ እንደፃፉትም ከትላልቅ ዓሊሞች ውስጥ የሚያስቀሩት ጥቂቶችን ብቻ ነው ። ኪታባቸው ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ተህዚር ! ተህዚር… ! ተጠንቀቁ ተጠንቀቁ .. ! በሚል ማስፈራሪያ የተሞላ ነው ። ካለፉትም ይሁን በህይወት ካሉት ዑለማኦች ፣ ዳዒዎችና የኢስላም ተንታኞች ውስጥ ሰዎች ሊሸሿቸው የሚገባቸውን አንድ በአንድ ይዘረዝራሉ ። ዓሊሞቹ የተናገሯቸውን ቃላት በመምዘዝም ‘ እገሌ በአንድ ወቅት እንዲህ ብሏል እገሌም እንዲህ ብሏል … እያሉ እራሣቸውን የዚህች ዓለም ብቸኛ ነቢይ አድርገው የማስቀመጥ ያህል ይፈርዳሉ ። ሲሻው ይሣደባሉ ፤ ካልሆነም ይራገማሉ ፤ ባስ ካለም ያከፍራሉ ። ስድባቸውን የሚጀምሩት ከታላቁ ሰሃባ ከሙዓዊያ ኢብኑ አቢሱፍያን ነው ። ስለ ዐምር ኢብኑል ዓስና ስለ እናታችን ዓዒሻም የሚሉት አላቸው ። ይህም ያለ አንዳች ኤዲቲንግ (ማስተካከያ) ከሺዓዎች የገለበጡት ቀጥተኛ የሆነ አቋማቸው እንደሆነ ብዙዎች ይስማሙበታል ። ከሰለፍ ዑለማኦች እነ ዳርሚይንና ኢብኑ ኹዘይማህን ወርፈዋቸዋል ። የተውሂድ አቀንቃኙ ኢብኑ ተይሚያህ ዋና ጠላታቸው ሲሆኑ ‘ ካፍር (ከሀዲ) ፤ ሙርተድ (ከኢስላም ወደ ክህደት የተመለሠ )’ በማለት ይገልጿቸዋል ። በተገኙበት ሁሉ ኪታቦቻቸው እንዲቃጠሉ አዘዋል ። የኢብኑ ተይሚያን ተማሪ ኢማም ኢብኑ አልቀይም አልጀውዚን እና ታላቁን ሙፈሲር (የቁርኣን ተንታኝ) ኢብኑ ከሲርንም አክፍረዋል ። ኢማም ዘሀቢን ኸቢስ (መጥፎ) ሲል ይዘልፏቸዋል ። ታላቁ የሀዲስ ሰው ሸይኸ አል አልባኒ ፣ የሳዑዲ ሙፍቲ የነበሩት ሸኽ ኢብኑ ባዝና ታላቁ ዓሊም ኢብኑ ዑሰይሚን እንዲሁም የወቅቱ የዓለም ሙስሊም ዑለማኦች ዋና ፀሃፊ የሆኑት ሸኽ ዶ/ር ዩሱፍ አል ቀርዳዊም በካፍርነት ከተፈረጁ መካከል ናቸው ። ሰዎች እንዲጠነቀቋቸው ከፃፉባቸው ሌሎች ሰዎች መካከል ታዋቂው ዳዒ ዶክተር ዐምር ካሊድ ፣ ፈይሰል መውለዊ ፣ ፈትሂ የኩን የመሣሠሉት ሲገኙ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው ምሁራን ይገኙባቸዋል ። የሱፊያው መሪ ሸኽ ሙሀመድ ሰዒድ አልቡጢ ውግዘቱ ተርፎአቸዋል ። ዶክተር ዛኪር ናይክና የፒስ ቲቪ ባልደረቦቹም በክህደት ከተወነጀሉት ውስጥ ናቸው ። አልሀበሺ ታላቁን የፍቅሂ ሰው ሰይድ ሳቢቅን መጁሲ /እሣት አምላኪ/ ሲል ይገልጿቸዋል ። ሰይድ ቁጥብን ከመራገም አልፈው እሱንና ተከታዮቹን በስቅላት በመግደሉ ለጀማል አብዱናስር ታላቅ አድናቆት አላቸው ። የስደቱ ምክኒያት ‘ አልሀበሺ አክጣኡሁ ወሹዙዙሁ /አልሀበሺ ስህተቶቹና ድልጠቶቹ / ’ የምትለውና በዐብዱረህማን አድ ድመሽቂያህ የተዘጋጀችው ትንሽ መፅሃፍ አንደምታትተው ከሆነ አልሀበሺ ከትውልድ ሀገራቸው ኢትዮጰያ ሸሽተው የወጡት በሀረር ሙስሊሞች መካከል ውዝግብ በማስነሣታቸው ነበር ። በወቅቱ የሀረር ገዠ ከነበሩት የሃይለሥላሴ አማች አንዳርጌ ጋር በመተባበር በሀረር የሚገኙ የቁርኣን ሂፍዝ ማዕከላትን ማስዘጋታቸውም ተነግሯል ። ጊዜውም በ1940 ዓ.ል ነበር ። በወቅቱ ወደ ተውሂድ ጥሪ የሚያደርጉ ዑለማኦች በአልሀበሺ ውንጀላ ከፍተኛ መንገላታታ የደረሠባቸው ሲሆን በርካቶች ወደ ግብፅና ሳዑዲ ዐረቢያ በመሰደድ ህይወታቸውን ሲያተርፉ የተቀሩት ደግሞ እንዲታሰሩና በጨቋኙ መንግስት እንዲዋረዱ ተደርጓል ። ሰዎችንም የሚያሣስሩበት ዋና ምክኒያትም ዛሬም ተከታዮቹ እንደሚወነጅሉት ‘ ወሃቢያ ነው ’ በማለት ነበር ። ሆኖም ግን ኋላ ላይ ተነቅቶባቸው እራሣቸው የለኮሱት እሣት ሊፈጃቸው እንደሆነ ሲረዱ የታሠሩና የተገደሉ ሰዎች ቤተሰቦችን በቀል በመፍራት ከሀጃጆች ጋር በመሆን በሶማሊያ በኩል አድርገው ሣዑዲ ሊገቡ ችለዋል ። ሸሁ ቀጥለውም ወደ ሀገረ ኢስራኤል ኋላም ወደ ሶሪያ በመሻገር በመጨረሻም ሊባኖስን ማረፊያቸው አደረጉ ። በሊባኖስ ቆይታቸውም ዓሊም መስለው በመቅረባቸው ብዙዎች በሣቸው ተታለዋል ። መጀመሪያ አካባቢ የተለያዩ አንዳንድ መፅሃፎችን በማረም ወደ ማህበረሰቡ ውስጥ ገቡ ። ቀጥሎም ለየት ያለ አዲስ አመለካከታቸውን ማስተዋወቅ ያዙ ። ተውሂድ ይዞ የነበረውን ህዝብም ወደኋላ አንሸራተቱ ፤ በፍቅር ይኖር በነበረው ማህበረሰብ መካከል ፍትናን በማሠራጨት ጥላቻን በመንዛታቸውም አንድነታቸው ተበተነ ። ሀይላቸውም ተዳከመ ። ቁጥራቸው ስንት ይሆን በዓለም ላይ የአህባሽ ተከታዮች ቁጥር ከ250 ሺህ እንደማይበልጥ ይገመታል ። የዓለም ሙስሊሞች ቁጥር ወደ ሁለት ቢሊዮን የተጠጋ ሲሆን በነሱ እይታ ከነሱ ውጭ የሆነው ሙስሊም ሁሉ ካፍር በአላህ ያላመነ ከሀዲ ነው ማለት ነው ። እስልምናቸውም ትክክል ስላልሆነ እንደገና ሸሃዳ እንድይዙ ይመክራሉ ። አህባሾች በእምነት ጉዳይ ከሺዓዎች የሚጋሯቸው በርካታ አመለካከት ያሏቸው ሲሆን ህዝቡላህን ከመሣሠሉ በኢራን ከሚደገፍ ፓርቲም ትልቅ ድጋፍ ያገኛሉ ። የሱና ጀመዓዎችን ለመቃረን ሲሉ ብቻ ከጥመትና ከኩራፋት ጀመዓዎች ጋር ፍቅራቸው እጅግ የጠነከረ ነው ። መሪዎቻቸውም ሆኑ ተከታዮቻቸው በስሜት የሚነዱ ፣ ለጥቅም ያደሩ ፣ ሥነምግባርና ዘመናዊ እውቀት የጎደላቸው ናቸው ። የሚያንቀሳቅሷቸው ድብቅ የሆኑ የሙስሊሙ ጠላት እጆች እንዳሉባቸው የብዙዎች ግምት ነው ። ሱፍያ ፣ አል አሽዐሪይ ፣ ኢማሙ ሻፊዒይና አህባሽ አህባሾች ‘ ሱፊዮች ነን የኢማም አሽ ሻፍዒና የአሽዓሪይ መዝሀብ ተከታዮች ነን ቢሉም አመለካከታቸው በብዙ መልኩ ከነሱ የተለዩ ነው ። ሱፊዮች ሙስሊሙን ሲያከፍሩ በታሪክ አልታየም ። ‘ ቁርኣን የአላህ ንግግር አይደለም ’ አይሉም ። ከመካና መዲና ኢማሞች ኋላ እንዳይሰገድም ብይን አያስተላልፉም ። ከካፍሮች (ከሀዲያን ) ጋር አብረውም ሙስሊሙን አይበድሉም ። ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይህ ወሠለም ሰሃቦች አንዱን እንኳ አይሰድቡም ። እነሱ ‘ እንከተላቸዋለን ’ የሚሏቸው ኢማሙ ሻፊዒይም ከአካሄዳቸው ፍፁም የጠሩ ናቸው ። ኢማሙ በቀደምት ሰሃቦች መካከል ስለተፈጠረው ልዩነት ደፍረውና አፋቸውና ሞልተው ለመናገር አላህን ይፈራሉ ፤ ኢማሙ ሻፊዒይ ‘ ያች በርግጥም ትልቅ ፈተና ናት ። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ከሷ እጃችንን አጥርቶልናል ። ታዲያ ምላሣችንን ማጥራት አይጠበቅብንም ’ ሲሉ በቀደምት ሰሃቦች ውስጥ የተከሰተውን ነገር ከመተንተን ይቆጠባሉ ። ኢማሙ ሻፊዒይ ሪባን /ወለድን / ም ሆነ ሰው ማጭበርበርን አይፈቅዱም ፣ ዘካን ከእስልምና አላስወጡም ፣ ለአላህ ባህሪያት ያለትርጉማቸው ትርጉም አልሠጡም ። ዋና ዋና አመለካከት ቁርኣን የመልአኩ ጅብሪል እንጂ የአላህ ንግግር አይደለም ይላሉ ። ቁርኣን የአላህ ንግግር ስለመሆኑ የሙስሊሞች ሁሉ እምነት ነው ። በነሱ ጥላ ሥር ያልተጠለለውን ማንኛውንም ሙስሊም ሁሉ ካፊር ነው ይላሉ ። እውነተኛ ሙስሊም ማለት የነሱን አካሄድ የተከተለ አመለካከታቸውን የተጋራ ነው ። ከሀዲ ማለትም ከነሱ መንገድ የወጣ ነው ። አመለካከታቸውን ያልተቀበለውን ሙስሊም ስለሚያከፍሩ ተከትለውት አይሰግዱም ። ማክፈር በነሱ ዘንድ እጅግ ቀላል ነገር ነው ። አንድ ካፊር ያልሆነውን ሙስሊም ወንድሙን ካፊር ያለ ሰው ንግግሩ ወደሱ ተመላሽ እንደምትሆን ነበያችን አስተምረውናል ። ‘ የሀረም ( የመካና መዲና ) ኢማሞችን ተከትሎ መስገድ ሀራም ነው’ ይላሉ ። ለሀጅ የሚሄድ ሰው እነሱን ተከትሎ መስገድ የለበትም ቢሰግድም ሰላቱ ትክክል አይደለም ብለው ያምናሉ ። ኢማማቸው አልሀበሺ ይህንን ያደረጉ እንደሆነ ደግመው እንዲሰግዱ ያዛቸዋል ። ለምን ቢባል በነሱ አመለካከት የሀረም ኢማሞች ከሀዲዎች ናቸውና ነው ። በዚህ አይነት በርካቶችን የሀረም ተስግዶ የሚገኘውን ከፍተኛ አጅር አሣጥተዋል ። የአላህን መልካም ባህሪያትና ሥሞች መካዳቸው ሌላው ነው ። አላህ ስለራሱ የተናገራቸውን ነገሮች ትርጉሙን በማጣመም ይተረጉማሉ ። ሲሻቸው ይቀንሣሉ ባሰኛቸውም ጊዜ ይጨምራሉ ። ቀደምት ሰለፎችና በተዋረድ እነሱን የሚከተሉ ሙስሊሞች ግን አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ስለራሱ በተናገረው መልኩ ያምናሉ ። እርሱ ለራሱ ያፀናውንም ባህሪ በሚገባው መልኩ ያፀናሉ ። ሀጃቸውን ለማስፈፀም መቃብር አካባቢ ይመላለሣሉ ። ሙታኖች ሰዎችን ይረዳሉ ፣ ያግዛሉ ፣ ከጭንቅም ያላቅቃሉ የሚል እምነት አላቸው ። ከዚህም የተነሣ የአላህን በር ችላ በማለት ውሎአቸውን ደሪህ ካባቢ ያደርጋሉ ። የአላህ ወሊዮች ከመቃብር ወጥተው የሰውን ጉዳይ ፈፅመው የመመለስ ብቃት አላቸው የሚል እምነት አላቸው ። ከአላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሥምም በላይ የወሊዮቹ ሥም ሲጠራ ይበረግጋሉ ። በዲን ውስጥ አዲስ ፈጠራን /ቢድዓን/ ያበረታታሉ ። ‘ መልካም ነገር እስከሆነ ድረስ ቢጨመርበት ግድ የለውም ’ በማለት ከሃይማኖት አስተምህሮ ውጭ የሆኑ ነገሮችን ይጨማምራሉ ። በዚህም የተነሣ አምልኮአዊ ተግባራቶቻቸው ከነቢዩ ሱናዎች ይልቅ በሌሎች መጤ ፈጠራዎች የተጥለቀለቁ ናቸው ። ኢማን ማለት የውስጥ እምነት ነው በሥራ ባይገለፅም ችግር የለውም የሚል አቋም አላቸው ። በመሆኑም በሸሪዓ ህግጋት ለመሥራት የተሠላቹ ናቸው ። ለሀላል ሀራሙም ነገር ግድ የላቸውም ። ይህም በመሆኑ በምድር ላይ የአላህ ህግ ተግባራዊ እንዳይሆን የሚፈልጉ በእጅጉ ይደግፏቸዋል ። ትክክለኞቹ ሙስሊሞች ግን ኢማን ማለት በቀልብ ውስጥ የሰረፀና በተግባርም የሚረጋገጥ ጉዳይ እንደሆነ ያምናሉ ። ከአራተኛው ኸሊፋ ዐሊ ኢብኑ አቢጣሊብ ጋር በሀሣብ የተለያዩትን ሰሃቦችን እነ ሙዓዊያን እና ዐምር ኢብን አልዓስን ‘ ከአላህ ተእዛዝ የወጡ ናቸው ’ በማለት ይወርፏቸዋል ። ይህም የሺዓን አመለካከት የሚጋሩ መሆናቸውን አመላካች ነው ። በሊባኖስም ከሺዓዎች ጋር በመተባበር የሱና ጀመዓዎችን ሲያሣድዱ ይስተዋላል ። አልሀበሺና ተከታዮቻቸው ከአመለካከታቸው ውጭ የሆኑትን ሙስሊሞች በመጥላት በመመቅኘትና እንዲሁም ሰሃቦች በመዳፈርና በመሣደብ ይታወቃሉ ። ይህም በመሆኑ በሊባኖስ ውስጥ ተስማምቶ ለመኖር የማያመች ወጣ ያለ የቁጣ ባህሪ ያለው ሰው ካጋጠመ የአል ሀበሺ ተከታይ እንደሆነ ይገመታል ። በሀገራችንም ውስጥ የምናየውም ሥራቸው ሰዎች ያላሉትን አሉ በማለት ትናንሹን ጉዳይ በማካበድ አንዳቸውን በሌሎች ላይ በማነሣሣት ነው ። ከአስገራሚ ፈትዋዎቻቸው በነጃሣ መስገድ ችግር የለውም ። ወለድ መብላት ይበቃል ። ሙስሊም ካልሆነ /ካፍር/ ጋር ቁማር ተጫውቶ መብላቱ ችግር የለም ። ችግር እስካልተፈራ ድረስ ። ሴትን ልጅ በተደጋጋሚ ማየቱ ነው እንጂ የሚከለከለው በመጀመሪያ እይታ ለረጅም ጊዜ ማየቱ ይበቃል ። ሴት ልጅ በየትኛውም ጊዜ ያለባሏ ፈቃድ ሽቶ ተቀብታና ተኳኩላ መውጣት ትችላለች ። ኢክቲላጥ /የሴቶችና ወንዶች ቅልቅል/ ችግር የለውም ። ለዚህም ሲባል ተከታዮቻቸው የሆኑ ወንድና ሴቶች ተቀላቅለው ይጨፍራሉ ። ሙስሊም ወዳልሆኑ ሀገሮች የሚሄድ ሰው ችግር ይገጥመኛል ብሎ የሚፈራ ከሆነ መስቀል ማንጠልጠል ይችላል ። ዘካ በወርቅና ብር እንጂ በወረቀት ገንዘብ ግዴታ አይሆንም ። ሆን ብሎ መዘግየትና መስነፍ ችግር የለውም ። ለምሣሌ ጁሙዓና ጀመዓ ላለመምጣት የፈለገ ሰው ነጭ ሽንኩርት መብላት ይችላል ። መኻሪጀልሁሩፍ /የዐረብኛ ቃላትን በትክክል ማንበብ ማይችሉ/ አሰጋጆችን ተከትሎ መስገድ አይበቃም ። ለሴት ልጅ ከላይ ሂጃብ እስከለበሠች ድረስ ከታች ጠባብ ጂንስ ብትለብስም ችግር የለውም ። በአንድ ወቅት በአህባሽ ብይን የተነሣ በአሜሪካና ካናዳ የሚገኙ ሙስሊሞች ከከዕባ አቅጣጫ 90 ድግሪ ያህል ዞረው ሰግደው ነበር ። ይህ ነው እንግዲህ ከእስልምና አስተምህሮ ወጣ ያለው ጥፋታቸውና አስቀያሚ አካሄዳቸው ። ልብ ያለው ልብ ይበል ። የአህባሽ አመለካከት ወደ አንድ ሀገር አይደርስም የሚከተሉት ነጥቦች ቢከተሉት እንጂ የሰዎች ለሰዎች ማህበራዊ ግንኙነት ይበላሻል ፣ የሙስሊሙ አንድነት አደጋ ውስጥ ይገባል ፣ ሽኩቻ ጥላቻና ውጥረት በመካከላቸው ይነግሣል ። ሙስሊሞች መሣቂያ መሣለቂያ ይሆናሉ ። በምእመናን መካከል መተሣብና መተዛዘን ይጠፋል ፣ አሉባልታና የውሸት ወሬ ይስፋፋል ። ከሱና ይልቅ ቢድዓ ቦታ ያገኛል ፣ ከቁርንና ሀዲስ በበለጠ መሠረተ ቢስ ታሪኮችና ትረካዎች /ቂሳዎች/ ይገናሉ ፣ ከታላቁ ነቢይ ሥም በላይ የወሊዮችና የሸሆች ሥሞች ይዘወተራሉ ። የአላህ የአንድነት ትምህርት ይሸረሸራል ሽርክና ወደ ሽርክ የሚያደርሱ መንገዶች ክፍት ይሆናሉ ፤ ተውሂድ በሽርክ ይተካል ፣ ንቃት በመሃይምነት ይተካል ፣ ብስለት በስሜታዊነት ፣ እዝነት በጭካኔ ፣ መተማመን በጥርጣሬ ፣ መቻቻል በብጥብጥ ይተካል ፣ ሚዛናዊነት በአክራሪነት ፣ አርቆ አስተዋይነት በችኩልነት ይተካል ። ከዚህም ባለፈ ሂጃብ በሱሪ ይተካል ፣ ቁርኣን በተለያዩ ሀድራዎችና ሙዚቃዎች ይተካል ። መናፍቃን ቦታ ያገኛሉ ፣ የሱና ሰዎች ይጠላሉ ፣ በኢስላም ሀግጋት ለመሥራት ደፋ ቀና የሚሉ ‘ አክራሪ ፣ አሸባሪ ’ ይባላሉ። አለማቀፍ ዓሊሞች ምን ይላሉ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ ከሱፊያም ሆነ ከሌላ ጀመዓ የሆኑ የአራቱ መዝሀብ አለማቀፍ እውቅና ያላቸው የዘመናችን ዓሊሞች ከዚህ ጀመዓ በማስጠንቀቅ ረገድ አንድ ሆነዋል ። አብዛኛዉ ዓሊሞቹ በሱፊያ መዝሀብ ላይ የሚገኙት የግብፁ ታላቁ ኢስላማዊ ተቋም አል አዝሀር እነሱን አላውቃቸውም ብሏል ። ጠማሞች ስለመሆናቸውም በተደጋጋሚ ገልጿል ። የአዝሀር ዩኒቨርስቲ ዳይሬክተር አህመድ ዑመር ሃሽም ‘ ይህ ጀመዓ በቁርኣንም ሆነ በሀዲስ የማይመራ ነው’ ብለውታል ። የሊባኖሱ ሙፍቲ ሸኽ ኻሊድ ሀሠን ከሀገሪቱ መንግስት ርእሰ ብሄር ረሺድ ከራሚ በአንድ ወቅት ዐብደላህ አልሀረሪ ከሀገር ወጥቶ በነበረበት ወቅት በሱና ሰዎች ላይ በሚያደርገው አደገኛ አካሄድ የተነሣ ወደ ሀገር ወስጥ እንዲገባ እንዳይፈቀድለት ጠይቀው የነበረ ሲሆን ለጥቂት ጊዜ ታግዶ ነገር ግን በተለያዩ ምእራባውያን ሀገራት ግፊት የተነሣ ሊገባ ችሏል ። የግብፁ ሙፍቲ ዶክተር ዐሊ ጁሙዓ ‘ ሥሙ ዐብዱላህ አልሀረሪ አልሀበሺ የሚባል ሰውየመሠረታት ይህች ጀመዓ ውስጣዊና ውጫዊ ገፅታም አላት ። ውጫዊ ገፅታዋን ስናይ በፍቅሂ የሻፊዒይ መዝሀብ ተከታይ ፣ በዐቂዳ ደግሞ አሽዐሪን ይመስላሉ ። ውስጣዊ ተልእኮዋ ግን ያላግባብ ሙስሊሞችን ማክፈር፣ ምእመናን ያላግባብ መወንጀልና በሀዝቦች መካከልል ውጥረትና ውዠንብር መፍጠር ነው ። ለዱኒያዊ ጥቅም ሲሉም ለኢስላም ጠላቶች ይሠራሉ ። ብለዋል ። በአውሮፓ የሙስሊም ኮሙኒቲ ሙፍቲ የሆኑት ዶክተር ፈይሰል መውለዊ ‘ የዐብደላህ አልሀረሪ ተከታዮች የሆኑት አህባሾች በጥቃቅን ነገሮች ሙስሊሙን ዑለማ የሚያከፍሩ ፤ አብዛኞቹ የሰለፍ ዑለማኦች የማይጋሯቸው የሆኑ የራሣቸው የሆነ አመለካከት /ዐቂዳ / ያላቸው ቡድኖች ናቸው ። ከሸኻቸው ውጭ ስለማይቀበሉ ከነሱ ጋር መነጋገር ጥቅም የለውም ። ከነሱ ጋር ላለመከራከር መስጅዳቸውን መሸሽ ይገባል ። ። እነሱ ከነሱ ውጭ የሆነውን ‘ ከሀዲ ነው ከነሱ በኋላ መስገድ አይበቃም ’ ብለው ቢያምኑም እኛ ግን ሙስሊሞች እንደሆኑና ከነሱ ጋርም ሆነ ተከትለዋቸው መስገዱ ይበቃል የሚል እምነት አለን ። የዓለም ሙስሊም ዑላማኦች ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶክተር ሼከ ዩሱፍ አልቀረዷዊም ‘ እነሱ የሚወክሉት የተወሰነ የማህበረሰብ ክፍል ብቻ ነው ። የሙስሊሙን የጋራ አቋም /ኢጅማዕ/ በመጣል ተለይተው የወጡ ናቸው ። የሙስሊም ዑላማኦችን አክፍረዋል ። አህባሾች በጥመት ውስጥም በጣም የሰጠሙ ናቸው ። ኢማም ዘሀቢን ፣ ኢብኑ ተይሚያን ፣ ኢብኑልቀይምን ፣ ኢማም ገዛሊን ፣ ኢብኑ ዐብዱልወሃብን ፣ ኢብኑ ባዝን ፣ ሰይድ ቁጥብን አንዱንም ሣይተው አክፍረዋል ። መሃይማን ብቻ ሣይሆኑ ድርብ ድርብርብ መሃይሞች ናቸው ። ሁኔታቸው አላህ እንዳለው ነው “ ሰዎች እንዳመኑት እመኑ በተባሉ ጊዜ ሞኞች እንዳመኑት እናምናለን እንዴ! ” ይላሉ ። የሶሪያው የሱፊያ ዓሊም የሆኑት ዶክተር ሙሀመድ ሰዒድ አልቡጢም ‘በበይሩት ዐብደላህ አልሀረሪ የሚባል ኢማም ያላቸው አህባሾች ወሃቢያን ተከትሎ መስገድ አይበቃም ፣ ኢብኑ ተይሚያ ካፊር ነው ይላሉ ። በመሠረቱ ወሃቢን ተከትሎ መስገድ ሀራም አይደለም ። ተከትሎ የሰገደም ሰላቱ ትክክል ናት ። አንድን ሙስሊም ማክፈር ይበቃም ሲሞት በኩፍር ላይ ሆኖ ስለመሞቱ ማረጋገጫ እስካልተገኘ ድረስ ። ስለሷ የምታነሱልኝ ጀመዓ ብዙ ሙስሊሞችን ያከፍራሉ ። ሙተወሊ ሸዕራዊን ቀርዷዊን እኔንም ያከፍራሉ ። ምናልባት ሙስሊሞች እነሱ ብቻ ሣይሆኑ አይቀሩም ።’ ብለዋል ። በሊባኖስ የሙስሊም ጀመዓዎች ተጠሪ የሆኑት ፈትሂ የኩን ‘ ዐብደላህ አልሀረሪም ሆነ ድርጅቶቹ ቀደምት ሰለፎችና የዚህ ኡመት ሚዛናዊ አመለካከት ያላቸው ምሁራን የጋራ አቋም የያዙበትን ነገር የሚቃረኑ ናቸው ።’ ብለዋል ። በኢስላማዊ ብይኖች የበላይ የሆነው የሰኡዲ ቋሚ የሆነው የእውቀትና የፈትዋ ኮሚቴ በአንድ ወቅት ‘ ዐብደላህ አልሀረሪ ኢስላምን አገለገለ ወይንስ አወደመው ? ’ ተብሎ በተጠየቀ ጊዜ እንዲህ በማለት መልስ ሰጥተዋል ። ‘ በሥም ተጠቃሹ እጅግ መጥፎ ሰው ነው ። በዘመኑ ካሉ የቢድዓና የጥመት መሪዎችም አንዱ ነው ። እሱም ሆነ ተከታዮቹ ሆንብሎ ነቢያችን ሰለላሁ ዐለይህ ወሠለም ሰሃቦችና ታቢዒዮች ያስተላለፉልን የሙስሊሞችን ቀደምት አመለካከት /ዐቂዳ / ለማጥፋት ቆርጦ የተነሣ ሰው ነው ። በፍቅሂ ዙሪያ የራሣቸው የሆነ አካሄድ አዘጋጅተዋል ከቁርኣንም ሆነ ከሱና ሰንሰለት በሌላቸው ለየት ባሉ እና በዘቀጡ አመለካከቶች የተሞሉ ናቸው ። በዐቂዳና በሥራ በኩል ከፍተኛ የሆነ ችግር አለባቸው ። የዚህን ኡማ ታላላቅ መሪዎች በማነወርም ይታወቃሉ ። ሁሉንም ሙስሊሞች ከነኚህ ጠማማ እና የተንሸራተተ ጀመዓ እንዲሁም ወጣ ካለ አመለካከታቸው እንዲጠነቀቁ እንመክራለን ።’ ብለዋል ። ታላቁ የሀዲስ ሰው ሼኽ ሙሀመድ ናስረዲን አል አልባኒም ‘ አህባሾች የዐብደላህ አልሀረሪ ተከታዮች ናቸው ። አመለካከታቸው በአጉል ፍልስፍና ላይ የተመሠረተ ሲሆን ቁርኣንና ሀዲስን በዐቅላቸው በመመራመር እንጂ በሰለፎች ግንዛቤ ላይ አይረዱም ። ተጠቃሽ ምንጮች
13860
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8B%B3%E1%88%8D
አዳል
የአዳል ሱልጣኔት ተብሎ ይታወቅ የነበረው ግዛት በመካከለኛው ዘመን (ከ1415 - 1577 ዓ.ም.) የነበረ በመጀመሪያዎቹ ከ1415–1559 መሪዎቹ የወላስማ ሱልጣኖች የአርጎባዎች እና የብዙ እስልምና ተከታይ ጎሳዎች ድብልቅ የነበረ ግዛት ነው። አንዳንድ ተመራማሪወች አብዛኛው አዳል የአፋር ጎሳዎች ተዋጾ ነበረበት ሲሉ አንዳንዶች ደግሞ ባብዛኛው ከዲር እና ዳሩድ የሶማሌ ነገዶች የተውጣጣ ነበር ይላሉ። የአዳልን ሱልጣኔት አብዛኛ ጎሳ ስብጥር ክርክር ይውደቅ እንጂ በርግጥም ሱልጥኔቱ የብዙ ጎሳዎች ስብስብ እንደነበር ግን ክርክር የለም። ስለ አዳል ሱልጣኔት በትንሹ (ከ1415- 1577 ዓ.ል.) በአብዱ እንድሪስ (ከሚሴ) አስራ ሁለተኛው የኢትዮጵያ ሰለሞናዊ ነጋሲ የነበረው ወጣቱ አጼ ዳዊት በ1413 ዓ.ል. በአጠገቡ በነበረው የኢፋት ሱልጣኔት ላይ ሀይለኛ ጥቃት ከፈተ። የሱልጣኔቱ ገዠ የነበረውን ሱልጣን ሰዓደዲንን በዜይላ ከተማ ከገደለው በኋላም ኢፋትን ከአጼው ግዛተ መንግስት ጋር ቀላቀለው። ሆኖም አጼ ዳዊት በቁጥጥር ስር ካዋለው የኢፋት ግዛት በሙሉ ሀይሉ ለመግዛት የቻለው ከአዋሽ ወንዝ በስተምዕራብ ያለውን ብቻ ነው። ከወንዙ በስተ-ምስራቅ ያለውና እስከ ዘይላ ድረስ የተንጣለለው ምድር ወዲያውኑ ነበር ከእጁ ያፈተለከው። አባታቸው በዘይላ ሲገደል በስደተኝነት ወደ የመን የሸሹት አስራ አንዱ የሰዓደዲን ልጆች በ1415 ዓ.ል. ከስደት ተመልሰው በምስራቃዊው የኢፋት ግዛት ላይ አዲስ ሱልጣኔት መሰረቱ። ዋና ከተማቸውን ከሀረር አጠገብ በነበረችውና “ደከር” በምትባለው መሬት ላይ ቆረቆሩ። ዳግማዊ ሰብረዲን የሚባለውን የሰዓደዲን ልጅ በወላስማው ወንበር ላይ ካስቀመጡ በኋላ ህልውናቸውን በይፋ አበሰሩ። ከእንግዲህ ወዲያም ለማንም እንደማይገብሩና ሀገራቸውንም ከጥቃት እንደሚከላከሉ በይፋ አወጁ። ለአዲሱ ሱልጣኔትም “አዳል” የሚል ስያሜ ሰጡ። የኢማም ኣህመድ ኢብን ኢብራሂም ኣል ጋዚ ዘመን ታዋቂው ገዥ ኢማም አህመድ ኢብኑ ኢብራሂም አል ጋዚ በሱልጣኔቱ ላይ ትልቅ ተጽእኖ ነበረው። ከ በለው ጎሳ የተወለደው አህመድ ግራኝ እንደ ማህፉዝ ባሉ ሌሎች የሙስሊም ገዥዎች ስር ብዙ ቦታዎችን ካገለገለ በኋላ በ1527 ወደ ስልጣን መጣ። ግራኝ በተለምዶ በኢትዮጵያ ታሪክ አብያተ ክርስቲያናትን በማፍረስ እና ለክርስቲያኖች የማይራራ ሰው ሆኖ ይገለጻል። ይህን ለመደገፍ አንዳንድ ማስረጃዎች ሊኖሩ ቢችሉም፣ አህመድ ግራኝ እስካሁን ድረስ በሀገሪቱ ላይ ተጽእኖ ያላቸውን በርካታ ስኬቶችን ኣስመዝግብዋል። እንደ መሪ፣ በክርስቲያን ግዛት ላይ ብዙ ዘመቻዎችን መርቷል፣ እና ብዙ ጦርነቶች ላይ ልብነ ድንግልን እና ሌሎች ገዥዎችን አሸንፏል። በእርሳቸው አገዛዝ ወቅት ንግድ ለክልሎች ኢኮኖሚ ህልውና ቁልፍ ነገር ነበር እናም አዳል ከተለያዩ ሀገራት በተለይም ከኦቶማን ቱርክ ጋር ጠንካራ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ነበረው። የእስልምና ሀይማኖት እንዲስፋፋም የጊዜው ነጋዴዎች ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። ይህም እስከ ዛሬ ድረስ በኣካባቢው ለሚኖሩ ሙስሊሞች መብዛት ምክንያት እንደሆነ ይታመናል። የአዳል ሱልጣኔት የተወለደው ከላይ በተገለጸው ሁኔታ ነው። በኢትዮጵያ ታሪክ ከታዩት ሱልጣኔታዊ መንግስታት ውስጥ እጅግ-ገናና ስም የነበረው ይኸው የአዳል ሱልጣኔት ነው። ይህ ሱልጣኔታዊ መንግስት የኢትዮጵያን ታሪክ ለመቀየር የቻሉትን እንደ አሚር ማሕፉዝ ሙሐመድ፣ ኢማም አሕመድ ኢብራሂም አል-ጛዚ (አሕመድ ግራኝ) እና አሚር ኑር ሙጃሂድን የመሳሰሉ ታላላቅ መሪዎችን አፍርቷል። በርካታ ጸሀፍት ስለርሱ ከትበዋል። በልዩ ልዩ ህዝቦች ስነ-ቃል ውስጥ እስካሁን ድረስ ያልቀዘቀዙ ወጎች እንዲከሰቱ ምክንያት ሆኗል። አሁንም ስለርሱ ታሪክ የሚያወሱ በርካታ ድርሳናት እየተጻፉ ነው። ከዚህ እልፍ ሲል ደግሞ “አዳል” የሚለው የሱልጣኔቱ መጠሪያ የሰው ስም ሆኖ ይገኛል። በተለይ የሚያስደንቀው ደግሞ በዚህ ስያሜ የሚጠሩት ከሙስሊሞች ይልቅ ክርስቲያኖች መሆናቸው ነው። ለዚህም ብዙዎች የሚያስታውሷቸውን እንደ ጋሻው አዳል፣ ዘሪኹን አዳልና ራስ አዳል ተሰማ (በኋላ ንጉስ ተክለ ሀይማኖት ተብለው በጎጃም የተሾሙት) የመሳሰሉ ስሞችን መጥቀስ ይቻላል። በሌላ በኩል የሰለሞናዊው አጼ መንግስት ከአዳል ሱልጣኔት ጋር በጦር ሜዳ እየተላለቀ ከነበሩት ክፍለ ጦሮች መካከል አንዱን “አዳል መብረቅ” በሚል ስያሜ ይጠራው ነበር። እርሱም በበኩሉ አዳልን እየጠላው ያደንቀው ነበር ማለት ነው። ከዚህ መረዳት እንደሚቻለው የሱልጣኔቱ ስመ-ገናናት በሁሉም ወገኖችና ህዝቦች ዘንድ ተደናቂነት ነበረው። “አዳል” የሚለው ስም ምንጭ በትክክል አይታወቅም። አንዳንዶች “አዳ አሊ” (በአፋርኛ የአሊ ቤት ለማለት ነው) ከሚል ሥርወ-ቃል እንደተገኘ ይገምታሉ። አንዳንዶች ደግሞ ጥንት የሀረር አሚር ከነበረው “አሚር ኢዳል” ስም የተገኘ እንደሆነ ይናገራሉ። ሆኖም እርግጠኛው ነገር ላይ አልተደረሰም። የስያሜው ጥንታዊነት ግን በብዙ ምንጮች የተረጋገጠ ነው። ለምሳሌ አቡ ፈድሉላህ አል-ዑመሪ የሚባለው ግብጻዊ ምሁር በ1349 ዓ.ል. በጻፈውና “መሳሊከል አብሳር ፊ መማሊከል መሳር” በሚባለው ዝነኛ መጽሀፍ ውስጥ አዳል ተደጋግሞ የተጠቀሰ ስም ነው። ከ1415 ዓ.ል. በፊት “አዳል” በኢፋት ሱልጣኔት ስር የነበረ የአንድ አውራጃ ስም ነበር። የዐጼ ዐምደ ጽዮን (1314-1344 ዓ.ል) ዜና መዋዕል ዘጋቢ እንደጻፈው ከሆነ የዚህ አውራጃ ዋና ከተማ “ተላቅ” የሚል ስያሜ ነበረው። “ፉቱሕ አል- ሐበሽ” የተሰኘው መጽሀፍ ደራሲ ሱልጣኔቱን “አዳል” ከሚለው ስም በተጨማሪ “በሪ ሰዓደዲን” (የሰዓደዲን በር) እና “ዳር ሰዓደዲን” (የሰዓደዲን ሀገር) በሚሉ ስሞችም ይጠራዋል። ይህም ሱልጣኔቱን ያቋቋሙት የሱልጣን ሰዓደዲን ልጆች እንደ ሰማዕት በሚያዩት አባታቸው ስም ያወጡለት የክብር ስያሜ ነው። የግዕዝ ምንጮችም ስለኢትዮጵያ ኢስላማዊ ግዛቶች በሚጽፉበት ጊዜ “አዳል” የሚለውን ስም በእጅጉ ይደጋግሙታል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ስያሜው ከግዛት መጠሪያነት ያልፍና የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በሙሉ በወል የሚጠሩበት ስም ሆኖ ይገኛል። በኢትዮጵያ ምድር ከታዩት ሱልጣኔቶች እምብዛም በማያደናግር ሁኔታ ታሪኩ የተጻፈለት “አዳል” ብቻ ነው (ከአንዳንድ አሻሚ ነጥቦች በስተቀር)። እጅግ ሰፊ ግዛት የሚያካልለውም “አዳል” ነው። ከሀረር ከተማ ታሪክ ጋር በእጅጉ የተቆራኘውም “አዳል” ነው። አዳል በስፋቱም ሆነ በሕዝቦቹ ብዛት በኢትዮጵያ ምድር ከታዩት ሱልጣኔታዊ ግዛቶች በእጅጉ ይልቃል። በፕሮፌሰር ኡልሪች ብራውኬምፐር ጥናት እንደተገለጸው አዳል በስተምዕራብ በኩል ከባሊ፣ ደዋሮና ፈጠጋር(የአሁኗ ቢሾፍቱ) ጋር ይዋሰናል። በስተሰሜን በኩል ደግሞ እስከ አውሳ በረሃ መጨረሻ ድረስ ይደርሳል። በምስራቅ እስከ ኤደን ባህረ ሰላጤ የሚደርስ ሲሆን በደቡብ ደግሞ ከህንድ ውቅያኖስ ጋር ይዋሰናል። በአዳል ግዛት ውስጥ የኦሮሞ፣ የአፋር፣ የሶማሊ፣ የሀረላ (ሀረሪ) እና የአርጎባ ህዝቦች ይኖሩ የነበረ ሲሆን በዘመናችን በውል የማይታወቁ ሌሎች ህዝቦችም ነበሩበት። ዘይላ፡ አራ፣ በርበራ፣ ዳርዱራ፣ ሳሊራ፣ ሆበት፣ ጊዳያ፣ ሐርጋያ፣ ሀረር እና ኩሰም ከአዳል ከተሞች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው። “ደከር” የሱልጣኔቱ የመጀመሪያ መዲና ነበረች፤ ከዚያም በዜይላ ተተካች፤ በስተመጨረሻም ሀረር የግዛተ መንግስቱ ዋና ከተማ ሆነች። አዳል የአዋሽ ወንዝ በሚፈስበት ክፍሉ እጅግ ለምና ለእርሻ ተስማሚ የሆነ መሬት ነበረው። አብዛኛው የሱልጣኔቱ ነዋሪ በግብርና ይተዳደር የነበረ ሲሆን ይህም የሰብል ማምረትንና የከብት እርባታን ያካተተ ነበር። በሌላ በኩል ሱልጣኔቱ የህንድ ውቅያኖስና የኤደን ባህረ ሰላጤ ተጎራባች መሆኑ ንግድ በክልሉ እንዲስፋፋ በእጅጉ ረድቷል። ዘይላ ሱልጣኔቱ ከውጪው ዓለም ጋር የሚገናኝበት ዋነኛ ወደብ ነበረች። የታጁራ፡ በርበራና መርካ ወደቦችም የሱልጣኔቱ አካላት ነበሩ። ከደቡብ፣ ከምዕራብና ከደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚመጡት የግብርና ውጤቶች፣ የዝሆን ጥርስ፣ ዝባድ ዘወተ.. ወደ ውጪ የሚላኩት በነዚሁ ወደቦች በኩል ሲሆን ከውጪው ዓለም የሚገቡ ሸቀጦችም ወደ ልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገቡት በሱልጣኔቱ ምድር ነው። ሰፊው የአዳል ሱልጣኔት በስሩ ያሉትን ክልሎች ሁሉ አንድ ወጥ በሆነ መንገድ አይደለም ያስተዳደረው። በስሩ ካሉት አካባቢዎች አንዳንዶቹ የራስ ገዝ አይነት አስተዳደር ነበራቸው። እነዚህ አስተዳደሮች “አሚር” የሚል ማዕረግ በነበራቸው ገዥዎች ይተዳደሩ ነበር። በአሚር ከሚተዳደሩት የአዳል ክፍለ ሀገራት በጣም ጎልተው የሚታዩት ዘይላ፣ ሁበትና ሀረር ናቸው። “አዳል” ሱልጣኔቱ በታሪክ የሚታወቅበት ትክክለኛ ስም ነው። ይህም ከላይ እንደገለጽኩት በበርካታ የጥንት ሰነዶች ውስጥ የተመዘገበ ስያሜ ከመሆኑም በላይ የሱልጣኔቱ ገዥዎችና የሀገሬውም ህዝብ በመጠሪያነት ይጠቀሙበት ነበር። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን አንዳንድ ጸሀፍት ስያሜውን ከታሪክ ሰነዶች የማውጣት አዝማሚያ እየታየባቸው ነው። ምክንያቱን ባይነግሩንም ከሁኔታዎች መገመት የሚቻል ይመስለኛል። ይኸውም የ“አፋር ህዝብ ስያሜውን እንደ ስድብ ያየዋል” በሚል ሰበብ ነው። በርግጥም የአፋር ህዝብ “አፋር” ተብሎ ነው መጠራት ያለበት። ይህንንም በ1969 ዓ.ል. በገዋኔ ከተማ በተደረገው ታላቅ ጉባኤ ባሳለፈው ውሳኔ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች አስታውቋል። እኛም ውሳኔውን በሙሉ ልባችን እናከብረዋለን። ስለዚህ “አዳል” የሚለው ስም የ“አፋር” ህዝብ መጠሪያ ሆኖ መቅረብ የለበትም። ነገር ግን በታሪክ ድርሳናት የሰፈረው “አዳል” የመንግስት ስም ከመሆኑ ውጪ የአፋር ህዝብን በተናጠል የሚመለከት ስያሜ አይደለም። ደግሞም ስያሜውን ለመንግስታቸው ያወጡት የጥንቱ ወላስማዎችና የሱልጣኔቱ ህዝቦች በዚህ ስም መጠራቱን ይወዱት ነበር። ዛሬ እኛ ተነስተን ጥንት “አዳል” ሲባል የነበረውን የሱልጣኔታዊ መንግስቱን ስያሜ “አፋር” ወደሚለው ከቀየርነው ታሪክ በጣም ይፋለሳል። ሱልጣኔቱ የበርካታ ህዝቦች ግዛት ሆኖ ሳለ የአንድ ህዝብ ብቻ አድርጎ ማቅረቡም ከባድ ስህተት ነው። ስለሆነም የጥንቱን ሱልጣኔት “አዳል” በሚለው ትክክለኛ ስሙ መጥራት ይገባል። ከዚህ ጋር መጠቀስ ያለበት ሌላ ጉዳይ ደግሞ በ“አዳል” ታሪክ ላይ የሚደረገው የታሪክ ሽሚያ ነው። በዘመናችን የተለቀቁ በርካታ የኢንተርኔት ገጾች “አዳል” የሶማሊዎች ሱልጣኔት እንደነበረና ግዛቱም ሶማሊዎች የሰፈሩበትን አካባቢ (ሶማሊያ፣ ሶማሊላንድ፣ ኦጋዴን ወዘተ...) ብቻ እንደሚያጠቃልል አድርገው ነው የሚጽፉት። እነኝህ የኢንተርኔት ጽሁፎች አንድ የማያስተባብሉት ነገር ቢኖር “ሀረር የአዳል ዋና ከተማ ነበረች” የሚለው ብቻ ነው (ይህንንም ማስተባበል ያልቻሉት በፉቱሑል ሐበሽ ውስጥ የተጻፈ ሀቅ ስለሆነ ነው)። የሶማሊያው ጄኔራል ሙሐመድ ዚያድ በሬ በ1970 ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜም ይህንን የአዳል ሱልጣኔት ታሪክ እንደ ባለቤትነት ማረጋገጫ () በማቅረብ “ከአዋሽና ዋቤ ሸበሌ ወንዞች በስተምስራቅና ደቡብ ያለው ግዛት በሙሉ የሶማሊያ ህጋዊ መሬት ነው” የሚል ፕሮፓጋንዳ ነዝቶ ነበር። ይሁንና ይህ ሁሉ ዐይን ያወጣ የታሪክ ዘረፋ ነው። በአዳል ግዛት ውስጥ ሶማሊዎች መኖራቸው እርግጠኛ ነገር ቢሆንም አዳልና የዛሬዋ ሶማሊያ በአፈጣጠራቸው፣ በማህበረ ህዝብ ተዋጾኦዋቸውና በታሪካዊ ጉዞአቸው በጭራሽ አይመሳሰሉም። አዳል የጥንታዊው የኢፋት ሱልጣኔት ቀጥተኛ ወራሽ () ሆኖ ነው የተቋቋመው። የሱልጣኔቱ መሪዎችም በኢፋት (የዛሬው ሰሜን ምስራቅ ሸዋ ) አካባቢ ማዕከላቸውን ከቆረቆሩት የጥንቱ የወላስማ ሱልጣኖች የዘር ሀረግ ነው የተገኙት። የሱልጣኔቱ ዋና መስራች የሚባሉት ህዝቦች የሚኖሩትም በአሁኑ የኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ነው። በአንድ ዘመን “አዳል” ሲባል የነበረው ስፍራ የተጠቃለለው በአሁኑ የኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ነው (“አዳል እና ኢሳ” እና “ጨርጨር፣ አዳልና ጋራ ጉራቻ” የሚባሉትን አውራጃዎች ታስታውሱ የለም?)። የዛሬዋ ሶማሊያ አብዛኛው ክፍል በአዳል ሱልጣኔት ስር የነበረ ግዛት ቢሆንም ሱልጣኔቱ ታሪክ ሲሰራ የነበረውም ሆነ ታሪኩ የተቀበረው አሁን በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ባለው ዋነኛ መሬቱ ላይ ነው። በአጭር አነጋገር የ“አዳል” መነሻም ሆነ እምብርቱ የነበረው በአሁኑ የኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ነው። በሌላ በኩል አዳል በዘመኑ (ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን) የነበሩት የኢትዮጵያ ሱልጣኔታዊ ግዛቶች ሁሉ (ሀዲያ፣ባሌ፣ ደዋሮ፣ ሻርካ፣ ደራ፣ አራባባኒ ወዘተ..) የፖለቲካዊና መንፈሳዊ መሪ እንደነበረም የታሪክ ድርሳናት ያረጋግጣሉ። ዛሬ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ 45 በመቶ ያህል የሚሸፍኑት ሙስሊም አማኞች መነሻም በነዚያ የጥንት ሱልጣኔታዊ ግዛቶች የሚኖሩት ሙስሊሞች ናቸው። በዚህ አንጻር ሲታይም የሱልጣኔቱ ታሪክ ህጋዊ ባለቤቶች መላው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች እንጂ በ1960 ዓ.ል የተወለደው የሶማሊያ መንግስትና የ“ታላቋ ሶማሊያ” መፈክር አቀንቃኞች አይደሉም። (ምንጭ፡- አፈንዲ ሙተቂ፣ “ሀረር ጌይ-2”- የሀረርና የአዳል ታሪካዊ ወጎች፡ ገጽ 33-35) (ምንጭ፡- አፈንዲ ሙተቂ፣ “ሀረር ጌይ-2”- የሀረርና የአዳል ታሪካዊ ወጎች፡ ገጽ 33-35) አዳል የምለው ስም የጉሣ ስም ይምሰልናል አፋር ውስጥ አዳአል ይምባል ጐሣ አለ ና አዳል የሚለው ስም የጐሣ ስም የምሰልናል የኢትዮጵያ ታሪክ ታሪካዊ አገሮች
14001
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%A0%E1%89%A0%20%E1%89%A2%E1%89%82%E1%88%8B
አበበ ቢቂላ
አበበ ቢቂላ ነሐሴ ፴ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም በሸዋ አውራጃ፣ ደነባ ልዩ ስሟ ጃቶ ከምትባል ሥፍራ ላይ ከአባቱ አቶ ደምሴ ዓለሜ እና ከእናቱ ከወይዘሮ ውድነሽ መንበሩ ተወለደ። ቢቂላ የሚለውን የአባት ሥም መጠርያ ያገኘው ግን ከእናቱ የመጀመርያ ባል እና ካሳደጉት አቶ ቢቂላ ነው። ወጣቱ አበበ እንደአካባቢው ልምድ በእረኝነትና በትምሕርት ተሰማርቶ በአሥራ ሁለት ዓመቱ የቄስ ትምሕርቱን አጠናቀቀ። በዚህ በጨቅላ ዕድሜው ስመ ጥሩ የገና ተጫዋች እንደነበር ይነገርለታል። በ፲፱፻፵፬ ዓ/ም አዲስ አበባ ሄዶ በክብር ዘበኛ በወታደርነት ይቀጠርና በገና ጨዋታ እና በስፖርት እየዳበረ ቆየ። ወዲያው በ፲፱፻፵፮ ዓ/ም የአራት ልጆቹን እናት ወይዘሪት የውብዳር ወልደጊዮርጊስን አገባ። በኅዳር ወር ፲፱፻፵፰ ዓ/ም በአሥራ ስድስተኛው የሜልቡርንኦሊምፒክ ላይ የተሳተፈውን የኢትዮጵያን ቡድን ለመቀበል በተደረገው ሰልፍ ላይ ከጀርባቸው ላይ የአገራቸው ስም የተጻፈበትን መለያ ልብሳቸውን ለብሰው አገራቸውን ወክለው የተወዳደሩትን ወጣቶች ባየ ጊዜ ምን ያህል የኩራት ስሜት እንደተሰማውና ያን ጊዜ እሱም እንደነሱ ለመሳተፍ እንደወሰነ ይጠቀሳል። በዚሁ ዘመን አበበ በብሔራዊ የሠራዊቱ እርስ በርስ ውድድር ላይ ተሳተፎ፣ በ፭ ሺህ ሜትር እና በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫ የብሔራዊውን ክብረ ወሰን የያዘው የጊዜው የስፖርት ጀግና ዋሚ ቢራቱ እና አበበ በማራቶን ውድድሩ ሲገጥሙ ተመልካቹ ሕዝብ ዋሚ ያሸንፋል ብሎ ነበር የሚጠብቀው። ከጥቂት ኪሎሜትሮች በኋላ አበበ ቢቂላ የተባለ ያልታወቀ ወጣት ቀድሞ ሩጫውን እየመራ እንደሆነ ሕዝቡ በራዲዮ ሰማ። አበበ በቀላሉ ይሄንን ውድድርም አሸነፈ። የዋሚንም የአምስት ሺ እና አሥር ሺ ሜትር ክብረ ወሰን በመስበር እየታወቀ መጣ። በዚህ ሁኔታ ነው አበበ ለ፲፱፻፶፪ ዓ/ም የሮማ ኦሊምፒክ በተወዳዳሪነት የተመረጠውና ካራት ዓመት በፊትም ያንን የአገሩን መለያ ልብስ በዓለም አቀፍ ውድድር ላይ ለብሶ ለመሳተፍ ያለመው ሕልሙን እውን ያደረገው። በጦር ካምፕ ውስጥ አበበ የሚያደርጋቸውን ልምምዶች እና ውድድሮች በጥሞና ይከታተሉ የነበሩት ስዊድናዊ አሰልጣኝ ኦኒ ኒስካነን የአበበን ችሎታ በመገንዘባቸው ከሌሎቹ አትሌቶች ጋር ተቀላቅሎ ልምምድ እንዲሠራ ያደርጉት እና የሮም ኦሎምፒክ እስኪቃረብ ድረስ በሚል ከሁለት ሺህ ሜትር በላይ ከፍታ ባላቸው ተራራማ ቦታዎች ላይ የመሮጥ እና የሺህ አምስት መቶ ሜትር ተደጋጋሚ የፍጥነት ሩጫ ልምምዶችን እንዲሠሩ ያደርጓቸዋል። “ሮማን የወረረው ብቸኛው ወታደር” አገራችውን ወክለው በዚህ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ከአሰልጣኙ ጋር ወደሮማ ካመሩት የኢትዮጵያ ተወዳዳሪዎች መሃል ለማራቶን ሩጫ የተመረጡት አበበ ቢቂላ እና አበበ ዋቅጅራ ነበሩ። ውድድሩ አንድ ወር ሲቀረው እዚያው ሮማ ከተማ ውስጥ ሲሰለጥኑ የቆዩት ሁለቱ አበበዎች፣ የሩጫውን መንገድ በጥንቃቄ እንዳጠኑና ሲሮጡም በባዶ እግርም በጫማም እንደተለማመዱ፣ አበበ በጫማ ሲሮጥ በአምስትና በስድስት እርምጃዎች ስለሚዘገይ ሁለቱም በባዶ እግራቸው እንዲሮጡ መወሰኑን አሰልጣኙ ኒስካነን ከውድድሩ በኋላ ለተባለ መጽሔት የተናገሩት ያሳያል። ኒስካነን ሩጫው በማታ ሰዐት ስለሚካሄድ የሞቀው የመንገድ ሬንጅ እንደማይጎዳቸውና ከውሳኔውም በኋላ ውስጥ እግራቸው እንዲጠነክርም ኦሊምፒክ መንደሩ ውስጥ ሁሉ በባዶ እግራቸው እንደነበር የሚሄዱት ይነግሩናል። በዚሁ መጽሔት ላይ ዋቢ ቢራቱ የተዘጋጀውም፣ የተመረጠውም ለ፲ ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር እንደነበረና ለኦሊምፒኩ ዝግጅት በሚያደርጉበት ጊዜ በራሱ ውሳኔ ከስልጠና ጣቢያቸው እስከ አዲስ አበባ ድረስ በአንድ ቀን መቶ ኪሎሜትር በመሮጥ በመታመሙ ከቡድኑ እንደወጣ ይነግሩናል፡፡ (ብዙ ስህተታዊ ዘገባዎች (ሀ) አበበ ቡድኑ ውስጥ የተጨመረው ዋቢ ቢራቱ በእግር ኳስ ጨዋታ ቁርጭምጭሚቱ በመሰበሩ የሱ ምትክ ሆኖ በመጨረሻው ሰዐት ነው (ለ) ስለዚህም የተሰጠው ጫማ ስለጠበበው/ሌላ ስላልነበረው ነው በባዶ እግሩ የሮጠው እያሉ ዘግበዋል።) አሰልጣኙ ኒስካነን ሁለቱን ኢትዮጵያውያን ሯጮች የጊዜውን ምርጥ ማራቶን ተወዳዳሪዎች፦ የሞሮኮው ራህዲ ቤን አብዴ ሰላም ፣ የኒውዚላንድ ባሪ ማጊ፣ የሶቪዬቱ ኮንስታንቲን ቮሮብዮቭ እና በወቅቱ የማራቶን ክብረ ወስን ባለቤት የነበረው ሰርጌይ ፖፖቭ እና የብሪታንያ ተወላጅ ዴኒስ ኦጎርማን እንደሆኑ በጥብቅ አስጠንተዋቸዋል። ራህዲ ይለብሳል የተባለው የመለያ ቁጥሩ ፳፮ መሆኑን ያጠናው አበበ ውድድሩ ላይ ይሄንኑ ቁጥር ለመለየት ሲፈልገው ለካስ ራህዲ በ፲ ሺህ ሜትር ውድድር ላይ ለብሶ የነበረውን መለያ ለብሶ ኖሮ አጠገቡ ሲሮጥም አላወቀውም። አበበ በውድድሩ ላይ ከሃያ እስከ ሠላሳ ኪሎሜትር ላይ ባሳየው ፍጥነት አብዛኛዎቹን ባላጋራዎቹን ጥሎ ሲሄድ የቀረው ራህዲ ብቻ ነበር። እሱም ብዙ አብሮት አልቆየም። አበበ ድሉን ከተቀዳጀ በኋላ “ከተማው ክልል ውስጥ ስገባ ከኋላዬ የምሰማቸው ኮቴዎች እየቀነሱ መጡ። ፍጥነትም ስጨምር እስከነአካቴው ድምጽም አልነበረም። ለአንድ ሰዐት ሙሉ የኮቴዎችን ካካታ ሳዳምጥ ከቆየሁ በኋላ አሁን ጸጥታ ሲሰፍን የተከተለኝ እንዳለ ለማየት ፊቴን ማዞር አስፈላጊ አልነበረም” ብሏል። አበበ አስተሳሰቡ ራዲ እስከሚያጋጥመው ድረስ ጉልበቱን ለመቆጠብ ስለነበር በዚህ ምክንያት ባይሆን ኖሮ ክብረ ወሰኑን በተሻሻለ ውጤት ይሰብር እንደነበር ኒስካኒን ጥርጣሬ እንዳልነበራቸውም ገልጸዋል። ሆኖም አበበ ቢቂላ ውድድሩን በሁለት ሰዐት ከአሥራ አምስት ደቂቃ ከአሥራ ስድስት ነጥብ ሁለት ሴኮንድ (2:15:16.2 ሰዓት) በማገባደድ የዓለምን ክብረ ወስን ሰብሮ ወርቅ አገኘ። ራህዲ ሁለተኛ እና ባሪ ማጊ ሦስተኛ ወጡ። የጣልያን ጋዜጦች በነጋታው “ኢትዮጵያን ለመውረር የጣልይን አገር ወታደር ሁሉ አስፈልጎ ነበር ኢትዮጵያ ግን አንድ ወታደር ብቻ ልካ ድፍን ሮምን ወረረችው” የሚል ጽሁፍ ይዘው ወጥተው ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ በኦሎምፒክ ውድድር አሸንፎ የወርቅ ሜዳሊያ የወሰደ ጥቁር አፍሪካዊ አበበ ቢቂላ ነው። ይህም አጋጣሚ ለብዙ ጥቁር አፍሪካውያን በዓለም አቀፍ ውድድር እንዲሳተፉ በር ከፍቷል። የአበበ ቢቂላ ዝናም ከአለም ጫፍ እስከ ጫፍ ተዳረሰ። የአበበ ቢቂላ አዲሱ የዓለም ክብረ ወሰን = 2:15:16.2 የሰርጌይ ፖፖቭ አሮጌው የዓለም ክብረ ወሰን = 2:15:17.0 አበበ ከዚህ ውድድር በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በተመለሰ በሁለት ወሩ በክብር ዘበኛ ሠራዊት ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄነራል መንግሥቱ ንዋይ እና በወንድማቸው ገርማሜ ንዋይ ጥንሰሳ የተካሄደው ፲፱፻፶፫ ዓ/ም የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ሲከሽፍ፣ የሠራዊቱ አባል የነበረው አበበም ከሌሎች ወታደሮች ጋር በመጠርጠር ለጥቂት ጊዜ ታስሮ ነበር። ከግርግሩ በኋላ ከታኅሣሡ ግርግር በኋላ እስከ ጥቅምት ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ድረስ አበበ በ ግሪክ በ ጃፓን እና በኮሲቼ በ ቼኮስሎቫኪያ በማራቶን ተወዳድሮ በሁሉም አንደኛ በመውጣት አሸንፏል። በሚከተሉት ሁለት ዓመታት ግን በማናቸውም የዓለም አቀፍ ማራቶን ውድድር ላይ ሳይሳተፍ ቆይቶ በሚያዝያ ፲፱፻፶፭ በቦስተን ከተማ በተካሄደው ማራቶን ላይ ተሳትፎ አምስተኛ ሆኖ ነው የጨረሰው። ሐምሌ ፫ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም አዲስ አበባ ላይ የተካሄደው የኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ማጣሪያ ውድድር በአበበ አሸናፊነት፤ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞማሞ ወልዴ እና ሦስተኛ የወጣው ደምሴ ወልዴ ወደ ቶክዮ እንደሚጓዙ ሲረጋገጥ በመላው ዓለም ኢትዮጵያ አንድ ብቻ ሳይሆን ሦስት ኃይለኛ ተወዳዳሪዎች እንዳላት ተሰማ። ሁለተኛው የኦሎምፒክ ወርቅ የ፲፱፻፶፯ ዓ/ም ፲፰ኛው የቶክዮ ኦሊምፒክ ሊካሄድ አርባ ቀናት ሲቀረው አበበ ቢቂላ በማራቶን ውድድር ልምምድ ላይ ነበር። በልምምዱ ላይ እያለም ህመም ቢሰማውምን ህመሙን ችላ በማለት ልምምዱን ቀጠለ። ነገር ግን በልምምድ ላይ ራሱን ስቶ ይወደቅና አንስተው ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱት ህመሙ ያበጠ የትርፍ አንጀት ሆኖ ተገኘ። ወዲያው ቀዶ ጥገና ተደርጎለት ለጥቂት ቀኖች ካገገመ በኋላ በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ በምሽት ልምምዱን ቀጠለ። አበበ ቢቂላ ከኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ቡድን ጋር አብሮ ወደ ቶኪዮ ሲጓዝ በርትቶ ይወዳደራል ብሎ ያሰበ ሰው አልነበረም። አበበ ግን (ጫማ አድርጎ) ለዚህ ማራቶን ውድድር ጥቅምት ፲፩ ቀን ከአርባ አንድ አገሮች ከተውጣጡ ሰባ ዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ጋር ተሰለፈ። ለአበበ ቢቂላ ምንም አዲስ ዘዴ አላስፈለገውም። አሰልጣኙ ኦኒ ኒስካነን እንደ ሮማው ኦሎምፒክ ከፊት ከሚመሩት ቡድኖች ጋር እስከ ሃያ ኪሎ ሜትር ድረስ አብሮ እንዲሮጥና ከዚያ በኋላ ውድድሩን እንዲመራ መከሩት። በዚህም ዕቅድ መሠረት ከሮጠ በኋላ ፍጥነቱን በጥንቃቄ ቀስ በቀስ እየጨመረ ሄደ። በአሥራ አምስተኛው ኪሎ ሜትር ላይ አብረውት የነበሩት የአውስትራሊያው ሮን ክላርክ እና የአየርላንድ ጄምስ ሆጋን ብቻ ነበሩ። አበበ ቢቂላ በቀዶ ጥገናውም ሆነ በሞቃታማው የአየር ሁኔታ ምንም ዓይነት እንከን አልታየበተም። እንዲያውም ሲሮጥ ለሚመለከተው ከመሬቱ በላይ የሚንሳፈፍ ይመስል ነበር። አሰልጣኙ ኦኒ ኒስካነን ትንሽ ጉልበት በመጠቀም እንዴት መሮጥ እንዳለበት ያስተማሩትን አበበ ቢቂላ በተግባር ላይ ሲያውለው እና ሩጫው ምንም ዓይነት ጥረት የማያስፈልገው ያስመስለው ነበር። አበበ ቢቂላ ኦሎምፒክ ስታዲዮሙ ውስጥ የገባው ብቻውን ነበር። በዚያም ይጠባበቅ የነበረው ፸ ሺህ ተመልካች በከፍተኛ ሁኔታ አድናቆቱን ገልጾለታል። በዚህ ውድድር ላይ የራሱን ክብረ ወሰን በድጋሚ በመስበር አሻሽሎታል። አዲሱ ክብረ ወሰንም ሁለት ሰዐት ከአሥራ ሁለት ደቂቃ ከአሥራ አንድ ነጥብ ሁለት ሴኮንድ ነበር። ውድድሩንም እንደጨረስ ምንም አይነት ድካም አልታየበትም። እንዲያውም ገና ሊሮጥ የሚሰናዳ ነበር የሚመስለው። ተመልካቹን በጣም ያስገረመው በውድድሩ ምክንያት ጡንቻው እና መገጣጠሚያዎቹ እንዳይተሳሰሩ የተለያዩ የሰውነት ማሟሟቂያ ስፖርቶች ሲሰራ መመልከታቸው እንዲሁም እርጋታው እና ቅልጥፍናው ነበር። አበበ ከውድድሩ በኋላ ተጠይቆ ሲመልስ ሌላ አስር ኪሎ ሜትር ጨምሮ መሮጥ ይችል እንደነበር ተናግሯል። ደምሴ ወልዴ በአሥረኛ ደረጃ ሲጨርስ ማሞ ወልዴ ግን አሥራ አምስት ኪሎሜትር ላይ አቋርጦ ከውድድሩ ወጣ። አበበ ከሮሙ ድሉ አራት ዓመት በኋላ ቶኪዮ ድሉን ሲደግም የኦሊምፒክን ብቻ ሳይሆን የዓለምንም ክብረ ወሰን መስበር ችሏል። ከእርሱ በፊት ማንም ያልፈጸመውን፣ ከእርሱም በኋላ ለ16 ዓመታት ማንም ያላደረገውን የኦሊምፒክ ማራቶን ሁለት ጊዜ አከታትሎ የመውሰድ ገድልንም ፈጸመ። ይኸም ብቻ አይደለም ባሻናፊነት የገባበት ሰዓትም እጅግ በጣም ፈጣንና በእንግሊዛዊው ባዝል ሔትሌይ በ2 ሰዓት 13 ደቂቃ 55 ሰኮንድ ተይዞ የነበረውን የዓለም ክብረወሰን በ1 ደቂቃ 43 ካልዒት (ሰከንድ)፣ 8 ሣልሲት (ማይክሮ ሰከንድ) የሰበረበት ነው:: ‹‹እንደ በረዶ ነጫጭ ጥርስ አብቅሎ፤ ይቆረጣጥማል ሰዓት እንደቆሎ፤›› ብለው በወቅቱ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዋና ጸሐፊና የልዑካኑ መሪ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ እንዲቀኙለት አድርጓቸዋል። ቻርሊ ሎቬት “ማራቶን በኦሎምፒክ” በሚለው መጽሐፉ ላይ ስለቶክዮው ውድድር ሲዘግብ “ግማሽ ሩጫውን እንዳገባደደ በአምስት ሰከንድ ልዩነት ይመራ ነበር” ይላል ። ሎቬት “የክፍለ ዘመኑ ሩጫ ብዙ ታሪክ የተጻፈለት እና የተወራለት ውድድር ነው” ሲል አበበ ቢቂላን ደግሞ “ወደር የማይገኝለት እውነተኛ የማራቶን ሯጭ ምሳሌ ነው” ይለዋል። ሪቻርድ በኔዮ ደግሞ “የማራቶን ጌቶች” በሚለው መጽሐፉ “አበበ ቢቂላ ሩጫው ምንም አይነት ጥረት የማያስፈልገው ያስመስለዋል” ብሎታል። “አበበ ቢቂላን ሲያዩት ረጅም ቀጠን ያለ በቀላሉ ተሰባሪ ይመስላል፣ ነገር ግን ከሚገባው በላይ ጠንካራ አትሌት” ነው ይልና “አበበ ቢቂላ ማናቸውም የማራቶን ሩጫ ተወዳዳሪ ሊሆን የሚገባው ምሳሌ ነው” ብሏል። ቀጥሎም “አበበ ቢቂላ ተፈጥሮ ካፈራቻቸው ምርጥ የዓለማችን አትሌቶች አንዱ ነው” ይልና “በዚህም (በቶክዮው) ድል የተነሳ ለሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ ማራቶንን ያሸነፈ ብቸኛ አትሌት አድርጎታል” ይላል። አበበ ቢቂላ ሁለተኛውን ወርቅ ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሰ የአዲስ አበባ ሕዝብ ተገልብጦ ወጥቶ የጀግና አቀባበል ካደረገለት በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ የሻምበልነት ማዕረግና አዲስ ቮልስ ዋገን ቢትል ሸለሙት። ሜክሲኮ ከተማ በ ፲፱፻፷ ዓ/ም ላይ በሜክሲኮ ከተማ የተካሄደው ፲፱ኛው ኦሊምፒክ ውድድር ከመጀመሩ በፊት አበበ በ፲፱፻፶፯ ዓ/ም እና ፲፱፻፶፰ ዓ/ም ሦስት ማራቶኖች ላይ ተሳትፎ ሦስቱንም አሸንፏል። በሰኔ ወር ፲፱፻፷ ዓ/ም እግሩ ላይ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት ዝግጅቱን እንዲያቋርጥ ተገዶ ነበር። በድ ግሪንስፓን “የኦሊምፒክ ተወዳጅ ታሪኮች” በሚባለው የትረካ ፊልም ላይ “ከውድድሩ ጥቂት ቀናት በፊት አበበ ትንሽ የእግር አጥንቱን ሰብሮ ነበር” ብሏል። ሜክሲኮ ሲገባም በእግሩ ላይ የደረሰው ጉዳት አልተሻለውም ነበር። ውድድሩ የሚካሄድበት ቦታ ከፍታው አበበ ቢቂላ ከለመደው በ አንድ ሺህ ጫማ ከፍታማ ቢሆንም እንድ አበበ ግምት ግን ከሌሎች አትሌቶች ይልቅ ይህ ከፍታ ለኔ ይጠቅመኛል ብሎ ነበር። የማራቶኑ ውድድር እሑድ ጥቅምት ፲ ቀን ፲፱፻፷ ዓ/ም ሲጀመር ከአርባ አንድ አገራት የተውጣጡ ሰባ አራት ሯጮች ተሰልፈው ነበር። ኢትዮጵያ በቶክዮው ማራቶን እንድተደረገው በሜክሲኮም ከአበበ ጋር ሦስት ሯጮችን አሰልፋለች። ማሞ ወልዴ እና ገብሩ መራዊ ሌሎቹ ተሳታፊዎች ነበሩ። አበበ ውድድሩን ጀምሮ ከፊት ከሚመሩት ጋር እስከ አስራ ሰባተኛው ኪሎሜትር ድረስ ከሮጠ በኋላ የእግሩ ሕመም ስለጠናበት አብሮት የነበረው ማሞ ወልዴ ባልገመተውና ባላሰበው ሰዓት በጆሮው ተምዘግዝጐ የገባውን የአበበን ቃላት ማመን አቃተው። እንደመደንገጥ ብሎ «ምን አልከኝ ?» በማለት ጠየቀው። አበበም የማሞን መደናገጥ ስለተገነዘበ እንደ ማባበል ዓይነት አለና « አይዞህ ታሸንፋለህ፤ እኔ አልቻልኩም፤ የ እግሬ ወለምታ በጣም ተሰምቶኛል፤ ሌላም የማላውቀው ስሜት እየተሰማኝ ነው። ስለዚህ አደራዬን ተቀበለኝ፤ የ ኢትዮጵያ ሕዝብ ይጠብቀናል፤ እኔ ስላልቻልኩ አንተ ቀጥል፤ የ ኢትዮጵያ አምላክ ይከተልህ» ካለው በኋላ አስፋልት ዳር ወደቀ። እውነትም በጣም ታሟል። ወዲያውኑ አበበ ሜክሲኮ ሆስፒታል በአስቸኳይ ተወሰደ። የአበበ አለመጨረስ ሲሰማ ያልደነገጠ ኢትዮጵያዊም ሆነ የአበበ አድናቂ አልነበረም። ሁናቴውን ታዋቂው ጋዜጠኛ ሰለሞን ተሰማ እንዲህ ገልፆት ነበር፤ «የአበበን መውጣት ስሰማ ማሞን ለማበረታታት የጮህኩት ጩኸት ድምፄን ለሦስት ቀናት ያህል ዘግቶት ነበር።» በዚህ ውድድር ገብሩ መራዊ ስድስተኛ ሆኖ ሲገባ ከአበበ ቢቂላ ጋር አብሮ የተጓዘው ማሞ ወልዴ አሸንፎ ለኢትዮጵያ ሦስተኛውን የማራቶን ወርቅ ተቀበለ። ማሞ ወልዴ ከውድድሩ በኋላ እንድብራራው አበበ ቢቂላ በሕመም ምክንያት ባያቋርጥ ኖሮ ያለምንም ጥርጥር ያሸንፍ ነበር ብሏል። አበበ ቢቂላ ከዚህ በኋላ ውድድር አላደረገም። አሳዛኝ አደጋ ሻምበል አበበ ቢቂላ በ፲፱፻፷፩ ዓ/ም በሽልማት የተሰጠውን ቮልስ ዋገን መኪና በአዲስ አበባ ውስጥ ሲነዳ አደጋ ደርሶበት ከወገቡ በታች ሽባ ሆነ። ንጉሠ ነገሥቱ ለሕክምና ወደ እንግሊዝ አገር ልከውት በታወቀው የስቶክ ማንደቪል ሆስፒታል () ሲረዳ ቢቆይም ከተሽከርካሪ ወንበር የማያላቅቀው በመሆኑ ወደሚወዳት ሀገሩ ኢትዮጵያ በቃሬዛ ተመለስ። አዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ቤተሰቡ፣ ወዳጆቹና ደጋፊዎቹ ሲቀበሉት በበዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም በየመንገዱ ዳር ተሰልፈው እያጀቡ ተቀበሉት። ከአደጋው በኋላ እነኛ ዓለምን ያስደነቁ እግሮች ሁለተኛ አልተራመዱም። አሰልጣኙ ኦኒ ኒስካነን የቀስት ኢላማ ውድድር ውስጥ እንዲሳተፍ ሲመክሩት ነበር፣ አበበ “በተሸከርካሪ ወንበሬ ላይ ሆኜ ማራቶንን አሸንፋለሁ” እያለ ይቀልድ ነበር። ሆኖም ከአደጋው በኋላ በስቶክ ማንደቪል አካላቸው በጎደለ ሰዎች ስፖርት ውስጥ በዚሁ የቀስት ኢላማ ውድድር ላይ ከመሳተፉም በላይ “መልካም ውጤት የሚያመጡ ሰዎች አሳዛኝ አደጋም ይገጥማቸዋል። በእግዚአብሔር ፍቃድ የኦሎምፒክ ማራቶንን ለማሸነፍ በቃሁ እንዲሁም በእግዚአብሔር ፍቃድ የመኪና አደጋ ደረሰብኝ። ድሉን እንደተቀበልኩ ሁሉ እንዲሁም መከራውን መቀበል አለብኝ። ሁለቱንም የሕይወት ሁኔታዎች ስለሆኑ በጸጋ ተቀብዬ ሕይወቴን በደስታ መኖር ነው ያለብኝ” ብሏል። የሁለቴው የኦሊምፒክ ማራቶን አሸናፊና የማራቶን የክብር ወሰን ባለቤት ሻምበል አበበ ቢቂላ በ፲፱፻፷፬ ዓ/ም በተካሄደው ፳ኛው የሙኒክ ኦሊምፒክ ውድድር ላይ በልዩ እንግዳነት ተጋብዞ በተሽከርካሪ ወንበሩ ላይ ተቀምጦ ውድድሩን ይመለከት ነበር። የማራቶኑን ውድድር ያሸነፈው አሜሪካዊው ፍራንክ ሾርተር ሽልማቱን ከተቀበለ በኋላ በቀጥታ ወደ አበበ ቢቂላ በመሄድ እና እጁን በመጨበጥ ያለውን ፍቅር እና አክብሮት ገልጾለታል። ጀግና ወደቀ ሻምበል አበበ ቢቂላ ፤ “ሮማን የወረረው ብቸኛው ወታደር”፤ በተወለደ በ ፵፩ ዓመቱ፤ የሜክሲኮውን ሩጫ አቋርጦ መንገድ ዳር በወደቀ በስድስት ዓመቱ ጥቅምት ፲፭ ቀን ፲፱፻፷፮ ዓ/ም የሕይወት ትግሉን ጨርሶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። ከተወዳደረባቸው አስራ አምስት የማራቶን ውድድሮች አስራ ሁለቱን በአንደኛነት የጨረሰው ኢትዮጵያዊው ጀግና ጉዞውን አከተመ። አበበ አዲስ አበባ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን ሲቀበር ዓፄ ኃይለ ሥላሴ በተገኙበት ዘመዶቹ ወዳጆቹ እና አድናቂዎቹ ጋር ከ፸፭ ሺህ በላይ የሚሆን ሕዝብ ተሰብስቦ እየተላቀሰ የመጨረሻ ስንብት አድርጎለታል። ዕለቱም በመላ ኢትዮጵያ የሐዘን ቀን ሆኖ እንዲውል ተደርጓል። “እኔ ዓለም ሁሉ እንዲያውቀው የምፈልገው አገሬ ኢትዮጵያ ሁል ጊዜ የምታሸንፈው በቆራጥነት እና በጀግንነት ነው” ሮማ ካሸነፈ በኋላ “መልካም ውጤት የሚያመጡ ሰዎች አሳዛኝ አደጋም ይገጥማቸዋል። በእግዚአብሔር ፈቃድ የኦሎምፒክ ማራቶንን ለማሸነፍ በቃሁ እንዲሁም በእግዚአብሔር ፈቃድ የመኪና አደጋ ደረሰብኝ። ድሉን እንደተቀበልኩ ሁሉ እንዲሁም መከራውን መቀበል አለብኝ። ሁለቱም የሕይወት ሁኔታዎች ስለሆኑ በጸጋ ተቀብዬ ሕይወቴን በደስታ መኖር ነው ያለብኝ።" የተሽከርካሪ ወንበር ተጠቃሚ ከሆነ በኋላ "እኔ የዓለም አንደኛ የኢትዮጵያ ግን ሁለተኛ ሯጭ ነኝ" ለዋሚ ቢራቱ ያለውን ፍቅር ክብር እና አድናቆት ሲገልጽ። “ለምወዳት አገሬ ኢትዮጵያ እና ሕዝቧ የሺህ ዓመት መኩሪያ እና መከበሪያ ታሪክ በእግዚአብሔር ፈቃድ ስለሠራሁ ከእንግዲህ በኋላ የምመኘው ነገር የለም።” እኛስ ኢትዮጵያውያን ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ምን አደረግንላት?(ተርጓሚው) የአበበ ቢቂላ የክብር መታወሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ አባ ኮራን ሰፈር የሚገኘው የቀድሞው የአሜሪካ ሕብረተሰብ ት/ቤት ስታዲየሙን በአበበ ስም ሰይሞታል አምስተርዳም - የአበበ ቢቂላ መንገድ አላት ሮማ አበበን የዘከረችው በሩጫ ብቻ ሳይሆን ከከተማዋ ፳፭ ኪሎ ማትር ርቀት ላይ በምትገኘዋ ላዲስፖሊ ከተማ የሚገኘውን አዲስ የእግር ድልድይና መንገድ በአበበ ቢቂላ ስም (ፖንቴ አበበ ቢቂላ) በመሰየም ነው፡፡ የሴኔጋል መዲና ዳካር በ፲፱፻፸፩ ዓ.ም. የመጀመሪያውን የአፍሪቃ አትሌቲክስ ውድድር አጋጣሚ በማድረግ ወደ “ዴምባ ዲዮፕ” ስታዲየም የሚያስገባውን መንገድ የአበበ ቢቂላ መንገድ ብላዋለች። የአበበ ቢቂላ የቶክዮ ድል “ቶክዮ ኦሊምፒያድ” በተባለ የትረካ ፊልም ላይ ተጨምሯል። ከዚሁ ፊልም የተወሰደ ጉራጅም በ፲፱፻፷፰ ዓ/ም በተሠራው “ማራቶን ማን” በተባለው ፊልም ላይ ይገኛል። “ቪብራም” የተባለ የአሜሪካ የጫማ ድርጅት በ፳፻፪ ዓ/ም “ፋይቭፊንገርስ ቢቂላ” () የተባለ ጫማ ገበያ ላይ አዋለ። ሮቢን ዊሊያምስ የተባለው አሜሪካዊ ቀልደኛ ‘የራስ ማጥፊያ መሳሪያዎች’ በተባለው ዝግጅቱ ላይ የአበበን በባዶ እግር መሮጥ ይጠቅሰዋል።
48333
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%80%E1%88%AB%E1%8A%95%E1%8B%AE%20%E1%88%98%E1%8B%B5%E1%8A%85%E1%8A%94%20%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D
ቀራንዮ መድኅኔ ዓለም
ደብረ ቀራንዮ መድኃኔአለም ቤተክርስቲያን ደብሩ ለመጀመርያ ጊዜ የተመሠረተው በንጉሥ ሣህለ ሥላሴ በ1826 ዓም ሲሆን ከአዲስ አበባ ቤተክርስቲያኖች በዕድሜ ትልቁ ነው። አሁን ያለውን ቤተክርስቲያን ያሠሩት ደግሞ አፄ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ናቸው።የደብረ ቀራንዮ መድኃኔዓለም ቤተክርስትያን ዳግማዊ ቀራንዮ ዘኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አንዱና ቀዳሚው የሆነው ይህ ደብር የተመሰረተው በ1826 ዓ/ም በንጉስ ሳህለስላሴ ሲሆነ አመሰራረቱም ንጉስ ሳህለ ስላሴ በሸዋ ግዛታቸው ውስጥ እየተዘዋወሩ አንድነትን ለማስተማር ባላቸው ጽኑ ዓላማ መሰረት ሰራዊታቸውን አስከትለው 1826 ዓ/ም ወደ ደቡብ ተጒዋዙ በዚህ ጉዙአቸው በወሊሶ በኩል አልፈው የጉራጌን ህዝብ ሀገር አስተማሩ ጉዞአቸውንም በማራዘም በአርሲ አካባቢ የሰሜኑን ክልል እነዲማር አድርገው በግራኝ ምክንያት ተለያይቶ የነበረውን ህዝብና ክልል አንድ ካደረጉ በኋላ ከጉዞአቸው ሲመለሱ ዛሬ ቀራንዮ ቀራንዮ መድኃኔዓለም ቤተክርስትያነ ከተመሰረተበት ቦታ ደርሰው ጥቂት ዕረፍት ቆይታ አደረጉ፡፡ በዚህም ጊዜ የእግዚአብሔር መንፈስ አመልክቷቸው በዚህ ቦታ እግዚአብሔር እንዲመለክበት በቦታውም ፅላተ መድኃኔዓለም ከእቲሳ መጥቶ በመረጡበት ቦታ እንዲተከል ትዕዛዝ ያስተላልፋሉ ታቦቱ በንጉሱ ትዕዛዝ መጥቶ በመረጡት በተዘጋጀለት መቃኞ ውስጥ ቢያርፍም ቦታው ደን ለበስ ስለነበረና ብዙ ኢአማንያን እንዲሁም ሽፍቶች ስለነበሩ መቃኞ ከአንድም ሶስት ጊዜ ሊቃጠል ችሎአል ሆኖም የንጉሱ አላማ ዕውቀትን ማበልጸግ ቤተክርስትያንን ማነጽ ስለነበር የሽፍቶቹን ኃይል በእግዚአብሔር አጋዥነት አሸንፈዋቸዋል ቤተክርስትያኑንም አጠገቡ ከሚገኘው አቃቂ ወንዝ ጋር በማጣመር አቃቂ መድኃዓለም ተብሎ ይጠራም ነበር የመድኃነኔዓለም ጽላት አመጣጥ በሚወሳበት ወቅት መምህር ተክለወልድና አባ ደጀን ተጠቃሽ ናቸው መምህር ተክለወልድ ከእቲሳ አምጥተው በዚህ ቦታበተሰራውመቃኞ ውስጥ እንዳስቀመጡት በአገልግሎታቸውም ወቅት ከባድ ፈተና እንዳጋጠማቸው ይነገራል በሌላ በኩል ደግሞ በሁለተኝነነት የጠቀስናቸው አባደጀን እንዳመጡት ይነገራል፡፡ከንጉስ ሳህለ ስላሴ ትዕዛዝ ተቀብለው ጽላቱም ከእቲሳ አስይዘውየላኳቸው አባ ዘወልደማርያም የተባሉ አባት እንደነበሩ ይታወሳል አባ ዘወልደማርያም በዚህም ቦታ ቦታ ሀገር በቀል እጽዋትን ተክለዋል አባ ደጀንም ከጽላቱ ጋር ድርሳነ ማህየዊ የተባለ በዚህቤተክርስትያን ብቻ የሚገኝ መጽሀፍ አምጥተዋል ደብሩ በዚህ አይነት ሁኔታ ከቀጠለ በኋላ 1899 ዓ/ም አጼ ምንሊክ ባወጁት አዋጅ የአብያተ ክርስትያናያ ምስረታና ዕደሳ መሰረት ቤተክርስትያኑ በሶስት አመት ውስጥ ተጠናቆ 1901 አጼው ባሰሩት አዲስ የሳር ክዳን ትልቅ ቤተክርስትያን ውስጥ ሊገባ ችሏል አጼ ምንሊክም በዚያው ዓመት በጃን ሜዳ መኳንንቱንና መሳፍንቱ ህዝቡ በተሰበሰበበት አቃቂ መድኃኔዓለም እንዳይባል እንዲህም ብሎ የጠራ ይቀጣል ከአሁን በኋላ ቀራንዮ መድኃኔዓለም ይባል እንጅ ብለው በአዋጅ ተናግረው አጸደቁ ቀራንዮ የሚለው ስያሜ ምንም እንኳን ለቤተመቅደሱ የተሰጠው ስያሜ ቢሆንም ለክልሉ ለአካባቢው እስከ አሁን ድረስ መጠሪያ በመሆን ያገለግላል፡፡ አፄ ምንሊክም ጌታችን ከተሰቀለበት ከኢየሩሳሌም ቀራንዮ አፈር በማስመጣት በግቢው ውስጥ ካስፈሰሱ ብኋላ ዳግማዊ ቀራንዮ ብለው መሰየማቸውን ታሪክ ይናገራል አዲሱን የሳር ክዳን ቤተክርስትያን ከንጉሱ ትዕዛዝ ተቀብለው ከነሰራተኞቻቸው ያሰሩት ኋላም የደብሩ የመጀመሪያ ገበዝ በመሆን ደብሩም ለብዙ አመታት የመሩት ደጃዝማች ወልደገብርኤል ነበሩ ደጃዝማች ወልደገብርኤል የቤተመንግሰቱንና የቤተክርስትያኑን ስራ በትጋት በመስራት ለቤተክርስትያኑ ታላቅ ሰው ነበሩ ኋላም ደጃዝማች ወልደገብርኤል የቤተመንግስቱ ስራ ፋታስላልሰጣቸው የደብሩን ቅርስና ሀብት ለህይወታቸው ሳይሳሱ ለጠበቁት ለቄሰገበዝ አስራት ሀብተሚካኤል አስረከቧቸው 1901 የተሰራው አዲሱ ቤተመቅደስ የምዕመናን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበዛበ መምጣቱ የተነሳና ለአገልግሎት አይመችም ነበር ይህንንም የተመለከቱት ንግስት ዘውዲቱ ሌላ ዘመናዊና ሰፊ ቤተክርስትያን ለማሰራት ያቅዳሉ ነገር ግን ሀሳባቸውን እውን ሳያደርጉ 1922 ዓ/ም ያርፋሉ ፡፡ ከዚህም በኋላ 1922 በዚያው ዓመት በግርማዊ ጃንሆይ እንደነገሱ የንግስት ዘውዲቱ ዕቅድና አላማ የነበረውና ታላቁን ቤተመቅደስ አሰሩ የቤተመቅደሱም ስራ 1922 ተጃምሮ 1925 በግርማዊ ጃንሆይ በነገሱ በሶስተኛ ዘመነ መንግስታቸው ተጠናቀቀ በዚሁ ዓመትም በታላቅ ድምቀት በአዲሱ ቤተክርስትያን በደመቀ ሁኔታ ተከበረ አሁን የሚገኘው ቤተክርስትያነ ግንባታው ተሰርቶ እስኪያልቅ ድረስ ደጃዝማች ወልደገብርኤል ለአፅማቸው ማረፊያ ባሰሩት ባለአንድ ፎቅ የቆርቆሮ ክዳን ቤት ውስጥ ነበር በዚህም ፅላቱ ሳለ ቅዳሴው በፎቁ ማህሌቱ በታች ይስተናገድ ነበር፡፡ አሁን የሚገኘው ህንጻ ቤተክርስትያን ምን ያህል ገንዘብ እንደፈጀ የሚገልጽ ሰነድ የለም ነገር ግን በግርማዊ ጃንሆይ በግል ገንዘባቸው እንዳሰሩት ታሪክ ይናገራል ህንጻውን የሰሩት ሁለት የጣልያን ዜግነት የነበራቸው በዚያም ዘመን በህንጻ ስራ ታዋቂ በነበሩት ሙሴ ፓፓጀማና ኩኞስ ነበሩ በደብሩም ብዙ የተለያዩ ቅርሶች የሚገኙ ሲሆን በአሁኑም ሰዓት ከ350 ዓመት በላይ ያስቆጠሩ እጽዋት ሲገኙ ከዚህም በተጨማሪም ደብሩ ከተለያዩ ነገስታት የተሰጡትና በአንዳንድ አባቶች የተሰጡት ጥንታዊ የብርሃና መጽሃፍት አልባሳት የተለያዩ ውድ የወርቅ የብር የነሀስ መስቀሎች ጥላዎች በንግስት ቪክቶርያ ለሳህለ ስላሴ የተሰጡ የተለያዩ ውድ ስጦታዎችና የባላብዙ ታሪከና ቅርስ ባለቤት ደብር ነው ደብረ ቀራንዮ በአጥቢያው ለሚገኙ ደብራትና አብያተክርስትያናት ብሎም ለአዲስ አበባ ከተማ መመስረት መነሻም ነው፡፡ የኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት አዲስ አበባ
51209
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%AD%E1%8D%8B%E1%89%B5%20%E1%8B%88%E1%88%8B%E1%88%B5%E1%88%9B%20%E1%88%A5%E1%88%AD%E1%8B%88%20%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%B5%E1%89%B5
የይፋት ወላስማ ሥርወ መንግስት
ሐረር ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ በአምስት መቶ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተማ ናት። በዘመኑ የአስተዳደር መዋቅር የሃረሪ ክልል ዋና ከተማ ናት። በ1,885 ሜትር ከፍታ ላይ፣ የወይና ደጋ የአይር ጠባይ በተላበሰ ቦታ ላይ አርፋለች። በምድር መጋጠሚያ ውቅር 9°19′ ሰሜን ኬክሮስ እና 42°07′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ናት። በ1987 ዓመተ ምህረቱ የህዝብ ቆጠራ መሰረት ሐረር 76,378 ሕዝብ ይኖርባታል። ሐረር ለዘመናት ከፍተኛ የንግድ ማዕከል ሆና ስትኖር ከመሃል አገር፣ ከአፍሪካ ቀንድ እና ከአረብ አገራት ጋር በንግድ መንገዶች ስትገናኝ ከቀሪው አለም ጋር ደግሞ በቀይ ባህር ወደቦች አማካኝነት ትገናኝ ነበር። የሐረር ጀጎል ግንብ ከ1998 ጀምሮ በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ይገኛል። በእስልምና ሃይማኖት "4ኛዋ የተቀደሰች ቦታ" ተብላም ስትታወቅ 82 መስጊዶች፤ አንዳንዶቹ ከ10ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበሩ፤ እንዲሁም 102 የቀብር ቦታዎች አሉዋት። ዋግነር፣ ዘ ዲክሽነሪ ኦፍ ኢትዮጵያን ባዮግራፊ፣ ገጽ 1፣ ቮልዩም 1፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናት ኢንስቲትዩት፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ።27 መድሃኒያለምና ሙስሊሟ ሀረር እኛ እርስበእርስ ስንናከስ ወይናደጋማዋ ሐረር እርስ በእርሱ ከሚበላላው ጅብ ጋር ሳይቀር ተግባብቶ የሚኖርባት ከተማ ናት፡፡ ሐረር ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ በአምስት መቶ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተማ ናት። በዘመኑ የአስተዳደር መዋቅር የሃረሪ ክልል ዋና ከተማ ናት። በ1,885 ሜትር ከፍታ ላይ፣ የወይና ደጋ የአይር ጠባይ በተላበሰ ቦታ ላይ አርፋለች። በ1987 ዓመተ ምህረቱ የህዝብ ቆጠራ መሰረት ሐረር 76,378 ሕዝብ ይኖርባታል። ሐረር ለዘመናት ከፍተኛ የንግድ ማዕከል ሆና ስትኖር ከመሃል አገር፣ ከአፍሪካ ቀንድ እና ከአረብ አገራት ጋር በንግድ መንገዶች ስትገናኝ ከቀሪው አለም ጋር ደግሞ በቀይ ባህር ወደቦች አማካኝነት ትገናኝ ነበር። የሐረር ጀጎል ግንብ ከ1998 ጀምሮ በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ይገኛል። በእስልምና ሃይማኖት "4ኛዋ የተቀደሰች ቦታ" ተብላም ስትታወቅ 82 መስጊዶች፤ አንዳንዶቹ ከ10ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበሩ፤ እንዲሁም 102 የቀብር ቦታዎች አሉዋት ኣው-ባዲር፣ አው-ባድር፣ አባዲር፦ (ዑመር አርሪዳ) (በግምት ወደ ፲፫ ኛው ክ/ዘ)፦ በ ፲፫ ኛው ክ/ዘመን ውስጥ የተፃፈውና ስለ ሐረር ጥንታዊ አፈታሪካዊ ታሪክ የሚዘክረው 'ፋዝ መዲናት ሐረር' የተባለው ያልታተመ መጽሐፍ እንደሚገልጸው አባድር (ዑመር አርሪዳ) እጅግ ከተከበሩት የሐረር ሼኽዎች ውስጥ አንዱና ዋንኛው ናቸው። በዚሁ መጽሓፍ አገላለጽ መሠረት፡ አባድር ከሌሎች በርካታ ሼኾች ጋር በመሆን ከሂጃዝ በ፮፻፩፪ ሂጅሪያ (1216 እ.ኤ.አ) ተነስተው ሐረር ከገቡ በኋላ በአካባቢው የጎሣ እና ኃይማኖት መሪዎች ተመርጠው ዒማም ሆኑ። የሀረር ህዝብ ታሪክ ፣ ባህል እና ማንነት ከሀረር ከተማ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው፡፡ ሀረሪዎች በረዥም ዘመን የስልጣኔ ታሪካቸው ያፈሯቸው ተንቀሳቃሽ እና የማይንቀሳቀሱ እንዲሁም የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ በርካታ ቁሳዊ እና መንፈሳዊ ቅርሶች ባለቤት ናቸው፡፡ ከእነዚህ ቅርሶች መካከልም የከተማዋ ልዩ መለያ ምልክት ከመሆንም አልፎ እ.ኤ.አ በ2006 በአለም ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል ግንብ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡በግንቡ ውስጥም ከ82 በላይ መስኪዶች እና በርከት ያሉ የሀረሪ ባህላዊ ቤቶች ይገኛሉ፡፡ ሀረር ከፍተኛ የስልጣኔ እድገት ደረጃ ላይ በደረሰችበት በ16ኛው ክፍለ ዘመንም በምስራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርት እና የንግድ ማዕከል ሆናም አገልግላለች፡፡ ይህም የበርካታ ታሪካዊ እና ባህላዊ ቅርሶች ባለቤት እንድትሆን አድርጓታል፡፡ የጀጎል ግንብ የሀረሪ ህዝብ የኪነ ህንፃ ችሎታውን የሚያስመሰክር የታሪክ እና የጥበብ መዘክር ነው፡፡ ይህ ግንብ በ16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በአሚር ኑርአማካኝነት እንደተገነባም ይነገራል፡፡ሐረር እንኳን ዛሬ ቀን ዘምኖ ትናንትናም ቢሆን ስንቱ ባህር አቋርጦ የከተመባት፤ ስንቱ ቅጥሯ ገብቶ ለትውልድ የተረፈ ትዝታ ያስቀመጠባት የውበትና የጥበብ መዲና ናት፡፡ የኢትዮጵያ ኢስላማዊ ኪነ ህንጻና ባህል ማንምም ሳይመስል፤ ሃይማኖታዊ መሰረቱን ሳይጥል የነገሰባት መዲና፤ ያው ጀጉልን መዞር ነው፡፡ በየቦታው መቆም፡፡ በየቦታው ማየት….በየቦታው መደምም…ጀጉልን ገብተው ይኖሯታል እንጂ አይጽፏትም፡፡ ጀጉልን ውስጥ ለውስጥ ከጀመርናት መቆሚያ የለውምና ከጊዜ እየተሻማን በበራፍ በበራፍ እንለፍ ሀረር ከቅርስነት ባሻገር እ.ኤ.አ በ2003/4 በሰላም ፣ በመቻቻል ፣ በመፈቃቀር እና በልማት ከተማነት አለም አቀፍ ሽልማት እና እውቅናን አግኝታለች፡፡ ይህም የተለያየ እምነት ፣ ባህል እና ቋንቋ ያላቸው ህዝቦች ለዘመናት በሰላም እና በፍቅር የኖሩባት እና ዛሬም የሚኖሩባት ከተማ በመሆኗ የተቀዳጀችው ክብር እና እውቅና ነው፡፡ ሀረር ዩኔስኮ ዕውቅናን የቸራት በዓለም ቅርስ ብቻ አይደለም፡፡ ከኪነ ህንጻዎቿ ልቀት ባለፈ ህያው ሆኖ ዛሬም እየኖረ ባለው ሰዋዊ እሴት ምርጥ ነሽ ብሏታል፡፡ ፈረስ መጋላ ይሉታል ሀረሮች ከፊት ለፊቱ የአሚር አብዱላሂ አደራሽ አለ፡፡ ሀረር መድኃኒዓለም በር ላይ፡፡ ጀጉል በሀገራችን በርካታ መስጂዶች የሚገኙባት ከተማ ናት፡፡ በግንብ የተከበበው ቅጥሯ ውስጥ የሚገኘው የመድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ከተማዋ ዩኔስኮ የተባለውን ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ስባ የመቻቻልና የሰላም ተምሳሌት የተባለ እውቅና እንድትቀበል አድርጓታል፡፡ በረዣዥም የመስጂድ ሚናራዎች የታጀበው የሀረር መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን በ27 በድምቀት ይነግሳል፡፡ የጀጉል መንገዶች ከጁምአ ዕለት ድምቀት በተጨማሪ በተለየ 27 ነጠላ ለባሾች ከየአሉበት ወደ ቅጥሯ የሚገቡበት ሌላ ትዕይንት ያስተናግዳሉ፡፡ ምዕተ ዓመት የተሻገረው ይህ ቤተ ክርስቲያን ንጉሰ ነገስቱ አጼ ምኒሊክ ኢትዮጵያን በሚመሩበት ራስ መኮንን የሀረርጌ ገዢ በነበሩበት ዘመን የታነጸ ነው፡፡ ያሰሩት ራስ መኮንን ናቸው፡፡ ክቧ ቤተክርስቲያን ውብ ናት፡፡ ዛፎቿ ጥቂት ናቸው ነገር ግን ከግቢዋ ስፋት አኳያ ጥሩ አድርገው አጅበዋታል፡፡ ዛሬ ከሁሉም አቅጣጫ ሰው ወደ ጀጉል እያመራ ነው፡፡ ሐረር ወይም ዱክ በር ከሚባለው በሗላ በተሽከርካሪ ማለፍ አይቻልም፡፡ ይሄ አጋጣሚ ሌላ ትዕይንት ፈጥሯል፡፡ ነጠላ ያጣፉ ጧፍ የያዙናና ሂጃብ የለበሱ መንገደኞች በጋራ እየተሳሳቁ መንገዱን ሞልተውታል፡፡ እጣንና ጧፍ የዘረጉ ነዋየ ቅድሳት የሚሸጡ መንገዱን ዳርና ዳር ይዘውታል፡፡ የኔ ቢጤዎች ስለ መድሐኒያለም እያሉ ይለምናሉ፡፡ መላው የሐረር ህዝብ አቦ እንወድሃለን! ሀገርን ለማጥፋት ለመበታተን ቀን ከሌት የሚተጋ መንግስት መሳይ ጊዜ አንግሶት እየገዛን ቢሆንም አንተም እንደኛው በቁምም በስጋም እየሞትክ ቢሆንም አብሽሩ እኛ አንድ ሆነን ሽ የሆንን ኢትዮጵያውያንነን! የመጣብንን ሰይጣናዊ የጥፋት ውሃ ከአምላክ ጋር አንድ ከሆን እናከሽፈዋለን!!! "ኢትዮጵያ" ማለት መንፈስ ነው፣ እሱም "አንድነት" ማለት ነው፡፡ ኢትዮጵያ የፍቅር ሀገር የመቻቻል ምድር ለዘላለም ትንሩልን!!!!
9597
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%8A%A8
ተረት ከ
ከህጻን ጋር አትብላ ድንች ድንቹን ይለቅምብሀል ከልብ ካለቀሱ ነጻ ምርጫ ይካሄዳል ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም ከልጅ አትጫወት ንፍጥ ይለቀልቅሀል ከልጅ ጋር አትጫወት ይወጋሀል በእንጨት ከልጅ ጋር አትጫወት አይንህን ያወጣዋል በእንጨት ከመሞት መሰንበት ከመሸም ጋዝ አለ ከመቶ ሀምሳ ዳዊት የልብ ቅንነት ከመናገር ደጃዝማችነት ይቀራል ከመደብደብ ይሻላል ማደብ ከማትረባ ጉልበት በህግ አምላክ ይሻላል ከማን ጋር እንደምትውል ንገረኝ አንተ ማን እንደሆንክ እነግርሀለሁ ከማያቁት ወዳጅ የሚያቁት ጠላት ይሻላል ከማያውቁት መልአክ የሚያውቁት ስይጣን ይሻላል ከማይረባ ቁርስ የጠዋት ጸሃይ ይሻላል ከሜዳ ወዲያ ፈረስ ካርባ ወዲያ ቄስ ከምኔው ሞትሽና አፈር አፈር ሸተትሽ ከምድር ውስጥ ልቃቂት አይወጣም ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል ከራስ በላይ ነፋስ ከርሞ ጥጃ አድሮ ቃሪያ ታጥቦ ጭቃ ከሰው ቀለብላባ ከመሬት ገብጋባ ከሰው ክፉ ደባል ከጭነት ክፉ አላል ከሰጠሽ ስጪኝ ካልፈለግሽ ፈግጪው ተቀምጠሽበት ከምትደፈጥጪው ከቁራ ጋር የዋለች እርግብ ላባዋ ባይጠቁርም ውስጧ ጠቁሮ ትመለሳለች ከቁርባን ውጭ ክርስትና ከቁንጫ መላላጫ ያወጣል ከበሉ አይቀር እንክት ከገሙ አይቀር ጥንብት ከበሮ በሰው ላይ ታምሪያለሽ ሲይዙሽ ታደናግሪያለሽ ከበሮ በሰው እጅ ታምር ሲይዙዋት ታደናገር ከባለቤቱ (በላይ) ያወቀ ቡዳ ነው ከባልሽ ባሌ ይበልጣል ማይክሮዌቭ አበድሪኝ ከባልሽ ባሌ ይበልጣል ሽሮ አበድሪኝ ከባልሽ ጋር ሁኚ ቢሏት የተለመነች መሰላት ከባቄላ አይጠፋም ዲቃላ ከባእድ የጠጡት ኮሶ ይወጣል ደም ጎርሶ ከተኛ አንበሳ ዞርዞር ያለ ቀበሮ ይሻለል ከነገረኛ ሰው ስንቅ አይደባልቁም ከነገሩ ጾም እደሩ ከነገሩ ጾም ይደሩ ከኑግ ጋር የተገኘ ሰሊጥ በጣም ይጣፍጣል ከናትዋ ልጅዋ ትብስ ባቄላ አሮባት እጅዋን ትልስ ከኔ ከወሰድሽው ተቀምጠሽ ልበሽው ከወንድም ደረቅ ከወጥ መረቅ ከዘመድ አጠገብ የተዳረች ልጅ ትዳር አትይዝም ከጠጅ ወዲያ አስካሪ ከባለቤት ወዲያ መስካሪ ከኛ ወዲያ ጎራሽ እህል አበላሽ ከኛ ወዲያ ፉጨት አፍ ለማሞጥሞጥ ከአህያ የዋለች ሳር መጋጥ ትማራለች ከአህያ የዋለች ጊደር ለከፋ ጀመረች ከአህያ የዋለች ጊደር ፈስ ተምራ መጣች ከአህያ የዋለች ጊደር ፈስ ተምራ ትመጣለች ከአማት መኖር መጋማት ከአባቱ ፊት የሚናገር አፍ ለምጽ ይሆናል ከአብሮ አደግህ ጋር አብረህ አትሰደድ ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ዘላለም ሲያለቅስ ይኖራል ከአፈርኩ አይመልሰኝ ከአፍ የወጣ አፋፍ ከአፍ የወጣ ቃል ከእጅ የወደቀ እንቁላል ከዘላለም ፈስ ያንድ ቀን ቅዘን ይሻላል ከዝንጀሮ ቆንጆ ምን ይመራርጡ ከዝንጀሮ ቆንጆ አንዷ ውድድሩን አሸነፈች ከዳቦ የተገኘ ወጥ አብረህ ግመጥ ከገሙ አይቀር መጠንባት ነው ከገሙ አይቀር ቅርንት ነው ከጦጣ የዋለ ጉሬዛ እህል ፈጅቶ ገባ ከፈሳም ቤት ቅዘናም ገባበት ከፍትፍቱ አጉርሱኝ ከፍትፍቱ አጉርሱኝ ከመረቁ ጾመኛ ነኝ ከፍትፍቱ ፊቱ ኩላሊት ካላየ አይን አያይም ካለመናገር ደጃዝማችነት ይቀራል ካለቀ መቆጠብ ከመሽ መንጠብጠብ ካለቀሰ አይቀር በደንብ ምታው ካለቃና ከጠገራ ፊት ዞር በል ካለ ፈጣሪ አሟጠሽ ጋግሪ ካላት ከፍላ ኑ ቅመሱ የምትል ናት ተቃመሱ ካልቀበጡ አይዘሉ ካልዘለሉ አይሰበሩ ካልበሉበት ደጀ ሰላም ከበሉበት ቤት ነው ካልታዘልኩ አላምንም አለች ሙሽራ ካልደፈረሰ አይጠራም ካልደፈረሰ አይጠራም ካልጠራ አይጠጣም ካልፈላ አይገነፍል ካልተጣደ አይበስል ካረገዘች ክታብ ያዘች ፈሷን ፈስታ ቂጧን ያዘች ካረጁ አይበጁ ካረጁ አይባጁ ካንቺ የተሻለች ሴት ባላገኝ ሌላ እንዳታገቢ ጠብቂኝ ካንድ ልጃገረድ ይገኛል ሁለት ዘመድ ካንዠት ካለቀሱ እንባ አይገድም ካያያዝ ይቀደዳል ካነጋገር ይፈረዳል ካገሩ የወጣ አገሩ እስኪመለስ ቢጭኑት አህያ ቢጋልቡት ፈረስ ኳስ ለራስሽ ስተይ ጎል ግቢ አለዚያ ፎሪ ብለው ይጠልዙሻል ካንጀት በላይ ፍቅር እያደር ያቃቅር ካንጀት ነው ካንገት ካዋቂ ጠያቂ ክረምት ከጭቃ በጋ ከግጫ ክረምትና በጋ ቆላና ደጋ ክረምትና ኮሶ ቤት በምሰሶ ክረምትና ወላድ ሲጠሉት ያከብራል ክረምትን የፈጀ በጋ እዳውን የፈጀ ዜጋ ክፉ ሴት በኑሮ ላይ ከባድ ሬሳ ትሆናለች ክፉ ሴት ጠዋት ወተት ማታ ሬት ክፉ ባይኖር የመልካም ዋጋ አይታወቅም
13074
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%8B%8B%E1%88%85%E1%8B%B6
ተዋህዶ
ተዋውጦ ( በዚህ እምነት ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር በነበረበት ጊዜ አንደ እና አንድ ብቻ ተፈጥሮ /ባሕርይ ነበረው ። ይህም ተፈጥሮ /ባሕርይ ሥጋ የሌለበት መለኮት ነበር የሚል ነው ። ሥጋ እንኳ ቢኖረው ፣ ባሕር ውስጥ ሟሙቶ እንደሚጠፋ አንድ ማንኪያ ጨው ፣ የክርስቶስ ሥጋም እንዲሁ በመለኮቱ ባሕር ሟሙቶ ጠፍቷል ይላሉ ። ተዋሕዶ ( 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3:16 እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ። ስንዴ እና ባቄላ እንደሚቀላቀሉት - ያለመቀላቀል፣ ኦክስጅንና ሀይድሮጅን ሲዋሐዱ ጸባያቸው እንድሚቀያየር - ያለመቀያየር፣ የተጋቡ ሰዎች እንደሚለያዩ - ለአንዳች ቅፅበት እንኳን ያለመለያየት፣ መለኮታዊ እና ሥጋዊ ተፈጥሮ በኢየሱስ ክርስቶስ አንድ ሆነ። ቅድስት ድንግል ማርያም ሰው ወይም አምላክ ወይም ደግሞ ኹለት ተፈጥሮ ያለው ሰው እና አምላክ ሳይሆን የወለደችው፣ የሰው እና የአምላክ ውሕደት፣ አንድ ተፈጥሮን፣ እየሱስ ክርስቶስን ነው። በዕለት ተዕለት ኑሯችን ይህን ዓይነት ኹኔታ የምናየው የአእምሮ እና የአንጎልን ውሕደት ልብ ስንል ነው። በዚህ ንግግር አእምሮ ማለት የሐሳባችን ስብስብ ሲሆን የማይጨበጥ እና የማይዳሰስ ነው፤ አንጎል /ጭንቅላት ማለት ደግሞ ተጨባጩ የማሰቢያ ክፍል ማለት ነው። የኹለቱ ውሕደት እንግዲህ ያለመቀላቀል፣ያለመለዋወጥ እና ያለመለያየት የሚሉትን ሐሳቦች ያንጸባርቃል። ተከፋፍሎ ( በዚህ እምነት እየሱስ ክርስቶስ ሁለት ተፍጥሮ አለው ተብሎ ይነገራል ፦ ስጋው እና መለኮታዊ ። እነዚህ 2 ተፈጥሮወች በአንድ ተፈጥሮ (እየሱስ ክርስቶስ ) ይኑሩ እንጂ አልተዋሀዱም ተብሎ ይታመናል ። የሰው ልጅ ፣ በጊዜና በቦታ የተወሰነ ሲሆን ፣ ስጋን ለመስዋእት ማቅረብ ከዘመን -ዘመን የሚሻገር የሐጥያት ስርየት አያመጣም ። እየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሲሞት ፣ ተፈጥሮውን ከፋፍሎ ፣ ስጋው ብቻ ሞተ ማለት ፣ ዮሐንስ 3:16 እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። የሚለውን ፉርሽ ያደርጋል ። በመስቀል ላይ የሞተው እየሱስ ክርስቶስ ፣ ተዋህዶ ወይንም አንድ ተፈጥሮ ነው ። የመለኮት ተፈጥሮ እንግዲህ ሞትንና መንገላታትን ባያውቅም ከስውነት ጋር ባለው ውህደት ግን አብሮ ተንገላቷል ማለት ነው ። ይህን ሀሳብ ለመረዳት የሚነድ ብረትን ያስታውሷል ። እሳት እና ብረት ያለመቀላቅል ሲዋሀዱ ፣ አንጥረኛ ብረትን በመዶሻ ሲመታ ፣ የመዶሻው ምት እሳት ላይ ምንም ሀይል ባይሆረውም ፣ እሳት እራሱ ከብረት ጋር ስለተዋሀደ ፣ ብረት ሲጣመም ፣ እንዲሁ እሳትም ይጣመማል ። ሉቃስ በሐዋርያት ስራ 20:28 በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ሲል እዚህ ላይ መርዳት ያለብን መለኮት በራሱ ደም የለውም ። ነገር ግን የመለኮት ተፈጥሮ እና የስው ተፈጥሮ ውህደትን ለማመልከት ያንዱን ባህርይ በሌላው ስም መጥቀስ ተችሏል ። እየሱስ ክርስቶስ በስጋ ከሞተ ፣ ለምን ወደዚህ አለም መምጣትስ አስፈለገው ። የስጋ መስዋእት ለዘላለም ስርእየት በቂ ከሆነ አንድ የተመረጠ ሰው ለዚህ ተግባር ማዋል ይቻል ነበር ፡ ስለማይቻል 'የእግዚአብሔር ልጅ ' 'ከሰው ልጅ ' ጋር ያለመቀላቀል ፣ ያለመለዋወጥ ፣ ያለመለያየት ተዋሐደ ። የዚህም ውህደት ውጤት ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ ፣ ከትውልድ እስከ ትውልድ የሚሸጋገር ድህነትን ለሰው ልጅ አተረፈ ። ዮሐንስ 3:16 እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። 1ቆሮ 2:8 አውቀውስ ቢሆኑ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉትም ነበር፤ ቅዱስ ጳውሎስ እዚህ ላይ «የእየሱስ ክርስቶስን ስጋ» አላለም ፣ የልቁኑ «የክብር ጌታ» በማለት ውሕደቱን በግልጽ አስቀምጧል ። ቅዱስ ጴጥሮስ በሐዋርያት ስራ 3:14-15 እናንተ ግን ቅዱሱን ጻድቁንም ክዳችሁ ነፍሰ ገዳዩን ሰው ይሰጣችሁ ዘንድ ለመናችሁ፥ የሕይወትንም ራስ ገደላችሁት፤ «የሕይወት እራስ» እንግዲህ የመለኮትነትን ባህርይ የሚያሳይ ሐረግ ነው ። እብራውያን 2:10 ብዙ ልጆችን ወደ ክብር ሲያመጣ የመዳናቸውን ራስ በመከራ ይፈጽም ዘንድ፥ ከእርሱ የተነሣ ሁሉ በእርሱም ሁሉ ለሆነ፥ ለእርሱ ተገብቶታልና። በመከራ ላይ እያለ እንኳን መለኮታዊ ባህርዩን (በእርሱ ሁሉ የሆነ ) አልረሳም ። ራእይ 1:17-18 ባየሁትም ጊዜ እንደ ሞተ ሰው ሆኜ ከእግሩ በታች ወደቅሁ። ቀኝ እጁንም ጫነብኝ እንዲህም አለኝ። አትፍራ፤ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ፥ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ። እዚህ ላይ ፣ እየሱስ ክርስቶስ እራሱ ፣ ስለስቅለቱ ሲናገር እራሱን በመከፋፈል በስጋ ሞትኩ አላለም ፣ ይልቁኑ ፊተኛውና መጨረሻው ሲሆን ፣ ለዘላለምም ሕያው ሲሆን ሳለ ፣ በመስቀል ላይ መሞቱን ያለክፍፍል ፣ በተዋህዶ አስረድቷል ። እንግዲህ አዲስ ኪዳን እንደሚያስረዳው ፣ በመስቀል ላይ የሞተው ፣ በሞቱም ከዘላለም እስከ ዘላለም የድህነት ጥላን የዘረጋልን «ስጋ» ብቻ ሳይሆን ፣ የ«ክብር ጌታ»፣ የ«ሕይወት እራስ»፣ «በእርሱ ሁሉ የሆነ»፣ 'ፊተኛው እና ሁዋለኛው ' የተባለው «ተዋህዶው» እየሱስ ክርስቶስ ነው ። የዮሐንስ ወንጌል 20:19 ያም ቀን እርሱም ከሳምንቱ ፊተኛው በመሸ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ተሰብስበው በነበሩበት፥ አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹ ተዘግተው ሳሉ፥ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው። ይህንም ብሎ እጆቹንም ጎኑንም አሳያቸው። ደቀ መዛሙርቱም ጌታን ባዩ ጊዜ ደስ አላቸው። ክርስቶስ በስጋው ነው በተዘጋ በር ያለፈው ወይንስ በመለኮት ነው ያለፈው ። በመለኮት ካለፈ እንዴት በስጋ ታያቸው ? በስጋስ እንዴት በተዘጋ በር አለፈ ? ይልቁኑ ፣ ከሞት የተነሳው ፣ ወልድ ዋህድ በተዘጋ በር አለፈ በአይንም ታየ ፡ ተገለጠም ። የቅዳሴ መጽሐፍ ስለእየሱስ ክርስቶስ ሞት እና መነሳት የሚናገረውን ጠቅሰን እንደምድም ፦ ነፍስና ስጋው ቢላቀቁም ፣ መለኮቱ ግን ከስጋውም ከነፍሱም ጋር ነበረች ። ነፍሱም ከመለኮቱ ጋር ሆና ለስብከትወደ ገሀነም ወረደች ፣ በእምነት ለሞቱትም የገነትን በር ከፈተች ። ነገር ግን ከመለኮት ጋር የተዋሀደው ስጋው በመቃብር ነበር ። በሶስተኛው ቀን ጌታ ሞትን ድል ነሳ ፣ ነፍሱም ከስጋው ጋር ተመልሳ ተዋሀደች ፣ መለኮት ግን ምንጊዜም አልተለየም ፣ ስለዚህም የዘላለም ድነት ሆነ ። አሜን ለዘለአለም።
49260
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%8B%E1%88%9A%20%E1%89%A2%E1%88%AB%E1%89%B1
ዋሚ ቢራቱ
ለ100 አመታት- ሩጫ እና ዋሚ ቢራቱ ዳግም ከበደ በሸራተን አዲስ ሆቴል እኔና የስራ ባልደረባዬ ተገኝተናል። በዚያ የተገኘንበት ምክንያት «የሩጫ ትራኩ» ጀግና አትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ ነበሩ። እርሳቸውም መልካም ስብእና እና ጠንካራ ተክለ ሰውነት ተላብሰው እንደኛው በዚያ ይገኛሉ። የዝግጅቱ አስተናባሪዎች አትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚን በህይወት እያሉ ሀገራቸው እና ለህዝባቸው ላደረጉት ሁሉ ለማመስገን ሰፊ ስራዎችን እየሰሩ ነው። ጥር 11 ለሚውለው ልደታቸው በርካታ ስራዎች እያከናወኑ ነው። የኛም እዛው መገኘት ስለ ልደት አከባበራቸው ሁኔታ መግለጫ ለመከታተል ነበር። ፍፁም ጠንካራ ተክለ ሰውነት፣ማራኪ ትህትና እና አስገራሚ እንቅስቃሴያቸውን በቦታው ተገኝቶ ለተመለከተ እድሜያቸውን ይጠራጠራል። ጠጋ ብሎ ሰላም ላላቸው ከመቀመጫቸው ተነስተው ጉንጫቸውን በመሳም «የኔን እድሜ ይስጣችሁ ተባረኩ» ይላሉ። ልጃቸው ጃጋማ ዋሚም አጠገባቸው ቆሞ «ተዉት ይነሳና ሰላም ይበላችሁ። በዚህ እድሜው እኔ የማልሰራውን ጅምናስቲክ ነው የሚሰራው። ጠንካራ ነው» በማለት ከመቀመጫቸው ተነስተው ሰላምታ ሲሰጡ የሚሳቀቁትን እንግዶች ያበረታታል። ሁኔታው እጅግ የሚያስገርም እና ደስ የሚል ነበር። ይህ ከሆነ አንድ ቀን አልፏል። በእለቱ የአትሌት ዋሚን ልደት የፎቶ አውደ ርእይ፣ የዶክመንተሪ ፊልም፣ በተወለዱበት ቦታ የሩጫ ውድድር እንዲሁም የተለያዩ ዝግጅቶችን በማድረግ በደማቅ ስነ ስርአት በተከታታይ ጊዜ እንደሚከበር ተረድተን ተለያይተናል። የልደት በአሉ ከዚያን ቀን ጀምሮ መከበር ይጀምር ነበር። በቀጣዩ ቀን ከቤት ተነስቼ ወደ ስራ እየሄድኩ ነው። ትናንት በአትሌት ዋሚ የልደት ዝግጅት ላይ የነበሩትን ሁነቶች እያስታወስኩ የትራፊክ መጨናነቁን እየሸወድኩት ነበር። የነበርኩበት የታክሲ ሹፌር ሙዚቃውን ዘግቶ ራዲዮኑን ከፈተ። አጋጣሚ ሆኖ ዝግጅቱ አንድ የስፖርት ፕሮግራም ላይ ነበር። ይዞት የቀረበው ዜና ግን የሚያስደነግጥ ነበር። «ማርሽ ቀያሪው አትሌት ሻለቃ ምሩፅ ይፍጠር ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል። ጀግናው አትሌት ብዙ የሰራ ግን ያልተዘመረለት ነበር» ይላል። እውነትም ሁኔታው እጅግ አሳዛኝ እና የሚያስቆጭ አይነት ነበር። ትናንት የአትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱን ስለማክበር እያወራን በነጋታው ተመሳሳይ ጀግናችንን አጣነው። ሁኔታው እጅግ የሚያሳዝንም የሚያስገርምም ነበር የሆነብኝ። በራዲዮው ላይ የሚያወሩት ሁለት የስፖርት ጋዜጠኞች ደግሞ «ኢትዮጵያን በአለም አቀፍ መድረክ ላይ በክብር ባንዲራዋን ያውለበለቡትን ጀግኖቻችንን በሚገባ ሳናከብር እና ሳናመሰግን መቅረታችን የሚያስቆጭ ነው» በማለት አበክረው ይናገራሉ። ሀሳባቸው ገዢ እና ትክክል ነበር። ነገር ግን አንድ ሌላ ሀሳብ ከፊት ለፊቴ ተደቅኖ ይሞግተኝ ጀመር። እነዚህ ታዋቂ የስፖረት ጋዜጠኞች ትናንት አትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱን ለማክበር እና ለማመስገን በተጀመረው ዝግጅት ላይ አልነበሩም። ስለ ሁኔታውም አልዘገቡም። ታዲያ ዛሬ የአትሌት ሻለቃ ምሩፅ ይፍጠር ሞት እጅግ እንዳንገበገባቸው እየተቀባበሉ ያወራሉ። መቼም ሞት አይቀርም ሁሉም ወደዚያው ነው። ሆኖም አፋችን ከተግባራችን ቢቀድም የተሻለ ይሆናል። ማዘን ባይከለከልም አላግባብ ቁጭት ማስመሰል ይሆናል። ከነዚህ ጋዜጠኞች ጋር የተቃርኖ ስሜቴ እንዲህ እያለ ቀጠለ። አትሌት ሻለቃ ምሩፅ ይፍጠርን ብናጣውን ሌላ ተመሳሳይ ማመስገን እና ማክበር ያለብን ጀግና በእጃችን አሉ «አትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ»፤ ይህ ለሁላችንም ሁለተኛ እድል ነው። ሌላ የሚኖረን አይመስለኝም። አትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ ማናቸው አትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ የተወለዱት በ1909 ዓ.ም በቀድመሞው ሸዋ ከፍለ አገር በመናገሻ አውራጃ በሱሉልታ ወረዳ በአካኮና መናበቹ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነው። ፓስፖርታቸው ላይ የተመዘገበው የአድሜ መረጃ እና ሌሎች ሰነዶች እንደሚናገሩት ከሆነ ጥር 11 ድፍን 100 አመት ይሞላቸዋል። በሩጫ መድረክ ላይ የነገሱትን ዋሚ ቢራቱ ወደዚህች ምደር ያመጧቸው እናታቸው ወይዘሮ ወርቄ አያና እና አባታቸው ቢራቱ በራቄ ናቸው። ዋሚ ጠንከር እያሉ ሲመጡ በመንደራቸው ላይ ቤተሰባቸውን ከብት በመጠበቅ እንዲሁም አንዳንድ የእርሻ ስራዎችን በማከናወን ይረዱ ነበር። ተሮጦ ዝነኛ እንደሚኮን እንዲሁም ሰዎችን ሌሎች ተፎካካሪዎችን መብለጥ እንደሚችሉ ያወቁት ባጋጣሚ ነበር። በሩጫ አገር ማስጠራት እንደሚቻልም እንደዚሁ። አጋጣሚውን የፈጠሩት ደግሞ እናታቸው ናቸው። ወይዘሮ ወርቄ አንዳንድ ነገሮች ለመሸማመት ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ። አስፈላጊውን ሁሉ ካከናወኑ በኋላም ወደ ቀዬአቸው ይመለሳሉ። ልጅ ዋሚ ደግሞ እናታቸው ሸክፈው የመጡትን እቃ ተቀብለው ወደ ቤት ይገባሉ። በዚህ እቃ ተጠቅልሎበት የመጣ ጋዜጣ እጃቸው ላይ ይገባል። ጋዜጣው የአንድ ሯጭ ምስልን ይዟል። ዋሚ ደግሞ በመንደራቸው ጋራ ተራራውን፣ ቁልቁለት ዳገቱን በሩጫ ሲቦርቁ ነው የሚውሉት። ሩጫ ስፖርት መሆኑን ተገንዝበውም እርሳቸው ጥሩ ሯጭ መሆን እንደሚችሉ በማመናቸው ልባቸው ይህን ማድረግ ይመኝ ጀመር። ይህ ከሆነ ከ 2ዓመት በኋላ ወንድማቸውን ሊጠይቁ ወደ አዲስ አበባ ጎራ አሉ። የወንድማቸው መኖሪያ አሮጌው አውሮፕላን ማረፊያ ሲሆን በዚያች ገጠመኝም አዲስ ወታደሮች ሲመለመሉ ተመለከቱ። ምልመላውን ቆመው ሲመለከቱ አንድ ሃምሳ አለቃም ዋሚን ለምን አትገባም ብሎ ጥያቄ አቀረቡላቸው ።ከመስከረም 5 ቀን 1945 ዓ.ም ጀምሮ ወታደር ሆነው ተቀጠሩ። ስልጠናቸው ሲጨርሱ ዋሚ ሁለተኛ ክፍለ ጦር ተመድበው ወደ አስመራ ሄዱ። በወቅቱ ምልመላ ወታደሮችና ነባሮች በህብረት ሩጫ ይወዳደሩ ነበር ። በ10 ኪ.ሜ ዋቢ አንደ ኛ ሆነው ማሸነፍ ቻሉ ። በዚህም ምክንየት ስፖርት ላይ በመደበኛነት ቆዩ ። 1947 ዓ.ም ለዋቢም ሆነ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዩ ዓመት ነበር። ለሜሊቦርን ኦሎምፒክ ማጣሪ የሙሉ ማራቶን ውድድር ተዘጋጀ ፡፡ ከዚያ በፊት ማራቶን ተብሎ ይሮጥ የነበረው 15 ኪ.ሜ ብቻ ነበር። በዚህ ዓመት ግን ማራቶኑ በመደበኛ 42 ኪ.ሜ ከ1950 ዓ.ም ሊሮጥ ተወሰነ። እያንዳንዱ ክፍለ ጦር ሶስት ሶስት ተወዳዳሪ ተመርጦ ከ8ኛ ክፍል ጦሮች 24 ተወዳዳሪ ተመረጠ ። በኋላ ግን የጦር ኃላፊዎቹ የሚፈልግ ሁሉ ይሩጥ ብለው አዘዙ። የተወዳዳሪዎቹ ቁጥር 50 ደረሰ። ውድድሩ ተጀመረ ዋሚ ያለ ምንም ችግር አንደ ኛ ሆነው አሸነፉ ፡፡ በቦታው የነበሩት ንጉሰ ነገስቱ አፄ ኃይለ ስላሴ ለአሸናፊዎቹ ዋንጫ አንዲሰጥ አዘዙ። ቀድሞ በ5 ሺህ እና በ10 ሺህ አሸንፈው የነበሩት ዋቢ ሶስት ዋንጫ ተሸለሙ ፡፡ በማራቶኑ ውድድር ዋሚን ተከትለው ሁለተኛ እና ሶስተኛ ሆኑት ነጋሽ ቤኛ እንዲሁም ገብሬ ብርቄ አንድ አንድ ዋንጫ ተሸለሙ። የመጀመሪያው የማራቶን ውድድር በዋሚ ቢራቱ አሸናፊ ተጠናቀቀ። ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጰያ ውስጥ በተዘጋጀው የማራቶን ውድድር አሸናፊ የሆኑት አትሌት ሻለቃ ዋሚ ቢራቱ ናቸው። ከዚያን በኋላ እነ አበበ ቢቂላ ማሞ ወልዴ መድረኩን ነግሰውበታል። ይሁንና የዋሚ እና የመጀመሪው መስሪያ ቤታቸው ጦር ሃይሎች ጋር ብዙም መቆየት አልቻሉም ነበር። በአጋጣሚ ከቀዬአቸው ወጥተው የጦር ሃሐይሎች ዓባል የሆኑት ዋሚ ቤተሰቦቻቸውን ለማየት ፈቃድ ጠየቁ። የፈቃድ ጥያቄው ግን ተቀባይነት አላገኘም ነበር። ዋሚና ጦር ሃይሎች ተኳረፉ። በዚህ የተነሳ በ1948 ዋሚ ክብር ዘበኛ ተቀጠሩ። 1949 ዓ.ም በልኡል መኮንን ሞት እንዲሰረዙ ተደረገ። ከ1950 እስከ 1952 በ5 ሺህ በ10 ሺህ እና በማራቶን ዋሚን የሚረታ ጠፋ። በተለይ በ1952 ዋሚ የማራቶን አንደኛነቱን ሲይዙ አበበ በቂላ 2ኛ ሆኖ ጨረሰ። ስለዚህም ዋሚ ቢራቱ እና አበበ በቂላ በሮም ኦሎምፒክ ኢትዮጵያን እንዲወክሉ ተመረጡ። በወቅቱ ይህንን ሁሉ ስኬት ሲያስመዘግቡ ፌዴሬሽንም ሆነ አሰልጣኝ አልነበራቸውም። የስፖርት ጥትቅ የሚባል ነገርም እንደዚሁ። ይሁንና ዋሚ ራሳቸውንም ሆነ አበበ ቢቂላን እያሰለጠኑ አዲስ ታሪክ መሰራቱን ቀጠሉ፡፡ በወቅቱ በኦሎምፒክ ህግ መሰረት አንድ ሰው አሰልጣኝም ተወዳዳሪም መሆን ሰለማይችል አሰልጣኝ መቅጠር ግድ ሆነ። ስለዚህም ሰዊዲናዊው ሜጆሮኒ ስካና አበበን እና ዋሚን ለማሰልጠን ተቀጠሩ። ስዊዲናዊው አሰልጣኝ በጥቂት ጊዜ ውስጥ የአለም ምርጥ አትሌቶች የሚሆኑ ብላቴናዎችን እያሰለጠኑ መሆንን ለመረዳት ጊዜ አልወሰደባቸውም። እኚህ የባህር ማዶ አሰልጣኝ በአበበ እና በዋሚ ኢትዮጵያ አማካኝነት በረጅም እርቀት ሩጫ ድል እንደምታስመዘግብ እርግጠኛ ሆነው ነበር። ይህንንም ለንጉሱ በወቅቱ ቀርበው ተናግረው ነበር። ይሁንና ያን ሁሉ ተስፋ ተጥሎባቸው የነበሩት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ በድንገት ታመሙ። የሮም ኦሎምፒክ ውድድር ስድስት ቀን ሲቀረው ኢትዮጵያ የተማመነችባቸው ጀግና 19 ቦታ ብጉንጅ ወጣባቸው። አሰልጣኙ ሁለተኛውን ምርጥ አትሌታቸውን አበበ ቢቂላን ለማሳለፍ ተገደዱ። ስለዚህም አበበ በሮም ጎዳናዎች ታላቁን ተልእኮ ለመሸከም እና ለመፈፀም ተገደደ። አበበ ኢትዮጵያን ሮም ላይ ወክሎ ሮጠ። ኢትዮጵያውያንን አላሳፈረም። ፌዴሬሽን የሌላት ትጥቅም የማታቀርበው ሀገር በባዶ እግሩ በሮጠው ሰው አሸናፊነት አዲስ ታሪክ አፃፈች። ብዙዎች «አንድ ጥቁር አፍሪካዊ ጣሊያንን በባዶ እግሩ ወረራት» በማለት ከአድዋ ድል ጦርነት ታሪክ ጋር አያያዙት። ከውድድሩ በኋላ በባዶ እግሩ ሮጦ ያሸነፈውን ጥቁር ሰው ጋዜጠኞች ጥያቄ አቀረቡለት «በሀገሬ እኔ አይደለሁም፤ በህመም ምክንያት አሸናፊው አልመጣም አላቸው» ሲል አጋሩን ዋሚ ቢራቱን አንቆለጳጰሰው። አበበ በሮም ላይ ያስመዘገበው ድል ለአለም ህዝብ ድንቅ ቢሆንም አትሌት ዋሚ ቢመጣ ኖሮ ከዚህ በላይ ተአምር ታዩ ነበር በማለት በአስተያየቱ አለምን ይበልጥ አስደነቀ። በዋሚ መንገድ አበበ በቂላ ፣ማሞ ወልዴ ፣ምሩፅ ይፍጠር ፣ሃይሌ ገ/ስላሴ ፣ደራርቱ ቱሉ ፣ቀነኒሳ በቀለ ፣ፋቱማ ሮባ ፣ብርሃኔ አደሬ ፣ጌጤ ዋሚ ፣ጥሩነሽ ዲባባ ፣መሰረት ደፋር ፣ስለሺ ስህል ፣ገንዘቤ ዲባባ የመሳሰሉ ጀግኖች መፍራታቸውን ብዙዎች ይናገራሉ። ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ በተለያዩ የሩጫ መድረክ ላይ አገራቸውን ያስጠሩበት ድል አስመዝግበዋል። ከነዚህ መካከል በ1ሺ500፣3ሺ፣5ሺ፣10ሺ፣21ኪሜ፣25ኪሜ፣በ32ኪ.ሜ በአገር አቋራጭ እና የተለያዩ የማራቶን ውድድሮች ላይ በመሳተፍ 51 የወርቅ፣ 44 የብር እና 30 የነሀስ ሜዳሊያዎችን ማገኘት ችለዋል። ከዚህም ሌላ 21 ሰርተፍኬት፣ 4 ዲፕሎማ እና ከ40 በላይ ዋንጫዎችን ወስደዋል። በተለያየ ወቅትም የኢትዮጰያ ባንዲራ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ አስችለዋል። የሶምሶማ እሩጫ በአገራችን እንዲለመድ ለማድረገ ጥረት ያደረጉ መሆናቸውም ይነገርላቸዋል። እኚህ አንጋፋ አትሌት ምንም እንኳን እድሜያቸው ቢገፋም በተለያየ ጊዜ ውድድሮችን እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ይታወቃሉ። ለጠንካራ ተክለ ሰውነታቸው እና በጤንነት ረጅም እድሜ መቆየታቸው ደግሞ በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች መሳተፋቸው ያመጣው ውጤት እንደሆነ ይነገራል። ከዚህ ጥንካሬያቸው መካከልም በእርጅና ዘመናቸው በታላቁ ሩጫ ላይ ተሳታፊ ሆነው ያለምንም ችግር ማጠናቀቃቸቸው ነው። ሻለቃ ባሻ ዋሚን ለማክበር ሻለቃ ባሻ ዋሚ የፊታችን ጥር 11 ድፍን 100 አመት ይሞላቸዋል። በአትሌቲክሱ ላይ ደግሞ ለ64 አመት ነግሰውበታል። የ100ኛ አመት ልደትና ሩጫ የጀመሩበት 64ኛ ዓመት በዓል በዶክሜንተሪ ፊልም፣ በስእል አውደ ርዕይ በስማቸው አደባባይና መንገድ በመሰየምና ወደ ትውልድ ከተማቸው በመሄድ ይከበራል። አትሌት ሻለቃ ባሻ ዋሚ ቢራቱ ሩጫን የተቀላቀሉት በውትድርና አገራቸውን እንዲያገለግሉ ከተመደቡበት ጊዜ አንስቶ ነው። ከዚያን ዘመን ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት ለአገራቸው ድልን በማስመዝገብ እንደ አበበ ቢቂላ ላሉ ብርቅዬ አትሌቶች አርአያ ቢሆኑም የሰሩትን ያህል አለመከበራቸውን በተለያየ ጊዜ ይገለፃል። አሁን ይህን ዝግጅት ለማድረግ ያሰቡት አካላትም ጀግኖቻችን በህይወት እያሉ እናክብራቸው የሚል ሀሳብ ሰንቀው ነው ስራውን የጀመሩት። እርሳቸውን ከማክበር እና ከመደገፍ ባሻገር የጥንካሬያቸውን ምስጢር ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ እድል ይፈጥራል።
11286
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%88%AB%E1%89%B5%20%E1%8B%88%E1%88%8D%E1%8B%B0%E1%8B%A8%E1%88%B5
አስራት ወልደየስ
ፕሮፈሰር አስራት ወልደየስ አዲስ አበባ ተወልደው ድሬዳዋ ያደጉ ሲሆኑ፣ ለመጀመርያ ጊዜ ፕሮፌስናል ስልጠና ያገኙ የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ ቀዶ ጠጋኝ ነበሩ። ፕሮፌሰር አስራት ወያኔ ስልጣን በያዘ ጊዜ የወያኔ ተቃዋሚ በመሆን መአሀድ የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት መስራችና ዋና ሊቀመንብር በመሆን ታላቅ የወያኔ ተቃዋሚ ሲሆኑ ወያኔም በፍረሀት ወደ እስርቤት ካስገባቸው በሗላ በሰሜን ሸዋ ደብረ ብርሀን፣ ጅሩ እነዋሪ፣ መንዝ፣ ተጉለትና ቡልጋ፣ አውራጃ ውስጥ እንዲሁም በመላው የአማራ ክልል የፕሮፌሰር አስራት ተከታዮች በማለት በጣም ብዙ ሕዝብ ጨፍጭፏል። በአሁን ሰዓትም የአማራ ብሔርተኝነት በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የመንፈስ ልጅነት እየተመራ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ሀኪሞች በመጀመሪያ ትክክል ነበሩ በኇላ አበላሹት:: ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ እና የአማራ ህዝብ ትግል!!!!! " አንደበት ላጣ ህዝብ ካልተናገሩለት ወንጀል አይሆንም ወይ ወገኑ ነኝ ማለት" ሀይሉ( ገሞራው) ይህ ፅሁፍ ከተፃፈ አራት አመት አልፎታል ፡፡ ነገር ግን በየአመቱ የጓደኞቼ ብዛት ስለሚጨምር ለአዲሶቹ አባላት የተወሰነ ስለ አባታችን ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ መረጃ ለመስጠት ያህል ሲሆን በዛውም የሙት አመታቸውን ለማስታወስ ያህል ነው፡፡ ሌላው ፅሁፉን ምስጋናው አንዷለም ( መለክ ሀራ) እኔን አስፈቅዶ << ግዮናዊነት>> የሚለው መፅሀፉ ውስጥ አካቶታል፡፡ ግዮናዊነት ሊወጣ ሲል ምስገጋናው ፅሁፉን በደንብ አጎልብተው እያለኝ እኔም በግሌ ከ 9- 12 ክፍል የሂሳብ መርጃ መፅሀፍ ( እየፃፍኩ በነበረበት ሰአት ስለነበረ ተደራረበብኝና ትንሽ ተዘናጋሁ መፅሀፉ ሲወጣ ግን ህዝቡም ሲወደው የተሻለ ባበረክት ኑሮ ብዬ ተቆጨሁ፡፡ ነገሩን ነው እንጂ አሁን ላይ በጋሻው መርሻ የተፃፈ << አንፀባራቂው ኮከብ>> የተባለ የፕሮፌሰር አስራትን ትግል የሚዳስስ መፅሀፍ ስላለ አንባቢዎች በጥልቀት ያንን ቢያነቡ ስል 1. ግለ ታሪክ እውቁ የቀዶ ጥገና መምህር ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ሀምሌ 11 1920ዓ.ም በአዲስ አበባ የተወለዱ ሲሆን፤ በሶስት አመታቸው ቤተሰቡ በሙሉ ወደ ድሬደዋ በመዛወሩ እድገታቸው ድሬደዋ ሊሆን ችሏል፡፡ ጣልያን ኢትዮጲያን ሲወር ገና የ8 አመት ልጅ ቢሆኑም የወረራው ወቅት ግን ለብላቴናው አስራት መጥፎ ትዝታን ጥሎ ያለፈ ነበር:: ገና በመጀመሪያ አመት ላይ ፋሽስት ጣሊያን አያታቸውን ቀኝ አዝማች ፅጌ ወረደን ወደ ጣልያን በምርኮ የወሰዳቸው ሲሆን፣ የ1932ቱን የግራዚያኒ ግድያ ሙከራ ተከትሎ ከ30,000 በላይ ኢትዮጲያዊ ሲያልቁ አባታቸው አቶ ወልደየስ አጥላየ አንዱ መስዋዕት ሆኑ፡፡ ይህንን ተከትሎም በባላቸው ሀዘን ከፍተኛ ህመም ላይ የወደቁት እናታቸው ወዲያውኑ ሞቱባቸው፡፡ በ1933ዓ.ም ኢትዮጲያ ከጣሊያን ነፃ ስትወጣ ወደ አዲስ አበባ የመጡት አስራት ወልደየስ በሚቀጥለው አመት ማለትም በ1934ዓ.ም በተፈሪ መኮንን ት.ቤት ዘመናዊ የቀለም ትምህርት ጀምረዋል፡፡ በትምህርት ላይ ጥሩ አቀባበል የነበበራቸው ይህ ምሁር በ1935ዓ.ም የፎቶ ካሜራ ተሸልመዋል፡፡ በኀላም ከ42ቱ ምርጥ ተማሪዎች አንዱ ሆነው የውጭ የመማር እድል አግኝተዋል፡፡ በግብፅ አሌክሳንደሪያ ቪክቶሪያ ኮሌጅ በ1948ዓ.ም በቀዶ ጥገና ሙያ በጥሩ ነጥብ ተመርቀው የወጡት ፕሮፌሰር አስራት ወደ ሌላ ለገር ለመሄድ ወለም ዘለም ሳይሉ ደሀውን ወገናቸውን ሊያገለግሉ ወደ ሀገራቸው መጥተዋል፡፡ ለተከታታይ አምስት አመታት ህዝቡን ሲያገለግሉ ቆይተው ወደ እስኮትላንዱ ለማድረግ ተመልሰው ሄደዋል፡፡ ትምህርታቸውን እንደጨረሱ ሀገር ቤት ከረጅም ግዜ ልፋት በኀላ የሙያ አጋሮቻቸው ጋር በመሆን የመጀመሪያውን የህክምና ት.ቤት አቋቁመዋል፡፡ በሙያቸው መምህር፣ ሀኪምና የት.ቤቱ ዲን ሆነው ደሀውን ህዝባቸውን አገልግለዋል፡፡ ለዚህም እስከ ንጉሱ የግል ሀኪምነት ድረስ ደርሰዋል፡፡ 2. በወታደራዊው ደርግ ዘመን ወታደራዊው መንግስት ስልጣን እንደያዘ ንጉሱን ገሎ ለህዝብ የሰጠውን መግለጫ ' በሚል መፅለፋቸው ሁኔታውን ሲገልፁት፦ " ." ይህም ማለት በግርድፉ (ደርግ ንጉሱን ገሎ ለህዝብ በሰጠው መግለጫ << ሲታመሙብን የግል ሀኪማቸውን እሰጠርቸን ነበር ግን ቤታቸው አልነበሩም>> ሲል ፕሮፌሰሩ ግን << በሰአቱ ቤቴ ነበርኩ መንም የጠራኝ የለም >> ሲሉ ንግግሩን ተቃውመዋል) በዚህ የተጀመረው ግንኙነት በኀላም የደርግ ካድሬዎች የህክምና ት.ቤቱ ላይ ሊያሳርፉት በሚሞክሩት የሶሻሊስት ፅንሰ ሀሳብ በተደጋጋሚ ፕሮፌሰሩ ጋር ሳያስማማቸው ኖሯል፡፡ ይህም ሆኖ ግን በ1970ወቹ መጀመሪያ አካባቢ ከሰሜን ተገንጣዮች ጋር ያደርገው የነበረው ፍልሚያ ላይ ፕሮፌሰር አሰራት ሙያዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ወደ ቦታው አቅንተው ነበር፡፡ 3. በኢህአዴግ ዘመን ምሁር በአይኔ አልይ የሚለው ይህ መንግስት ገና ከጅማሮው ነበር ፕሮፌሰሩሠ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ የጀመረው፡፡ በወቅቱ በመንግስት ቁጥጥር ስር ይታተሙ በነበሩ ጋዜጦች( እፎይታ፣ ማለዳ፣ አዲስ ዘመን፣ አቢዮታዊ ዲሞክራሲ...) ፕሮፌሰሩ ከደርግ ጋር ሆነው እንደወጉት አድርገው መፃፍ ጀመሩ፤ በወቅቱ ፕሮፌሰሩ ሲጠየቁ ግን፦ " እኔ የህዝብ ልጅ ነኝ በሙያየ ከንጉሱ እስከ መንግስቱ ሀ/ ማርያም ቤተቦች፤ ከድሀ ገበሬ አስከ ወታደር የሙያው ስነምግባር በሚጠብቅ ሁኔታ አገልግያለሁ። እነሱ እንደሚሉትም ሳይሆን ምፅዋ ላይ የኢትዮጲያ ወታደር ወይም የተገንጣይ ሳንል አክመናል፡፡ አሁንም ቢሆን እርዳታየ ካስፈለጋቸው ለእነሱም ለማገልገል ችግር የለብኝም፡፡" ነበር ያሉት፡፡ ፕሮፌሰር አስራትን ለየት የሚያደርጋቸው ስብእና በሙያው እንዳሉ ሌሎች አጋሮቻቸው፤ የራሳቸው የግል ህክምና ተቋም ገንብተው ገንዘብ ለመሰብሰብ አንድም ቀን ያልሞከሩ ሲሆን፤ ህይወታቸውን በሙሉ ለህዝብ ችግር አሳልፈው የሰጡ ነበሩ፡፡ 4. የፖለቲካ ህይወት እዚሀህ ላይ ብዙዎች የሚጠይቁት ጥያቄ ዋናው ይህ ትልቅ ምሁር እንዴት ወደ ዘር ፖለቲካ ሊገቡ ቻሉ? የሚለው ነው። ለዚህም ራሳቸውን ጨምሮ ብዙ ፀሀፊዎች እንደሚያስቀምጡት የተለያዩ ምክንያተቶች አሉ ከእነሱም ውስጥ፦ ሀ. በሰኔ መጨረሻ 1983ዓ.ም በአውሮፓውያን እና አሜሪካ አቀናባሪነት የተደረገው "" ፕሮፌሰሩ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ወክሎ የታደመው ቡድን አባል ሆነው ተሰብስበው ነበር፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ የተለያዩ ዘሮችን የወከሉ ቡድኖች ሲኖሩ በህዝብብዛቱ ሁለተኛ የሆነውን አማራን የወከለው ቡድን የለም ነበር፡፡ የስብሰባው ዋነኛ አጀንዳም 'ስለተጨቆኑ ብሄር ብሄረሰቦች ...ምናምን ' ሲሆን ጨቋኝ ሆኖ የቀረበው ቡድን ደግሞ አማራው ነበር፡፡ ይህ ነገር መንግስት በሚቆጣጠራቸው ሚዲያ ሳይቀር አማራው ደርግና የአፄው ስርአት ላጠፉት ጥፋቶች ሁሉ እንደ ዋና ባለቤት ተደርጎ ተወሰደ፤ ቋንቋው ቆሻሻ ቋንቋ/ / ወይም እንደ ኦነግ አጠራር ) ተብሎ ይጠራ ጀመር፡፡ በግልፅም የመንግስት አካል የነበረው የወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስተር ታምራት ላይኔ ሳይቀር ኤርትራ ሄዶ በአማራው ስም "በነፍጠኛው ስርአት ለተደረጉ ማንኛውም ግፍ እና በደል እኔ በአማራው ስም ይቅርታ እጠይቃለሁ" የሚል ሰንፋጭ ንግግር አድርጎ መጣ፡፡ ይህ ሁሉ በሬ ወለደ ፕሮፓጋንዳ ፍሬ አፍርቶ ወደ ተግባር ተለወጠ፡፡ ለ. ይህንን የቃላት ጦርነት ወደ ተግባር ለመለወጥ ሁለም ታጣቂ ሀይሎች ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ኦነግ፣ ኦህዲድ/ ኢህአዲግ/... በበደኖ 154 ሰው፣ ጊራዋ፣ ኩርፋ ጨሌ፣ ለንጋ፣ ኬርሳ፣ ሶካ፣ ደደር፣ ሂርና፣ ቁኒ፣ መስላ፣ ጋሊቲ፣ ደባ የቸባሉ አካባቢዎች ከ 1000 ሰው በላይ፤ አርባ ጉጉ ላይ ከሞተው ውጭ ከ32,000 በላይ ሰው ከመኖሪያው ተፈናቅሏል ፡፡ አርሲ ነገሌ 60 ሰው፣ ወለጋ ከ200 ሰው በላይ እንደ ዱር እንስሳ ታድነው ተገለዋል፡፡ ይህ ከብዘ በጥቂቱ ነው፡፡ ሴቶችን መድፈር፣ ፅንሳቸውንን በጩቤ እያወጡ ማሳየት ዋና መዝናኛቸው ነበር፡፡ ይህ ሁላ ሲሆን ወያኔ/ህወሀት/ ዳር ቆሞ ለኦነግ እና ሌሎቸች መሳሪያ እያስታጠቀ ያልታጠቁ ንፁህ ገበሬ አማሮችን አስጨፈጨፈ። የሚገርመው በቀደመ ስሙ ኢህዲን የጥምቀት ስሙ ብአዲን የሚባለው ድኩማን ድርጅት ይህ ሁሉ ጭፍጨፋ ሲካሄድ አንድም ተቃውሞ አላደረገም፡፡ ከበአዲን ይልቅ # የኢሳ_ ሶማሌ_ጎሳዎች ለመንግስት ባስገቡት ደብዳቤ እንደገለፁት "ይህ በኦነግ እና ኦህዲድ አማካኝነት የሚደረግ ንፁሀን ጭፍጨፋ ማስቆም ካልቻላችሁ እኛ ጣልቃ ገብተን እናስቆማለን" የሚል የወንድማዊ እና ታሪክ የማይረሳው ስራ እንግዲህ ከላይ የጠቀስናቸው ምክንያቶች እና ሌሎችም ተጨምረው ናቸው ፕሮፌሰሩን መአህድን ጥር ወር 1984ዓ.ም ሊያቋቁሙ ያስቻላቸው፡፡ መአህድ ( መላው አማራ ህዝባዊ ድርጅት) ገና ከጅማሮው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ፅህፈት ቤት የከፈተ ሲሆን፡፡ በተለያየ መንገድ ተፅዕኖ ማድረግ ጀመረ፡፡ በህዳር ወር 1985ዓ.ም ደብረ ብርሃን ላይ ያደረገው ህዝባዊ ስብሰባ ድርጅቱን በመንግስት ደህንነቶች ክትትል ስር እንዳይወጣ አደረገው፡፡ መአህድን እንደፈሩት የሚያስታውቀው በወቅቱ የመከላከያ ሚኒስተር የነበሩት አቶ ስየ አብርሃ የድርጅታቸው ስብሰባ ላይ፦ ( መአህድ ) " ....ይህ የሚያመለክተው ወያኔ መአህድን ምን ያህል ፈርቶት እንደነበረ ነው፡፡ ከመስከረም እስከ ሀምሌ 1985ዓ.ም ብቻ ከ40 በላይ የመአህድ ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ታስረዋል፡፡ ፕሮፌሰር አስራት ከአርባ አንዱ የዩኒቨርስቲ መምህሮች ጋር 'በአቅም ማነስ' በሚል ፖለቲካዊ ስም ማጥፋት ታርጋ በገነት ዘውዴ በሚመራው ትምህርት ሚኒስተር ተባረዋል፡፡ ይህ እንግዲህ የሚሆነው ከ የተመረቁትን ምሁር በደደቢት በረሀ ምሩቃን መሆኑ ነው፡፡ በ1986ዓ.ም መንግስታዊው ጁንታ እውቁን ምሁር ደብረ ብርሃን ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር አማካኝነት " መንግስትን በሀይል ለመገልበጥ አሲረዋል" ሲል ሁለት አመት ፈረደባቸው፡፡ እዛው እስር ላይ እያሉ በ1988ዓ.ም እንደገና በሌላ ክስ ሶስት አመት ጨመረባቸው፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው ከ65 አመት በላይ የነበሩ አዛውንት ላይ ነበር፡፡ ፕሮፌሰር ከዚህ አመት በኀላ ግን ጤና አጡ በተከታታይም ሀኪሞች የውጭ ህክምና ያስፈልጋቸዋል ቢባልም መንግስት ሊቀበል አልቻለም፡፡ በመጨረሻ ከተዳከሙ በኀላ በታህሳስ ወር 1991ዓ.ም ወደ ውጭ እንዲሄዱ ቢፈቀድም በጣም ተዳክመው ስለነበር ከ5 ወር በኀላ ግንቦት 6 1991ዓ.ም በ ሊያርፉ ችለዋል፡፡ የዚህ ፅሁፍ ባለቤት ከተለያየ ቦታ የጨመቀውን ይችን ፅሁፍ የፃፈው አንድም ታላቁን መምህር ለማስታወስ ነው፡፡ ሌላው የአሁኑ ትውልድ ከዚህ ምን ይማራል? የሚለውን ሁሉም በየቤቱ እንዲያስብበት ነው ፡፡ በተጨማሪም የአማራው_መደራጀት ግድ መሆኑን ለማስመር ነው፡፡ በመጨረሻ ስለ አማራዊነት ማሰብ ተመርጦ የሚገባበት ጉዳይ ሳይሆን ከመገፋት፣ ከጭቆና የሚመጣ መሆኑን ለማጠየቅ ነው፡፡ 1. ነፀብራቅ 2. ዶ.ር አሰፋ ነጋሽ "
45331
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%88%85%E1%88%99%E1%8B%B5%20%E1%8A%A0%E1%88%85%E1%88%98%E1%8B%B5
ማህሙድ አህመድ
በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ አሻራቸውን መጣል ከቻሉ ስመ ጥሩ ዘፋኞች ውስጥ አንዱ ማህሙድ አህመድ ነው፡፡ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ተወዳጅነትን፣ ተደናቂነትን፣ ተፈቃሪነትን ማትረፍ የቻለ ፈርጥ እንደሆነ ብዙዎች ያምናሉ፡፡ ሙሉ ሕይወቱን በሙዚቃ ያሳለፈው ማህሙድ በሙዚቃው ይተነፍሳል፣ ይናገራል፣ ሰውን ያዝናናል፡፡ ከአርባ ዓመታት በላይ በቆየውም የሙዚቃ ሕይወቱ የተለያዩ ትውልድን በሙዚቃው አንድ ላይ ማምጣት የቻለ ትልቅ አርቲስት ነው፡፡ በተለያዩ ኮንሠርቶች በሚዘፍንበትም ወቅት በተለያዩ ዕድሜ ክልል የሚገኙ ሰዎች ብሔራዊ መዝሙር በሚመስል መልኩ አብረውት በመዝፈንም በዘፈኑ አንድነትን ያሳያሉ፡፡ ማህሙድ የዝና ጣራ ላይ መድረስ ችሏል፡፡ በሕዝቡ ዘንድ ከመወደዱና ከመፈቀሩ በተጨማሪ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይም ዝናው ናኝቷል፡፡ የሰዎችን ልብ ከማሸነፉ በተጨማሪ ከኮንሠርቱ በፊት ቲኬቶቹ ተሸጦ የሚያልቅበት አጋጣሚም ተደጋጋሚም ነው፡፡ የተለያዩ ሽልማቶችንም ለማሸነፍም ችሏል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አንዱ የቢቢሲ ወርልድ ሚዩዚክ አዋርድ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ምንም እንኳን ይሔን ያህል የጣራ ዝና ላይ ቢሆንም ትሁት፣ ሰዎችን የሚያከብርና በቀላሉም የሚግባባ ሰው ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ነበር የሰላም ዓለም አቀፍ ሙዚቃ ፌስቲቫል አካል ሆኖ ከያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጋር ሙዚቃ ሕይወቱን ያካፈለው፡፡ አዳራሹ በተማሪዎች ተሞልቶ የነበረ ሲሆን ለብዙዎች ማህሙድን ማየት ትልቅ ነገር ነው፡፡ በተለይም በአካል ተገኝቶ ከእነርሱ ጋር ማውራቱ እንደ ዕድልም ነው ያዩት፡፡ በሚያስደንቅ ሁኔታ ግን ማህሙድ በስሜት ተሞልቶ ከተማሪዎቹ በላይ ያለቀሰበት ሁኔታ ታይቷል፡፡ በሳግ በተቆራረጠ ድምፅም እዚህ ቦታ ላይ መገኘቱ ለእሱ ልዩ እንደሆነም ተናግሯል፡፡ ‹‹ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ከተማሪዎች ጋር ስለሙዚቃ ሕይወቴ ሳወራ፤ ዛሬ ብሞትም ምንም አይመስለኝም፡፡ በጣም ዕድለኛ ነኝ፡፡ እግዚአብሔርም በሕይወት ያቆየኝ ለዚህ ይመስለኛል፤›› ብሏል፡፡ ማህሙድ ከልጅነቱ ጀምሮ ያጋጠመውን ውጣ ውረድ በማስታወስ አሁን ያለበትን ደረጃም እግዚአብሔርን በማመስገን ተናግሯል፡፡ የተወለደው በ1933 ዓ.ም. አዲስ አበባ በአሜሪካን ግቢ አካባቢ ነው፡፡ ሥራንም ሆነ ሕይወትን በራሱ መጋፈጥ የጀመረው ገና በሕፃንነቱ ነው፡፡ አባቱ በሚሠራበት ግሪክ ክለብ አብሮ በመሔድ ቅርጫት ኳስና የቴኒስ ሜዳዎቹ ላይ ይሠራም ነበር፡፡ በስድስት ዓመቱም ሊስትሮ ሆኖ መሥራት ጀመረ፡፡ በትምህርት ቤት ቆይታው ብዙ ጐበዝ እንዳልነበር ፈገግ ብሎ የሚያወራው ማህሙድ ቤተሰቦቹንና ራሱን መርዳት እንዳለበትም የተረዳው ገና በሕፃንነቱ ነው፡፡ የሙዚቃ ሕይወቱ ሀ ብሎ የተጀመረው አንድ ክለብ ውስጥ ሳንድዊች እንዲያቀርብ በተቀጠረበት ጊዜ ነው፡፡ እንደ አጋጣሚም ሆኖ በዚያው ክለብ ውስጥ ጥላሁን ገሠሠ ይዘፍንበት የነበረ ቦታ ነበር፡፡ በአንድ አጋጣሚም ሁሉም ድምፃውያን ወደ ድሬዳዋ ሔደው ሙዚቀኞቹ ያለ ድምፃዊ እየተለማመዱ ነበር፡፡ የተፈራ ካሣን ‹‹አልጠላሽም ከቶ››ን የተዘራን ‹‹ይሔም አለ ለካ››ንና የጥላሁን ዘፈን እየተለማመዱ ነበር፡፡ በድምፅ መዝፈን እንደሚፈልግም ጠየቃቸው፡፡ ‹‹በጣም ቀጭን ነበርኩ እናም ‘ትችያለሽ? ወይ›› ብለው ጠየቁኝ፣ እናም እሞክራለሁ አልኩ›› በማለት ማህሙድ ይናገራል፡፡ ‹‹አልጠላሽም ከቶ›› የሚለውን ዘፈን በሚዘፍንበት ሰዓት የኮንጐ ዘማቾች በቦታው ነበሩ እናም አስደነቃቸው፡፡ እንደገናም እንዲዘፍን ተጠየቀ፡፡ የክለቡ ባለቤት በቦታው የነበረ ሲሆን አድናቆት በተሞላ ድምፅም ‹‹የአላህ ያለ መዝፈን ትችላለህ!›› እንዳለው ማህሙድ ያስታውሳል በዚህም አጋጣሚ ከአስተናጋጅነት ወደ ዘፋኝነት ተቀየረ፡፡ የቤቱ ባለቤትም ሙሉ ልብስ ገዛለት፡፡ ጥላሁንና ሌሎቹ ዘፋኞች በተመለሱበት ወቅት የእሱ መዝፈን በጣም ነው ያስገረማቸው፤ የግጥም ደብተርም ሰጡት፡፡ መዝፈን በጀመረበት ወቅት የተለያዩ ዘፋኞችን ሙዚቃ በመዝፈን ነበር፡፡ በዚህም ክለብ ነበር ‹‹አላወቅሽልኝም›› የሚለው የመጀመሪያው ዘፈኑ የሆነው ግጥም የተሰጠው፡፡ ክብር ዘበኛ መቀጠር ፍላጐቱ የነበረ ሲሆን መጀመሪያ ግን ፖሊስ ኦርኬስትራና ምድር ጦር ለመቀጠር ጠየቀ፡፡ በተለያዩ ምክንያቶችም እንደማይቀጥሩት ነገሩት፡፡ መቶ አለቃ ግርማ ሐድጉም (በኋላ ሻለቃ) ክብር ዘበኛ መቀጠር ይፈልግ እንደሆነ ጠየቁት፣ እሱም ተስማማ ከመቀጠሩ በፊት ግን በሕዝብ ፊት ዘፍኖ ማለፍ ነበረበት፡፡ የዚያን ጊዜ የነበረውን እያንዳንዷን ጥቃቅን ነገር በጥልቅ ያስታውሳል፤ የታምራት ሞላን ‹‹ተስፋ አትቁረጪ›› እንዲሁም ‹‹አላወቅሺልኝም››ን ሲዘፍን የተመልካቹ መልስ ለየት ያለ ነበር፡፡ ‹‹የኤልቪስ ፕሪስሊን ዳንስም እየደነስኩ ነበር፣ እናም የተመልካቹ መልስ የማይታመን ነበር፤›› በማለት ማህሙድ ይገልጻል፡፡ መቶ አለቃ ግርማም ወታደር ሆኖ እንዳይቀጠር መከሩት፣ የክብር ዘበኛ ሰዎችም በወታደርነትና ሙዚቀኝነት 120 ብር እንክፈልህ ብለው ጠየቁት፡፡ እሱ ግን ባለመስማማቱም በሙዚቀኝነት ብቻ በ1955 ዓ.ም. አካባቢ ተቀጠረ፡፡ ለአሥራ አንድ ዓመታትም ያህልም በዚህ ቦታ ሠርቷል፡፡ ‹‹ለዚህ ያበቃኝ፣ የማውቀውን ነገር ሁሉ ያስተማረኝ ለእኔ ወንድሜ ጥላሁን ገሠሠ ነው፡፡ ሌሎችም ሙዚቀኞች እንዲሁ በእኔ ላይ አሻራ ጥለዋል፤›› ይላል ማህሙድ፡፡ በዚያን ወቅት ሙዚቀኞች አንድ ላይ ይሰባሰቡበት የነበሩ ብዙ አጋጣሚዎች ነበሩ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ክብር ዘበኛ ይሠራ በነበረበት ወቅት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ይደረግ የነበረው የሙዚቀኞች ውድድር አንዱ ነው፡፡ የተለያዩ ባንዶች እንደ ምድር ጦር፣ ክብር ዘበኛና የፖሊስ ኦርኬስትራ ባንዶች ከድምፃውያኖቻቸው ጋር ይመጣሉ፡፡ እያንዳንዱም ድምፃዊ አንድ ወይም ሁለት ዘፈን ይዘፍናል፡፡ ይሔም ለሙዚቀኞች ጥሩ አጋጣሚ እንደነበር ይናገራል፡፡ ከአሥራ አንድ ዓመታት ቆይታም በኋላ በተለያዩ ክለቦች መሥራት ጀመረ፡፡ ለዚህም ምክንያቱ የነበረው ያገኘው የነበረው 60 ብር አምስት እህቶቹና ወንድሞቹ በአጠቃላይ ቤተሰቦቹን መደገፍ አልቻለም፡፡ በወቅቱ አባቱ ሥራ ያልነበራቸው ሲሆን እናቱ ብቻ ነበረች የምትሠራው፤ መጨረሻ ላይ ከክብር ዘበኛ በለቀቀበት ወቅት ደመወዙ 250 ብር ደርሶ ነበር፤ ከዚያም ከአይቤክስ ባንድ ጋር ተጠቃልሎ ራስ ሆቴል ተቀጥሮ መሥራት ጀመረ፡፡ በሙዚቃ ሕይወቱ ውስጥ ብዙ ውጣ ውረዶችን እንዳሳለፈ የሚናገረው ማህሙድ ዘመኑ ለሙዚቀኞችም ሆነ ለሙዚቃ ዕድገት የተመቻቸ እንደሆነ ይገልጻል፡፡ እንደሚናገረው ከሆነ ይሔ ዕድገትም የተገኘውና እዚህ መድረስ የተቻለው በዱሮ ሙዚቀኞች መስዋዕትነት ነው፡፡ ‹‹እነዚህ ሙዚቀኞች አሻራቸውን ጥለው ማለፍ ችለዋል፤›› የሚለው ማህሙድ በዚያን ጊዜ የነበሩት ሙዚቀኞች ምንም እንኳን ችሎታው ቢኖራቸውም የሙዚቃ ትምህርት ቤት አልሔዱም፡፡ የዚያን ጊዜውንም በማስታወስ ለሙዚቀኞች እንዴት ከባድ እንደነበር ይናገራል፡፡ ሙያውም እንዴት ይናቅ እንደነበርም ያስታውሳል፡፡ በ1963 ከአይቤክስ ባንድ ጋር ራስ ሆቴል በሚሠራበት ወቅት ‹‹ኩሉን ማን ኳለሽ››፣ ‹‹አምባሰል››፣ ‹‹ችቦ አይሞላም ወገቧ›› እና ‹‹አልማዝ ምን ዕዳ ነው›› የመሳሰሉ ዘፈኖችን ይዘፍን ነበር፡፡ እነዚህ ዘፈኖች ከአንዳንድ ወገኖች ከፍተኛ ትችትም አጋጠመው፡፡ የዱሮ ዘፈኖችን በአዲስ መልክ ትጫወታለህ ለማለት አንድ ጋዜጠኛ ‹‹ፍራሽ አዳሽ›› ብሎ የጠራውን አጋጣሚም አሁንም አይረሳውም፡፡ ‹‹አላዘንኩም፡፡ የዱሮ ዘፈኖችን አዲስ ሕይወት በመስጠት ዘፍኛለሁ፡፡ ፍራሽም እንደ አዲስ ሲታደስ ይተኛበታል›› ይላል፡፡ ማህሙድ ከዚህም በተጨማሪ ‹‹ዓባይ ማዶ››፣ ‹‹ደኑን ጥሰሽ›› እና ‹‹የት ነበርሽ›› የሚሉት ዘፈኖቹም የተለየ ርዕዮተ ዓለም ያስተላልፋሉ በሚልም ተወቅሶ ነበር፡፡ የማህሙድ ዓለም አቀፍ ዕውቅና የመጣው ፍራንሲስ ፋልሴቶ ኢትዮጲክስ የሚለውን የሙዚቃ ስብስብ ካወጣ በኋላ ሲሆን ማህሙድም ውለታውን የረሳ አይመስልም፡፡ ፋልሴቶ ፈረንሣዊ ፕሮሞተር ሲሆን የማህሙድን ‹‹መላ መላ›› የሚለውን ዘፈን ሬዲዮ ላይ ሰምቶ አብረን እንሥራ ብሎ ጠየቀው፣ ማህሙድ መጀመሪያ ላይ ተጠራጥሮ እንደነበር ያስታውሳል፡፡ እየተደራደሩ ባሉበት በ1960ዎቹ አካባቢ ማህሙድ ወደ ፈረንሣይ አቅንቶ ሙላቱ አስታጥቄ ጋር አብሮ ዘፍኗል፡፡ በዚያችው ከተማም ማይክል ጃክሰን በዚያው ምሽት ዘፍኗል፡፡ ከተመለሰም በኋላ ነው ኢትዮጲክስ የወጣው፡፡ በዚሁ መድረክ ላይ አዲስ እየሠራው ያለውን ‹‹አብራኝ ናት›› ስለሚለው ዘፈኑም ተናግሯል፡፡ አዳራሽ ውስጥ እየጠቆመ ምን ያህል እንደሚያፈቅራትም ተናግሯል፡፡ ‹‹አብራኝ ናት ከልጅነት እስከ ዕውቀት አብራኝ ናት፡፡ እዚሁ አለች በመንፈስም በሥራዎቼም ውስጥ አብራኝ ናት፡፡ እዚህ ለመድረሴም ምክንያት እሷ ናት፡፡ ትመክረኛለች፤ ከዓመታት በፊት ‹‹አልማዝ አልማዝዬ›› ብዬ ዘፍኘላታለሁ፤ አሁን ደግሞ ‹‹አብራኝ ናት ብዬ›› እዘፍንላታለሁ፤›› ብሏል፤ ማህሙድ፡፡
1687
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%A3%E1%89%A2%E1%88%8E%E1%8A%95%20%E1%8C%8D%E1%8A%95%E1%89%A5
የባቢሎን ግንብ
በመጽሐፍ ቅዱስ ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 11 ዘንድ፣ የባቢሎን ግንብ ሰማይን እንዲደርሱ የተባበሩት ሰው ልጆች የሠሩ ግንብ ነበር። ያ ዕቅድ እንዳይከናወንላቸው ለመከልከል፣ እግዚአብሔር እያንዳንዱ በተለየ ቋንቋ እንዲናገርበት ልሳናታቸውን አደባለቀ። መግባባት አልተቻላቸውምና ስራው ቆመ። ከዚያ በኋላ፣ ሕዝቦቹ ወደ ልዩ ልዩ መሬት ክፍሎች ሄዱ። ይህ ታሪክ ብዙ የተለያዩ ዘሮችና ቋንቋዎች መኖሩን ለመግለጽ እንደሚጠቅም ይታስባል። ከዕብራይስጥ ብሉይ ኪዳን የባቢሎን ግንብ (ዘፍ. 11፡1-9) ምድርም ሁሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች። ከምሥራቅም ተነሥተው በሄዱ ጊዜ በሰናዖር ምድር አንድ ሜዳ አገኙ፤ በዚያም ተቀመጡ። እርስ በርሳቸውም፦ ኑ፣ ጡብ እንሥራ፣ በእሳትም እንተኲሰው ተባባሉ። ጡቡም እንደ ድንጋይ ሆነላቸው፤ የምድርም ዝፍት እንደ ጭቃ ሆነችላቸው። እንዲህም፦ ኑ ለእኛ ከተማና ራሱ ወደ ሰማይ የሚደርስ ግንብ እንሥራ፤ በምድር ላይ ሳንበተንም ስማችንን እናስጠራው አሉ። እግዚአብሔርም የአዳም ልጆች የሠሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ። እግዚአብሔርም አለ፡ - እነሆ፣ እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፣ ለሁሉም አንድ ቋንቋ አላቸው፤ ይህንም ለማድረግ ጀመሩ፤ አሁንም ያሰቡትን ሁሉ ለመሥራት አይከለከሉም። ኑ፣ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው። እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተዉ። ስለዚህም ስምዋ ባቢሎን ተባለ፣ እግዚአብሔር በዚያ የምድርን ቋንቋ ሁሉ ደባልቋልና፤ ከዚያም እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ እነርሱን በትኖአቸዋል። የሰው ልጆች ሁሉ አንድ ኅብረተሰብ ሆነው የሠፈሩባት አገር ሰናዖር ለኤፍራጥስ ወንዝ ቅርብ ነበረች። ባቢሎን በጥንታዊ አካድኛ ምንጭ በተገኘ ባቢሉ (ባብ-ኢሉ) ማለት «የአማልክት በር» ለማለት ነው። በዕብራይስጥ ትርጉም ግን የ«ባቤል» ስም «መደባለቅ» ለማለት ለሚለው ቃል ይመስላል። ከውድቀቱ በፊት የተናገረው ቋንቋ አንዳንዴ «የአዳም ቋንቋ» መሆኑ ይባላል። በታሪክ አንዳንድ ሰው በግምት ያም ሆነ ይህ ቋንቋ መጀመርያው ቋንቋ እንደ ነበር የሚለው ክርክር አቅርቧል። ለምሳሌ ቋንቋው ዕብራይስጥ፣ አራማይስጥ፣ ግዕዝ ወይም ባስክኛ ቢሆንም እንደ ነበር በልዩ ልዩ አስተያየቶች ዘንድ ተብልዋል። በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 10 ባቢሎን ከተማ የናምሩድ ግዛት መጀመርያ እንደ ነበር ይላል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ያለው አፈ ታሪክ በሱመር (ሳንጋር) አፈ ታሪክ ተመሳሳይ ተረት አለ። በኤንመርካርና የአራታ ንጉስ የኡሩክ (ኦሬክ) ንጉስ ኤንመርካር አንድ ታላቅ መቅደስ በኤሪዱ ሲሠራ ለግንቡ የወርቅና የዕንቁ ግብር ከአራታ ያስገድዳል። አንድ ጊዜ 'ኤንኪ' የተባለውን አምላክ ኗሪ ያለባቸው አገሮች ሁሉ ወደ አንድ ቋንቋ እንዲመልሳቸው ይለምናል። (በሌላ ትርጉም ግን ኤንኪ የአገሮች ቋንቋ እንዲያደባለቅ ይላል።) እነዚህ አገሮች ስሞች ሹባር፣ ሐማዚ፣ ሱመር፣ ኡሪ-ኪ (የአካድ ዙሪያ) እና የማርቱ አገር ይባላሉ። በአንድ ዘመናዊ አስተሳሰብ መሠረት፣ የኤንመርካር መታወቂያ የብሉይ ኪዳን ናምሩድ አንድ ነው በመገመት የባቢሎን ግንብ ፍርስራሽ በውኑ ኤሪዱ በሚባል ከተማ ውስጥ ይገኛል ይላል። በዚህ ሀሳብ ኤሪዱ መጀመርያይቱ «ባቤል» እንደ ነበረች ማስረጃ ያቀርባል። 447 ከክርስቶስ በፊት የግሪክ ታሪክ መምህር ሄሮዶቱስ በባቢሎን ከተማ ስለተገኘ ታላቅ ግንብ ጻፈ። ይህ ምናልባት ሜሮዳክ የተባለው ጣኦት ቤተ መቅደስ ነበር፤ አንዳንድ ሊቅ ይህ መቅደስ የባቢሎን ግንብ ታሪክ ምንጭ እንደ ነበር የሚል እምነት አለው። 570 ከክርስቶስ በፊት የባቢሎን ንጉስ ናቡከደነጾር እንዲህ ብሎ ጻፈ፦ የዱሮ ንጉስ «የምድር ሰባት ብርሃናት» ቤተ መቅደስ አገነባ፤ ነገር ግን ራሱን አልጨረሰም። ከጥንት ጀምሮ ሰዎች ያለ ስርዓት ቃላቸውን ሳይገልጹ ትተውት ነበር። ከዚያ በኋላ መንቀጥቀጥና መብራቅ ደረቁን ሸክላ በትነውት ነበር፤ ጡቦቹ ተሰንጥቀው የውስጡ መሬት በክምር ተበትኖ ነበር። ትልቁ ጌታ ሜሮዳክ ሕንፃውን ለመጠገን አእምሮዬን አስነሣ። ሥፍራውን አላዛወርኩም፤ ዱሮ እንደነበር መሠረቱን አልወሰድኩም። እንግዲህ እኔ መሰረትኩት፤ ሠራሁት፤ በጥንት እንደነበር፣ ጫፉን እንዲህ ከፍ አደረግኩት። በአይሁድና በዲዩተሮካኖኒካል ሥነ ጽሁፍ በኦሪተ ዘፍጥረት እግዚአብሔር ግንቡን እንዳጠፋው ወይም ሥራውን ዝም ብሎ እንዳቆመ ምንም አይለንም። መጽሐፈ ኩፋሌ ግን በታላቅ ንፋስ ግንቡን እንዳገለበጠ ይመሰክራል። የድሮ ታሪክ ጸሐፊዎች አብዴንስ፥ ቆርኔሌዎስ አሌክስንድሮስ እና ዮሴፉስ እንዲሁም የሲቢሊን ራዕዮች ሁላቸው ግንቡ በንፋሶች እንደ ተገለበጠ ጻፉ፡ መጽሐፈ ኩፋሌ መጽሐፈ ኩፋሌ ስለ ግንቡ ብዙ ይላል። ...በአራተኛው ሱባዔ ጡቡን ሠርተው በእሳት ተኰሱ። ጡቡም እንደ ድንጋይ ሆነላቸው፤ የሚመርጉበት ጭቃውም ከባሕር በሰናዖር አገርም ከውኃዎች ምንጭ የሚወጣ የባሕር አረፋን ሆነላቸው። በአርባ ሦስት ዓመት ሠሩት። ፍጹም ጡብ አድርገው ሲሠሩት ኖሩ። ወርዱ ሦስት ክንድ፣ ቁመቱ አሥር ክንድ፣ አንድ ወገን የሚሆን አቈልቋዩ ሦስት ክንድ ነው። ቁመቱ አምስት ሺህ ከአራት መቶ ከሠላሳ ሦስት ክንድ ከሁለት ስንዝር ወደ ሰማይ ወጣ። አቈልቋዩ አሥራ ሦስት ምዕራፍ ነው... የአይሁድ ሚድራሽ የአይሁድ ረቢዎች ሥነ ጽሑፍ ስለ ባቢሎን ግንብ ማገንባት ምክንያቶች የተለያዩ አስተያየቶች ያቀርባሉ። በእግዚአብሔር ላይ አመጽ እንደ ማድረግ ሚሽና ይቈጥረዋል። የግንቡ ሰሪዎች በአንዳንድ አይሁዳዊ ምንጭ ደግሞ «የመነጣጠል ትውልድ» ይባላሉ። እነሱ፦ «እግዚአብሔር ላየኛውን አለም ለራሱ ለመምረጥ ታቸኛውንም ለኛ ለመልቀቅ መብት የለውም፣ ስለዚህ ግንብ እንስራ፣ በጫፉም ሰይፍ የያዘ ጣኦት ይኑር፤ ከእግዚአብሔር ጋራ መዋጋት የምናስብ እንዲታይ» እንዳሉ ሚድራሽ ደግሞ ይጽፋል። አንዳንድ ጽህፈት ደግሞ አብርሃም አስጠነቀቃቸውና ሰሪዎቹም የተቃወሙ አብሪሃም ነበር ይላል። ከዚያ በላይ በየ1656 አመታት ወሃ በምድር አፍስሶ ሰማይ ስለሚንገዳገድ እንግዲህ ማየ አይህ እንዳይዳግምብን በዓምዶች እንደግፈው ማለታቸው በአይሁዶች ታሪክ ማንበብ ይቻላል። እንኳን ተልሙድ በተባለ አይሁዳዊ መጽሐፍ ስለ ግንቡ ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር መዋጋት እንደ ፈለጉ ይመዝገባል። ፍላጻ ወደ ሰማይ ልከው በደም ተቀብቶ ሲመለስ ተበረታቱ ይላል። ጆሲፉስና አንድ ሚድራሽ ናምሩድ የስራ እቅዱ መሪ እንደ ነበር ይጽፋሉ። 3 ባሮክ ክግሪክና ከስላቮኒክ ቅጂ ብቻ የሚታወቀው 3 ባሮክ ስለ ግንብ ሲያውራ ለአይሁዳዊው ልማድ ሊስማማ ይችላል። ባሮክ በራእይ መጀመርያ የነፍሶች እረፍት ቦታ ለማየት የወሰዳል። እነዚህ በእግዚአብሔር ላይ የሁከት ግንብ የሰሩ ይባላሉ። ከዚያ በኋላ ሌላ ቦታ ያያል፣ እዚያም በውሻ መልክ፣ ግንቡን ለመስራት የመከሩ ናቸው፣ የምታያቸው ብዙ ወንድንና ሴት ጡብ ለመስራት ነዱአቸውና፤ ክነዚህም አንዲት ጡብ የምትሰራ ሴት በመውለድዋ ሰዓት ልትፈታ አልተፈቀደችም፤ ነገር ግን ጡብ እየሰራች ወለደች፤ ልጅዋንም በሽርጥዋ ውስጥ ተሸከመች፤ ጡብንም መስራትዋን አላቋረጠችም። ገታም ታያቸው ንግግራቸውንም ደባለቀ፤ ይህም ግንቡ ለ463 ክንድ ቁመት በሰሩት ጊዜ ሆነ። መሠርሠርያንም ይዘው ሰማይን ለመውጋት አሰቡ፣ እንዲህ ሲሉ፦ ሰማይ ሸክላ ወይም ነሃስ ወይም ብረት መሆኑን እናውቅ። እግዜር ይህንን አይቶ አልፈቀደላቸውም፤ ነገር ግን አሳወራቸው ንግግራችውንም ደባለቀ፤ አንተም እንደምታያቸው አደረጋቸው። በቁርዓንና በእስልምና በስም ባይታወቅም፣ የባቢሎንን ግንብ የሚመስል ንባብ በቁርዓን ውስጥ ይገኛል። በሱራ 28፡38 እና 40፡36-37 እንደሚለው፣ ፈርዖን ወደ ሰማይ ወጥቶ የሙሴን አምላክ እንዲቃወም ሐማንን የሸክላ ግንብ እንዲሰራለት ጠየቀው። በሱራ 2:96 ደግሞ የ'ባቢል' ስም ቢገኝም ብዙ ተጨማሪ ዝርዝር አያቀርብም ። ይሁንና በያቁጥ አል ሃርናዊ ጽሕፈት እና ልሳን ኤል አራብ በተባለ መጽሐፍ ዘንድ ስለ ግንብ ምንም ባይጻፍም የሰው ልጆች 'ባቢል' ወደሚባል ሜዳ በንፋሶች ሃይል ተወስደው እዚያ አላህ ለየወገናቸው ልዩ ልዩ ቋንቋ እንደ መደባቸውና ንፋሶች ከዚያ ሜዳ እንደ በተናቸው ይተረታል። በ9ኛ መቶ ዘመን የነቢያትና የነገሥታት ታሪክ የጻፉት የእስላም ታሪከኛ ሙሐመድ እብን ጃሪር አል-ታባሪ ይህን የመሰለ ተረት ያቀርባል ። በዚህ መሠረት ናምሩድ ግንቡን አስገንቦ አላህ አጠፋውና የሰው ልጅ ቋንቋ ከዚያ ቀድሞ የሶርያ (አራማያ) ሲሆን የዛኔ ወደ 72 ልሣናት ይደባለቃል። ከዚያ በላይ ደግሞ በ13ኛ መቶ ዘመን የጻፉት ሌላ የእስላም ታሪከኛ አቡ አል-ፊዳ ይህን መሰል ታሪክ ሲያወራ የአብርሃም ቅድመ-አያት ዔቦር ግንቡን ለመሥራት እምቢ ስላለ የፊተኛው ቋንቋ ዕብራይስጥ እንዲቀርለት ተፈቀደ ብሎ ይጽፋል። መጽሐፈ ሞርሞን የሞርሞኖች መጽሐፍ መጽሐፈ ሞርሞን ስለ ግንቡ ካለበት መረጃ አብዛኛው ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ይስማማል። በተጨማሪም በመጽሐፈ ኤጠር ዘንድ የያሮዳውያን ወገን ቋንቋቸው ሳይደባለቅ ወጥተው በስሜን አሜሪካ ሠፈሩ። ነገር ግን እነኚህ «ያሮዳውያን» የሚባል ሕዝብ እስከ ዛሬ በተገኘ ከሞርሞን በተቀር በምንም ሌላ እምነት ጽሁፍ አልታወቁም። በሌሎች ባህሎች አፈታሪክ በሜክሲኮ እና በማዕከል አሜሪካ አፈታሪክ ውስጥ ለባቢሎን ግንብ በጣም ተመሳሳይ ተረቶች አሉ። ለምሳሌ በአንድ ተረት ዘንድ፣ ሸልኋ ከማየ አይህ ያመለጡ 7 ራጃጅሞች አንዱ ሲሆን፣ ሰማይን ለመውረር ታላቅ ፒራሚድ በቾሉላ ሠራ። አማልክት ግን በእሳት አጥፈውት የሠሪዎቹን ቋንቋ አደናገሩ። የስፓንያዊው መነኩሴ ዲየጎ ዱራን (1529-1580 የኖሩ) ሜክሲኮ ከተወረረ በኋላ ይህንን ተረት ከባለ መቶ አመት ቄስ ሰምተው ጻፉበት። እንዲሁም ጥንታዊ ቶልቴክ ሕዝብ ሌላ ትውፊት እንደ ነበራቸው ኗሪው የታሪክ ሊቅ ዶን ፈርዲናንድ ዳልቫ እሽትልሾችትል ይጠቅሳል። በዚህ ተረት ከታላቅ ጎርፍ በኋላ የሰው ልጆች በዝተው ሌላ ጎርፍ እንዳይዳግምባቸው አንድ ረጅም ግንብ ሠሩ ይላል። ነገር ግን ልሳናታቸው ተደባልቀው ወደ ተለያዩ አገሮች ተጓዙ። እንደገና ሌላ ትውፊት በአሪዞና ቀይ ኢንዲያኖች ጎሣ በቶሆኖ ኦኦዳም ብሔር መካከል ይገኛል። በዚህ መሠረት ሞንተዙማ የሚባል ሃያል ከታልቅ ጎርፍ ከማምለጡ በኋላ እጅግ ክፉ ሆነና እስከ ሰማይ ድረስ የሚረዝም ቤት ለመሥራት ቢሞክር 'ታላቁ መንፈስ' በመብራቅ አጠፋው። ከዚያ በላይ በታዋቂው መርማሪ ዶክቶር ሊቪንግስተን ዘንድ በ1871 ዓ.ም. በንጋሚ ሀይቅ አፍሪቃ ተመሳሳይ ተረት አገኙ። በዚህ ትርጉም ግንቡ ሲወድቅ የሠሪዎቹ ራሶች ተሰባበሩ። ጸሐፊው ጄምስ ጆርጅ ፍሬዘር ደግሞ የሊቪንግስተን ወሬ በሎዚ ጎሣ አፈ ታሪክ ከሚገኝ ተረት ጋር ግንኙነቱን አጠቁሟል። በዚህ ተረት ዘንድ፣ ፈጣሪ አምላካቸው 'ኛምቤ' ወደ ሰማይ በሸረሪት ድር ሸሽቶ ክፉ ሰዎች እንዲያሳድዱት ከተራዳዎች ግንብ ቢሠሩም ተራዳዎቹ ግን ሲወድቁ ሰዎቹ ይጠፋሉ። በተጨማሪ በአሻንቲ ጎሣ እንዲህ መሰል ተረት ሲያገኝ በተራዳዎቹ ፈንታ ግን ግንቡ የተሠራ ከአጥሚት ዘነዘናዎች ክምር ነው። ፍሬዘር ደግሞ እንደነዚህ ያሉ ትውፊቶች በኮንጎ ሕዝብ እና በታንዛኒያ ጠቅሶአል፤ በነዚህ ትውፊቶች ሰዎቹ ወደ ጨረቃ ለመድረስ ሲሞክሩ ተራዳዎች ወይም ዛፎች ይከምራሉ።. ይህን የመሠለ ታሪክ ደግሞ በጣሩ ሕዝብ እንዲሁም በካርቢና በኩኪ ብሔሮች በስሜን ሕንድ ተገኝቷል። ከዚህ በላይ በምየንማ የሚኖረው ካሬን ሕዝብ ያላቸው ልማድ ይህን አይነት ተጽእኖ ያሳያል። በዚያ ልማድ መሠረት፣ ከአዳም 30 ትውልዶች በኋላ በካሬን-ኒ አገር ታላቅ ግንብ በተተወበት ቋንቋዎችም በተደባለቀበት ጊዜ የካሬን ቅድማያቶች ከካሬን-ኒ ተለይተው ወደ አገራቸው እንደ ፈለሱ ይባላል። እንደገና በአድሚራልቲ ደሴቶች ሌላ አፈታሪክ ሰዎች እስከ ሰማይ ድረስ ታላቅ ቤቶች ለማድረስ ሞክረው ከወደቁ በኋላ ልሳናታቸው ተደባለቁ ይላል። የግንቡ ቁመት ኦሪት ዘፍጥረት ስለ ግንቡ ቁመት (ከፍታ) ምንም ባይነግረንም፣ በሌላ ምንጭ ግን ልዩ ልዩ መልስ ሊገኝ ይቻላል። መጽሐፈ ኩፋሌ 5,433 ክንድ እንደ ደረሰ ሲል ይህ ከዛሬ ሕንጻዎች እንኳ በእጥፍ የሚልቅ ነው። እንዲሁም በ3ኛ ባሮክ መሠረት እስከ 463 ክንድ (212 ሜትር) ድረስ መሆኑን ሲነግረን ይህ ቁመት እስከ ዘመናዊው (1881 ዓ.ም.) አይፈል ግንብ ድረስ አልተበለጠም። ናቡከደነጾር ክ.በ. 570 አካባቢ ያሠራው ግንብ 100 ሜትር ገደማ ከፍ እንዳለ ይታመናል። በሌሎች ምንጭ ዘንድ፦ በ586 ዓ.ም. አካባቢ የጻፉት ታሪከኛ የቱር ጎርጎርዮስ የቀድሞውን ታሪከኛ ኦሮስዮስን (409 ዓ.ም. አካባቢ) ሲጠቅሱ፣ ስለ ግንቡ ቁመት 200 ክንድ ይሰጣል። በ1292 ዓ.ም. - ጣልያናዊው ጸሐፊው ጆቫኒ ቪላኒ እንዳለው፣ የግንቡ ከፍታ እስከ 4000 ፔስ (ፔስ = 1 ሜትር ያሕል) ድረስ ዘረጋ፣ ደግሞ ዙሪያው 80 ማይል ነበር። የ14ኛ ክፍለ ዘመን ጉዞኛ ጆን ማንደቪል ደግሞ ስለ ግንቡ ሲገልጽ ቁመቱ 64 ፉርሎንግ (8 ማይል ያሕል) ደረሰ ብሎ ጻፈ። የ17ኛ ክፍለ ዘመን ታሪከኛ ፈርስቴገን ስለ ከፍታው 5164 ፔስ (7.6 ማይል) ይላል። ከዚህ በላይ ወደ ላይ የሚወስደው ጠምዛዛ መንገድ በይበልጥ ሰፊ በመሆኑ ለሠራተኞችም ሆነ ለእንስሶች ማደሪያ ለመስራት እንኳ የመኖ እርሻ ለመብቀል በቂ እንደ ነበር ይጽፋል። የተበተኑት ልሳናት አቆጣጠር ከመካከለኛው ዘመን ጽነ ጽሁፍ መካከል በባቢሎን ግንብ የተበተኑትን ልሳናት ለመቆጠር የሚሞክሩ ታሪኮች ብዙ ናቸው። በኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 10 ውስጥ የኖህ ተወላጆች ስሞች ሁሉ ሲቆጠሩ ለያፌት ልጆች 15፣ ለካም ልጆች 30፣ ለሴም ልጆች 27 ስሞች ይሠጣል። እነዚህም ቁጥሮች ከባቤል (ባቢሎን) መደባለቅ የወጡት 72ቱ ልሣናት ሆነው ተመሠረቱ፤ ሆኖም የቋንቋዎች መታወቂያ በጊዜ ላይ ይለያይ ነበር። (የዕብራይስጥ ትርጉም ግን የይልሳና የቃይንም ስሞች ስለሌለው አይሁዳዊ ምንጮች እንደ ሚሽና ስለ '70 ልሳናት' ይናገራሉ።) 72 (ወይም 73) ልሳናት የሚሉ ጥንታዊ ምንጮች ክርስቲያናዊው ጸሐፊዎች የእስክንድርያ ቄሌምንጦስና አቡሊደስ (2ኛ ክፍለ ዘመን) እንዲሁም በ350 ዓ.ም. ገዳማ የተጻፈው በዓተ መዛግብት፤ በ365 ዓ.ም. ገደማ ፓናሪዮን የጻፉት የሳላሚስ ኤጲፋንዮስና በ404 ዓ.ም. ገደማ የግዜር ከተማ የጻፉት ቅዱስ አውግስጢኖስ ናቸው። የሴቪሌ ኢሲዶሬ (625 አካባቢ) ስለ 72 ቋንቋዎች ቢያወራ ከኦሪት ስሞቹን ሲዘረዝር ግን የዮቅጣን ልጆች ቀርተው የአብርሃምና የሎጥ ልጆች ተተኩ፤ ስለዚህ 56 ስሞች ብቻ አሉ። ከዚያ በራሱ ዘመን ከታወቁት ወገኖች እንደ ላንጎባርዶችና ፍራንኮች ይዘረዝራል። ከዚሁ ሂሳብ ተጽእኖ የተነሣ በኋለኞቹ ታሪኮች ለምሳሌ በአይርላንድ መንኩሳዊ መጻሕፍት አውራከፕት ና ኔከሽና የ11ኛ ክፍለ ዘመን ሌቦር ጋባላ ኤረን እንዲሁም በአይሁዳዊው ሚድራሽ መጽሐፈ ያሸር፤ ሎምባርዶችና ፍራንኮች እራሳቸው የያፌት ልጅ ልጆች ስሞች ሆኑ። ከነዚህ ሌሎች ከባቤል ስለተበተኑት ስለ 72 (ወይም 70) ልሣናት የሚናገሩት ምንጮች ብዙ ናቸው። ከነሱም፡ የነቢያትና የነገሥታት ታሪክ ከእስላማዊው መሐመድ እብን ጃሪር አል-ታባሪ (9ኛ ክፍለ ዘመን)፤ የጥንታዊ እንግሊዝኛ ግጥም ሰሎሞንና ሳቱርን፤ አይሁዳዊው ካባላ ጽሑፍ ባሒር (1166 ዓ.ም.)፤ የአይስላንዳዊው ስኖሪ ስቱርሉሶን ንዑስ ኤዳ (1190 ዓ.ም. አካባቢ)፤ በጽርዕ የተጻፈው መጽሐፈ ንቡ (1214 ዓ.ም.)፤ ጌስታ ሁኖሩም ኤት ሁንጋሮሩም (1276 ዓ.ም.)፤ የጆቫኒ ቪላኒ ታሪክ (1300 ዓ.ም.)፤ እና አይሁዳዊው ሚድራሽ ሃ-ጋዶል (14ኛ ክ.ዘ.) ናቸው። በቪላኒ ትርጉምም ግንቡ «ከማየ አይህ በኋላ 700 አመት ተጀምሮ ከአለሙ ፍጥረት እስከ ባቢሎን ግንብ መደባለቅ ድረስ 2354 አመቶች ነበሩ። በስራ ላይ ለ107 አመታት እንደ ቆዩም እናገኛለን፤ ሰዎች በዛኛ ዘመን ለረጅም ዕድሜ ይኖሩ ነበርና።» በጌስታ ሁኖሩም ኤት ሁንጋሮሩም መሠረት ግን ሥራ እቅዱን ከማየ አይህ በኋላ 200 አመት ብቻ ጀመሩ። የ72ቱ ቋንቋዎች ልማድ እስከ ኋለኛ ዘመን ድረስ ቆየ። ስፓንያዊው ሆዜ ዴ አኮስታ በ1568 ዓ.ም. ከዚህ ቁጥር አብልጦ በፔሩ ብቻ ስንት መቶ እርስ በርስ የማይግባቡ ቋንቋዎች እንዳገኘ ተገረመ፤ ከመቶ አመት በኋላ እንደገና ፖርቱጊዙ አንቶኒዮ ቪዬራ ስለ ብራዚል ቋንቋዎች ብዛት ተመሳሳይ አስተያየት አቀረበ። ዘመናዊ ባሕል የባቢሎን ግንብ በዘመናዊ ልብ ወለድ ታሪክ፣ ፊልሞችና ጨዋታዎች ሚና ተጫውቷል። ለምሳሌ ባንድ ደራሲ ኒል ስቲቨንሶን ልብ ወልደ ታሪክ ስኖ ክራሽ፣ የግንቡ ትርጉም ሰዎች ወደ ሰማይ በመንኮራኩር የመድረስ ሙከራ ምሳሌ ነው። እንደገና በሌላ ልብ ወለድ፣ የዳግላስ አዳምስ ዘ ሂችሃይከርስ ጋይድ ቱ ዘ ጋላክሲ፣ የባቤል ዓሣ በጆሮ ውስጥ ሲገባ ማንኛውንም ቋንቋ ለማስተርጉም ችሎታ አለው። በ1920 ፊልሙ ሜትሮፖሊስ፣ የባቢሎን ግንብ በአለማዊ መንግሥት ሁለተኛ ይሰራል። ከዚሁ በላይ የባቢሎን ግንብ በበርካታ የኮምፒዩተርና የቪዴዮ ጨዋታዎች ውስጥ ይታያል። እነሱም ዚኖጊርስ፣ ፋይናል ፋንታሲ 4፣ ዱም፣ ፕሪንስ ኦፍ ፐርዝያ፡ ዘ ቱ ስሮንስ፣ ዶሺን ዘ ጃየንት፣ ሲሪየስ ሳም፡ ሰከንድ እንካውንተር፣ ፍሪስፔስ 2፣ ፔንኪለር፣ ኢሉዠን ኦቭ ጋያ፣ እና ክሩሴድር ኦቭ ሰንቲ የሚባሉ የቪዴዮ ጨዋታዎች ናቸው። እንዲሁም ሻዶው ኦቭ ዘ ኮሎሰስ፣ ሲቪላይዜሸን 3፣ ዴቪል መይ ክራይ 3፣ እና ሜጋ ማን ኤክስ፡ ኮማንድ ሚሸን በሚባሉ ጨዋታዎች የባቢሎን ግንብ ምሳሌዎች ሊታዩ ይችላሉ። መጽሐፍ ቅዱስ
2802
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8B%E1%8A%95%20%E1%8B%AA%E1%8A%95%E1%8C%8D
ጋን ዪንግ
ጋን ዪንግ () በ89 ዓ.ም. በቻይና አበጋዝ ባን ቻው ወደ ሮማ የተላከ የቻይና ተልእኮ ተወካይ ነበር። ወደ ጳርቴ ምዕራብ ጠረፍ ከገሰገሱት ከባን ቻው ሳባ ሺህ ጭፍሮች አንዱ ነበር። ጋን ዪንግ ምናልባት እስከ ሮማ ከተማ ድረስ መቸም ባይደርስም፣ በታሪካዊው መዝገብ እንደተመለከተው ከቻይናውያን ሁሉ በጥንት ወደ ምዕራብ የተጓዘው እሱ ሲሆኑ የተቻለውን መረጃ ስብስቦ ተጽፎ ነበር። ሆው ሀንሹ በተባለው በቻይና ኋለኛው ሃን ስርወ መንግሥት (17-212 ዓ.ም.) ዜና መዋዕል ታሪክ ዘንድ፦ «በዘጠነኛው አመት (89 ዓ.ም.) ባን ቻው ምክትላቸውን ጋን ዪንግ ልከው እስከ ምዕራባዊው ባሕር ድረስ አማተሮ ተመለሰ። የቀደሙት ትውልዶች እነኚህን አቅራቢያዎች ከቶ ደርሰው አያውቁም ነበር። ሻንጂንግ የተባለው መጽሐፍ ስለነሱ ምንም ወሬ የለበትም። ስለነርሱ ልማዶች ምርመር እንዳዘጋጀ ብርቅና ትንግርት ዕቃዎቻቸውንም እንደ ተመራመረ አይጠራጠርም።» «በዘጠነኛው የዮንግዩዋን አመት (89 ዓ.ም.) በንጉስ ሄ ዘመን፣ ጠባቂ አበጋዝ ባን ቻው ጋን ዪንግን ወደ 'ዳ ጪን' (የሮማ መንግሥት) ልከውት ነበር። እስከ 'ትያውጅር' (ካራቄኔ) እና ሶስያና ድረስ ከታላቅ ባሕር አጠገብ ደረሰ። እሱንም መሻገር ፈልገው ነበር፣ ነገር ግን የአንሺ (ጳርቴ) ምዕራብ ጠረፍ መርከበኞች እንዲህ አሉት፦ 'ውቅያኖስ እጅግ ታላቅ ናትና ደርሶ መልስ ያደረጉ ንፋሶቹ ተስማሚ ከሆኑላቸው በሦስት ወሮች ውስጥ ሊጓዙት ይችላሉ። ዳሩ ግን የሚያቆዩህ ንፋሶች ቢያጋጥሙህ ሁለት አመታት ሊፈጅ ችሏል። ስለዚህ በባሕር ላይ የጓዙ ሰዎች ሁሉ የሶስት አመት ስንቅ ይወስዳሉ። ሰፊው ውቅያኖስ ሰዎች ስለ አገራቸው እንዲያሰቡ ይግፋፋቸዋል አገራቸውንም በጣም ይናፍቃሉ አንዳንዶችም ይሞታሉ።' ጋን ዪንግ ይህንን ሰምቶ አሳቡን ለቀቀው።» በሆው ሃንሹ ውስጥ በሌላ ክፍል ደግሞ እንዲህ ይላል፦ «የሮማ ግዛት ለብዙ ሺህ ሊ [1 ሊ ማለት ግማሽ ኪሎሜትር ያሕል] ይዘረጋል። ከአራት መቶ በላይ ባለ-ቅጥር መንደሮች ይገኙበታል። ብዙ አሥሮች ትንንሽ ጥገኛ መንግሥታት አሉት። የመንደሮችም ቅጥሮች የተሰሩ ከድንጋይ ነው። የፖስታ ጣቢያዎች በየስፍራው አቋቁመው ሁላቸውም የተመረጉና በነጭ ቀለም የተቀቡ ናቸው። ጥድና ዝግባ አለ፣ ደግሞም ዛፎችና አትክልት በየአይነቱ።» ጋን ዪንግ ደግሞ ስለ ሮማ ንጉስ ስለ ኔርቫ መንግስት ስለ ሮማውያንም መልክና ስለ ንግድ ዕቃዎቻቸው እንዲህ ሲል መግለጫ ሰጥቷል፦ «ንጉሶቻቸው ዘላቂ አይደሉም። እነሱ ከሁሉ የገባውን ዕጩ መርጠው ይሾሙታል። በግዛቲቱ ላይ ድንገተኛ መቅሰፍት ለምሳሌ ያልተለመደ ንፋስ ወይም ዝናብ ብዙ ጊዜ ቢደርስባት፣ ያለምንም ስነሥርዐት ተሽረው ይተካሉ። የተሻሩትም ዝም ብለው መሻራቸውን ተቀብለው አይቆጡበትም።» «የዚህ ሀገር ሕዝብ ሁሉ ረጅምና ቅን ናቸው። 'የማዕከል መንግስት' [ቻይና] ሕዝቦች ይመስላሉና ስለዚህ ይህ አገር 'ዳ ጪን' [ማለት ታላቁ ቻይና] ተብሏል። ይህች መሬት የምታስገኝ በርካታ ወርቅና ብር፣ ብርቅ ዕንቁዎችም ያብረቀረቀ ጌኛ፣ 'የብሩህ ጨረቃ ሉል'፣ የ'ሃይጂ' አውራሪስ፣ ዛጎል፣ ቢጫ ሙጫ፣ የተቀለመ ብርጭቆ፣ ነጭ ኬልቄዶን፣ ቀይ ቀለም ያለው ባዜቃ ድንጋይ፣ አረንጓዴ ዕንቁዎች፣ የወርቅ ፈተል ያለበት ጥልፍ፣ የተሸመነ ወርቅ ፈተል መረብ፣ በወርቅ የተቀባ ረቂቅ ግምጃ በየቀለሙ፣ የአዝቤስጦስም ጨርቅ ናቸው።» «ደግሞ አንዳንድ ሰዎች፦ ከ'ባሕር በጎች' ሱፍ ተሰራ ነው (የባሕር ሐር) የሚሉት በውኑ ግን ከተፈጥሮ ሐር ትል ጎጆ የተሠራ ረቂቅ ጨርቅ አላቸው። መዓዛዎችን በየአይነቱ ይቀላቁበታልና ጭማቂውን በመፍላት ውሑድ ሽቶ ይፈጥራሉ። ከተለያዩት ውጭ አገሮች የሚመጡ ብርቅና ውድ ነገሮች ሁሉ አሏቸው። የወርቅና የብር መሐለቅ ገንዘብ የሰራሉ። አሥር የብር መሐለቆች ዋጋ እንደ አንድ የወርቅ መሐለቅ ነው። ከ'አንሺ' (ጳርቴ) እና ከ'ትየንጁ' (ስሜን-ምዕራብ ሕንድ) ጋር በመርካብ ይነግዳሉ። የሚተርፉበት ለአንድ እጅ አሥር እጥፍ ነው። የዚሁ አገር ንጉስ ምንጊዜም ወደ ሃን [ቻይናዎች] ተወካዮችን ለመላክ ወድደው 'አንሺ' ግን የተቀለሙት የቻይና ግምጃዎች ንግድ ለመቆጣጠር ፈልገው ሮማውያን ወደ ቻይና እንዳይገቡ መንገዱን አገዱባቸው።» ታሪካዊ ተጓዦች የቻይና ታሪክ የቻይና ሰዎች
52795
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8D%E1%88%AB%E1%8A%95%E1%8A%AD%20%E1%88%B2%E1%8A%93%E1%89%B5%E1%88%AB
ፍራንክ ሲናትራ
ፍራንሲስ አልበርት ሲናትራ (ዲሴምበር 12፣ 1915 - መይ 14፣ 1998 እ.ኤ.አ.) አሜሪካዊ ዘፋኝ እና ተዋናይ ነበሩ። "የቦርዱ ሊቀመንበር" የሚል ቅጽል ስም ተሰጥቷቸው በኋላም «አሮጌ ሰማያዊ አይኖች» ተብለው የሚጠሩት ሲናትራ በ1940ዎቹ፣ 1950ዎቹ እና 1960ዎቹ ውስጥ በጣም ታዋቂ ከሆኑ አዝናኝ አዘጋጆች አንዱ ነበሩ። ወደ 150 ሚሊዮን የሚገመት የሪከርድ ሽያጭ ካላቸው የአለም ከፍተኛ ሽያጭ ካላቸው አርቲስቶች አንዱ ናቸው። በሆቦከን፣ ኒው ጀርሲ ከኢጣሊያውያን ስደተኞች የተወለዱ ሲሆን፣ በልጅነት ሲናታራ ለማናዳመጡ ቅርብና ቀላል ከሆነላቸው ከሚስተር ቢንግ ክሮዝቢ የድምጽ ቄንጥ የተነሣ አንድ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድረው ነበር። እና የሙዚቃ ስራውን በዥዋዥዌ ዘመን ከባንዲራዎች ሃሪ ጄምስ እና ቶሚ ዶርሴ ጋር ጀመረ። እ.ኤ.አ. በ 1943 ከኮሎምቢያ ሪከርድስ ጋር ከተፈራረመ በኋላ እንደ ብቸኛ አርቲስት ስኬት አገኘ ፣ “የቦቢ ሶክስሰሮች” ጣኦት ሆነ። ሲናትራ የመጀመሪያውን አልበሙን በ 1946 የፍራንክ ሲናራ ድምጽን አወጣ። በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ የፊልም ስራው ሲቆም ሲናትራ ወደ ላስ ቬጋስ ዞረ፣ እዚያም በጣም ከሚታወቁት የመኖሪያ ፈፃሚዎች አንዱ እና የታዋቂው የአይጥ ጥቅል አካል ሆነ። የትወና ስራው በ 1953 ከሄ እስከ ዘለአለም በተባለው ፊልም ሲናትራ የአካዳሚ ሽልማት እና የጎልደን ግሎብ ሽልማትን በምርጥ ደጋፊ ተዋናይነት አግኝቷል። ከዚያም ሲናትራ ከካፒቶል ሪከርድስ ጋር ተፈራርሞ በርካታ በጣም የተወደሱ አልበሞችን አወጣ፣ አንዳንዶቹም በኋላ እንደ መጀመሪያዎቹ “የፅንሰ-ሃሳብ አልበሞች” ተደርገው ተቆጠሩ፣ በዊን ትንሽ ሰአት ፣ ለስዊንጊን አፍቃሪዎች ዘፈኖች! ፣ ኑ ከእኔ ጋር ፍላይ ፣ ብቸኛ ብቸኛ ፣ ማንም አያስብም ፣ እና ። ሲናትራ በ1960 ካፒቶልን ለቆ የራሱን ሪፕሪስ ሪከርድስ የተባለውን የሪከርድ መለያ ለመጀመር እና በርካታ የተሳካ አልበሞችን ለቋል። እ.ኤ.አ. በ 1965 ሴፕቴምበር ኦፍ የእኔ ዓመታት አልበም ቀረጸ እና በኤምሚ አሸናፊ የቴሌቪዥን ልዩ ፍራንክ ሲናትራ፡ ሰው እና ሙዚቃው ላይ ተጫውቷል። በ1966 መጀመሪያ ላይ ከተደጋጋሚ ተባባሪ ካውንት ባዚ ጋር በቬጋስ ውስጥ በሚገኘው ሳንድስ ሆቴል እና ካዚኖ ተመዝግቦ የሚገኘውን ሲናትራን በአሸዋ ላይ ከለቀቀ በኋላ በሚቀጥለው ዓመት ከቶም ጋር ካደረጋቸው በጣም ታዋቂ የትብብር ስራዎች አንዱ የሆነውን አልበም ፍራንሲስ አልበርት ሲናትራ እና አንቶኒዮ ካርሎስ ኢዮቢም መዝግቧል። በ 1968 ፍራንሲስ ኤ እና ኤድዋርድ ኬ ከዱክ ኤሊንግተን ጋር ተከተለ። ሲናትራ በ 1971 ለመጀመሪያ ጊዜ ጡረታ ወጣ ፣ ግን ከሁለት ዓመት በኋላ ከጡረታ ወጥቷል ። ብዙ አልበሞችን ቀርጾ በቄሳርስ ቤተመንግስት ዝግጅቱን ቀጠለ እና በ1980 "ኒውዮርክ፣ ኒውዮርክ"ን ለቋል። የላስ ቬጋስ ትርኢቱን እንደ መነሻ በመጠቀም በ1998 ከመሞቱ ጥቂት ቀደም ብሎ በዩናይትድ ስቴትስ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ጎብኝቷል። ሲናትራ የፊልም ተዋናይ በመሆን ከፍተኛ ስኬታማ ሥራን ሠራ። ከዚህ እስከ ዘላለም በተሰኘው ምርጥ ደጋፊ ተዋናይ የአካዳሚ ሽልማትን ካሸነፈ በኋላ፣ በወርቃማው ክንድ ያለው ሰው እና የማንቹሪያን እጩ ውስጥ ተጫውቷል። ሲናትራ እንደ ኦን ዘ ታውን ፣ ጋይስ እና አሻንጉሊቶች ፣ ከፍተኛ ሶሳይቲ እና ፓል ጆይ ባሉ ሙዚቀኞች ውስጥ ታየ፣ ይህም ሌላ ወርቃማ ግሎብ አሸንፏል። በስራው መገባደጃ አካባቢ በቶኒ ሮም ውስጥ ያለውን የማዕረግ ባህሪ ጨምሮ መርማሪዎችን በተደጋጋሚ ይጫወት ነበር። ሲናትራ የጎልደን ግሎብ ሴሲል ቢ ደሚል ሽልማትን በ1971 ተቀበለ።በቴሌቪዥን ላይ የፍራንክ ሲናትራ ትርኢት በ1950 በሲቢኤስ የጀመረ ሲሆን በ1950ዎቹ እና 1960ዎቹ በሙሉ በቴሌቪዥን መታየት ቀጠለ። ሲናራ ከ1940ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ በፖለቲካ ውስጥ በጥልቅ የተሳተፈች እና ለፕሬዝዳንቶች ፍራንክሊን ዲ. ከማፍያ ቡድን ጋር ስላለው ግንኙነት በኤፍቢአይ ተመርምሯል። ሲናራ ሙዚቃን እንዴት ማንበብ እንዳለበት ባይማርም በሁሉም የሙዚቃ ዘርፎች ችሎታውን ለማሻሻል ከልጅነቱ ጀምሮ ጠንክሮ ሰርቷል። ፍጽምና ጠበብት፣ በአጻጻፉ እና በመገኘቱ የሚታወቅ፣ ሁልጊዜ ከባንዱ ጋር በቀጥታ ለመቅዳት አጥብቆ ጠየቀ። በቀለማት ያሸበረቀ የግል ህይወቱን ይመራ ነበር እና ከአቫ ጋርድነር ጋር ሁለተኛውን ጋብቻውን ጨምሮ በተጨናነቀ ግንኙነቶች ውስጥ ተሳትፏል። በኋላም በ1966 ሚያ ፋሮውን እና በ1976 ባርባራ ማርክስን አገባ።ሲናትራ ብዙ ሀይለኛ ግጭቶች ነበሯት፤ ብዙ ጊዜ ከጋዜጠኞች ጋር ተገናኝተው ወይም ከስራ አለቆቹ ጋር አለመግባባት ፈጠሩ። ሲናራ በ1983 በኬኔዲ ሴንተር ክብር ተሸላሚ ነበር፣ በ1985 በሮናልድ ሬጋን የፕሬዚዳንትነት ሜዳሊያ ተሸልሟል፣ በ1997 የኮንግረሱ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸልሟል። የግራሚ ባለአደራ ሽልማትን፣ የግራሚ አፈ ታሪክ ሽልማትን እና የግራሚ ሽልማትን ጨምሮ አስራ አንድ የግራሚ ሽልማቶችን አግኝቷል። የህይወት ዘመን ስኬት ሽልማት። በ20ኛው ክፍለ ዘመን 100 ከፍተኛ ተደማጭነት ያላቸውን ሰዎች በታይም መጽሄት ስብስብ ውስጥ ሲናትራ ተካትታለች። ሲናትራ ከሞተ በኋላ፣ አሜሪካዊው የሙዚቃ ሃያሲ ሮበርት ክሪስጋው “የ20ኛው ክፍለ ዘመን ታላቁ ዘፋኝ” ሲል ጠርቶታል እና እንደ ተምሳሌት ሰው መቆጠሩን ቀጥሏል። የአሜሪካ ዘፋኞች የአሜሪካ የፊልም ተዋናዮች
50954
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%8B%E1%89%85%E1%88%8B%E1%88%9A
ዋቅላሚ
የቃሉ መሰረታዊ አመጣጥ ዋቅላሚ የሚለው ቃል የተገኘው “ውሃ” እና “አቅላሚ” ከተሰኙ ሁለት የአማርኛ ቃላት ሲሆን “” ለሚለው የላቲን ቃል የአማርኛ አቻ ቃል ነው። ስያሜው እንደሚያመለክተው በዚህ መደብ ስር ያሉ ፍጡራን ውሃን የማቅለም ባህርይ አላቸው። ነጠላቁጥር የሆነውና አልጋ "" የተሰኘው ቃል በላቲን የባህር አረም "" ማለት ሲሆን በእንግሊዝኛም ተመሳሳይ ትርጉም አለው፡፡ የባህር አረም ''የሚለው ቃል በጥንታዊ ግሪክ ፋይኮስ ) ይባል የነበረ ሲሆን ትርጓሜውም የባህር አረም(ምናልባትም ቀይ ዋቅላሚ) ወይም ከቀይ ዋቅላሚ የሚገኝ ቀለም ማለት እንደነበር ይታመናል፡፡ የዋቅላሚ ጥናት ፋይኮሎጂ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን አልጎሎጂ የተሰኘው ቃል ከአገልግሎት ውጭ እየሆነ የመጣ ቃል ነው። ዋቅላሚ የሚለው ቃል ከተለያዩ ስርወዘራዊ ቡድኖች የተገኙ እና በተለያዩ የሥርዓተ ምደባ ዘርፎች ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ሕይወት ያላቸው ፍጡራንን የሚወክል ሰፊ ቡድን ነው። በአጠቃላይ ዋቅላሚዎች ስንል እያልን ያለነው፦ በአብዛኛው እውነተኛ ስር፣ግንድ፣ ቅጠል እና ሥርአተሸንዳ የሌላቸው ባለ ቀላል የመራቢያ መዋቅር የሆኑ እና ምግብሰሪ የሆኑ የውሃውስጥ ዕፅዋትመሰል ፍጡራንን ነው። በመላው ዓለም ማለትም፦ በባሕር፣ በጨው አልባ ዉሃማ አካላት እና እርጥበታማ የየብስ ክፍሎች ተሰራጭተው ይገኛሉ። አብዛኛዎቹ ሚክሮስኮፓዊ ሲሆኑ ጥቂቶች ግን በጣም ግዙፎች ናቸው። ለምሳሌ አንዳንድ የባሕር ውስጥ አረሞች () እስከ ፶ ሜትር ያህል ሊረዝሙ ይችላሉ። በውሃ ላይ የሚንሳፈፉ ዋቅላሚዎች ፋይቶፕላንክተን ይባላሉ፡፡ ዋቅላሚዎች ብዙ የመራቢያ ስልቶች አሏቸው፤ ክለኤ ቁርሰት ከተሰኘው ተራ ኢ-ጾታዊ የመራቢያ ስልት ውስብስብ እስከሆኑ ጾታዊ የመራቢያ ስልቶች ይታይባቸዋል፡፡ ስርዓተ ምደባ የአለምአቀፉ የእፅዋት ስያሜ ኮድ ኮሚቴ ለዋቅላሚ ስርዓተምደባ የሚያገለግሉ የተወሰኑ ቅጥያዎችን ለመጠቀም ምክረሃሳብ አቅርቧል፡፡ እነዚህም ቅጥያዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ -ፋይታ ለክፍለሰፍን፣ ፋይሲያይ ለመደብ፣ ፋይሲዲያይ ለንዑስ መደብ፣ አለስ ለክፍለመደብ፣ ኢናለስ ለንዑስ ክፍለመደብ፣ አሲያይ ለአስተኔ፣ ኦይዲስ ለንዑስ አስተኔ፣ የግሪክ መሰረት ያለው ስያሜ ለ ወገን፣ የላቲን መሰረት ያለው ስያሜ ለዝርያ ናቸው፡፡ ከ 800 በላይ የዋቅላሚ ወገኖች ሲኖሩ እያንዳንዱ የዋቅላሚ ወገን በስሩ የተለያዩ ዝርያዎችን ይይዛል። ለመጀመሪያ ደረጃ ምደባ መሰረት የሆኑ የዋቅላሚዎች ባህሪያት የዋቅላሚዎች የመጀመሪያ ደረጃ ምደባ የተወሰኑ የስነቅርፅ ገፅታዎች ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ከነዚህ ገፅታዎች መካከል ዋና ዋናዎቹ፡- (ሀ) የህዋስ የቀለም ተዋፅኦ፣ (ለ) የተከማቸ ምግብ ኬሚካላዊ ተፈጥሮ፣ (ሐ)የተንቀሳቃሽ ህዋሳት ልምጭት አይነት፣ ቁጥር፣ የመጋጠሚያ ነጥብ እና አንፃራዊ ርዝመት (መ)የህዋስ ግንብ መዋቅር እና (ሠ) በህዋሱ ውስጥ በትክክል የተደራጀ ኒውክለስ የመኖርና ያለመኖር ሁኔታ ወይም በተለየ ሁኔታ ጉልህ የሆነ የህዋስ መዋቅር ናቸው። ዋና ዋናዎቹ የዋቅላሚ ስርወዘራዊ ቡድኖች የሚከተሉት ናቸው አረንጓዴ ዋቅላሚዎች ( ባልጩት ዋቅላሚዎች ( ወርቃማ ዋቅላሚዎች ( ኢዩግሊኖፋይታ ( ዳይኖፍላጅላታ ( ቡናማ ዋቅላሚዎች ( ቀይ ዋቅላሚዎች ( ሰማያዊ አረንጓዴአማ ዋቅላሚዎች ( ስነ ቅርፅ ዋቅላሚዎች አስገራሚ የስነቅርፅ ተለያይነት የሚታይባቸው ፍጥረቶች ናቸው፡፡ ስነ ቅርፃቸው ላይ በመመስረት ዋቅላሚዎች ፡- አንድህዋሴ ዋቅላሚዎች፣ ኩይዋሳዊ ዋቅላሚዎች፣ዘሃዊ ዋቅላሚዎች፣ መቆ ዋቅላሚዎች እና ዥንቃዊ ዋቅላሚዎች በሚባሉ መደቦች ሊመደቡ ይችላሉ፡፡ 1. አንድ-ህዋሴ ዋቅላሚዎች ()፦ ህዋስግንብ ያላቸው የማይንቀሳቀሱ ነጠላ ህዋሳት ወይም በሚያጣብቅ ነገር ውስጥ ያሉ የማይንቀሳቀሱ ህዋሳት ናቸው። 2. ኩይዋሳዊ ዋቅላሚዎች()፦ የትናንሽ ተንቀሳቃሽ ህዋሳት መደበኛ ቡድኖች። 3. ዘሃዊ ዋቅላሚዎች()፦ እንደ ጨሌ ገመድ ሰንሰለት ሰርተው የተደረደሩ ህዋሳት ህዋሳት ናቸው። እንደ ስፓይሮጋይራ ያሉ ዝርያዎች ቅርንጫፍ ይሌላቸው ሲሆኑ እንደ ስቲጎኔማ ያሉት ደግሞ ቅርንጫፍ አላቸው። 4. መቆ ዋቅላሚዎች()፦ መቆ ዋቅላሚዎች የሚባሉት በአንድ ህዋስ ውስጥ ብዙ ኒውክለሶች ያሏቸው ፣ ማለትም በህዋስ ግንቦች ባልተከፋፈለ አንድ ቤተህዋስ ውስጥ ብዙ ኒውክለሶች የሚገኙበት የዋቅላሚ አይነት ነው፡፡ 5. ዥንቃዊ ዋቅላሚዎች()፦ ህብረህዋስ መሰል የሆነ ብቃይ አካል ያላቸው ዋቅላሚዎች ናቸው። ለምሳሌ በብዙ ሜትር የሚለካ ርዝመት ያለው ማክሮሲስቲስ ከዥንቃዊ ዋቅላሚዎች አንዱ ነው። ስነ ምሕዳር ዋቅላሚዎቸ በውሃ አካላት ውስጥ በስፋት ይገኛሉ፤ በየብስ ላይም በተለመደ መልኩ ይገኛሉ እንዲሁም በበረዶ አካላት ላይና ባልተለመዱ ቦታዎች ይገኛሉ። የባሕር ውስጥ አረሞች የሚባሉት ከ100 ሜትር በላይ ጥልቀት በሌላቸው የውሃ አካላት ውስጥ ይገኛሉ። ነገርግን እንደ ናቪኩላ ፔናታ ያሉ ዝርያዎች እስከ 360 ሜትር ጥልቀት ድረስ እንደሚገኙ ተመዝግቧል። የተለያዩ የዋቅላሚ ዝርያዎች ለውሃ ስነ ምህዳር ወሳኝ ሚና አላቸው። በውሃማ አካላት ውስጥ ተንሳፍፈው የሚገኙ ዋቅላሚዎች (ፋይቶፕላንክተኖች) ለአብዛኛው የባህር ውስጥ የምግብ ሰንሰለት መሰረት ሆነው ያገለግላሉ።በሳይንቲስቶች ግምት መሰረት በከባቢ አየር ውስጥ ከሚገኘው ኦክሲጅን ውስጥ 70 በመቶ የሚሆነው የሚመረተው የብርሃን አስተፃምሮ በሚያካሂዱ ዋቅላሚዎች ነው፡፡ በተፈጥሮ የሚያድጉ ዋቅላሚዎች በጣም ጠቃሚ የምግብ ምንጭ ናቸው። በተለይ በእስያ አህጉር በአንዳንዶች እጅግ በጣም ጠቃሚ ተብለው የተለዩ አሉ። ቫይታሚን 6, እና ቪታሚን ይዘው ይገኛሉ። በአዮዲን፣ ፖታሲየም፣ ብረት፣ማግኒዥየም እና ካልስየም የበለፀጉ ናቸው። በተጨማሪም ለገበያ የሚመረቱ ደቂቅዋቅላሚዎቸ ሲያኖባክቴሪያዎችን ጨምሮ እንደ ስፓይሩሊና እና ክሎሬላ ያሉት ለስርዓተ-ምግብ ማሟያ ተብለው ይሸጣሉ። በቤታ ካሮቲን ከበለፀገው ዱናሌላ የቪታሚን ማሟያ ይመረታል። ዋቅላሚዎች በብዙ አገራት ብሔራዊ ምግብ ናቸው። በቻይና ፋት ቾይን ጨምሮ ከ70 በላይ የዋቅላሚ ዝርያዎች ለብግብነት ይውላሉ። በጃፓን ኖሪ እና አውኖሪን ጨምሮ ከ20 በላይ የዋቅላሚ ዝርያዎች ለምግብነት ይውላሉ። በአየርላንድ ደልስ፣ በቺሊ ኮካዩዮ ለምግብነት የሚውሉ የዋቅላሚ አይነቶች ናቸው። በዌልስ የሌቨርዳቦ ወይም ባረ ለውር የሚባለውን ምግብ ለማዘጋጀት ሌቨር የሚባል ዋቅላሚ ጥቅም ላይ ይውላል፤ በኮሪያ ደግሞ ጂም የሚሰኝ ዋቅላሚ ለምግብነት ያግለግላል። በስኮትላንድ፣ አየርላንድ፣ ግሪንላንድ እና አይስላንድ የባህር ሰላጣ() እና ባደርሎክ የሰላጣ ግብዓቶች ናቸው። በአሁኑ ሰዓት ዋቅላሚዎች የአለምን የምግብ ችግር ለመፍታት እምቅ አቅም ያላቸው አማራጭ መሆናቸው ከግምት ውስጥ እየገባ ነው። ለምግብ ዝግጅት የሚያገለግሉ ሁለት ታዋቂ የዋቅላሚ ዝርያዎች አሉ፡ ክሎሬላ፦ ይህ የዋቅላሚ ዝርያ በጨው እልባ የውሃ አካላት ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በአረንጓቀፉ ውስጥ ለፎቶሲንተሲስ የሚያግለግሉ ቀለማት አሉት። በብረት፣ ዚንክ፣ ማግኒዥየም፣ ቪታሚን እና ኦሜጋ-3 ፋቲአሲድ የበለፀገ ነው። በተጨማሪም ሰውነታችን በራሱ ያማያመርታቸውን ዘጠኙንም አሚኖ አሲዶች ይዞ ይገኛል። ስፓይሩሊና፦ የሲያኖባክቴረያ ዝርያ ሲሆን በፕሮቲን ይዘቱ በ10% ከክሎሬላ የላቀ ነው፤ እንዲሁም ከክሎሬላ የተሻለ የመዳብ እና የቪታሚን 1 ይዘት አለው። አጋር ከቀይ ዋቅላሚ የሚዘጋጅ ወፍሮ የመጋገር ባህሪይ ያለው ልዩቁስ() ሲሆን በንግዱ አለም ከፍተኛ ተፈላጊነት አለው። አብዛኛዎቹ ደቂቅ አካላት አጋርን ማብላላት የማይችሉ በመሆናቸው በላዩ ላይ ባክቴሪያ እና ፈንገስ ለማሳደግ ምቹ ማሳደጊያ ነው። አርጂኒክ አሲድ ወይም አርጂኔት ከቡናማ ዋቅላሚዎች የሚገኝ ውህድ ነው። ጥቅሞቹ ለምግብ ማወፈሪያ ከመዋል አንስቶ ለቁስል መሸፈኛነት ጭምር ነው። በባዮቴክኖሎጂ ዘርፍ ሰፊ አገልግሎት አለው። በኒውሜክሲኮ አርጂኔት ለማዘጋጀት እና ለአበሎኒ ምግብነት በኣመት ከ100,000 እስከ 170,000 ቶን የሚደርስ ማክሮሲስቲስ ይመረታል። የሀይል ምንጭ ለወደፊቱ ተወዳዳሪ ለመሆን እና በየጊዜው ከሚቀያየረው የሀገርውስጥ ፖሊሲ ባለፈ ራስን ለመቻል የባዮፊውል ዋጋ ከተፈጥሮ ነዳጅ ዋጋ ማንስ አለበት ካልሆነም እኩል መሆን ይኖርበታል። እዚህ ጋ ዋቅላሚን መሰረት ያደረጉ የነዳጅ ውጤቶች ትልቅ ተስፋ ሰጪ ቦታ ይይዛሉ፤ ይህም በቀጥታ የሚያያዘው በተወሰነ ቦታ ላይ በአንድ አመት ውስጥዋ ቅላሚዎች ባላቸው ከፍተኛ ምርት የመስጠት አቅም ላይ ነው። ለብክለት ቁጥጥር ፍሳሽ ቆሻሻ በዋቅላሚዎች ሊታከም ይችላል፤ ይህም ለፍሳሽ ቆሻሻ ማከሚያ የሚውሉ ከፍተኛ መጠን ያላቸው መርዛማ ኬሚካሎችን ለመቀነስ አይነተኛ መፍትሔ ነው። ዋቅላሚዎች ከእርሻ በጎርፍ ታጥበው የሚሄዱ ማዳበሪያዎችን ለማጥመድ ይጠቅማሉ፤ በቀጣይነት በማዳበሪያ የበለጸገውን ዋቅላሚ እንደማዳበሪያ መጠቀም ይቻላል። የውሃ ማቆሪያዎችን ወይም ኩሬዎችን በዋቅላሚ አማካኝነት ማጽዳት ይቻላል፤ ይህም የሚሆነው ወይም የሚባል መሳርያ ባለብት ዋቅላሚዎች በውሃ ውስጥ ያለውን ንጥረነገር እንዲመጡ በማድርግ ነው። የግብርና ምርምር አገልግሎት ተመራማሪዎች በጎርፍ ታጥቦ ከሚሄደው ናይትሮጅን ከ60–90%የሚሆነው እንዲሁም ከ70–100% የሚሆነው ፎስፈረስ በ አማካኝነት ከፍግ ፍሳሾች ውስጥ መሰብሰብ እንደሚቻል ደርሰውበታል። ዋቢ ምንጭ ሥነ ሕይወት
49163
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B4%E1%89%AA%E1%8B%B5%20%E1%8B%89%E1%8B%B3%E1%88%AD%E1%8B%B5
ዴቪድ ዉዳርድ
ዴቪድ ውድዋርድ (ልደት ኤፕሪል 6፣ 1964) አሜሪካዊ ፀሐፊና ኮንዳክተር ነው፡፡ በ1990ዎቹ የፕሪኪየም የሚባለውን ቃል ፈጠረ፣ ይህ የመግቢያና የሬኪየም መዚቃ ስብጥር ነው፣ ይህም በነበረበት የቡዲዝም ዕምነት ልምድ መሰረት ከሟች ህልፈት በኋላ ወዲያው ወይም በቅርበተ-ህልፈት ወቅት የሚጫወት ሙዚቃ ነው፡፡ሎሳንጅለስ ውድዋርድ በኮንዳክተርነትና በሙዚቃ ዳይሬክተርናት የነበረበት የሎሳንጅለስ መታሰቢያ አገልግሎት በ2001 አሁን ላይ ስራ ባቆመው ኤንጅልስ ፍላይት በተሰኘው ጥምዝምዝ የባቡር ሀዲድ ላይ የአደጋ ሰለባዎች የሆኑትን ሟች ሊዎን ፕራፖርት እና የተጎዳች ባለቤቱን ሎላን ላምስታወስ የተደረገውን የ2001 የሙዚቃ ዝግጅት ይጨምራል፡፡ የዱር እንስሳት ወደ ታች ወርደው በተከሰከሱበት የማህር ዳርቻ አካባቢ የተደረገውን የካሊፎርኒያን ብራውን ፌሊካን ዝግጅት ጨምሮ በርካታ ሬኪየሞች ኮንዳክት አድርጓል፡፡ ውድዋርድ የድሪም ማሽንን ተመሳሳይ በመስራቱ ይታወቃል፣ ይህ በመጠኑ ሳይኮአክቲቭ የሆነ አምፖል ነው፣ ይህም በዓለም ዙሪያ ባሉ የጥበብ ማዕከሎች ለህዝብ ዕይታ ቀርቧል፡፡ በጀርመን እና በኔፓል በዴር ፍሬውንድ ጋዜጣ ላይ በሚጽፋቸው ጽሑፎች ይተታወቃል፣ ጽሑፎቹ በኢንተር-ስፒሲስ ካርማ እና በዕጽዋት ንቃተ-ህሊና እንዲሁም ኒዩቫ ጀርመኒያ የተሰኘውን የፓራጓዮች መስፈር ዙሪያ የተጻፉ ናቸው፡፡ ውድዋርድ የተማረው ሴይንት ባርባራ በሚገኙት ዘ ኒው ስኩል ፎር ሶሻል ሪሰርች እና ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ካሊፎርኒያ በተሰኙ የትምህርት ተቋማት ነው፡፡ ኒዩቫ ጀርመኒያ በ 2003 ውድዋርድ በጁኒፐር ሂልስ (ሎሳንጅለስ ግዛት) ካሊፎርኒያ ውስጥ አማካሪ ሆነ፡፡ በዚህ ስራ እያለ ከፕራግ ከተማ ኒዩቫ ጀርመኒያ ጋር የእህትማማችነት ግንኙነት ሀሳብ አቀረበ፡፡ ሀሳቡንም ለማሳካት ወደ ኤረስትዋይል/ሴት ዘመሟ መቀመጫ በመጓዝ ከከተማው አስተዳደሮች ጋረ ተወያይቷል፡፡ የመጀመሪያውን ጉብኝት ተከትሎ ለወዳጅነቱ ተጨማሪ ግፊት ሳያደርግ ቢቀርም ከማህረሰቡ ለሚቀጥሉት የጽሑፍ ስራዎቹ የሚጠቅሙ ጉዳዮች አግኝቷል፡፡ ለግምታዊ አቃጁ ሪቻርድ ቫግነር እና ከባሏ በርናርድ ፎርስተር ጋር በፈጠሩት ግዛት ከ1886 እስከ 1889 የኖረችው ኤልሳቤጥ ፎርስተር ኒቼ ፕሮቶ-ትራንሹማኒስት ሀሳቦች የተለየ ግምት አለው፡፡ ሪቻርድ ቫግነር ከ 2004 እስከ 2006 ውድዋርድ ብዙ ጉዞዎችን ወደ ኒዩቫ ጀርመኒያ መርቷል፣ ይህን በማድረጉም በወቅቱ ከነበሩት የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዲክ ቼኒ ድጋፍ አግኝቷል፡፡ በ 2011 ውድዋርድ ለስዊዙ ደራሲ ክርስቲያን ራችት በመካከላቸው ስለነበረው በአብዛኛው በኒዩቫ ጀርመኒያ ዘሪያ የተደረገ መጻጻፍ በሁለት መድብል በሀኖቨር ዩኒቨርሲቲ ስር በሚገኘው ዌርሃም ቬርለላግ እንዲታተም ፈቃድ ሰጥቷል፡፡ በነበራቸው የደብዳቤ ልውውጥ ውስጥ ፍራንክፈርተር አለጌሚኒ ዜቱን እንዲህ ይላል፣ "[ውድዋርድ እና ራችት] በህይወትና በጥበብ መካከል ያለውን ድንበር አጥፉ፡፡" የመጀመሪያው መድብል፣ አምስት ዓመት፣ ዕትም 1 ኢምፔሪየም ለተሰኘው ቀጣይ የራችት ድርሰት "መዘጋጃ መንፈሳዊ ስራ " ነው ሲል ደር ስፓይግል ግምቱን ያስቀምጣል፡፡ እንደ አንዲሪው ማክካን፣ "ራችት ከድዋርድ ጋር ከውድመት ወደ ተረፈውና የመጀመሪያዎቹ ሰፋሪዎች ቀጣይ ተውልድ በወረደ የአኗኗር ሁኔታ [ስር] ወደሚኖሩበት ስፍራ ተጉዟል፡፡ ጋዜጠኛው እንደሚያጋልጠው፣ ወድዋርድ ስለማህበረሰቡ የማወቅ ፍላጎት እንዲያዳብርና በአንድ ወቅት የኤልሳቤጥ ፍርስተር ኒቼ ቤተሰቦች መኖሪያ በነበረው ስፍራ ባይሬውዝ የተሰኘውን መዘውተርያ ኦፔራሃውስ እንዲገነባ አስገዳጅ ሁኔታ ፈጥሮበታል፡፡" በቅርብ ዓመታት ኒዩቫ ጀርመኒያ መኝታ፣ ቁርስና ማረፊያ ሆኖ ወደ ተወዳጅ መዘውተሪያ ስፍራነት ተቀይሯል፡፡ ድሪም ማሽን ከ 1989 እስከ 2007 ውድዋርድ በብራይን ጋይሲን እና አያያ ሶቨርቪል የተበጀውን ከመዳብ ወይም ከወረቀት የተሰራ የተቀደደ ስሊንደር የያዘና በኤሌክትሪክ አምፖል ዙሪያ የሚሽከረከር ዓይን ተጨፍኖ ሲደመጥ የመድሃኒት ስካር ተጽዕኖ ወይም የህልም ስሜት ውስጥ የሚከት የድሪም ማሽን ተመሳሳይ የስትሮቦስኮፒክ ኮንትሮቫንስ ፈጠረ፡፡ ለዊሊያም ኤስ. ቦሮውስ የ1996 ኤል ኤ ሲ ኤም ኤ ዕይታዊ የጀርባ ማስገቢያዎች ድሪም ማሽን ካበረከተ በኋላ ውድዋርድ ከጸፊው ጋር በመወዳጀት ለ83ኛ ዓመት ልደቱ “ቦሄሚናል ሞዴል” (ወረቀት) ድሪም ማሽን ስጦታ አበርክቶለታል፡፡ ሶዝቢ የመጀመሪያውን ማሽን በ2002 ለግል ሰብሳቢ በጨረታ ሸጧል፣ የመጨረሻው በተራዘመ ውሰተት ከቦሮው ተወስዶ በስፔንሰር የጥበብ ሙዚየም ይገኛል፡፡ ማጣቀሻዎችና ማስታወሻዎች የውጭ መያያዣ ውኪ ጥቅሶች: ዴቪድ ውድዋርድ የአሜሪካ የጥበብ ሰዎች የአሜሪካ ሙዚቀኞች የአሜሪካ ሰዎች
52326
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%88%B5%E1%8A%AD%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%88%AD%20%E1%8A%90%E1%8C%8B
እስክንድር ነጋ
እስክንድር ነጋ (ህዳር 7 ቀን 1969 እ.ኤ.አ. የተወለደው) ኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛ፣ ጦማሪ እና ፖለቲከኛ ሲሆን በኢትዮጵያ መንግስት በአገር ክህደት እና በሽብርተኝነት ተከሷል። በአገር ክህደት ወይም በሽብርተኝነት ወንጀል ጥፋተኛ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ሳይኖር በገዥው መንግስት የውሸት ክስ ውድቅ ተደርጓል። እስክንድር ነጋ ሌላ መጠሪያ ቢኖረው ፅናት ወይም እዉነት ሊሆን ይችላል ብየ አስባለሁ። እስክንድር ነጋ ለኢትዮጵያውያን የዲሞክራሲ እና የነፃነት ትግል ከፊት ቆሞ የታገለ እንዲሁም ኢህአዴግን ጨምሮ በአሁኑም መንግስት በእስር በድብደባ እየተንገላታ ለእዉነት የታገለ ኢትዮጵያዊ ጀግና ነዉ። እስክንድር ነጋ ጋዜጠኛ እንደመሆኑ እና አለም አቀፉን የ ወርቃማው ብዕር ሽልማት እንደመሸለሙ ይሄንን ያህል ጊዜ ሲታሰር እና ድብደባ እንዲሁም ሰብዓዊ እንግልት ሲደርስበት አለም አቀፉ የ ጋዜጠኞች ማህበር ዝም ማለቱ ያስገርማል። ፍትህ ለ ወርቃማዉ ጋዜጠኛ!!! የመጀመሪያ ህይወት እስክንድር ከፍተኛ ትምህርት ካገኙ ወላጆቹ የተወለደ ሲሆን አባቱ ሩትገርስ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ስራዎችን ሰርቷል እናቱ ደግሞ በቤሩት አሜሪካ ዩኒቨርስቲ ተወለደ። በመጨረሻ ተፋቱ እና እስክንድር አብረውት የሚኖሩ እናቱ ክሊኒክ ከፈቱ። እስክንድር በአዲስ አበባ ሳንድፎርድ ትምህርት ቤት ገብቷል። እስክንድር በ1980ዎቹ ወደ አሜሪካ ሄዶ ኮሌጅ ገብቷል፣ ከዚያም በአሜሪካ ዩኒቨርሲቲ ኢኮኖሚክስ ተምሯል። እስክንድር እ.ኤ.አ. በ1991 ማርክሲስት ደርግን በኢህአዴግ ሃይሎች ከተወገደ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ።በእርግጥም በቀጣዮቹ አመታት የአገዛዙ ተቃዋሚዎች አንዱ ሆነ።የመጀመሪያውን ኢትዮጲስ ጋዜጣ በ1993 አቋቋመ።ሌሎች ጋዜጦችንም አቋቋመ። ፣ አስኳል ፣ ሳተናው እና ምኒልክ። 1998: የአገር ክህደት ጥፋተኛ እስክንድር የሳተናው ጋዜጣ አዘጋጅ ሆኖ በግንቦት 15 ቀን 2005 የተካሄደውን የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ ውጤት በመቃወም ህዳር 28 ቀን 2005 ተይዞ ታስሯል። ሴራ" አምነስቲ ኢንተርናሽናል የህሊና እስረኛ ብሎ የፈረጀው፣ “ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብቱን በመጠቀሙ ብቻ የታሰረ” እና በአስቸኳይ እንዲፈታ ጠይቋል። ቡድኑ በቀርቸሌ ማረሚያ ቤት ያለበትን “ደሃ እና ንጽህና የጎደለው” ሁኔታ ተቃውሟል። እስክንድር በ2007 ዓ.ም መጨረሻ ላይ በፕሬዝዳንት ይቅርታ ከመፈታቱ በፊት ጥፋተኛ ተብሎ የአስራ ሰባት ወራት እስራት ማረፈ።ፍርዱን ተከትሎ ነጋ የጋዜጠኝነት ፍቃድ ተሰርዞ ጋዜጣው በ2007 በባለስልጣናት ተዘግቶ የነበረ ሲሆን በምትኩ በመስመር ላይ ማሳተም ጀመረ። 2005: የሽብርተኝነት ክስ አብዛኛዎቹ ቀናት ከአውሮፓውያን አቆጣጠር የመጡ ናቸው። የኢትዮጵያ መንግስት ጋዜጠኞች በአሸባሪነት ተጠርጥረው መያዛቸውን እና የኢትዮጵያ ተዋናይ እና አክቲቪስት ደበበ እሸቱን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሚወቅስ አንድ አምድ በማተም እስክንድር ከአራት ፖለቲከኞች ጋር መስከረም 14 ቀን 2011 በድጋሚ ታስሯል። የኢትዮጵያ የጸረ-ሽብር ህግ "ለቡድኖች 'ለማበረታታት' ወይም 'የሞራል ድጋፍ ይሰጣል' ተብሎ የሚታሰበውን ዘገባ እና መንግስት 'አሸባሪ' ብሎ እንዲፈርድ የሚያደርግ ማንኛውንም ዘገባ ይከለክላል። እስክንድር እና ተከሳሾቹ አንዱአለም አራጌን ጨምሮ በቅርቡ በኢትዮጵያ የአሸባሪ ድርጅቶች ስም ዝርዝር ውስጥ በገባው ግንቦት ሰባት ውስጥ እጃቸው አለበት ተብሎ ተከሰዋል። በህዳር ወር እሱ እና ተከሳሾቹ "የውጭ ሃይሎች ሰላዮች" ናቸው በሚል በመንግስት ሚዲያ ተከሰው ነበር። በጥር 23 ቀን 2004 የሽብርተኝነት ክስ ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል።እ.ኤ.አ. ጁላይ 13 ቀን 2004 እስክንድር በሽብርተኝነት ተከሶ የአስራ ስምንት አመት እስራት ተፈርዶበታል። እ.ኤ.አ. በ2013 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእስክንድር ነጋ እስር የአለም አቀፍ ህግን የጣሰ ነው ብሎታል። ውሳኔውን ለሰባት ጊዜያት ካዘገየ በኋላ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እስክንድር የ18 አመት እስራት በግንቦት 1 ቀን 2006 ዓ.ም አጽድቆታል። እ.ኤ.አ. 2018–2020፡ መልቀቅ፣ ተጨማሪ እስራት እና እንደገና ተለቀቀ (አውሮፓዊ) በጃንዋሪ 2018 እስክንድር ነጋ በእስር ላይ የሚገኘው ማረሚያ ቤት እንደሚዘጋ ተገለጸ፣ የፖለቲካ እስረኞች የተፈቱት "ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር" በሚል ሲሆን ነፃነት የተፈቀደለት የግንቦት ሰባት ቡድን አባል ነኝ ሲል የእምነት ቃል ከፈረመ ብቻ ነው። በፌደራል መንግስት በአሸባሪነት የተፈረጁ; ነገር ግን እስክንድር ከበርካታ የፖለቲካ እስረኞች ጋር በፌብሩዋሪ 14/2018 ከእስር ተፈትቷል የተባለው የሀሰት ኑዛዜ ነው በማለት እስክንድር እምቢ ብሏል። በመቀጠልም ኢትዮጲስ የተባለውን ሳምንታዊ የአማርኛ ጋዜጣ ከፍቷል። እ.ኤ.አ. መጋቢት 25 ቀን 2010 ምሽት ላይ የኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች እስክንድርን እና ሌሎች ጋዜጠኞችን እና ፖለቲከኞችን ከመዲናይቱ አዲስ አበባ ዉጭ በተደረገ ማህበራዊ ዝግጅት ላይ በድጋሚ በቁጥጥር ስር አውለዋል። እስክንድር ይፋዊውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጣስ የተከለከለውን ብሄራዊ ባንዲራ በማሳየቱ እና በመሰብሰቡ ተከሶ ነበር ነገር ግን በኋላ ላይ አስራ ሁለት ቀናትን በዘለቀው ኢሰብአዊ እስራት ካሳለፈ በኋላ ሚያዚያ 5 አመሻሽ ላይ ያለምንም ክስ ተለቋል። በሴፕቴምበር 2019 እስክንድር ነጋ ባልደራስን ለዴሞክራሲ ፓርቲ መስርቶ ነበር። ኤፕሪል 25 ቀን 2020 እስክንድር እስካሁን ባልተገለጸ ነገር ግን በዚያው ቀን በተለቀቁት ምክንያቶች በአዲስ አበባ ፖሊስ ተይዟል። እ.ኤ.አ. ሰኔ 30 ቀን 2020 በሐጫሉ ሁንዴሳ ግርግር ወቅት ብጥብጥ እና ትርምስ በማነሳሳት እንደገና ታሰረ። እ.ኤ.አ. ጥር 7 ቀን 2022 በኢትዮጵያ ገና የገና በዓል ላይ እስክንድር ነጋ ከአንድ አመት ተኩል እስራት በኋላ ተፈቷል። የአብይ መንግስት ያለ ምንም ማስረጃ የመናገር ነፃነት ታጋዩን ካሰረ በኋላ። የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች
15726
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9D%E1%88%B5%E1%8A%AB%E1%8B%AC%20%E1%8A%85%E1%8B%99%E1%8A%93%E1%8A%95%20%E1%88%98%E1%8B%B5%E1%8A%80%E1%8A%94%20%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D
ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም
ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን፣ አዲስ አበባ የዚህ ቤተ ክርስቲያን ጽላት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አገራችን ኢትዮጵያ በፋሺስት ኢጣልያ በተወረረች ጊዜ በስደት እንግሊዝ አገር ባዝ በተባለ ከተማ ሲኖሩ፣ ጥር ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በጊዜው በስደት ኢየሩሳሌም ለነበሩት ወደ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ (በኋላ አቡነ ባስልዮስ) አንድ ፅላትና ለአገልግሎት የሚበቁ አምስት መነኮሳትን ወደእንግሊዝ አገር እንዲልኩላቸው በአባ ሐና ጅማ በላኩት ደብዳቤ መሠረት ተልኮ በስደት የኖረ ፅላት ነበር። ጃንሆይ]] የስደት መልእክት== “ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ ፤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ይድረስ ከብፁዕ አባቴ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ እንደምን ሰንብተዋል ፤ እኛ እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነን። እስካሁን ባለነው አኳኋን የምናስበው ለናንተ ነው እንጂ ወደኛ ምንም የሚያሳስብ የለም። ይልቁንም የኛ እዚህ መሆንና በየጊዜው ጀኔቭ በሚደረገው ስብሰባ ፤ ቢፈቀድልን የኛ መሄድ ባይፈቀድልንም መላክተኛችንን መላክ ለመጣንበት ጉዳይ ዋና ረዳታችን ስለሆነ የፈጣሪያችን ፍርድ የኢትዮጵያን ጉዳይ እስካጠቃለልን ድረስ እዚሁ ሆኖ ማዳመጥ የሚያስፈልግ መሆኑን ስለተረዳነው የፈጣሪያችንን ቁርጥ እስክናውቅ ድረስ በዚሁ በእንግሊዝ አገር ለመቆየት ቆርጠናል። የእግዚአብሔር ቸርነት ፈቅዶልንና አሰናብቶን ወደ ኢየሩሳሌም እስከምንመጣበት ቀን ድረስ የሃይማኖት ችግር እንዳያገኘን የሚያድጉትም ልጆቻችን የሃይማኖታቸውን መሠረት እንዳያጡት አስበን አንድ ጽላትና አምስት መነኮሳት የሚያስፈልጉትን ንዋየ ቅድሳትና መጻሕፍት ሰጥተውት ይዞ እንዲመጣ አባ ሐናን ልኬዋለሁና ከመምህር ገሪማ ጋራ ተማክራችሁ ዐቢይ ጾም ሳይገባ እንዲደርስ አድርጋችሁ እንድትልኩልን ይሁን። በየጠረፋችንም ተሰደው በሰው ግዛት ላሉትም ሰዎቻችን እንደዚሁ ሰው መላክ አስፈላጊ ሳይሆን አይቀርምና እየተመካከራችሁበትና ፈቃዱ የሚሆን መነኩሴ እየመረጣችሁ እስክናስታውቃችሁ ድረስ መጠበቅ ነው። ጥር ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም ፣ ሎንዶን” እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስም ይሄ መልእክት እንደደረሳቸው በኢየሩሳሌም ዴር ሡልጣን የኢትዮጵያ ገዳም የነበረውን፣ በስመ መድኀኔ ዓለም የተጠራ ጽላት ፤ ለቁርባንና ለጸሎት የሚያስፈልጉትን ንዋየ ቅድሳት እና መጻሕፍት ጭምር በአምስት መነኮሳት እጅ አስይዘው በፍጥነት ወደእንግሊዝ አገር ላኩ። የተላኩትም መነኮሳት፦ ፩ኛ/ መምህር ገብረ ኢየሱስ - መነኮስ ወቆሞስ ፪ኛ/ አባ ሐና ጅማ - መነኮስ ፫ኛ/ አባ ማርቆስ - መነኮስ ፬ኛ/ አባ ኃይሌ ብሩክ - መነኮስ ፭ኛ/ አባ ገብረ ማርያም - መነኮስ ናቸው። እነዚህ መነኮሳትም እንግሊዝ አገር እንደደረሱ፣ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም አንድ መካነ ጸሎት ባርከው እንደ ቤተ ክርስቲያን ሕግ የጸሎትና የቁርባን ሥርዓት ያደርጉ ጀመር። ከዚያም የተነሳ ያች ቤተ ክርስቲያን በስደት ያለች ኦርቶዶክሳዊት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተብላ ትጠራ ጀመር። የፋሺስት ኢጣልያ ኃይል ተደምስሶ የኢትዮጵያ ነጻነት ሲመለስ ይሄ በስደት እንግሊዝ አገር የነበረው የመድኀኔ ዓለም ጽላትም ከግርማዊት እቴጌ መነን ጋር ነሐሴ ፳፫ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም ተመልሶ አገሩ ገባ። ከዚያም በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፭ ዓ/ም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሆስፒታል ቅጽር ግቢ በታነፀው ቤተ ክርስቲያን “ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም” ተብሎ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ። በስደት በነበሩበት ዘመናት ሥርዓተ ቅዳሴ እንደተለመደው በግዕዝ ሲዘመር፣ በሥርዓቱ ውስጥ የተካተቱት ጸሎቶችም ሆኑ የቅዱስ ወንጌል ምንባብ፣ ወዘተ. ግን በአማርኛ ቋንቋ ነበር የሚነበቡት። አሁንም ይሄ ታቦት ተመልሶ ከገባ በኋላ በአባ ሐና ጅማ እና በአባ ኃይሌ ብሩክ መሪነት ሥርዓቱ ቀጠለ። በአገሪቱም ይሄ አዲስና ምእመኑን የሚያሳትፍ ተራማጅ ሥርዓት በኢትዮጵያ በጊዜው ያልተለመደ ቢሆንም የከተማው ምእመናን ጧት እና ማታ የምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለምን ቤተ ክርስቲያን ማዘውተር ልምድ ሆነ። በተጨማሪም፣ የአጥቢያው ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት እና እቴጌ መነን ትምህርት ቤት ተማሪዎች እሑድ እሑድ የማይለዩ አስቀዳሾች ነበሩ። በዚህ ዓይነት እስከ ፲፱፻፵ ዓ/ም ቆይቶ በጊዜው የነበረበት የቅዳሴ ቤት መጥበብ ግልጽ ስለሆነ ንጉሠ ነገሥቱ አሁን ቤተ ክርስቲያኑ የሚገኝበትን ቦታ ለአዲስ ቤተ ክርስቲያን ግንባት እንዲሆን አዘዙ። የቤተ ክርስቲያን ግንባታ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የአዲሱን የምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን መሠረት ድንጋይ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም ሲያስቀምጡ አትኩሮታቸው ወጣቱ ትውልድ ላይ እንደነበር ያደረጉት ንግግር ያመለክታል። “… በተፈሪ መኮንን ተማሪ ቤት ክበብ ውስጥ ይህን የአዲሱን ቤተ ክርስቲያን መሠረት ስንመሠርት በዚህ ተማሪ ቤት የሚማሩት ክርስቲያናውያን ወጣቶች የኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታቸውን ሥርዓት እንዲጠቀሙበት አስበን ነው። የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ፤ ሃይማኖቱን የማያከብር ሃይማኖት የሌለው፣ እርሱም የሚያምነው ደገፋ የሌለው፣ እርሱንም ማንም የማያምነው የሁለት ዓለም ስደተኛ ነው። ፍሬውን ለማየት ተስፋችን እርሱ ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ነው።” የቤተ ክርስቲያኑ ሕንፃ ግንባታ በሚካሄድበት ጊዜ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ በቅርብ እንደተረዳው፣ ንጉሠ ነገሥቱ፣ ልዑላን እና ልዑላት ቤተ ሰቦቻቸው፤ መሳፍንቱ እና መኳንንቱ የሕንፃውን መገንቢያ ድንጋይ በትከሻቸው እያቀረቡ እንደተሳተፉ ተገንዝቧል። በዚህ ዓይነት እርምጃ ተገንብቶ፣ ልክ በሁለት ዓመቱ በ፲፱፻፵፪ ዓ/ም ግንባታው ተፈጽሞ ቤተ ቅዳሴው ሚያዝያ ፳፯ ቀን ተመረቀ። ዋቢ ምንጭ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሐዋርያዊ ድርጅት፣ “ትንሣኤ፡ የሃያ አምስት ዓመታት መንፈሳዊ እርምጃ” (፲፱፻፶፱ ዓ/ም) ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት። አብያተ ክርስቲያናት
15333
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%8D%8D%E1%88%AA%E1%89%83%20%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%8A%90%E1%89%B5%20%E1%8B%B5%E1%88%AD%E1%8C%85%E1%89%B5
የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (አ.አ.ድ.) (እንግሊዝኛ፡ ))፣ (ፈረንሳይኛ፡ ))ግንቦት ፲፯ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ/ም አዲስ አበባ ላይ ተመሥርቶ የድርጅቱ መመሪያ ውል () በ፴፪ቱ መሥራች አገር መሪዎች ጸድቆ ተፈርሟል። የድርጅቱም ጠቅላይ መሥሪያ ቤቱ በአዲስ አበባ እንዲቆይ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ባቀረቡት ግብዣ መሠረት እስካሁን ድረስ እዚያው አዲስ አበባ ላይ ይገኛል። ይህ ድርጅት በ፲፱፻፺፬ ዓ/ም ተደምስሶ የአፍሪካ ኅብረት በሚባለው ድርጅት ተተክቷል። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምሥረታ ለብዙ ሺ ዓመታት ኢትዮጵያ ብቻዋን በአኅጉሩ ውስጥ ከአውሮፓውያኖች የቅኝ ግዛት ቀንበር ውጪ ቆይታ የሙሶሊኒ ፋሺስት ኢጣልያ በ፲፱፻፳፰ ዓ/ም ወርራት በነበረ ጊዜ አርበኞች ልጆቿ ውድ አገራቸውንና ነጻነታቸውን አሳልፈው ላለመስጠት አምስት ዓመታት ሙሉ ተዋጉ። ንጉሠ ነገሥታቸውም የእዚህን የግፍ ወረራ ለማጋፈጥ በዓለም መንግሥታት ማኅበር መድረክ ላይ ሲቀርቡ፣ ከአፍሪቃ አኅጉር ብቸኛዋ አባል ኢትዮጵያ ማንም አጋዥ አገር አልነበራትም። ለአኅጉሩ ነጻነት በቅኝ ግዛት ሥርም የነበሩት ሕዝቦች፤ በነጻነትም ላይ የነበሩት አገራት የአውሮፓውያንን መዥገራዊ ልጥፍነት ለማላቀቅ ብዙ ከታገሉ በኋላ በሰሐራዊ አፍሪቃ የካቲት ፳፯ ቀን ፲፱፻፵፱ ዓ/ም ጋና ነጻ ሆነች። ከዚያ አስከትሎ የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት እስከተመሠረተ ድረስ በ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ጊኒ ነጻ ስትሆን በ ፲፱፻፶፪ ዓ/ም አሥራ አምስት አገራት፤ በ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ሦሥት አገራት፤ በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ደግሞ አራት አገራት ነጻነታቸውን ተቀዳጁ። የአኅጉሩ መሪዎች በዓለም መድረክ ላይ ለበለጠ ተሰሚነት የትብብርን ግንባር ማሳየት እንደነበረባቸው በመገንዘብና ገና ነጻ ላልወጡትም ወንድም አገሮች ሉዐላዊነት መታገል ስለነበረባቸው ዓላማቸውን ግብ ለማድረስ በሁለት ቡድን ተከፍለው ፣ ባንድ በኩል እራሱን “የዘመናዊ ተራማጅ” ብሎ የሚጠራው፣ በጋናው ፕሬዚደንት ክዋሜ ንክሩማ የሚመራው የ “ካዛብላንካ ቡድን” በ ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ተመሠረተ። ይሄ ቡድን የአኅጉሩን መንግሥታት በኅብረት ለማዋሃድ ዓላማ የያዘ ሲሆን አባላቱ ጋና፣ አልጄሪያ፣ ጊኒ፣ ሞሮኮ፣ ግብጽ፣ ማሊ እና ሊቢያ ነበሩ። ሁለተኛው ቡድን የ”ሞንሮቪያ ቡድን” ሲሆን የተመራው በ ሴኔጋል ፕሬዚደንት ሊዮፖልድ ሴዳር ሴንግሆር ነበር። አባላቱ ሴኔጋል፣ ናይጄሪያ፣ ላይቤሪያ እና ኢትዮጵያ ሲሆኑ የነሱ የኅብረት አስተያየት ደግሞ የዱኛ ኅብረት ሳይሆን ፍላጎታቸው ረጋ ባለ ሁኔታ የዱኛኪን ኅብረት አንድነትን ያስከትላል የሚል ነበር። መጨረሻ ላይ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ከተማ ይፍሩ ታላቅ ጥረትና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ድጋፍ ሁለቱም ወገኖች አዲስ አበባ ላይ እንዲገናኙ በተደረገው ጥሪ መሠረት ተሰባስበው የአፍሪቃ አንድነት ድርጅትን የስምምነት ውል ፴፪ ነጻ ሀገሮች ሲፈርሙ ድርጅቱ ተመሠረተ። ፴፪ቱ መሥራች መሪዎች የካዛብላንካ ቡድን የካቲት ፳፯ ቀን ፲፱፻፵፱ ዓ/ም ነጻነቷን በዶክቶር ክዋሜ ንክሩማ መሪነት ከብሪታንያ የተቀዳጀችው ጋና በዚህ በመጀመሪያው የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የምሥረታ ስብሰባም የተወከለችው በኒህ ታላቅ መሪ ነበር። ዶክቶር ንክሩማ የ”ካዛብላንካ ቡድን” መሪ ሲሆኑ በሽከታ ኅብረት () የሚባለው ፍልስፍና ምንጭ እንደነበሩ ይገመታል። ሞሮኮእስከ መጋቢት ፳፱ ቀን ፲፱፻፵፰ ዓ/ም ድረስ በፈረንሳይ ሥር ነበረች። ከነጻነት ወዲህ መሪዋ ግርማዊ ዳግማዊ ሀሰን የሞሮኮ ንጉሥ በጋናው ፕሬዚደንት ክዋሜ ንክሩማ የሚመራው የ “ካዛብላንካ ቡድን” በ ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በካዛብላንካ ከተማቸው እንዲመሠረትና በዓላማው እንዲገፋበት ጥረዋል። ወደፊትም በ ሞሮኮ ሥር በምትገኘው ሰሐራዊ የአረብ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ነጻነት ምክንያት ከድርጅቱ ጋር በተፈጠረው አለመግባባት አግራቸውን ከአባልነት አስወግደዋል። የአልጄሪያ የነጻነት ትግል ፲፱፻፵፮ ዓ/ም በጦርነት ሲጀመር የነጻነት አውጪ ግንባር ዓባል የነበሩት አህመድ ቤንቤላ አገሪቱ ነጻነቷን ከፈረንሳይ ሰኔ ፳፮ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ስትቀዳጅ በመሪነት የፕሬዚደንትነቱን ሥልጣን ጨበጡ። ጋማል አብደል ናስር ከመጀመሪያው የግብጽ ፕሬዚደንት ሙሐመድ ናጊብ ጋር በ፲፱፻፵፬ ዓ/ም የወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት አካሂደው ንጉሡን ቀዳማዊ ፋሩክን ገለበጡ። ናሰር የፕሬዚደንትነቱን ሥልጣን በ፲፱፻፵፰ ዓ/ም ሲጨብጡ የአገሪቱ ሁለተኛው ፕሬዚደንት በመሆን እስከ ዕለተ ሞታቸው፣ መስከረም ፲፰ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ/ም ድረስ አገልግለዋል። ባማኮ ከተማ ላይ ግንቦት ፳፯ ቀን ፲፱፻፯ ዓ/ም የተወለዱት ሞዲቦ ኬይታ አገራቸው ማሊ ነጻነቷን ከፈረንሳይ ሰኔ ፲፫ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ስትቀዳጅ የፕሬዚደንትነቱን ሥልጣን ጨብጠው እስከ ፲፱፻፷ ዓ/ም አገልግለዋል። ሊቢያ ሉዓላዊ እና ነጻ፣ በሕገ መንግሥት የሚተዳደር የዘውድ ሥርዐተ መንግሥት ታኅሣሥ ፲፬ ቀን ፲፱፻፵፬ ዓ/ም ላይ ስታውጅ በንጉሥ ኢድሪስ መሪነት ነበር። የአፍሪቃ አንድነት ድርጅትም ሲመሠረት አዲስ አበባ ላይ በመሳተፍ ውሉን የፈረሙት እኒሁ ንጉሥ ኢድሪስ ነበሩ። በኋላ በነሐሴ ፳፮ ቀን ፲፱፻፷፩ ዓ/ም በሀያ ሰባት ዓመቱ ወጣት መኮንን፣ ሙአማር ጋዳፊ የተመራ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ንጉሡን ቱርክ አገር በህክምና ላይ እንዳሉ ከሥልጣን አወረዳቸው። ንጉሥ ኢድሪስ በግንቦት ፲፱፻፸፭ ዓ/ም ካይሮ ላይ አረፉ። ጊኒ ነጻነቷን ከፈረንሳይ መስከረም ፳፪ ቀን ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ተቀዳጀች። የአገሪቷ የመጀመሪያ ፕሬዚደንት ሴኩ ቱሬ ሲሆኑ በ ፲፱፻፸፮ ዓ/ም እስከሞቱ ድረስ በዚሁ ሥልጣን ቆይተዋል። የሞንሮቪያ ቡድን ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት : የስብሰባው አስተናጋጅና የተከፋፈሉትን ሁለት ቡድኖች በማስተባበር አንድ ድርጅት እንዲመሠረት ያደረጉ መሪ ሲሆኑ፤ የማኅበሩም የውል ረቂቅ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው በአቶ ከተማ ይፍሩ ትጋትና ድካም ተዘጋጅቶ እንዲፈረም አድርገዋል። በአብዝኛው ዓለም አቀፍ አስተያየት “የአፍሪካ አባት” የሚል ስምም አትርፎላቸዋል። ክቡር ፕሬዚደንት ዶክቶር ዊሊያም ተብማን፦ የላይቤሪያ ፕሬዚደንት እና ሁለተናውን በ ሴኔጋል ፕሬዚደንት ሊዮፖልድ ሴዳር ሴንግሆር የሚመራውን “የሞንሮቪያ ቡድን” መሥራች ሲሆኑ አገራቸው ደግሞ ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም በአሜሪካ ነጻ በወጡ የቀድሞ ግሎሌዎች (የግድ ሎሌ) ወይም ‘ባርያዎች’ ከተመሠረተች በኋላ በአፍሪቃ አኅጉር በነጻነት ዕድሜ ከኢትዮጵያ ተከትላ ሁለተኛዋ አገር ናት። ሴኔጋል እስከ መጋቢት ፳፮ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም የፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነበረች። በዚያን ዕለት ነጽ ስትወጣ፣ በሥነ ጽሁፍ እና ቅኔ ባለሙያነታቸው የሚታወቁት መሪ እና “የሞንሮቪያ ቡድን” የሚባለውን ሁለተኛውን ቡድን የመሩት ሊዮፖልድ ሴጋር ሴንግሆር ነበሩ። የቀድሞዋ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ናይጄሪያ መስከረም ፳፩ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ነጻነቷን ስትቀዳጅ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም ጠቅላይ ሚንስትር የነበሩት አል ሃጅ አቡባካ ታፌዋ ባሌዋ ነበሩ። ባሌዋ በአስተማሪነት የሠለጠኑ ሲሆን በሥልጣን ጊዜያቸው ደግሞ ስለአፍሪቃ ራሷን በራሷ የማስተዳደር መብት ብዙ የታገሉ ከመሆናቸውም ባሻገር ለአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ምሥረታ ብዙ ጥረት አድርገዋል። በፈረንሳይኛ እና እንግሊዝኛተናጋሪ አገሮች መሃል ስምምነትና ወዳጅነት እንዲፈጠርም አመቻችተዋል። መጨረሻ ላይ በአገራቸው በተካሄደ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ጥር ፯ ቀን ፲፱፻፶፰ ዓ/ም ተገደሉ። እሬሳቸውም በተገደሉ በስድስተኛው ቀን በሌጎስ ከተማ መንገድ ዳር ላይ ተጥሎ ተገኘ። ቡድን ያልለዩ ዓባላት የቀድሞዋ ዳሆሜ (አሁን ቤኒን) ነጻነቷን ሐምሌ ፳፭ ቀን ፲፱፻፶፪ ከፈረንሳይ ስትቀዳጅ ሁበርት ማጋ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንትነትን ሥልጣን ይዘው ወዲያው በታኅሣሥ ወር ላይ በተካሄደ ምርጫ ጸደቀላቸው። የቱኒዚያን ሪፑብሊክ መጋቢት ፲፩ ቀን ፲፱፻፵፰ ዓ/ም በነጻነት የመሠረቱትና ከ ሐምሌ ፲፱ ቀን ፲፱፻፵፱ ዓ/ም ጀምሮ ለሠላሳ ዓመታት እስከ ጥቅምት ፴ ቀን ፲፱፻፹ ዓ/ም ድረስ በፕሬዚደንትነት ያገለገሉት ሀቢብ ቡርጊባ ነበሩ። ከነጻነት [[ታኅሣሥ ፳፪] ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ጀምሮ ለሀያ ሁለት ዓመታት እስከ ኅዳር ፳፩ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ/ም አገራቸውን ካሜሩንን በፕሬዚደንትነት የመሩት አማዱ ባባቱራ አሂጆ ነበሩ። አስተማሪና የሠራተኞች ማኅበር ቀስቃሽ የነበሩት ፍራንስዋ ቶምቦልባይ መጀመሪያ በቅኝ ግዛት ሥር የአስተዳደሩ ርዕስ በመሆን ቻድ ነሐሴ ፭ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ከፈረንሳይ ነጻነቷን ስትቀዳጅ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ቶምቦልባይ በተወለዱ በ፶፯ ዓመታቸው ሚያዝያ ፭ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም አረፉ። የምዕራብ አፍሪቃዋ ቶጎ ከፈረንሳይ የቅኝ ግዛትነት ሚያዝያ ፲፱ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ነጻ ስትወጣ ሲልቫኑስ ኦሊምፒዮ መጀመሪያ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከዚያም በፕሬዚደንትነት አገልግለዋል። ጥር ፭ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ/ም በተነሳ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት በጥይት ተገደሉ። የሶማልያ ሪፑብሊክ በብሪታንያ ስር በሙሀመድ ሃጂ ኢብራሂም ኤጋል ይተዳደር የነበረውን ክፍልና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስም በኢጣልያ ስር በአደን አብዱላ ኦስማን ዳር መሪነት ይተዳደር የነበረውን ክፍል በማዋሃድ ሰኔ ፳፫ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ተመሠረተ። በቀድሞው የኢጣልያ የቅኝ ግዛት በመንግሥት ሠራተኛነት ሲያገለግሉ የነበሩት ክቡር ዶክቶር አብዲራሺድ አሊ ሸርማርክ የአገሪቱ የመጀመሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ። አይቮሪ ኮስት (ኮት ዲቯር) ሕዝባቸው ባቆላማጭ መንፈስ “አባባ ሁፍዌ” ይላቸው የነበሩት አንጋፋው ፌሊክስ ሁፍዌ ቧኝ በ፲፰፻፺፯ ዓ/ም ተወለዱ። በፈረንሳይ የሕግ ምክር ቤት አባልነት ከመረጣቸው በፊት በልዩ ልዩ ግዜያት የመንደር ዓለቃ፣ የህክምና ዶክቶር፣ የእርሻ አስተዳዳሪ እና የሠራተኞች ማኅበር ዓለቃ በመሆን አገልግለዋል። በፈረንሳይ መንግሥትም በልዩ ልዩ ክፍሎች በሚኒስትርነት አገልግለዋል። አገራቸው ከፈረንሳይ ግዛትነት ነሐሴ ፩ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ነጻ ከወጣች በኋላ በፖሊቲካ ዘመናቸው የአፍሪቃ አኅጉርን የቅኝ ግዛትነት ቀንበር ለማስለቀቅ ብዙ የደከሙ ሲሆን አገራቸውንም በፕሬዚደንትንት በመሩባቸው ዘመናት ራዕያዊ ዕቅዶችን በመተመንና የአገሪቱን ዋና ምርቶች የሆኑትን ኮኮ እና ቡና በማዳበር በምዕራብ አፍሪቃ የላቀ እድገትን አስገኝተዋል። ከምዕራባውያን ጋር የነበራቸው መልካም ግንኙነት እና ለኮሙኒስት ዓላማ የነበራቸው ጥላቻ በሌሎች የጎረቤት አገር መሪዎች ላይ የተነሱ የመፈንቅለ መንግሥት ሴራዎችን ይደግፉ ነበር እየተባሉ ይታማሉ። ሲወለዱ የተሰጣቸው ስም “ካማው ዋ ንጌንጊ” ሲሆን በክርስትና ሲጠመቁ “ዮሐንስ ጴጥሮስ” ተብለው ነበር። በኋላ መጠሪያ ስማቸውን ጆሞ ኬንያታ ብለው ሰየሙ። ኬንያታ አገራቸው ኬንያ ለነጻነት በምትታገልበት ጊዜ ከ፲፱፻፵፭ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ የተካሄደውን “ማው ማው” የተባለውን የአርበኝነት ግንባር መርተዋል። በዚህም ምክንይት በብሪታንያ አስተዳደር ታስረው ነበር። “ምዚ” (አዛውንቱ) ጆሞ ኬንያታ በ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሎንዶን በነበሩ ጊዜ ከጋናው ክዋሜ ንክሩማ ጋር “የአፍሪቃ አኅጉር የሽከታ ኅብረት” () የተባለውን ፍልስፍና መሥርተው ያራምዱ ነበር። ከዘመናት በኋላ አገራቸው ኬንያታኅሣሥ ፪ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም በአፍሪቃ ሠላሣ ሁለተኛዋ ነጻ አገር ሆና ሉዓላዊ ስትሆን፣ ኬንያታ መጀመሪያ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከአንድ ዓመት በኋላ ደግሞ በፕሬዚደንትነት እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ አገልግለዋል። ኮንጎ ብራዛቪል አሁን ኮንጎ ሪፑብሊክ የምትባለው ኮንጎ ብራዛቪል ነሐሴ ፱ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ከፈረንሳይ የቅኝ ግዛት ቀንበር ተላቃ ነጻ ሉዐላዊ አገር ሆነች። በነጻነት ጊዜ አገሪቷን በመሪነት ሥልጣን ይመሩ የነበሩት ቀድሞ የካቶሊክ እምነት ቄስ የነበሩት አቤ ፉልበርት ያውሉ ነበሩ። ያውሉ በ፲፱፻፶፭ ዓ/ም መሪውን ፓርቲያቸውን ብቻ ሕጋዊ ፓርቲ ለማድረግ ሲነሳሱ ሕዝባቸው ይሄንን በመቃወም በነሐሴ ወር ላይ ባካሄደው የሦስት ቀን የተቃውሞ ሁከት ሥልጣናቸውን ለመልቀቅ ተገደዱ። የቀድሞዋ የፈረንሳይ የቅኝ ግዛት ጋቦን ነጻነቷን ነሐሴ ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም አገኘች። በሽግግሩ ጊዜ በጠቅላይ ሚንስትርነት ከነጻነት በኋላ ደግሞ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት በመሆን ያገለገሉት ገብርኤል እምባ ነበሩ። የጋቦን ሽከታ ተዋናይነትን በ ፲፱፻፴፰ ዓ/ም የጀመሩት ፕሬዚደንት እምባ በ፲፱፻፶፮ ዓ/ም በዱኛ ባላጋራቸው ጃን ሂሌይር ኦባም ቀስቃችነት የተነሳውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በፈረንሳይ እርዳታ ካከሸፉ በኋላ በ፲፱፻፶፱ ዓ/ም በፕሬዚደንትነት ተመርጠው ነበር። ዳሩ ግን በነበረባቸው የነቀርሳ በሽታ ምክንያት በኅዳር ወር በሞት ተለዩ። ፊሊበርት ጺራናና በ፲፱፻፬ ዓ/ም የተወለዱ የማዳጋስካር ሽከተኛ ነበሩ። አገራቸውን በመሪነት ሰኔ ፲፱ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ለነጻነት ካበቁ በኋላ በፕሬዚደንትነት እስከ ፲፱፻፷፬ ዓ/ም ድረስ መርተዋል። በመሪነታቸው የ”ማዳጋስካር ሕብረተ-ሰብዓዊ ሽከታ” በሚሉት የአስተዳደራቸው መመሪያ ብዙ ስህተቶችን እንደሠሩ ይዘገባል። ሆኖም በአገራቸው ስማቸው የተከበረ፣ እስካሁንም “የነጻነት አባት” የሚል ቅጽል ስም አስጥቷቸዋል። ፕሬዚደንት ፊሊበርት ጺራናና በሚያዝያ ፰ ቀን ፲፱፻፸ ዓ/ም አረፉ። ሞሪታንያ ነጻነቷን ኅዳር ፲፱ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ከፈረንሳይ ተቀዳጀች። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በ፲፱፻፸ ዓ/ም በተካሄደ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት እስከተገለበጡ ድረስ ሞክታር ኡልድ ዳዳ አገራቸውን በፕሬዚደንትነት አገልግለዋል። ፕሬዚደንት ኡልድ ዳዳ የአንድ ፓርቲ ሽከታን ብቻ ሕጋዊ አድርገው ተቃራኒ በሌለባቸው ሦሥት ምርጫዎች አሸንፌያለሁ ብለዋል። በ፲፱፻፷፫ ዓ/ም የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት (አ. አ. ድ.) ፕሬዚደንት ሆነው ነበር። ጥቅምት ፬ ቀን ፲፱፻፺፮ ዓ/ም አረፉ። የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ የመጀመሪያውና ሦሥተኛው ፕሬዚደንት፣ በ፲፱፻፳፪ ዓ/ም የተወለዱት ዴቪድ ዳኮ ናቸው። ከፕሬዚደንትነቱ ሥልጣን ሁለቴም የወረዱት በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሲሆን፤ በአገራቸው ሽከታ ለግማሽ ምዕት ዓመት ተሳትፈዋል። የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ነጻነቷን ነሐሴ ፯ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ስትቀዳጅ፣ ጊዜያዊ ፕሬዚደንት ከሆኑ በኋላ በፈረንሳይ መንግሥት ድጋፍ እስከ ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ፲፱፻፶፯ ዓ/ም ድረስ በፕሬዚደንትነት ሲመሩ ቆይተው ጄኔራል ጃን ቢዴል ቦካሳ (በኋላ ንጉሠ ነገሥት) ስኬታም ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት አካሂደው ዳኮን ከሥልጣን አወረዷቸው። ከአሥራ አምስት ዓመት አምባ ገነናዊ ግዛት በኋላ ንጉሠ ነገሥት ቦካሳ በፈረንሳይ ምርጥ ወታደሮች ኃይል ከሥልጣን ሲወርዱ ዴቪድ ዳኮ ለሁለተኛ ጊዜ የፕሬዚደንትነቱን ሥልጣን ጨበጡ። ሁለተኛው ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት በመስከረም ፲ ቀን ፲፱፻፸፬ ዓ/ም ተካሂዶ ዳኮን ለሁለተኛና መጨረሻ ጊዜ ከሥልጣን አወረዳቸው። አፐር ቮልታ ሐምሌ ፳፱ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ነጻነቷን ከፈረንሳይ የተቀዳጀችው አፐር ቮልታ (አሁን ቡርኪና ፋሶ) የመጀመሪያ ፕሬዚደንትነትን ሥልጣን የሰጠችው ለሞሪስ ያሜዎጎ ነበር። ያሜዎጎ የአይቮሪ ኮስትን ፕሬዚደንት ፌሊሽ ሁፌ ቧኝ የቅርብ ወዳጅ እና በዕድሜያቸው እንደታላቅ ወንድም የሚያይዋቸው፣ መካሪያቸው እንደነበሩ ይነገራል። ያሜዎጎ መጀመሪያ በአይቮሪ ኮስት እና በአፐር ቮልታ መሃል የተዋህዶ መንግሥት ለመመሥረት ጥረው ስከታማ ሳይሆን ቀረ። በኋላ ደግሞ ይሄንን ዓላማ ለማራመድ በሴኔጋል፣ ማሊ፣ ዳሆሚ እና አፐር ቮልታ መሃል በአንድ መንግሥት የሚመራ የኅብረት ውህደትን ለማግኘት ይለፉ ነበር። ዳሩ ግን በፕሬዚደንት ቧኝ እና በፈረንሳይ መንግሥት ተቃዋሚነት ይህን አሳብ ለመተው ተገደዋል። ያሜዎጎ ከሥልጣን እስከወረዱበት ታኅሣሥ ፳፭ ቀን ፲፱፻፶፰ ዓ/ም ድረስ ከቧኝ ጋር የሁለቱን አገር ሕዝቦች በመንታ ዜግነት ማስተዳደር የሚያስችል አሳብ ያራምዱ ነበር። እሳቸው ከሥልጣን ሲወገዱ ይሄም አሳብ አብሮ ወደቅ። ሲዬራ ሊዮን የሲዬራ ሊዮን የመጀመሪያዋ ጠቅላይ ሚኒስትር “ሰር” () ሚልተን ማርጋይ አገራቸው የብሪታንያ ቅኝ ግዛት በነበረች ጊዜ የህክምና ዶክቶር በመሆን ከመመረቃቸውም ባሻገር በግዛቱ ላይ በተገዢው ሕዝብ ቁጥጥር ሥር የሆነውን የመጀመሪያ ጋዜጣ ያቋቋሙ ናቸው። አገሪቷ ነጻነቷን ሚያዝያ ፲፱ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ተቀዳጀች። እስከዚያም ጊዜ በቅኝ አስተዳደር ውስጥ በዋና ሚኒስትርነት ሲያገለግሉ የነበሩት እና አገራቸውንም ወደነጻነት የመሩት ማርጋይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ። በዚህ ሥልጣን ላይ እንዳሉ በ፲፱፻፶፮ ዓ/ም በሞት ሲለዩ የተቅላይ ሚኒስትርነቱን ሥልጣን ወንድማቸው ወረሱ። “የምንገነባት አፍሪቃ ሌላው ዓለም አይቷት “ስለሕብረተ ሰብ ያላቸውን ህልም ግብ ያደረሱ ነጻ ሕዝቦችን ማየት ከፈለጋችሁ አፍሪቃ ሂዱ!” የሚሉላት መሆን አለባት። ለመላው የሰው ልጅ ሁሉ የተስፋ አኅጉር ማለት ይቺ ናት።” መምህር ጁሊዬስ ኒዬሬሬ (፲፱፻፶፪ ዓ/ም) ጁሊዬስ ካምባራጌ ኒዬሬሬ የብሪታንያን ጭቆና፣ የአገር ውስጥ መከፋፈልን እና የጊዜውን የ”ቀዝቃዛ ጦርነት” ሽከታ ተቋቁመው ኅዳር ፴ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ/ም አገራቸውን ታንጋኒካን በሰላም ወደነጻነት የመሩ ሲሆኑ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ነበሩ። ከዚህም ሌላ፣ አብላጫነት በሌላቸው ነጮች የሚተዳደሩትን የደቡባዊ አፍሪቃ አገሮችን የነጻነት ትግል በመደገፍ ግንባር ቀደም ነበሩ። ኒዬሬሬ በ፲፱፻፲፬ ዓ/ም ተወለዱ። በትምህርት ስጦታ የነበራቸው ምሁር ሲሆኑ በከፍተኛ ትምህርት ከተመረቁ በኋላ በመምህርነት አገልግለዋል። የስዋሂሊ ቋንቋ ለአንድነት ጠቃሚ መሆኑን ለማሳየት የሼክስፒርን “ጁሊዬስ ቄሳር” ወደዚህ የአፍሪቃ ቋንቋ ተርጉመው አሳትመዋል። ኒዬሬሬ፣ ያልተሳካላቸው ትልቅ ህልም የምሥራቅ አፍሪቃን አገሮች በኅብረት መንግሥት ማዋሃድ ቢሆንም ታንጋኒካን እና የዛንዚባርን ደሴት በማዋሃድ አዲሷን ታንዛኒያን በ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ስኬታማ አድርገዋል። በኚህ ታላቅ መሪ የሥልጣን ዘመናት ጠቅላላው ሕዝባቸውን ከሞላ ጎደል የማንበበ እና መጻፍ ችሎታ ሰጥተውታል። ፕሬዚደንት ኒዬሬሬ በጊዜውም ሆነ እስካሁን በአፍሪቃ ሽከታ ተሰምቶም ተደርጎም የማይታወቅ በፈቃዳቸው በ፲፱፻፸፯ ዓ/ም ሥልጣናቸውን ሲለቁ አገራቸው በዴሞክራሲ የዳበረች ሰላምና አንድነትን ያቀፈች አገር ነበረች። መምህር ጁሊዬስ ኒዬሬሬ ባደርባቸው የደም ነቀርሳ () በሽታ በተወለዱ በ፸፰ ዓመታቸው ጥቅምት ፬ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ/ም ሎንዶን ላይ አረፉ። በ፳፻፩ ዓ/ም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ስብሰባ “ዓለም አቀፍ የፍትሐዊ ሕብረተ ሰብ ጀግና” ብሎ ሰይሟቸዋል። የቡሩንዲ የቀድሞ ቅኝ ገዥ የነበረችው አለማኛ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ስትሸነፍ በዚያን ጊዜ የጀርመን ምሥራቅ አፍሪቃ (አሁን ቡሩንዲ እና ርዋንዳ) የሚባለውን ግዛት ጥቅምት ፲ ቀን ፲፱፻፲፯ ዓ/ም ለቤልጅግ መንግሥት አስረከበች። ቤልጅግ ይችን ግዛት በነጻነት ሰኔ ፳፬ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ስታስረክብ በመሪነት የተረከቡት ንጉሥ ግርማዊ ምዋሚ ምዋምቡትሳ ፬ኛ ነበሩ። ንጉሡ ለአራት ዓመታት አገራቸውን ካስተዳደሩ በኋላ መጋቢት ፲፭ ቀን ፲፱፻፶፰ ዓ/ም ልጃቸውን እንደራሴ አድርገው ሾመው ኑሯቸውን ስዊስ አገር አደረጉ። ከሦሥት ወራት በኋላ ግን ሐምሌ ፩ ቀን በጄኔራል ሚኮምቤሮ መሪነት ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ተካሂዶ ንጉሥ ምዋሚ ምዋምቡትሳ ፬ኛ ተገለበጡ። ንጉሡ እዚያው መኖሪያቸው አገር ዠኔቭ ከተማ ላይ ሚያዝያ ፳፫ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓ/ም አረፉ። ታኅሣሥ ፲፱ ቀን ፲፱፻፲፰ ዓ/ም የተወለዱት የኡጋንዳ የመጀመሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የመጀመሪያ ፕሬዚደንት አፖሎ ሚልተን ኦቦቴ ለዚህ ሥልጣን የበቁት ከነጻነት በፊት በብሪታንያ የቅኝ አስተዳደር በተካሄደ ምርጫ ከቡጋንዳ የዘውድ ቡድን ጋር የሽከታ ኅብረት በመፍጠር ነበር። ይሄ የሽከታ ኅብረት በኡጋንዳ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብዙኃን ነትን ሲያገኝ ኦቦቴ ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ/ም የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ።ወዲያው አገሪቷ መስከረም ፳፱ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ/ም ነጻነቷን ተቀዳጀች። በ፲፱፻፶፰ ዓ/ም በጠቅላይ ሚንስትር ኦቦቴ እና በቡጋንዳው ንጉሥ ሙቲሳ መሃል የተከሰተውን የሥልጣን ፉክክር ምክንያት በማድረግ ኦቦቴ ሕገ መንግሥቱን ለውጠው በዓመቱ እራሳቸውን ፕሬዚደንት አደረጉ። ሆኖም ጥር ፲፯ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ/ም ፕሬዚደንት ኦቦቴ ሲንጋፖር ላይ ይካሄድ በነበረው የ”ኮመን ዌልዝ” ርዕሰ መንግሥታት ስብሰባ ላይ ሲሳተፉ በጄኔራል ኢዲ አሚን የተመራ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን አስወገዳቸው። የታንዛንያ ሠራዊት ኢዲ አሚንን ሚያዝያ ፭ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም ከሥልጣን ካወረደ በኋላ ኦቦቴ አገራቸው ተመልሰው ታኅሣሥ ፰ ቀን ፲፱፻፸፫ በሰፊው የትጭበረበረ ምርጫ ለሁለተኛ ጊዜ ፕሬዚደንት ሆኑ። ይሄ ምርጫ እና የኦቦቴ አምባ ገነንነት ያስከተለው የጦርነት ትግል ለሁለተኛው የወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ምክንያት ሆኖ ሐምሌ ፳ ቀን ፲፱፻፸፯ ዓ/ም ለሁለተኛና ለመጨረሻ ጊዜ ሥልጣናቸውን ለቀው ተሰደዱ። ሚልተን ኦቦቴ ባደረባቸው የኩላሊት በሽታ በደቡብ አፍሪቃ ከተማ ጆሃንስበርግ ላይ በተወለዱ በ ፹ ዓመታቸው መስከረም ፴ ቀን ፲፱፻፺፰ ዓ/ም አረፉ። ሱዳን ነጻነቷን ከብሪታንያ የተቀዳጀችው ታኅሣሥ ፳፪ቀን ፲፱፻፵፰ ዓ/ም ነው። ማርሻል ፋሪቅ ኢብራሂም አቡድ ጥቅምት ፲፮ ቀን ፲፰፻፺፫ ዓ/ም በቀይ ባሕር አጠገብ ሞሐመድ ጋል በተባለች ሥፍራ ተወለዱ። ካርቱም በሚገኘው የ’ጎርዶን መታሰቢያ ኮሌጅ” እና በብሪታንያ በምሕንድስና የተመረቁት አቡድ፣ በውትድርና ምክትል መቶ ዓለቃ ሆነው በግብጽ ሠራዊት ውስጥ አገልግለዋል። ወደ ሽከታ ዓለም ከመዛወራቸው በፊት በጦር መሐንዲስነት እና በተለያዩ ወታደራዊ ሥልጣኖች ተመድበው ይሠሩ ነበር። የሱዳንንም ጠቅላላ ሠራዊት አዛዥ በመሆን የመጀመሪያው ሱዳናዊ ነበሩ። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ኢጣልያን ከአፍሪቃ ለማስወገድ በተካሄዱት ጦርነቶች ላይ በሊቢያ እና በኢትዮጵያ ግዛቶች ውስጥ ተሰልፈው በታላቅ ጀብድ እንደተዋጉ ተመዝግቦላቸዋል። በ፲፱፻፶ ዓ/ም የሱዳንን ርዕሰ ብሔር ሥልጣን የጨበጡት አቡድ፣ የደቡብ ሱዳንን የመገንጠል ዓላማ ወኮሎቹን በማሰር፣ በመግደል ወይም በማሰደድ እና በመላ አገሪቱም ላይ የእስላምን የሻሪያ ሕግ በመጠቀም፣ አገሪቱን ወደ አረባዊው ዓለም በመምራትና የውጭ የክርስትና ኃይማኖት ሰባኪዎችን በማባረር እንዲሁም በደቡብ ሱዳን የነበሩትን አብያተ ክርስቲያናት በመዝጋት የሕዝባቸውን ሰብዓዊ መብት የጨቆኑ መሪ ነበሩ። አቡድ በ፲፱፻፷፬ ዓ/ም በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን ለቀው ለብዙ ዓመታት በስደተኝነት ብሪታንያ ኖረዋል። በመጨረሻ ዘመናቸው ወደአገራቸው ተመልሰው ጳጉሜ ፫ ቀን ፲፱፻፸፭ ዓ/ም፣ በተወለዱ በ፹፪ ዓመታቸው ካርቱም ላይ አረፉ። የኒጄር የውጭ ጉዳይ ሚንስትር እና ፕሬዚደንት ሀማኒ ዲዮሪ ሱዱሬ በሚባል የምዕራብ ኒዤር ክፍል በ1908 ዓ/ም ተወለዱ። በትምህርት ከተመረቁ በኋላ በ[ናያሚ]]፣ ማራዲ እና ፓሪስ ውስጥ በአስተማሪነትም በትምህርት ቤት አስተዳዳሪነትም አገልግለዋል። ከዚህም ሌላ የኒዤር ተራማጅ ቡድን ከመሠረቱት አንዱ ናቸው። በ፲፱፻፶ ዓ/ም ቅኝ ገዢዋ ፈረንሳይ ኒዤር እራሷን እንድታስተዳድር ተፈቀደ። ዲዮሪ ፕሬዚደንት ሆነው ነጻነት [ሐምሌ ፳፯]] ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ሲታወጅ የአዲሷ ሪፑብሊክ ፕሬዚደንት ሆኑ። ሀማኒ ዲዮሪ እና መንግሥታቸው በአኅጉሩ በአስታራቂነት ቢመሰገኑም እንኳ በአገር ውስጥ ግን በሙሰኝነት ይወነጀላሉ። በመጨረሻው በሌፍተናንት ኮሎኔል ሴይኒ ኩንቼ የተመራ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሚያዝያ ፯ ቀን ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ዲዮሪን ከሥልጣን አውርዶ ለስደስት ዓመታት በእስር ተቆጣጠራቸው። ሲፈቱም በቁም እስር እስከ ፲፱፻፸፱ ዓ/ም ቆይተው ኑሯቸውን በስደት ሞሮኮ ላይ መሥርተው ሲኖሩ ሚያዝያ ፲፭ ቀን ፲፱፻፹፩ ዓ/ም በተወለዱ በ ፸፪ ዓመታቸው እዚያው ሞሮኮ ውስጥ አረፉ። ኮንጎ ሊዮፖልድቪል የኮንጎ ደሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ መጀመሪያ ፕሬዚደንት ዮሰፍ ካዛቩቡ ነበሩ። በወጣትነት ዘመናቸው በአስተማሪነት እና በሒሳብ ተቆጣጣሪነት ሠርተዋል። በ፲፱፻፴፰ ዓ/ም የሙግት ማኅበር አባል ሲሆኑ የሽከታ ሕይወታቸው ተጀምሮ ቀስ በቀስ ዝናቸው እየታወቀ እስከ ነጻነት ዘመን ቆዩ። በሽከታ ዓለም ካዛቩቡን ስኬታማ ያደረጓቸው በተፈጥሮ ጠባያቸው አሰላሳይነታቸውና በጥፋት ጊዜ ሌሎችን የማጋፈጥ ችሎታቸው ናቸው። በ ፲፱፻፶፪ ዓ/ም መግቢያ ወራት በቀድሞዋ ኮንጎ ሊዮፖልድቪል (አሁን ኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ) በተከሰተው የሕዝብ ሽብር እና ሁከት መነሻነት፣ የቅኝ ገዥዎቿ የቤልጂግ ባለ ሥልጣናት አገሪቱን በስድስት ወራት እንደሚለቁና ነጻነቷን እንደሚሰጧት ጥር ፲፰ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም አስታወቁ። በዚህ መሠረት አገሪቷ ሰኔ ፳፫ ቀን ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ስሟን ወደኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ለውጣ ነጻ ወጣች። ወዲያው የሕዝብ ምርጫ ተካሂዶ በጠቅላይ ሚንስትርነት ብሔራዊው ፓትሪስ ሉሙምባን ሲመረጡ በፕሬዚደንትነት ደግሞ የምዕራባውያን ደጋፊ የነበሩት ዮሴፍ ካዛቩቡ ተመረጡ። ይሄ በሆነ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሕዝብ ሽብር ሲነሳ በተፈጥሮ ሀብት ባለጸጋ የሆነችው የካታንጋ ግዛት በሞይስ ቾምቤ መሪነት ከሪፑብሊኩ ተገነጠለች። የአገሪቱን ጸጥታ ለማስከበርና በሁለቱ ወገኖች (ሉሙምባ እና ካዛቩቡ) የተከሰተውን ጦርነት ለማብረድ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሀያ ሺ ወታደሮች ላከ። በታኅሣሥ ወር አሜሪካ ካዛቩቡን በመደገፍ የላኩት መሣሪያና የ “ሲ አይ ኤ” () ሰላዮች ከካዛቩቡ ጋር በመረዳዳት ሉሙምባን ገድለው የካዛቩቡን ሥልጣን አጠናከሩ። ካዛቩቡ ኅዳር ፲፮ ቀን ፲፱፻፶፰ ዓ/ም፣ እስከዚያ ድረስ ታማኝ በነበረው መኮንን፣ ኮሎነል ሞቡቱ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ተወገዱ። በፕሬዚደንትነት ዘመናቸው ለአገራቸውና ሕዝባቸው እድገትና ለውጥ እምብዛም አመጡ የሚባልላቸው ነገር ባይኖርም በዚያ በነጻነት ማግስት በተከሰተው ጭፍጨፋ እና ሁከት ጊዜ በአሰላሳይነታቸው እራሳቸውን የአንድነት አርማ አስደርገው ማሳያታቸው ይጠቀሳል። ዮሴፍ ካዛቩቡ መጋቢት ፲፭ ቀን ፲፱፻፷፩ ዓ/ም አረፉ። ሄስቲንግስ ካሙዙ ባንዳ ግንቦት ፯ ቀን ፲፰፻፺ ዓ/ም ተወለዱ። ባንዳ አገራቸውን ማላዊን ለሰላሳ ዓመታት ያስተዳደሩ ሲሆን በትምህርታቸው ጤና ጥበቃ አጥንተው በእንግሊዝ አገር ውስጥ በሕክምና ዶክቶርነት በሊቨርፑል፣ ኒውካስትል እና ሃርልስደን ሲያገለግሉ በታካሚዎቻቸው ዘንድ በጣም ተወዳጅ እንደነበሩ ይዘገባል። ባንዳ ለ፵፫ ዓመታት በስደት ከኖሩ በኋላ ያኔ በቅኝ ግዛትነት ሥር ወደነበረችው አገራቸው ኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ሲመለሱ የአገራቸውን ቋንቋ ረስተው፣ ሁኔታቸው ሁሉ ከአውሮፓውያን የበለጡ አውሮፓዊ ነበሩ። ይሄም ሁኔታ ለሽከታ ዓላማቸው እንቅፋት ሳይሆንባቸው አልቀረም። አማካሪም ሲያስፈልጋቸው የበለጠውን ዕምነት የጫኑባቸው የለመዷቸው የብሪታንያ ዜጎችን ነበር። ሆኖም በምሁርነታቸው እና የእንግሊዞች ተደጋፊ በመሆናቸው መጀመሪያ የኒያሳላንድ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው ተሾሙ። ኒያሳላንድ በአዲስ ስሟ ማላዊ ተብላ ሰኔ ፳፱ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ነጻነቷን ከተቀዳጀች በኋላ በተካሄደው የሕዝብ ምርጫ በትልቅ ድምጽ ብዛት ለፕሬዚደንትነት ሲመረጡ የአምባ ገነንነት ባህሪያቸው ይፋ እየሆነ መጣ። በሁሉም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች “እንግዋዚ” () ወይም “ድል አድራጊ” እየተባሉ እንዲጠሩ አዘዙ። ከጥቂት ዓመታትም በኋላ “የዘላለም ፕሬዚደንት” ነኝ አሉ። ለ፴ ዓመታት በፈላጭ ቆራጭነት ማላዊን ከገዙ በኋላ በምዕራባውያን ለጋሽ አገሮች ተጽዕኖ ማላዊ የአንድ ፓርቲ አገር ወይስ የብዙኀን ፓርቲዎች ትሁን የሚል “ውሳኔ ሕዝብ” አካሂደው በተገኘው ውጤት መሠረት በግንቦት ወር ፲፱፻፹፮ ዓ/ም የፕሬዚደንት ምርጫ ተደርጎ ባንዳ በመሸነፋቸው ሥልጣን ለቀቁ። ካሙዙ ሄስቲንግስ ባንዳ በተወለዱ በ፻ ዓመታቸው በደቡብ አፍሪቃ ከተማ ጆሃንስበርግ ላይ ኅዳር ፲፮ ቀን ፲፱፻፺ ዓ/ም አረፉ። የ አ. አ. ድ. ዓላማዎች የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት (አ. አ. ድ.) ሲመሠረት ሁለት ዐቢይ ዓላማዎችን ተመርኩዞ ነበር። እነኚህም፦ ለአኅጉሩ የሽከታና የዱኛኪን እርምጃዎች ወሳኝ ጉዳይ የነበረው ጉዳይ ድርጅቱ የአኅጉሩን አንድነትና ትብብር ለማራመድና የጋራ ልሣን እንዲሆን። ሁለተኛው ዓላማ ደግሞ በዚያን ጊዜ ከቅኝነት ቀንበር ያልወጡ ብዙ የአፍሪቃ አገሮች ስለነበሩ የእነሱን ነጻነት ዐቢይ ዓላማ አድርጎ መታገል ሲሆን፤ ማኅበረተኞቹ እንደቀድሞው በውጭ ኃያላን ቁጥጥር ሥር እንዳይሆኑ በዓለም ዓቀፍ የሽከታ ጉዳዮች አባላቱ ገለልተኞች እንዲሆኑ ነው። ከነኚህ ዐቢይ ዓላማዎች ሌላ፣ ማኅበሩ ሁሉም አፍሪቃውያን ሰብዓዊ መብታቸው የተከበር እንዲሆን የሁሉም አፍሪቃውያን የኑሮ ደረጃ የተሻሻለ እንዲሆን የእርስ በእርስ ግጭቶችንና አለመግባባት በኃይል ሳይሆን በሰላማዊና ሚዛናዊ ሽምግልና መፍታት የተስማማባቸውና የያዛቸው ዓላማዎች ነበሩ። ሆኖም በርስ በርስ ውስጣዊ ጉዳዮች ላይ ጣልቃ ገብነትነት የማይፈልግ ማኅበርም በመሆኑ እና በሽምግልና የማይፈቱ ቅራኔዎች በተፈጠሩም ጊዜ ሰላምን የሚያስክብርበት መሣሪያ የሌለው ጥርስ የለሽ መንጋጋ ብቻ የነበር ድርጅት በመሆኑ የአኅጉሩ ሕዝቦች የጓጉበትን የሰብዓዊ መብት መከበርም ሆነ እንደናይጄሪያ እና አንጎላ ላይ የተካሄዱትንም ብሔራዊ እልቂቶች ለመግታት ያልቻለ ድርጅት ነበር። ስለዚህም በአብዛኛ አፍሪቃውያኖች እና በሰፊውም ዓለም አስተያየት ይሄ ድርጅት ውጤተ ቢስ የወሬ ማኅበር በመባል በይፋ ይተች ነበር። የድርጅቱ ዋና ጸሐፊዎች የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት በ፲፱፻፶፭ ዓ/ም ተመሥርቶ የአፍሪቃ ሕብረት ሐምሌ ፪ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም እስከተካው ድረስ በየጊዜው ከአባል አገራት የተመረጡ ዘጠኝ ቋሚ ዋና ጸሐፊዎች አገልግለውታል። በድርጅቱ መመሪያ ውል () መሠረት ዋና ጸሐፊው ለአራት ዓመታት እንዲያገለግል ይመረጣል። የመጀመሪያው ዋና ጸሐፊ ድርጅቱ አዲስ አበባ ላይ በተመሠረተ ጊዜ ለስብሰባው ጸሐፊ ሆነው ያገለገሉት በጊዜው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ልዑካን መሪ የነበሩት ዶክቶር ተስፋዬ ገብረ እዝጊ ነበሩ። በዚያው ስብሰባ ላይ ቋሚ ዋና ጸሐፊ እስኪገኝ ድረስ ተመርጠው ከ ግንቦት ፲፯ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ/ም እስከ ሐምሌ ፲፬ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ድረስ ያገለገሉት ኢትዮጵያዊው አቶ ክፍሌ ወዳጆ ነበሩ። ሁለተኛው ዋና ጸሐፊ ከድርጅቱ ምሥረታ በኋላ ዋና ጽሕፈት ቤቱ የሚቋቋምበትን ከተማ ለመምረጥ ያስከተለውን እሽቅድምድም እና ፉክክር ለማክሸፍና አዲስ አበባን ለማስመረጥ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር የነበሩት አቶ ከተማ ይፍሩ ከጊኒው መሪ ሴኩ ቱሬ ጋር ባደረጉት ውል መሠረት፤ ጊኒ የአዲስ አበባን መመረጥ ልትደግፍ፣ ኢትዮጵያ ደግሞ ለድርጅቱ ዋና ጸሐፊነት የጊኒውን ተወላጅ ቡባካር ዲያሎ ቴሊን ለማሳጨት እና ለማስመረጥ እንደተስማሙ የአቶ ከተማ ልጅ መኮንን ከተማ በሚል ርዕስ ላይ አስፍረውታል። ቴሊ ከ ሐምሌ ፲፬ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሰኔ ፰ ቀን ፲፱፻፷፬ ዓ/ም ድረስ ሁለት ጊዜ ተመርጠው በድርጅቱ ዋና ጸሀፊነት አገልግለዋል። ዲያሎ ቴሊ በሴኩ ቱሬ ትዕዛዝ ታስረው የካቲት ፳፪ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓ/ም በረሀብ ሞተዋል። ሦሥተኛው ዋና ጸሐፊ ሰኔ ፰ ቀን ፲፱፻፷፬ ዓ/ም ሥራቸውን የጀመሩት ሦሥተኛው ጸሐፊ የካሜሩን ተወላጁ እንዞ ኤካንጋኪ ነበሩ። በአለማኛ የተማሩት ኤካንጋኪ ከአገራቸው ነጻነት በኋላ በውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትርነትና የሥራ ሚኒስትር ሆነው ካለገሉ በኋላ የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሆነው ተመረጡ። የተመረጡበትን የሥልጣን ጊዜ ሳይጨርሱ በሁለት ዓመቱ ድርጅቱ በአኅጉሩ ውስጥ የተፈጥሮ ነዳጅ ምርምር እንዲያካሂድ ከመረጠው የ”ሎንሮ” () ድርጅት ሙስና ተቀብለዋል ተብለው ሲታሙ ሰኔ ፱ ቀን ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀቁ። አራተኛው ዋና ጸሐፊ የካሜሩኑ ዜጋ እንዞ ኤካንጋኪ ሥልጣናቸውን ሲለቁ የካሜሩን ፕሬዚደንት አህማዱ አሂጆ የአገራቸውን ሰው ዊሊያም ኦሬሊዬን እቴኪ እምቡሙዋን በተተኪነት አጭተው አቀረቡ። በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሹ ላይ በተካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ላይ የቀረቡት የሶማሌ እና የዛምቢያ እጩዎች የሚያስፈልገውን ከሦሥት ሁለት እጅ የድምጽ ድጋፍ ባለማግኘታቸው ስብሰባው በሦሥተኛ አማራጭነት እቴኪን በሙሉ ድምጽ መረጠ። ዊሊያም እቴኪ እስከ ሐምሌ ፲፬ ቀን ፲፱፻፸ ዓ/ም አገልግለዋል። አምስተኛው ዋና ጸሐፊ ከሐምሌ ፲፬ ቀን ፲፱፻፸ ዓ/ም እስከ ሰኔ ፭ ቀን ፲፱፻፸፭ ዓ/ም ድረስ ያገለገሉት አምስተኛው ዋና ጸሐፊ በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም ላይ በተካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ላይ የተመረጡት የቶጎው ተወላጅ፣ ኤድዋርድ ኮጆ (ኤደም ኮጆ) ናቸው። በኮጆ የሥልጣን ዘመን በሞሮኮ አስተዳደር ሥር ያለችው የሰሐራዊ የአረብ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ጉዳይ እና እሷንም በተመለከተ የሳቸው አቋም የድርጅቱን አባላት አቃቅሮ ነበር። ኮጆ የካቲት ፳፩ ቀን ፲፱፻፸፬ ዓ/ም በተካሄደ ስብሰባ ላይ የዚችን ግዛት ልዑካን እንደ አባል መቀመጫ እንዲይዙ ማድረጋቸውን በመቃወም ሞሮኮ እና እሷን የሚደግፉ አገራት የድርጅቱ ስብሰባዎች ላይ ላለመሳተፍ ወስነው ነበር። በዚህ ጉዳይ የተነሳ የሴኔጋል ፕሬዚደንት አብዱ ዲዩፍ ኮጆን “ነገር አማሳይ/በጥባጭ” ብለዋቸዋል። ስድስተኛው ዋና ጸሐፊ ሰኔ ፭ ቀን ፲፱፻፸፭ ዓ/ም የዋና ጸሐፊነቱን ሥልጣን በስድስተኛነት ተራ የተረከቡት ናይጄሪያዊው ዶክቶር ፒተር ኦኑ ናቸው። ዶክቶር ኦኑ ለሁለት ዓመታት ብቻ አገልግለው ሐምሌ ፲፫ ቀን ፲፱፻፸፯ ዓ/ም ለቀቁ። ሰባተኛው ዋና ጸሐፊ ከዶክቶር ኦኑ በተከታይነት ሰባተኛ ዋና ጸሐፊ ሆነው ሐምሌ ፲፫ ቀን ፲፱፻፸፯ ዓ/ም የተሾሙት የኒጄር ተወላጁ ኢዴ ኡማሩ ናቸው። በዳካር እና በፓሪስ ከፍተኛ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁት ኡማሩ፣ በአገራቸው በጋዜጠኝነት፣ አምባሳዶርነት እና የውጭ ጉዳይ ሚንስትርነት የሠሩ ሲሆን በ፲፱፻፷፰ ዓ/ም አገራቸው ላይ ከተካሄደውመፈንቅለ መንግሥት በኋላ ለወታደራዊ ርዕሰ መንግሥቱ ሴይኒ ኩንቼ የቅርብ አማካሪ ሆነውም ሠርተዋል። ኡማሩ የመጀመሪያውን የጸሐፊነት አራት ዓመታት መስከረም ፱ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ/ም ሲያጠናቅቁ ለሁለተኛ ጊዜ እንዲያገለግሉ ታጭተው ነበር። ዳር ግን በውድድሩ የታንዛንያው ሳሊም አህመድ ሳሊም አሸንፈው ሥልጣኑን ተቀበሉ። ስምንተኛው ዋና ጸሐፊ ስምንተኛው ተረኛ ዋና ጸሐፊ ዛንዚባር ደሠት ላይ የተወለዱት የታንዛንያው ዜጋ ሳሊም አህመድ ሳሊም ሲሆኑ፣ ሥልጣኑን ከ ኤዲ ኡማሩ መስከረም ፱ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ/ም ተቀበሉ። ጥር ፲፭ ቀን ፲፱፻፴፬ ዓ/ም የተወለዱት ሳሊም አገራቸውን በዲፕሎማትነት ለብዙ ዘመናት ያገለገሉ ሲሆን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት፤ በመከላከያ ሚንስትርነት፤ በምክትል እና ጠቅላይ ሚንስትርነትም አገልግለዋል። ሳሊም የጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የዛንዚባር ጋዜጠኞች ማኅበር ዋና ጸሐፊም ነበሩ። ሳሊም አህመድ ሳሊም እስከ መስከረም ፯ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም ድረስ ካገለገሉ በኋላ ሥልጣናቸውን አስረክበዋል። ዘጠነኛውና የመጨረሻው ዋና ጸሐፊ ሐምሌ ፪ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም በዛምቢያ ዋና ከተማ ሉሳካ ላይ የተካሄደው የድርጅቱ ስብሰባ የአፍሪቃ አንድነት ድርጅትን በአንድ ዓመት ውስጥ በአፍሪቃ ኅብረት ለመተካት የተስማማበትን ዓላማ ግብ የሚያደርስ ዋና ጸሐፊ ሲመርጥ ዘጠነኛውና የመጨረሻው ዋና ጸሐፊ ሆነው የተመረጡት የኮት ዲቯር ተወላጁ አማራ ኤሲ ናቸው። አማራ ኤሲ ሥልጣኑን መስከረም ፯ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም ተረክበው፣ የአፍሪቃ ኅብረት እስከተመሠረተበት ሐምሌ ፪ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም ድረስ ካገለገሉ በኋላ ለአዲሱ የአፍሪቃ ኅብረት ኮሚሲዮንም ጊዜያዊ ሊቀ መንበር ሆነው ተሹመው ነበር። ዋቢ ምንጮች (እንግሊዝኛ) ፡ (እንግሊዝኛ) ፣ ፣ ፣ (እንግሊዝኛ) መኮንን ከተማ ፣ (እንግሊዝኛ) ፣ ፣ የአፍሪካ ኅብረት
50223
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%93%E1%88%A9%E1%88%82%E1%89%B6
ናሩሂቶ
ናሩሂቶ (፣ ይጠራ []፤ የተወለደው የካቲት 23 ቀን 1960) የጃፓን ንጉሠ ነገሥት ነው። በሜይ 1 2019 የሪዋ ዘመን በመጀመር የአባቱ አኪሂቶ ከስልጣን መውረድን ተከትሎ ወደ ክሪሸንተምም ዙፋን ተቀላቀለ። በጃፓን ባህላዊ የሥርዓት ሥርዓት መሠረት 126ኛው ንጉሥ ነው። ናሩሂቶ በቶኪዮ የተወለደችው የአኪሂቶ እና የሚቺኮ የበኩር ልጅ ሲሆን የዚያን ጊዜ ዘውድ ልዑል እና የጃፓን ልዕልት ነው። እ.ኤ.አ. ጥር 7 ቀን 1989 የአፄ ሸዋን ሞት ተከትሎ አባቱ ንጉሠ ነገሥት ሆነው በተሾሙበት ወቅት አልጋ ወራሽ ሆነ እና በ 1991 ዘውድ ልዑል ሆነው መዋዕለ ንዋያቸውን ሰጡ ። በቶኪዮ የጋኩሹይን ትምህርት ቤቶች ገብተው ትምህርታቸውን በጋኩሹን ዩኒቨርሲቲ እና እንግሊዘኛን በሜርተን ተምረዋል። ኮሌጅ, ኦክስፎርድ. እ.ኤ.አ. በ 1993 የሃርቫርድ ምሩቅ እና ዲፕሎማት ማሳኮ ኦዋዳን አገባ ፣ ከእርሷ ጋር አንዲት ሴት ልጅ አላት፣ አይኮ ፣ ልዕልት ቶሺ (እ.ኤ.አ. የተወለደ 2001)። በተፈረደባቸው የጦር ወንጀለኞች ላይ የአያቱን እና የአባቱን ቦይኮት በመቀጠል የያሱኩኒ መቅደስን ጎብኝቶ አያውቅም። ቦይኮቱ የተጀመረው እ.ኤ.አ. በ1975 ነው። ናሩሂቶ በውሃ ፖሊሲ እና በውሃ ጥበቃ ላይ ፍላጎት አለው እና ቫዮላን መጫወት ይወዳል። እሱ የ2020 የበጋ ኦሎምፒክ እና የ2020 የበጋ ፓራሊምፒክ የክብር ፕሬዝዳንት ሲሆን የአለም የስካውት እንቅስቃሴ ድርጅት ደጋፊ ነው። ንጉሠ ነገሥት ከመሆናቸው በፊት በአጠቃላይ በጃፓን ፕሬስ ውስጥ በተሰየመው ስም እና የልዑል ማዕረግ ይጠቀሳሉ. ዙፋኑን ሲረከብ፣ በስሙ አልተጠራም፣ ይልቁንም “ግርማዊ ንጉሠ ነገሥቱ” ተብሎ ይጠራል፣ እሱም “ግርማዊነቱ” (፣ ሄካ) ተብሎ ሊጠራ ይችላል። . በጽሑፍ፣ ንጉሠ ነገሥቱ በመደበኛነት “የሚገዛው ንጉሠ ነገሥት” (፣ ኪንጆ ቴኖ) ተብሎም ይጠራል። የናሩሂቶ የግዛት ዘመን “ሪኢዋ” () የሚል ስም አለው።እና እንደ ልማዱ እሱ ከሞተ በኋላ በካቢኔ ትእዛዝ ንጉሠ ነገሥት ሬይዋ (፣ ሬይዋ ቴኖ፣ “ከሞት በኋላ ያለው ስም ይመልከቱ”) ይባላል። በእሱ ምትክ የሚቀጥለው ዘመን ስም ከሞተ በኋላ ወይም ከመውረዱ በፊት ይቋቋማል የመጀመሪያ ህይወት ናሩሂቶ በየካቲት 23 ቀን 1960 ከቀኑ 4፡15 ላይ ተወለደ። በቶኪዮ ኢምፔሪያል ቤተ መንግሥት ኢምፔሪያል ቤተሰብ ኤጀንሲ ሆስፒታል ውስጥ። እንደ ልዑል በኋላ፣ “የተወለድኩት በበረንዳ ውስጥ ባለው ጎተራ ውስጥ ነው። ወላጆቹ አኪሂቶ እና ሚቺኮ ያኔ የጃፓን ዘውድ ልዑል እና ዘውድ ልዕልት ሲሆኑ የአባታቸው አያት ሂሮሂቶ በንጉሠ ነገሥትነት ነገሠ። ሮይተርስ እንደዘገበው የናሩሂቶ ቅድመ አያት እቴጌ ኮጁን ምራቷን እና የልጅ ልጆቿን በ1960ዎቹ ሚቺኮ ለልጇ ተስማሚ አይደለችም በማለት ያለማቋረጥ በመክሰስ ምራቷን እና የልጅ ልጆቿን ለመንፈስ ጭንቀት እንዳዳኗቸው ሮይተርስ ዘግቧል። የናሩሂቶ የልጅነት ጊዜ ደስተኛ እንደነበረ ተዘግቧል፣ እና እንደ ተራራ መውጣት፣ መጋለብ እና ቫዮሊን መማር ባሉ እንቅስቃሴዎች ይደሰት ነበር። ከንጉሣዊው ቻምበርሊን ልጆች ጋር ተጫውቷል እና በማዕከላዊ ሊግ ውስጥ የዮሚዩሪ ጃይንቶች ደጋፊ ነበር ፣ የእሱ ተወዳጅ ተጫዋች ቁጥር 3 ፣ በኋላ የቡድን አስተዳዳሪ ፣ ሺጊዮ ናጋሺማ። አንድ ቀን ናሩሂቶ በታሪክ የመጀመሪያ ዲግሪውን እና ሁለተኛ ዲግሪውን የሚያቀርበውን የትራንስፖርት ታሪክ ቀልብ የሳበው የጥንታዊ መንገድ ፍርስራሽ በቤተ መንግስት ቅጥር ግቢ ውስጥ አገኘ። በኋላ ላይ "ከልጅነቴ ጀምሮ ለመንገድ ከፍተኛ ፍላጎት ነበረኝ. በመንገድ ላይ ወደማይታወቀው ዓለም መሄድ ትችላለህ. በነፃነት ለመውጣት ጥቂት እድሎች ባለኝ ህይወት እየመራሁ ስለነበርኩ, መንገዶች ለመንገዱ ውድ ድልድይ ናቸው. ያልታወቀ ዓለም ፣ ለመናገር። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 1974 ልዑሉ 14 ዓመት ሲሆነው ወደ ሜልቦርን፣ አውስትራሊያ ለመኖሪያ ተላከ። የናሩሂቶ አባት፣ ያኔ የዘውድ ልዑል አኪሂቶ፣ ከዓመት በፊት በነበረው ጉዞ በዚያ ጥሩ ተሞክሮ ነበረው፣ እና ልጁም እንዲሄድ አበረታተው። ከነጋዴው ኮሊን ሃርፐር ቤተሰብ ጋር ቆየ። ከአስተናጋጁ ወንድሞቹ ጋር ተግባብቶ በፖይንት ሎንስዴል ዙሪያ እየጋለበ፣ ቫዮሊን እና ቴኒስ በመጫወት እና ኡሉሩ ላይ አንድ ላይ ወጣ። አንድ ጊዜ በገዥው ጄኔራል ሰር ጆን ኬር በተዘጋጀው በመንግስት ቤት በተዘጋጀው የመንግስት እራት ላይ ለታላላቅ ሰዎች ቫዮሊን ተጫውቷል። ናሩሂቶ የአራት ዓመት ልጅ እያለ ብዙ የጃፓን ልሂቃን ቤተሰቦች እና ናሪኪን (የኖውቪክ ሀብት) ልጆቻቸውን በሚልኩበት በታዋቂው የጋኩሹይን ትምህርት ቤት ተመዘገበ። በከፍተኛ ደረጃ ናሩሂቶ የጂኦግራፊ ክለብን ተቀላቀለ። ናሩሂቶ በማርች 1982 ከጋኩሹን ዩኒቨርሲቲ በታሪክ በፊደል ባችለር ዲግሪ ተመርቋል። እ.ኤ.አ. በጁላይ 1983 ናሩሂቶ በዩናይትድ ኪንግደም ሜርተን ኮሌጅ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ከመግባቱ በፊት የሶስት ወር የጠነከረ የእንግሊዘኛ ኮርስ ወሰደ እና እስከ 1986 ተምሯል። ቴምዝ በ18ኛው ክፍለ ዘመን እስከ 1989 ዓ.ም. በኋላ እነዚህን አመታት ዘ ቴምስ እና እኔ - በኦክስፎርድ የሁለት አመት ማስታወሻ በተባለው መጽሃፉ ላይ በድጋሚ ጎበኘ። ትራውት ኢንን ጨምሮ 21 ያህል ታሪካዊ መጠጥ ቤቶችን ጎብኝቷል። ናሩሂቶ የጃፓን ሶሳይቲ እና የድራማ ማህበረሰብን ተቀላቀለ እና የካራቴ እና የጁዶ ክለቦች የክብር ፕሬዝዳንት ሆነ። ኢንተር-ኮሌጅ ቴኒስ ተጫውቷል፣ በሜርተን ቡድን ውስጥ ቁጥር ሶስትን ከስድስት ውስጥ ዘርግቷል፣ እና የጎልፍ ትምህርቶችን ከፕሮፌሽናል ወሰደ። በሜርተን ባሳለፈው ሶስት አመታትም በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ በሶስቱ የምርታማነት ሀገራት ከፍተኛውን ከፍታ ላይ ወጥቷል፡ የስኮትላንድ ቤን ኔቪስ፣ የዌልስ ስኖውደን እና ስካፌል ፓይክ በእንግሊዝ። በኦክስፎርድ በነበረበት ጊዜ ናሩሂቶ በመላው አውሮፓ ለመጎብኘት እና የብሪታንያ ንጉሣዊ ቤተሰብን ጨምሮ አብዛኛው ንጉሣዊ ሥልጣኑን ማግኘት ችሏል። የዩናይትድ ኪንግደም ንጉሣዊ ቤተሰብ አባላት በአንጻራዊ ሁኔታ ዘና ያለ ምግባር አስደንቆታል፡- “ንግሥት ኤልሳቤጥ ዳግማዊ፣ በመገረም አስተውላ፣ የራሷን ሻይ አፍስሳ እና ሳንድዊች አቀረበች። ከሊችተንስታይን ልዑል ሃንስ-አዳም 2ኛ ጋር በበረዶ መንሸራተቻ ሄዷል፣ በሜዲትራኒያን ባህር ውስጥ በማሎርካ ከስፔኑ ንጉስ ጁዋን ካርሎስ 1ኛ ጋር እረፍት አድርጓል፣ እና ከኖርዌይ ልዑል ሃራልድ እና የዘውድ ልዕልት ሶንጃ እና የኔዘርላንድ ንግስት ቢአትሪክስ ጋር በመርከብ ተሳፍሯል። ናሩሂቶ ወደ ጃፓን ሲመለስ በጋኩሹዊን ዩኒቨርሲቲ በታሪክ ማስተር ኦፍ ሂውማኒቲስ ዲግሪ አግኝቶ በ1988 በተሳካ ሁኔታ ዲግሪውን አግኝቷል። የግል ሕይወት ጋብቻ እና ቤተሰብ ናሩሂቶ በህዳር 1986 በቶኪዮ ዩኒቨርሲቲ ስታጠና ከማሳኮ ኦዋዳ (በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች) ከስፔን ኢንፋንታ ኢሌና ሻይ ጋር ተገናኘች። ልዑሉ ወዲያውኑ በእሷ ተማረከ እና በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ብዙ ጊዜ እንዲገናኙ አመቻችቶላቸዋል። በዚህ ምክንያት በ1987 ዓ.ም. የንጉሠ ነገሥቱ ቤተሰብ ኤጀንሲ ማሳኮ ኦዋዳን ባይቀበልም፣ እና ለቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት በቦሊኦል ኮሌጅ ኦክስፎርድ ብትማርም፣ ናሩሂቶ የማሳኮ ፍላጎት አላት። ጃንዋሪ 19 ቀን 1993 የኢምፔሪያል ቤተ መንግስት መቀላቀላቸውን ከማስታወቁ በፊት ሶስት ጊዜ ሀሳብ አቀረበላት። ሰርጉ የተፈፀመው ሰኔ 9 ቀን በተመሳሳይ አመት በቶኪዮ ኢምፔሪያል ሺንቶ አዳራሽ ከ 800 ተጋባዥ እንግዶች በፊት ሲሆን ይህም በርካታ የአውሮፓ መንግስታት እና የንጉሳውያን መሪዎችን ጨምሮ።በትዳራቸው ጊዜ የናሩሂቶ አባት ዙፋን ላይ ስለወጣ ናሩሂቶ በየካቲት 23 ቀን 1991 ልዑል ሂሮ ( ፣ ሂሮ-ኖ-ሚያ) በሚል ማዕረግ እንደ ዘውድ ልዑል ተሰጥቷል። የማሳኮ የመጀመሪያ እርግዝና በታኅሣሥ 1999 ታወጀ፣ ነገር ግን ፅንስ አስወገደች። ንጉሠ ነገሥት ናሩሂቶ እና እቴጌ ማሳኮ አንዲት ሴት ልጅ አሏቸው አይኮ፣ ልዕልት ቶሺ ፣ ታኅሣሥ 1 ቀን 2001 በቶኪዮ ኢምፔሪያል ቤተ መንግሥት በሚገኘው ኢምፔሪያል ቤተሰብ ኤጀንሲ ሆስፒታል ተወለዱ። የትርፍ ጊዜ ማሳለፊያዎች እና ፍላጎቶች ናሩሂቶ በውሃ ፖሊሲ እና በውሃ ጥበቃ ላይ ፍላጎት አለው. በመጋቢት 2003 የሶስተኛው አለም የውሃ ፎረም የክብር ፕሬዝዳንት በመሆን በፎረሙ የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ "የኪዮቶ እና የአካባቢ ክልሎችን የሚያገናኝ ውሀዎች" በሚል ርዕስ ንግግር አድርገዋል። እ.ኤ.አ. በመጋቢት 2006 ሜክሲኮን ጎብኝተው በአራተኛው የዓለም የውሃ ፎረም “ኢዶ እና የውሃ ትራንስፖርት” የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። እና በታህሳስ 2007 የመጀመሪያው የእስያ-ፓሲፊክ የውሃ ስብሰባ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ "ሰዎች እና ውሃ: ከጃፓን ወደ እስያ-ፓሲፊክ ክልል" ንግግር አቅርበዋል. ናሩሂቶ ቫዮላን ይጫወታል፣ ከቫዮሊን በመቀየሩ የኋለኛው "በጣም ብዙ መሪ፣ በጣም ታዋቂ" ለሙዚቃ እና ለግል ምርጫው ተስማሚ ነው ብሎ ስላሰበ። በትርፍ ሰዓቱ መሮጥ፣ የእግር ጉዞ ማድረግ እና ተራራ መውጣት ያስደስተዋል። የጃፓን ልዑል የዘውዱ ልዑል የ1998 የክረምት ኦሎምፒክ እና የ1998 የክረምት ፓራሊምፒክ ደጋፊ ነበር። ልዑሉ የዓለም የስካውት ንቅናቄ ደጋፊ ናቸው እና በ 2006 በጃፓን የስካውት ማህበር በተዘጋጀው የጃፓን ብሄራዊ ጃምቦሬ በ 14 ኛው ኒፖን ጃምቦሬ ተገኝተዋል ። ዘውዱ ልዑል ከ1994 ጀምሮ የጃፓን ቀይ መስቀል ማህበር የክብር ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ. በ2012 ለሁለት ሳምንታት ናሩሂቶ የአባቱን ሃላፊነት በጊዜያዊነት በመምራት ንጉሰ ነገስቱ ገብተው ከልብ ቀዶ ጥገና ሲያገግሙ ነበር። የናሩሂቶ ልደት በሺዙካ እና ያማናሺ አውራጃዎች ለተራራው ፍቅር ስለነበረው "" ተብሎ ተሰይሟል። የጃፓን ንጉሠ ነገሥት እ.ኤ.አ. ታኅሣሥ 1 ቀን 2017 መንግሥት የናሩሂቶ አባት አፄ አኪሂቶ በ30 ኤፕሪል 2019 ከስልጣን እንደሚነሱ እና ናሩሂቶ ከግንቦት 1 ቀን 2019 ጀምሮ የጃፓን 126ኛው ንጉሠ ነገሥት እንደሚሆን አስታውቋል። ሚያዝያ 30 ቀን ከሰዓት በኋላ የስልጣን መልቀቂያ ሥነ ሥርዓትን ተከትሎ፣ አኪሂቶ የግዛት ዘመን እና የሃይሴይ ዘመን እስከ ቀኑ መጨረሻ ድረስ ቀጠለ። ከዚያም ናሩሂቶ በሜይ 1 መጀመሪያ ላይ በንጉሠ ነገሥትነት ተተካ፣ የሪዋን ዘመን አስገኘ። ሽግግሩ የተካሄደው እኩለ ሌሊት ላይ ነው። የናሩሂቶ የንጉሠ ነገሥት ቦታ በሜይ 1 ጥዋት ላይ በተካሄደ ሥነ ሥርዓት ላይ መደበኛ ነበር ። በንጉሠ ነገሥትነቱ የመጀመሪያ መግለጫው ፣ አባታቸው የተከተሉትን አካሄድ በጥልቀት ለማሰላሰል እና ሕገ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ቃል ገብተዋል "የጃፓን የሀገር እና የህዝብ አንድነት ምልክት" ናቸው ። በህገ መንግስቱ አንቀፅ 4 ስር የናሩሂቶ ሚና ሙሉ በሙሉ ስነ-ስርዓት እና ተወካይ ተብሎ ይገለጻል, ከመንግስት ጋር የተገናኘ ምንም ስልጣን የለም; የፖለቲካ መግለጫ እንዳይሰጥ ተከልክሏል። የእሱ ሚና በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት የክልል ሥራዎችን በመፈጸም ላይ ብቻ የተገደበ ነው, ከዚያም በሕገ መንግሥቱ መስፈርቶች እና በካቢኔው አስገዳጅ ምክሮች የተገደበ ነው. ለምሳሌ ጠቅላይ ሚኒስትሩን በይፋ ሲሾም በብሔራዊ አመጋገብ የሚሾመውን ሰው መሾም ይጠበቅበታል። የናሩሂቶ የንግሥና ሥነ ሥርዓት የተካሄደው በ22 ኦክቶበር 2019 ነበር፣ እሱም በትክክል በጥንታዊ የአዋጅ ሥነ ሥርዓት ላይ በተቀመጠበት። በጁላይ 23 2021 ናሩሂቶ አያቱ ሂሮሂቶ በ1964 እንዳደረጉት ሁሉ በ2020 የበጋ ኦሊምፒክ (በመጀመሪያ በ2020 ሊደረግ የታቀደው፣ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ የተራዘመ) በቶኪዮ ከፈተ። –የክሪሸንተሙም ከፍተኛ ትዕዛዝ አንገትጌ (ግንቦት 1 ቀን 2019) – የ የበላይ ትዕዛዝ ግራንድ ኮርዶን (የካቲት 23 ቀን 1980) – የጳውሎውኒያ አበቦች ትዕዛዝ ግራንድ ኮርዶን (ግንቦት 1 ቀን 2019) – የባህል ቅደም ተከተል (ግንቦት 1 ቀን 2019) – ወርቃማው ፋዘር ሽልማት የጃፓን ሰዎች
50403
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A8%E1%8A%AD%E1%88%AD%E1%88%B5%E1%89%B6%E1%88%B5
ቅዱስ ገብረክርስቶስ
ገብረክርስቶስ የቆንስታቲኖፕሉ ንጉስ ቲወዲሰይስ ልጅ የነበረ ጻድቅ ነው። የዚህ ጻዲቅና መባዓ ጽዮን የተባለው የኢትዮጵያ ጻዲቅ ገድሎች ተከለ ሃይማኖት በተባለ ሃብታምና ሚስቱ ወለተ ጽዮን አነሳሽነት ምክሖ ጊዮርጊስ በተባለ ፀሐፊ በአንድ መጽሃፍ እንዲጻፉ ተደረገ ። ይህ መጽሐፍ እጅግ በተዋቡ ደማቅ ስዕሎች ያሸበረቀ ሲሆን ሰአሊው "ኢግናጦስ" የሚባል ሰው ሊሆን ይችላል በማለት ታሪክ ተመራማሪው ዋሊስ በጅ ገምቷል መጽሃፉ በዓፄ ቴወድሮስ መቅደላ ላይ ሊያሠሩት ለነበረው ቤ/ክርስቲያናቸው እንደስጦታ አዘጋጅተውት በመሃሉ በእንግሊዞች ተወስዶ እንግሊዝ አገር ውስጥ ይገኛል ። የመጀመሪ ሕይወት ታሪኩ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ወላጅ አባቱ የቍስጥንጥንያው ንጉሥ ቴዎዶስዮስና እናቱ ንግሥት መርኬዛ በስለት ያገኙት ብቸኛ ልጃቸው ስለሆነ ሃይማኖትን እያስተማሩት በምግባር በእጅጉ ተንከባክበው አሳድገውታል፡፡ የአባቱን ንግሥና በመውረስ ቍስጥንጥንያን እንዲገዛላቸው በመፈለግ ወላጆቹ ለአካለ መጠን ሲደርስ የሮሙን ንጉሥ ሴት ልጅ አጋቡት፡፡ እርሱ ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም የተዘጋጀ ነበርና የሠርጉ ዕለት ሌሊት የእርሱንም ሆነ የሙሽይቱን ድንግልና እንደጠበቀ ላንቺም ለእኔም ይህ ነገር የሚጠቅመን አይደለም ብሎ ከጫጉላ ቤት ወጥቶ በመርከብ ተሳፍሮ ሩቅ ሀገር በመሄድ በቤተክርስቲያን ተቀምጦ ከነዳያን ጋር ተደባልቆ በመለመን ለምኖ ያገኘውንም ለሌሎች እየመጸወተ በጾም በጸሎት ተጠምዶ 15 ዓመት ኖረ፡፡ የዓላማው መታወቅ እመቤታችን ተገልጻ ለአንድ የቤተክርስቲያኑ አገልጋይ የገብረ ክርስቶስን ጽድቅ ብትነግረው ምሥጢሩን ለሀገሩ ሁሉ አዳረሰበት፡፡ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስም ‹‹ግብሬ ታወቀ፣ ከዚህ ውዳሴ ከንቱ ልሽሽ›› በማለት ወደሌላ ሀገር በመርከብ ሲጓዝ ፈቃደ እግዚአብሔር መርከቢቱን ያለ አቅጣጫዋ ወስዶ አባቱ ደጅ አደረሰው፡፡ ማንነቱን እንደደበቀና ዓለምን ምን ያህል እንደናቃት ይረዳ ዘንድ በአባቱና በንጉሡ ደጅ የኔ ቢጤ ለማኝ ሆኖ ለአባቱ ውሾች የሚሰጠውን ፍርፋሪ እየተመገበ አሁንም 15 ዓመት ሙሉ በትዕግስት ተቀመጠ፡፡ የአባቱ አሽከሮች እንኳን እጣቢና ቆሻሻውን ሁሉ እየደፉበት ሲያሠቃዩት የአባቱ ውሾች ግን የእግሩን ቁስል ይልሱለት ነበር፡፡ በአጠቃላይ ገብረ ክርስቶስ እጅግ የተከበረ የታላቅ ንጉሥ ልጅ ሲሆን ነገር ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ ስለ ጽድቅ ተሰዶ እየለመነ ያገኘውን እየመጸወተ በጾም በጸሎት እየተጋደለ 30 ዓመት ሙሉ ተቀመጠ፡፡ በመጨረሻም ጌታችን እመቤታችንን፣ ቅዱሳን መላእክትን ሁሉ፣ ከገብረ ክርስቶስ በፊት የነበሩ ነቢያትን ሁሉ፣ ሐዋርያትን፣ ጻድቃንን፣ ሰማዕታትን ሁሉ አስከትሎ መጥቶ ቃልኪዳን ከገባለት በኋላ ከጌታችን ጋር አብረውት የመጡት ሁሉ በታላቅ ክብርና ምስጋና እያመሰገኑት ጌታችን ክብርት ነፍሱን በእቅፉ ተቀብሎ አሳርጓታል፡፡ የቁስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ በቅዳሴ ላይ ሳሉ ከንጉሡ ቤት ሄደው የገብረ ክርስቶስን ሥጋ እንዲያመጡ የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ በትእዛዝ መጣላቸውና ሄደው ቢያዩ የገብረ ክርስቶስን ሥጋ በንጉሥ አባቱ ደጅ ወድቆ አገኙት፡፡ በገብረ ክርስቶስም እጅ ላይ በጥቅል ወረቀት የተጻፈ ደብዳቤ ነበርና ወስደው ሊያነቡት ሲሞክሩ ወረቀቱ አልላቀቅ ብሎ ፈጽሞ እምቢ አላቸው፡፡ ብዙ ምሕላና ጸሎት ከተደረገ በኋላ ወረቀቱ ከእጁ ላይ ተላቀቀና ሲነበብ ገብረ ክርስቶስ ስለ አምላኩ ፍቅር ብሎ ለ30 ዓመታት ያሳለፈውን እጅግ አሠቃቂ መከራ በተለይም በአባቱ ደጅ ማንም ሳያውቀው ያሳለፈውን እጅግ አሳዛኝ መከራና በኀዘን የሚያስለቅሰውን ታሪኩን በራሱ እጅ በዝርዝር ጽፎት ተገኝቷል፡፡ ንጉሡ አባቱና ንግሥት እናቱም ይህንን ልጃቸው የጻፈውን መልእክት ባነበቡ ጊዜ የሚሆኑት ጠፋቸው፡፡ በጣም የሚገርመው ደግሞ ወላጆቹ ሚስት አድርገው ያመጡለት የሮሙ ንጉሥ ሴት ልጅ ለባሏ ታማኝ ሆና 30 ዓመት ሙሉ በእናት አባቱ ቤት በትዕግስት ስትጠብቀው መኖሯ ነው፡፡ እርሷም ታሪኩ ሲነበብ ብትሰማ እንደ ዕብድ ሆነች፡፡ የቅዱስ ገብረ ክርስቶስን ሥጋውን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዱ እጅግ አስገራሚ ተአምራት በድውያን ሕመምተኞች ላይ ተፈጽሟል፡፡ ከተአምራቱ የተነሣ መንገዱ በሕዝብ ተጨናንቆ አላሳልፍ ቢላቸው ንጉሡ በመንገድ ዳር ወርቅ እየበተነ ሰው ወርቁን ለማንሳት ሲሄድ በፍጥነት ወደ ቤተ ክርስቲያን አድርሰውታል ፡፡ ከገድለ ገብረክርስቶስ የተወሰዱ ጥንታዊ ስዕሎች
51875
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%A1%E1%8A%90%20%E1%8A%A0%E1%88%A8%E1%8C%8B%E1%8B%8A
አቡነ አረጋዊ
የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት አቡነ አረጋዊ የተሰወሩበት፤ ቅዱስ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍት ቅዱስ ሙሴ_እግዚአብሔር በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡(ታቦታቸው በቀጨኔ ደብረሰላም ያለ) በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ #_ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ጥቅምት 14 ፤ አቡነ አረጋዊ ( ዘሚካኤል ) ወቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር አቡነ አረጋዊ ( ዘሚካኤል ) ፠ ከእንጦንስ ከመቃርስ እና ከጳኵሚስ የምንኵስና ሐረግ አራተኛ ትውልድ ናቸው፣ ፠ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም 6 ሺህ የደረሱ ናቸው፣ ፠ ከቅዱስ ያሬድ ጋር እጅግ ይዋደዱ የነበሩ ፣ ዝማሬውንም ለመስማት ከጐንደር ለመጣ ሲል በጸጋ አይተው ደብረ ዳሞ ላይ ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ሰብሰበው ይጠብቁ የነበሩ ፡፤ ፠ ታላላቅ የኢትዮጵያ ነገሥታትን ለባረኩ ይመጠላቸው የነበረ .. ፠ አጼ ገብረ መስቀል በተመስጦ የቅዱስ ያሬድን እግር በጦር በወጋው ጊዜ ታለቅ ግብዣን አድርገ የዛኔም አቡነ አረጋዊ ቀድሰዋል፣ ቅዱስ ያሬድም ዘምሯል ፤ ታላቅ ሥርዓትንም አስጀምረዋል፡፡ ፠ ትውልዳቸው ሮም ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከአባታቸው #ይስሐቅና ከእናቸው #እድና የተገኙ የቅዱሳን ፍሬ ናቸው ፤ ወንድሞቹም #ቴዎድሮስ እና #ገብረ አምላክ ይባላሉ፡፡ ፠ የቀድሞው ስማቸው #ዘሚካኤል ነበር፡፡ “አረጋዊ” የተባሉት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ነው፡፡ በእድሜ ልጅ ሲሆኑ በመንፈሳዊ ሕይወታቸውና ሥራቸው አዋቂ ስለነበሩ አረጋዊ ብለዋቸዋል፡፡ ፠ወላጆቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን እያስተማሩ አሳደጉት፤ እሱም በመንፈስ ቅዱስ ኀይል እየጸናና እየበረታ ሄደ፡፡ ዕለት ዕለት ጧትና ማታም ወደቤተክርስቲያን እየሄደ ጸሎት ከመጸለይ አያቋርጥም ነበር፡፡እድሜውም ለጋብቻ ሲደርስ አባትና አናቱ ያገባ ዘንድ ሚስት አጩለት፡፡ እሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ የምንኵስና ሕይወትን ለመኖር ፈልጓልና፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የምንኵንስና ሕይወትን ለመኖር ወደ አባ ጳኵሚስ ዘንድ ሄደ፤ ወደ ገዳሙም በገባ ጊዜ አንድ መነኵሴ አገኙትና ‹‹ልጄ ሆይ ከወዴት መጥተሃል እነሆ አንተ ሕፃን እንደሆንክ እመለከታለሁና›› አሉት፡፡ እሱም አመጣጡ ከሮም እንደሆነና ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ የሚፈልገው ነገር እንዳለ ነገራቸው፡፡ እሳቸውም ነገሩን ከሰሙ በኋላ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ ወሰዱት፡፡አባ ጳኩሚስም በአየው ጊዜ ከመንበሩ ተነስቶ በፍፁም ፍቅር አቅፎ ሳመው የእግዚአብሔር ጸጋ በእሱ ላይ አድሯልና፡፡ ከዚያም ቀጥሎ ስለምን ጉዳይ ወደ እሱ እንደመጣ ጠየቀው፡፡ አባ ዘሚካኤልም ‹‹እንደአንተ እንደ አባቴ መነኵሴ እሆን ዘንድ መጥቻለሁ›› አለው፡፡ አባ ጳኩሚስም ‹‹ልጄ ሆይ አንተ የንጉሥ ልጅ እንደመሆንህ መጠን የመንግሥቱ ወራሽ ነህና መንኵሰህ ለመኖር እንደምን ይቻልሃል?›› ሲል መለሰለት፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን የምድር መንግሥት ኀላፊ ጠፊ እንደሆነ ያውቃልና ከዓለም ንግሥና ይልቅ ዘለዓለማዊ መንግሥትን ይወርስ ዘንድ እንደሚሻ ያመነኵሰውም ዘንድ አጥብቆ ጠየቀው፡፡ አባ ጳኩሚስም ፈተናን ፈትኖት መቋቋም የሚችል ከሆነ እንደሚያስገባው ነግሮ የተለያዩ ፈተናዎችን ፈትነው፡፡ አባ ዘሚካኤልም የተባለውን የታዘዘውን ሁሉ በትጋት ፈጸመ፡፡ አባ ጳኵሚስም ስለሃይማኖቱ ጽናት ስለጠባይና ስለቅንነቱ እጅግ አድርጐ ወደደው፡፡ ከዚያም አስኬማው ወይም ቆቡ ላይ ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ አመነኰሰው፤ ስሙንም ዘሚካኤል ብሎ ጠራው፤ በዚህ ጊዜ #እድሜው 14 ዓመት ነበር፡፡ ፠አባ ዘሚካኤል አስኬማ ካደረገ በኋላም በታላቅ ትጋቱ በጸሎቱና በጾሙ አባ ጳኵሚስ ተደነቀ፡፡ ስለሱም ዝናው በየሀገሩ ሁሉ እስከ አባቱ አገር ሮም ድረስ ተሰማ፡፡ አባ ዘሚካኤል ገና በሕፃንነቱ የምንኵስና ማዕረግ መቀበሉን ከሰሙ በኋላ ወደ እሱም 8 ቅዱሳን የመጡ ነበሩ፡፡ እነሱም፦ አባ #_ ሊቃኖስ ከቁስጥንጥንያ(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ )፣ አባ #_ ይምዓታ (ገዳማቸው በኃውዜን የሚገኝ (ትግራይ) ከሀገረ ቁስያ፣ አባ #_ ገሪማ ከሮም(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ ፣ ከአንፆኪያ አባ #_ ድሕማ፣ ከቂልቅያ አባ #_ ጉባ፣ ከእስያ አባ #_ አፍጼ፣ ከሮሚያ አባ #_ ጴንጠሌዎንከሮም(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ ) ፣ ከቂሳርያ አባ አሌፍ ነበሩ፡፡ እነሱም አባ ጳኵሚስ የምንኵስናውን አፅፍ አጐናፀፏቸውና አመነኮሷቸው፡፡ ለእያንዳንዳቸውም ስማቸውን ሰየሟቸው፡፡ እኒህም አባቶች ስለትዕግስት፣ አርምሞ፣ ትህትና፣ ስለሥርዐተ ማኀበር አመሠራረት ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ ተማሩ፡፡ ፠ ከዚህ በኋላ በዚያ ገዳም ለብዙ ዓመታት በፍቅር በአንድነት ከአባ ቴዎድሮስ ጋር ተቀመጡ፡፡ በዚህን ጊዜ ግን አባ ጳኩሚስ አርፈው አባ ቴዎድሮስ ተተክተው ነበር፡፡ እነዚህም አባቶች ወደየሃገራቸው ሄደው ማስተማርና ሃይማኖትንማስፋፋት እንዳለባቸው ተስማምተው ወደየሀገራቸው ተመለሡ፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን በዚያው ቆየ፡፡ እሱ ልቡን የነካችዉ ዜናዋንም የሰማላት ሃገር ነበረችና፡፡ ይህቺውም ሃገራችን #ኢትዮጵያ ነበረች፡፡ እሱም ማንም ሰው ሳያውቅና ሳያየው ከሁለቱ ደቀመዛሙርቱ ጋር ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መጥተው ጐብኝተዋታል፡፡ ያለመምህራንና ያለአስተማሪ ያመነች የዚህችን ሀገረ እምነቷንና ሥነስርዐቷን ተመልክቶ ተደነቀ፡፡ እነዚያን 8 መነኰሳትም ከያሉበት ስለሃገሪቷ እየነገረ ጠራቸው የሚገርመው ግን እነሱም ስለዚህች ሀገር እንደሰሙ ያለምንም ማመንታት መጥተዋል፡፡ እነሱም ሕዝቡን እንደሰሙት አገኙት፡፡ አባ ዘሚካኤል አቡነ አረጋዊ የሚለውን ስያሜ ያገኙት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ትህትናቸውና ታዛዥነታቸው እሳቸውሲመነኩሱ ገና ሕፃን ነበሩ ስራቸው ግን የአረጋውያን ነበርና አንተስ ሐፃን አይደለህም የልጅ አዋቂ ነህ ሲሉ #አረጋዊ አሏቸው፡፡ አባታችን አቡነ አረጋዊ ወደ ኢትዮጵያ የገቡበትም ቀን ጥቅምት 11 ነበር ፡፡ አቡነ አረጋዊ በኢትዮጵያ ሲኖሩ በሄዱበት ስፍራ ብቻቸውን የሚፀልዩበትን ቦታ ሁል ጊዜ ይፈልጉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም በመንገድ እየሄዱ ሳሉ ትልቅ ተራራን (ደብረ ዳሞን) ተመለከቱ፤ ከሦስተኛው ቀን በኃላም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ‹‹አንተ እግዚአብሔር ያከበረህ ቅዱስ ሆይ ምን ያስጨንቀሃል›› አለው፡፡ አባታችንም አቡነ አረጋዊም ‹‹ከዚህች ተራራ ላይ ወጥቼ ስለኃጥያቴ እናዘዝና እለማመን ስለበደሌም ይቅርታን እጠይቅ ዘንድ እወዳለሁ›› አለው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም እንዲፀልይና ታላቅ ዘንዶም ወደርሱ እንደሚላክለት ነገረው፡፡ በሦስት ሰዓትም ዘንዶው መጣ፤ አባታችንም የዘንዶውን ጅራት ይዘው ወደ ላይ ወጡ ብቻቸውን አልነበሩም ፡፡ ዘንዶው እንዳያስደነግጣቸውና እንዳይጐዳቸው ሰይፍን ይዞ ቅዱስ ሚካኤል ይጠብቃቸው ነበር እንጂ፡፡ ቢዚያችም ሰዓት ተራራዋ ደብረ ታቦርን መስላ ነበር:: በዚህችም ላይ ንጉሥ አጼ ገብረ መስቀል ቤ/ክ ከአነጹ በኃላ የቅዳሴ ቤቱ ዕለት አቡነ አረጋዊ ቀድስው ንጉሡም ሠራዊትም ሕዝቡም ጳጳሳቱም ጭምር ሥጋ ወደሙን ተቀብለዋል፡፡ ንጉሡም በረከተን ከአባታችን ተቀብሉ ወደ አኵሱም ተመልሷል፡፡ ሲመለስም ሰርቶት የነበረውን ድልድላይ ላፍረሰው ወይ ሲላቸው ዳሕምሞ ብለውታል ትርጕሙም ‹‹የሰራኸውን ደረጃ ናደው ፥ አፍርሰው እንጂ አትተወው›› ፡፡ ከዚ በመነሳት ዳሞ ተብላለች፡፡ እግዚአብሔርም ሰማያዊ ኅብስት ትሁነህ ብሎ ደብረ ዳሞን ስጥቶዋቸዋል ይህም በመንፈስ ለሚወለዱት ልጆቹ እስከ ዘለዓለም ማርፍያ እንድትሆን ነው ፡፡ ፠ አባታችን አቡነ አረጋዊም የእርጅና ዘመናቸው በደረሠ ጊዜ እግዚአብሔር ወደ እርሱ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ ይኸውም ‹‹መታሰቢያህን ያደርግ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ቧለሟልነትን እሰጠዋለሁ፤ በእውነተኛ ሀይማኖት ሁሉ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ፤ ያጻፈ፤ የተረጐመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፤ ይህ ሁሉ ላደረገም እስከ 14 ትውልድ ድረስ እምርልሀለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን አልሞተም በዓመቱ "ሞትን የማይቀምሱ አሉ፡፡" ብሎ እንደተናገረው /ማቴ 16 ፥ 28/ ጥቅምት 14 ቀን 558 ዓ/ም #ተሠወረዋል፡፡ ይህም እንዲህ ነው አባታችን አቡነ አረጋዊ ማትያስ ለተባለው ደቀ መዛሙር ጌታችን ተገልጦ የሰጣቸውን ቃል ኪዳንና ይህ መጽሐፍ ተጽፎ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ነገሩት፤ (መዝ ፻፲፩/፻፲፪፥፮) ወንድሞቹ ደቀ መዛሙርቶቹ በተሰበስቡበትም ሁሉንም ከአስተማሩ በኋላ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ በሥጋ አታዩኝም›› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም በመሪር ኃዘን እግራቸው ሥር ወድቀው አለቀሱ፤ አባታችን አቡነ አረጋዊም አጽኗኗቸው፡፡ ጥቅምት ፲፬ ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ በ፺፱ ዓመታቸው ተሰወሩ፤ በዚያም #ከመቋሚያና #ከመስቀል በስተቀር ምንም የተገኘ የለም፡፡ ገድላቸውንም ደቀ መዛሙርታቸው ማትያስ እና ዮሴፍ ጽፈዋል፡፡ ከዚያም አባ ማትያስ ደብረ ደሞን ለማስተዳደር ተሾመዋል፡፡ ከጻድቁ አባት በረከት ይክፈለን፤ በቃልኪዳናቸው ይጠብቀን፤ አሜን፡፡ #_ እግዚአብሔር አምላክህ አንተን መርጦሃልና እንደ ኹለቱ ነቢያት ለተከወነ መሠወርህ ሰላምታ የሚገባህ ደግ አገልጋይና የታመንህ መጋቤ ቤቱ ቅዱስ አረጋዊ ሆይ በዐሥሩ አህጉር ተሹመህ ኀምስቱን መካልይ የተቀበልህ አንተ አይደለህምን?፡፡ _# #መልክአ አቡነ አረጋዊ ፨#ቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር በዓለ #ዕረፍታቸው_፡፡(ታቦታቸው በቀጨኔ ደብረሰላም ያለ) ታሪኩ ከሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስና ከቅዱስ ቶማስ ዘቶርማቅ ጋር ተመሳሳይ የሆነው(ቅዱስ ያሬድ ለእመቤታቸን ( ትዕግሥትኪ ፈድፈደ እምትዕግሥተ ኢዮብ ጻድቅ ፤ወእማርቆስ #ዘቶርማቅ ፤ ወገብረ ክርስቶስ መርዓዊ ተወካፌ ሕማም መጽዕቅ፡፡ ) ብሎ እንደጻፈው ቅዱስ ቶማስ ዘቶማርቅ እንደ ኢዮብ ታጋሽ የሆነ ጻድቅ ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔር ሰው የተባለ ትዕግሥኛው ቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡ ፠፠ ፠፠፠ ፠፠፠ ፠ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/
52404
https://am.wikipedia.org/wiki/Fred%20Swaniker
Fred Swaniker
ፍሬድ ስዋኒከር (እ.ኤ.አ. የተወለደ እ.ኤ.አ. ፍሬድ በ17 አመቱ በእናቱ የተመሰረተ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ሆኖ ሲያገለግል የአመራር እና የትምህርትን አስፈላጊነት ተገንዝቦ አፍሪካን ለመለወጥ የሚያስፈልገው የጎደለው ንጥረ ነገር ጥሩ አመራር እንደሆነ ያምን ነበር። ያንን ችግር ለመፍታት፣ የአፍሪካ አመራር ቡድንን ፈጠረ - የስነ-ምህዳሩ ድርጅት አዲስ የስነ-ምግባር፣ የስራ ፈጣሪ የአፍሪካ መሪዎች ዘመንን የሚያበረታታ። ባለፉት 16 ዓመታት ውስጥ ከዩኒቨርሲቲ በፊት በደቡብ አፍሪካ የሚገኘውን የአፍሪካ ሊደርሺፕ አካዳሚን ፣ በሞሪሸስ እና በሩዋንዳ ካምፓሶች ያለው የአፍሪካ አመራር ዩኒቨርስቲ ፣ የአፍሪካ አመራር ኔትወርክ ፣ (የቀጣይ ትውልድ የአመራር ልማት መድረክ) እና መርተዋል። ክፍሉ (ከፍተኛ ችሎታ ያለው ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ)። በአጠቃላይ እነዚህ ጥረቶች በ2035 3 ሚሊዮን የአፍሪካ መሪዎችን በማፍራት አፍሪካን ለመለወጥ ያለመ ነው። በተጨማሪም የክፍሉን ኢንተለጀንስ ፕላትፎርምን ለማጎልበት እና የ ተደራሽነትን በአፍሪካ፣ እስያ ፣ ላቲን አሜሪካ ፣ ሰሜን አሜሪካ እና አውሮፓ ውስጥ ባሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተሰጥኦ ያላቸውን ግለሰቦች ለማስፋፋት ከአማዞን ድር ሰርቪስ () ጋር ትብብር ማድረጉን አስታውቋል። . እ.ኤ.አ. በ2019 ታይም መጽሄት “በአለም ላይ ካሉ 100 ተፅእኖ ፈጣሪ ሰዎች” አንዱ እንደሆነ እውቅና ሰጥቶታል እና ፈጣን ኩባንያ የአፍሪካ ሊደርሺፕ ቡድንን በአለም ላይ ካሉ 50 እጅግ ፈጠራ ፈጣሪ ኩባንያዎች መካከል አካቷል። የመጀመሪያ ህይወት እና ትምህርት አባቱ ጠበቃ እና ዳኛ ነበር; እናቱ አስተማሪ ነች። ሁለቱም ጋናዊ ናቸው፣ ነገር ግን በ4 አመቱ ቤተሰቦቹ ከወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በኋላ ከጋና ሸሹ እና በ18 አመቱ በአፍሪካ በአራት ሀገራት ኖሯል። በሚኒሶታ ማካሌስተር ኮሌጅ ገብቷል። እሱ መጀመሪያ ላይ በጆሃንስበርግ ውስጥ በ ተቀጥሮ በካሊፎርኒያ ስታንፎርድ ምረቃ ትምህርት ቤት ከመግባቱ በፊት፣ ኤምቢኤን ተቀብሎ አርጄ ሚለር ምሁር ተብሎ የተሰየመ ሲሆን ይህም ከእያንዳንዱ ተመራቂ ክፍል 10% ከፍተኛ ሽልማት አግኝቷል። በስታንፎርድ. በስታንፎርድ በነበረበት ወቅት ስዋኒከር ከሥራ ባልደረባው እና መስራቹ ክሪስ ብራድፎርድ ጋር በመሆን የአፍሪካን አመራር አካዳሚ የቢዝነስ እቅድ ፃፉ፣የአፍሪካን የወደፊት መሪዎችን የሚያዘጋጅ ልዩ የፓን አፍሪካ ትምህርት ቤት። ይህም ለአፍሪካ እድገት ትልቅ ማነቆ የሆነው የመልካም አመራር እጦት ነው ብሎ በማመኑ ነው። የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት የሲሊኮን ቫሊ ግንኙነቱን ተጠቅሞ አካዳሚውን በ2004 እንደጨረሰ አስጀመረ። የሙሉ ጊዜ የመኖሪያ አዳሪ ትምህርት ቤት ከአፍሪካ ላሉ ተማሪዎች በዓለም ዙሪያ ላሉ ዩኒቨርሲቲዎች ሲያዘጋጃቸው የአመራር እና የስራ ፈጠራ ችሎታዎችን ያስተምራል። በ2017፣ ወደ 1,000 የሚጠጉ የወደፊት መሪዎች የአካዳሚውን ደረጃዎች ተቀላቅለዋል። ለአብዛኛዎቹ ተማሪዎች ከኮሌጅ ከተመረቁ በኋላ ወደ አፍሪካ እንደሚመለሱ ቃል ከገቡ ክፍያ ተቋርጧል። እ.ኤ.አ. በ2014 በብራዚል በተካሄደው የቴዲ ኮንፈረንስ ስዋኒከር ራዕዩን ማስፋፋቱን አስታውቋል፡ አዲስ የ25 የአፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች ኔትወርክ በመጨረሻ በ2060 3 ሚሊዮን መሪዎችን እንደሚያዘጋጅ አስታውቋል። እ.ኤ.አ. በ2016 መገባደጃ ላይ ሁለት ካምፓሶች ተከፍተዋል አንደኛው በሞሪሺየስ እና ሌላው በሩዋንዳ። ፋስት ካምፓኒ ይህንን የዩኒቨርሲቲዎች ትስስር በአፍሪካ 3ኛው '' ሲል እውቅና ሰጥቷል እና ሲ ኤን ኤን ደግሞ ዩኒቨርሲቲውን 'የአፍሪካ ሃርቫርድ' ሲል የሰየመውን ገፅታ አውጥቷል። የኔልሰን ማንዴላ ሚስት የሆነችው ግራካ ማሼል የዩኒቨርሲቲው ቻንስለር በመሆን እያገለገለች ሲሆን የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶናልድ ካቤሩካ ደግሞ የዩኒቨርሲቲው ግሎባል አማካሪ ካውንስል ሊቀመንበር ሆነው ያገለግላሉ። እ.ኤ.አ. በ2021፣ ለአፍሪካ አመራር ቡድን ለማስተማር ደፋር አዲስ ስልትንም አስታውቋል የስዋኒከር የትምህርት ሥራ ፈጣሪነት ሥራ በዩኤስ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ እና በሌሎች ታዋቂ ዓለም አቀፍ ሰዎች አድናቆት አግኝቷል። ] እሱ እንደ እና የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ወጣት ግሎባል መሪ እውቅና አግኝቷል። እ.ኤ.አ. በ 2011 ፎርብስ መጽሔት የመስመር ላይ ባህሪ በአፍሪካ ከምርጥ አስር ወጣት ሃይሎች አንዱ ተብሎ ተመርጧል። እ.ኤ.አ. በ2006 'በአለም ላይ ካሉ 15 ከፍተኛ ማህበራዊ ስራ ፈጣሪዎች' አንዱ' እንደሆነ አውቆታል። እ.ኤ.አ. በ2017 ፍሬድ ስዋኒከር ሁለት የክብር ዶክትሬቶችን ተቀብሏል- አንደኛው በአሜሪካ ከሚገኘው ሚድልበሪ ኮሌጅ እና ሁለተኛው በደቡብ አፍሪካ ከሚገኘው ከኔልሰን ማንዴላ ዩኒቨርሲቲ። እ.ኤ.አ. በ 2018 ፣ በአሜሪካ ውስጥ ከሚገኘው ማካሌስተር ኮሌጅ ሶስተኛውን የክብር ዶክትሬት አግኝቷል እ.ኤ.አ. በኤፕሪል 2018 ፖል ካጋሜ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አድርገው ሾሟቸው ፣ እሴትን እንደሚጨምሩ እና የሀገሪቱን ከቱሪዝም ገቢ የማስገኘት አጀንዳ ላይ እገዛ ያደርጋሉ። እ.ኤ.አ. በ 2019 በታይም መጽሔት እንደ "በዓለም ላይ ካሉ 100 ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች" አንዱ እንደሆነ ታውቋል እና ፈጣን ኩባንያ የአፍሪካ ሊደርሺፕ ቡድንን በዓለም ላይ ካሉ 50 በጣም ፈጠራ ካምፓኒዎች መካከል አካትቷል። "ፍሬድ ስዋኒከር - የአፍሪካ አመራር አካዳሚ" የአፍሪካ አመራር አካዳሚ፣ 2022፣ /። "ቢቢሲ ወርልድ ሰርቪስ - አውትሉክ፣ የነገውን የአፍሪካ መሪዎች መፍጠር" ቢቢሲ፣ 2022፣ ።
13366
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%8B%E1%88%85
አላህ
በአረቢኛ ድምጽ ያላቸው “ተነባቢ ፊደላት”” 28 ሲሆኑ “አጫዋች ፊደል”” ደግሞ 1 ሲሆን እርሱም “አሊፍ” ነው። በመካከላቸው ስናነባቸው የሚቀጥን ፊደል 19 ሲሆን “ተርቂቅ” ይባላል፣ የሚወፍር ፊደል ደግሞ 7 ሲሆን “ተፍሂም” ይባላል፣ ነገር ግን ተርቂቅና ተፍሂም የሆኑ ሁለት ሃርፎች “ራ” እና “ላም” ናቸው፤ “ራ” በፈትሃና በደማ ይወፍራል በከስራ ይቀጥናል፣ “ላም” ደግሞ በለፍዙል ጀላላ ማለትም በአላህ ስም ላይ ትወፍራለች። ይህንን እሳቤ ይዘን የአላህ ስምን ስናጠና “አሏህ” የሚለው ስም 2699 ጊዜ በቁርአን የመጣ ሲሆን ትርጉሙ “የሚመለክ” ወይም “አምልኮ የሚገባው” ማለት ነው፤ አላህ ኢስሙል ዛት” ማለትም “የህላዌው ስም” ነው፤ “ዛት” ማለት “ምንነት” ሲሆን አላህ በምንነቱ የሚመለክ ነው፤ ይህ ስም በሙያ እንዲህ ተቀምጧል፤ “ኢዕራብ” ማለት “ሙያ”” ማለት ሲሆን ይህ ሙያ “ፈትሐ” “ከስራ” “ደማ” በሚባሉ አጭር አናባቢ ሃርፎች ላይ ያገለግላሉ፦ “መንሱብ”፦ በፈትሐ የሚያገለግለው ሙያ “መንሱብ” ማለትም ተሳቢ ሙያ”” ሲሆን አሏህ በፈትሐ ስንጠቀም “አሏሀ” َ ይሆናል። “መጅሩር”፦ በከስራ የሚያገለግለው ሙያ “መጅሩር” ማለትም አገናዛቢ ሙያ”” ሲሆን አሏህ በከስራ ስንጠቀም “ሊሏሂ” ِ ይሆናል። “መርፉዕ”፦ በደማ የሚያገለግለው ሙያ ደግሞ “መርፉዕ” ማለትም ባለቤት ሙያ”” ሲሆን አሏህ በደማ ስንጠቀም “አሏሁ” ُ ይሆናል። ለምሳሌ፦ “አሏሁ-ማ” َّ ማለት “ያ-አሏህ” ማለት ነው። ይህ ስም የፈለግነውን ሃርፍ ከላዩ ላይ ቢቀነስ ትርጉም አለው፦ @ አሏህ በሚለው መነሻ የመጀመሪያውን አንድ ሀርፍ ስንቀንሰው “ሊሏህ” የሚል ይሆናል፡፡ ትርጉሙም “የአላህ” ማለት ነው። @ አሏህ በሚለው የመጀመሪያዎቹን ሁለት ሃርፎች ስንቀንሰው ደግሞ ውጤቱ “ለሁ” ُ የሚል ይሆናል፡፡ ትርጉሙም “የእርሱ” የሚል ነው፡፡ @ አሏህ በሚለው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ሃርፎች ስንቀንሰው ደግሞ ውጤቱ “ሁ” ُ የሚለው ይሆናል፡፡ ትርጉሙም “እርሱ” የሚል ነው፡፡ @ አሏህ በሚለው ሀርፎች ከመሀል ከሁለቱ የላም ሃርፎች አንዱን ስንቀንሰው ውጤቱ “ኢላህ” የሚለው ይሆናል፤ ትርጉሙ “አምላክ” ማለት ነው፤ “ኢላህ” የሚለው ቃል 147 ጊዜ በቁርአን የመጣ ሲሆን ተባታይ ነው፤ አንስታይ ሲሆን ደግሞ “ኢላሃህ” ነው፤ የኢላህ ብዙ ቁጥር ደግሞ “አሊሀህ” ٌ ነው፤ “ኢላህ” በተለያየ አገናዛቢ ተውላጠ ስም ላይ ሲመጣ፦ “ኢላሂ” “አምላኬ” “ኢላሁና” “አምላካችን” “ኢላሀከ” َ “አምላክህ” “ኢላሀኩም” ْ “አምላካችሁ” “ኢላሀሁ” ُ “አምላኩ” “ኢላሀሁም” ْ “አምላካቸው” ይሆናል። “ኢላህ” ማለት “አምላክ” ተብሎ በትርጉም መጠቀም ይቻላል፤ ግን “አላህ” የተፀውዖ ስም ስለሆነ እራሱ ነው የሚቀመጠው፦ 17:22 “ከአላህ” ጋር ሌላን “አምላክ” አታድርግ፤ የተወቀስክ ረዳት የሌለህ ትሆናለህና ፤ 28:88 “ከአላህም” ጋር ሌላን “አምላክ” አትጥራ َ ፡፡ 26:213 “ከአላህም” ጋር ሌላን “አምላክ” አትጥራ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና َ ፡፡ አሏህ በዕብራይስ አሁንም “ላሜድን” ተሽዲድ ስናደርገው “አሏህ” ‎‎ ሲሆን ከውስጡ ሁለት “ላሜድ” ሲኖረው አንዱን ስንቀንስ እና በፈትሃ ስንጨርሰው “ኤሎሃ” ּ ይሆናል፤ ትርጉሙም “አምላክ” ማለት ነው፤ የኤሎሃ ብዜት ደግሞ “ኤሎሂም” ነው፤ “ኤል” የኤሎሃ ምፃረ-ቃል ሲሆን የኤል ብዜት ደግሞ “ኤሊም” ነው፤ “ያ-አሏህ” “አሏህ ሆ” እና “ወ-ሏህ” “በአሏህ” ይባላል። አሏህ በአረማይክ አሁንም “አሏህ” ሲሆን ከውስጡ “ኤላህ” ማለትም “አምላክ” የሚል ቃል አለ፤ ዋቢ መጽሐፍት፦ እንግዲህ ኢየሱስ፣ ሔኖክ፣ ኖህ እና አብርሐም የሚጠቀሙበት ዘዬ አረማይክ ከነበረ እና ሌሎች የእስራኤል ነብያት የዕብራይስጥ ዘዬ ሲጠቀሙ ከነበረ “አሏህ” የሚለውን ስም መጠቀማቸው ግድ ይላል፤ ነገር ግን አሁን በዘመናችን የአላህ ጥንታዊ ነቢያት የተሰጣቸው ኪታባት የተዋቀረበት አንጓ፣ የተናገሩበት ቋንቋ፣ የመልዕክቱ ምጥቀት ሆነ የቃላቱ ልቀት በዘመናችን እንደሌሉ የታሪክ ምሁራን ያትታሉ፣ ለምሳሌ የእስራኤል ልጆች ውስጥ የነበሩት ነቢያት ሲናገሩበት የነበረው ቋንቋ ዕብራይስጥ ሲሆን እነርሱ የተናገሩበት መጽሐፍት የሉም፣ በጣም ቀደምትነት አለው የሚባለው የነቢያት መጽሐፍት ግልባጭ በግሪክ ሰፕቱአጀንት የተዘጋጀው ሲሆን ከሰፕቱአጀንት በኋላ የተዘጋጁት የሙት ባህር ጥቅል፣ ማሶሬቲክ፣ ሰመሪያን ይህንኑ የግሪኩን መሰረት አድርገው ነው የተተረጎሙት፣ ከሰፕቱአጀንት በፊት የነበረው የነቢያት መጽሐፍት ዛሬ የለም፣ ከሌለ አላህ የሚለው ቃል ይጠቀሙ አይጠቀሙ ምንም ምንጭ የለም ማለት ነው፣ ወደ ኢየሱስም ስንመጣ ኢየሱስ ሲናገርበት የነበረ ቋንቋ አረማይክ ሲሆን ሃዋርያቱም ሲናገሩበት የነበረው ይህን ቋንቋ ነው፣ ነገር ግን ወደ ሁለተኛው ትውልድ ይህ የኢየሱስ ትምህርት ሲገባ የተጻፈው ኮይኔ በሚባል የግሪክ ቋንቋ ነው፣ ስለዚህ ነቢያት አምላካቸውን ማን ብለው እንደነበር የሚያሳይ የቋንቋ መረጃ በዛሬ ጊዜ የለም። አላህ የሚለውን ስም ነቢያቶች ተናግረውት አያውቁም የሚለው አሉባልታ ምንጭ አልባና ሰነድ አልባ ነው፣ ይህን ደፍሮ ለመናገር ስረ-መስረት ያለው አንጓ፣ ቋንቋ፣ ምጥቀት ሆነ ልቀት ያስፈልጋል፣ በተረፈ “”እግዚአብሔር፣ ቴኦስ፣ ጋድ፣ ጉድ”” የሚሉት ቃላት ባዕደ-ቃላት እና ኢላህ ለሚለው ቃል ትርጉም ናቸው እንጂ አሏህ ለሚለው ቃል ትርጉም አይደሉም። አላህ ጥንት ነቢያቶች የሚያመልኩት የነቢያት አምላክ መሆኑን የምናውቀው ከጥንቶቹ ነቢያት ጋር የነበረውን መስተጋብር ለመግለጽ፦ “ቁልና” *አልን* ፣ “አርሰልና” *ላክን*፣ “አውሃይና” *አወረድን* በማለት ጥንትም ነቢያትን ሲልክ የነበረው፣ ግልጠተ-መለኮት** ሲያወርድ የነበረውና በተለያየ መንገድ ሲያናግራቸው የነበረው እርሱ መሆኑን ይገልጻል፦ 1. አልን፦ 20:116 ለመላእክትም፣ ለአዳም ስገዱ፣ *ባልን* ጊዜ አስታውስ፤ 2:35 «አደም ሆይ! አንተ ከነሚስትህ በገነት ተቀመጥ፤ ከርሷም በፈለጋችሁት ስፍራ በሰፊው ተመገቡ፤ ግን ይህችን ዛፍ አትቅረቡ፤ ከበደለኞች ትኾናላችሁና» *አልንም*፡፡ 11:40 ትእዛዛችንም በመጣና እቶኑም በገነፈለ ጊዜ፣ በርሷ ውስጥ ከየዓይነቱ ሁሉ ሁለት ሁለት፣ ወንድና ሴት ቤተሰቦችህንም ቃል ያለፈበት ብቻ ሲቀር ያመነንም ሰው ሁሉ ጫን *አልነው*፤ 22:26 ለኢብራሂምም የቤቱን ስፍራ መመለሻ ባደረግንለት ጊዜ፣ በኔ ምንንም አታጋራ፤ ቤቴንም፣ ለሚዞሩትና ለሚቆሙበት፣ ለሚያጎነብሱትና በግንባራቸውም ለሚደፉት ንጹሕ አድርግላቸው፣ *ባልነው* ጊዜ አስታውስ። 2:125 ወደ ኢብራሂምና ወደ ኢስማዒልም ቤቴን ለዘዋሪዎቹና ለተቀማጮቹም ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ *ስንል* ቃል ኪዳን ያዝን፡፡ 2:60 ሙሳም ለሕዝቦቹ መጠጥን በፈለገ ጊዜ የኾነውን አስታውሱ፡፡ «ድንጋዩንም በበትርህ ምታ» *አልነው*፡፡ 17:2 ሙሳንም መጽሐፉን ሰጠነው፤ ለእስራኤልም ልጆች መሪ አደረግነው፤ ከኔ ሌላ መጠጊያን አትያዙ *አልናቸውም*። 2. ላክን፦ 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ አላህን ተገዙ፤ ጣዖትንም ራቁ፤ በማለት መልክተኛን በእርግጥ *ልከናል*፤ 57:25 መልክተኞቻችንን በግልጽ ማስረጃዎች በእርግጥ *ላክን*፤ 23:32 በውስጣቸውም ከእነሱ የኾነን መልክተኛ አላህን ተገዙ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የላችሁም አትጠነቀቁምን በማለት *ላክን*፡፡ 7:59 ኑሕን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላክነው፤ 11:50 ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን፤ 11:61 ወደ ሠሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ 11:84 ወደ መድየንም ወንድማችውን ሹዐይብን፣ ላክን፤ 3. አወረድን፦ 4:163 እኛ ወደ ኑሕና ከርሱ በኋላ ወደ ነበሩት ነቢያት *እንዳወረድን*፣ ወደ አንተም *አወረድን*፤ ወደ ኢብራሂምም፣ ወደ ኢስማዒልም፣ ወደ ኢስሐቅም፣ ወደ ያዕቆብም፣ ወደ ነገዶቹም ወደ ዒሳም፣ ወደ አዮብም፣ ወደ ዩኑስም፣ ወደ ሀሩንና ወደ ሱለይማንም *አወረድን*፤ ለዳዉድም ዘቡርን ሰጠነው። 21:25 ከአንተ በፊትም፣ እነሆ ከኔ ሌላ አምላክ የለምና ተገዙኝ፣ በማለት ወደርሱ *የምናወርድለት* ቢሆን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም። 12:109 ካንተ በፊትም ከከተሞች ሰዎች ወደ እነርሱ ራዕይ *የምናወርድላቸው* የሆኑን ወንዶችን እንጂ አልላክንም፤ 21:7 ከአንተም በፊት ወደ እነርሱ *የምናወርድላቸው* የኾኑ ሰዎችን እንጂ ሌላን አልላክንም፤ 16:43 ከአንተም በፊት ወደ እነርሱ ወሕይን *የምናወርድላቸውን* ሰዎችን እንጂ፣ ሌላን አልላክንም፤ አላህ የነቢያት አምላክ ነው፤ ኑሕ፣ ሁድ፣ ሷሊህ፣ ኢብራሒም፣ ሹዐይብ፣ ሙሳ እና ኢሳ አላህ እያሉ ይጠቀሙ እንደነበር ቃሉ ይነግረናል፦ 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ “አላህን” አምልኩ፤ ጣዖትንም ራቁ፤ በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤ 11:25-26 ኑሕንም ወደ ሕዝቦቹ በእርግጥ ላክን፤ አላቸውም ፦ እኔ ለናንተ ግልጽ አስፈራሪ ነኝ። አላህን እንጂ ሌላን አትገዙ፤ እኔ በናንተ ላይ የአሳማሚን ቀን ቅጣት እፈራላችኋለሁና። 11:50 ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን አላቸው ፦ ወገኖቼ ሆይ አላህን ተገዙ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፤ እናንተም ቀጣፊዎች እንጂ ሌላ አይደላችሁም። 11:61 ወደ ሠሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ ፦ሕዝቦቼ ሆይ አላህን ተገዙ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ፣ የላችሁም፤ .. አላቸው። 19:48 እናንተንም ከአላህ ሌላ የምትግዙትንም እርቃለሁ፤ ጌታየንም እግዛለሁ፤ ጌታየን በመገዛት የማፍር አለመኾኔን እከጅላለሁ። 11:84 ወደ መድየንም ወንድማችውን ሹዐይብን፣ ላክን፤ አላቸው ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ የላችሁም፤ ስፍርንና ሚዛንንም አታጉድሉ፤ እኔ በጸጋ ላይ ሆናችሁ አያችኋለሁ፤ እኔም በናንተ ላይ የከባቢን ቀን ቅጣት እፈራለሁ። 7:104-105 ሙሳም አለ፦ፈርኦን ሆይ! እኔ ከዓለማት ጌታ የተላክሁ መልክተኛ ነኝ፤ በአላህ ላይ ከእውነት በቀር አለመናገር ተገቢዬ ነው፤ ከጌታችሁ በታምር በእርግጥ መጣኋችሁ፤ የእስራኤልንም ልጆች ከኔ ጋር ልቀቅ። 3:51 አላህ ጌታየና ጌታችሁ ነዉ፤ ስለዚህ ተገዙት፤ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነዉ አላቸዉ። ነጥብ ሶስት “አሏህና ታሪካዊ ፍሰት” አሏህ የሚለው ስም ነብያችን ነብይ ሆነ ከመላካቸው በፊትና ቁርአን ከመውረዱ በፊት በሴመቲክ ዳራ ደግሞ ከሁሉ በላይ የሆነው አንዱ አምላክ ሲጠራበት የነበረ ስም እንደነበር የተለያየ መድብለ-እውቀቶች** ሆኑ ታሪካዊ ፍሰቶች ያትታሉ፦ 1. የሃይማኖት መድብለ-እውቀት 1987: “አላህ የሚለው ስም ስረ-መሰረት የጋራ በሆኑ በተለያዩ ጥንታዊ የሴም ቋንቋዎች ይገኛል” ገጽ 27. 2. የክርስትና መድብለ-እውቀት 2001: “ ቅድመ-ቁርአን አረብ ተናጋሪ ክርስቲያንና አይሁድ እንዲሁ አላህ ለታላቁ አምላክ ይጠቀሙበት ነበር” ገጽ 101. 3. የኢስላም መድብለ-እውቀት 1913: “አረቦች ቅድመ-ነቢዩ ሙሃመድ በነበሩት ዘመናት አላህ የሚባል ታላቅ አምላክ ያመልኩ ነበር” ገጽ 302. 4. የብሪታኒካ መድብለ-እውቀት 1996: “ቅድመ-ቁርአን በነበሩት አረቢያን መጽሐፍት ውስጥ አላህ የሚለው ቃል ይገኛል” ገጽ 106. አላህ እና ጣዖታት አንድን እምነት ለማመን ቅድሚያ ስለዚያ እምነት በቂ እውቀት ይጠይቃል፤ በመሃይምነት እውር ድንብር የሆነ ፀለምተኛ እምነት መከልተል በኢስላም አይሰራም፦ 17፥36 ለአንተም በእርሱ #እውቀት #የሌለህን ነገር #አትከተል፤ የእውቀት መጀመሪያ ደግሞ የፈጠረንን ፈጣሪያችንን ማወቅ ነው፤ በኢስላም የመጀመሪያው እርምጃ “ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩ” ማመን ሳይሆን “ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩን” ማወቅ ነው፦ 47:19 እነሆ “ከአላህ ሌላ አምላክ” ُ አለመኖሩን #እወቅ፤ "ላ ኢላሃ ኢለ ሏህ" ُ "ከአሏህ በቀር ሌላ አምላክ የለም" ማለት ነው፣ ጣኦታትን የምንክድበት፣ ከአላህ ሌላ በሃቅ ሊመለክ የሚችል አምላክ አለምኖሩን የምናምንበት ቃለ-ምስክርነት ነው፦ 2:256 ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ፡፡ #በጣዖትም "የሚክድ" እና #በአላህ "የሚያምን" ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ፡፡ 39:17 እነዚያም #ጣዖትን "የሚያመልኳት" ከመሆን የራቁ ወደ #አላህም የዞሩ ለእነርሱ #ብስራት አላቸው፤ ስለዚህ ባሮቼን አብስር ። 43፥26-27 ኢብራሂምም ለአባቱ እና ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ አስታውስ፦ "እኔ ከምታመልኩት ሁሉ #ንጹሕ ነኝ፤ ከዚያ #ከፈጠረኝ #በቀር #አላመልክም እርሱ በእርግጥ ይመራኛልና"። 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ "#አላህን #አምልኩ #ጣዖትንም #ራቁ" በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤ ይህ ቃለ-ምስክርነት በቁርአን "ጠንካራን ዘለበት" ይባላል፦ 31:22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ُ ወደ አላህ የሚሰጥም ْ ሰው፣ #ጠንካራ #ገመድ ِ በእርግጥ ጨበጠ፤ የነገሩም ሁሉ ፍጻሜ ወደ አላህ ነው። 2:256 በጣዖትም የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን #ጠንካራ #ዘለበት ِ በእርግጥ ጨበጠ፡፡ አላህም ሰሚ ዐዋቂ ነው፡፡ ይህ ቃለ-ምስክርነት ሁለት ማዕዘናት አለው፤ አንደኛው ነፍይ ሲሆን ሁለተኛ ኢሥባት ነው፤ ይህንን እሳቤ ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦ ነጥብ አንድ "ነፍይ" ማለት "አፍራሽ" ሲሆን አሉታዊ ቃል ነው፤ ይህም አሉታዊ ቃል፦ "ላ ኢላሃ" َ "ሌላ አምላክ የለም" ብለን ስንል ማንኛውንም ጣኦታት ውድቅ የምናደርግበት ነው፤ በቁርአን ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ "ጣኡት" ِ ፣ "አውሳን" እና "አስናም" ይባላሉ፣ እነዚህ ጣኦታት ከዓለማቱ ጌታ ሌላ የሚመለኩ ምንነትና ማንነት ናቸው፤ እጅጉን ከዓለማቱ ጌታ ከአላህ ተለይተው ተቀምጧል፦ 1. "ጣኡት" 2:256 #በጣዖትም ِ የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ፡፡ 4:76 እነዚያ ያመኑት ሰዎች፣ በአላህ መንገድ ይጋደላሉ፤ እነዛ የካዱትም #በጣዖት ِ መንገድ ይጋደላሉ፤ 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ አላህን አምልኩ #ጣዖትንም ِ ራቁ፤ በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤ 29:17 ከአላህ ሌላ የምታመልኩት #ጣዖታትን ብቻ ነው፤ ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፤ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኩአቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፤ 29:25 ኢብራሂም አለም፦ ከአላህ ሌላ #ጣዖታትን አማልክት የያዛችሁት በቅርቢቱ ሕይወት በመካከላችሁ ለመዋደድ ብቻ ነው፤ ከዚያም በትንሣኤ ቀን ከፊላችሁ በከፊሉ ይክዳል፤ ከፊላችሁም ከፊሉን ይረግማል፤ መኖሪያችሁም እሳት ናት፤ ለእናንተም ከረዳቶች ምንም የላችሁም። 3. "አስናም" 6:74 ኢብራሒምም ለአባቱ ለአዘር «#ጣዖታትን አማልክት አድርገህ ትይዛለህን እኔ አንተንም ሕዝቦችህንም በግልጽ መሳሳት ውስጥ ኾናችሁ አያችኋለሁ» ባለ ጊዜ አስታውስ. 21:57 በአላህም ስም እምላለሁ ዟሪዎች ሆናችሁ ከኼዳችሁ በኋላ #ጣዖቶቻችሁን ተንኮል እሰራባቸዋለሁ፣ አለ። 14:35 ኢብራሂምም ባለ ጊዜ አስታውስ ፦ ጌታዬ ሆይ! ይህንን አገር ጸጥተኛ አድርገው፤ እኔንም ልጆቼንም #ጣዖታትን ከማምለክ አርቀን፤ ነጥብ ሁለት "ኢሥባት" ማለት "ማፅደቅ" ሲሆን አውንታዊ ቃል ነው፤ ይህም አውንታዊ ቃል፦ "ኢለ ሏህ” ُ "ከአላህ በቀር" ብለን ስንል አንዱን አምላክ በብቸኝነትና በእውነት ልናመልከው የምናፀድቅበት ነው፤ አንዱ እምላክ አላህ ነገሮችን ካለመኖር ወደመኖር የፈጠረ፣ የሚያሞት ህያው የሚያደርግ፣ መጥቀምና መጉዳት የሚችል፣ ሁሉን የሚያውቅ፣ ሁሉን የሚያይ፣ ሁሉን የሚሰማና በእኔነት የሚናገር ነው፦ 1. "ሁሉን የፈጠረ ነው" 46:4 #ከአላህ ሌላ የምታመልኳቸው አያችሁን? ከምድር ምንን እንደ #ፈጠሩ# አሳዩኝ ወይም በሰማያት ለእነርሱ መጋራት አላቸውን? 50:38 ሰማያትንና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ #ፈጠርን፡፡ 49:13 እላንተ ሰዎች ሆይ እኛ ከወንድና ከሴት #ፈጠርናችሁ፤ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፤ 2. "የሚያሞት ህያው የሚያደርግ ነው" 30:40 አላህ ያ የፈጠራችሁ፣ ከዚያም ሲሳይን የሰጣችሁ፣ ከዚያም #የሚያሞታችሁ#፥ ከዚያም #ሕያው# የሚያደርጋችሁ ነው፤ ከምታጋሩዋቸው ጣዖታት ውስጥ ከዚኻችሁ አንዳችን የሚሠራ አልለን? 44:8 ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ #ሕያው ያደርጋል#፣ #ያሞታልም፣ ጌታችሁ፣ የመጀመሪያ አባቶቻችሁም ጌታ ነው። 3. "መጥቀምና መጉዳት የሚችል ነው" 20:89 ወደ እነነሱ ንግግርን የማይመልስ ለእነርሱም #ጉዳትንና #ጥቅምን የማይችል መሆኑን አያዩምን? 10:106 ከአላህም በቀር #የማይጠቅምንና #የማይጎዳን አታምልክ፡፡ ብትሠራም አንተ ያንጊዜ ከበደለኞቹ ትሆናለህ» ተብያለሁ" በላቸው፡፡ 5:76 ከአላህ ሌላ ለእናንተ #መጉዳትንና #መጥቀምን የማይችልን ታመልካለህን? በላቸው፤ 4. "ሁሉን የሚያውቅ ነው" 60:1 #እኔ የምትደብቁትንና የምትገልጹትን #የማውቅ ስሆን ወደ እነርሱ በፍቅር ትመሣጠራላችሁ፤ 64:4 በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለውን ሁሉ ያውቃል፤ የምትደብቁትንም የምትገልጡትንም ያውቃል አላህ በልቦች ውስጥ ያለውን ሁሉ ዐዋቂ ነው። 5. "ሁሉ ተመልካች ነው" 34:11 #እኔ የምትሠሩትን ነገር ሁሉ ተመልካች ነኝና። 57፥4 #አላህም የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው። 6. "ሁሉን የሚሰማ ነው" 2:186 ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ፡- እኔ ቅርብ ነኝ፡፡ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ #እቀበለዋለሁ፡፡ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፤ በእኔም ይመኑ፤ እነርሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡ 9:103 ለእነርሱም ጸልይላቸዉ፤ ጸሎትህ ለእነርሱ እርካታ ነዉና አላህም "ሰሚ" ዐዋቂ ነው። 7. "እኔነት ያለው ተናጋሪ ነው" 21:92 "#እኔም" ጌታችሁ #ነኝ እና "አምልኩኝ"። 2:160 እነዚህም በእነርሱ ላይ ጸጸታቸውን እቀበላለሁ፤ #እኔም ጸጸትን በጣም ተቀባይ አዛኙ #ነኝ፡፡ ነብያችን"" ወደ መካ ሲገቡ በካዕባህ የሚመለኩ 360 ጣዖታትን ሰባብረዋል፤ ያስቀሩት አንድም ጣዖት የለም፤ አል-ሐጀሩል አስወድ ከ 360 ጣዖታት መካከል ነበር የሚለው ዲስኩር የሚሽነሪዎች ቅጥፈት እንጂ የታሪክ ሆነ የሥነ-ቅርስ መረጃ የለም፤ ሐጀሩል አስወድ መጉዳትንና መጥቀምን የማይችልና የአላህን ቤት መዞር የሚጀመርበት መነሻ ነጥብ እንጂ አምልኮ የሚቀበል አይደለም። ይህንን ከሐዲስ መረዳት ይቻላል፦ ኢማም ቡሃሪ መጽሐፍ 25, ሐዲስ 83: ዑመር ወደ ሃጀሩል አስወድ ቀረቦ ሳመውና፦ አውቃለው #አትጠቅምም #አትጎዳም ነብዩ"" ሲስሙህ ባላይ ኖሮ አልስምህም ነበር። ሃጀሩል አስወድ መስማት፣ መናገር፣ ማየት፣ ማወቅ የማይችል ህያው ያልሆነው ነገር ነውና አይጠቅምም አይጎዳም፣ የማይጠቅምና የማይጎዳ ነገር አይመለክም፤ የሚመለከው መጥቀና መጉዳት የሚችለው የሰማያትና የምድር ጌታ ብቻ ነው፦ 13:16 የሰማያትና የምድር ጌታ ማን ነው? በላቸው፤ አላህ ነው በል፤ #ለነፍሶቻቸው #ጥቅምንም #ጉዳትንም የማይችሉን ረዳቶች ከእርሱ ሌላ ያዛችሁን? በላቸው፤ የፈጣሪ ሃቅ አምልኮ፣ መለማመን፣ ስለት መሳል፣ መስገድ ወዘተ ነው፤ ይህንን ሃቅ ከመሳም ጋር ማምታታት የለብንም፤ ሲጀመር "መሳም" የመውደድ መገለጫ እንጂ በራሱ መውደድ አይደለም፤ ምክንያቱም ሳንስማቸው የምንወዳቸው ሰዎች ስላሉ፤ ሲቀጥል "መሳም" የፈጣሪ ሃቅ አይደለም፤ ፈጣሪ አይሳምምና፤ ሲሰልስ "መሳም" የፍጡራን መብት ነው፤ አንድ ሰው አባቱን ሳመ ማለት አመለከ ማለት አይደለም፤ አንድ ሰው በእግር ኳስ አሸንፎ ዋንጫ ቢስም አመለከ አይባልም፤ ለሃጅሩል አስወድ አምልኮ፣ መለማመን፣ ስለት መሳል፣ መስገድ ወዘተ ቢቀርብ ኖሮ ይህ ማሻረክ ወይም ባእድ አምልኮ ይሆን ነበር፤ ነገር ግን ይህ ፈፅሞ ሽርክ ነው፤ በኢስላም በድንጋይና በድንጋይ ላይ የሚደረግ አምልኮ "ኑሱብ" እና "አዝላም" ሲባል በአላህ ላይ ማሻረክ የሆነ አመፅ ነው፦ 5:90 እላንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ፣ ቁማርም፣ "አንሳብ" ُ "አዝላምም"* ِ ከሰይጣን ሥራ የሆኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፤ እርኩስን ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና። 5:3 ለኑሱብ" ِ የታረደው *በአዝላምም* ِ ዕድልን መፈለጋችሁ በእናንተ ላይ እርም ተደረገ ይሃችሁ "አመፅ" ነው። በእስልምና እምነት አላህ ማለት በሴማዊ ቋንቋ ውስጥ "አምልኮ የሚገባው"ፍፁም ፍጥረታትን የማይመስል፣ ከ"" (ከዙፋኑ) በላይ ያለ ፣ ከፍጥረታቱ የተነጠለ፣ በአዕምሮ መንሰላሰል ሊደረስበት የማይችል ኃያል ጌታ ማለት ነው። ከነብዩ ከአደም (አ.ሰ) ጀምሮ እስከ ነብዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) ድረስ ያሉትን በቁርአን ላይ እንደተጠቀሱት ፪፭ ሃያ አምስት እና ከዛ በላይ ያልተጠቀሱ ነብያትን የላከ አንድ እና ብቸኛ አምላክ. አላህ በቁርአን ላይ የተጠቀሱ ፱፱ (ዘጠና ዘጠኝ) ስሞች አሉት ሁሉም የሚናገሩት ስለማነነቱ እና ስለባህሪዉ ነዉ. የአላህን ለማወቅ የፈለገ ሰዉ ስሞችሁን ማስተንተን እና መረዳት ከቻለ አልላህን በመጠኑም ቢሆን ማወቅ ይችላል አሏህ መ በቁርኣን አላህ 99 ባሕርያቱን የሚገልጹ ስሞች አሉት== አላህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል አስማኡል ሁስና ٰመልካም ስሞች አሉት፦ 59:24 እርሱ አላህ ፈጣሪው ከኢምንት አስገኚው ቅርጽን አሳማሪው ነው፤ ለርሱ መልካም ስሞች ٰ አሉት፤ 20:8 አላህ ከርሱ ሌላ አምላክ የለም ለርሱ መልካም የሆኑ ስሞች ٰ አሉት። 17:110 ፦አላህን ጥሩ፤ ወይም አልረሕማንን ጥሩ፤ ማንኛውንም ብትጠሩ፣ መልካም ነው፤ ለርሱ መልካም ስሞች ٰ አሉትና በላቸው፤ 7:180 ለአላህም መልካም ስሞች ٰ አሉት፤ ስትጸልዩ በርሷም ጥሩት እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተውዋቸው፤ እነዚህ 99 የባህርይ መልካም ስሞች በቁርአን የተገለጹት ናቸው እንጂ የአላህ መልካም ስሞች 99 ብቻ ናቸው ማለት አይደለም፣ ” አላህ 99 ስሞች አሉት ” ነው እንጂ ” የአላህ ስሞች 99 ናቸው ” የሚል የለም፣ ምክንያቱም ነቢያችን ራስህን በሰየምክበት፡ በመጽሐፍህም ውስጥ በጠቀስከው፡ ከፍጡሮችህም ለማንኛውም ባሳወቅከው፡ አንተ ዘንድም ብቻህን ባወቅከው ስሞችህ እለምንሀለሁ ብለዋል፦ በቁርአን የተገለጹ 99 ስሞች ማፈዝ፣ ማወቅ፣ ትርጉማቸውን ተረድቶ በእነዚህ ስሞች አላህን መጥራት የጀነት ያደርጋል፦ 3.ትርጉማቸውን መረዳትና መተግበር ነጥብ ሶስት የአላህ ስሞች የሚከተሉት ናቸው፦ 1.አል-ረሕማን፦ ሙእሚንም ካሐዲም ለሆኑ ፍጡራን እዝነቱ ሰፊና ትልቅ:: 1.1 2.አር-ረሒም፦ ለሙእሚኖች በተለየ ሁኔታ በጎ ዋይ እና አዛኝ::1.1 3.አል-መሊክ፦ በግዛቱ ያሻውን የሚፈጽም ንጉስ:: 59.23 4.አል-ቁዱስ፦ ሊታሰብ ከሚችል ባህሪ ሁሉ የጸዳ::59.23 5.አስ-ሰላም፦ ሰላሙን በፍጡራኑ ላይ የሚያሰፍን::59.23 6.አል-ሙእሚን፦ የተናገረውን የሚያጸድቅ ታማኝ::59.23 7.አል-ሙሀይሚን፦ በምሉእ ችሎታው ሁሉንም ነገር የሚቆጣጠር:: 59.23 8.አል-ዓዚዝ፦ አቻ የለሽ ሐያልና አሸናፊ:: 59.23 9.አል-ጀባር፦ ፈቃዱን በሐይል የሚፈጽም፣ ጠጋኝ እና ፈዋሽ::59.23 10.አል-ሙተከቢር፦ የልዕልና ባህሪያቱ ብቸኛ ባለቤት::59.23 11.አል-ኻሊቅ፦ ፍጡራንን በፈቃዱ የፈጠረ::59.23 12.አል-ባሪእ፦ ፍጡራንን በፈቃዱ ያስገኘ::59.23 13.አል-ሙሶዊር:- ለእያንዳንዱ ፍጡር የተለየ ቅርጽ የሰጠ::59.23 14.አል-ገፋር፦ መጥፎ ድረጊትን ይቅር የሚል::20.82 15.አል-ቀህሃር፦ አምባነገኖችን ሁሉ የሚያሸንፍ::12.39 16.አል-ወህሃብ፦ በችሮታው የሚያንበሸብሽ::3.8 17.አል-ረዛቅ፦ ሲሳዮችን የሚሰጥ::51.59 18.አል-ፈትታሕ፦ ለባሮቹ የችሮታውን ካዝናዎች የሚከፍት::32.26 19.አል-ዓሊም:- በእውቀቱ ሁሉንም ነገር ያካበበ::2.158 20.አል-ቃቢድ:- ከፍጡራኑ ለሚሻው፣ የፈለገውን ነገር የሚነሳ::2.245 21.አል-ባሲጥ :- ምስጢራቱን ለሚሻው አካል የሚያካፍል::2.245 22.አል-ኻፊድ:- ካሐድያንና ወንጀለኞችን ዝቅ የሚያደርግ::56.3 23.አር-ራፊዕ:- ወዳጆቹን ከፍ የሚያደርግ::58.11 24.አል-ሙዒዝ:- እርሱን ለሚታዘዙ አማኞች ክብር የሚለግስ::3.26 25.አል-ሙዚል:- ከሀዲያንን የሚያዋርድ::3.26 26.አስ-ሰሚዕ :- ፍጡራንን ሁሉ የሚሰማ:: 2.127 27.አል-በሲር:- ፍጡራንን ሁሉ የሚመለከት::4.58 28.አል-ሐኪም:- የነገሮችና የፍርዶች ሁሉ መመለሻ::22.69 29.አል-ዓድል:- በግዛቱ ውስጥ ነውር ወይም ጉድለት የሌለበት::6.115 30.አል-ለጢፍ:- ለባሮቹ የሚያዝን::6.103 31.አል-ኸቢር:- ግልጽም ስውርም የሆኑ ነገሮችን ሁሉ የሚያውቅ::6.18 32.አል-ሐሊም:- ለቅጣት የማይቸኩል::2.235 33.አል-ዐዚም:- ከአእምሮ ግንዛቤና ችሎታ በላይ የሆነ::2.255 34.አል-ገፉር:- ጠላቱን የሚምርና ተውበትን የሚቀበል::2.173 35.አሽ-ሸኩር :- ባሮቹን የሚመነዳ::35.30 36.አል-ዐሊይ:- ከሁሉ በላይ የኾነው::4.34 37.አል-ከቢር :- ከአልባሌ ነገሮች የጠራ::13.9 38.አል-ሐፊዝ:- ፍጡራንን ከመናጋት የሚጠብቅ::11.57 39.አል-ሙቂት:- ለፍጡራን ቀለባቸውን የሚፈጥር እና የሚያከፋፍል::4.85 40.አል-ሐሲብ:- የፍጡራንን ጉዳይ በፍትህ የሚተሳሰብ::4.86 41.አል-ጀሊል:- ልእልናውና ምሉእነቱ የላቀ::55.27 42.አል-ከሪም :- ስጦታው የማይነጥፍ::27.40 43.አር-ረቂብ:- ፍጡራንን የሚያውቅና የሚከተታተል::4.1 44.አል-ሙጂብ:- ዱዓን ተቀባይ::11.61 45.አል-ዋሲዕ :- እውቀቱ በጊዜና በቦታ የማይወሰን::2.268 46.አል-ሐኪም:- ከምሉእነቱ ጋር የሚቃረኑ ተግባራትን ከመፈጸም የጠራ::31.27 47.አል-ወዱድ:- ፍጡራኑን የሚወድ::11.90 48.አል-መጂድ:- በማንነቱም ሆነ በስራው የላቀ::11.73 49.አል-ባኢሥ:- ሙታንን ለምርመራ የሚቀሰቅስ::22.7 50.አሽ-ሸሂድ :- ግልጽም ስውርም የሆኑ ጉዳዮችን ሁሉ የሚመለከት::4.166 51.አል-ሐቅ:- ከሁሉንም ነገር የላቀ እውነት::6.62 52.አል-ወኪል:- የሁሉንም ጉዳዮች ሐላፊና ከዋኝ።3.173 53.አል-ቀዊይ:- ምንም ነገር የማይሳነው::22.40 54.አል-መቲን:- ምንም ነገር የማያሸንፈው::51.58 55.አል-ወሊይ:- በወዳጆቹ ተወዳጅ፣ የነርሱ ረዳትና አለኝታ::4.45 56.አል-ሐሚድ:- ለምስጋናና ለውዳሴ ተገቢ::14.8 57.አል-ሙሕሲ:- ጥቃቅን ጉዳዮች የማያመልጡትና ታላላቆች የማይሳኑት::72.28 58.አል-ሙብዲእ:- ፍጡራንን መጀመሪያ ካልነበሩበት ያስገኘ ፈጣሪ::10.34 59.አል-ሙዒድ:- ፍጡራንን ወደ ሞት የሚመልስ::10.34 60.አል-ሙሕይ:- የበሰበሱ አጥንቶችን ዳግመኛ ሕያው የሚያደርግ::70.158 61.አል-ሙሚት:- ነፍስን ከአካል በመነጠል የየሚያሞት::7.158 62.አል-ሐይ:- ያለና የሚኖር ሕያው::2.255 63.አል-ቀዩም:- ሁሉንም ነገር ያለ ረዳት የሚያከናውን::2.255 64.አል-ዋጅድ:- የሚፈልገውንና ያሻውን ሁሉ ማግኘት የሚችል::38.44 65.አል-ማጅድ:- የተላቀ ችሮታና በጎ ምግባር ባለቤት::85.15 66.አል-ዋሒድ:- በህላዌው አንድ የሆነ::2.163 67.አል-አሐድ:- በማንነት አንድ የሆነ::112.1 68.አስ-ሰመድ:- ጉዳዮች የሚከጀሉበት መጠጊያ::112.2 69.አል-ቃዲር:- ሁሉንም ነገር ያለ ረዳት የሚያከናውን ሁሉን ቻይ::6.65 70.አል- ሙቅተዲር:- የሻውን ነገር የሚወስን::18.45 71.አል-ሙቀዲም:- ከፍጡራን የሚሻውን የሚያስቀድም::16.61 72.አል-ሙአኽኺር:- ጠላቶቹን ከእዝነቱ በማራቅ የሚያዘገይ::71.14 73.አል-አወል:- ሁሉንም ነገር የቀደመ::57.3 74.አል-አኺር:- ፍጡራን ከጠፋ በኋላ ወደኋላ የሚቀር::57.3 75.አዝ-ዛሂር:- በምልክቶቹ፣ በተአምራቱና በአድራጎቱ ግልጽ የሆነ::57.3 76.አል-ባጢን:- ከእይታ የተሰወረ፣ ሚስጥራትን ሁሉ አዋቂ:: 57.3 77.አል-ዋሊ:- የነገሮች ባለቤት፣ በችሮታው ውለታ የሚውል።13.11 78.አል-ሙተዓል:- ደረጃው ከፍ ያለ፣ በክብሩና በሕልውናው የላቀ::13.9 79.አል-በር:- ለለመኑት ቸር::52.28 80.አት-ተዋብ:- ከባሮቹ ተውበትን ንስሃን የሚቀበል::2.128 81.አል-ሙንተቂም:- ብቀላው የሚፈራ::32.22 82.አል-ዓፍዉ:- ወንጀልን የሚያብስ::4.99 83.አር-ረኡፉ :- ለባሮቹ በጣም አዛኝ::3.30 84.ማሊከል ሙልክ:- በንግስናው የፈለገውን የሚያደርግ::3.26 85.ዙልጀላሊ ወልኢክራም:- የልእልናዎችና የልቅናዎች ሁሉ ባለቤት::55.27 86.አል-ሙቅሲጥ:- ፍትሕ አስፋኝ ፍትሐዊ::7.29 87.አል-ጃሚዕ:- ሁሉ የሰበሰበ ሰብሳቢ::3.9 88.አል-ገንይ:- አንዳች ነገር የማይከጅል ሐብታም::3.97 89.አል-ሙግኒ:- ከባሮቹ ለሚሻው ሰው የሚሰጥ::9.28 90.አል-ማኒዕ:- ባሮቹን ለመጠበቅ የሚያቅብ::67.21 91.አድ-ዷር:- ከባሮቹ የሚሻውን የሚጎዳ::6.17 92.አን-ናፊዕ:- የመጥቀም ባለቤት::30.37 93.አን-ኑር:- የእውነተኞችን ልቦናዎች የሚያበራ::24.35 94.አል-ሃዲ:- ሁሉንም ነገር የፈጠረና የመራ::22.54 .95.አል-በዲዕ:- ጥበበ-ረቂቅ ፈጣሪ::2.117 96.አል-ባቂ:- ዝንተ ዓለም የሚኖር::55.27 97.አል-ዋሪስ:- ፍጡራንን ሁሉ ወራሽ::15.23 98.አር-ረሺድ:- የሚመራ አመላካች::2.256 99.አስ-ሰቡር:- የሚታገስ፣ የማይቸኩል። 2.153
3410
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%88%9E%20%E1%8B%8D%E1%8B%B5%E1%8A%90%E1%88%85
ማሞ ውድነህ
ማሞ ውድነሀህሀህሀህሀህህ የቴአትር ደራሲ፥ ጋዜጠኛና ለ12 አመት የቀድሞው የኢትዮጵያ ደራሲዎች ማኅበር ሊቀ መንበር ነበሩ ። በአቡነ ጳውሎስ በሚመራው የሃይማኖት ኮሚቴ ውስጥ በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል ሰላምን ለማምጣት ጥረት ካደረጉ ሰዎችም አንዱ ነበሩ። የ54 መጻህፍት ደራሲና ተርጓሚ የነበሩት አቶ ማሞ በማስታወቂያ ሚኒሰቴር ስር በሚታተሙ ጋዜጦችና መጽሔቶች በጋዜጠኝነት የሰሩ ሲሆን የፖሊስና እርምጃው ጋዜጣ መስራችና ተባባሪ ዋና አዘጋጅ ነበሩ፡፡ በኤርትራ ጠቅላይ ግዛት የማስታወቂያ ሚኒስቴር ተጠሪ ሆነዉ በተመደቡበት የጋዜጠኝነትና የፖለቲካ ስራ በተጨማሪ ህብረት በተሰኘዉ ሳምንታዊ የአማርኛ ጋዜጣ ዘገባዎችና ትንታኔዎች ያቀርቡ ነበር። ባደረባቸዉ ሕመም ምክንያት በተለያዩ ሆስፒታሎች ህክምናቸዉን ሲከታተሉ የነበሩት አቶ ማሞ ዓርብ የካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡ፀሎተ ፍትሐቱ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳዉሎስ ፓትሪያሪክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ መሪነት ተፈፅሟል፡፡ አስክሬናቸውም በደራሲ ሐዲስ ዓለማየውና ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድኅን መካነ መቃብር አጠገብ አርፏል፡፡ በቀብራቸዉ ላይ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ የቀድሞዉ የአዲስ አበባ ከንቲባዎች ከንቲባ ዘውዴ ተክሉና ከንቲባ ብርሃነ ደሬሳ ተገኝተዋል፡፡ ጥቅምት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. በቀድሞው የወሎ ክፍለ ሃገር በዋግ አውራጃ ዐምደ ወርቅ ከተማ ከአባታቸው አቶ ውድነህ ተፈሪና ከእናታቸው ወይዘሮ አበበች ወልደየስ የተወለዱት ማሞ ውድነህ በፋሺስት ኢጣልያ ወረራ ጊዜ ወላጆቻቸውን አጥተዋል። የሕይወት አጋጣሚ በሻጊያን በቦምብ ከደደቡት ፓይለቶች አንዱን እንዲያገኙ አብቅቶያችው ይቅር እንዳሉት በአንድ ጽሁፋቸው ዘግበዋል ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በ 15 አመታቸው የጀመሩት አቶ ማሞ በተለያዩ ችግሮች ምክኒያት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን መጨረስ ባይችሉም በአዲስ አበባ እና አስመራ ውስጥ የሚታተሙ ፖሊስ እና እርምጃው፣ህብረት እና የዛሬይቱ ኢትዮጲያ የተሰኙ ጋዜጦች ውስጥ አገልግለዋል። የግል ህይወት አቶ ማሞ ከባለቤታቸዉ ወይዘሮ አልማዝ ገብሩ ስድስት ልጆችና 10 የልጅ ልጆችን አፍርተዋል፡፡ የደራሲ ማሞ ውድነህ ገጸ በረከቶች አቶ ማሞን ይበልጥ ታዋቂና ተወዳጅ ያደረጋቸው በሥነ ጽሑፉ መስክ ያበረከቱት መጠነ ብዙና ዘርፈ ሰፊ የድርሰት ሥራዎቻቸው ናቸው፡፡ 53 መጻሕፍት ያሳተሙ ሲሆን፣ 54ኛው ‹‹ጣጣኛው›› ልብወለድ በሕትመት ላይ ነው፡፡ ሥራዎቻቸው በስለላ፣ በታሪክ፣ በልብለወድና በተውኔት ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡ ከነዚህ ውስጥ የሚከተሉት ይገኛሉ። 1.ሁለተኛው የዓለም ጦርነት 2.የሴቷን ፈተና 3.ከወንጀለኞቹ አንዱ 4.ቬኒቶ ሙሶሊኒ 5.የገባር ልጅ 6.ሁለቱ ጦርነቶች 7.አደገኛው ሰላይ 8.ዲግሪ ያሳበደው 9.ካርቱም ሔዶ ቀረ? 10.የ፮ቱ ቀን ጦርነት 11.የደቡብ ሱዳን ብጥብጥ 12.ብዕር እንደዋዛ 14.የኤርትራ ታሪክ 15.“የኛው ሰው በደማስቆ“ 16.የ፪ ዓለም ሰላይ 18.ሰላዩ ሬሳ 19.የ፲፯ቱ ቀን ጦርነት 20.የካይሮ ጆሮ ጠቢ 21.የበረሃው ተኰላ 22.ዘጠና ደቂቃ በኢንተቤ 23.ጊለን-የክፍለ ዘመኑ ሰላይ 24.የኦዲሣ ማኅደር 26.ከሕይወት በኋላ ሕይወት 27.ስለላና ሰላዮች 28.ምርጥ ምርጥ ሰላዮች 30.አሉላ አባነጋ 31.የሰላዩ ካሜራ 32.“ሰላይ ነኝ“ 33.በዘመናችን ከታወቁ ሰዎች 35.ሾተላዩ ሰላይ 37.በረመዳን ውዜማ 38.የበረሃው ማዕበል 40.ሲ.አይ.ኤና ጥልፍልፍ ሲሆኑ 41.ዩፎስ-በሪራ ዲስኮች 42.መጭው ጊዜ 44.የአሮጊት አውታታ 45.እኔና እኔ 46.ኤርትራና ኤርትራውያን 47.ሞት የመጨረሻ ነውን? የውጭ ማያዣ ", በማሞ ውድነህ የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች
1542
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%80%E1%88%90%E1%8B%AD
ፀሐይ
ፀሓይ (ምልክት፦) በምድር ሥርዐተ-ፈለክ መኻል ያለች ኮከብ ናት። ምድር ሞላላ ቀለበት በሚመስል የዑደት ምሕዋር እየተጓዘች ፀሓይን ትዞራታለች። ሌሎች ሰማያዊ አካላትም፣ ፈለኮች፣ ፈለክ-አስተኔዎች፣ ጅራታም ከዋክብት እና ኅዋዊ ብናኞች በፀሓይ ዙሪያ ይዞራሉ። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገውን አንድ ዙር ጉዞ ለመጨረስ አንድ ዓመት ይፈጅባታል፤ ይህን ጉዞ ስታደርግም በገዛ ራሷ ዘንጎ ወይም ምሽዋር ዙሪያ እየሾረች ነው። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ወቅቶች በዓመታዊ ዑደት እንዲለዋወጡ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ሲኾን፣ በራሷ ዘንጎ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ደግሞ በዕለታዊ ዑደት መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ምክንያት ነው። ፀሓይ ለሥርዐተ-ፈለካችን በጣም ብሩህ የኾነ ብርሃን ትሰጣለች። ያለ ፀሓይ ብርሃን ሙቀትም ኾነ ሕይወት በምድር አይኖርም ነበር። ለምሳሌ አረንጓዴ ዕፅዋት ያለ ፀሓይ ብርሃን ሊኖሩ አይችሉም፤ ለህልውናቸው የሚያስፈልጓቸውን ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች ለማስተጻመር የሚችሉት በፀሓይ ብርሃን ብቻ ነውና። ከምድር ይልቅ ለፀሓይ ይበልጥ ቅርብ የኾኑ ፈለኮች ለከፍተኛ ጨረር እና ግለት የተጋለጡ በመኾናቸው በምድር ላይ ላለው ዐይነት ሕይወት ተስማሚ አይደሉም። ከምድር ጋር ሲነጻጸር ከፀሓይ በጣም ርቀው ያሉ ፈለኮችም ለሕይወት መኖር ምቹ ኹኔታዎች የሏቸውም፤ በቂ ብርሃን እና ሙቀት ካለማግኘታቸው የተነሣ። የፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። (በጣም ጐልተው ከሚታዩ ሜጋሊቶች ውስጥ ጥቂቱ በ ናባታ ፕላያ፣ ግብጽ፣ እና በ ስቶንሄንጅ፣ እንግሊዝ፣ ውስጥ ይገኛሉ።) ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። በምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል።
11578
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%88%E1%8C%8B%E1%8B%A8%E1%88%81%20%E1%8B%B0%E1%8C%8D%E1%8A%90%E1%89%B1
ወጋየሁ ደግነቱ
አርቲስት ሻለቃ ወጋየሁ ደግነቱ ከአባቱ ከአቶ ደግነቱ ጅማ ከእናቱ ከወ/ሮ አበራሽ ወዳጆ ጥር 12 ቀን 1940 ዓ/ም. በሀረርጌ ክ/ሀገር በወበራ አውራጃ በጎሮ ጉቱ ወረዳ ልዩ ስሙ መካኒሳ በተባለው ስፍራ ተወለደ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በሐረር ልዑል ራስ መኮንን አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትሏል። በነበረው ልዩ የሙዚቃ ፍቅር የተነሳ መጋቢት 1 ቀን 1955 ዓ.ም. በሐረርጌ ክ/ሀገር ፖሊስ ሙዚቃ ክፍል በታዳጊነት ዕድሜው ተቀጠረ። ከ1957 ዓ/ም ጀምሮ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅና ተፈቃሪ ድምፃዊ ለመሆን የበቃው ሻለቃ ወጋየሁ ደግነቱ በ1959 ዓ/ም ከድምፃዊነቱ በተጨማሪ የሐረር ፖሊስ ሙዚቃ ክፍል የተወዛዋዥ ቡድን አሰልጣኝ የዜማ እና የግጥም ደራሲ ሆኗል። ይኸው ለኪነ-ጥበብ ያለው ፍቅር እየጎለበተ እያበበና እየጎመራ በመሄዱ ወጋየሁ በቀድሞ ፖሊስ ሠራዊት ውስጥ በ1960ዎቹ የተውኔት ባለሞያና አዘጋጅ የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋች የሙዚቃ መሣሪያዎች ቴክኒሻን ጭምር በመሆን የዘርፈ ብዙ ባለሞያዎች ባለቤት መሆኑን ለባልደረቦቹ እና ለአለቆቹ ለማሳየት ችሏል። ከሙዚቃ ስራው በተጓዳኝ የአቋረጠውን ትምህርት በማታው የትምህርት ክፍል በመከታተል ለተጨማሪ እውቀት የነበረውን ትጋትም አሳይቷል። በ1964 ዓ/ም የሙሉ 10 አለቅነት ማዕረግ ያገኘው ወጋየሁ ቀጥሎም የመኮንንነትን ኮርስ በሰንዳፋ ፖሊስ ኮሌጅ በመውሰድ ሚያዚያ 14 ቀን 1968 ዓ/ም በምክትል መቶ አለቃነት ማዕረግ ተመርቋል። በፖሊስ ሠራዊት ባልደረባነቱ ወቅት በቀድሞ ኤርትራ ክ/ሀገርና በመላው ሀገሪቱ ተዘዋውሮ በሙያው ሀገሩን ያገለገለው ወጋየሁ ኤርትራ ውስጥ በነበረው በ5ኛ ሻለቃ ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ውስጥ የመቶ መሪ በመሆን ወቅቱ የጠየቀውን ሐገራዊ ግዳጅ ተወጥቷል። ሀገሩ እና ወገኖቹ ሁሉ ሊዘነጉት የማይቻላቸውን የጀግንነት ተግባርም በመወጣት በመኮንንነቱ የተዋጊ አዋጊነት ዘመን ፈጽሟል። ስለ እናት ኢትዮጵያ ክብር «የደስታሽ ሕይወት ተካፋይ ለችግርሽ ሆኜ ተወካይ መቆሜን አውቃለሁ ጠንቅቄ ታሪክሽን ለማኖር ጠብቄ…» ብሎ ያዜመው ስለ ወላጅ እናት ፍፁምነት እና መተኪያ አልባነት «የሰው የእንስሣት የአራዊት… እናት እኮነች መድኃኒት” በማለት ያንጎራጎረው እና “አርኬ የሁማ…» በተሰኘው ማሕበረሰባዊ ተወዳጅ የኦሮምኛ ዜማው የሚታወቀው ሻለቃ ወጋየሁ ደግነቱ ከጦር ግንባር ግዳጅ መልስ በመስከረም ወር 1969 ዓ.ም. የኤርትራ ክ/ሀገር ፖሊስ ሙዚቃ ክፍል አዛዥ ሆኖ አገልግሏል። በ1978 ዓ.ም. የሻለቅነት ማዕረግ እስካገኘበት ጊዜ ድረስ እና ከዚያም በኋላ በኪነ-ጥበብና በፖሊሳዊ ሙያው ከሀረርጌ ጫፍ እስከ አሰብና የቀድሞይቱ ኢትዮጵያ ደሴቶች ድረስ በመነቃነቅ ከእሱ ይጠበቅ የነበረውን የዜግነት ድርሻ ተወጥቷል። አርቲስት ሻለቃ ወጋየሁ ደግነቱ፤ በቀድሞ የኢትዮጵያ ፊናንስ ፖሊስ፣ የፖሊስ ሠራዊት የሙዚቃና የቴአትር እንደሁም በአዲስ አበባ ፖሊስ መምሪያ የ6ኛ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መከላከል ክፍል ኃላፊ ሆኖ ሰርቷል። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲም የህግ ፋኩልቲ በማታው የትምህርት ክፍል የህግ ሙያን በመከታተል በ1984 ዓ/ም ወርሀ ታህሣስ የህግ ዲፕሎማውን የተቀበለው አርቲስት ወጋየሁ ደግነቱ ጅማ በጥብቅናና በህግ አማካሪነት ሙያ ሕብረተሰቡን በቅንነት ሲያገለግል የቆየ ስሙ ጥሩ ኢትዮጵያዊ ነበረ። በሳቂታነቱ፣ የተጣሉትን በማስታረቅ ተግባሩ፣ በተግባቢነቱና በጨዋታ አዋቂነቱ፣ በሥራ እና በወገን ወዳድነቱ በኢትዮጵያዊን ዘንድ ልዩ አክብሮትን ያገኘ ሰው ነበረ። ሻለቃ ወጋየሁ ባለትዳር እና የአንድ ሴት ልጅ አባት እንደዚሁም የአንድ ወንድ ልጅ አያት ሲሆን፤ ከወራት በፊት በአጋጠመው የጤና መታወክ ምክንያት በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በ61 ዓመቱ አርብ ሐምሌ 10 ቀን 2001 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶናል ። የቀብሩ ስነ-ሥርዓትም ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2001 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ እና በርካታ አድናቂዎቹ በተገኙበት ከቀኑ በ10 ሰዓት ተፈጽሟል። ቤተሰቦቹ ታሞ ህክምና እየተከታተለ በነበረበት ሰዓትም ሆነ በሐዘናቸው ጊዜ ከጎናቸው ላልተለዩ የአርቲስቱ ልባዊ ወዳጆች እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ የከበረ ምስጋና ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ ዘፋኞች
2482
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%B5%E1%89%B1%20%E1%8A%83%E1%8B%AD%E1%88%88%20%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D
መንግስቱ ኃይለ ማርያም
ይህን ታሪክ የጸፍው ግለሰብ የመንግስት ሀይለማሪያ ቀንደኛ ደጋፊ እንደሆነ ከፁሁፉ አንጸር መርዳት አያዳግትም ትክክለኛውን ታሪክ ከምንጭ ጋር እንደሚያስተካክልው ተስፍ አደርጋለሁ። መንግሥቱ ኀይለማሪያም በግንቦት 27 በ1929 እ.ኤ.አ. በአዲስ አበባ ተወለዱ። አባታቸው ሃምሳዓለቃ ሃይለማሪአም ወልዴ፣ እናታቸው ብዙነሽ ተሰማ ነበሩ የአሁኑ መንግስት እና ብዙ የምእራባውያን መንግስታት እሱን እንደ ኮሚኒስት ተኮር አምባገነን አድርገው የሚቆጥሩት ሲሆን የቀድሞው አምባገነን ሮበርት ሙጋቤ የጥገኝነት ጥያቄውን ከተቀበሉ ወዲህ ወደዚምባብዌ ተሰዷል ፡፡ ምንም እንኳን መንግስት እንደዚህ ያሉ ክሶችን በተደጋጋሚ ቢክድም በ 2006 በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ፍ / ቤት በዘር ማጥፋት ወንጀል ተከሷል ፡፡ ሆኖም በሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል እንዲከሰስ በሄግ አልተከሰሰም ፡፡ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለ ማርያም' ከ1966 እስከ 1983 ዓ.ም. (1974 እስከ 1991 እ.ኤ.አ.) ለ17 ዓመታት የኢትዮጵያ መሪ ነበሩ። ወደ ስልጣን የወጡት በደርግ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን በመገልበጥ ሲሆን የአብዮቱ መሪ ሆነው ከቆዩ በኋላ በመለስ ዜናዊ በሚመራው በኢሓዴግ ሽምቅ ተዋጊ ቡድን እና በአሜሪካው የቀድሞው የሲአይኤ ዳሪክተር ሃርማንኮህ እርዳታ በ1983ዓ.ም ከስልጣን ተወገዱ። በአሁኑ የሀገሩ መንግስት እና በአብዛኞቹ የምዕራባውያን አገራት የኮሚኒስት አምባገነን ተደርጎ ፣ ይህ መፈንቅለመንግስት በሲአይኤ ስውር ዘዴ የተከናወነ ሲሆን የህወሓትና የሻእብያው መሪ ከሱዳን በቦይን 777 ከቀድሞው ከሲአይኤ ዳሪክተር ከ ሃርማንኮህ ጋር ታጅበው አዲስ አበባ ገብተዋል። ይህነው የኮሎኔል መንግሰቱ ኃይለማርያም የመንግሰቱ ግልበጣ ሳቦታጅ!! መንግስቱ ኃይለማርያም ያላሰበው ግልበጣ ተቀናብሮበት ያለአማራጭ በአየርላይ ቀረ እንጂ በራሱ ፍላጎት ሸሽቶ ዚምቡዋቤ ተሸሸገ የሚለው አባባል ከእውነት የራቀነው። ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም በቃላቸው የሚገኙ አገር ወዳድ ጀግና ሰው እንደነበሩ እናውቃለን። መንግሥቱ ኃይለማሪያም ወደ ርዕሰ ብሄርነት ሥልጣን ብቅ ሲሉ ገና የ፫፯ ዓመት ወጣት የነበሩ ሲሆኑ በሀረር የ3ኛ ክፍለ ጦር የመሳሪያ ግምጃ ቤት ውስጥ ይሰሩ ነበር። በወቅቱ በክፍለ ጦሩ አዛዥ የነበሩት ጀነራል ሓይሌ ባይከዳኝ የሚባሉ ኮ/ መንግስቱን በባህሪያቸው በመጠርጠራቸው ከአጠገባቸው ዞር ለማድረግ ወደ ኦጋዲን አዛውረዋቸው እንደ ነበር ይነገራል። በእዚያም ጥቂት ጊዜ በኋላ ለትምህርት ወደ አሚሪካ ሜሪላንድ ለወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት ተላኩ። ከትምህርት ሲመለሱም በ3ኛ ክፍለ ጦር የመሳሪያ ግምጃ ቤት ሃላፊ ሆነው ተሾሙ። ከዛም በደረጃ እድገት ካገኙ በሁዋላ የአፄ ኃይለስላሴን ጨቋኝ አገዛዝ ለመገርሰስ የደርግ ኩዴታን መሰረቱ በመኮንኖች ህብረት የተመሰረተው ደርግ በአብዛኛው ተደማጭነትና የፓለቲካ ብስለት በነበራቸው በቆራጥነታቸው ታዋቂ በሆኑት በመንግስቱ ኃይለማርያም ስልታዊ አደረጃጀት ተቀናብሮ የንጉሱን ወንበር ገለበጡት ይህ በሆነ ወቅት በነበረው አለመረጋጋት በከተማው የተኩስ ልውውጥ ተደረጎነበር። የመጀመርያውን ስልጣን በመያዝ የደርግ ሊቀመንበር ሆነው የተሾሙት ጀኔራል አማን አምዶም ነበሩ። በተለያየ አመታት በተለያየ ክህደትና አሻጥር የተገኙ አመራሮች ከስልጣን ሲወገዱ ቆይተው በአራ0ተኛው ዙር ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የኢትዮጵያ የመጀመርያው ፕሬዚዳንት ለመሆን በቅተዋል። ወደ ስልጣን በመጡ ማግስት ሶማሊያየዚያድባሬ መንግስት በሶቭየቶች ተደግፋ ሀገራችንን ድንገት ወረረች። በወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩትን ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተርን ፈጣን ወታደራዊ እርዳታ ጠይቀው እሳቸውም የንጉሱ የቅርብ ወዳጅ ስለነበሩ በስዊስ ባንክ ያለውን የኢትዮጵያ ሃብት ለመንግስቱ ኃይለማርያም ከሰለመስጠት በተደረገው ውይይት የአሜሪካ እጅ ስለነበረበት መንግስቱ ነጮችን በ73 ሰአት ውስጥ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ አድርጎ ስለነበር በዚህ ቂም ጥያቄውን ሳይቀበሉ ቀሩ። በእዚህም ምክንያት አማራጭ ያጣው ደርግና መንግሥቱ ሀገሪቱ በከፍተኛ ስጋት ላይ በመውደቋ የግድ ወደ ሞስኮ መሳሪያ ልመና ልኡካን ላኩ። በሌላ በኩል ሞስኮ ከሶማሊያ ጋር ጥቅምዋን በማወዳደር ለመንግስቱ መሳሪያ መስጠት ካስፈለገ በፊርማ ሶሻሊስት ካምፐ መግባቱን እንዲያረጋግጡ ስለ ጠየቀች ኮ/መንግሥቱ ይህን በማድረጋቸው በይፋ የሚመሩት አብዩት የሌኒኒስት ማርክሲስት መሆኑን በአዋጅ አሳወቁ። ኮ/መንግሥቱ የቼጉቬራና የሶቬቱን ማርክሲዝም አሜሪካ ለወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት በተላኩበት ዘመን ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ሃር ሳይመለሱ ወደ ሞስኮ በማምራት የራሻን ሶሻሊዝም በግላቸው ተምረው ነበር፣ወደ አገር ሲመለሱም ንጉሱ በዚህ ድርጊታቸው ለሁለት አመት በኦጋዴን በረሃ በቅጣት እንዲቆዩ ተደርጎነበር። የመንግስቱ ስለሶቪየት ሶሸሰሊዝም ፖለቲካ እውቀት የሚያውቁት የቅርብ መኮንኖች በደርግ ኩዴታው የነቃውንና ብስለት ያለውን ደፋሩን መንግስቱ ኃይለማረወያምን ነበር በአደራጅነት የመደቡት። ከስምምነቱም በሁዋላ በ፪ ወር ጊዜ ውስጥ የብዙ ሚሊዮን ዶላር ታንክና የጦር መሣሪያ እርዳታ ማግኘት ብቻ ሳይሆን በሞስኮ በኩል የኩባን የጦር አማካሪዎች በማግኘታቸው የወራሪውን የሶማሊያን ኃይል መመከት ችለዋል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አሜሪካ የጭንቅ ጊዜ ጥያቄ መላሽ ሆና ባለመገኘትዋና በንጉሱ ስም በስዊስ ባንክ የተቀመጠውን በትሪሊዮን የሚቆጠር ዶላርና ወርቅ የስዊስ ባንክ ለኢትዮጵያ መንግስት እንድትመልስ መንግስቱ ኃይለማረወያም ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ በማድረጓ የአሜሪካ ትብብር በመኖሩ ምክንያት መንግስቱ ኃይለማርያም በስልጣን እስከቆዩበት ዘመን ሁሉ በዋና ጠላትነት ተፈርጀዋል። አንዳንድ ሚሲዮናዊያንንም ከአገር አባረሩ። በንጉስ ኃይለስላሴ ፊርማ በስዊስባንክ የነበረው የኢትዮጵያ ሃብት እስካሁን አልተመለሰም። አብይ አህመድ ይህን የመጠየቅ ወኔ የለውም፣ምፅዋእት ከመለመን በቀር። በወቅቱ በአገር ውስጥ ግንባር ቀደም ተቃናቃኝና ተቃዋሚ ከነበረው ከኢህአፓ ጋር የከተማ ለከተማ ውጊያና መገዳደል ተጀመረ። ሁለቱም ወገኖች ቀን በቀን ግድያም ለብዙ ወጣትና አዋቂ እልቂት ምክንያት ሆኑ። መንግሥቱ ኃ/ማሪያም በወታደራዊ አመራር ውስጥ የተከስተው የስልጣን ዝቀጠትና ምግባረ ብልሹነት፤ የደህንነቱ ክፍል በሁለት ቢላዋ መብላት፣ ተደማምሮ ውድቀታቸውን እንዳፋጠነው የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ። የመንግስቱን አስተዳደር ለውድቀት ያበቃው የኮሎኔሉ አምባገነን አመራር ነው የሚሉት ተቀናቃኞቻቸውና በሁለት ቢለዋ እየበሉ አገርን ለመሸጥ ያስማሙ የነበሩ በወቅቱ (በመኢሶን) ውስጥ ተሰግስገው የነበሩ የኦነግ ስውር ባንዳ መኮንኖችና የ() እና የ () ሰላዮችና አገር በሆድና በስልጣን የሸጡ የመንግስቱ ተቀናቃኞች መረጃን አሾልኮ ለተቃዋሚ ኃይሎች አሳክፎ በመስጠት እንደሆነ ይታወቃል። በመንግስቱ ኃይለማርያምላይ የተቀነባበረ የ 16 ግዜ የመግደል ሙከራ ተደርጎባቸው አምልጠዋል። ጠላቶቻቸው ከውስጥና ከውጭ ብዙ ስለነበሩ ለ17 አመታት ቀንና ሌሊት ሲዋጉ አገርን በልማት በምርት ዘመቻ፣በትምህርትዘመቻ፣እንዲሁም ስራአጥነትንና ሴተኛ አዳሪነትን ለማስወገድ የኢንዱስትሪ ስራዎችን በመክፈትና በማስፋፋት መሬትን ለአራሹ በመሰከፋፈል፣ ለደሃው ህዝብ ርካሽ የቤትክራይን በመደንገግ፣ለአገራቸው ከፍተኛ አገልግሎት ያበረከቱ ታላቅ መሪናቸው። ይህን በጎ ተግባራቸውን ለመናገር የሚያንቃቸው የግል ጥቅማቸውን ከአገር ጥቅም ይልቅ አብልጠው የሚወዱ ተቀናቃኝ ሰዎች ብቻ ናቸው። መንግሥቱ (የቀድሞው) ርዕሰ ብሔር ማንኛውም መሪ ላይ ሊከሰት የሚችል ስህተት ነው የፈፀሙት...ስለ ሐገር ስለ ብሔራዊ ክብር እና ኩራት ግን እርሳቸው ! ከፊት ቢሠለፉ የሚገባቸውና የሚያምርባቸው ናቸው። የኮሎኔል መንግስቱን ህይወት ተቀጥፋ ለማየት የጓጉና የፎከሩ ሁሉ ቀድመዋቸው ሞተዋል!! የእድሜ በለፀጋው ጓድ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የሦስት ልጆች አባት ሲሆኑ 3ስቱም ልጆቻቸው ዶክተሮች ናቸው። ዛሬ የ 83 አመት አዛውንት ሆነው በሃራሬ በህይወት ይገኛሉ። ማህበራዊ አውታረ መረቦች መንግስቱ በፌስቡክ
48862
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%93%E1%8D%93%20%E1%8D%8D%E1%88%AB%E1%8A%95%E1%88%B2%E1%88%B5%E1%8A%AE%E1%88%B5
ፓፓ ፍራንሲስኮስ
ፓፓ ፍራንሲስኮስ ወይም ፖፕ ፍራንሲስ፣ ልደት ስም ሖርጌ ማሪዮ ቤርጎልዮ (1929 ዓም አርጀንቲና ተወለዱ) ከ2005 ዓም ጀምሮ የሮሜ ፓፓ ወይም የሮማን ካቶሊክ መሪ ናቸው።ከ 2013 (አውሮፓውያን) ጀምሮ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ እና የቫቲካን ከተማ ግዛት ሉዓላዊ ገዥ ናቸው። ፍራንሲስ የኢየሱስ ማኅበር አባል ለመሆን የመጀመሪያው ጳጳስ ነው፣ የመጀመሪያው ከአሜሪካ፣ የመጀመሪያው ከደቡብ ንፍቀ ክበብ፣ በ 8ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከገዛው ሶርያዊ ጎርጎርዮስ ሳልሳዊ በኋላ ከአውሮፓ ውጪ የመጀመሪያው ጳጳስ ነው። በቦነስ አይረስ፣ አርጀንቲና የተወለደው ቤርጎሊዮ በወጣትነት ጊዜ የኬሚስትነት ሙያ ከማሰልጠን በፊት በምግብ ሳይንስ ላብራቶሪ ውስጥ በቴክኒሻንነት ከመስራቱ በፊት በባውንተርነት እና በፅዳት ሰራተኛነት ለተወሰነ ጊዜ ሰርቷል። ከከባድ ሕመም ካገገመ በኋላ በ1958 የኢየሱስ (የጀሱሳውያን) ማኅበር አባል ለመሆን ተነሳሳ። በ1969 የካቶሊክ ቄስ ሆኖ ተሹሟል፤ ከ1973 እስከ 1979 በአርጀንቲና ውስጥ የየየሱሳውያን ጠቅላይ ግዛት የበላይ ሆኖ ተሾመ። እ.ኤ.አ. በ1998 የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ እና በ2001 በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ካርዲናል ፈጠሩ። በታህሳስ 2001 በአርጀንቲና በተፈጠረው ሁከት የአርጀንቲና ቤተ ክርስቲያንን መርተዋል። የኔስቶር ኪርችነር እና የክርስቲና ፈርናንዴዝ ደ ኪርችነር አስተዳደሮች እንደ ፖለቲካ ተቀናቃኝ አድርገው ይመለከቱት ነበር። እ.ኤ.አ. ለአሲሲው ቅዱስ ፍራንሲስ ክብር ሲል ፍራንሲስን የጵጵስና ስም አድርጎ መረጠ። በአደባባይ ህይወቱ በሙሉ፣ ፍራንሲስ በትህትናው፣ በእግዚአብሔር ምህረት ላይ አፅንዖት በመስጠት፣ በአለም አቀፍ ደረጃ እንደ ጳጳስ ታይነት፣ ለድሆች ተቆርቋሪነት እና በሀይማኖቶች መካከል ውይይት ለማድረግ ባለው ቁርጠኝነት ይታወቃሉ። ለጵጵስናው ከቀደምቶቹ ያነሰ መደበኛ አቀራረብ እንደነበረው ይነገርለታል፡ ለምሳሌ ቀደምት ሊቃነ ጳጳሳት ይገለገሉበት በነበረው የሐዋርያዊ ቤተ መንግሥት የጳጳሳት አፓርታማዎች ውስጥ ከመኖር ይልቅ በዶሙስ ሳንክታ ማርቴ የእንግዳ ማረፊያ ውስጥ መኖርን መርጧል። ፍራንሲስ ውርጃን፣ ቀሳውስትን አለማግባትን እና የሴቶችን መሾም በተመለከተ የቤተክርስቲያኗን ትውፊታዊ አመለካከቶች ይጠብቃሉ፣ ነገር ግን በዲቁናነት ዕድል ላይ ውይይት ጀምሯል እና ሴቶችን በሮማን ኪዩሪያ የዲያስትሪክት ሙሉ አባላት አድርጓል። ቤተክርስቲያኑ ለኤልጂቢቲ ማህበረሰብ አባላት የበለጠ ክፍት እና እንግዳ ተቀባይ መሆን እንዳለባት ይጠብቃል። ፍራንሲስ ያልተገራ የካፒታሊዝም እና የነፃ ገበያ ኢኮኖሚክስ፣ የፍጆታ ተጠቃሚነት እና ከመጠን በላይ እድገትን የሚተቹ እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃ እንዲወስዱ ተሟጋቾች የሉዳቶ ሲ' አዋጅ የጵጵስና ስልጣናቸው ትኩረት ነው። በአለምአቀፍ ዲፕሎማሲ, በዩናይትድ ስቴትስ እና በኩባ መካከል ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን ለማደስ እና በአውሮፓ እና በመካከለኛው አሜሪካ የስደተኞች ቀውሶች ወቅት የስደተኞችን ጉዳይ ደግፏል. ከ 2018 ጀምሮ እሱ የሕዝባዊነት ተቃዋሚ ነው።ኢኩሜኒዝምን ማስፋፋቱን ጨምሮ፣ እንዲሁም በሲቪል የተፋቱ እና እንደገና የተጋቡ ካቶሊኮች ከአሞሪስ ላቲሺያ እትም ጋር እንዲተባበሩ ማድረጉን ጨምሮ በብዙ ጥያቄዎች ላይ ከሥነ-መለኮት ወግ አጥባቂዎች ትችት ገጥሞታል። የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ጆርጅ ማሪዮ ቤርጎሊዮ ታኅሣሥ 17 ቀን 1936 (አውሮፓዊ) ወይም በኢትዮጵያ 1929 በቦነስ አይረስ ሰፈር ፍሎሬስ ተወለደ። እሱ የማሪዮ ሆሴ ቤርጎሊዮ እና ሬጂና ማሪያ ሲቮሪ የአምስት ልጆች ታላቅ ነበር። ማሪዮ ቤርጎሊዮ በጣሊያን ፒዬድሞንት ግዛት በፖርታኮማሮ (የአስቲ ግዛት) የተወለደ ጣሊያናዊ ስደተኛ አካውንታንት ነበር። ሬጂና ሲቮሪ በቦነስ አይረስ የተወለደች የቤት እመቤት ነበረች። የማሪዮ ሆሴ ቤተሰቦች ከቤኒቶ ሙሶሎኒ ፋሺስታዊ አገዛዝ ለማምለጥ በ1929 ጣሊያንን ለቀው ወጡ። ማሪያ ኤሌና ቤርጎሊዮ (በ1948 ዓ.ም.) እንደተናገረችው፣ የጳጳሱ ብቸኛ ሕያው ወንድም እህት፣ እነሱ በኢኮኖሚያዊ ምክንያቶች አልተሰደዱም። ሌሎች ወንድሞቹ አልቤርቶ ሆራሲዮ ፣ ኦስካር አድሪያን (1938 - ሟች) እና ማርታ ሬጂና ነበሩ። ሁለት የልጅ ልጅ የሆኑት አንቶኒዮ እና ጆሴፍ በትራፊክ ግጭት ሞቱ። የእህቱ ልጅ ክሪስቲና ቤርጎሊዮ በስፔን ማድሪድ ውስጥ ሰአሊ ነው። በስድስተኛ ክፍል ቤርጎሊዮ በቦነስ አይረስ ግዛት ራሞስ ሜጂያ በሚገኘው የዶን ቦስኮ የሽያጭ ሰዎች ትምህርት ቤት ዊልፍሪድ ባሮን ደ ሎስ ሳንቶስ አንጄልስ ተምሯል። በቀድሞው የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ስም የተሰየመውን ን በቴክኒካል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሎ በኬሚካል ቴክኒሻን ዲፕሎማ ተመርቋል (አንዳንድ ሚዲያዎች በስህተት እንደዘገቡት በኬሚስትሪ የማስተርስ ዲግሪ አይደለም)። በዚ ብቃቱ፣ በሂኪቲየር-ባችማን ላብራቶሪ የምግብ ክፍል ውስጥ በአስቴር ባሌስቲሪኖ ስር ሰርቶ ለብዙ አመታት አሳልፏል። ቤርጎሊዮ በኬሚካል ቴክኒሻንነት ከመስራቱ በፊት እንደ ባር ቆጣቢ እና እንደ ጽዳት ፎቆችም ሰርቷል። የ21 ዓመት ልጅ እያለ ለሕይወት አስጊ በሆነ የሳንባ ምች እና በሦስት የሳይሲስ በሽታ ተሠቃይቷል። ብዙም ሳይቆይ የሳንባ ክፍል ተቆርጧል። ቤርጎሊዮ የሳን ሎሬንዞ ደ አልማግሮ የእግር ኳስ ክለብ የዕድሜ ልክ ደጋፊ ነው። ቤርጎሊዮ የቲታ ሜሬሎ፣ ኒዮሪያሊዝም እና ታንጎ ዳንስ ፊልሞች አድናቂ ነው፣ የአርጀንቲና እና የኡራጓይ ባህላዊ ሙዚቃ ሚሎንጋ በመባል ይታወቃል። ጀሱት ቤርጎሊዮ የክህነት ጥሪውን ያገኘው የፀደይ ቀንን ለማክበር በጉዞ ላይ እያለ ነው። ኑዛዜ ለመሄድ በቤተ ክርስቲያን በኩል አለፈ፣ እናም በካህኑ ተመስጦ ነበር። ቤርጎሊዮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ሴሚናሪ ኢንማኩላዳ ኮንሴፕሲዮን ሴሚናሪ በቪላ ዴቮቶ ቦነስ አይረስ ከተማረ በኋላ ከሦስት ዓመታት በኋላ ወደ ኢየሱስ ማኅበር ጀማሪ መጋቢት 11 ቀን 1958 ገባ። ያገኛትን ልጅ አፍቅሮ ሃይማኖታዊ ሥራውን ለመቀጠል በአጭሩ ተጠራጠረ። እንደ ጀማሪ ጀማሪ በሳንቲያጎ፣ ቺሊ የሰው ልጅን አጥንቷል። በኢየሱስ ማኅበር ውስጥ ከጀመረ በኋላ፣ ቤርጎሊዮ መጋቢት 12 ቀን 1960 ዓ.ም የሃይማኖታዊ ሙያውን የድህነት፣ የንጽሕና እና የሥርዓት አባል ታዛዥነትን በፈጸመ ጊዜ በይፋ ኢየሱሳዊ ሆነ። እ.ኤ.አ. በ1960 ቤርጎሊዮ በቦነስ አይረስ ግዛት ሳን ሚጌል ከሚገኘው ከኮሌጂዮ ማክስሞ ደ ሳን ሆሴ የፍልስፍና ፈቃድ አገኘ። ከ1964 እስከ 1965 በሳንታ ፌ በሚገኘው ኮሌጂዮ ዴ ላ ኢንማኩላዳ ኮንሴፕሲዮን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስነ-ጽሁፍ እና ስነ ልቦና አስተምሯል።በ1966 በቦነስ አይረስ በሚገኘው ኮሌጆ ዴል ሳልቫዶር ተመሳሳይ ኮርሶችን አስተምሯል። ፕሬስባይቴሬት እ.ኤ.አ. በ1967 ቤርጎሊዮ የነገረ መለኮት ትምህርቱን በፋኩልታዴስ ደ ፊሎሶፊያ ጀመረ እና በታህሳስ 13 ቀን 1969 በሊቀ ጳጳስ ራሞን ሆሴ ካስቴላኖ የክህነት ማዕረግ ተሹሟል። በዚያ ለነበረው ክፍለ ሀገር የጀማሪዎች አለቃ ሆኖ አገልግሏል እና የነገረ መለኮት መምህር ሆነ። ቤርጎሊዮ የመጨረሻውን የመንፈሳዊ የስልጠና ደረጃውን በአልካላ ዴ ሄናሬስ፣ ስፔን አጠናቀቀ እና የመጨረሻውን የኢየሱስዊት ቃል ኪዳን ገባ። እ.ኤ.አ. የዮም ኪፑር ጦርነት። የስልጣን ዘመናቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በ1980 የተማሩበት የሳን ሚጌል የፍልስፍና እና ስነ መለኮት ፋኩልቲ ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ። ይህንን አዲስ ሹመት ከመውሰዱ በፊት፣ እ.ኤ.አ. በ1980 የመጀመሪያዎቹን ሶስት ወራት በአየርላንድ እንግሊዘኛ ለመማር አሳልፏል፣ በዱብሊን ሚልታውን የስነመለኮት እና የፍልስፍና ተቋም ውስጥ በጄስዊት ማእከል ቆየ። እ.ኤ.አ. እስከ 1986 ድረስ በሳን ሚጌል ለስድስት ዓመታት አገልግሏል ፣ በጄሱሳዊው ጄኔራል ፒተር ሃንስ ኮልቨንባች ውሳኔ ፣ በኢየሱስ ማኅበር ውስጥ ካለው ዓለም አቀፋዊ የማህበራዊ ፍትህን ከማጉላት አዝማሚያ ጋር በሚስማማ ሰው ተተካ ። በታዋቂው ሃይማኖታዊ እና ቀጥተኛ የአርብቶ አደር ሥራ ላይ. በጀርመን ፍራንክፈርት በሚገኘው የሳንክት ጆርጅገን የፍልስፍና እና የነገረ መለኮት ምረቃ ትምህርት ቤት የመመረቂያ ርእሶችን በማጤን ብዙ ወራት አሳልፏል። የጀርመናዊውን/ ጣሊያናዊውን የሃይማኖት ምሁር ሮማኖ ጋርዲኒ ሥራ በመቃኘት ላይ ተሰማርቷል፣ በተለይም በ1925 በዴር ጌንሣትዝ ሥራው ላይ ያሳተመውን 'ንፅፅር' ጥናት። ነገር ግን፣ በኮርዶባ ለሚገኘው የጄሱስ ማህበረሰብ መናዘዝ እና መንፈሳዊ ዳይሬክተር ሆኖ ለማገልገል ያለጊዜው ወደ አርጀንቲና ሊመለስ ነበረበት። በጀርመን በአውስበርግ የሚገኘውን ሜሪ ፣ ዩኒት ኦቭ ኖትስ የተሰኘውን ሥዕል አይቷል እና የሥዕሉን ቅጂ ወደ አርጀንቲና አመጣ እና አስፈላጊ የማሪያን አምልኮ ሆነ። በሣሌዥያ ትምህርት ቤት ተማሪ በነበረበት ጊዜ፣ ቤርጎሊዮ በዩክሬን ግሪክ ካቶሊክ ቄስ ስቴፋን ክዝሚል ተማክሮ ነበር። ቤርጎሊዮ ብዙ ጊዜ ከክፍል ጓደኞቹ ከሰአታት በፊት ተነስቶ ለ ቅዳሴን ለማገልገል። በ 1992 ቤርጎሊዮ ከየየሱሳውያን መሪዎች እና ሊቃውንት ጋር በተፈጠረው አለመግባባት ፣የቤርጎሊዮን “አለመስማማት” ስሜት ፣ የካቶሊክ ኦርቶዶክሱን እና የነፃነት ሥነ-መለኮትን በመቃወም እና በሠራው ሥራ በ 1992 በጄሱሳውያን ባለሥልጣናት እንዳይኖር ተጠየቀ ። የቦነስ አይረስ ረዳት ጳጳስ። እንደ ኤጲስ ቆጶስነቱ ለጄሱሳዊ አለቃው ተገዥ አልነበረም። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ, እሱ ኢየሱስ ቤቶችን አልጎበኘም እና ጳጳስ ሆኖ እስከተመረጠበት ጊዜ ድረስ "ከኢየሱሳውያን የራቀ" ነበር. ቅድመ-ጳጳስ ኤጲስ ቆጶስ ቤርጎሊዮ በ1992 የቦነስ አይረስ ረዳት ጳጳስ ተብሎ ተሰይሟል እና በጁን 27 ቀን 1992 የአውካ ጳጳስ ፣ የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አንቶኒዮ ኳራሲኖ ፣ ዋና ገዳም ሆነው ቀደሱ። እንደ ኤጲስ ቆጶስነት መሪ ቃል መረጠ። በማቴዎስ 9፡9-13 ላይ “በምሕረት አይቶ ስለ መረጠው” ከሚለው የቅዱስ በዴ ስብከት የተወሰደ ነው። ሰኔ 3 ቀን 1997 ቤርጎሊዮ የመተካት መብት ያለው የቦነስ አይረስ አስተባባሪ ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ተሾመ። እ.ኤ.አ. በዚ ተግባር፣ በርጎሊዮ አዲስ አድባራትን ፈጠረ እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጽ/ቤቶችን በአዲስ መልክ አዋቅሮ፣ ለሕይወት ደጋፊ የሆኑ ተግባራትን መርቷል፣ እና የፍቺ ኮሚሽን ፈጠረ። እንደ ሊቀ ጳጳስ የቤርጎሊዮ ዋና ተነሳሽነቶች አንዱ የቤተክርስቲያንን መገኘት በቦነስ አይረስ ሰፈር ውስጥ ማሳደግ ነው። በእሱ መሪነት, በድሃ መንደሮች ውስጥ እንዲሰሩ የተመደቡት ካህናት ቁጥር በእጥፍ ጨምሯል. ይህ ሥራ "የድሆች ጳጳስ" ተብሎ እንዲጠራ አድርጎታል. ቤርጎሊዮ የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ወቅት የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን አክሲዮኖች በተለያዩ ባንኮች በመሸጥ ሒሳቡን ወደ መደበኛው ዓለም አቀፍ ባንኮች ተቀይሯል። በባንክ የነበረው አክሲዮን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ወደ ከፍተኛ ወጪ እንዲሸጋገር አድርጓታል፣ በዚህም ምክንያት ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለኪሳራ እየተቃረበ ነበር። የባንኩ መደበኛ ደንበኛ እንደመሆኖ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በከፍተኛ የፊስካል ዲሲፕሊን ውስጥ እንድትገባ ተገድዳለች። እ.ኤ.አ. ህዳር 6 1998 የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ ሆነው ሳለ፣ በአርጀንቲና ላሉ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ለሌላቸው የምስራቅ ካቶሊኮች ተራ ተባሉ። ሜጀር ሊቀ ጳጳስ በርጎሊዮ የሼቭቹክ ዩክሬንኛ የግሪክ ካቶሊካዊ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ፣ ሥርዓት እና መንፈሳዊነት እንደሚረዳና ሁልጊዜም የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ጊዜ ለምስራቅ ካቶሊኮች እንደ ተራ ነገር “የአርጀንቲና ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅ ነበር” ብለዋል። በ2000 ቤርጎሊዮ ብቸኛው የቤተ ክርስቲያን ባለሥልጣን ነበር በ1972 የአርጀንቲናውን አብዮት ወታደራዊ አምባገነን መንግሥት በመቃወም በካህንነት ከታገደው ከጄሮኒሞ ፖዴስታ ከቀድሞው ጳጳስ ጋር ያስታረቀ። በዚያው ዓመት ቤርጎሊዮ የአርጀንቲና ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በ1970ዎቹ በቆሸሸው ጦርነት ወቅት “በአምባገነኑ ዘመን ለተፈፀሙት ኃጢአት የሕዝብን የንስሐ ልብስ መልበስ አለባት” ብሏል። ቤርጎሊዮ እንደ እስር ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ የጡረተኞች መኖሪያ ቤቶች ወይም ሰፈር ባሉ ቦታዎች የእግር መታጠብን የቅዱስ ሀሙስ ስነ ስርዓት ማክበርን ልማዱ አድርጎታል። እ.ኤ.አ. በ2007፣ በነዲክቶስ 16ኛ ከሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ በፊት የነበሩትን የቅዳሴ ቅጾች ለመጠቀም አዲስ ሕግ ካወጡ ከሁለት ቀናት በኋላ፣ ብፁዕ ካርዲናል ቤርጎሊዮ በዚህ ያልተለመደ የሮማውያን ሥርዓት ለሳምንታዊ ቅዳሴ የተወሰነ ቦታ አቋቋሙ። በየሳምንቱ ይከበር ነበር። እ.ኤ.አ. ህዳር 8 ቀን 2005 ቤርጎሊዮ የአርጀንቲና ኤጲስ ቆጶስ ኮንፈረንስ ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ ለሦስት ዓመታት ። በኅዳር 11 ቀን 2008 ለሌላ የሶስት ዓመት የሥራ ዘመን ተመረጠ። የኮሚሽኑ ቋሚ የአስተዳደር አካል አባል ሆኖ ቆይቷል። ፣ የአርጀንቲና ጳጳሳዊ ካቶሊካዊ ዩኒቨርሲቲ የኮሚቴው ፕሬዝዳንት እና የቅዱስ ቤተመቅደሶች እንክብካቤ የቅዳሴ ኮሚቴ አባል። በርጎሊዮ የአርጀንቲና ካቶሊካዊ ጳጳሳት ጉባኤ መሪ በነበረበት ወቅት በቆሻሻ ጦርነት ወቅት ቤተ ክርስቲያናቸው ሰዎችን ከጁንታ ለመከላከል ባለመቻሏ የጋራ ይቅርታ ጠይቀዋል። በታህሳስ ወር 2011 75 ዓመት ሲሞላቸው ቤርጎሊዮ የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳስ ሆነው መልቀቂያቸውን ለጳጳስ በነዲክቶስ 16ኛ በቀኖና ሕግ አስረከቡ።ነገር ግን ምንም አስተባባሪ ሊቀ ጳጳስ ስላልነበራቸው በቫቲካን የሚሾመውን ሰው በመጠባበቅ በቢሮው ቆዩ እ.ኤ.አ. በጥቅምት 14 ቀን በዚያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመደበኛነት ተጭኗል። ለሥነ ሥርዓቱ ወደ ሮም ሲሄድ እሱና እህቱ ማሪያ ኤሌና አባታቸው የተወለደበትን ሰሜናዊ ኢጣሊያ መንደር ጎበኙ። እንደ ካርዲናል፣ ቤርጎሊዮ በሮማን ኩሪያ ውስጥ ለአምስት የአስተዳደር ቦታዎች ተሾመ። እሱ የመለኮታዊ አምልኮ እና የቅዱስ ቁርባን ተግሣጽ ጉባኤ፣ የካህናት ጉባኤ፣ የተቀደሰ ሕይወት ተቋማት ጉባኤ እና ሐዋርያዊ ሕይወት ማኅበራት ጉባኤ፣ የቤተሰብ ጳጳሳዊ ምክር ቤት እና የላቲን አሜሪካ ኮሚሽን አባል ነበሩ። በዚያው ዓመት ብፁዕ ካርዲናል ኤድዋርድ ኤጋን በሴፕቴምበር 11 ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ ወደ ኒውዮርክ ሲመለሱ፣ ቤርጎሊዮ በጳጳሳት ሲኖዶስ ውስጥ በሪተርተር (ዘጋቢ ፀሐፊ) ተክተው እንደ ካቶሊካዊ ሄራልድ ገለጻ፣ “እንደ ሰው ክፍት ሆኖ ጥሩ ስሜት ፈጠረ። ወደ መግባባት እና ውይይት" ብፁዕ ካርዲናል ቤርጎሊዮ በግላዊ ትሕትና፣ በአስተምህሮ ወግ አጥባቂነት፣ እና ለማህበራዊ ፍትህ ባለው ቁርጠኝነት ይታወቃሉ። ቀላል የአኗኗር ዘይቤ በትሕትና እንዲታወቅ አስተዋጽኦ አድርጓል። እሱ በኦሊቮስ ከተማ ውስጥ ባለው የሚያምር ጳጳስ መኖሪያ ውስጥ ሳይሆን በትንሽ አፓርታማ ውስጥ ይኖር ነበር። የህዝብ ማመላለሻ ወስዶ የራሱን ምግብ ያበስል።በሮም የነበረውን ጊዜ ለ"መብረቅ ጉብኝት" ወስኗል። ለሊሴው ቅድስት ቴሬሴ ያደሩ እንደነበር ይታወቃል፣ እና በጻፋቸው ደብዳቤዎች ላይ የእርሷን ትንሽ ምስል "ታላቅ ሚስዮናዊት ቅድስት" በማለት ጠርቷታል። ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጆን ፖል ዳግማዊ በኤፕሪል 2 2005 ከሞቱ በኋላ ቤርጎሊዮ በቀብራቸው ላይ ተገኝተው የጵጵስና ሹመትን ለመተካት እንደ አንዱ ተደርገው ይቆጠሩ ነበር። በ2005 ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቤኔዲክት 16ኛን በመረጠው የጳጳስ ጉባኤ እንደ ካርዲናል መራጭ ተሳትፈዋል። በብሔራዊ የካቶሊክ ዘጋቢ፣ ጆን ኤል አለን ጁኒየር በ2005 የጉባኤው ግንባር ቀደም ተዋናይ እንደነበር ዘግቧል። በሴፕቴምበር 2005 ሊምስ የተሰኘው የኢጣሊያ መጽሔት ቤርጎሊዮ በዚያ ጉባኤ ብፁዕ ካርዲናል ራትዚንገር 2ኛ እና ዋና ተፎካካሪ እንደነበር ገልጿል። እና በሶስተኛው ድምጽ 40 ድምጽ አግኝቷል, ነገር ግን በአራተኛው እና ወሳኝ ድምጽ ወደ 26 ወድቋል. የይገባኛል ጥያቄዎቹ የተመሠረቱት በጉባኤው ላይ ተገኝተው ያልታወቁ የካርዲናሎች ንብረት ናቸው በሚባል ማስታወሻ ደብተር ላይ ነው። እንደ ጣሊያናዊው ጋዜጠኛ አንድሪያ ቶርኒዬሊ፣ ይህ የድምጽ ቁጥር ለላቲን አሜሪካ ፓፓቢል ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ አልነበረውም። ላ ስታምፓ እንደዘገበው በምርጫው ወቅት ቤርጎሊዮ ከራትዚንገር ጋር በቅርበት ይከራከር ነበር፣ ካርዲናሎቹ እንዳይመርጡለት በስሜት ተማፅኖ እስኪያቀርብ ድረስ።እንደ ቶርኒዬሊ ገለጻ ቤርጎሊዮ ይህን ጥያቄ ያቀረበው ስብሰባው በምርጫው ላይ ብዙ እንዳይዘገይ ለመከላከል ነው። ጳጳስ ። እንደ ካርዲናል፣ ቤርጎሊዮ የታማኝ ማኅበራት በመባል የሚታወቀው የካቶሊክ ወንጌላዊ እንቅስቃሴ ከሆነው ከቁርባን እና ነፃ አውጪ ጋር የተያያዘ ነበር። በጣሊያን የበጋ ወራት መጨረሻ ላይ በተካሄደው የሪሚኒ ስብሰባ ተብሎ በሚጠራው አመታዊ ስብሰባ ላይ አንዳንድ ጊዜ ብቅ ብሏል። እ.ኤ.አ. በ2005፣ ካርዲናል ቤርጎሊዮ በሳን ፓትሪሲዮ ቤተክርስትያን እልቂት ለተገደሉ ስድስት የፓሎቲን ማህበረሰብ አባላት የድብደባ - ሶስተኛው የቅድስና ደረጃ ጥያቄን ፈቀዱ። በተመሳሳይ ጊዜ ቤርጎሊዮ በግድያዎቹ ላይ ምርመራ እንዲደረግ አዘዘ ይህም በብሔራዊ መልሶ ማደራጀት ሂደት ፣ አርጀንቲና ላይ ይገዛ የነበረው ወታደራዊ ጁንታ በሰፊው ተከሷል ።
49985
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%88%A9%E1%8D%8B%E1%8A%A4%E1%88%8D
ቅዱስ ሩፋኤል
ቅዱስ ሩፋኤል (በዕብራይስጥ: ) ሲነበብ ሩፋኤል ፣ ከ፯ቱ ሊቀመላእክት መዐረጉ ሦሥተኛ ነው ። ሩፋኤል መላእከ ኃይል በግዕዝ : ፈታሔ መኀፀን ወሰፋድል ። መወለድ መንፈሳዊ ። ወሐኪም ሰማያዊ ይባላል ። የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ ስለተሾመ ከጌታ አዋላጅ ብትኖርም ባትኖርም ሩፋኤል አይታጣም ፣ በምጥ ጊዜ ሴቶች ሁሉ በባላገር ያሉ መልኩን ያነግታሉ ማየ ጸሎቱንም ይጠጣሉ ቶሎም በፍጥነት ይወልዳሉ ። ድርሳነ ሩፋኤል ክፍል ፩ ፩ ፤ በአብ ስም አምነን አብ ወላዲ ብለን በወልድ ስም አምነን ወልድን ተወላዲ ብለን በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን መንፈስ ቅዱስን ሠራፂ ብለን ምንም ለአጠይቆ አካላት ሦስት ብለን በባሕርይ በሕልውና በመለኮት አንድ አምላክ ብለን አምነን አስቀድሞ በኅዳር ፲፪ ቀን እንደተናገርነው ክቡራን የሚሆኑ ከሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሦስተኛ የሚሆን የቅዱስ ሩፋኤል በዓለ ንግሥ በጳጉሜ ሦስት ቀን የሚከበርና የሚታሰብ መሆኑን እንናገራለን ። ፪ ፤ ይህም ዕለት በሊቀ ጳጳሱ በአባ ቴዎፍሎስ ዘመን እስክንድርያ በምትባል አገር ዳርቻ ባለች ደሴት በውስጧ ብዙ ተአምራት የተፈፀመባት በቅዱስ ሩፋኤል ስም የታነፀች ቤተ ክርስቲያን የተባረከችበትና የተቀደሰችበት ዕለት ነው ። ፫ ፤ ይህም የሆነው አንዲት በጣም ሀብታም የሆነች ሮማዊት የሮም ሀገር ሴት ንዑድ ክቡር የሚሆን የቅዱስ ሩፋኤልን ሥዕልና ልጆችዋን እንዲሁም ከባልዋ በውርስ ያገኘችውን ብዙ ገንዘብ ይዛ ወደ ሊቀ ጳጳሱ ወደ ቴዎፍሎስ ዘንድ በመጣችበት ጊዜ ነበር ። ፬ ፤ ከመጣችም በኋላ በሊቀ ጳጳሱ ቤት ፊት ለፊት ያለውን ኮረብታ አስቆፈረችና ከመሬት ውስጥ ወርቅ የተከማቸበት ሣጥን ተገኘ ። ፭ ፤ ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሱ አባ ቴዎፍሎስ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን አሣነፀ ከነዚህም ውስጥ እስክንድርያ በምትባል አገር ዳርቻ ባለች ደሴት ላይ ክቡር በሚሆን በቅዱስ ሩፋኤል ስም የተሠራች ቤተክርስቲያን ትገኝበት ነበር ሥራዋንም ሠርቶ በፈፀመ ጊዜ በዚችው ዕለት በታላቅ ክብር አክብሮ ባረካት ቀደሳትም ። ፮ ፤ ምእመናኑ ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየጸለዩ ሳሉ እንሆ ቤተ ክርስቲያኒቱ ተንቀጠቀጠች ተናወጠች ታወከች። በመረመሩ ጊዜም ከባሕር አንበሪዎች በአንዱ ታላቃ ዓሣ አንበሪ ላይ ተሰርታ አገኙዋት ከቦታው ሳይንቀሳቀስ ኑሮ ነበር ። ፯ ፤ በላዩ የሰው ሁሉ እግር በበዛና በከበደው ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አወከው። ምእምናኑና ሊቀ ጳጳሳቱ አንድ ሆነው ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ጮሁ ። ወደ ከበረ መልአክ ወደ ሩፋኤልም ለመኑ ። ፰ ፤ ያን ጊዜ ልዑል እግዚአብሔር የከበረ መልአክ ሩፋኤልን ላከው ሰዎችንም ይቅር አላቸው ። በእግዚአብሔር ትእዛዝ ጸንተህ ቁም ከቦታህም አትንቀሳቀስ ብሎ ዓሣውን በጦር ወጋ ። ያን ጊዜም ዓሣ አንበሪ በቦታው ጸንቶ ቆመ አልተቀንቀሳቀሰም ። በዚችም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብዙ ድንቅ ተአምራት ተደረገ ። ለታመሙትም ታላቅ ድኅነት ሆነ ። ይህችም ቤተ ክርስቲያን እስላሞች እስከ ነገሡ ደረስ እንደዚህ ኖረች ። ፱ ፤ እስላሞች በነገሡ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈረሰች ዓሣ አንበሪውም ተንቀሳቀሰ ዳግመኛም ባሕሩ ተናወጸ በዚያ ቦታ ላይ የነበሩትን ብዙ ሰዎችም አሰጠማቸው ። ፲ ፤ የከበረ የመላእክት አለቃ የሩፋኤል ይቅርታ ልመናውና በረከቱ ከኛ ጋር ይኑር ። ለዘለዓለሙ አሜን ። ፲፩ ፤ የሰውን ልብ ደስ የሚያሰኛት ልዩ ስጦታ ላለው ለሩፋኤል ሰላም እላለሁ ደዌ ኃጢያትን ይፈውሳል ቁስለ ነፍስንም ያክማልና ። ስለዚህም እውነትን የሚከተሉ ይቅርታን ያገኛሉ ። በተንኮል ጎዳና የሚግዋዙ ግን በነፍሳቸውም በሥጋቸውም ጥፋትን ያስከትላሉ ሲል ለጦቢት አስረዳው አስገነዘበው ። ድርሳነ ሩፋኤል ክፍል ፪ ፲፪ ፤ አባ ዮሐንስ የተናገረው የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል የክብሩ ዜና ዳግምኛም የቁስጥንጥንያው አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስ ይህን የገናናነቱን ነገር ተናገረ፣ ደገኛውን ንጉሥ አኖሬዎስን አንዲህ አለው ንጉሥ ሆይ ዕወቅ እኛ ወደ አንተ ልንመጣ በመረከብ ተሳፍረን ነበርና ስንሔድ ሳለን በከበረች በቀዳሚት ቀን በደሴት ላይ የተሰራች አንዲት ቤተ ክርስቲያን አየን። ከወደቡ ደረስን በዕለተ እሑድም ሥጋውን ደሙን እንቀበል ዘንድ ከዚያ አደርን ። በዚች ቤተ ክርስቲያን አጠገብም ትንሽ ገዳም አገኘን ። በውስጧም መነኮሳት አሉ ። ክብር ይግባውና በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ እነሱ ደረስን ። መነኮሳቱንም ከቀደሙት ሰዎች ዘመን የተላለፈ ብሉይ መጽሐፍ ከእናንተ ዘንድ እንደ አለ እመከርበት ዘንድ ስጡኝ አልኳቸው ። አንሆ በቤተ ክርስቲያን ብዙ መጻሕፍት አሉ ትርጓሜያቸውን ግን እኛ አናውቅም ብለው መለሱልኝ ። ፲፫ ፤ አምጡልኝ ልያቸው አልኳቸው አመጡልኝ ። መረመርኳቸው ። እግዚአብሔር በደቀ መዛሙርቱ ፊት ስለ አደረጋቸው ድንቅ ሥራዎችና ተአምራቶች ስለ ሰማያትና ስለ ምድር ተፈጥሮ ይህ ዓለም እስኪያልፍ ድረስ ያለውን የሚናገር ጽሑፍ አገኘሁ ። ፲፬ ፤ እኔ መጻሕፍትን ሁሉ ስመረምር ንጹሐን አባቶቻችን ሐዋርያት ስለ ሰባቱ የመላእክት አለቆች ሹመት የጻፉትን አንድ መጽሐፍ አገኙ። እንዲህ ይላል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በደብረ ዘይት ተቀምጦ የጌትነቱን ሚሥጢር ሲገልጥላቸው ሳለ ሐዋርያትም እንዲህ ብለው ለመኑት። ፲፭ ፤ ጌታችን ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ሆይ የከበረ መልአክ የሩፋኤልን ክብር ታስረዳን ዘንድ አንለምንሃለን። በመቸ ወር በመቸ ቀን ሾምከው። ከባልንጀሮቹ ከመላእክት አለቆች ጋር የተተካከለ ነውን ። የሱን ነገር ለዓለም ሁሉ እናስተምር (እንናገር) ዘንድ ። ፲፮ ፤ በታናሹ ወር በሦስተኛው ቀን በዓሉን አድርጉለት ይኸውም ጳጉሜ ነው አላቸው ። ፲፯ ፤ ስለዚህም በዚህ መልአክ አማላጅነት ከእግዚአብሔር ይቅርታ ቸርነት ያገኙ ዘንድ በችግራቸውና ጭንቀታቸው ጊዜ በዚች ቀን ሰዎች ሁሉ ልመናቸውን ያቀርቡለታል ። ፲፰ ፤ ያን ጊዜም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስቱን የመላእክት አለቆች ሚካኤልን ገብርኤልን ሩፋኤልን ከሦስተኛዪቱ ሰማይ ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው ። እነሱም ደስ እያላቸው መጥተው ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ሰገዱ ። ፲፱ ፤ በዚያም ጊዜ ጌታችንም ሩፋኤልን ጠቀሰውና ፣ የክብርህን ታላቅነት ያውቁ ዘንድ ስምህን ለሐዋርያት ንገራቸው አለው ። ፳ ፤ የመላእክት አለቃ ሩፋኤልም ሐዋርያትን እንዲህ አላቸው እኔ ሩፋኤል እባላለሁ የዋህ ነኝ ከመላእክት አለቆችም ሦስተኛ ነኝ ። የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከቀድሞ ጀምሮ የመላእክት ሁሉ አለቃ ነው ስሙም ዕፁብ ድንቅ ፣ ይቅር ባይ ማለት ነው። ፳፩ ፤ ገብርኤልም ሁለተኛ የመላእክት አለቃ ነው። ይኸውም አምላክ ሰው ሆነ (አምላክ ወሰብ) እየተባለ ይጠራል ። የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መወለድ ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ይነግራት ዘንድ የተላከ ነው ። ፳፪ ፤ እኔም አንደ ነገርኳችሁ ስሜ ሩፋኤል እባላለሁ ልቡናን ደስ የሚሰኝ የዋህ ቸር ለኃጥአን የምራራ ነኝ። ሰዎችን ስለ ኃጢኣታቸው ወደ እግዚአብሔር አላሳጣቸውም ። ስለ ደግነቴ ሰውን ስለመውደዴ የሚራዱ መላእክትን ወደ ኃጥአን ነፍስ እልካለሁ አንጂ ። ከኃጢአታቸውም እስኪመለሱ ድረስ እታገሳቸዋለሁ በደላቸውንም ይቅር እላቸዋለሁ ። ፳፫ ፤ እግዚአብሔር በሐያ ሦስቱ ነገደ መላእክት ላይ የሾመኝ እኔ ሩፋኤል ነኝ ። እግዚአብሔር አብን ይቅር ባይ ልጁን ደስ የሚያሰኝ መንፈስ ቅዱስን አመሰግነዋለሁ ። ፳፬ ፤ በደብረ ጸዮን በሺው ዓመት ሠርግ ለወዳጆቹ በጎ ነገርን እሰጣቸው ዘንድ እግዚአብሔር ያዘዘኝ እኔ ሩፋኤል ነኝ ። በንጹሕ ዙፋኑ ላይ ተቀምጦ ከእርሱ ጋር ለተቀመጡ የዕውነተኛ ክብርን ከተመላ ጽዋ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያጠጣቸው ጊዜ ። ፳፭ ፤ በዚያች በድኅነትና በደስታ ቀን ለክርስቲያን ከዕፀ ሕይወት እሰጣቸው ዘንደ እግዚአብሔር የአዘዘኝ እኔ ሩፋኤል ነኝ። ፳፮ ፤ ሰማያውያን መዛግብት በእጄ የሚጠበቁ እኔ ሩፋኤል ነኝ። እግዚአብሔር እንደ አዘዘኝ ልከፍታቸውና ልዘጋቸው የምችል አኔ ነኝ ። ፳፯ ፤ አንድ ሰው በእኔ ስም በዚህ ዓለም መከራ ለአገኘው ሰው በጎ ቢያደርግ ። የሹመቴን መጽሐፍ የሚጽፍ በእኔ ስምም ከድኆቹ አንዱን የሚያስብ ሰው ቢኖር ጳጉሜን ሦስት ቀን በምትሆነው እግዚአብሔር እኔን ከሾመባት በመላእክት ሹመት ባከበረባት በመታሰቢያዬ ቀን ፍሬ ግብር ዕጣን ጧፍ የሚሰጥ ቢኖር እኔ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም አስኪገቡ ድረስ በብርሃን ሠረገላ አወጣቸዋለሁ። ፳፰ ፤ በዚህ ዓለም ፈጽሞ እንደሱ ያለ የማይገኝ ሽታው እጅግ የተወደደ የሽቱ አበባ በእጃቸው እንዲይዙ አደርጋለሁ። ፳፱ ፤ እግዚአብሔር የመረጣቸው ሐዋርያት ሆይ በእግዚአብሔር ፊት እስክትቆሙ ድረስ ሁል ጊዜ እጠብቃችሁ እረዳችሁ ዘንድ ከእኔ ረድኤትን እሹ ። በመላው ዓለም ላሉ ሰዎችም መታሰቢያዬን ያደርጉ ዘንድ ንገሩ አስተምሩ ። አኔ ስለነሱ ወደ እግዚአብሔር እማልዳለሁ ከመከራችውም አድናቸዋለሁ ቅጣትንም ፈጽሞ አያዩም ። ይህን ብሎ ቅዱስ ሩፋኤል በእግዚአብሔር ፊት ሰገደ ወደ ሰማያትም ዐረገ ። ፴ ፤ ሐዋርያትም ጌታችን እንደአዘዛቸው በዓሉን አከበሩ ዜናውን አስተማሩ። ስለዚህም ሰዎች በኃዘናቸውና በመከራቸው ጊዜ ይጠሩታል። በዚህ መልአክ አማላጅነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ጸጋንና ይቅርታን ያገኙ ዘንድ። የመላእክት አለቃ በዚህ የከበረ መልአክ የሩፋኤል ተአምራት ብዙ ነው። እኛም ሁል ጊዜ መታሰቢያውን እናደርግ ዘንድ ይገባናል ። እሱ ስለእኛ ወደ እግዚአብሔር ይማልደናል። አማላጅነቱ ጸሎቱ በረከቱ ከእኛ ጋር ይኑረ ለዘለዓለሙ አሜን። ዘአቅረብኩ ማኅሌተ በል። መጽሐፈ ጦቢት ስለ ቅዱስ ሩፋኤል በሰፊው ያስተምራል በተለይ ጦቢት ፥ ፲፪-፲፭ ። በተጨማሪም መጽሐፈ ሄኖክ ይመልከቱ ።
1820
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8D%E1%88%8D%E1%88%B5%E1%8D%8D%E1%8A%93
ፍልስፍና
ፍልስፍና የሚለው ቃል ከግሪኩ «» /ፊሎስ/ ማለትም ፍቅር እና፣ «» /ሶፎስ/ (ጥበብ) የተገኘ ውሁድ ነው። በቀጥታው የጥበብ ፍቅር ወይም ፍቅረ ጥበብ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። በመሆኑም ፍልስፍና እውቀትን፣ እውነትን፣ ጥበብን መውደድ፣ መሻት፣ መመርመር ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። ባንድ በኩል ወደ ጥበብ የተሳበ፣ ጥበብን የወደደ እንደዚሁም የጥበብ ባለሟልን የሚያመለክት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ጥበብን ወዶ ሌላውም እንዲወድ ምክንያት የሚሆን ለማለት ይውላል። ይህ የጥናት ክፍል በዋናነት ነገሮችን በመላምታዊ መንገድ ለመመርመር ይሞክራል። የፍልስፍናን ምንነት ለማወቅ የሚጠይቃቸውን ዋነኛ ጥያቄዎች እንመልከት። ፍልስፍናዊ ጥያቄዎች ፍልስፍና የሚመረምራችው አምስት ዋነኛ ቁምነገሮች ህላዌ፣ ግብረገብ፣ ዕውቀት፣ እውነት፣ እና ውበት ናቸው። ፈላስፋዎችን ለብዙ ዘመናት ሲያስጨንቁ ከቆዩ ጥያቄዎች ውስጥ እውነት ምንድር ነው? አንድን አስተያየት ለምንና እንዴት እውነት ወይም ሃሰት መሆኑን እናውቃለን? ጥበብስ ምንድር ናት? አዋቂነት የሚቻል ነገር ነውን? ማወቃችንን እንዴት እናውቃለን? አዋቂነት የሚቻል ነገር ከሆነ የታወቀ እና ያልታወቀ ማለት ምንድር ነው? ከታወቀው ያልታወቀውን እንዴት መሻት እንችላለን? ግብረገብ በሆነው እና ባልሆነው መካከል ልዩነት አለን? ካለስ ልዩነቱ ምንድር ነው? የትኞቹ ድርጊቶቻችን ናቸው ልክ? ልክ ያልሆኑትስ የትኞቹ ናቸው? ሥነምግባራዊ መስፈርቶች ቋሚ ናቸው ወይስ ተነፃፃሪ? እንዴትስ መኖን አለብኝ? ገሃድ የሆነው ምንድር ነው? የገሃድ ነገሮች ተፈጥሮአቸው እንዴት ያለ ነው? እውን አንዳንድ ነገሮች ከኛ ግንዛቤ ውጭ መኖር ይቻላቸዋልን? ውበት ምንድር ነው? ውብ የሆኑ ነገሮች ከሌሎቹ በምን ይለያሉ? ሥነጥበብ ምንድር ነች? ሃቀኛ ውበት የገኛልን? የሚሉት ናቸው። እነዚህ ከላይ በደፈናው የተጠቀሱ ጥያቄዎች እንደ ቅደም ተከተላቸው አመክንዮአዊ፣ ሥነ-እውቀታዊ፣ ሥነ-ምግባራዊ፣ ሥነ-ኃልዮአዊ፣ እና ሥነ-ውበትአዊ በመባል ይታወቃሉ። ምንም እንኳን እነዚህ ዋነኞቹ ጥያቄዎች ይሁኑ እንጂ ብቸኞቹ አይደሉም። በተጨማሪም በመካከላቸው አንዳንድ መደራረብ ይታያል። ታዋቂው የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ ሥነ-መንግሥት፣ ሥነ-ተፈጥሮ፣ ሥነ-ምድር፣ ሥነ፡ሕይወት፣ ሥነ-አየር እና ሥነ ፈለክ የፍልስፍና ክፍሎች ናቸው ብሎ ያምን ነበር። ሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ "ፍልስፍና" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። ፍልስፍናዊ ባህሎች የምዕራቡ ዓለም ፍልስፍና የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ ዓለም ፍልስፍና የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ ፍልስፍና በኢሥላም “ሐኪም” ማለት “ጥበበኛ” ማለት ሲሆን “ሓኪም” ማለት ደግሞ “ፈራጅ” ማለት ነው፤ ሁለቱም “ሐከመ” َ ማለትም “ፈረደ” “ተጠበበ” ከሚል ግስ የመጡ ናቸው፤ “ሒክማህ” ማለት “ጥበብ” ማለት ሲሆን “ሑክም” ደግሞ “ፍርድ” ማለት ነው፤ ጥበብ እና ፍርድ የጥበበኛው እና የፈራጁ አላህ ባህርያት ናቸው፤ አላህ እጅግ በጣም ጥበበኛ ነው፦ 28፥9 «ሙሳ ሆይ! እነሆ እኔ አሸናፊው *ጥበበኛው* አላህ ነኝ፡፡ 3፥6 እርሱ ያ በማሕጸኖች ውስጥ እንደሚሻ አድርጎ የሚቀርጻችሁ ነው፡፡ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ አሸናፊው *ጥበበኛው* ነው፡፡ አላህ ለሚሻው ሰው ጥበብን ይሰጣል፤ ጥበብን ከአላህ የተሰጠው ሰው ብዙን መልካም ነገር በእርግጥ ተሰጦታል፦ 2፥269 *ለሚሻው ሰው ጥበብን ይሰጣል፤ ጥበብንም የሚሰጠው ሰው ብዙን መልካም ነገር በእርግጥ ተሰጠ*፡፡ የአእምሮዎች ባለቤቶች እንጂ ሌላው አይገሰጽም፡፡ አላህ ጥበብን ለሰው ልጆች በዐቅል እና በነቅል ይሰጣል፤ እነዚህ ሁለት የጥበብ ጭብጦችን ነጥብ በነጥብ እንይ፦ ነጥብ አንድ “ዐቅል” ማለት “ግንዛቤ”” ማለት ሲሆን አላህ በቁርአን “ለዐለኩም ተዕቂሉን” ይለናል፦ 12:2 በእርግጥ እኛ *ትገነዘቡ ዘንድ* ዐረብኛ ቁርአን ሲሆን አወረድነው። 2:242 እንደዚሁ አላህ አንቀጾቹን *ትገነዘቡ ዘንድ* ለእናንተ ያብራራላችኋል፡፡ “ትገነዘቡ ዘንድ” የሚለው ቃላት በአጽንዖትና በእንክሮት ልናጤነው የሚገባ ሃይለ ቃል ነው፤ የሰው ልጅ “አዕምሮ” እራሱ “ዐቅል” ይባላል፤ ዐቅል የጥበብ ተውህቦ”” ነው፤ የሰው ልጅ በተፈጥሮ ጥበብን ይወዳል፤ “ፊሎሶፍይ” የሁለት ቃላት ውቅር ነው፤ “ፊሎስ” “ፍቅር” እና “ሶፎስ” “ጥበብ” ሲሆን “የጥበብ ፍቅር” ማለት ነው፤ ይህም ሥነ ጥበብ በውስጡ፦ ሥነ-አመክንዮ ””፣ ሥነ-ኑባሬ ””፣ ሥነ-እውነት ””፣ ሥነ-ዕውቀት ””፣ ሥነ-መለኮት ””፣ ሥነ-ምግባር ””፣ ሥነ-ውበት ””፣ ሥነ-መንግሥት ””፣ ሥነ-ቋንቋ ” የመሳሰሉት እሳቦት ይዟል። ጥበብ”” እራሱ፦ ሥነ-ጥበብ፣ እደ-ጥበብ፣ ኪነ-ጥበብ እና አውደ-ጥበብ ለአሉታዊ ነገር ከተጠቀሙበት ምግባረ-እኩይ”” ሲሆን በአውንታዊ ከተጠቀምንበት ምግባረ-ስናይ”” መማሪያም ነው፤ አላህ፦ “አፈላ ተዕቂሉን” ይለናል፦ 21:10 *ክብራችሁ በውሥጡ ያለበትን መጽሐፍ ወደ እናንተ በእርግጥ አወረድን፤ አትገነዘቡምን*? “አትገነዘቡምን?” የሚለው ቃላት በአጽንዖትና በእንክሮት ልናጤነው የሚገባ ሃይለ ቃል ነው፤ ቁርአን ክብራችን በውሥጡ ያለበትን መጽሐፍ ነው፤ አዎ የሰው ልጆች ሊከብሩበት የሚችሉበት ጥበብ ይዟል። ነጥብ ሁለት “ነቅል” - “ነቅል” ማለት “አስተርዮ”” ማለት ሲሆን “ወሕይ” ነው፤ አምላካችን አላህ ወደ ነብያችን”””” ጥበብን አውርዷል፦ 4፥113 አላህም በአንተ ላይ መጽሐፍንና *ጥበብን* አወረደ፡፡ *የማታውቀውንም ሁሉ አስተማረህ*፡፡ የአላህም ችሮታ በአንተ ላይ ታላቅ ነው፡፡ ይህም ጥበብ ክብራችን በውሥጡ ያለበትን መጽሐፍ ቁርአን ነው፤ ቁርአን ጥበብ የተሞላ መጽሐፍ ነው፦ 10፥1 “አሊፍ ላም ራ” ይህቺ *ጥበብ* ከተመላው መጽሐፍ ከቁርኣን አንቀጾች ናት፡፡ 30፥2 ይህች *ጥበብ* ከተመላው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡ 36፥2 *ጥበብ* በተመላበት ቁርኣን እምላለሁ፡፡ ስለዚህ ክብራችን በውስጡ ያለበትን ይህንን ጥበብ የተሞላ መጽሐፍ መገንዘብ ግድ ይላል ማለት ነው፤ የእሳት ሰዎች “የምናገናዝብ” በነበርን ኖሮ በነዳጅ እሳት ጓዶች ውስጥ ባልሆን ነበር ብለው ይፀፀታሉ፦ 67:10 የምንሰማ ወይንም *”የምናገናዝብ”* በነበርን ኖሮ በነዳጅ እሳት ጓዶች ውስጥ ባልሆን ነበር ይላሉ። (✍ከወንድም ወሒድ ዑመር) ተግባራዊ ፍልስፍና
52637
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8B%E1%8A%93%E1%88%9C%20%E1%8B%AB%E1%8A%A2
ጋናሜ ያኢ
ጋናሜ ያኢ አንዲት ኦሮሞ ሴት ለባርነት የተሸጠች፤ እሷም የኦሮምኛ ስነ ጽሁፍ መሰረት ሆናለች በ18ኛው እና በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ብዙ ቁጥር ያለው የኦሮሞ ህዝብ በተለያዩ ሀገራት ለባርነት ትሸጥ ነበር። ከእነዚህ መካከል አንዷ የሆነች ሴት ማንነቷን ሳትዘነጋ ለኦሮምኛ ቋንቋ እና ስነ-ጽሁፍ እድገት መሰረታዊ አስተዋፅኦ ስላደረገች ሴት ጠየቅናት። የትውልድ ስሟ ነው፣ በጀርመንኛ ግን ፓውሊን ፋጢማ ትባላለች። ጋናሜ ማን ናት? ለባርነት የተሸጠችውስ እንዴት ነው? ጋናሚን በ1830ዎቹ መጀመሪያ ላይ በጅማ አውራጃ በጉማ ተወለደች፣ የህይወት ታሪኳን የፃፈች ጀርመናዊት መምህር ተናግራለች። በወቅቱ በባሪያ ንግድ ወቅት ብዙ ልጆች ከቤተሰቦቻቸው ተዘርፈዋል ወይም በጎሳ መካከል በሚደረጉ ጦርነቶች ለባርነት ተወስደዋል ሲሉ የቋንቋና ስነ-ጽሁፍ መምህር ተፈሪ ንጉሴ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጋናሚ ከቤተሰቦቿ የተሰረቀችው በባሪያ ነጋዴዎች ሊሆን እንደሚችል ተናግሯል። የጋናሚ ያኢን የሕይወት ታሪክ በመመርመር፣ ሊደርሆስ አባቷ በጦርነቱ የተገደለው በስድስት ዓመቷ እንደሆነ ጽፋለች። አንድ ቀን በ9 ዓመቷ የአባቷን መቃብር እየጎበኘች በባሪያ ነጋዴዎች ታግታለች። ከዚያም “ከጅማ ወደ ጎንደር፣ ከዚያ ወደ ግብፅ ተሸጠች” አለ ተፈሪ። በግብፅ 12 ጊዜ ደጋግማ ከተሸጠች በኋላ ወደ ካይሮ የተወሰደችው የግብፃዊው መህመት አሊ ንብረት እንደሆነ ሊዳርሆስ አንቀፅ ገልጿል። በሱ ክፍል ውስጥ እንደምትሰራ እና እስልምናን እንደምትከተል ጽፏል። “ጀርመናዊቷ ጆን ባሮን በ1847 ወደ ግብፅ በተጓዘች ጊዜ ሕይወቷን ለውጦታል” በማለት የቀድሞ ጀርመናዊ ተመራማሪና ፕሮፌሰር ዎልበርት ስሚዝ ተናግረዋል። ግብፃዊው ጋናሚ ለጆን ባሮን በስጦታ ሰጠው። ዎልበርት ስሚዝ በምርምርው ላይ እንዳሳተመዉ ጀርመን ቆርኔሌዎስ ስትደርስ ስሟ ፋጢማ ተብሎ ተቀየረ እና ከክርስትና ጥምቀት በኋላ ስሟ ወደ ፓውሊን ዮሃን ተቀየረ። የወንጌል ትምህርት እና ሕይወት በጀርመን ከተገዛች በኋላ ጋናሜ ወደ ትምህርት ቤት የሄደችው የቤት ውስጥ እንክብካቤን ለመማር እና "በትምህርቷ በጣም ጠንካራ ስለነበረች" ከሚስዮናውያን ጋር መሥራቷን ቀጠለች ይላል ታፋሪ። ከተባለው ተሰጥኦዋ አንዱ እንግሊዘኛ፣ ጀርመንኛ እና አረብኛን ጨምሮ ወደ አምስት የሚጠጉ ቋንቋዎችን አቀላጥፋ ተናግራለች። በጠዋት ክርስትናን ተቀብላ በ1852 ከተጠመቀች በኋላ ከካህናትና ከሚሲዮናውያን ጋር ተቀራርቦ መሥራት ጀመረች። ባህል እና ቋንቋን በማስተማር ላይ ያለው አስተዋፅዖ ጋናሜ በስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴ ውስጥ ትልቅ ሚና እንደነበራት ሚስተር ተፈሪ ተናግረዋል። ጋናሚን 'የኦሮሞ ልጅ' የተሰኘ ትዝታዎቿን መፅሃፍ ፅፋ ከሞተች በኋላ ታትሞ ከ30 በላይ ቋንቋዎች ተተርጉሟል። መጽሐፏ ተጠናቀቀ እና በጀርመን ሊደር ሃውስ ታትሟል። «ኦሮሞን ለአለም አሳውቃለች በተለይ አውሮፓ።» በሚያዝያ 1855 ጋናሜ ወንጌሉ ለህዝቦቿ እንዲደርስ ያላትን ፍላጎት በመግለጽ ለሚስዮናውያን ደብዳቤ ጻፈች። ጋናመን ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ ተልዕኮ ለመመስረት ዋና ምክንያት ሊሆን ይችላል ብለዋል። ተልእኮው ለኦሮሞ ህዝብ እንዲደርስ፣ ወንጌልን ወደ ኦሮምኛ ለመተርጎም ጥረት በማድረግ እና ሌሎች ተግባራት ላይ የራሱን አስተዋፅኦ አድርጓል። “የኦሮሞ ልጅ” ማለዳ መፅሃፋችንም ሲሸጥ የተገኘው ገቢ ለተልዕኮው ተሰጥቷል ተብሏል። ይህ ተልእኮ በኦሮሚያ ትምህርት ቤቶች፣ አብያተ ክርስቲያናት እና የተለያዩ ማዕከላት ግንባታ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ህዳር 1855 እ.ኤ.አ. ጥዋት ላይ በድንገት በመተንፈሻ አካላት በሽታ ተይዛ በየካቲት 11 ሞተች ። ወልበርት ስሚዝ ጋናመን የተቀበረው በሪየን እንደሆነ ጽፏል። የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች‎ ኢትዮጵያ በ19ኛው ክፍለ ዘመን
15696
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%88%B2%E1%8B%B3%E1%88%9B%20%E1%89%A3%E1%88%95%E1%88%8B%E1%8B%8A%20%E1%88%90%E1%8B%AD%E1%88%9B%E1%8A%96%E1%89%B5
የሲዳማ ባሕላዊ ሐይማኖት
የሲዳማ ባህላዊ ሐይማኖት ሲዳማ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች መካከል አንዱ ሲሆን፡ ቀድሞ የሲዳሞ ክፍለ አገር ይባል በነበረው እና በአሁኑ ጊዜ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት አካል በሆነው ሲዳማ ዞን ውስጥ የሚገኝ ህዝብ ነው። ህዝቡ ከሲዳማ ዞን ውጪ በአጎራባቹ የኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖች ውስጥ ይኖራል። የህዝብ ብዛቱም ከአራት ሚሊዮን በላይ እንደሆነ የተለያዩ ዶክመንቶች ያመለክታሉ። ሲዳማዎች የአፍሮ - እስያቲክ ግንድ ካላቸው እና በሰሜን አፍሪካ፣ በአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም በደቡብ ምዕራብ እስያ ከሚነገሩ 375 ቋንቋዎች አንዱ የሆነ እና ከኩሽ ወይም ከኩሺቲክ የቋንቋ ቤተሰብ የሚመደብ ቋንቋ ይናገራሉ። ከቋንቋቸው ባሻገር እንደሌሎቹ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ሁሉ የራሳቸው የሆነ ባህል፣ እምነት፣ አስተዳደራዊ ስርዓት፣ መገበያያ ገንዘብ፣ የጊዜ እና ዘመን አቆጣጠር ስርዓት እና ሌሎች ማህበራዊ እሴቶች ያሉት ህዝብ ነው። ሲዳማዎች ለዘመናት ከአባት ወደ ልጅ እያወረሱ ካቆዩት እሴቶቻቸው መካከል ባህላዊ ሐይማኖት ይገኝበታል። በሐይማኖቱ መሰረት ሲዳማዎች በማጋኖ ( አምላክ ወይም እግዚአብሔር) ያምናሉ። ማጋኖ ፣ ሐላሌ ( እውነት) እና አካካ ( አባቶች፣ አያቶች፣ ቅድመ አያቶች) የእምነታቸው ምሰሶዎች ናቸው። በእነዚህ ሶስቱ ምሰሶዎች ላይ እና በእምነቱ አጠቃላይ ጽንሰ ሐሳብ ላይ አንዳንድ ሀሳቦችን ከማንሳት በፊት ስለአካኮዎች ወይም አባቶች፣ አያቶች፣ ቅድመ አያቶች ወይም ስለሲዳማ ጎሳዎች ትንሽ ልበል። ሲዳማዎች ከመካከለኛው ምስራቅ ባህርን ተሻግረው ወደ አፍሪካ ቀንድ መምጣታቸውን፣ በመጀመሪያ «ዳዋ» 1 ከሚባል ቦታ ላይ መስፈራቸውን ቀጥሎም በባሌ አድርገው አሁን ወዳሉበት አከባቢ መምጣታቸውን የብሔሩ ሽማግሌዎች ይተርካሉ። በትረካቸውም አሁን ወዳሉበት አከባቢ እንዲመጡ ያደረጋቸው የአባታቸው ጉዛዜ መሆኑን ይናገራሉ። እንደሽማግሌዎቹ ገለፃ፡ ሲዳማዎች የሁለት አባቶች ልጆች ሲሆኑ፡ ቡሼ የሚባለው አንደኛው አባታቸው ሲሞት ከመቃራቸው ጉድጓድ የሚወጣው አፈር ከተቀበሩ በሃላ ሲመለስ ከመሬት ከፍ ወይም ዝቅ ከሚል ቦታ እንዳይቀብራቸው በተናዘዙት መሰረት የአባታቸውን ሬሳ በተለያዩ አካባቢዎች እና ቦታዎች ለመቅበር ሞክረው ስላልተሳካላቸው መጀመሪያ ከሰፈሩበት አካባቢ ተነስተው በባሌ አድርገው እግሬ መንገዳቸውን የአባታቸውን ሬሳ እየቀበሩ እያወጡ ዛሬ ወዳሉበት አከባቢ መጥተዋል። በአከባቢውም የአባታቸውን ሬሳ ሲቀብሩ በተናዘዙት መሰረት ከመቃብር ጉድጓድ የወጣው አፈር ወደ መቃብሩ ሲመለስ ከመሬት እኩል በመሆኑ የአባታቸው የመጨረሻ የመቃብር ቦታ ሆነ። ከአባታቸው የመቃብር አከባቢ መራቅ ያልፈለጉት ሲዳማዎችም በአከባቢው ሰፍረው እስከአሁን ይኖራሉ። እንግዲህ ስለሲዳማዎች አባት ኑዛዜ አፍጻጸም ያለምክንያት አይደለም ያነሳሁት፡ በብሔሩ ባህላዊ ሐይማኖት መሰረት የእርሱ የመቃብር ቦታ እና ሌሎች መሰል የጎሳ አባቶች መቃብሮች በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ ቦታ ስላላቸው ነው። ወደታች በስፋት አነሳዋለሁ። ለባህላዊ ሐይማኖቱ መሰረት የሆነው ሌላው ማጋኖ ነው። ከላይ እንዳነሳሁት የሐይማኖቱ ተከታዮች በማጋኖ ( አምላክ ወይም እግዚአብሔር ) ያምናሉ። ለማጋኖ፤ ካላቃ (ፈጣሪ)፣ ካሊቃ (ሃያል ሁሉን ቻይ) እና ሐላላንቾ (እውነተኛ) በማለት ሶስት ገጽታዎችን ይሰጡታል። ከዚህም በተጨማሪ ማጋኖ፤ እውነተኛ ወዳጅ፣ ለልጆቹ የሚሳሳ፣ የሚራራ፣ ሲያጠፉ የሚገጽጽ፣ ሀጢኣያታቸው የሚምር ሩህሩህ አባት ነው ይላሉ። በሐይማኖቱ ማጋኖ አምሳያ የለውም። በአምሳሉ የተቀረጹ ወይም የቆሙ ወይም መልኩን የሚያሳዩ ቁሶች የሏቸውም፤ ነገር ግን ቀን በቀን ከመሃከላቸው እንደሚገኝ ያምናሉ። ስሙ በራሱ የሚፈራ እና የሚከበር በመሆኑ ለመልካም ስራ ካልሆነ ለክፉ ተግባራት ማለትም ለማታለሊያነት፣ ውሸት ለመናገር፣ ወዘተ አይጠራም። ለክፋት ስሙን ማንሳት ወይም መጥራት ማጋኖን ያስቆጣል ተብሎ ይታመናል። ማጋኖ የሰውን ልጅ ከአፈር ፈጥሮ ትንፋሹን ከሰጠው በኋላ ወደ ሰማይ አረገ። ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ከፈጠው የሰው ልጅ ጋር በሐላሌ አማካይነት ይገናኝ ነበር። ሐላሌም በሰው እና በካሊቃ መካከል እንደድልድይ ሆነ ስለ ሰው ልጅ ያማልዳል ነበር። የእምነቱ ተከታዮች እንደምሉት ከሆነ፤ ሐላሌ ሲዳማዎች ከፈጣሪያቸው ጋር የሚገናኙበት ብቸኛው ድልድይ በመሆኑ ታላቅ ክብር እና ዋጋ ይሰጡት ነበር። በመጀመሪያ ላይ ሐላሌ በአይን የምታይና በእጅ የምዳሰስ፤ ሰዎች በሚያሹት ወቅት በየትኛውም ቦታ እና ጊዜ የሚገኝ ብሎም በሰው ልጆች መካከል የሚመላለስ ነበር። ሐላሌ ለሲዳማዎች ቅርብ ከመሆኑ እና ሲዳማዎችም ለሐላሌ ካላቸው ክብር የተነሳ በእርሱ ይተዳደሩ ነበር፤ ሐላሌም ሲዳማን ያስተዳድር ነበር። ነገር ግን ከብዙ ዓመታት በኋላ የሰው ልጆች በክፋት፣ ጥላቻ፣ ተንኮል ፣ ክህደት እና በሌሎች ክፉ ተግባራት እየተሰማሩ የፈጣሪን ትዕዛዛት እየጣሱ ሲመጡ፤ ሐላሌ ከመሃከላቸው መመላለስን እና ማስተዳደሪን ትቶ ወደ ፈጣሪ ወይም ካሊቃ ዘንድ ለመሄድ ተነሳ። ሐላሌ ከመካከላቸው እንደማይኖር እና ጥሏቸው ወደ ካሊቃ (ማጋኖ) እንደሚሄድ የተረዱ እና ከእንግዲህ ከፈጣሪ ጋር እንደት ሆኖ እንደምገናኙ ያልተረዱት የእምነቱ ተከታዮች ሐላሌ ለማን ጥሏቸው እንደሚሄድ ጠየቁት። ሐላሌም ከእንግዲህ ከካሊቃ ጋር የምትገናኙት በአባቶቻችሁ በኩል ነው። አባቶቻችሁ ከፈጣሪ ጋር ያገናኟችሃል፣ ስለእናንተ ፈጣሪን ይማለዱላችሃል ብሏቸው ወደ ሰማይ አረገ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሐይማኖቱ ተከታዮች በሞት የተለዮቸው አባቶቻቸው፣ አያቶቻቸው፣ ቅድመ አያቶቻቸው ከማጋኖ ጋር ይኖራሉ ብለው አመኑ፤ ከማመንም በላይ ከማጋኖ ጋር ለመገናኘት አባቶቻቸውን መጠቀም ጀመሩ። በእምነቱ ፊልስፊና መሰረት «እኔ ከእኔ በላይ አባቴ ፣ ከአባቴ በላይ ቀደሚት አባቶቼ፣ ከቀደሚት አባቶቼ በላይ ካሊቃ (ማጋኖ)» ተብሎ ይታመናል። ከእምነቱ ጋር በተያያዘ እና በሌሎች ማህበራዊ ምክንያቶች የተነሳ ሲዳማዎች ለአባቶች እና ለአረጓውያን የተለየ አክብሮት አላቸው። እንግዲህ ሐላሌ ወደ ካሊቃ ካረገበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ አባቶች የእምነቱን ተከታዮች ከፈጣሪ ያገናኛሉ፣ ያስታርቃሉ፣ ስለእነርሱ ይማለዳሉ።ከዚህም ባሻገር የማህበረሰቡ ስነ ምግባር ወይም የግብረገብነት እና ሐይማኖታዊ ሕግጋት መከበራቸውን ይቆጣጠራሉ። የአባቶቻቸው የመቃብር ቦታም የእምነቱ ስነስርዓት ማካሄጃ ቦታ ሆነው ያገለግላሉ። ከላይ ከመግቢያዬ ላይ እንዳነሳሁት፤ የሲዳማ ጎሳዎች አባቶች በተለይ ሁለቱ የሲዳማ ዘር የተነሳባቸው አባቶች መቃብር ቦታዎች በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ቅዱስ ቦታዎች ናቸው። በሲዳምኛ ሞጎ ተብለው የሚታወቁት የአባቶች እና ቅድመ አባቶች ወይም የአካኮች መቃብሮች፤ ታጥረው በጥንቃቄና በንፅህና የተያዙ፣ የእምነቱ ተከታዮች ፈጣሪውን ለማምለክ የሚሰባሰብባቸው፣ እንዲሁም ፈጣሪን መማጸኛ መስዋዕቶችን የሚያቀርቡበት ቅዱስ ስፍራ ነው። በእነዚህ በትላልቅ ዛፎች በተሞሉ 2 ቅዱስ ስፍራዎች የእምነቱ መሪዎች ይኖራሉ። በጥቅሉ ቃዶ ተብሎ የሚጠሩት እነዚህ የእምነቱ መሪዎች በቁጥር አራት ሲሆኑ፤ ከስራ ሐላፊነታቸው አንፃር ጋና፣ ቃሪቻ፣ ዎማ እና ጋዳላ ይባላሉ። ከላይ እንዳነሳሁት የእምነቱን ተከታዮች ከፈጣሪ ወይም ከካሊቃ ጋር እንደድልድይ ሆኖ ያገናኛቸው የነበረው እና ያስተዳድራቸው የነበረው ሐላሌ ወደ ካሊቃ ከሄደ በሃላ ከፈጣሪ ጋር የማገናኘቱን ስራ ለአባቶች ስሰጥ ህዝቡን የማስተዳደር ስራ ሐላሌን ተክቶ እንዲሰሩ ከእምነቱ ተከታዮች መካከል ለተመረጡ ሰዎች ተሰጥቷል። ሐላፊነቱን የወሰዱት እነዚሁ ቃዶዎች ናቸው። የእምነቱ ተከታዮች ከእምነቱ እና ከእለትለት ማህበራዊ ኑሮ ጋር በተገናኘ የሚገጥሟቸውን ችግሮች እና ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ መንፈሳዊ ማበረታቻዎችን እና ማህበራዊ ፍትሕ ለማግኘት ወደነዚህ ቅዱስ ቦታዎች በመሄድ ቃዶዎቹን ያገኟቸዋል። ቃዶዎቹም ሐላፊነት ከተቀበሉበት ጊዜ ጀምሮ ከቅዱስ ቦታዎቹን እየተንከባከቡ እድሜ ልካቸውን እዛው ይኖራሉ በምትካቸው ሌላ ቃዶ የሚመረጠው ሲሞቱ ብቻ ነው። አራቱም የተለያየ የስራ ሐላፊነቶች ሲኖሯቸው፤ አንደኛው በሌላኛው ስራ ላይ ጠልቃ መግባት አይችሉም። ከዚህም በተጨማሪ እነርሱ በምሰጡት ውሳኔዎች ላይ ማንኛውም ውጫዊ አካል ጠልቃ መግባት አይችልም። እንግዲህ የሲዳማ ባህላዊ ሐይማኖትን በተመለከተ በጣም በጥቂቱ ይህንን የሚመስል ሲሆን፤ ባህላዊ ሐይማኖቱ እንደሌሎቹ የዓለማችን ትላልቅ ሐይማኖቶች ሁሉ የራሱ የሆኑ ሕጎች ያሉት፣ የራሱ የሆነ አስተዳደራዊ መዋቅሮች ያሉት፣ በብዙ መቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተከታዮች ያሉት፣ የራሱ የሆነ ማምለኪያ ስፍራ ያለው እና በራሱ ሙሉ የሆነ ነው። የሲዳማ ባሕላዊ ሐይማኖት የኢትዮጵያ ብሔር ነው። የኢትዮጵያ ብሔሮች
1912
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%89%A3%E1%89%A0%E1%88%A9%E1%89%B5%20%E1%8C%8D%E1%8B%9B%E1%89%B6%E1%89%BD
የተባበሩት ግዛቶች
ይህ ፅሑፍ ስለ አገሪቱ ነው። ስለ አህጉሮች ለመረዳት፣ ስሜን አሜሪካ ወይንም ደቡብ አሜሪካን ይዩ። ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ (ዩኤስኤ ወይም ዩኤስኤ)፣ አሜሪካ በተለምዶ ዩናይትድ ስቴትስ ( ወይም በ18ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ዩኤስ በሰሜን አሜሪካ መስፋፋት ጀመረች፣ ቀስ በቀስ አዳዲስ ግዛቶችን ማግኘት፣ አንዳንዴም በጦርነት፣ አሜሪካዊያን ተወላጆችን በተደጋጋሚ እያፈናቀለች እና አዳዲስ ግዛቶችን መቀበል ጀመረች። እ.ኤ.አ. በ 1848 ዩናይትድ ስቴትስ አህጉሩን ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ዘረጋች። በባርነት ተግባር ላይ የተነሳው ውዝግብ ያበቃው በአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት የቀሩትን የሕብረቱን ግዛቶች ተዋግቶ በነበረው የአሜሪካ ኮንፌዴሬሽን ግዛቶች መለያየት ነው። በህብረቱ ድል እና ጥበቃ፣ ባርነት በአስራ ሶስተኛው ማሻሻያ ተወገደ። እ.ኤ.አ. በ 1900 ዩናይትድ ስቴትስ የዓለም ትልቁ ኢኮኖሚ ሆነች ፣ እና የስፔን-አሜሪካ ጦርነት እና አንደኛው የዓለም ጦርነት አገሪቷን የዓለም ኃያል ሀገር አድርጓታል። እ.ኤ.አ. በ 1941 ጃፓን በፐርል ሃርበር ላይ ከደረሰች ድንገተኛ ጥቃት በኋላ ዩናይትድ ስቴትስ በተባበሩት መንግስታት ወደ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ገባች ። ከጦርነቱ በኋላ ዩናይትድ ስቴትስ እና ሶቪየት ኅብረት የዓለም ሃያላን አገሮች ሆኑ። በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት ሁለቱም አገሮች የርዕዮተ ዓለም የበላይነትን ለማስፈን ትግል ቢያካሂዱም ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭትን አስቀርተዋል። በ1969 የአሜሪካ የጠፈር በረራ ሰዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በጨረቃ ላይ ባሳረፈው የጠፈር ሬስ ውድድርም ተወዳድረዋል። በተመሳሳይ ጊዜ፣ የሲቪል መብቶች እንቅስቃሴ የግዛት እና የአካባቢ የጂም ክራውን ህጎች እና ሌሎች በአፍሪካ አሜሪካውያን ላይ የሚደርሰውን የዘር መድልዎ የሚሽር ህግ አወጣ። እ.ኤ.አ. በ 1991 የሶቪየት ህብረት መፍረስ የቀዝቃዛውን ጦርነት በማቆም ዩናይትድ ስቴትስ የዓለም ብቸኛ ልዕለ ኃያል ሀገር እንድትሆን አድርጓታል። እ.ኤ.አ. በ2001፣ የሴፕቴምበር 11 ጥቃቶችን ተከትሎ፣ ዩናይትድ ስቴትስ የአፍጋኒስታን ጦርነትን እና የኢራቅ ጦርነትን ን ጨምሮ የአለም አቀፍ ጦርነት በሽብርተኝነት ግንባር ቀደም አባል ሆነች። ዩናይትድ ስቴትስ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ነው, ሁለት የተለያዩ የመንግስት አካላትን ጨምሮ ሶስት የተለያዩ የመንግስት ቅርንጫፎች አሉት. ሊበራል ዲሞክራሲ ሲሆን የገበያ ኢኮኖሚ አለው። በአለም አቀፍ የህይወት ጥራት፣ የገቢ እና የሀብት መለኪያ፣ የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነት፣ የሰብአዊ መብቶች፣ ፈጠራ እና የትምህርት ደረጃዎች በጣም ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ዝቅተኛ የሙስና ደረጃ አለው. ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም ላይ ካሉ ማናቸውም ፖሊሲዎች በእያንዳንዱ ሰው ከፍተኛውን መካከለኛ ገቢ አላት። ከፍተኛ የእስር እና የእኩልነት እጦት እና ሁለንተናዊ የጤና እንክብካቤ የላትም። የባህሎች እና የብሄር ብሄረሰቦች መፍለቂያ፣ ዩኤስ የተቀረፀው በዘመናት በዘለቀው የኢሚግሬሽን ነው። ዩናይትድ ስቴትስ በከፍተኛ ደረጃ የበለጸገች አገር ናት፣ ኢኮኖሚዋ ከዓለም አቀፉ የሀገር ውስጥ ምርት ሩብ ያህል የሚሸፍን ሲሆን በገበያ ምንዛሪ ዋጋ ከዓለም ትልቁ ናት። በዋጋ ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም ትልቁ አስመጪ እና ሁለተኛዋ ላኪ ነች። ምንም እንኳን ከጠቅላላው የአለም ህዝብ ከ 4.2% በላይ ብቻ ቢይዝም, ዩኤስ በአለም ላይ ካለው አጠቃላይ ሀብት ከ 30% በላይ ይዛለች, በየትኛውም ሀገር ትልቁን ድርሻ ይይዛል. ዩናይትድ ስቴትስ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፣ የአለም ባንክ ፣ የአለም የገንዘብ ድርጅት ፣ የአሜሪካ መንግስታት ድርጅት ፣ ኔቶ ፣ የኳድሪተራል የደህንነት ውይይት መስራች አባል እና የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባል ነች። ሀገሪቱ ከሲሶ በላይ ለሚሆነው የአለም ወታደራዊ ወጪ ተጠያቂ ስትሆን በአለም ላይ ግንባር ቀደም ወታደራዊ ሃይል እንዲሁም መሪ የፖለቲካ፣ የባህል እና የሳይንስ ሃይል ነች። ሥርወ ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የታወቀው "አሜሪካ" የሚለው ስም በ 1507 የጀመረው በጀርመናዊው የካርታግራፍ ባለሙያ ማርቲን ዋልድሴምሙለር በተዘጋጀው የዓለም ካርታ ላይ በፈረንሳይ ሴንት-ዲዬ-ዴስ ቮስጌስ ከተማ ውስጥ ታይቷል. በካርታው ላይ ስሙ ለአሜሪጎ ቬስፑቺ ክብር ሲባል አሁን ደቡብ አሜሪካ ተብሎ በሚጠራው በትልልቅ ፊደላት ይታያል። ምዕራብ ህንዶች የእስያ ምሥራቃዊ ድንበርን እንደማይወክሉ ነገር ግን ቀደም ሲል ያልታወቀ የመሬት ስፋት አካል መሆናቸውን የገለፀው ጣሊያናዊው አሳሽ የመጀመሪያው ነው። እ.ኤ.አ. በ 1538 የፍሌሚሽ ካርቶግራፈር ጄራርደስ መርኬተር "አሜሪካ" የሚለውን ስም በራሱ የዓለም ካርታ ላይ ተጠቅሞ በመላው ምዕራባዊ ንፍቀ ክበብ ላይ ተግባራዊ አደረገ. "ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ" ለሚለው ሐረግ የመጀመሪያው ዶክመንተሪ ማስረጃ በጥር 2, 1776 በስቴፈን ሞይላን ለጆርጅ ዋሽንግተን ረዳት-ደ-ካምፕ ጆሴፍ ሪድ ከጻፈው ደብዳቤ ጀምሮ ነው። ሞይላን በአብዮታዊ ጦርነት ጥረት ውስጥ እርዳታ ለመጠየቅ “ከአሜሪካ ወደ ስፔን በሙሉ እና በቂ ሃይሎች ለመሄድ ፍላጎቱን ገልጿል። ለመጀመሪያ ጊዜ የታወቀው “ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ” የሚለው ሐረግ ስም-አልባ በሆነ መጣጥፍ ውስጥ ነበር። የቨርጂኒያ ጋዜት ጋዜጣ በዊልያምስበርግ፣ ሚያዝያ 6 ቀን 1776 በጆን ዲኪንሰን ተዘጋጅቶ ከሰኔ 17 ቀን 1776 በኋላ የተጠናቀቀው ሁለተኛው የኮንፌዴሬሽን አንቀጾች ረቂቅ “የዚህ ኮንፌዴሬሽን ስም ‘ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ’ ይሆናል።” የአንቀጾቹ የመጨረሻ እትም አወጀ። እ.ኤ.አ. በ1777 መጨረሻ ላይ ለማፅደቅ ወደ ግዛቶች ተልኳል ፣ “የዚህ ኮንፌዴሬሽን ስቲል “ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ” ይሆናል ብለዋል ። በሰኔ 1776 ቶማስ ጄፈርሰን "የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ" የሚለውን ሐረግ በሁሉም አቢይ ሆሄያት "የመጀመሪያው ሻካራ ድራግ" የነጻነት መግለጫ ርዕስ ላይ ጽፏል. ይህ የሰነዱ ረቂቅ እስከ ሰኔ 21 ቀን 1776 ድረስ አልወጣም እና ዲኪንሰን በሰኔ 17 የኮንፌዴሬሽን አንቀጾች ረቂቅ ላይ ቃሉን ከመጠቀሙ በፊት ወይም በኋላ መጻፉ ግልፅ አይደለም ። አጭር ቅጽ "ዩናይትድ ስቴትስ" እንዲሁ መደበኛ ነው. ሌሎች የተለመዱ ቅርጾች ""፣ "" እና "አሜሪካ" ናቸው። የቃል ስሞች "" ናቸው። እና በአለም አቀፍ ደረጃ "ግዛቶች". በ 18 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በነበሩት የአሜሪካ ግጥሞች እና ዘፈኖች ታዋቂ የሆነው "ኮሎምቢያ" መነሻው ከክርስቶፈር ኮሎምበስ ነው ። ሁለቱም "" እና "" በዩኤስ የቦታ-ስሞች, ኮሎምበስ, ኦሃዮን ጨምሮ በተደጋጋሚ ይታያሉ; ኮሎምቢያ, ደቡብ ካሮላይና; እና የኮሎምቢያ ዲስትሪክት. በምዕራባዊው ንፍቀ ክበብ ውስጥ ያሉ ቦታዎች እና ተቋማት ኮሎን፣ ፓናማ፣ የኮሎምቢያ ሀገር፣ የኮሎምቢያ ወንዝ እና የኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ሁለቱን ስሞች ይይዛሉ። "ዩናይትድ ስቴትስ" የሚለው ሐረግ በመጀመሪያ በአሜሪካውያን አጠቃቀም ብዙ ቁጥር ነበረው። የግዛቶች ስብስብን ገልጿል-ለምሳሌ, "ዩናይትድ ስቴትስ ናቸው..." የነጠላ ቅርጽ የእርስ በርስ ጦርነት ካበቃ በኋላ ታዋቂ ሆነ እና አሁን መደበኛ አጠቃቀም ነው. የዩናይትድ ስቴትስ ዜጋ "አሜሪካዊ" ነው. "ዩናይትድ ስቴትስ", "አሜሪካዊ" እና "ዩ.ኤስ." አገሪቷን በቅጽል ("የአሜሪካ እሴቶች"፣ "የአሜሪካ ኃይሎች") ተመልከት። በእንግሊዘኛ "አሜሪካዊ" የሚለው ቃል ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በቀጥታ ያልተገናኙ ርዕሰ ጉዳዮችን ወይም ጉዳዮችን እምብዛም አያሳይም። የአገሬው ተወላጆች እና የቅድመ-ኮሎምቢያ ታሪክ የሰሜን አሜሪካ የመጀመሪያዎቹ ነዋሪዎች በቤሪንግ የመሬት ድልድይ ከሳይቤሪያ እንደተሰደዱ እና ቢያንስ ከ 12,000 ዓመታት በፊት እንደደረሱ በአጠቃላይ ተቀባይነት አግኝቷል ። ይሁን እንጂ አንዳንድ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የመድረሻ ቀን እንኳን ቀደም ብሎ ነበር። ከክርስቶስ ልደት በፊት በ11,000 አካባቢ ብቅ ያለው የክሎቪስ ባህል የአሜሪካን አሜሪካን የመጀመሪያ የሰፈራ ማዕበል ይወክላል ተብሎ ይታመናል። ይህ ምናልባት በሰሜን አሜሪካ ወደ ፍልሰት ከሦስት ዋና ዋና ማዕበል መካከል የመጀመሪያው ነበር; በኋላ ላይ ማዕበሎች የአሁኖቹ የአታባስካን፣ የአሌውትስ እና የኤስኪሞስን ቅድመ አያቶች አመጡ። በጊዜ ሂደት፣ በሰሜን አሜሪካ ያሉ የአገሬው ተወላጆች ባህሎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰቡ እየጨመሩ ይሄዳሉ፣ እና አንዳንዶቹ እንደ ደቡብ ምስራቅ የቅድመ-ኮሎምቢያ ሚሲሲፒያን ባህል የላቀ ግብርና፣ አርክቴክቸር እና ውስብስብ ማህበረሰቦችን አዳብረዋል። የካሆኪያ ከተማ-ግዛት በዘመናዊቷ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ትልቁ፣ በጣም ውስብስብ የቅድመ-ኮሎምቢያ አርኪዮሎጂ ጣቢያ ነው። በአራት ማዕዘናት ክልል፣ የአባቶች ፑብሎአን ባህል ከብዙ መቶ ዓመታት የግብርና ሙከራ አድጓል። በደቡባዊ ታላቁ ሀይቆች አካባቢ የሚገኘው የተመሰረተው በአስራ ሁለተኛው እና አስራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን መካከል በሆነ ወቅት ነው። በአትላንቲክ ውቅያኖስ ዳርቻ ላይ በጣም ታዋቂ የሆኑት የአልጎንኩዊያን ጎሳዎች ነበሩ ፣ አደን እና ወጥመድን ይለማመዱ ፣ ከእርሻ ውስንነት ጋር። በአውሮፓ ግንኙነት ጊዜ የሰሜን አሜሪካን ተወላጅ ህዝብ መገመት ከባድ ነው። የስሚዝሶኒያን ተቋም ባልደረባ የሆኑት ዳግላስ ኤች ኡቤላከር በደቡብ አትላንቲክ ግዛቶች 92,916 ህዝብ እና 473,616 ህዝብ በባህረ ሰላጤው ግዛቶች እንዳሉ ይገምታሉ፣ ነገር ግን አብዛኞቹ ምሁራን ይህን አሃዝ በጣም ዝቅተኛ አድርገው ይመለከቱታል። አንትሮፖሎጂስት ሄንሪ ኤፍ ዶቢንስ የህዝቡ ብዛት እንደሆነ ያምኑ ነበር። በሜክሲኮ ባሕረ ሰላጤ ዳርቻ ወደ 1.1 ሚሊዮን አካባቢ፣ 2.2 ሚሊዮን ሰዎች በፍሎሪዳ እና በማሳቹሴትስ መካከል፣ 5.2 ሚሊዮን በሚሲሲፒ ሸለቆ እና ገባር ወንዞች፣ እና በፍሎሪዳ ባሕረ ገብ መሬት ውስጥ ወደ 700,000 የሚጠጉ ሰዎች ይጠቁማሉ። የአውሮፓ ሰፈራዎች በኖርስ የባህር ዳርቻ ኒው ኢንግላንድ ቅኝ ግዛት ቀደም ብሎ የይገባኛል ጥያቄዎች አከራካሪ እና አከራካሪ ናቸው። በ1513 ወደ ፍሎሪዳ የተጓዘው እንደ ሁዋን ፖንሴ ዴ ሊዮን ያሉ የስፔን ድል አድራጊዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የተረጋገጠው አውሮፓውያን ወደ አህጉራዊው ዩናይትድ ስቴትስ መግባታቸው የተረጋገጠ ነው። ቀደም ሲልም ክሪስቶፈር ኮሎምበስ በ1493 ጉዞው በፖርቶ ሪኮ እና ሳን ላይ አርፏል። ጁዋን ከአሥር ዓመት በኋላ በስፔኖች ሰፍሯል። ስፔናውያን በፍሎሪዳ እና በኒው ሜክሲኮ የመጀመሪያዎቹን ሰፈሮች አቋቁመዋል፣ ለምሳሌ እንደ ሴንት አውጉስቲን ፣ ብዙ ጊዜ የሀገሪቱ ጥንታዊ ከተማ እና ሳንታ ፌ። ፈረንሳዮች በሚሲሲፒ ወንዝ አጠገብ የራሳቸውን ሰፈራ መስርተዋል፣ በተለይም ኒው ኦርሊንስ። በሰሜን አሜሪካ ምስራቃዊ የባህር ጠረፍ የተሳካው የእንግሊዝ ሰፈር በቨርጂኒያ ቅኝ ግዛት በ1607 በጄምስታውን እና ከፒልግሪሞች ቅኝ ግዛት በፕሊማውዝ በ1620 ተጀመረ።በአህጉሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጠው የህግ አውጭ ምክር ቤት የቨርጂኒያ የቡርጌሰስ ቤት በ1619 ተመሠረተ።እንደ ሰነዶች ያሉ የሜይፍላወር ኮምፓክት እና የኮነቲከት መሠረታዊ ትዕዛዞች በመላው የአሜሪካ ቅኝ ግዛቶች የሚለሙ ተወካዩ ራስን በራስ ማስተዳደር እና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን አቋቁመዋል። ብዙ የእንግሊዝ ሰፋሪዎች የሀይማኖት ነፃነት ለማግኘት የመጡ ክርስቲያኖችን ይቃወሙ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1784 ሩሲያውያን በአላስካ ፣ በሦስት ቅዱሳን ቤይ ሰፈር ለመመስረት የመጀመሪያዎቹ አውሮፓውያን ነበሩ። ራሽያ አሜሪካ በአንድ ወቅት አብዛኛውን የአላስካ ግዛት ይዛለች። በቅኝ ግዛት ዘመን መጀመሪያ ላይ፣ ብዙ የአውሮፓ ሰፋሪዎች ለምግብ እጥረት፣ ለበሽታ እና በአሜሪካ ተወላጆች ጥቃት ይደርስባቸው ነበር። የአሜሪካ ተወላጆችም ብዙ ጊዜ ከአጎራባች ጎሳዎች እና ከአውሮፓ ሰፋሪዎች ጋር ይዋጉ ነበር። በአብዛኛዎቹ ሁኔታዎች ግን የአገሬው ተወላጆች እና ሰፋሪዎች እርስ በርስ መደጋገፍ ጀመሩ. ሰፋሪዎች ለምግብ እና ለእንስሳት እርባታ ይገበያዩ ነበር; ተወላጆች ለጠመንጃ፣ መሳሪያዎች እና ሌሎች የአውሮፓ እቃዎች። የአገሬው ተወላጆች ብዙ ሰፋሪዎች በቆሎ፣ ባቄላ እና ሌሎች ምግቦችን እንዲያለሙ አስተምረዋል። አውሮፓውያን ሚስዮናውያን እና ሌሎች የአሜሪካ ተወላጆችን "ማሰልጠን" አስፈላጊ እንደሆነ ተሰምቷቸው የአውሮፓን የግብርና ልምዶች እና የአኗኗር ዘይቤዎችን እንዲከተሉ አሳስበዋቸዋል። ነገር ግን፣ በሰሜን አሜሪካ በተስፋፋው የአውሮፓ ቅኝ ግዛት፣ የአሜሪካ ተወላጆች ተፈናቅለው ብዙ ጊዜ ተገድለዋል። የአሜሪካ ተወላጆች አውሮፓውያን ከደረሱ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች ቀንሷል, በዋነኝነት እንደ ፈንጣጣ እና ኩፍኝ ባሉ በሽታዎች. የዩናይትድ ስቴትስ ካርታ በምስራቅ የባህር ዳርቻ ላይ የመጀመሪያዎቹን አስራ ሶስት ቅኝ ግዛቶች ያሳያል የመጀመሪያዎቹ አሥራ ሦስት ቅኝ ግዛቶች (በቀይ የሚታየው) በ1775 ዓ.ም አውሮፓውያን ሰፋሪዎችም የአፍሪካን ባሪያዎች ወደ ቅኝ ግዛት አሜሪካ በትራንስ አትላንቲክ የባሪያ ንግድ ማዘዋወር ጀመሩ።የሐሩር ክልል በሽታዎች ዝቅተኛ ስርጭት እና የተሻለ ህክምና በመኖሩ ባሪያዎች በሰሜን አሜሪካ ከደቡብ አሜሪካ የበለጠ የህይወት ተስፋ ነበራቸው።ይህም ፈጣን እድገት አስከትሏል። ቁጥራቸው. የቅኝ ገዥው ማህበረሰብ በባርነት ሃይማኖታዊ እና ሥነ ምግባራዊ አንድምታዎች ላይ በአብዛኛው የተከፋፈለ ሲሆን በርካታ ቅኝ ግዛቶች ድርጊቱን የሚቃወሙ እና የሚደግፉ ድርጊቶችን ፈጽመዋል። ነገር ግን፣ በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ላይ፣ አፍሪካውያን ባሮች በተለይ በአሜሪካ ደቡብ የሚኖሩ አውሮፓውያን አገልጋዮችን እንደ ጥሬ ገንዘብ ሰብል ተክተው ነበር። አስራ ሶስቱ ቅኝ ግዛቶች (ኒው ሃምፕሻየር፣ ማሳቹሴትስ፣ ኮነቲከት፣ ሮድ አይላንድ፣ ኒው ዮርክ፣ ኒው ጀርሲ፣ ፔንስልቬንያ፣ ዴላዌር፣ ሜሪላንድ፣ ቨርጂኒያ፣ ሰሜን ካሮላይና፣ ደቡብ ካሮላይና እና ጆርጂያ) በእንግሊዞች ይተዳደራሉ እንደ የውጭ አገር ጥገኛዎች. ያም ሆኖ ግን ለአብዛኞቹ ነፃ ሰዎች ምርጫ ክፍት የሆኑ የአካባቢ መንግስታት ነበሯቸው። እጅግ በጣም ከፍተኛ በሆነ የወሊድ መጠን፣ ዝቅተኛ የሞት መጠን እና የተረጋጋ ሰፈራ፣ የቅኝ ገዥው ህዝብ በፍጥነት አደገ፣ የአሜሪካ ተወላጆችን ሸፈነ። የ1730ዎቹ እና 1740ዎቹ የክርስቲያን ተሀድሶ እንቅስቃሴ ታላቁ መነቃቃት በመባል የሚታወቀው በሃይማኖት እና በሃይማኖታዊ ነፃነት ላይ ፍላጎት እንዲጨምር አድርጓል። በሰባት አመታት ጦርነት በአሜሪካ የፈረንሳይ እና የህንድ ጦርነት በመባል በሚታወቀው የብሪታንያ ሃይሎች ካናዳን ከፈረንሳይ ያዙ። የኩቤክ ግዛት ሲፈጠር፣ የካናዳ የፍራንኮፎን ህዝብ ከኖቫ ስኮሺያ፣ ኒውፋውንድላንድ እና አስራ ሶስት ቅኝ ግዛቶች እንግሊዝኛ ተናጋሪ የቅኝ ግዛት ጥገኝነት ተነጥሎ ይቆያል። እዚያ ይኖሩ የነበሩትን የአሜሪካ ተወላጆችን ሳይጨምር፣ አስራ ሶስት ቅኝ ግዛቶች በ1770 ከ2.1 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ነበራቸው፣ ይህም ከብሪታንያ አንድ ሶስተኛው ያህል ነበር። አዲስ መጤዎች ቢቀጥሉም, የተፈጥሮ መጨመር መጠን በ 1770 ዎቹ ጥቂት አሜሪካውያን ወደ ባህር ማዶ የተወለዱት በጣም ትንሽ ነበር. ቅኝ ግዛቶቹ ከብሪታንያ ርቀው ራስን በራስ የማስተዳደር እድገት አስችሏቸዋል፣ ነገር ግን ከዚህ በፊት ታይቶ የማያውቅ ስኬት የብሪታንያ ነገስታት በየጊዜው የንጉሣዊ ሥልጣኑን እንደገና ለማስከበር እንዲሞክሩ አነሳስቷቸዋል። ነፃነት እና መስፋፋት በአስራ ሶስት ቅኝ ግዛቶች ከብሪቲሽ ኢምፓየር ጋር የተዋጋው የአሜሪካ አብዮታዊ ጦርነት አውሮፓዊ ያልሆነ አካል በዘመናዊ ታሪክ ከአውሮፓ ሃይል ጋር የፈፀመው የመጀመሪያው የተሳካ የነጻነት ጦርነት ነው። አሜሪካውያን የ"ሪፐብሊካኒዝም" ርዕዮተ ዓለም አዳብረዋል፣ መንግሥት በሕዝብ ፍላጎት ላይ ያረፈ መሆኑን በአካባቢያቸው የሕግ አውጭ አካላት ላይ አስረግጠው ነበር። “እንደ እንግሊዛዊ መብታቸውን” እና “ያለ ውክልና ግብር አይከፈልም” ሲሉ ጠይቀዋል። እንግሊዞች ግዛቱን በፓርላማ እንዲያስተዳድሩ አጥብቀው ጠየቁ፣ ግጭቱም ወደ ጦርነት ተለወጠ። ሁለተኛው ኮንቲኔንታል ኮንግረስ፣ የተባበሩት ቅኝ ግዛቶችን የሚወክል ጉባኤ፣ የነጻነት መግለጫን ሐምሌ 4 ቀን 1776 በሙሉ ድምፅ አጽድቋል። ይህ ቀን በየዓመቱ የነፃነት ቀን ተብሎ ይከበራል ። እ.ኤ.አ. በ 1777 የኮንፌዴሬሽን አንቀጾች ያልተማከለ መንግሥት እስከ 1789 ድረስ ይሠራ ነበር ። እ.ኤ.አ. በ 1781 በዮርክታውን ከበባ ከተሸነፈች በኋላ ብሪታንያ የሰላም ስምምነት ፈረመች ። የአሜሪካ ሉዓላዊነት በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አገኘ፣ እና ሀገሪቱ ከማሲሲፒ ወንዝ በስተምስራቅ ያሉትን ሁሉንም መሬቶች ተሰጥቷታል። ከብሪታንያ ጋር ያለው ውጥረት ግን ቀረ፣ ወደ እ.ኤ.አ. በ1812 ወደ ጦርነት አመራ፣ እሱም በአቻ ተፋልሟል። ብሔርተኞች በ1787 የፊላዴልፊያ ኮንቬንሽን በመምራት በ1788 በክልላዊ ስምምነቶች የፀደቀውን የዩናይትድ ስቴትስ ሕገ መንግሥት በመጻፍ በ1789 በሥራ ላይ የዋለው ይህ ሕገ መንግሥት የፌደራል መንግሥቱን በሦስት ቅርንጫፎች በአዲስ መልክ አዋቅሮ ሰላምታና ሚዛንን በመፍጠር መርህ ላይ አዘጋጀ። ኮንቲኔንታል ጦርን ለድል ያበቃው ጆርጅ ዋሽንግተን በአዲሱ ሕገ መንግሥት መሠረት የተመረጠ የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት ነበር። የመብቶች ህግ፣ የፌዴራል የግል ነፃነቶችን ገደብ የሚከለክል እና የተለያዩ የህግ ከለላዎችን የሚያረጋግጥ፣ በ1791 ጸድቋል። ወደ ምዕራብ መስፋፋቱን የሚያሳይ የዩኤስ ካርታ በ1783 እና 1917 መካከል የዩናይትድ ስቴትስ ግዛት ግዥዎች ምንም እንኳን የፌደራል መንግስት በ1807 የአሜሪካን በአትላንቲክ የባሪያ ንግድ መሳተፍን ቢከለክልም፣ ከ1820 በኋላ፣ ከፍተኛ ትርፋማ የሆነውን የጥጥ ሰብል ማረስ በጥልቁ ደቡብ ውስጥ ፈነዳ፣ ከሱም ጋር የባሪያው ህዝብ። የሁለተኛው ታላቅ መነቃቃት በተለይም በ1800-1840 ሚሊዮኖችን ወደ ወንጌላዊ ፕሮቴስታንትነት ለወጠ። በሰሜን ውስጥ, አቦሊቲዝምን ጨምሮ በርካታ የማህበራዊ ማሻሻያ እንቅስቃሴዎችን አበረታቷል; በደቡብ፣ ሜቶዲስቶች እና ባፕቲስቶች በባሪያ ህዝቦች መካከል ወደ ክርስትና ተቀየሩ። ከ 18 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ጀምሮ ፣ አሜሪካዊያን ሰፋሪዎች ወደ ምዕራብ መስፋፋት ጀመሩ ፣ ይህም ረጅም ተከታታይ የአሜሪካ ህንድ ጦርነቶችን አስከትሏል ። የ 1803 የሉዊዚያና ግዢ የሀገሪቱን አካባቢ በእጥፍ ጨምሯል ፣ ስፔን በ 1819 ፍሎሪዳ እና ሌሎች የባህረ ሰላጤ የባህር ዳርቻ ግዛቶችን ሰጠች ፣ የቴክሳስ ሪፐብሊክ ተቀላቀለች። እ.ኤ.አ. በ 1845 በመስፋፋት ወቅት እና በ 1846 ከብሪታንያ ጋር የተደረገው የኦሪገን ስምምነት የአሜሪካን የአሜሪካን ሰሜን ምዕራብ እንዲቆጣጠር አደረገ ። በሜክሲኮ-አሜሪካ ጦርነት ድል በ 1848 የካሊፎርኒያ የሜክሲኮ መቋረጥ እና አብዛኛው የአሜሪካ ደቡብ ምዕራብ አሜሪካን አህጉር እንድትሆን አድርጓል። እ.ኤ.አ. እንደ የሐዋርያት ሥራ፣ ከዩናይትድ ስቴትስ አጠቃላይ ስፋት 10% የሚጠጋውን እና ለግል የባቡር ሐዲድ ኩባንያዎች እና ኮሌጆች እንደ የመሬት ዕርዳታ ለነጮች አውሮፓውያን ሰፋሪዎች ሰፊ መጠን ያለው መሬት መሰጠቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን አነሳሳ። ከእርስ በርስ ጦርነት በኋላ፣ አዲስ አህጉር አቋራጭ የባቡር ሀዲዶች ሰፋሪዎችን በቀላሉ ማዛወርን፣ የውስጥ ንግድን ማስፋት እና ከአሜሪካውያን ተወላጆች ጋር ግጭቶችን ጨምሯል። እ.ኤ.አ. በ1869 አዲስ የሰላም ፖሊሲ የአሜሪካ ተወላጆችን ከጥቃት ለመጠበቅ፣ ተጨማሪ ጦርነትን ለማስወገድ እና የመጨረሻውን የአሜሪካ ዜግነታቸውን ለማስጠበቅ ቃል ገብቷል። ቢሆንም፣ መጠነ ሰፊ ግጭቶች በመላው ምዕራብ እስከ 1900ዎቹ ድረስ ቀጥለዋል። የእርስ በርስ ጦርነት እና የመልሶ ግንባታ ጊዜ በአፍሪካውያን እና በአፍሪካ አሜሪካውያን ባርነት ላይ የማይታረቅ የክፍል ግጭት በመጨረሻ ወደ አሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት አመራ። እ.ኤ.አ. በ1860 የሪፐብሊካን አብርሃም ሊንከን ምርጫ በአስራ ሶስት የባሪያ ግዛቶች የተካሄዱት ኮንቬንሽኖች መገንጠልን በማወጅ የአሜሪካ ኮንፌዴሬሽን ግዛቶችን ("ደቡብ" ወይም "ኮንፌዴሬሽን") ሲመሰርቱ የፌደራል መንግስት ("ህብረት") መገንጠል ህገወጥ ነው ሲል ይህንን መገንጠል ለማምጣት ወታደራዊ እርምጃ በተገንጣዮቹ ተጀመረ እና ህብረቱም ምላሽ ሰጠ። የሚቀጥለው ጦርነት በአሜሪካ ታሪክ ውስጥ እጅግ ገዳይ የሆነ ወታደራዊ ግጭት ይሆናል ፣ ይህም ወደ 620,000 የሚጠጉ ወታደሮች እና ከ 50,000 በላይ ንፁሀን ዜጎች ሞት ምክንያት ሆኗል ። ህብረቱ መጀመሪያ ላይ ሀገሪቱን አንድነቷን ለመጠበቅ ተዋግቷል ። ቢሆንም፣ ከ1863 በኋላ የተጎዱት ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ እና ሊንከን የነጻነት አዋጁን ሲያወጣ፣ ከህብረቱ እይታ አንጻር የጦርነቱ ዋና አላማ ባርነትን ማስወገድ ሆነ። በእርግጥ፣ ህብረቱ በኤፕሪል 1865 ጦርነቱን ሲያሸንፍ፣ በተሸነፈው ደቡብ ውስጥ ያሉት እያንዳንዱ ግዛቶች የአስራ ሦስተኛውን ማሻሻያ እንዲያፀድቁ ይጠበቅባቸው ነበር፣ ይህም እንደ ቅጣት ሰራተኛ ካልሆነ በስተቀር ባርነትን ይከለክላል። ሌሎች ሁለት ማሻሻያዎችም ጸድቀዋል፣ የዜግነት እና የጥቁሮችን የመምረጥ መብቶችን ያረጋግጣሉ። ከጦርነቱ በኋላ ተሃድሶው በከፍተኛ ሁኔታ ተጀመረ። ፕሬዘዳንት ሊንከን በህብረቱ እና በቀድሞው ኮንፌዴሬሽን መካከል ወዳጅነትን እና ይቅርታን ለመፍጠር ሲሞክሩ፣ በኤፕሪል 14, 1865 የተገደለው ግድያ በሰሜን እና በደቡብ መካከል እንደገና እንዲፋታ አደረገ። በፌዴራል መንግስት ውስጥ ያሉ ሪፐብሊካኖች የደቡብን መልሶ ግንባታ ለመቆጣጠር እና የአፍሪካ አሜሪካውያንን መብት ለማረጋገጥ ግባቸው አድርገዋል። እ.ኤ.አ. በ1877 በተደረገው ስምምነት ሪፐብሊካኖች በ1876 የተካሄደውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዴሞክራቶች እንዲቀበሉ በደቡብ የሚገኙ የአፍሪካ አሜሪካውያንን መብት መጠበቅ ለማቆም ሲስማሙ ቆይተዋል። የደቡብ ነጮች ዴሞክራቶች፣ ራሳቸውን "ቤዛዊ" ብለው የሚጠሩት፣ ከዳግም ግንባታው ማብቂያ በኋላ፣ የአሜሪካን የዘር ግንኙነት መነሻ በማድረግ ደቡብን ተቆጣጠሩ። ከ1890 እስከ 1910 ድረስ ቤዛዎች የጂም ክሮው ህግ የሚባሉትን አቋቁመዋል፣ ይህም የብዙ ጥቁሮችን እና አንዳንድ ድሆች ነጮችን በመላ ክልሉ ተነጠቁ። ጥቁሮች በአገር አቀፍ ደረጃ በተለይም በደቡብ ውስጥ የዘር መለያየት ያጋጥማቸዋል። ተጨማሪ ኢሚግሬሽን፣ መስፋፋት እና ኢንዱስትሪያላይዜሽን በሰሜን ከከተማ መስፋፋት እና ከደቡብ እና ከምስራቅ አውሮፓ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የፍልሰተኞች ፍልሰት ለአገሪቱ ኢንዳስትሪላይዜሽን ተጨማሪ የሰው ኃይል አቅርቦ ባህሏን ቀይሯል። ብሄራዊ መሠረተ ልማት፣ ቴሌግራፍ እና አህጉር አቋራጭ የባቡር ሀዲዶችን ጨምሮ፣ የኢኮኖሚ እድገትን እና የአሜሪካን ኦልድ ምዕራብ የበለጠ ሰፈራ እና ልማት አነሳስቷል። ከጊዜ በኋላ የኤሌክትሪክ መብራት እና የስልክ ፈጠራ የመገናኛ እና የከተማ ህይወት ላይ ተጽእኖ ይኖረዋል. ዩናይትድ ስቴትስ ከ1810 እስከ 1890 ከሚሲሲፒ ወንዝ በስተ ምዕራብ የሕንድ ጦርነቶችን ተዋግታለች። አብዛኛዎቹ እነዚህ ግጭቶች የተጠናቀቁት የአሜሪካ ተወላጆች ግዛት በማቋረጥ እና በህንድ በተያዙ ቦታዎች ላይ በመታሰሩ ነው። በተጨማሪም፣ በ1830ዎቹ የእምባ መሄጃ መንገድ ህንዶችን በግዳጅ የሰፈረውን የህንድ የማስወገድ ፖሊሲ ምሳሌ ነው። ይህ በሜካኒካል እርሻ ስር የሚገኘውን የአከርክ እርሻን የበለጠ በማስፋፋት ለአለም አቀፍ ገበያዎች ትርፍ ጨምሯል። የሜይንላንድ መስፋፋት በ1867 አላስካን ከሩሲያ መግዛትን ያጠቃልላል። በ1893 በሃዋይ የሚገኙ የአሜሪካ ደጋፊ አካላት የሃዋይን ንጉሳዊ አገዛዝ ገልብጠው የሃዋይ ሪፐብሊክን መሰረቱ፣ በ1898 ዩናይትድ ስቴትስ የተቀላቀለችውን የሃዋይ ሪፐብሊክን መሰረተች። ፖርቶ ሪኮ፣ ጉዋም እና ፊሊፒንስ ተሰጡ። በስፔን በዚያው ዓመት፣ የስፔን-አሜሪካን ጦርነት ተከትሎ። አሜሪካዊው ሳሞአ በ1900 ከሁለተኛው የሳሞአ የእርስ በርስ ጦርነት ማብቂያ በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ ተገዛ። የዩኤስ ቨርጂን ደሴቶች በ1917 ከዴንማርክ ተገዙ። በ19ኛው እና በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት የበርካታ ታዋቂ ኢንደስትሪ ሊቃውንት እድገት አበረታቷል። እንደ ኮርኔሊየስ ቫንደርቢልት፣ ጆን ዲ ሮክፌለር እና አንድሪው ካርኔጊ ያሉ ባለሀብቶች ሀገሪቷን በባቡር ሀዲድ፣ በፔትሮሊየም እና በብረት ኢንዱስትሪዎች እድገት መርተዋል። ባንኪንግ የምጣኔ ሀብት ዋና አካል ሆነ፣ ጄ.ፒ. ሞርጋን ጉልህ ሚና ተጫውቷል። የአሜሪካ ኤኮኖሚ አደገ፣ የዓለማችን ትልቁ ሆነ። እነዚህ አስደናቂ ለውጦች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው ኢ-እኩልነት እና ማህበራዊ አለመረጋጋት የታጀበ ሲሆን ይህም የተደራጀ የሰው ኃይል ከፖፕሊስት፣ ሶሻሊስት እና አናርኪስት እንቅስቃሴዎች ጋር እንዲስፋፋ አድርጓል።ይህ ወቅት በመጨረሻ የፕሮግረሲቭ ዘመን መምጣት ጋር አብቅቷል፣ ይህም የሴቶች ምርጫን፣ አልኮልን ጨምሮ ከፍተኛ ለውጦችን አድርጓል። መከልከል ፣ የፍጆታ ዕቃዎችን መቆጣጠር እና ለሠራተኛ ሁኔታዎች ውድድርን እና ትኩረትን ለማረጋገጥ የበለጠ ፀረ እምነት እርምጃዎች ። አንደኛው የዓለም ጦርነት፣ ታላቅ ጭንቀት፣ እና ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ዩናይትድ ስቴትስ አንደኛው የዓለም ጦርነት ከተቀሰቀሰበት እ.ኤ.አ. በ 1914 እስከ 1917 ድረስ ጦርነቱን ከአንደኛው የዓለም ጦርነት አጋሮች ጋር በመሆን ጦርነቱን በተቀላቀለችበት ጊዜ “ተዛማጅ ኃይል” ሆና በመካከለኛው ኃያላን ላይ ማዕበሉን ለማዞር ስትረዳ ቆይታለች። እ.ኤ.አ. በ1919፣ ፕሬዘደንት ውድሮው ዊልሰን በፓሪስ የሰላም ኮንፈረንስ የመሪነት ዲፕሎማሲያዊ ሚና ነበራቸው እና ዩናይትድ ስቴትስ የመንግስታቱን ሊግ እንድትቀላቀል አጥብቀው ተከራከሩ። ሆኖም ሴኔቱ ይህንን ለማጽደቅ ፈቃደኛ ባለመሆኑ የመንግሥታትን ማኅበር ያቋቋመውን የቬርሳይ ስምምነት አላፀደቀም። እ.ኤ.አ. በ1920 የሴቶች መብት ንቅናቄ የሴቶችን ምርጫ የሚሰጥ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ አሸነፈ። እ.ኤ.አ. በ 1920 ዎቹ እና 1930 ዎቹ ውስጥ የሬዲዮ ስርጭት ለሰፊ ግንኙነት እና ቀደምት ቴሌቪዥን መፈጠር ታየ ። የሮሪንግ ሃያዎቹ ብልጽግና በ 1929 የዎል ስትሪት ግጭት እና በታላቁ ጭንቀት መጀመሪያ አብቅቷል ። እ.ኤ.አ. በ 1932 ፕሬዝዳንት ሆነው ከተመረጡ በኋላ ፍራንክሊን ዲ. ሩዝቬልት በአዲሱ ስምምነት ምላሽ ሰጡ ። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን አሜሪካውያን ከደቡብ አሜሪካ የወጡበት ታላቅ ፍልሰት ከአንደኛው የዓለም ጦርነት በፊት የጀመረው እና በ1960ዎቹ የተራዘመ ነው። እ.ኤ.አ. በ1930ዎቹ አጋማሽ የነበረው የአቧራ ጎድጓዳ ሳህን ብዙ ገበሬዎችን ድህነት ዳርጓል እና አዲስ የምዕራባዊ ፍልሰት ማዕበልን አነሳሳ።በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ዩናይትድ ስቴትስ በማርች 1941 በብድር-ሊዝ መርሃ ግብር አማካኝነት ለተባበሩት መንግስታት ቁሳቁሶችን ማቅረብ ጀመረች። ታኅሣሥ 7 ቀን 1941 የጃፓን ኢምፓየር በፐርል ሃርበር ላይ ድንገተኛ ጥቃት በመሰንዘር ዩናይትድ ስቴትስ ከአክሲስ ኃይሎች ጋር ከተባበሩት መንግሥታት ጋር እንድትቀላቀልና በሚቀጥለው ዓመት ወደ 120,000 የሚጠጉ የዩኤስ ነዋሪዎችን (አሜሪካውያንን ጨምሮ) የጃፓናውያን ነዋሪዎችን ለመለማመድ አነሳሳ። መውረድ። ጃፓን ዩናይትድ ስቴትስን ቀድማ ብታጠቃም፣ ዩኤስ ነገር ግን "የአውሮፓ መጀመሪያ" የመከላከያ ፖሊሲን ተከትላለች።በዚህም ዩናይትድ ስቴትስ ሰፊውን የኤዥያ ቅኝ ግዛት ፊሊፒንስን ገለል አድርጋ ከጃፓን ወረራ እና ወረራ ጋር የተሸነፈችውን ትግል ታግላለች። በጦርነቱ ወቅት ዩናይትድ ስቴትስ ከብሪታንያ፣ ከሶቪየት ኅብረት እና ከቻይና ጋር በመሆን ከጦርነቱ በኋላ ያለውን ዓለም ለማቀድ ከተሰበሰቡት “አራቱ ኃያላን” አንዷ ነበረች። ምንም እንኳን ሀገሪቱ ወደ 400,000 የሚጠጉ ወታደራዊ ሰራተኞችን ቢያጣም ከጦርነቱ የበለጠ ጉዳት ሳይደርስበት በኢኮኖሚ እና በወታደራዊ ተጽእኖ ታየ። ዩናይትድ ስቴትስ በ እና ኮንፈረንሶች ላይ የመሪነት ሚና ተጫውታለች, በአዳዲስ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት እና በአውሮፓ ድህረ-ጦርነት እንደገና ማደራጀት ላይ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል. በአውሮፓ የተባበሩት መንግስታት ድል እንደተጎናጸፈ፣ እ.ኤ.አ. ከዚያም ዩናይትድ ስቴትስ እና ጃፓን በታሪክ ግዙፉ የባህር ኃይል ጦርነት በሆነው በሌይት ባሕረ ሰላጤ ጦርነት ተዋግተዋል። ዩናይትድ ስቴትስ የመጀመሪያውን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ በማዘጋጀት በጃፓን በሄሮሺማ እና ናጋሳኪ ከተሞች በኦገስት 1945 ተጠቀመችባቸው። ሁለተኛው የዓለም ጦርነት አብቅቶ በሴፕቴምበር 2 ጃፓኖች እጅ ሰጡ። ቀዝቃዛ ጦርነት እና በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ዩናይትድ ስቴትስ እና ሶቪየት ኅብረት በካፒታሊዝም እና በኮምኒዝም መካከል በነበረው የርዕዮተ ዓለም ልዩነት ተገፋፍተው የቀዝቃዛው ጦርነት ተብሎ በሚጠራው ጦርነት ለሥልጣን፣ ለተጽዕኖ እና ለክብር ተወዳድረዋል። ዩኤስ እና የኔቶ አጋሮቿ በአንድ በኩል በሶቪየት ህብረት እና በዋርሶ ስምምነት አጋሮቿ በሌላ በኩል የአውሮፓን ወታደራዊ ጉዳዮች ተቆጣጠሩ። ዩኤስ የኮሚኒስት ተጽእኖን ለማስፋፋት የመከላከል ፖሊሲ አዘጋጅታለች። ዩናይትድ ስቴትስ እና ሶቪየት ኅብረት በውክልና ጦርነት ውስጥ ሲሳተፉ እና ኃይለኛ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ሲያዘጋጁ ሁለቱ አገሮች ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭትን አስወገዱ። ዩናይትድ ስቴትስ በሶቪየት ደጋፊነት የምትመለከታቸዉን የሶስተኛው አለም እንቅስቃሴዎችን ትቃወም ነበር እና አልፎ አልፎም በግራ ክንፍ መንግስታት ላይ የአገዛዝ ለዉጥ እንዲደረግ ቀጥተኛ እርምጃ ትወስድ ነበር። የአሜሪካ ወታደሮች እ.ኤ.አ. በ1950-1953 በኮሪያ ጦርነት የኮሚኒስት የቻይና እና የሰሜን ኮሪያ ጦርን ተዋግተዋል። እ.ኤ.አ. በ 1957 የሶቪየት ኅብረት የመጀመሪያውን ሰው ሰራሽ ሳተላይት ወደ አመጠቀችው እና እ.ኤ.አ. በቬትናም ጦርነት ፣ በ1965 የውጊያ ኃይሎችን አስተዋውቋል። በቤት ውስጥ፣ ዩኤስ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ መስፋፋት እና የህዝቡ እና የመካከለኛው መደብ ፈጣን እድገት አጋጥሟታል። የሴቶች የጉልበት ተሳትፎ ከጨመረ በኋላ በተለይም በ1970ዎቹ በ1985 አብዛኞቹ ሴቶች 16 እና ከዚያ በላይ የሆናቸው ሴቶች ተቀጥረው ነበር። የኢንተርስቴት ሀይዌይ ሲስተም ግንባታ በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ውስጥ የሀገሪቱን መሠረተ ልማት ለውጦታል። ሚሊዮኖች ከእርሻ እና ከውስጥ ከተሞች ወደ ትላልቅ የከተማ ዳርቻዎች የመኖሪያ ቤቶች ተንቀሳቅሰዋል። እ.ኤ.አ. በ 1959 ዩናይትድ ስቴትስ በመደበኛነት ከተከታታይ ዩናይትድ ስቴትስ አልፋለች ፣ የአላስካ እና የሃዋይ ግዛቶች በቅደም ተከተል ፣ 49 ኛው እና 50 ኛው ግዛቶች ወደ ህብረት ሲገቡ። እያደገ የመጣው የሲቪል መብቶች ንቅናቄ መለያየትን እና መድልዎን ለመጋፈጥ አል-አመጽ ተጠቅሟል። ኪንግ ጁኒየር ታዋቂ መሪ እና መሪ መሆን። እ.ኤ.አ. በ 1968 በሲቪል መብቶች ህግ ውስጥ የተጠናቀቁ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች እና ህጎች ጥምረት የዘር መድልዎ ለማስቆም ፈለገ ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ፣ የፀረ-ባህል እንቅስቃሴ ጨመረ ፣ ይህም በ ትናም ጦርነት ፣ በጥቁር ኃይል እንቅስቃሴ እና በጾታዊ አብዮት ተቃውሞ የተነሳ። የ"ድህነት ጦርነት" መጀመር የመብቶች እና የበጎ አድራጎት ወጪዎችን አስፋፍቷል፣ ከነዚህም መካከል ሜዲኬር እና ሜዲኬይድ መፍጠር፣ ሁለቱን መርሃ ግብሮች ለአረጋውያን እና ድሆች በቅደም ተከተል የጤና ሽፋን ይሰጣሉ፣ እና በምክንያት የተፈተነ የምግብ ስታምፕ ፕሮግራም እና ለቤተሰቦች ርዳታ ጥገኛ ልጆች. እ.ኤ.አ. በ 1970 ዎቹ እና በ 1980 ዎቹ መጀመሪያ ላይ የ መጀመሪያ ታየ። ዩናይትድ ስቴትስ በዮም ኪፑር ጦርነት ወቅት እስራኤልን ደግፋለች; በምላሹም ሀገሪቱ ከኦፔክ መንግስታት የነዳጅ ማዕቀብ ገጥሟታል፣ ይህም የ1973 የነዳጅ ቀውስ አስከትሏል። ከተመረጡ በኋላ ፕሬዚደንት ሮናልድ ሬጋን ለኢኮኖሚው መቀዛቀዝ በነጻ ገበያ ተኮር ማሻሻያዎች ምላሽ ሰጥተዋል። የዲቴንቴ ውድቀትን ተከትሎ “መያዣን” ትቶ ወደ ሶቪየት ዩኒየን የበለጠ ጨካኝ የሆነውን “የመመለሻ” ስትራቴጂን አነሳ። እ.ኤ.አ. በ1980ዎቹ መገባደጃ ላይ ከሶቪየት ኅብረት ጋር በነበረው ግንኙነት “ቀለጥን” አመጣ እና በ1991 መውደቅ በመጨረሻ የቀዝቃዛ ጦርነትን አቆመ። . ይህ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የዓለም የበላይ ኃያላን እንደመሆኗ አለመወዳደር አመጣ። ከቀዝቃዛው ጦርነት በኋላ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት በ1990 ኢራቅ የዩናይትድ ስቴትስ አጋር የሆነችውን ኩዌትን በወረረችበት ወቅት ቀውስ አስከትሏል። አለመረጋጋት እንዳይስፋፋ በመፍራት በነሀሴ ወር ፕሬዝዳንት ጆርጅ ኤች.ደብሊው ቡሽ በኢራቅ ላይ የባህረ ሰላጤውን ጦርነት ከፍተው መርተውታል። እ.ኤ.አ. እስከ የካቲት 1991 ድረስ ከ34 ሀገራት በተውጣጡ ጥምር ሃይሎች ሲካሄድ የነበረው የኢራቅ ጦር ከኩዌት በማባረር እና የንጉሳዊ ስርዓቱን ወደ ነበረበት በመመለስ አበቃ። በዩኤስ ወታደራዊ መከላከያ አውታሮች ውስጥ የመነጨው በይነመረብ ወደ አለም አቀፍ የትምህርት መድረኮች ከዚያም በ1990ዎቹ ወደ ህዝብ ተሰራጭቶ በአለም ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና ባህል ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል። በዶት ኮም ቡም ፣ የተረጋጋ የገንዘብ ፖሊሲ ​​እና የማህበራዊ ደህንነትን ቀንሷል። እ.ኤ.አ. በ 1990 ዎቹ ውስጥ በዘመናዊው የአሜሪካ ታሪክ ውስጥ ረጅሙ ኢኮኖሚያዊ መስፋፋት ታይቷል ። ከ 1994 ጀምሮ ዩኤስ የሰሜን አሜሪካን የነፃ ንግድ ስምምነት () ተፈራረመ ፣ ይህም በአሜሪካ ፣ በካናዳ እና በሜክሲኮ መካከል የንግድ ልውውጥ እንዲጨምር አድርጓል ። 21 ኛው ክፍለ ዘመን በሴፕቴምበር 11, 2001 የአልቃይዳ አሸባሪ ጠላፊዎች የመንገደኞች አውሮፕላኖችን በኒውዮርክ ከተማ ወደሚገኘው የአለም ንግድ ማእከል እና በዋሽንግተን ዲሲ አቅራቢያ በሚገኘው ፔንታጎን በመብረር ወደ 3,000 የሚጠጉ ሰዎችን ገድለዋል። በኋላ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ከጥቃቶቹ ጋር በተያያዙ ህመሞች ሞተዋል፣ እና ምናልባትም በሺዎች የሚቆጠሩ የመጀመሪያ ምላሽ ሰጭዎች፣ የጽዳት ሰራተኞች እና የተረፉ ሰዎች በረጅም ጊዜ ተፅእኖዎች ይሰቃያሉ። በምላሹም ፕሬዝዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽ ከ2001 እስከ 2021 በአፍጋኒስታን ለ20 ዓመታት የሚጠጋ ጦርነት እና የ2003-2011 የኢራቅ ጦርነትን ጨምሮ በሽብር ላይ ጦርነት ከፍተዋል። . ተመጣጣኝ ቤቶችን ለማራመድ የተነደፈው የመንግስት ፖሊሲ፣ በድርጅታዊ እና የቁጥጥር አስተዳደር ውስጥ የተንሰራፋ ውድቀቶች እና በፌዴራል ሪዘርቭ የተቀመጡት በታሪካዊ ዝቅተኛ የወለድ ተመኖች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የመኖሪያ ቤት አረፋ በ 2006 አምርቶ ነበር ፣ ይህም በ 2007-2008 የፋይናንስ ቀውስ እና ታላቁ የኢኮኖሚ ድቀት ከታላቁ የኢኮኖሚ ድቀት በኋላ በሀገሪቱ ትልቁ የኢኮኖሚ ውድቀት። በችግር ጊዜ በአሜሪካውያን የተያዙ ንብረቶች ዋጋቸውን አንድ አራተኛ ያህል አጥተዋል። የመጀመሪያው የብዝሃ ዘር ፕሬዝዳንት የሆኑት ባራክ ኦባማ የአፍሪካ-አሜሪካዊ የዘር ግንድ ያላቸው በ2008 በችግር ጊዜ ተመርጠዋል እና በመቀጠልም የአሜሪካን የማገገም እና መልሶ ኢንቨስትመንት የ2009 የኢኮኖሚ ማነቃቂያ ህግን እና የዶድ-ፍራንክ ዎል ስትሪት ማሻሻያ እና የሸማቾች ጥበቃ ህግን በመከላከል አሉታዊ ውጤቶቹ እና ቀውሱ እንደገና እንደማይከሰት ያረጋግጣል። 48ቱ ተቀራራቢ ግዛቶች እና የኮሎምቢያ ዲስትሪክት 3,119,885 ስኩዌር ማይል (8,080,470 ኪ.ሜ.) ጥምር ቦታን ይይዛሉ። ከዚህ አካባቢ 2,959,064 ስኩዌር ማይል (7,663,940 ኪ.ሜ.2) የሚጣረስ መሬት ነው፣ ከጠቅላላው የአሜሪካ የመሬት ስፋት 83.65% ያቀፈ ነው። ከሰሜን አሜሪካ በስተደቡብ ምዕራብ በመካከለኛው ፓስፊክ ውስጥ የሚገኘውን ደሴት የምትይዘው ሃዋይ በአከባቢው 10,931 ስኩዌር ማይል (28,311 ኪ.ሜ.2) ነው። አምስቱ ህዝብ የሚኖርባቸው ግን ያልተቀላቀሉት የፖርቶ ሪኮ ፣ የአሜሪካ ሳሞአ ፣ ጉዋም ፣ ሰሜናዊ ማሪያና ደሴቶች እና የአሜሪካ ቨርጂን ደሴቶች በአንድ ላይ 9,185 ካሬ ማይል (23,789 ኪ.ሜ.) ይሸፍናሉ። በመሬት ስፋት ብቻ ሲለካ ዩናይትድ ስቴትስ ከሩሲያ እና ከቻይና በመቀጠል በሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፤ ከካናዳ ጥቂት ቀደም ብሎ። ዩናይትድ ስቴትስ በጠቅላላ በቦታ (በመሬት እና በውሃ) ከአለም ሶስተኛዋ ወይም አራተኛዋ ሀገር ነች፣ ከሩሲያ እና ካናዳ ቀጥላ እና ከቻይና ጋር እኩል ነች። የደረጃ አሰጣጡ በቻይና እና በህንድ የተከራከሩ ሁለት ግዛቶች እንዴት እንደሚቆጠሩ እና የዩናይትድ ስቴትስ አጠቃላይ መጠን እንዴት እንደሚለካ ይለያያል። የአትላንቲክ ውቅያኖስ የባህር ዳርቻ ሜዳ ለገደል ደኖች እና ለፒዬድሞንት ተንከባላይ ኮረብታ የበለጠ ወደ መሀል ሀገር ይሰጣል። የአፓላቺያን ተራሮች የምስራቃዊውን የባህር ዳርቻ ከታላላቅ ሀይቆች እና ከመካከለኛው ምዕራብ የሳር ምድር ይከፋፍሏቸዋል። ሚሲሲፒ–ሚሶሪ ወንዝ፣ በአለም አራተኛው ረጅሙ የወንዞች ስርዓት፣ በዋነኛነት ከሰሜን እስከ ደቡብ በሀገሪቱ እምብርት በኩል ይሰራል። የታላቁ ሜዳ ጠፍጣፋ ለም መሬት ወደ ምዕራብ ይዘልቃል፣ በደቡብ ምስራቅ በደጋ ክልል ተቋርጧል። በሰሜን አሪዞና የሚገኘው ግራንድ ካንየን ከታላቁ ሜዳ በስተ ምዕራብ የሚገኙት የሮኪ ተራሮች በኮሎራዶ ውስጥ 14,000 ጫማ (4,300 ሜትር) ከፍታ ላይ የሚገኙት በመላ አገሪቱ ከሰሜን እስከ ደቡብ ይዘልቃሉ። በስተ ምዕራብ ራቅ ያሉ ዓለታማ ታላቁ ተፋሰስ እና እንደ ቺዋዋ እና ሞጃቭ ያሉ በረሃዎች አሉ። የሴራ ኔቫዳ እና ካስኬድ የተራራ ሰንሰለቶች ወደ ፓሲፊክ የባህር ዳርቻ ቅርብ ናቸው፣ ሁለቱም ክልሎች ከ14,000 ጫማ (4,300 ሜትር) በላይ ከፍታ ላይ ይደርሳሉ። በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ዝቅተኛው እና ከፍተኛው ነጥቦች በካሊፎርኒያ ግዛት ውስጥ ይገኛሉ፣እና በ84 ማይል (135 ኪሜ) ልዩነት። በ20,310 ጫማ (6,190.5 ሜትር) ከፍታ ላይ፣ የአላስካ ዴናሊ በሀገሪቱ እና በሰሜን አሜሪካ ከፍተኛው ጫፍ ነው። ንቁ እሳተ ገሞራዎች በአላስካ አሌክሳንደር እና አሌውቲያን ደሴቶች የተለመዱ ናቸው፣ እና ሃዋይ የእሳተ ገሞራ ደሴቶችን ያቀፈ ነው። በሮኪዎች ውስጥ የሚገኘው የሎውስቶን ብሔራዊ ፓርክ የአህጉሪቱ ትልቁ የእሳተ ገሞራ ባህሪ ነው። ትልቅ መጠን ያለው እና ጂኦግራፊያዊ ዝርያ ያላት ዩናይትድ ስቴትስ አብዛኛዎቹን የአየር ንብረት ዓይነቶች ያካትታል። ከ100ኛው ሜሪዲያን በስተምስራቅ የአየር ሁኔታው ​​​​ከሰሜን እርጥበት አዘል አህጉር እስከ ደቡብ ሞቃታማ የአየር ጠባይ ይደርሳል። ከ100ኛው ሜሪድያን በስተ ምዕራብ ያሉት ታላቁ ሜዳዎች ከፊል-ደረቅ ናቸው። አብዛኛው የምዕራባውያን ተራሮች የአልፕስ አየር ንብረት አላቸው። የአየር ንብረቱ በታላቁ ተፋሰስ፣ በደቡብ ምዕራብ በረሃ፣ በሜዲትራኒያን በባህር ዳርቻ በካሊፎርኒያ፣ እና በውቅያኖስ ዳርቻ በኦሪገን እና በዋሽንግተን እና በደቡባዊ አላስካ ውስጥ ደረቅ ነው። አብዛኛው አላስካ ንዑስ ክፍል ወይም ዋልታ ነው። ሃዋይ እና የፍሎሪዳ ደቡባዊ ጫፍ ሞቃታማ ናቸው, እንዲሁም በካሪቢያን እና በፓስፊክ ውቅያኖስ ውስጥ ያሉ ግዛቶች. ከሜክሲኮ ባሕረ ሰላጤ ጋር የሚዋሰኑ አገሮች ለአውሎ ንፋስ የተጋለጡ ናቸው፣ እና አብዛኛው የአለም አውሎ ነፋሶች በአገሪቱ ውስጥ በተለይም በቶርናዶ አሌይ አካባቢዎች በመካከለኛው ምዕራብ እና በደቡብ ውስጥ ይከሰታሉ። በአጠቃላይ ዩናይትድ ስቴትስ ከማንኛውም ሀገር የበለጠ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ የአየር ሁኔታ ሁኔታዎችን ትቀበላለች። በዚህ አለም. ብዝሃ ህይወት ዩኤስ ከፍተኛ መጠን ያላቸው ሥር የሰደዱ ዝርያዎች ከያዙ 17 ሜጋዳይቨርሲቲ አገሮች አንዷ ነች፡ 17,000 የሚያህሉ የደም ሥር እፅዋት ዝርያዎች በተባበሩት ዩናይትድ ስቴትስ እና አላስካ ውስጥ ይከሰታሉ፣ እና ከ1,800 በላይ የአበባ እፅዋት ዝርያዎች በሃዋይ ይገኛሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ ጥቂቶቹ በ .ዩናይትድ ስቴትስ 428 አጥቢ እንስሳት ዝርያዎች, 784 የአእዋፍ ዝርያዎች, 311 የሚሳቡ ዝርያዎች እና 295 አምፊቢያን ዝርያዎች እንዲሁም 91,000 የሚጠጉ የነፍሳት ዝርያዎች ይገኛሉ. በብሔራዊ ፓርክ አገልግሎት የሚተዳደሩ 63 ብሔራዊ ፓርኮች እና በመቶዎች የሚቆጠሩ በፌዴራል የሚተዳደሩ ፓርኮች፣ ደኖች እና ምድረ በዳ አካባቢዎች አሉ። በአጠቃላይ መንግስት ከሀገሪቱ የመሬት ስፋት 28% ያህሉን ይይዛል፣ በተለይም በምእራብ ግዛቶች። አብዛኛው ይህ መሬት የተጠበቀ ነው፣ ምንም እንኳን አንዳንዶቹ ለዘይት እና ጋዝ ቁፋሮ፣ ማዕድን ማውጣት፣ ሎጊ ወይም የከብት እርባታ ቢከራዩም .86% ገደማ ለውትድርና አገልግሎት ይውላል። የአካባቢ ጉዳዮች በነዳጅ እና በኒውክሌር ኢነርጂ ላይ ክርክር ፣ የአየር እና የውሃ ብክለትን ፣ የዱር እንስሳትን ለመጠበቅ ኢኮኖሚያዊ ወጪዎች ፣ የደን ጭፍጨፋ እና የአየር ንብረት ለውጥን ያካትታሉ ። በጣም ታዋቂው የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ በፕሬዝዳንት ትእዛዝ የተፈጠረው የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ () ነው። እ.ኤ.አ. በ 1970. የምድረ በዳ ሀሳብ ከ 1964 ጀምሮ የህዝብ መሬቶችን አስተዳደር በበረሃ ህግ ፣ 1973 የመጥፋት አደጋ ላይ ያሉ ዝርያዎችን እና በዩናይትድ ስቴትስ የአሳ እና የዱር አራዊት ቁጥጥር ስር ያሉትን መኖሪያዎቻቸውን ለመጠበቅ የታሰበ ነው ። አገልግሎት. ዩናይትድ ስቴትስ በአካባቢ አፈጻጸም መረጃ ጠቋሚ ውስጥ ከሀገሮች 24ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ሀገሪቱ በ2016 የአየር ንብረት ለውጥ የፓሪስ ስምምነትን የተቀላቀለች ሲሆን ሌሎች በርካታ የአካባቢ ጥበቃ ቁርጠኝነትም አላት። በ2020 የፓሪስ ስምምነትን ትቶ በ2021 እንደገና ተቀላቅሏል። ዩናይትድ ስቴትስ የ 50 ግዛቶች ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ነው, የፌደራል አውራጃ, አምስት ግዛቶች እና በርካታ ሰው አልባ የደሴቶች ንብረቶች. በዓለም ላይ እጅግ ጥንታዊ የሆነው ፌዴሬሽን ነው። ፌደራላዊ ሪፐብሊክ እና ተወካይ ዲሞክራሲ ነው "በህግ በተጠበቁ አናሳ መብቶች የአብላጫዎቹ አገዛዝ የሚናደድበት"። እ.ኤ.አ. በ 2021 ዩኤስ በዲሞክራሲ መረጃ ጠቋሚ 26 ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ፣ እናም “የተበላሸ ዴሞክራሲ” ተብሎ ተገልጿል ። በትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የ2019 የሙስና አመለካከቶች መረጃ ጠቋሚ፣ የመንግስት ሴክተር ደረጃው በ2015 ከነበረበት 76 ነጥብ በ2019 ወደ 69 ዝቅ ብሏል። በአሜሪካ ፌደራሊዝም ስርዓት ዜጎች በአብዛኛው በሶስት የመንግስት እርከኖች ተገዢ ናቸው፡ ፌዴራል፣ ክልል እና አካባቢያዊ። የአካባቢ አስተዳደር ተግባራት በተለምዶ በካውንቲ እና በማዘጋጃ ቤት መካከል የተከፋፈሉ ናቸው። በሁሉም ጉዳዮች ላይ ከሞላ ጎደል አስፈፃሚ እና ህግ አውጭ ባለስልጣኖች የሚመረጡት በዲስትሪክት በዜጎች የብዙሃነት ድምጽ ነው። መንግሥት የሚቆጣጠረው በዩኤስ ሕገ መንግሥት በተገለጸው የፍተሻና ሚዛን ሥርዓት የአገሪቱ የሕግ ሰነድ ሆኖ ያገለግላል።ሕገ መንግሥቱ የፌዴራል መንግሥቱን አወቃቀሮችና ኃላፊነቶች እንዲሁም ከግል ክልሎች ጋር ያለውን ግንኙነት ያዘጋጃል። አንቀጽ አንድ የ ኮርፐስ ጽሑፍ የማግኘት መብትን ይከላከላል። ሕገ መንግሥቱ 27 ጊዜ ተሻሽሏል፣ የመጀመሪያዎቹ አሥር ማሻሻያዎች፣ የመብቶች ቢል የሚያካትቱት፣ እና አሥራ አራተኛው ማሻሻያ የአሜሪካውያን የግለሰብ መብቶች ማዕከላዊ መሠረት ናቸው። ሁሉም ህጎች እና የመንግስት አካሄዶች ለፍርድ ይመለከታሉ እና ፍርድ ቤቶች ህገ መንግስቱን የሚጥስ ነው ብለው ከወሰኑ ማንኛውም ህግ ውድቅ ሊሆን ይችላል. የዳኝነት ግምገማ መርህ፣ በህገ መንግስቱ ውስጥ በግልፅ ያልተጠቀሰ፣ በጠቅላይ ፍርድ ቤት በማርበሪ . ማዲሰን በዋና ዳኛ ጆን ማርሻል በተሰጠው ውሳኔ የተመሰረተ ነው። የፌዴራል መንግሥት ሦስት ቅርንጫፎችን ያቀፈ ነው- ህግ አውጪ፡ በሴኔቱ እና በተወካዮች ምክር ቤት የተዋቀረው የሁለት ምክር ቤት የፌደራል ህግ ያወጣ፣ ጦርነት አውጀዋል፣ ስምምነቶችን ያፀድቃል፣ የኪስ ቦርሳው ስልጣን ያለው እና የመከሰስ ስልጣን ያለው ሲሆን በዚህም የተቀመጡ አባላትን ያስወግዳል። መንግስት. ሥራ አስፈፃሚ፡ ፕሬዝዳንቱ የወታደሩ ዋና አዛዥ ነው፣ የሕግ አውጪ ሂሳቦች ሕግ ከመውጣታቸው በፊት (በኮንግረሱ መሻር ምክንያት) እና የካቢኔ አባላትን (የሴኔትን ፈቃድ በማግኘት) እና ሌሎች ባለሥልጣናትን ይሾማል፣ የፌዴራል ህጎችን እና ፖሊሲዎችን ማስፈጸም። ዳኝነት፡- የጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የስር ፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞቻቸው በሴኔት ይሁንታ በፕሬዝዳንት የሚሾሙ ህግጋትን ተርጉመው ሕገ መንግሥታዊ ናቸው ያሏቸውን ይሽራሉ። የተወካዮች ምክር ቤት 435 ድምጽ ሰጪ አባላት ያሉት ሲሆን እያንዳንዳቸው የሁለት ዓመት የስራ ዘመን የኮንግረስ ወረዳን ይወክላሉ። የቤት መቀመጫዎች በሕዝብ ብዛት ከክልሎች የተከፋፈሉ ናቸው። እያንዳንዱ ክልል ከቆጠራው ክፍፍል ጋር ለመስማማት ነጠላ አባል የሆኑ ወረዳዎችን ይስላል። የዲስትሪክት ኦፍ ኮሎምቢያ እና አምስቱ ዋና ዋና የአሜሪካ ግዛቶች እያንዳንዳቸው አንድ የኮንግረስ አባል አላቸው - እነዚህ አባላት ድምጽ እንዲሰጡ አይፈቀድላቸውም። ሴኔቱ 100 አባላት ያሉት ሲሆን እያንዳንዱ ግዛት ሁለት ሴናተሮች አሉት ፣ ከትልቅ እስከ ስድስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተመርጠዋል ። በየሁለት ዓመቱ አንድ ሶስተኛ የሴኔት መቀመጫዎች ለምርጫ ይቀርባሉ. የኮሎምቢያ ዲስትሪክት እና አምስቱ ዋና ዋና የአሜሪካ ግዛቶች ሴናተሮች የላቸውም።ፕሬዚዳንቱ ለአራት ዓመታት ያገለግላሉ እና ለቢሮው ከሁለት ጊዜ በላይ ሊመረጡ ይችላሉ። ፕሬዚዳንቱ የሚመረጡት በቀጥታ ድምጽ ሳይሆን በተዘዋዋሪ የምርጫ ኮሌጅ ስርዓት ሲሆን ይህም ድምፅ የሚወስኑት ለክልሎች እና ለዲስትሪክት ኦፍ ኮሎምቢያ የሚከፋፈሉበት ነው። በዩናይትድ ስቴትስ ዋና ዳኛ የሚመራው ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዘጠኝ አባላት አሉት። ለሕይወት የሚያገለግሉ. የፖለቲካ ክፍሎች ዋና መጣጥፎች፡ የዩናይትድ ስቴትስ የፖለቲካ ክፍሎች፣ የአሜሪካ ግዛት፣ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች፣ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች እና ግዛቶች ዝርዝር እና የህንድ ቦታ ማስያዝ ተጨማሪ መረጃ፡ የዩናይትድ ስቴትስ የግዛት ዝግመተ ለውጥ መግለጫውን ይመልከቱ የዩናይትድ ስቴትስ ካርታ 50ቱን ግዛቶች፣ የኮሎምቢያ ዲስትሪክት እና አምስቱን ዋና ዋና የአሜሪካ ግዛቶች ያሳያል። 50ዎቹ ክልሎች በሀገሪቱ ውስጥ ዋና የፖለቲካ ክፍፍሎች ናቸው። እያንዳንዱ ክልል ከፌዴራል መንግስት ጋር ሉዓላዊነት በሚጋራበት በተወሰነ መልክዓ ምድራዊ ግዛት ላይ የዳኝነት ስልጣን አለው። እነሱ በካውንቲዎች ወይም በካውንቲ አቻዎች የተከፋፈሉ እና ተጨማሪ ወደ ማዘጋጃ ቤቶች ይከፋፈላሉ. የኮሎምቢያ ዲስትሪክት የዩናይትድ ስቴትስ ዋና ከተማ የሆነችውን የዋሽንግተን ከተማን የያዘ የፌደራል ዲስትሪክት ነው። ግዛቶች እና የኮሎምቢያ ዲስትሪክት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንትን ይመርጣሉ። እያንዳንዱ ግዛት በኮንግሬስ ውስጥ ካሉት ተወካዮቻቸው እና ሴናተሮች ብዛት ጋር እኩል የሆነ ፕሬዚዳንታዊ መራጮች አሉት። የኮሎምቢያ ዲስትሪክት በ 23 ኛው ማሻሻያ ምክንያት ሶስት አለው. እንደ ፖርቶ ሪኮ ያሉ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች ፕሬዝዳንታዊ መራጮች የላቸውም, እና በእነዚያ ግዛቶች ውስጥ ያሉ ሰዎች ለፕሬዝዳንት ድምጽ መስጠት አይችሉም.ዩናይትድ ስቴትስ እንዲሁ ከግዛቶች ሉዓላዊነት ጋር እንደሚደረገው ሁሉ የአሜሪካ ተወላጆች አሜሪካዊ ብሔረሰቦችን የጎሳ ሉዓላዊነት በተወሰነ ደረጃ ትመለከታለች። የአሜሪካ ተወላጆች የዩኤስ ዜጎች ናቸው እና የጎሳ መሬቶች በዩኤስ ኮንግረስ እና በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሥልጣን ተገዢ ናቸው. እንደ ክልሎች ትልቅ የራስ ገዝ አስተዳደር አላቸው፣ ነገር ግን እንደ ክልሎች ጎሳዎች ጦርነት እንዳይፈጥሩ፣ የራሳቸው የውጭ ግንኙነት እንዲያደርጉ፣ ገንዘብ ማተም እና ማውጣት አይፈቀድላቸውም። ምንም እንኳን 12 የተያዙ ቦታዎች የግዛት ድንበሮችን የሚያቋርጡ ቢሆንም አብዛኛውን ጊዜ የተያዙ ቦታዎች የአንድ ግዛት አካል ናቸው።የህንድ ሀገር በሲቪል እና በወንጀል ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ስልጣን በጎሳዎች፣ ክልሎች እና በፌደራል መንግስት የተጋራ ነው። ዜግነት ሲወለድ በሁሉም ግዛቶች፣ በዲስትሪክት ኦፍ ኮሎምቢያ እና ከአሜሪካ ሳሞአ በስተቀር በሁሉም ዋና ዋና የአሜሪካ ግዛቶች ይሰጣል። በህገ መንግስቱ መሰረት ትንሽ ተጨማሪ ሉዓላዊ ስልጣን በተሰጠው የአሜሪካ ተወላጅ ምክንያት አሁንም ለፍርድ የሚቀርቡበት ምክንያት አይደሉም። ፓርቲዎች እና ምርጫዎች ዩናይትድ ስቴትስ ለአብዛኛው ታሪኳ በሁለት ፓርቲ ሥርዓት ስትንቀሳቀስ ቆይታለች። በአብዛኛዎቹ ደረጃዎች ላሉ ተመራጭ ቢሮዎች፣ በመንግስት የሚተዳደረው የመጀመሪያ ደረጃ ምርጫዎች ለቀጣይ አጠቃላይ ምርጫ ዋና ዋና የፓርቲ እጩዎችን ይመርጣሉ። እ.ኤ.አ. ከ1856 አጠቃላይ ምርጫ ጀምሮ ዋና ዋናዎቹ ፓርቲዎች በ1824 የተመሰረተው ዴሞክራቲክ ፓርቲ እና በ1854 የተመሰረተው የሪፐብሊካን ፓርቲ ፓርቲ ናቸው። የእርስ በርስ ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ አንድ የሶስተኛ ወገን ፕሬዝዳንታዊ እጩ ብቻ - የቀድሞ ፕሬዚዳንት ቴዎዶር ሩዝቬልት እንደ አንድ ምርጫ ይወዳደሩ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1912 ተራማጅ - ከሕዝብ ድምጽ 20% ያህል አሸንፏል ፣ ምንም እንኳን በራስ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገው የሮስ ፔሮት የተሃድሶ ፓርቲ ዘመቻ በ 1992 18.9% ወስዷል። ፕሬዚዳንቱ እና ምክትል ፕሬዚዳንቱ በምርጫ ኮሌጅ ተመርጠዋል። በአሜሪካ የፖለቲካ ባህል የመሀል ቀኝ የሪፐብሊካን ፓርቲ “ወግ አጥባቂ”፣ የማዕከላዊ ግራው ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ደግሞ “ሊበራል” ነው የሚባለው። የሰሜን ምስራቅ እና የምእራብ ጠረፍ ግዛቶች እና አንዳንድ የታላላቅ ሀይቆች ግዛቶች፣ "ሰማያዊ ግዛቶች" በመባል የሚታወቁት በአንጻራዊ ሁኔታ ሊበራል ናቸው። የደቡብ "ቀይ ግዛቶች" እና የታላቁ ሜዳ እና የሮኪ ተራሮች ክፍሎች በአንጻራዊነት ወግ አጥባቂዎች ናቸው። የ2020 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊ እና የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ዴሞክራቱ ጆ ባይደን 46ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ። በሴኔት ውስጥ ያለው አመራር ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስን፣ ፕሬዘዳንት ፕሮቴም ፓትሪክ ሌሂን፣ የአብላጫውን መሪ ቹክ ሹመርን እና አናሳ መሪ ሚች ማክኮንን ያጠቃልላል። በምክር ቤቱ ውስጥ ያለው አመራር የምክር ቤቱ አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ፣ የአብላጫ ድምጽ መሪ ስቴኒ ሆየር እና አናሳ መሪ ኬቨን ማካርቲን ያጠቃልላል። በ117ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኮንግረስ የተወካዮች ምክር ቤት እና ሴኔት በዲሞክራቲክ ፓርቲ ጠባብ ቁጥጥር ስር ናቸው። ሴኔቱ 50 ሪፐብሊካኖች እና 48 ዲሞክራቶች ከዲሞክራትስ ጋር በመተባበር ከዲሞክራቶች ጋር ግንኙነት ያላቸው ምክትል ፕሬዚደንት ሃሪስ ግንኙነታቸውን ማፍረስ የሚችሉ ሁለት ገለልተኛ አባላትን ያቀፈ ነው። ምክር ቤቱ 222 ዴሞክራቶች እና 211 ሪፐብሊካኖች አሉት።የክልሉ ገዥዎች 27 ሪፐብሊካኖች እና 23 ዴሞክራቶች አሉ። ከዲሲ ከንቲባ እና ከአምስቱ የክልል ገዥዎች መካከል ሶስት ዴሞክራቶች፣ አንድ ሪፐብሊካን እና አንድ አዲስ ፕሮግረሲቭ አሉ። የውጭ ግንኙነት ዩናይትድ ስቴትስ የተቋቋመ የውጭ ግንኙነት መዋቅር አላት። የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባል ነው, እና ኒው ዮርክ ከተማ የተባበሩት መንግስታት ዋና መሥሪያ ቤት ነው. እንዲሁም የ7፣ 20 እና አባል ነው። ሁሉም አገሮች ማለት ይቻላል በዋሽንግተን ዲ.ሲ ኤምባሲዎች አሏቸው፣ እና ብዙዎቹ በሀገሪቱ ዙሪያ ቆንስላ አላቸው። እንደዚሁም፣ ሁሉም ማለት ይቻላል የአሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖችን ያስተናግዳሉ። ይሁን እንጂ ኢራን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ቡታን እና ታይዋን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር መደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የላቸውም (ምንም እንኳን ዩኤስ ከታይዋን ጋር ይፋዊ ያልሆነ ግንኙነት ቢኖራትም እና ወታደራዊ መሣሪያዎችን የምታቀርብ ቢሆንም)። ዩናይትድ ስቴትስ ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር "ልዩ ግንኙነት" እና ከካናዳ, አውስትራሊያ, ኒውዚላንድ, ፊሊፒንስ, ጃፓን, ደቡብ ኮሪያ, እስራኤል እና ፈረንሳይ, ጣሊያን, ጀርመን, ስፔን እና ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ህብረት አገሮች ጋር ጠንካራ ግንኙነት አላት. ፖላንድ ከኔቶ አባላት ጋር በወታደራዊ እና በደህንነት ጉዳዮች እና ከጎረቤቶቿ ጋር በአሜሪካ መንግስታት ድርጅት እና በነጻ ንግድ ስምምነቶች እንደ የዩናይትድ ስቴትስ-ሜክሲኮ-ካናዳ የሶስትዮሽ ስምምነት በቅርበት ይሰራል። ኮሎምቢያ በተለምዶ በዩናይትድ ስቴትስ በደቡብ አሜሪካ ውስጥ በጣም ታማኝ አጋር እንደሆነች ትቆጠራለች። ዩኤስ ሙሉ አለምአቀፍ የመከላከያ ስልጣንን እና ለማክሮኔዥያ፣ ማርሻል ደሴቶች እና ፓላው በኮምፓክት ኦፍ ፍሪ ማህበር በኩል ሀላፊነት ትሰራለች። የመንግስት ፋይናንስ ይህ መጣጥፍ በአጠቃላይ እና ይህ የንዑስ ክፍል ክፍል የአውሮፓውያንን የቀን አቆጣጠር ከአቅም በላይ የያዘ በመሆኑ ከኢትዮጵያ አቆጣጠር ጋር መምታታት የለበትም። በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ያለው ግብር በሂደት ላይ ያለ ነው፣ እና በፌዴራል፣ በክልል እና በአከባቢ መስተዳድር ደረጃዎች የሚከፈል ነው። ይህም በገቢ፣ በደመወዝ ክፍያ፣ በንብረት፣ በሽያጭ፣ ወደ አገር ውስጥ በማስገባት፣ በንብረት ላይ እና በስጦታ ላይ የሚደረጉ ታክሶችን እንዲሁም የተለያዩ ክፍያዎችን ይጨምራል። በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ያለው ግብር በዜግነት ላይ የተመሰረተ እንጂ በነዋሪነት አይደለም. ሁለቱም ነዋሪ ያልሆኑ ዜጐችም ሆኑ ግሪን ካርድ የያዙ የውጭ ሀገር ዜጎች በሚኖሩበት ቦታ ወይም ገቢያቸው ምንም ይሁን ምን በገቢያቸው ላይ ቀረጥ ይጣልባቸዋል። ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም ላይ ካሉ ጥቂት አገሮች አንዷ ነች። እ.ኤ.አ. በ 2010 በፌዴራል ፣ በክልል እና በማዘጋጃ ቤት የተሰበሰቡ ታክሶች ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ውስጥ 24.8% ነበሩ። ለ 2018፣ ለሀብታሞች 400 አባወራዎች ውጤታማ የሆነው የታክስ መጠን 23 በመቶ ሲሆን ከ 24.2 በመቶው ጋር ሲነፃፀር ለታችኛው የአሜሪካ ቤተሰቦች ግማሽ። በ2012 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት 3.54 ትሪሊዮን ዶላር በጀት ወይም ጥሬ ገንዘብ አውጥቷል። የ2012 በጀት አመት ዋና ዋና ምድቦች፡ ሜዲኬር እና ሜዲኬይድ ፣ ማህበራዊ ዋስትና ፣ የመከላከያ መምሪያ ፣ መከላከያ ያልሆነ ውሳኔ ፣ ሌላ አስገዳጅ እና ወለድ እ.ኤ.አ. በ 2018 ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም ላይ ትልቁ የውጭ ዕዳ ነበራት። ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት () በመቶኛ በ 2017 በዓለም ላይ 34 ኛው ትልቁ የመንግስት ዕዳ ነበረው. ይሁን እንጂ የቅርብ ጊዜ ግምቶች ይለያያሉ. በ2019 አራተኛው ሩብ ዓመት የዩናይትድ ስቴትስ አጠቃላይ ብሄራዊ እዳ 23.201 ትሪሊዮን ዶላር ወይም 107% የሀገር ውስጥ ምርት ነበር። በ2012 አጠቃላይ የፌደራል ዕዳ ከ 100% በልጧል። ዩኤስ የክሬዲት ደረጃ + ከስታንዳርድ እና ድሆች፣ ከ እና ከ ፕሬዚዳንቱ የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ኃይሎች ዋና አዛዥ ሲሆኑ መሪዎቹን፣ የመከላከያ ፀሐፊን እና የስታፍ ጄነንት አለቆችን ይሾማሉ። የመከላከያ ሚኒስቴር ከስድስቱ የአገልግሎት ቅርንጫፎች አምስቱን ያስተዳድራል፣ እነሱም ከሠራዊት፣ የባህር ኃይል፣ የባህር ኃይል፣ የአየር ኃይል እና የጠፈር ኃይል የተዋቀሩ ናቸው። የባህር ዳርቻ ጥበቃ፣ እንዲሁም የጦር ሃይሎች ቅርንጫፍ፣ በመደበኛነት በአገር ውስጥ ደህንነት መምሪያ የሚተዳደረው በሰላም ጊዜ እና በጦርነት ጊዜ ወደ ባህር ሃይል ዲፓርትመንት ሊዛወር ይችላል። እ.ኤ.አ. በ2019፣ ሁሉም ስድስቱ የዩኤስ ጦር ሃይሎች ቅርንጫፎች 1.4 ሚሊዮን ሰራተኞች በንቃት ስራ ላይ መሆናቸውን ሪፖርት አድርገዋል። የተጠባባቂዎች እና የብሔራዊ ጥበቃ ወታደሮች አጠቃላይ ቁጥርን ወደ 2.3 ሚሊዮን አድርሰዋል. የመከላከያ ሚኒስቴር ኮንትራክተሮችን ሳይጨምር ወደ 700,000 የሚጠጉ ሲቪሎችን ቀጥሯል። ምንም እንኳን በጦርነት ጊዜ በ በኩል የግዳጅ ግዳጅ ሊኖር ቢችልም በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የውትድርና አገልግሎት በፈቃደኝነት ነው። ከ 1940 እስከ 1973 ድረስ, በሰላም ጊዜም ቢሆን የግዴታ ግዴታ ነበር. ዛሬ የአሜሪካ ኃይሎች በአየር ሃይል ትላልቅ የትራንስፖርት አውሮፕላኖች፣ የባህር ኃይል 11 ንቁ አውሮፕላን ተሸካሚዎች እና የባህር ኃይል ጉዞ ክፍሎች ከባህር ኃይል ጋር በባህር ላይ እና በጦር ኃይሎች አየር ወለድ ኮር እና 75 ኛ ሬንጀር ሬጅመንት በአየር ሃይል ማጓጓዣ አውሮፕላኖች ሊሰማሩ ይችላሉ። . የአየር ሃይሉ በስትራቴጂክ ቦምብ አውሮፕላኖች አማካኝነት ኢላማዎችን በመላው አለም ሊመታ ይችላል፣የአየር መከላከያውን በመላው ዩናይትድ ስቴትስ ይጠብቃል እና ለሰራዊት እና የባህር ኃይል ጓድ የምድር ሃይሎች የቅርብ የአየር ድጋፍ ያደርጋል።የህዋ ሃይል የአለም አቀማመጥ ስርዓትን ይሰራል፣ምስራቅን ይሰራል። እና ዌስተርን ሬንጅ ለሁሉም የጠፈር መንኮራኩሮች፣ እና የዩናይትድ ስቴትስ የጠፈር ክትትል እና የሚሳኤል ማስጠንቀቂያ አውታሮችን ይሰራል። ወታደሩ ወደ 800 የሚጠጉ መሰረቶችን እና መገልገያዎችን በውጭ ሀገራት ይሰራል፣ እና በ25 የውጭ ሀገራት ውስጥ ከ100 በላይ ንቁ ሰራተኞችን ያሰማራል። አሜሪካ እ.ኤ.አ. በ2019 649 ቢሊዮን ዶላር በወታደርዋ ላይ አውጥታለች፣ ከአለም አቀፍ ወታደራዊ ወጪ 36% ነው። በ4.7% ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ()፣ መጠኑ ከሳዑዲ አረቢያ በመቀጠል ከከፍተኛ 15 ወታደራዊ ወጪ አድራጊዎች መካከል በሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።የመከላከያ ወጪ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንቨስትመንት ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ሲሆን ከአሜሪካ የፌዴራል ምርምር እና ልማት ግማሹ በዲፓርትመንት የተደገፈ ነው። .የመከላከያ አጠቃላይ የአሜሪካ ኢኮኖሚ ድርሻ ከቅርብ አሥርተ ዓመታት ወዲህ ባጠቃላይ ቀንሷል፣ የቀዝቃዛው ጦርነት መጀመሪያ በ1953 ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 14.2% እና በ1954 ከነበረው የፌደራል ወጪ 69.5% ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 4.7% እና በ2011 የፌደራል ወጪ 18.8% ደርሷል። በአጠቃላይ የሰራተኞች ብዛት፣ ዩናይትድ ስቴትስ በአለም ላይ ከቻይና ህዝቦች ነፃ አውጪ ጦር እና የህንድ ጦር ሃይሎች ቀጥሎ በሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ዩናይትድ ስቴትስ ከአምስቱ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ግዛቶች አንዷ እና የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት ከሆኑ ዘጠኝ ሀገራት አንዷ ነች። ከሩሲያ በመቀጠል በአለም ሁለተኛ ደረጃ ያለው የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ክምችት አላት። ዩናይትድ ስቴትስ ከ40 በመቶ በላይ የሚሆነው የዓለም 14,000 የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት ነች። በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የሕግ አስከባሪ አካላት በዋነኛነት የአካባቢ ፖሊስ መምሪያዎች እና የሸሪፍ ቢሮዎች ኃላፊነት ነው፣ የክልል ፖሊስ ሰፋ ያለ አገልግሎት ይሰጣል። እንደ የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) እና የዩኤስ ማርሻል አገልግሎት ያሉ የፌዴራል ኤጀንሲዎች የሲቪል መብቶችን ፣ የብሔራዊ ደህንነትን እና የዩኤስ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ውሳኔዎችን እና የፌዴራል ህጎችን ማስከበርን ጨምሮ ልዩ ተግባራት አሏቸው። የፍትህ ቢሮ ስታትስቲክስ ቢሮ እና ቻርልስ ኤች ራምሴ የተባሉ የቀድሞ የፊላዴልፊያ፣ ፔንስልቬንያ ፖሊስ አዛዥ በ ላይ እንደገለፁት በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ወደ 18,000 የሚጠጉ የአሜሪካ ፖሊስ ኤጀንሲዎች አሉ። ያ ቁጥር የከተማ ፖሊስ መምሪያዎች፣ የካውንቲ የሸሪፍ ቢሮዎች፣ የክልል ፖሊስ/የሀይዌይ ፓትሮል እና የፌደራል ህግ አስከባሪ ኤጀንሲዎችን ያጠቃልላል። የክልል ፍርድ ቤቶች አብዛኛውን የወንጀል ችሎት ሲያካሂዱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የተወሰኑ ወንጀሎችን እና እንዲሁም ከክልል የወንጀል ፍርድ ቤቶች የተወሰኑ ይግባኞችን ይይዛሉ። እ.ኤ.አ. በ 2010 የዓለም ጤና ድርጅት የሟችነት ዳታቤዝ ላይ የተደረገ ተሻጋሪ ትንታኔ እንደሚያሳየው የዩናይትድ ስቴትስ የነፍስ ግድያ መጠን "ከሌሎች ከፍተኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት በ7.0 እጥፍ ከፍ ያለ ሲሆን ይህም በጠመንጃ ግድያ መጠን በ25.2 እጥፍ ከፍ ያለ" ነው። እ.ኤ.አ. በ 2016 የዩኤስ ግድያ መጠን ከ 100,000 5.4 ነበር ። ከ1980ዎቹ እስከ 2000ዎቹ ባለው ጊዜ ውስጥ የታሰሩ አሜሪካውያን ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን የሚያሳይ ገበታ አጠቃላይ በዩናይትድ ስቴትስ እስራት በአመት ዩናይትድ ስቴትስ በእስር ቤት ከፍተኛ ቁጥር ያለው የእስር ቤት ብዛት እና በዓለም ላይ ትልቁ የእስር ቤት ህዝብ አላት። የፍትህ ዲፓርትመንት እ.ኤ.አ. በ 2019 በግዛት ወይም በፌዴራል ተቋማት ውስጥ ከአንድ አመት በላይ የተፈረደባቸው ሁሉም እስረኞች የእስራት መጠን ከ 100,000 ነዋሪዎች 419 የደረሰ ሲሆን ይህም እ.ኤ.አ. በ 1,430,800 ይህም ከአስር አመታት በፊት ከነበረው የህዝብ ቁጥር 11% ቅናሽ አሳይቷል.እንደ እስር ቤት ፖሊሲ ኢኒሼቲቭ ያሉ ሌሎች ምንጮች በ 2020 ውስጥ የእስረኞችን ጠቅላላ ቁጥር 2.3 ሚሊዮን አድርገው ነበር. በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ቢሮ መሰረት, አብዛኛዎቹ እስረኞች ናቸው. በፌደራል ማረሚያ ቤቶች የተያዙት በአደንዛዥ እፅ ወንጀሎች የተከሰሱ ናቸው።የእስር ቤቱን ህዝብ ቁጥር ለመቀነስ የሚደረገው ጥረት የመንግስት ፖሊሲዎችን እና መሰረታዊ ጅምሮችን የሚያበረታቱ ናቸው - የቅርብ ጊዜ ምሳሌዎች በፌዴራል እና በክልል ደረጃ ያሉ ህጎችን ለምሳሌ እንደ ፍትሃዊ ፍርድ ህግ፣ የመጀመሪያ እርምጃ ህግ፣ የሜሪላንድ ፍትህ መልሶ ኢንቨስትመንትን ያጠቃልላል። ህግ እና የካሊፎርኒያ ገንዘብ ዋስ ማሻሻያ ህግ። ወደ 9% ገደማ የሚሆኑ እስረኞች በግል እስር ቤቶች ውስጥ ተይዘዋል, ይህ አሰራር በ 1980 ዎቹ ውስጥ የጀመረው እና የክርክር ርዕሰ ጉዳይ ነው. በጥር 26, 2021 የቢደን አስተዳደር የፌዴራል መንግስት ከግል እስር ቤቶች ጋር የገባውን ውል ማደስን የሚያቆም አስፈፃሚ ትዕዛዝ ተፈራርሟል, ነገር ግን ሰነድ የሌላቸውን ስደተኞች የሚያዙ የማቆያ ማዕከላትን አይመለከትም። ምንም እንኳን አብዛኛዎቹ ሀገራት የሞት ቅጣትን ቢያጠፉም በዩናይትድ ስቴትስ በተወሰኑ የፌደራል እና ወታደራዊ ወንጀሎች እና በመንግስት ደረጃ በ 28 ግዛቶች ውስጥ እገዳ ተጥሎበታል, ምንም እንኳን ሶስት ክልሎች በገዥዎቻቸው የተጣለባቸውን ቅጣት ለመፈጸም እገዳዎች ቢኖሩም. እ.ኤ.አ. በ2019 ሀገሪቱ ከቻይና፣ ኢራን፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኢራቅ እና ግብፅ በመቀጠል ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። በፉርማን . ጆርጂያ የቀድሞውን ልምምድ ያፈረሰ. ከውሳኔው ጀምሮ ግን ከ1,500 በላይ የሞት ቅጣት ተፈፅሟል። በቅርብ ዓመታት ውስጥ፣ የሞት ቅጣት እና የሞት ቅጣት ሕጎች መገኘት ቁጥር በአገር አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ መጥቷል፣ ብዙ ክልሎች በቅርቡ ቅጣቱን ሰርዘዋል። እንደ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የ22.7 ትሪሊዮን ዶላር አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት መጠን 24 በመቶውን በገበያ ምንዛሪ እና ከጠቅላላ የአለም ምርት ከ16 በመቶ በላይ የሚሆነው በግዢ ሃይል መጠን ይይዛል። እ.ኤ.አ. በየካቲት 2፣ 2022 ዩናይትድ ስቴትስ የ30 ትሪሊዮን ዶላር ብሄራዊ ዕዳ ነበራት። በነፍስ ወከፍ ወደ ውጭ የሚላከው በአንጻራዊ ሁኔታ ዝቅተኛ ቢሆንም ዩናይትድ ስቴትስ ትልቁን የሸቀጥ አስመጪ እና ሁለተኛዋ ላኪ ነች። እ.ኤ.አ. በ 2010 አጠቃላይ የዩኤስ የንግድ ጉድለት 635 ቢሊዮን ዶላር ነበር። ካናዳ፣ ቻይና፣ ሜክሲኮ፣ ጃፓን እና የአውሮፓ ህብረት ዋነኛ የንግድ አጋሮቿ ናቸው። ከ1983 እስከ 2008 የዩኤስ እውነተኛ የተቀናጀ አመታዊ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት 3.3% ነበር፣ ከተቀረው 7 አማካይ 2.3% ክብደት ጋር። ሀገሪቱ በስመ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ ከዓለም አምስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፣ በጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ በ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። የአሜሪካ ዶላር የአለም ቀዳሚ የመጠባበቂያ ገንዘብ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2009 የግሉ ሴክተር 86.4% ኢኮኖሚን ​​ይመሰርታል ተብሎ ይገመታል ። ኢኮኖሚዋ ከኢንዱስትሪ በኋላ የዕድገት ደረጃ ላይ ቢደርስም፣ ዩናይትድ ስቴትስ ግን የኢንዱስትሪ ኃያል ሆና ቆይታለች። በነሐሴ 2010 የአሜሪካ የሠራተኛ ኃይል 154.1 ሚሊዮን ሰዎችን ያቀፈ ነበር። 21.2 ሚሊዮን ህዝብ ያለው የመንግስት ሴክተር የስራ መስክ ቀዳሚ ነው። ትልቁ የግል የስራ ዘርፍ የጤና እንክብካቤ እና ማህበራዊ ድጋፍ ሲሆን 16.4 ሚሊዮን ሰዎች አሉት። አነስተኛ የበጎ አድራጎት ግዛት ያላት እና ብዙ ገቢ ካላቸው ሀገራት ያነሰ ገቢን በመንግስት እርምጃ ታከፋፍላለች። ዩናይትድ ስቴትስ ለሠራተኞቿ ለዕረፍት ክፍያ የማይሰጥ ብቸኛ የላቀ ኢኮኖሚ ነች እና እንደ ህጋዊ መብት ያለ ክፍያ የቤተሰብ ፈቃድ ከሌላቸው ጥቂት የአለም ሀገራት አንዷ ነች። የሙሉ ጊዜ አሜሪካዊያን ሰራተኞች 74% የሚሆኑት የህመም እረፍት ያገኛሉ ይላል የሰራተኛ ስታትስቲክስ ቢሮ ፣ ምንም እንኳን የትርፍ ሰዓት ሰራተኞች 24% ብቻ ተመሳሳይ ጥቅሞችን ያገኛሉ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩናይትድ ስቴትስ ከ 19 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ጀምሮ በቴክኖሎጂ ፈጠራ እና በሳይንሳዊ ምርምር ከ 20 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ ግንባር ቀደም ነች። ተለዋጭ ክፍሎችን ለማምረት የሚረዱ ዘዴዎች በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ በፌዴራል የጦር መሳሪያዎች በዩኤስ የጦርነት ዲፓርትመንት ተዘጋጅተዋል. ይህ ቴክኖሎጂ ከማሽን መሳሪያ ኢንዱስትሪ መመስረት ጋር በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ዩኤስ ከፍተኛ መጠን ያለው የልብስ ስፌት ማሽኖችን፣ ብስክሌቶችን እና ሌሎች እቃዎችን እንዲያመርት አስችሎታል እና የአሜሪካ የማምረቻ ስርዓት በመባል ይታወቃል። በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የፋብሪካ ኤሌክትሪፊኬሽን እና የመሰብሰቢያ መስመር እና ሌሎች የሰው ኃይል ቆጣቢ ቴክኒኮች የጅምላ ምርትን ስርዓት ፈጥረዋል. በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን በግምት ሁለት ሦስተኛው የምርምር እና የልማት ገንዘብ ከግሉ ሴክተር ነው የሚመጣው። ዩናይትድ ስቴትስ በሳይንሳዊ ምርምር ወረቀቶች እና በተፅዕኖ ምክንያት ዓለምን ትመራለች። እ.ኤ.አ. በ 1876 አሌክሳንደር ግርሃም ቤል ለስልክ የመጀመሪያ የዩኤስ ፓተንት ተሰጠው ። በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የቶማስ ኤዲሰን የምርምር ላቦራቶሪ የፎኖግራፍ፣ የመጀመሪያው ረጅም ጊዜ የሚቆይ አምፖል እና የመጀመሪያው ውጤታማ የፊልም ካሜራ ፈጠረ። የኋለኛው ደግሞ ዓለም አቀፋዊ የመዝናኛ ኢንዱስትሪ እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል. በ20ኛው መቶ ዘመን መጀመሪያ ላይ የራንሶም ኢ ኦልድስ እና ሄንሪ ፎርድ የተባሉት የመኪና ኩባንያዎች የመሰብሰቢያውን መስመር በሰፊው አበዙት። የራይት ወንድሞች፣ በ1903፣ የመጀመሪያውን ቀጣይነት ያለው እና የተቆጣጠረውን ከአየር በላይ የከበደ በረራ አደረጉ። እ.ኤ.አ. በ1920ዎቹ እና 30ዎቹ የፋሺዝም እና ናዚዝም መነሳት ብዙ የአውሮፓ ሳይንቲስቶች አልበርት አንስታይን፣ ኤንሪኮ ፈርሚ እና ጆን ቮን ኑማንን ጨምሮ ወደ አሜሪካ እንዲሰደዱ አድርጓቸዋል። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የማንሃታን ፕሮጀክት የኒውክሌር ጦር መሳሪያን በማዘጋጀት የአቶሚክ ዘመንን አስከትሏል ፣ የስፔስ ውድድር ደግሞ በሮኬት ፣ በቁሳቁስ ሳይንስ እና በኤሮኖቲክስ ፈጣን እድገት አስገኝቷል። በ 1950 ዎቹ ውስጥ ትራንዚስተር ፈጠራ በሁሉም ዘመናዊ ኤሌክትሮኒክስ ውስጥ ቁልፍ ንቁ አካል ፣ ብዙ የቴክኖሎጂ እድገቶችን እና የዩኤስ የቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪን ጉልህ መስፋፋት አስከትሏል። ይህ ደግሞ በካሊፎርኒያ ውስጥ እንደ ሲሊከን ቫሊ ያሉ በሀገሪቱ ውስጥ ብዙ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን እና ክልሎችን ማቋቋም አስችሏል. የአሜሪካ ማይክሮፕሮሰሰር ኩባንያዎች እንደ ) እና ከሁለቱም የኮምፒዩተር ሶፍትዌሮች እና ሃርድዌር ኩባንያዎች እንደ አዶቤ ሲስተምስ፣ አፕል ኢንክ.፣ አይቢኤም፣ ማይክሮሶፍት እና ሰን ማይክሮ ሲስተምስ ያሉ ግስጋሴዎች ግላዊ ኮምፒዩተሩን ፈጥረው ተወዳጅ አደረጉት። ኤአርፓኔት በ1960ዎቹ የተገነባው የመከላከያ ሚኒስቴር መስፈርቶችን ለማሟላት ነው፣ እና ወደ በይነመረብ ከተሻሻሉ ተከታታይ አውታረ መረቦች ውስጥ የመጀመሪያው ነው። እ.ኤ.አ. በ2021 ዩናይትድ ስቴትስ ከስዊዘርላንድ እና ስዊድን በመቀጠል በሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ገቢ፣ ሀብት እና ድህነት ከዓለም ህዝብ 4.24 በመቶውን የሚሸፍኑት አሜሪካውያን በአጠቃላይ 29.4% የሚሆነውን የዓለም ሀብት ይይዛሉ። እ.ኤ.አ. በ 2020 724 ቢሊየነሮች እና 10.5 ሚሊዮን ሚሊየነሮች ያሏት አሜሪካ በዓለም ላይ ካሉ ቢሊየነሮች እና ሚሊየነሮች አንደኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ከ2019-2021 ዓለም አቀፍ -2 ወረርሽኝ በፊት ክሬዲት ስዊስ 18.6 ሚሊዮን የአሜሪካ ዜጎችን ዘርዝሯል። ከአንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ የተጣራ ሀብት ያለው። እ.ኤ.አ. በ2020፣ የምግብ ዋስትና መረጃ ጠቋሚ ዩናይትድ ስቴትስን በምግብ ዋስትና 11ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፣ ይህም አገሪቱ 77.5/100 ነጥብ አስገኝታለች። አሜሪካውያን በአማካይ በአንድ መኖሪያ ቤት ከእጥፍ በላይ እና በአንድ ሰው ከአውሮፓ ህብረት ነዋሪዎች የበለጠ የመኖሪያ ቦታ አላቸው። ለ 2019 የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም በሰብአዊ ልማት መረጃ ጠቋሚ (ኤችዲአይ) ከ189 ሀገራት ዩናይትድ ስቴትስ 17ኛ እና ከ151 ሀገራት መካከል 28ኛ በእኩልነት የተስተካከለ ) አስቀምጧል።እንደ ገቢ እና ግብሮች ያሉ ሀብቶች በጣም የተከማቸ ነው; በጣም ሀብታም 10 በመቶው የአዋቂ ህዝብ 72% የሀገሪቱን ቤተሰብ ሀብት ይይዛሉ ፣ የታችኛው ግማሽ 2% ብቻ አላቸው። እንደ ፌዴራል ሪዘርቭ ዘገባ ከሆነ በ 2016 ከፍተኛው 1% የሀገሪቱን ሀብት 38.6% ተቆጣጥሯል ። በ 2018 በኦኢሲዲ ጥናት መሠረት ዩናይትድ ስቴትስ ከማንኛውም የበለፀጉ አገራት ማለት ይቻላል ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ሠራተኞች የበለጠ ነው ። ደካማ የጋራ ድርድር ሥርዓት እና ለአደጋ የተጋለጡ ሰራተኞች የመንግስት ድጋፍ እጦት. ከዓመታት መቀዛቀዝ በኋላ፣ ለሁለት ተከታታይ ዓመታት የተመዘገበ እድገትን ተከትሎ በ2016 አማካይ የቤተሰብ ገቢ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። ሆኖም የገቢ አለመመጣጠን በከፍተኛ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፣ ከጠቅላላ ገቢዎች ውስጥ ግማሹን የሚበልጠው አምስተኛው ከፍተኛ ገቢ ያላቸው። እ.ኤ.አ. በ1976 ከነበረበት ዘጠኝ በመቶ በእጥፍ አድጎ በ2011 ወደ 20 በመቶ የደረሰው የጠቅላላ አመታዊ ገቢ ከፍተኛው አንድ በመቶ ድርሻ ከፍ ማለቱ የገቢ አለመመጣጠን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳደረ ሲሆን ዩናይትድ ስቴትስ ከመካከላቸው ሰፊ የገቢ ክፍፍል ውስጥ አንዷ ሆናለች። አባላት. ከ2009 እስከ 2015 ከተገኘው ገቢ ከፍተኛው አንድ በመቶው የገቢ ገቢ 52 በመቶውን ይሸፍናል፣ ገቢውም የመንግስትን ሽግግር ሳይጨምር የገበያ ገቢ ተብሎ ይገለጻል። የገቢ አለመመጣጠን መጠን እና አግባብነት አከራካሪ ጉዳይ ነው። በጃንዋሪ 2019 በዩኤስ ውስጥ ወደ 567,715 የተጠለሉ እና ያልተጠለሉ ቤት አልባ ሰዎች ነበሩ ፣ ከሁለት ሶስተኛው የሚጠጉት በድንገተኛ መጠለያ ወይም የሽግግር ቤት ፕሮግራም ውስጥ ይቆያሉ የቤት እጦትን ለመዋጋት የሚደረጉት ሙከራዎች ክፍል 8 የቤት ቫውቸር ፕሮግራም እና የቤቶች የመጀመሪያ ስትራቴጂ በሁሉም ላይ መተግበርን ያጠቃልላል። የመንግስት ደረጃዎች. እ.ኤ.አ. በ2011፣ 16.7 ሚሊዮን ሕፃናት በምግብ ዋስትና ባልተረጋገጠ ቤተሰብ ውስጥ ይኖሩ ነበር፣ ከ2007 ደረጃዎች 35 በመቶው ይበልጣል፣ ምንም እንኳን 845,000 የአሜሪካ ሕፃናት ብቻ በዓመቱ ውስጥ በተወሰነ ጊዜ የምግብ አወሳሰድ ወይም የአመጋገብ ስርዓት መስተጓጎል ያዩ ቢሆንም አብዛኛዎቹ ጉዳዮች አልነበሩም። ሥር የሰደደ. እ.ኤ.አ. ከሰኔ 2018 ጀምሮ፣ 40 ሚሊዮን ሰዎች፣ በግምት 12.7% የሚሆነው የአሜሪካ ህዝብ፣ 13.3 ሚሊዮን ህጻናትን ጨምሮ በድህነት ይኖሩ ነበር። ከድሆች መካከል 18.5 ሚሊዮን ያህሉ በጥልቅ ድህነት ውስጥ ይኖራሉ (የቤተሰብ ገቢ ከድህነት ወለል ከግማሽ በታች) እና ከአምስት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት “በሦስተኛው ዓለም” ሁኔታ ውስጥ ይኖራሉ። እ.ኤ.አ. በ 2017 ዝቅተኛ እና ከፍተኛ የድህነት መጠን ያላቸው የአሜሪካ ግዛቶች ወይም ግዛቶች ኒው ሃምፕሻየር እና አሜሪካዊ ሳሞአ ነበሩ። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ያስከተለው ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖ እና የጅምላ ስራ አጥነት የጅምላ መፈናቀል ቀውስ ስጋትን ፈጥሯል ፣የአስፐን ኢንስቲትዩት ባደረገው ትንታኔ በ2020 ከ30 እስከ 40 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች የመፈናቀል አደጋ ላይ መሆናቸውን አመልክቷል።ሲዲሲ እና የቢደን መንግስት የፌድራል ማፈናቀል እገዳን አውጥቷል ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ትዕዛዙን ውድቅ አድርጎታል ፣ ይህንን ለማድረግ በፌዴራል ህጎች መሠረት ስልጣን እንደሌላቸው ወስኗል ። የግል ማጓጓዣ በአውቶሞቢሎች የተያዘ ሲሆን በ4 ሚሊዮን ማይል (6.4 ሚሊዮን ኪሎ ሜትር) የህዝብ መንገዶች አውታር ላይ የሚሰሩ ናቸው። ዩናይትድ ስቴትስ ከዓለም ሁለተኛዋ የአውቶሞቢል ገበያ ያላት ሲሆን በዓለም ላይ በነፍስ ወከፍ ከፍተኛ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ያላት ስትሆን 816.4 ተሽከርካሪዎች ከ1,000 አሜሪካውያን ። እ.ኤ.አ. በ 2017 255,009,283 ባለሁለት ጎማ ያልሆኑ የሞተር ተሽከርካሪዎች ወይም በ 1,000 ሰዎች 910 ያህል ተሽከርካሪዎች ነበሩ ። የሲቪል አየር መንገድ ኢንዱስትሪ ሙሉ በሙሉ የግል ነው እና ከ 1978 ጀምሮ በአብዛኛው ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል, አብዛኛዎቹ ዋና ዋና ኤርፖርቶች ግን በህዝብ ባለቤትነት የተያዙ ናቸው. በተሳፋሪዎች የተሸከሙት በዓለም ላይ ሦስቱ ትላልቅ አየር መንገዶች ዩ.ኤስ. የአሜሪካ አየር መንገድ እ.ኤ.አ. በ2013 በአሜሪካ አየር መንገድ ከገዛ በኋላ አንደኛ ነው። ከአለማችን 50 በጣም በተጨናነቀ የመንገደኞች አውሮፕላን ማረፊያዎች፣ 16ቱ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ይገኛሉ፣ በጣም የሚበዛውን ሃርትፊልድ–ጃክሰን አትላንታ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ። ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም ላይ ረጅሙ የባቡር ኔትወርክ አላት፣ ከሞላ ጎደል ደረጃውን የጠበቀ መለኪያ። አውታረ መረቡ በአብዛኛው ጭነትን ያስተናግዳል፣ በመንግስት የሚደገፈው አምትራክ ከአራቱም ግዛቶች በስተቀር የከተማ አቋራጭ የመንገደኞች አገልግሎት ይሰጣል። መጓጓዣ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ትልቁ ነጠላ የግሪንሀውስ ጋዝ ልቀቶች ምንጭ ነው። ሀገሪቱ በቻይና ብቻ በልጦ በሙቀት አማቂ ጋዞች ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ዩናይትድ ስቴትስ በግሪንሀውስ ጋዝ ልቀትን በነፍስ ወከፍ በዓለም ትልቁን ያቀፈች ስትሆን ከካናዳ ጋር በሦስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። እ.ኤ.አ. ከ2019 ጀምሮ ዩናይትድ ስቴትስ 80% የሚሆነውን ኃይል ከቅሪተ አካል ነዳጆች ታገኛለች። እ.ኤ.አ. በ 2019 ትልቁ የሀገሪቱ የኃይል ምንጭ ከፔትሮሊየም ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ፣ የድንጋይ ከሰል ፣ ታዳሽ ምንጮች እና የኒውክሌር ኃይል ። አሜሪካውያን ከዓለም ህዝብ ከ 5% በታች ናቸው ነገር ግን 17% የሚሆነውን የኃይል ፍጆታ ይጠቀማሉ ከዓለም የነዳጅ ፍጆታ 25% ያህሉ ሲሆኑ ከዓለማችን ዓመታዊ የፔትሮሊየም አቅርቦት 6% ብቻ ያመርታሉ.
46315
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B4%E1%88%8C%E1%8C%8D%E1%88%AB%E1%8D%8D
ቴሌግራፍ
ቴሌግራፍ የመልእክት ግኑኝነት - የፅሁፍ ህትመት ማተሚያ መሳሪያ ቀደም ብሎ ዋና የመገናኛ መንገድ ነበር፤ ቀጥሎም ቴሌግራፍ ፈጣን ግኑኝነትን ከሩቅ ስፍራ ድረስ አስቻለ፤ የራዲዮ ስርጭት መጀመርም የቴሌግራፍን ዝና ቀነሰው እናም ሽቦ አልባ ቴሌግራፍ ብሎም ስልክ የቀጥታ እንድ ለአንድ ግኑኝነት መቻል ደረጃ ሲደረስ ፤መገናኛ ብዝኋን በቴሌቪዥን መስኮት ዋናው የግኑኝነት መንገድ ሆነ፡፡ በኢንተርኔት ዘመን ቴሌግረፊክ ወይንም የመልእክት ግኑኝነት በሽቦ መስመር ላይ በዘዴው እና በአጠቃቀሙ ጎልብቶ እና ቀሎ እነ ጋዜጣ፤ ራዲዮ፤ ቴሌቪዥን ፤ ስልክንም ጨምሮ በመጠቅለል ላይ ይገኛል። የቴሌግራፍ ታሪክ ቴልግራፊ(ከግሪክ «ቴሌ» ማለት ከርቀት፤ «ገራፋይን» ማለት መፃፍ) ሲሆን የረዥም ርቀት የፅሁፍ ወይንም የምልክት መልእክቶች ማስተላለፍን የሚወክል ሲሆን ይህም መልእክቱን የሚሸከም ወይንም የሚያደርስ አካልን አያካትትም፡፡ የኤኬክትሪክ ቴሌግራፍ፤ የኤሌክትሪክ ቴሌግራፍ የኤሌክትሪክ ሲግናልን በተዘጋጀ የሽቦ መስመር ወይንም በራዲዮ ሞገድ መልክ መላክን ይገልፃል፤ ይህም አዲስ የተገኘውን የኤሌክትሪሲቲ ከስተት ማለትም ኃይሉን ማምረት፤ መቆጣጠር ሲቻል አብረው ያሉትንም እንደ፡ የኬሚካል ለውጦች፤ ብልጫታዎቹን፤ የማይለዋወጡ ቻረጆች የስበት ሀይል፤ የኤሌክትሪክ ንዝረት እና የማግኔቲዝም ጠባዩ ላይ ምርምር እና ክትትል ሲቀጥል ነው፡፡ የቴሌግራፍ አይነቶች እና ዕድገቱ በጀርመኖቹ ፊዚሺያኖች የኤሌክትሮኬሚካል ቴሌግራፍ ዘዴ የሚጠቀመው በአንድ ወገን ብዙ ሽቦዎች እያንዳንዳቸው ልዩ የሆነ ስም ወይንም ፊደል የሚወክሉ አንድበአንድ በኤሌክትሪክ ቻረጅ ሲደረጉ በሌላኛው በኩል እነዚህ ሽቦዎች ጫፋቸው የኬሚካል እቃ ውስጥ ተነክረው ቻርጅ በተደረገው ሽቦ መስመር ያለው ኬሚካል በሚፈጥረው እንፋሎት መሰል ምልክት ወይንም በብል ትርጉም መስጠትን ይመስላል ዴቪስ ሪሌይ () በማበል የሚታወቀውም ትንሽ ከረንት ፍሰት ትልቅ የኤሌክትሮማግኔት እንቅስቃሴን በማስነሰቱ ይህም የኤሌክትሪክ ሲገናል ማስተላለፍ ወይንም ቴሌግራፍ፤የኤሌክትሮማግኔትም መታወቅ እናም ጥቅል ሽቦዎችን በማብዛት ኢነሱሌትድ በሆነ ብረት ዙሪያ የመፈጠረውን የማገኔቲክ ኃይል ከፍ በማድረግ ሳይንቲስቱ ሃንስ ክ. አረስትድ() በ1820 እ.ኤ.አ. የኤሌክትሪክ ዥረት የማግኔቲዝም ኃይል እንደሚፈጥር እና ይህም የደቡባዊ ዋልታ የሚያመለክት አመልካችን እንደሚያንቀሳቅስ፤ ቀጥሎም ጆ. ሽቫይገር() የተባለው ጋልቫኖሜትር ወይንም የኤሌክትሪክ ዝረትን ፍሰት አመልካች መሳሪያ በመፈልሰፉ፤ አ.ማ. አምፐርም() ጋልቫኖሜትሮችን በማሰባሰብ ልከ እንደ ኤሌክትሮኬሚካሎቹ ዎች በእያንዳንዱ ሽቦ ላይ የሚመጣውን የኤሌክትሪክ ፍሰት በማመልከት የቴሌግራፍ ጥቅም እንደሚገኝ አመልክቷል ሳሙኤል ሞርስ () የሞርስ ኮድም () የሚባለውን ለእያንዳንዱ ፊደሎች የተለየ ድምፅ በመቀጠል በቴሌግራፍ ታዋቂ ነው የጋውስ () ጋልቫኖሜትርም በዘዴው ተሸሽሎ ኮሚውታቶር በመጠቀም ፤ከቮልታይክ ፒል ወይንም ከባትሪ መሰል ይልቅ የኢንዳክሽን የኤሌክትሪክ ኃይል (ፐልስ) በማድረግ በኮሚውታቶሩ አማካኝነት የዝረት አመልካች ቀስቷን በፖዘቲቭ እና በኔጌቲቭ አቅጣጫ በማንቀሳቀስ በዚሁ ኮድ የተሰጠውን ፊደሎች ማስተላለፍ መቻሉ ሲሆን እነዚህ ፖሰቲቭ እና ኔጋቲቭ መጠኖችም ሊገኙ የቻሉት ጥቅል ሽቦዎችን በማግኔቱ ዙሪያ ወደ ላይ ችና ወደታች በማንቀሳቀስ ነበር፤ በዚህም ሰባት 7 ፊደሎችን በደቂቃ ማስተላለፍ ተችሎ ነበር፤ የቻርልስ ዊትሰቶን() ቴሌግራፍ አመለካች ቀስትን እንደ ሰዐት ቆጣሪ ገበታ ላይ መልእክቱን እንዲያመለክት ማድረግ ነበር ይህም የቴሌግራፍ መልእክቶችንም ከኮዳቸው ወደ ግልፅ ትርጎሜ ለማምጣት የሰለጠኑ ሰዋች ፍላጎት ያስቀረ ነበር እንዲሁም መልእክቱ በሚመጣበት ወቅት ተርጎሚዎች መኖር ነበረባቸው እናም በ1846 አሌክአንደር ባ.() የኬሚካል ቴሌግራፍን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ዥረት ሲግናል የብረት ጠቆሚን በወረቀት ላይ የቀለም ምልክት እንዲያደርግ በማድረግ ከዛም እነዚህን ምልክቶችንም በሌላ ጊዜ መተርጎም ያመለክታል፤ ቀጥሎም የፊደል ገበታ ያላቸው መሳሪያዎች (ኪ-ቦርድ) መልእክት የሚልኩ ቴሌግራፎችን በመጠቀም ፊደሎቹን ሲቀበሉ ወዲያውኑ በሞርስ ኮድ ማተም ተጀመር፤ ሌላውም በሞርስ ኮዶች መሰረት የኤሌክትሪክ ሲግናሉ ሲመጣ በታመቀ አየር በመጠቀም ቀዳዳዎችን በወረቀት ላይ በመብሳት ቀጥሎም መተርጎም ይከተላል ፡፡ የሽባውች የመጠነ አቃቢነት ወይንም ካፓሲታንስ እና ሽቦው በረዘመ ቁጥር የኃይሉ መጠን እንቅፋት ወይንም ረዚስታንስ እየጨመረ በመሄዱ የሚገኘውን የመልእክት ፍጥነት ላይ ተፅእኖ አስድሯል ለዚህም ሲፎን መቀበያ"" የሚባ መሳሪያ በ…… የሚሰራ ፍጥነቱን ወደ 20 ፊደሎች በደቂቃ አድርሷታል ኦሊቨር ሄቪሳይድም () የማስተላለፊያ መስመሩን የሲግናል መዛባት ለማጥፋት በሽቦው ላይ የዥረት አቃቢነት ወይንም ኢንደክታንስ ቢጨመርበት የሚለውን ሀሳብ አፈለቀ እነደዚሁም ይህ ኢንሱሌትድ ሽቦ የኤሌክትሮማግኔት ፀባዩን ከፍ በማድረግ ረዚስታንሱ የሚያመጣውን ጉድለት ቀንሶታል፤ ይህ ኢነሱሌተር ወይንም ኤልክትሪክ የማያስተላለፍ ፕላስቲክ መሰል ከኢሴያ ከ/አለም ከሚገኝ ዛፍ ጉታ ፐርቻ () እነደሚገኝ ታውቆ በስኮትላንድ ሀኪም ታውቆ ነበር እናም ይህ በእነ ፋራዳይ ለኤሌክትሪክ ኢነሱሌተርነት እንዲውል አደረጉት ሌላው የቴሌግራፍ ተግዳሮት የነበረው የመላኪያ ፍጥነቱን መጨመር ነበር(ፊደሎች/በደቂቃ) ይህም በሰው የሚሰር እጅ ስራን ማስቀረት ይጨምራል፤ ለዚህም የድምፅ ሰራተኞችን በመዝግቦ በመተንተን… ሞርስ ኦፐሬተር የተበላው መሳሪያ ዶት እና ዳሽ ኮዶችን በመለየት በሚጠቀመው ዘዴ……… የቶማስ ኤዲሰንም መልቲፕሌክ ቴሌግፍ ፣ ሢግናሎችን በጊዜ በፍጥነት በመከፋፈል የሚገኘውን እስከ ቤል ቴሌፎን ዕያለ መሻሻል አሳይቷል የአጠቃቀሙ ዕድገቱ ጋውስ በ1835 በጀርመን የባቡር መስመር ጣቢያ የቴሌግራፍ መስመር ለትግበራ ውሎ ነበር በ1840 ሞርስ የኤሌክትሪክ ቴሌግራፉን ለዕይታ ባቀረበበት ወቅት የታላከው መልእክት ፈጣሪ በመጀመሪያ ምን አለ “?” የሚል ትርጎሜ ይመስላል፤ እናም ለአሜሪካው ምክርቤት በፃፈው ማስታወሻ ሞርስ እንዲህ ብሎ ነበር - ይህን መሰሉ የፈጣን ግኑኝነት መሳሬያ ትልቅ ወጤት ያለው ስለሚሆን ስለዚህም ልክ እንደ አያያዛችን ለጥሩም ለመጥፎም ሊውል ይችላል" ኮክ እና ዊትስቶን የኤሌክትሪክ ቴሌግራፍ ካምፓኒ() መስርተው በ13ኪሜ ርዝመት ያለው ለንግድ ያዋለውን የቴሌግፍ መስመር በግሬት ዌስተርን ሬይልዌይ () አካባቢ ዘረጉ ይህም ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ ነበር በ1850ወቹ በእንግሊዝ እና በ ፈረንሳይ መካከል የቴሌግራፍ መስመር ሲዘረጋ በመጀመሪያ ባይሳካም በሁለተኛ ሙከራ ግኑኘነት ማድረግ ተችሎል ቀጥሎም በ1860ዎቹ አትላንቲክ ውቂያኖስን ያቆረጠ የትሌግራፍ መስመር መዘርጋት ተችሎ በአሁጉራት መካከል ያለውን የጊዜ እና የቦታ ርቀት ከበደትን ያሳጣው ሆኗል፤ ዌስተርን ዩኒየን የመሳሰሉ ድርጅቶች ዋና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ነበሩ፤ እነደዚህም እያለ በፓሲፊክ ላይ የቴሌግራፍ ግኑኝነት በ 1902 ሲጠናቀቅ የቢሪቲሽ የባህር ውስጥ መስመር ዝርጋታ አብዛኛውን የወከለ ነበር፤ የዌስተርን ዩኒየን የቴሌግራፍ ግልጋሎት እስከ 2006 ድረስ ሲሰራ የነበረ ሲሆን የህንድም ተልግራፍ አገልግሎት እስከ 2013 ድረስ ጥቅም ላይ ውሎ ነበር፡፡ ኮክ እና ዊትስቶን የኤሌክትሪክ ቴሌግራፍ ካምፓኒ() መስርተው በ13ኪሜ ርዝመት ያለው ለንግድ ያዋለውን የቴሌግፍ መስመር በግሬት ዌስተርን ሬይልዌይ () አካባቢ ዘረጉ ይህም ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ ነበር ↵↵-➞በ1850ወቹ በእንግሊዝ እና በ ፈረንሳይ መካከል የቴሌግራፍ መስመር ሲዘረጋ በመጀመሪያ ባይሳካም በሁለተኛ ሙከራ ግኑኘነት ማድረግ ተችሎል ቀጥሎም በ1860ዎቹ አትላንቲክ ውቂያኖስን ያቆረጠ የትሌግራፍ መስመር መዘርጋት ተችሎ በአሁጉራት መካከል ያለውን የጊዜ እና የቦታ ርቀት ከበደትን ያሳጣው ሆኗል፤ ዌስተርን ዩኒየን የመሳሰሉ ድርጅቶች ዋና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ነበሩ፤ እነደዚህም እያለ በፓሲፊክ ላይ የቴሌግራፍ ግኑኝነት በ 1902 ሲጠናቀቅ የቢሪቲሽ የባህር ውስጥ መስመር ዝርጋታ አብዛኛውን የወከለ ነበር፤ የዌስተርን ዩኒየን የቴሌግራፍ ግልጋሎት እስከ 2006 ድረስ ሲሰራ የነበረ ሲሆን የህንድም ተልግራፍ አገልግሎት እስከ 2013 ድረስ ጥቅም ላይ ውሎ ነበር፡፡
8913
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A1%E1%8A%93
ቡና
ቡና የተክል አይነትና ከዚህ ተክል ቡን የሚባል መጠጥ የሚወጣው ነው። መጀመርያ የታወቀው በኢትዮጵያ ሲሆን ምናልባት በዚህ የተነሳ ቡና በተለያዩ የዓለም ቋንቋዎች ከፋ ከሚለው ስም ጋር ተቀራራቢ የሆነ ስሞች ተስጥተውት ይገኛል (ለምሳሌ እንግሊዝኛ፦ /ኮፊ/ በፈረንሳይኛ ካፌ ()በዳች ኮፊ () በእብራይስጥኛ ካፈ () በስዊድንኛ ካፈ () ወዘተ ) ምናልባት ከድሮው የከፋ መንግሥት በተዛመደ መልኩ ሊሆን ይችላል። በአንድ ትውፊት መሠረት በመጀመርያ ያገኘው ሰው ካልዲ የተባለ አንድ ኢትዮጵያዊ እረኛ ፍየሎቹ ፍሬውን በልተው ሲጨፍሩ ስለተመለከተ ነበር። የቡና የስነ ፍጥረት ስሙ (ኮፊ ኣራቢካ) ሲሆን የዚህ የኢትዮጵያ ቡና ዘር በጣዕሙ ጥሩነት የተነሳ በጣም ተወዳጅ ነው። በደራሲው ዊሊያም ኡከርስ መጽሐፍ 'ኦል አባውት ኮፊ' (ስለ ቡና ኅልዮ/ምንነት) እንደተገለጸው ቡና ወደ የመን የገባው በአክሱም ዘመነመንግሥት በ517 ዓ.ም. አካባቢ ነበር። የፋርስ ሃኪም አል-ራዚ (857-917 ዓ.ም. የኖሩ) ተክሉን «ቡንቹም» ብሎ ምናልባት በታሪክ አንደኛው ስለ ቡና መግለጫ የመዘገበው ጸሐፊ ይሆናል። ሌላ እብን-ሲና(972-1029 ዓ.ም.)የተባለ ፋርስ ሀኪም ደግሞ ስለ «ቡንቹም» ጥቅም ጽፏል። የሞሮኮ ደርቡሽ ሼክ አቡል-ሀሳን አሽ-ሻዲሊ (1167-1250 ዓ.ም.) በአሰብ ዙሪያ ሲጓዝ ኗሪዎች ስለ ቡና መጠጥ እንደገለጹለት ይነገራል። የአደን ሙፍቲ ሼክ ጃማል-አል-ዲን አል-ዳባኒ በ1446 ዓ.ም. ገደማ ለመጀመሪያ ጊዜ መጠጡን እንዳስገባ ተመዝግቧል። በ1449 ዓ.ም. መጀመርያው ቡና ቤት «ኪቫ ሃን» በኢስታንቡል ቱርክ ተከፈተ። ሆኖም በ1503 ዓ.ም. የማካህ ይማሞች ቡና ቤት ስላልወደዱ መጠጡን ሃራም (እርም) አሉት። ነገር ግን የኦቶማን ቱርክ ሡልጣን 1 ሰሊም በ1509 ዓ.ም. ማካህን በ1516 ዓ.ም. ይህን ድንጋጌ ገልብጦ የተቀደሰ መጠጥ አደረገው። ከዚያ በኋላ እስላሞች ቡናን በተለይ በጣም ወደዱት። ለኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እስከ 1881 ዓ.ም. ድረስ ቡና እንደ ተከለከለ ዛሬ በሰፊ አይታወቅም። ከ1872 እስከ 1878 ድረስ ቡና በመጠጥነት በኢትዮጵያ በጣም ስለ ተስፋፋ አጼ ምኒልክ ከጠጡት በኃላ በ1881 ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ሆነው አቡነ ማቴዎስ 10ኛ ቡናን አጸደቁት። ቡና ወደ አውሮፓ ለመጀመርያ ጊዜ በ16ኛ ክፍለ ዘመን ያስገቡት ነጋዴዎች ከቬኒዝ ጣልያን ነበሩ። በ1592 ዓ.ም. የሮማ ጳጳስ 8 ቄሌምንጦስ ስላጸደቁት በፍጥነት ዘመናዊ መጠጥ ሊሆን በቃ ። የመጀመርያው ቡና ቤት በአውሮፓ በጣልያን በ1637 ዓ.ም. ተከፈተ። አረቦች ግን በጣም አጥብቀው ለምለሙ ተክል ከአረብ ዓለም እንዲወጣ ምንም ባይፈቅዱም፣ በ1600-1650 ዓ.ም. ገደማ አንድ ስሙ ሃጂ ባባ ቡዳን የሚባል ህንዳዊ እስላም ከሞቃ የመን በስውር የቡና ዘር ይዞ ወደ ሚሶር ሕንድ አገር ተመለሰና ተክሉን እዚያ አበቀለው። በ1608 ዓ.ም. የሆላንድ ሰዎች ለ አደን መጥተው ለምለም የቡና ዘር ይዘው ወደ አገራቸው ተመለሱ። በ1690ዎቹ በሆላንድ ቅኝ አገሮች በጃቫ (ዛሬ ኢንዶኔዥያ) እና በሱሪናም (ደቡብ አሜሪካ) በብዛት እንዲስፋፋ አደረጉት። በአሁኑ ጊዜ ቡና በዓለም ላይ ከሚጠጡ መጠጦች አንደኛን ስፍራ ይዟል። በተጨማሪም የቡና ቅጠል በወተት ተፈልቶ ቁጢ እንዲሁም የቡና ዘር ሽፋኑ/ቅርፊቱ ተፈልቶ የሚጠጣው አሻራ ተወዳጆች ናቸው። ቁጢና አሻራ ከኢትዮጵያ ውጪ እንደሚታውቁ መረጃ የለም። ዮርባ የትዳር የኢትዮጵያ የቡና አፈላል ስርአት 1,የቡና እቃ አጥበን እናቀራርባለን፦ረከቦት፣ሲኒ፣ብረት ምጣድ ወ.ዘ.ተ.... 2,ከሰል እናቀጣጥላለን 3,ቡናችንን ለቅመን እናጥብና ወደ ብረት ምጣድ አድርገን ምድጃዉ ላይ ይጣዳል 4,በመቀጠል ቡናዉ እንዳያር በመቁያ እናማስላለን 5,ቡናዉ አጋም ሲመስል ከእሳት ላይ እናወርዳለን 6,ከዛም በመቀጠል ቡናውን በሙቀጫ እስኪደቅ ድረስ እንወቅጣለን 7,ዉሀ በጀበና ምድጃዉ ላይ እንጥዳለን 8,ዉሀዉ ሲፈላ ደቀቀዉን ቡና ወደ ጀበናዉ ጨምረን በድጋሚ እንጥዳለን 9,ቡናዉ ሲንተከተክ ጀበናዉን ከእሳት ላይ አዉርደን እስኪሰክን ድረስ 5 ደቄቃ ድረስ እንቆያለን 10,በምድጃዉ ላይ በብረት ጀበና ዉሀ እንጥዳለን 11,ከዛ በእርጋታ ጀበናዉን ይዘን ወደ ሲኒዋቹ ላይ እንቀዳለን 12,ቡናዉ ሲያልቅ በቡረት ጀበናዉ ላይ የጣድነውን ዉሀ ወደ ጀበናዉ ገልብጠን እንጥዳለን 13,እንደዛዉ እየተባለ እሰከ 3ተኛ(በረካ)ድረስ ይጠጣል። ለጠቅላላ እዉቀት፦1ኛ(አቦል) የውጭ መያያዣ መረጃ ስለ ቡና (እንግሊዝኛ) ስመ ኣትክልት ከዶ/ር ኣበራ ሞላ
3530
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%B0%E1%89%A5%E1%88%A8%20%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%83%E1%8A%95
ደብረ ብርሃን
ደብረ ብርሃን በሸዋ ክፍለ ሀገር የጅሩ ሸዋ ሜዳ ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ የሰሜን ሸዋ ዞን (አውራጃ) አስተዳደር ርዕሰ ከተማ ከመሆኗ ባሻገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም ዋና ጽሕፈት ቤት እዚሁ ይገኛል። በ፲፱፻፺፰ ዓ/ም ማዕከላዊ የስታትስቲክስ ባለስልጣን እንደተመነው ደብረ ብርሃን ከተማ የ፷፯ ሺህ ፪፻፵፫ ሰው መኖሪያ ስትሆን ከነሱም ፴፬ ሺህ ፶፭ ወንዶችና ፴፫ ሺህ ፻፹፰ ሴቶች ይገኙባታል ይላል። በሌላ ገለልተኛ የግምት ትመና ደግሞ ከተማዋ የ፶፯ ሺህ ፯፻፹ ሕዝብ መኖሪያ እንደሆነች ተገምቷል። የከተማዋ አቀማመጥ በ ላይ ነው። ደብረ ብርሃን ከአዲስ አበባ ፻፴ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በደሴ መስመር ላይ የምትገኝ ስሆን ፱ የአስተዳደር ቀበሌዎችም አሏት። የአየር ንብረቷ ደጋማ ነው። የተቆረቆረችውና ስያሜዋን ያገኘችው ደግሞ በ፲፬፻፵፮ ዓ/ም አካባቢ በዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ነበር። ከተማዋ ድሮ የንጉሡ የግራ በአልቴሃት (ግራ በአልቴሃት ከንጉሡ ሦሥት ሚስቶች የአንደኛዋ የክብር ስም ነው) ርስት ነበረች። በ፲፬፻፵ዎቹ መጀመሪያ አጤው ከእንደግብጣን ወጨጫ ተራራ ማለትም ከአዲስ አበባ በስተምዕራብ ከነበረው ያባታቸው አጤ ዳዊት መናገሻ ሥፍራ ተነስተው ሲጓዙ በአካባቢው ውበት ስለተደሰቱ የድንኳን ከተማቸውን ከተሙባት። በኋላም ቤተ መንግሥት አሳንፀውና ባለወርቅ ጉልላት የነበረውን የሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አሰርተው ቆረቆሯት። "ተአምረ ማርያም" የተሰኘ የጥንት ድርሳን የከተማዋን ስያሜ ከአንድ ተአምራዊ ሁነት ጋር አያይዞ ይገልፀዋል። በ፲፬፻፵፮ ዓ/ም በክርስትና ሃይማኖት ካህናትና በጥቂት የሃይማኖቱ ተከራካሪዎች መካከል ክርክር ይነሳል። ንጉሡና የካህናቱ አለቆች በተገኙበት አንድ ዕለት በጉባዔ ክርክሩ ተካሄደ። በመጨረሻም «እስጢፋኖሳውያን» በሚል መጠሪያ የሚታወቁት ተከራካሪዎች አቋማቸውን እንዲያስተካክሉ ተጠይቀው አሻፈረን በማለታቸው ከፍተኛ ቅጣት ይደርስባቸዋል። ይህ በሆነ በ፴፰ኛው ቀን በመጋቢት ፲ ቀን 1446|፲፬፻፵፮ ዓ/ም ረዘም ላለ ጊዜ / ምናልባትም ለቀናት/ የቆየ ቦግ ያለ ብርሃን ከሰማይ ይወርዳል። የብርሃኑ መውረድ ለእስጢፋኖሳውያን ስህተተኛነት ለካህናቱ ደግሞ ትክክለኛነት ምስክር ነው በሚል ተተርጉሟል። ስለዚህ ብርሃን መውረድ የንጉሡ ዜና መዋዕልም ያትታል። በዚህ ሳቢያ ንጉሡ የሥፍራውን ስም ደብረ ብርሃን /የብርሃን አምባ/ በማለት ሰይመውታል። ይህ መንግስቱ ያመነበት ነግር ነው በብዙዎች ዘንድ የሚታመነው እውነታ ግን በዚያ ግዜ የነበሩ ደቂቀ እስጢፋኖሳውያን እውነተኛውን ኃይማኖት አንክድም ለስዕል አንሰግድን ማለታቸው ነበር ንጉሱን ያስቆጣው በዚህም ምክንያት ነበር ንጉሱ እስጢፋኖሳውያን እስከ እንገታቸው እንዲቀበሩና በላያቸው የፈረስ ሰራዊት ሄዶባቸው በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲገደሉ ያዘዘው. ከዚህም የተነሳ የመጣው መብረቅ የመሰለ አስፈሪ ብርሀን የመጣው የእግዚእብሔር ቁጣ ነበር እንጂ ደስታው አልነበም። ዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ከንግሥና ዘመናቸው ፲፬ ዓመታት የሚሆነውን በደብረ ብርሃን ከተማ እንዳሳለፉና አብዛኛዎቹን የሃይማኖትና የፍልስፍና ድርሰቶቻቸውን የፃፉት በዚሁ ከተማ መሆኑ ይነገራል። በዘመኑም ደብረ ብርሃን ከፍተኛ የትምህርት ማዕከል የነበረች ሲሆን በንጉሡ ትእዛዝ በርካታ የሃይማኖት መፃሕፍት የትርጉም ሥራ ተከናውኖባታል። በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የኣዲስ ኣበባ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሲጣበቡ ለሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተማሪዎች እንዲያገልግል ኃይለ ማርያም ማሞ ፪ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ደብረ ብርሃን ተሠራ። ለመጀሪያዎቹ ስድስት ዓመታት ለተማሪዎቹም መጀመሪያ በየወሩ ፳ ብር በኋላም ፲፭ ብር እየተፈልላቸው ነበር የተማሩት። ከምሩቃኖቹም መካከል ዶ/ር ኣበራ ሞላ ታላቅ ወንድማቸው ዶክተር በቀለ ሞላና ታናሽ ወንድማቸው ጌታቸው ሞላ ይገኙበታል። የአማራ ብሔራዊ ክልል፤ ባህል፣ ቱሪዝምና ማስታወቂያ ቢሮ፤ “የአማራ ክልል የቱሪስት መስህብ ሃብቶች (አጭር ቅኝት)”፤ አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት (፲፱፻፺፩ ዓ/ም) የኢትዮጵያ ከተሞች
12157
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5%20%E1%8C%8A%E1%8B%AE%E1%88%AD%E1%8C%8A%E1%88%B5%20%E1%8B%A8%E1%8A%A5%E1%8C%8D%E1%88%AD%20%E1%8A%B3%E1%88%B5%20%E1%89%A1%E1%8B%B5%E1%8A%95
ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ቡድን
ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በሌላ መልኩ ቅዱስ ጊዮርጊስ በመባል የሚታወቀው በአዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ የባለሙያ እግር ኳስ ክለብ ነው። በኢትዮጵያ እግር ኳስ ከፍተኛ ዲቪዚዮን ማለትም በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ይጫወታሉ። በ 1935 የተቋቋመው ክለቡ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሲሆን በፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ኃይሎች ላይ የኢትዮጵያዊነት እና የመቋቋም ምልክት ሆኖ ተመሠረተ። መመስረት እና የአርበኝነት ትግል ክለቡ በጆርጅ ዱካስና በአያሌ አጥናሽ አራዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) የእግር ኳስ ክለብ ሆኖ በታህሳስ 1928 ዓ.ም ተመሠረተ። ክለቡ የተሰየመበት ሰፈር ፣ አዲስ አበባ አራዳ (“አራዳ ጊዮርጊስ” ተብሎም ይጠራል) ተብሎ ተሰይሟል። ለክለቡ የተጫወቱት የመጀመሪያዎቹ ተጫዋቾች ከዱካስና ከአትናሽ ትምህርት ቤቶች ፣ ከተፈሪ መኮንን እና ቅዱስ ጊዮርጊስ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) የተሰበሰቡ ተማሪዎች ናቸው። ፋሽስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት የተቋቋመው ክለቡ በጣሊያን ወረራ መካከል የኢትዮጵያዊነት ተምሳሌት ሆነ። የ1930 ዎቹ የአርበኞች ተጋድሎ በክለቡ እና በአራዳ ሰፈር ላይ የማይጠፋ አሻራ ጥሎ ነበር ፣ ሁለቱንም ለመጪዎቹ ምዕተ ዓመታት ይገልፃል። የክለቡ ታሪክ ብዙውን ጊዜ በዚህ ሰፈር ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድራል ተብሎ ይታሰባል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በ 2 ቴገራ ብር ፣ በ 1 ኳስ ፣ በግብ ኳሶች እና በማኅተም ብቻ እንደጀመረ ተነግሯል። በአራዳ ፖሊስ በተከለከላቸው ገደቦች ምክንያት ብዙውን ጊዜ በአከባቢ ሜዳዎች ላይ እግር ኳስ መጫወት ከባድ ሆኖበት ክለቡ ያለማቋረጥ ከቦታ ወደ ቦታ መንቀሳቀስ ነበረበት። በአንድ ወቅት የክለቡ አባላት የግብ ልጥፎችን ወደ ‹ፊልመሃመዳ› (በአሁኑ ጊዜ ከብጁ ባለሥልጣናት ዋና መሥሪያ ቤት አጠገብ ይገኛል) ሞክረዋል ፣ ነገር ግን በመጨረሻ በባለሥልጣናት አባረሯቸው። በ ‹እቴጌ መነን› ሜዳ ላይ ‘አሮገ ቄራ’ ላይ ለመጫወት ያደረግነው ሙከራም ደስተኛ ያልሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች በመባረራቸው አልተሳካም። ከዚያም ወደ 'በላይ ዘለቀ' 'ዘበግና ሰፈር' መንደር ቢሄዱም የአራዳ ፖሊስ መጥቶ እንደገና አባረራቸው። እንደ ሌሎች የአካባቢው ቡድኖች ወይም ቡድኖች እንደ አዲስ አበባ የአርሜኒያ ማህበረሰብ ባሉ ቡድኖች ላይ ግጥሚያዎች ተዘጋጁ። ሆኖም ክለቡ የነበራቸውን የተጫዋቾች ብዛት አጭር ስለነበር ሌሎችን ለጨዋታ መመልመል ችሏል። ይድነቃቸው ተሰማ የቡድኑ አባል ለመሆን የመጣው በዚህ መንገድ ነው ፣ በአዲስ ጎዳናዎች ላይ ተገኝቶ ለጨዋታው እንዲቀላቀል ተጠይቋል። በራድ መኮንን ድልድይ አቋርጦ ሲታይ መታየቱና ሁሉም የክለቡ አባላት ትምህርት ቤት ወደሄዱበት ወደ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ከሄደ ጀምሮ እሱን ያውቁ ነበር ተብሏል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከእነሱ ጋር ለመቀላቀል ከተስማማ በኋላ በራሱ ይድነቃቸው ሁለት ግቦች የአርሜኒያ ቡድኑን 2-0 ማሸነፍ ችሏል። የክለቡ የመጀመሪያ ማሊያዎች በወቅቱ ለገንዘብ ታጥቆ ለነበረው ክለብ ቡናማና ነጭ ፣ ተመጣጣኝ ጨርቅ ነበር። ከመሥራቾቹ አንዱ ጆርጅ ዱካስ ክለቡን ለመደገፍ ከወላጆቹ የተሰበሰበውን ገንዘብ ተጠቅሟል። ሌሎች በክለቡ ውስጥ ለክለቡ ገንዘብ ለማግኘት እንደ “ሆያ ሆዬ” ያሉ ባህላዊ ዘፈኖችን እየዘፈኑ በሩን በማንኳኳት ነበር። ለዝማሬ ጥረታቸው የተለመደው ሽልማት ዳቦ ሳይሆን ገንዘብ ነበር ፣ ግን ይህንን ዳቦ በሠራተኞች መንደር ውስጥ ለመሸጥ በከረጢት ውስጥ ለመሰብሰብ ችለዋል። ክለቡ አንዳንድ ገንዘቦችን ማግኘት ከቻለ በኋላ ከኢትዮጵያ ባንዲራ ቀለሞች ጋር አንድነታቸውን የሚያመለክት ኒው ጀርሲ ማግኘት ችለዋል። የመጀመሪያውን ማሊያ ለሁለተኛው ቡድን ሰጥተው አዲሱን ማልበስ የጀመሩት በተያዘው የፖሊስ ኃይል ግፊት ይህንን ኒው ጀርሲ በልብሳቸው ስር እንዲደብቁ እስኪያደርጉ ድረስ ነው። የክለቡ የመጀመሪያ ማሊያዎች በወቅቱ ለገንዘብ ታጥቆ ለነበረው ክለብ ቡናማና ነጭ ፣ ተመጣጣኝ ጨርቅ ነበር። ከመሥራቾቹ አንዱ ጆርጅ ዱካስ ክለቡን ለመደገፍ ከወላጆቹ የተሰበሰበውን ገንዘብ ተጠቅሟል። ሌሎች በክለቡ ውስጥ ለክለቡ ገንዘብ ለማግኘት እንደ “ሆያ ሆዬ” ያሉ ባህላዊ ዘፈኖችን እየዘፈኑ በሩን በማንኳኳት ነበር። ለዝማሬ ጥረታቸው የተለመደው ሽልማት ዳቦ ሳይሆን ገንዘብ ነበር ፣ ግን ይህንን ዳቦ በሠራተኞች መንደር ውስጥ ለመሸጥ በከረጢት ውስጥ ለመሰብሰብ ችለዋል። ክለቡ አንዳንድ ገንዘቦችን ማግኘት ከቻለ በኋላ ከኢትዮጵያ ባንዲራ ቀለሞች ጋር አንድነታቸውን የሚያመለክት ኒው ጀርሲ ማግኘት ችለዋል። የመጀመሪያውን ማሊያ ለሁለተኛው ቡድን ሰጥተው አዲሱን ማልበስ የጀመሩት በተያዘው የፖሊስ ኃይል ግፊት ይህንን ኒው ጀርሲ በልብሳቸው ስር እንዲደብቁ እስኪያደርጉ ድረስ ነው። ክለቡ በገንዘቡ ማሊያ ከገዛ በኋላ በቀሪው ገንዘብ ለተጫዋቾች ምግብ ገዝቷል። የክለቡ አባላት እና ተጫዋቾች ከጨዋታ እና ከስልጠና በኋላ ዳቦ እና ሻይ መብላት ይፈልጋሉ። ጣሊያን ቅዱስ ጊዮርጊስን በቀጥታ ለማጥፋት ያደረገው ጥረት ሳይሳካ ሲቀር ክለቡ ስሙን ቀይሮ ጣሊያኖች ‹6 ኪሎ› ከሚባለው ክለብ ጋር እንዲጫወት አስገድደውታል። ይህ ክለብ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለማዳከም እና ተስፋ ለማስቆረጥ ሆን ተብሎ በጣሊያኖች የተፈጠረ ነው። በአቅራቢያው በሚገኘው 'ኩግናክ አሎቮ' ፋብሪካ 6 ስፖንሰር (ሐምሌ 5 ለማለትም ‹ሴንኮ ማጄ› ተብሎም ይጠራል) ፣ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የበለጠ ገንዘብ እና ቁሳቁስ ነበረው። ቅዱስ ጊዮርጊስን በተለያዩ አጋጣሚዎች አሸንፈዋል ቅዱስ ጊዮርጊስም እንዲሁ አድርጓል ግን እነዚያ ግጥሚያዎች ሁልጊዜ በአራዳ (ጣሊያን) ፖሊስ በመደብደብ ይጠናቀቃሉ። በዚህ ወቅት እየተካሄደ ያለው የሽምቅ ውጊያ ለክለቡ እና ለአባላቱ እጅግ አስፈላጊ ነበር። ጣሊያኖች ይህንን በማወቃቸው የሽምቅ ተዋጊዎችን ለማደናገር እና ለማጥመድ ክለቡን ለራሳቸው አስተዳደር የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ አድርገው ለመጠቀም ይሞክራሉ። ጣሊያኖች እንደ ራስ ላሉ የመቃወም መሪዎች መልእክት ላኩ። አበበ አረጋይ አዲስ አበባ በሚገኘው ተወዳጅ ሜዳ ጃንሜዳ ላይ የእግር ኳስ ጨዋታ እንዲመለከት ጋብዞ ‹‹ መጥቶ ሕዝቡ በሰላም ነው ›› እንዲል። ይህንን የሰሙ የሽምቅ ተዋጊዎች አንድ ጣሊያናዊ ጄኔራል ጣልያኖችን እና ራስን የማይታመን አድርገው ወስደዋል። አበበ አረጋይ ሁኔታውን እንዲመረምር ደምሴ ወ/ሚካኤልን ልኳል። ጨዋታውን በሰላም ለመጫወት ከእጅ በፊት ማስጠንቀቂያ የተሰጠው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ “6 ኪሎ” ጋር ለመጫወት ተመርጧል። ተመልካቾች ብዙውን ጊዜ ከጨዋታው ይልቅ ትግሉን ለማበረታታት እና ፉጨት ከተጫወቱ በኋላ ጨዋታው በፍጥነት ወደ አካላዊ ውጊያ ተለወጠ። ከዚያ ጨዋታው ተቋርጦ የጣሊያኖች እቅድ ከሽ .ል። እ.ኤ.አ. በ 1941 ኢትዮጵያ ከፋሽስት ኢጣሊያ ቁጥጥር ነፃ ስትወጣ እና ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በተመለሱበት ወቅት “ኢትዮጵያ ሆይ ዴ ይበልሽ” (ትርጉሙ ፣ ኢትዮጵያን ደስ ይበላችሁ) የሚለውን ብሔራዊ መዝሙር የዘመሩት የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች ከአዲስ አበባዎች ጋር በመሆን አቀባበል አድርገውላቸዋል። እሱን መልሰው። በአንድ ግዙፍ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊ ዮፍታሔ ንጉሴ የተፃፈ እና በካፒቴን ናልባዲን የተዘጋጀ መዝሙር። የኢትዮጵያ ሊግ እግር ኳስ የመጀመሪያው በይፋ እውቅና የተሰጠው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ሊግ ስሪት በ 1944 ተቋቋመ። በመጀመሪያ አምስት ቡድኖችን ቅዱስ ጊዮርጊስን (ኢትዮጵያዊ) ፣ ፎርቱዶ (ጣሊያንኛ) ፣ አራራት (አርሜኒያ) ፣ ኦሎምፒያኮስ (ግሪክ) እና እንግሊዞችን ጨምሮ የተለያዩ ቡድኖችን የሚወክሉ አምስት ቡድኖች ነበሩ። በኢትዮጵያ ወታደራዊ ተልዕኮ (ቢኤምኤምኤም) በቢኤምኤም አሸናፊነት ለመወዳደር ተወዳድሯል። በ 1947 የአገሪቱ መደበኛ ብሔራዊ ሊግ በሦስት ቡድኖች ተጀመረ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ መቻሌ እና ከዓይ ባህር። ደርግ የእግር ኳስ ሊጎችን ከማደራጀቱ በፊት ክለቡ በሊጉ ውስጥ ለሃያ አምስት ዓመታት የቆየ ሲሆን ነባር ክለቦችን በሙሉ እንዲዘጋ አስገድዷል። በዚህ ሂደት ክለቡ ስሙን በአዲስ አበባ ቢራ ፋብሪካ በ 1972 ተቀይሮ ከአራት ዓመት በኋላ ብቻ ለመለወጥ ነበር። ክለቡ ስያሜውን ለ 19 ዓመታት ወደ ኋላ ቀይሮ ደርግ እስኪወድቅ ድረስ በ 1991 ክለቡ በይፋ ስሙን ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቀይሯል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በ 60 ዎቹ መገባደጃ ላይ የተወሰነ የበላይነትን አግኝቶ ከዚያ በኋላ ሊጉ በ 70 ዎቹ እና በ 80 ዎቹ አንጻራዊ የእኩልነት ጊዜን አሳል ል። ሆኖም በፕሪምየር ሊጉ ዘመን ከ 1997-98 የውድድር ዘመን ጀምሮ አስደናቂ 14 ርዕሶችን በማሰባሰብ ከቅዱስ ጊዮርጊስ አ.ሲ. ከ 2017 ጀምሮ ክለቡ በድምሩ 29 ከፍተኛ የምድብ ዋንጫዎችን የያዘ ሲሆን ይህም በኢትዮጵያ እግር ኳስ እጅግ የላቀ ነው። ፕሪሚየር ሊግ (1997- አሁን) በጥቅምት ወር 2020 የጀርመን አሰልጣኝ ኤርነስት ሚድንድዶር የ 3 ዓመት ኮንትራት ከፈረሙ በኋላ ከካይዘር አለቆች ኤፍ.ሲ ወጥተው ክለቡን ተቀላቀሉ። እ.ኤ.አ ኖቬምበር 2020 ሚድንድዶር በኢትዮጵያ የፖለቲካ አለመረጋጋት ስጋት የተነሳ ከስልጣናቸው ለቀቁ ፣ በምክትላቸው አሰልጣኝ ማሃየር ዴቪድ ተተክተዋል። ዴቪድ በ 15 ግጥሚያዎች ላይ ብቻ በመጋቢት 2021 የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ሆኖ ተባረረ። እሱን ለመተካት ስኮትላንዳዊው ፍራንክ ኑትታል ተቀጥሮ ቡድኑን በሊጉ ወደ አሳዛኝ ሦስተኛ ደረጃ እንዲመራ መርቷል። እ.ኤ.አ. በ 2021 ሐምሌ ክለቡ ሰርቢያዊው ዝላኮ ክሪምቶቲ አዲሱን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ቀጠረ። ክለቡ የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ማህበር ነው። እንዲሁም በገንዘብ የሚደገፈው በሳውዲው ታዋቂው ነጋዴ መሐመድ ሁሴን አል አሙዲ እና የክለቡ ሊቀመንበር በሆኑት ኢትዮጵያዊው አቤኔት ገብረመስቀል ነው። በሰኔ ወር 2018 ክለቡ አብዛኞቹን የአክሲዮን ድርሻ ለደጋፊዎች እንደሚሸጥ ተገለጸ። በኖቬምበር 2020 ክለቡ ውስን አክሲዮኖችን በቀጥታ ከ 100,000 በላይ ለተመዘገቡ አባላቱ ለመሸጥ ዕቅድ ያለው የአክሲዮን ኩባንያ ማቋቋሙን አስታውቋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በሁሉም የኢትዮ እግርኳስ ትልቁ የደጋፊ መሰረት ያለው ሲሆን በሀገር ውስጥ ጨዋታዎች በሚያደርጉት ደማቅ ማሳያ ይታወቃሉ። የቡድኑ ኦፊሴላዊ የደጋፊ ክለብ 32,000 የተመዘገበ አባል ያለው ሲሆን በአድናቂው ክለብ በተደረጉ ጥናቶች መሠረት በመላው አገሪቱ እና በኢትዮጵያ ዲያስፖራ 8 ሚሊዮን የሚገመቱ ደጋፊዎች አሉ። ብዙ ጊዜ የክለቡን መዝሙር በመዘመር ቢጫ እና ብርቱካንማ የቼክ ባንዲራዎችን በማውለብለብ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች በኢትዮጵያ እግርኳስ ውስጥ አንዳንድ የበዓል አከባቢዎችን ያቀርባሉ። የክለቡ አልትራሎች በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ በጣም ተስፋፍቶ በሚገኝ ሆሎጋኒዝም ውስጥ እንደሚሳተፉ ታውቋል። በተለይ እንደ “ሸገር ደርቢ” ባሉ የደርቢ ጨዋታዎች ወቅት ከተፎካካሪ የድጋፍ ቡድኖች ጋር ግጭቶች የተለመዱ ናቸው። በመጀመሪያዎቹ ቀናት የክለቡ ደጋፊዎች ይደጋገሙ የነበሩት የዘፈን ግጥሞች እንደሚከተለው ነበር። ቀደምት ተቀናቃኞቻቸውን “6 ኪሎ” በመጥቀስ - “ይጫወቱ ነበር በቴስታ በጋንባ ፣ መገን 6 ጥያቄን ለመውሰድ ገባ።” ትርጉሙ “6 ኪሎ ፣ በእግራቸው ቢጫወቱም እና ተጫዋቾችን በጭንቅላት ቢረግጡም ሁልጊዜ ይሸነፋሉ” መስራች አየለ አትናሽ በመጥቀስ። «ግጥም አይነቃነቅም የብረት ዲጂግኖ ፣ ለእናንተ ነህ አየለ የአራዳ ተርሲኖ?» ትርጉሙ “እንደ ብረት መስረቅ ጽኑ ፣ የአራዳ ቴርሲኖ አየለ አትናሽ እንዴት ነህ?” ድንቅ ተጫዋቾችን ኤልያስን (በኋላ አብራሪ ሆኑ) እና ይድነቃቸው። “በሰማይ ኤልያስ በምድር ይድነቃቸው ፣ ለመታሰቢያነት እግዜር ፈጠራቸው።” ትርጉም “ኤልያስ በሰማይ ፣ ይድነቃቸው መሬት ፣ እግዚአብሔር በግብር ፈጥሯቸዋል”። ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግን በተለያዩ አመታት አሸናፊ ሁንዋል። እነዚህም፦ 1950, 1966, 1967, 1968, 1971, 1975, 1987, 1991, 1992, 1994, 1995, 1996, 1999, 2000, 2002, 2003, 2005, 2006, 2008, 2009 (እ.ኤ.አ.) ናቸው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦች
13992
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%A3%E1%8B%AD%E1%89%B1%20%E1%89%A5%E1%8C%A1%E1%88%8D
ጣይቱ ብጡል
«ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። በልጅነት ዘመናቸው በዚሁ ደብር ውስጥ ዳዊትን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በጊዜው ይሰጡ የነበሩትን ሌሎች የሃይማኖት ትምህርቶች በየታላላቁ አድባራት በመዘዋወር ያጠናቀቁ ስለመሆናቸው ታሪክ አዋቂዎች ይናገራሉ። የተማሩባቸውም መፃሕፍት ተጽፈው ይገኙ የነበረበትን የግዕዝ ቋንቋ አጣርተው ያውቁ ነበር። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። ከንጉሥ ምኒልክ ጋር ጋብቻ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው የፋሲካን በዓል በባሕር ዳር አቅራቢያ ሱሉልታ ላይ ዋሉና ደብረ መይ በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከዚያም ዋና ከተማቸው ወደነበረችው ደብረ ብርሃን ተመልሰው መጡ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ። አፈወርቅ ገብረ ጊዮርጊስ “ዳግማዊ አጤ ምኒልክ” በተባለው መጽሐፋቸው ገጽ ፴፱--፵፩ ላይ “ከልዢነት ጀምረው ሲመኟት እንደ ህልም ሲአልሟት ትኖር የነብረችው ጣይቱ ብጡል በ፲፰፻፸፭ ዓ/ም ደብረ ብርሃን ገባች ንግሥተ ሸዋ ሆነች ወዲያው የፋሲካ ለት አንኮበር መድኃኔ ዓለም ቆርበው ሁለቱ ተጋቡ። … ፀሐይቱ ለማለት ጣይቱ ተባለች ነገር ግን ከጣይቱ እጣይቱ ለመባል ይገባታል።” ይላሉ «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» ዘውድ ጫኑ ንጉሡ «አፄ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ» የሚለውን ስም በተቀዳጁ በማግሥቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፹፪ አ/ም ወይዘሮ ጣይቱ ብጡል እቴጌ ተብለው ተሰየሙ። የስርዓተ ዘውዱ አፈፃፀም በከፍተኛ መሰናዶ የተጠናቀቀ በመሆኑ እጅግ ደማቅ እንደነበር ከተፃፉ ፅሁፎች ለማወቅ ይቻላል። እቴጌ ጣይቱም ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ ከንጉሠ ነገሥቱ እጅ የተቀበሉትን ዘውድ ደፉላቸው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በታወቁበት «እቴጌ ጣይቱ ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል የክብር ስም ማኅተም ተቀረፀላቸው። እነዚሁ ታሪካዊ ሂደቶች እቴጌይቱን በኢትዮጵያ ዱኛዊ፣ ወታደራዊና ማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ከፍተኛና ብሩህ ሚና ለመጫወት የቻሉ አድረገዋቸዋል። የዱኛ (ፖለቲካ) ተግባራት እቴጌ ጣይቱ በዱኛ አስተዳደር አንፃር የነበራቸው ችሎታና ተግባራዊ እንቅስቃሴ በታሪክ አዋቂዎች ዘንድ ተደናቂነትን አትርፎላቸዋል። በየጊዜው ይነሱ በነበሩ የሀገር ጉዳዮች ላይ ይይዙት የነበረው አቋም፣ ይሰጡት የነበረው ውሳኔና ያስተላልፉት የነበረው ትዕዛዝ ተሰሚነትና ተቀባይነት እያገኘ እንደመሄዱ መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ይሄድ ለነበረው የዱኛ ሥልጣናቸው ዓይነተኛ ምክንያት ነበር። እቴጌ ጣይቱ በኢትዮጵያ ዱኛ ተሳትፏቸው የገነነውና በአገር አስተዳደርም ውስጥ ከፍተኛ ሚና መጫወት የጀመሩት ኢትዮጵያ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፹፩ ዓ/ም በውጫሌ ላይ ከኢጣሊያ ጋር በተፈራረመችው ውል ውስጥ በጣልያንኛው ትርጉም ሀገሪቷን ነፃነት እንደሌላት ጥገኛ በማስመሰል ዓላማ ላይ የተመረኮዘ ውንብድና መኖሩ ከታወቀ ወዲህ ነው። ይህ ለአድዋ ጦርነት መነሳት ምክንያትና ዋነኛ መንስዔ የሆነው ጉዳይ ሊታወቅ የቻለው እቴጌ ጣይቱ የውጫሌው ውል አንቀፅ ፲፯ ላይ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ የተባሉት ቋንቋ አዋቂ ዓፄ ምኒልክ በሰጧቸው ትዕዛዝ መሠረት የውሉን ሰነድ በመመርመር የውሉ አስራ ሰባተኛው አንቀፅ የያዘውን የትርጉም መዛባት በመግለፅ ጉዳዮ ኢትዮጵያ የምትጐዳበት ስለመለሆኑ ጭምር በማስረዳት በሰጡት ቃል ሲሆን እቴጌ በዚህ ወቅት ነገሮችን በጥንቃቄ የሚከታተሉ ስለነበር ዓፄ ምኒልክ በመጀመሪያ ሳይረዱ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ እንዲታሰሩ ቢያደርጉም እቴጌ ጣይቱ ግን እኒህ ሰው ትክክለኛ የኢትዮጵያ ወዳጅ መሆናቸውን ለዓፄ ምኒልክ በማስረዳት ከሦስት ዓመታት እስራት በኋላ ማስፈታቸው ይታወቃል። በዚህ በኩል ሲታይ እቴጌ ጣይቱ የምኒልክ የቅርብ አማካሪ በመሆን በፖለቲካ ተግባሮች ምን ያህል አስተዋፅኦ እንዳበረከቱ መገንዘብ ይቻላል። እቴጌ እንደተናገሩትም «ዓፅመ ጊዮርጊስ ቢታሰር ቢፈታም ለሀገሩ የሚገባውን ሠርቶ ነው። ኧረ ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ዮሴፍ፣ ጣሊያኖች በተንኮል ገብተው በማታለል ይህን የመሰለ ሥራ ሲሠሩ አነጋጋሪ ሆኖ ሳለ እንዴት ሳይስጠነቅቅዎ ቀረ?» በማለት የእቴጌ ጣይቱ የቁጣ መዓት ወደ ዮሴፍ ዞረ። ከዚያም ጨምረው «ከእንግዲህ ወዲህ የኢትዮጵያን ጥቅም የሚነካ፣ ሥር የሚነቅል፣ መሠረት የሚያፈርስ ጉዳዮን ሁሉ እኔ ሳላየው እንዳያልፍ ይፍቀዱልኝ» ብለው ለንጉሡ ባመለከቱት መሠረት ይኸው አንቺ ሳታይው ሳትመረምሪው አያልፍም በማለት ፈቀዱላቸው፣ ይህ እንደሚያመለክተው እቴጌ ጣይቱ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበራቸውን ተገቢ ቦታ የሚያመለክት ነው። ውሉንም ለማስተካከል ዓፄ ምኒልክ ያደረጉት የዲፕሎማቲክ ጥረት ውጤታማ ሊሆን ባለመቻሉ ሚኒስትሮች የጦር አለቆችና መኳንንት የሚገኙበት ጉባዔ እንዲጠራ አደረጉ። እያንዳንዱ ሰው ስለተነሳው ችግር ያለውን አስተያየት ሀገር ፍቅር በተሞላበት አንደበትና የጋለ መንፈስ ሲገለፅ ቆየ። እቴጌ ጣይቱም በበኩላቸው «እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም። ሆኖም ይህን ኢትዮጵያን የኢጣሊያ ጥገኛ የሚያድርግ ውል ከመቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ» ብለው በታሪክ ቅርስነቱ በማንኛውም የሀገሪቱ ትውልድ ትተውት ያለፉት አባባል ዘመን ተለውጦ ዘመን እየተተካ በሄደ ቁጥር የሚነገር በመሆኑ የእቴጌን ጀግንነት የቁርጠኛ ኢትዮጵያዊ ልጅ ለመሆናቸው ሌላ ማረጋገጫ ማቅረብ አያስፈልግም። እቴጌ ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌን አተኩረው በማየት በታወቀው ጀግና አንደበታቸው የተሰበሰበውን ሕዝብ ስሜት ለመቀስቀስ ድምፃቸውን እንዲያሰሙ ማድረጋቸው ይነገራል። እሳቸውም፦ «መልኩ ከመልካችን የማይመሳሰል እግዚአብሔር በባህር ከልሎ የሰጠንን አገራችንን የሚቀማ ጠላት መጥቶ እንዴት ዝም እንላለን እንዋጋለን እንጂ» በማለት የሀገሪቱን ቁንጅና ልምላሜ የምታፈራውን የእህልና የከብት ዓይነት እየጠቃቀሱ በማንሳት «ኧረ ለመሆኑ ተራራው ሸለቆው ወንዛወዙ ጨፌው ሜዳው ማነው ቢሉት የማነው ብሎ ሊመልስ ነው እንገጥመዋለን እንጂ!» በማለት የተሰበሰበውን ሕዝብ ልብ የሚነካና ወኔውን የሚቀሰቅስ ንግግር በማድረግ የተዋጣ የቅስቀሳ ችሎታቸው በአገኙት መድረክና አጋጣሚ የሚጠቀሙ አንደበተ ርቱዕ ነበሩ። ስለ እቴጌ ጣይቱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በምሳሌነት ሊቀርብ የሚችል ሌላ ዓይነተኛ ታሪክ ዓፄ ዮሐንስ በሞቱ በአንድ ዓመታቸው በመጋቢት ፲፰፻፹፪ ዓ/ም ዓፄ ምኒልክ አገሩን ለማረጋጋት ሲሉ መሃል ትግሬን ለመጐብኘት በሄዱ ጊዜ እቴጌ ጣይቱ ለሸዋም፣ ለወሎም፣ ለበጌምድርም፣ ለየጁም መካከል በሆነችው ደሴ ከተማ ሆነው አገሩን እንዲጠብቁ በማለት ትተዋቸው እንደሄዱ እዚያ ሆነው ያከናወኑት ተግባር የረጋ አስተዋይና የተዋጣላቸው ዲፕሎማት አሰኝቷቸዋል። በተለይም በሁለት የጦር አበጋዞች መሃል የሚፈጠር አለመግባባትን አግባብቶ በመፍታት በኩል ተወዳዳሪ አልነበራቸውም። እቴጌ ጣይቱ ከሕዝቡ ጋር በነበራቸው ግንኙነት በተለይም ያሳዩት በነበረው ርህራሄና ልግስና በጣም የተወደዱና የተመሰገኑ በመሆናቸው በሚያውቋቸው ዘንድ በሰፊው ይወራላቸዋል። ግልፅ የሆነው የፖለቲካ አስተያየታቸውና ጽኑ የሆነው ተግባራዊ ውሳኔያቸው፣ ዘዴንና ሥልጣንን እንዲሁም ምክርን ኃይልን ምን ጊዜ በእንዴት ያለ መጠን መጠቀም እንዳለባቸው በትክክል የመገመት ችሎታቸው ሲታይ በዓለም ከታወቁት የፖለቲካ አርበኞች ውስጥ ሊወሳ የሚገባ ታሪካዊ ስፍራ እንዳላቸው አጠራጣሪ አይሆንም። ስመ ጥሩነታቸውን ለማትረፍ ካስቻላቸው ጉዳዮች ጽኑ በሆነ መንፈሳዊ ኑሮአቸው አኳያ የሚታየው የልግስናና የቤተ ክርስቲያን ነፃ ተግባሮች አንዱና ዓይነተኛው ነው። ይህ ከሃይማኖት መሪዎች ጋር ልዩ ግንኙነት ለመመስረት ያስቻላቸው ከመሆኑም በላይ የፖለቲካ ሥልጣናቸውን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳደረገ ከሌሎች ታላላቅ የፖለቲካ ሰዎች ታሪካዊ አነሳስ ለመገንዘብ ይቻላል። በዚህ በኩልም እቴጌ ጣይቱ ብጡል በማህበራዊ ህይወት ሲያደርጉ የነበሩት በጐ ተግባር በመንፈሳዊ ኑሮአቸው በእምነቱ ተከታዮች ያላቸው ተቀባይነትም እጅግ የጐላ እንደነበረ የሚታወቅ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ለየካ ቅዱስ ሚካኤል ሠላሳ ጋሻ መሬት፣ ለሐመረ ኖህ ኪዳነ ምሕረት አሥራ ስድስት ጋሻ መሬት የሰጡት ለአብነት ያህል የሚጠቀሱ ናቸው። እቴጌ ጣይቱ ለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች መረጋጋት የሚያረጋግጥ የሀገር ግንባታ ተግባሮች በማከናወን ረገድና የአዲስ አበባ ከተማ መቆርቆር በእቴጌ ጣይቱ ከተጠናቀቁት የግንባታ ተግባሮች አንዱ ነው። በመሆኑም የአዲስ አበባ ስም በተጠራ ጊዜ እቴጌ ትዝ የሚሉን ሲሆን በዚሁ በአዲስ አበባ በከፍተኛ ቀበሌ ፲፪/ፒያሳ/ አካባቢ የሚገኘው የከተማዋ የመጀመሪያው ሆቴል «ጣይቱ ሆቴል» የቅርብ ትዝታችን ነው። ምንም እንኳን እቴጌ ጣይቱ የተቀረፀላቸው ሐውልትና ለትውልድ የሚተላለፍ ስማቸውን የሚያስጠራ ልጅ ባለመውለዳቸው /መሐን/ ቢሆኑም የዓፄ ምኒልክን ልጆች አክብሮታዊ ፍቅር ሳይለያቸው ቤተሰባዊ ፍቅርን የተላበሱ እንደነበረ ከተለያዩ መፃህፍት ለመረዳት ይቻላል። የሕይወት ጓዳቸው የሕይወት ፍጻሜ እቴጌ ጣይቱ ባለቤታቸው ዓፄ ምኒልክ በጽኑ በታመሙበት ዘመን ከጭንቀታቸው የተነሣ የሚከተለውን ረጅም ደብዳቤ ለጀርመን ንጉሥ እንደላኩ በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል፡፡ በ፳፻፪ ዓ/ም "አስደናቂዎቹ የነገሥታትና የመሳፍንት ደብዳቤዎች" በሚል ርዕስ በታተመው መጽሐፍ ውስጥ የእቴጌ ጣይቱ ደብዳቤ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ "ይድረስ ከክቡር ወዳጃችን ከዳግማዊ ዊልሄልም የጀርመን ንጉሠ ነገሥት፡፡ የተላከ ከእቴጌ ጣይቱ ብርሃን ዘኢትዮጵያ፡፡ ሰላምና ጤና ለእርስዎ ይሁን፡፡ በብዙ ማክበርና በትሕትና ይህንን ደብዳቤ ልጽፍልዎ አሰብሁ፣ ስለዚህ ይህንን የደረሰብኝን የሚያሳዝን ነገር ደፍሬ ልጽፍልዎ የግድ ሆነብኝ ልታገሰው አልተቻለኝምና፡፡ ስለ አጤ ምኒልክ ጤና መጉደል፤ ጌታዬን፣ ወዳጄን አጣቸው ይሆን ብዬ አጥብቄ ተጨንቄአለሁ፡፡ ለሴቶች ካባት ከናት ከልጅ ከወንድምም የጮኛ ነገር ጭንቅ እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ ስለዚህ የጀርመን መንግሥት ሐኪም የጥብቅ ረቂቅ ብልሃት ስመ ጥሩነቱ አስከኔ ደርሶ ንጉሠ ነገሥቱ ተፈውሰው እንደቀድሟቸው ሆነው ለማየት የተቃጠለ ምኞቴ እንዲፈጸምልኝና በብርቱ አጥብቆ ለሚወዳቸውም ሕዝባችን ንጉሡ በሕይወት እንዲቆዩለት ለመፈወስ የሚያስፈልግ ነገር ሳይደረግላቸው እንዳይቀር ብለን የጀርመንን ስመጥሩ የጥበብ ረቂቅ ብልኃት እረዳትነት ለመንን፡፡ ንጉሡ በቸርነትዎ ሐኪሙንም ምክር የሚረዳንንም ይስደዱልን ያልነውን ዶክቶር ዲንትግራፍን ጨምረው ሰደዱልን፡፡ እነሱም በመምጣታቸው እኛንም ሠራዊታችንንም እጅግ ደስ አለን፡፡ ነገር ግን እንደተመኘነው ሳይሆንልን ቀረ፡፡ አለመሆኑንም ለማስረዳት ከዚህ ቀጥሎ በሚጻፈው ቃል አስታውቃለሁ፡፡ ሐኪሙ ዶክቶር ስትይሂክለር በሚያዝያ ፳፪ ቀን ገቡ፡፡ ከዚያም አንስቶ እስከ ግንቦት ፲፭ቀን ጧት ማታ እየተመላለሱ፣ ለንጉሥ መድኃኒቱን ሲያደርጉ ሰነበቱ፡፡ በግንቦት ፲፭ቀን ግን በንጉሠ ነገሥቱ ደም የመርዝ ፍለጋ አገኘሁ ይጠንቀቁ ብለው ለኔ ነገሩኝ፡፡ እኔም ባጤ ምኒልክ መርዝ ማን ያደርግባቸዋል፡፡ ይህ ነገር አይጠረጠርም አልሁ፡፡ ሐኪሙም ከወጥ ቤት ዕቃም ከምንም ከምን እድፍ መጠንቀቅ ነው አሉ፡፡ የከበሩም እጮኛዬ ሕመምዎ ከጀመረዎ ቀን አንስቶ እስካሁን ድረስ የዛሬው ሰዓት በኔ ዘንድ የተወደዱ ስለሆኑብኝ፣ ያለዕረፍት በብርቱ ትጋትና ጥንቃቄ ከብቤ ጌታዬን የማስታምምዎ እኔው ራሴ ነኝና፣ የሐኪሙን ትእዛዝ ሁሉ መፈጸሙን ተደላድዬ ማስረዳት የሚቻለኝ ስለሆነ ይህንንስ እሺ የሚሰናዳውም ምግብ ሁሉ ከኔ ቤት ነው አልሁ፡፡ ከዚያም ወዲህ ዳግመኛ መርዝ አገኘሁ ብለው አልነገሩንም፡፡ እንደፊተኛው መድኃኒቱን ሲያደርጉ ቆዩ፡፡ ዶክቶር ዲንትግራፍም እሳቸው ያሉትን ሁሉ አድርገን ለሳቸው የሚመቻቸውን ማለፊያ የተሰናዳ ቤት ሰጥተን አክብረን አስመችተን አኑረናቸው ነበር፡፡ በሐምሌ በ፱ ቀን ግን ዶክቶር ዲንግራፍም ሐኪሙን ይዘው መጥተው የኛ መኳንንቶችና ሠራዊት ከተሰበሰበበት ላይ በንጉሡ ክፉ ነገር ተደርጎባቸዋልና በብርቱ የታመኑትን አገልጋዮቻችንን፣ እጃቸውን ተይዘው ይመርመሩ፡፡ ይህ ካልሆነ ሐኪሙ ገብተው መድኃኒት አያደርጉም ብለው ከለከሉ፡፡ በበነጋውም ዶክቶር ዲንትግራፍ ከንጉሥ ልገናኝ ብለው ላኩ፡፡ እኛም እሺ ብለን ፪ታችንም ፩ ላይ ሁነን ጠራናቸው፡፡ እሳቸውም እነዚህ ሰዎች እጃቸው ተይዘው ይመርመሩ አሉ፡፡ የታመኑ አሽከሮቻችን ናቸው፡፡ አይጠረጠሩም፡፡ እጃቸው ተይዘው የሚመረመሩት ምንድነው ብንላቸው ተይዘው ካልተመረመሩ ሐኪሙ አይገቡም አሉ፡፡ ደግሞ በበነጋው ምንስቲሩን ሙሴ ሽለርን ጠርተን እነዚህ ፪ቱ ሹሞቻችንን ይያዙ ያሉበት ምንድነው ነገሩ ብለን ብንጠይቃቸው በንጉሡ ምግብ ውስጥ መርዝ ተገኝቷል፡፡ በመብልና በመጠጥ ውስጥ ሆኖ ንጉሡን አልጎዳቸውም እንጂ ሐኪሙ አግኝተዋል፡፡ ብለው ነገሩን፡፡ እኔም ለምንስቲሩ ንጉሥ የሚመገቡት ሁሉ የሚሰናዳ ከኔ ቤት ነው የኔ ሹሞች ናቸው የሚያሰናዱ፡፡ እነዚህ ሰዎች ግን በኔ ቤት በምንም በምን አይደርሱም ብዬ አስታወቅሁ፡፡ ንጉሡም እነዚህ ሰዎች በዚህ ነገር አይጠረጠሩም ሥራቸው አይደለም ብለው ተናገሩ፡፡ ሕዝቡም አጤ ምኒልክ እንደነፍሱ እንዲያውም ከነፍሱ አልቆ እንዲያፈቅረዎ ንጉሡም በሕዝቡ አክብሮትና አፍቅሮት መከበብዎን ተደላድዬ አውቃለሁና ይህኑን ሥራ በሕይወታቸው ላይ ሊሠራባቸው ማንም የሚችል ሰው የለም፡፡ ሚኒስትሩ ግን ምንም ቢሆን እነዚህ ሰዎች ካልወጡ አይሆንም ንጉሥን የሚጠብቅ ሐኪሙ ሌላ ሰው መርጠው ያግቡ አሉ፡፡ ሐኪሙም እንደዚሁ እነዚህ ሰዎች ካልወጡ አልገባም ብለው ቀሩ፡፡ እኔም በዚህ ነገር እኔን የሚጠብቅ ሌላ ሹም መቀበሉ ታላቅ ሸክም ሆነብኝ፡፡ በገዛ ሰውነቴ ላይ መርዝ በማድረግ መጠርጠር አይቻልምና፡፡ ደግሞ የዚያኑለት ማታ ዶክተር ዲንትግራፍ እነዚህ ሰዎች ካልተሻሩና ካልወጡ እኔ አልቀመጥም ብለው የሰጠናቸውን ቤት ለቀው ሄዱ፡፡ እዚያም ከሄዱ በኋላ እነዚህ ሰዎች ካልወጡ፣ እኔን አሰናብቱኝ ብለው ወደ ንጉሡ ወረቀት ጻፉ፡፡ ንጉሥም አንተም ልሰናበት ያልክበት፣ እነዚህስ ሰዎች የሚወጡበት ብልሃቱ ካልተገለጠ እንዴት ይሆናል አንተው ይመርመሩ ባልክበት ነገር በ፳ ሐምሌ ማክሰኞ እንድትመጡ ብለው ላኩባቸው፡፡ በዚያው ለነሱ ባስታወቅንበት ቀን አባታችን አቡነ ማቴዎስም በከተማም ያሉት ሐኪሞች የኛም መኳንንቶች ሁሉ ተሰብስበው ከ፬ እስከ ፯ ሰዓት ሲጠብቁ ውለው እነሱ ሳይመጡ ቀሩ፡፡ የተሰበሰበውም ሰው በየቤቱ ገባ፡፡ ዶክተር ዲንትግራፍም ዳኛውስ ማነው ስፍራውስ ወዴት ነው ብሎ ሳይመጡ ቀሩ፡፡ ሐኪሙም እነዚህ ሰዎች ፈጽመው ካልተከለከሉ እኔ አልገባም ደግሞም ስገባ እኔ የምወደውን አስተርጓሚ ይዤ ነው የምገባ ውሌ ይህ ነው ብሎ ወረቀት ጻፉ፡፡ በዚህ ምክንያት ወደፊትም እንዲያስታምሙልን እርዳታቸውን ለመፈለግ የማይመቸን የማይመስለን ሆነብን፡፡ ደግሞ ፫ተኛ እነዚህ ሰዎች ከዚህ ተከልክለው ወደሌላ አገር ካልሄዱ እኔ አልኖርምና አሰናብቱኝ ብለው በራስ ቢቶደድ ተሰማ እጅ ወረቀት ላኩ፡፡ ንጉሥም እኔም በነዚህ በሰዎች በሹመት ነገር ሌላ የተመቀኛቸው ሰው ተነስቶ አስወጡልን ያላቸው ሰው ይኖር ይሆን እነዚያማ ከመጡ ጥቂት ነው አገሩን አያውቁት ሰውን አለመዱት ከነሱም ጋር ጠብ የላቸውም ይህ ነገር ምን ይሆን ብለን ገረመን፡፡ ከዚህ በኋላ ይህ ካልሆነ አሰናብቱኝ ብለው ፫ጊዜ ወረቀት ላኩ፡፡ ከዚህማ ወዲያ አላሰናብትም አሉኝ ብለው ወደ መንግሥታቸው የላኩት እንደሆነ የከበሩ ንጉሠ ነገሥት ወዳጄ ይቀየሙኛል ብለው ለዶክተር ዲንትግራፍ ይመርምሩ ብትሉ እሺ ብለን ቀን ቆርጠን ብናስታውቃችሁ ሳትመጡ ቀራችሁ፡፡ እኔ የማምናቸውን ያሳደግኋቸውን የሾምኋቸውን ሹማምንቶቼን ከዚህ ወጥተው ወደ ሌላ አገር ካልሄዱ ከነሱ ጋራ ለመኖር አይሆንልኝም ብለህ መሰናበትህን ከወደድህ እሺ አሰናብቼሃለሁ ብለው ጻፉለት፡፡ በዚህ በኛ ዘንድ ያሉን ምንስቲሩ ሙሴ ሽለር ግን መልካም ሰው ናቸው ዳሩ ግን ነገሩን መርምረው ለኛ ባለማስታወቃቸው አዘንን፡፡ ስለሆነም የተመኘነውን ፈቃዳችንን ለመፈጸም ብለው በታላቅ ቸርነትዎ ላደረጉልን በጎ አድራጐት እኔው እራሴ በፍጹም ልቤ ግርማዊ ሰውነትዎን አመሰግናለሁ፡፡ ይህንን ሁሉ ነገር መጻፋችን እነሱን ለማዋረድ ብለን አይደለም። የንጉሡ ልቡና እንዳይቀየምብን ብለን ነው እንጂ፡፡ ዳሩ ግን አንድነት የማያዋህደንን ታላቁን ፍቅራችንን ለማሰናከል ይህ ትንሽ ነገር ምክንያት ይሆናል ተብሎ አለመጠርጠሩ ግልጥ ነገር ነው፡፡ የንጉሡ ፈቃድዎ ቢሆን ከዚህ በኋላ ሁሉንም ነገር ለሚጠይቋቸው ምላሽ የሚናገሩ ከኛ ዘንድ መልዕክተኞች ለመስደድ እንመኛለን፡፡ ነገሩ ብዙ ስለሆነ በወረቀት አይጠቀለልምና ፊት ከሙሴ ሮዝ ጋራ መጥተው የነበሩት ሐኪም ሀንስ ቮልብረሽት ለኔም መድኃኒት አድርገውልኝ አድነውኝ ነበርና ዛሬም ለጥቂት ቀን እንዲመጡልን እንመኛለን፡፡ የከበሩ ንጉሠ ነገሥትም በቸርነትዎ ይሰዱልናል በማለት ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ለእሰዎ እድሜና ጤና ለሕዝብዎም ሰላምና ዕረፍት እንዲሰጥልን እግዚአብሔርን እንለምናለን፡፡ ነሐሴ ፲፩ ቀን ፲፱፻፩ ዓመተ ምሕረት አዲስ አበባ ተጻፈ፡፡ ደብዳቤው ማኀተም አለው፡፡ ማኀተሙ በግዕዝ እንደተቀረጸው ዝማኅተም ዘእቴጌ ጣይቱ ብርሃን ዘኢትዮጵያ ይላል፡፡ የሥልጣን ፍጻሜ ባላቸው ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ከሞቱ በኋላ በልጅ እያሱና በደጃዝማች ተፈሪ መኮንን መካከል በተፈጠረው የሥልጣን ሽኩቻ አማካኝነትና ባስከተለው በጦሩ መሃልም መከፋፈል በመታየቱ በልጅ ኢያሱ አስተዳደር ዘመንም እቴጌይቱ ከቤተ መንግሥት ተወግደው በግዞት ላይ ለአንድ ዓመት ከመንፈቅ ከሃያ ሁለት ቀናት ተቀመጡ። ሆኖም ታማኝ አሽከሮቻቸውና መላው ሠራዊት የእቴጌነታቸውን ልዕልና አላጐደለባቸውም። መሳፍንቱ መኳንንቱና ወይዛዝርቱም ቢሆን ተገቢውን አክብሮት ሳይነፍጓቸው ዕለት በዕለት ይጠይቋቸው ነበር። አቤቶ ኢያሱም ቢሆኑ የተለያዩ ስጦታዎችን ይዘው በመሄድ ይጠይቋቸው ነበር። የጦር ሚኒስትሩ ፊታውራሪ ሀበተ ጊዮርጊስ ዲነግዴም የተለያዩ እጅ መንሻ ይዘው ይጠይቋቸው ነበር። የልጅ እያሱ ሥልጣን ብዙም ሳይቆይ ከላይ በተገለጸው ‘የሥልጣን ክርክር’ ተሸንፈው መስከረም ፲፯ ቀን ፲፱፻፱ ዓ/ም የሚኒስትሮች ካቢኔ ወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክ ንግሥተ ነገሥታት ተብለው መንግሥቱን በመምራት እንዲተኳቸው መደረጉ ለእቴጌ ጣይቱ ታላቅ ድል ሆነ። በመሆኑም የእቴጌም የእስራት ቀንበር ሦስት ወር ባልሞላ ጊዜ ሊወድቅላቸው ቻለ። ንግስት ዘውዲቱ ሥልጣናቸው ተዳክሞ ትዕዛዛቸው እንዳይዛባ በማለት ከተጋዙበት ከእንጦጦ ሳይቀር ምክር መለገሳቸውን አላቋረጡም ነበር። እቴጌ ጣይቱ የደረሰባቸውን ፈተና ሁሉ በትዕግስት ተቀብለው ጥቂት እፎይ ካሉ በኋላ ከዓፄ ምኒልክ ጐን ሆነው የኢትዮጵያን አንድነትና ጥንካሬ ለማረጋገጥ ሲታገሉ ያለፉት ዘመን ከዕለታት አንድ ቀን ትዝ ስላላቸው ከሰገነት ላይ ብቅ ብለው «ያ ቤት የትኛው ነው» ብለው ሲጠይቁ ከደንገጡሮቹ አንዷ «የእመቤቴ እልፍኝ ግምጃ ቤት ነበር» አለች። እሳቸውም ትንሽ ተከዝ ብለው ከቆዩ በኋላ ቀበል በማድረግ «ነበር ለካስ እንዲህ ቅርብ ኖሯል» አሉ ይባላል። እቴጌ ጣይቱ ሰኞ የካቲት ፬ ቀን ፲፱፻፲ ዓ/ም በመንፈቀ ሌሊት ህመም ፀንቶባቸው ከሚወዱትና ከሚወዳቸው ሕዝብ በሞት ተለዩ። የእረፍታቸውን ዜና የሀዘኑንም ሥነ ስርዓት ለማወጅ የቤተ መንግሥቱ መድፍ ሃያ አምስት ጊዜ ድምፁን አሰማ። በሀዘኑ ስርዓትም ላይ እቴጌ በአድዋ ጦር ሜዳ ላይ ያሳዩትን የቆራጥነትና የጀግንነት ሙያቸውን እየጠቀሱ በግጥም እየገለጡ በማሞገስ ይሸልሉ ይፎክሩና ያቅራሩ ነበር። የእቴጌም አስክሬን በወርቅ ሀረግ በተከበበ የእንጨት ሳጥን ተደርጐ በብረት ሳጥን ውስጥ ከገባ በኋላ በቀድሞ ቤተ ፀሎታቸው ውስጥ ሸራ ቤት እየተባለ ይጠራ በነበረው መንበረ ፀሐይ እንጦጦ ማርያም ቤት ውስጥ በታላቅ ክብር አረፉ። ለተሰበሰበው ሕዝብ ትልቅ ግብዣ ተደርጐ የቀብሩ ፍፃሜ ሆነ። እቴጌ ጣይቱ ከማረፋቸው አስቀድመው ለንግሥት ዘውዲቱ «ልጄ ማሚቴ ሆይ አደራዬን ሰጥቼሻለሁ» ብለው መናዘዛቸው በታሪክ ይወሳል። በዚሁ መሠረት ንግሥት ዘውዲቱ በታሕሣሥ ወር ፲፱፻፳ ዓ/ም የዓፄ ምኒልክን ዓፅም ከቤተ መንግስቱ አስወጥተው ለማረፊያው በታዕካ ነገሥት በዓታ ቤተ ክርስቲያን አሳንፀው በነበረ ጊዜ የእቴጌንም ዓጽም እዚሁ እንዲያርፍ ቢፈልጉም የእንጦጦ ማርያም ካህናት እቴጌ ጣይቱ ለኛም እናታችን ናቸውና መታሰቢያነታቸውን እንሻለን በማለት የተቃውሞ ድምፅ አሰሙ። ቢሆንም የኑዛዜውን ቃል አብራርተው በማስረዳታቸው ፈቅደውላቸዋል። በመጨረሻም የእቴጌ ጣይቱ፣ የዓፄ ምኒልክና የንግሥት ዘውዲቱ መካነ መቃብር በታዕካ ነገሥት በዓታ ቤተ ክርስቲያን ምድር ቤት ውስጥ በመንበሩ ትይዩ ሳጥኖች ተፈልፍለው በተሰሩ እብነ በረድ ታሽገው እንደቆዩ በወለሉ ላይ መደዳውን ተቀምጠው ይገኛሉ። እቴጌ ጣይቱ በሞት የተለዩዋቸውን የሕይወት ጓደኛቸውን ጥለው በግዞት እንዲቆዩ በተገደዱበት በእንጦጦ አፋፍ ላይ ሆነው አዲስ አበባ ብለው የሠየሟትን መዲና በዓይን በመቃኘት «ያ ቤት የትኛው ነው» ብለው የጠየቁት የምኒልክን መቃብር በዓይናቸው ሲፈልጉ ይሆን? የሰው ሕይወት ኃላፊ ነው፣ ታሪክ ግን ሠሪዋን ለዘላለም ታስታውሳለች። በዚያች ደቂቃ እቴጌ ጣይቱ ስማቸውን የሚያስጠራ ታሪካቸውን የሚያስታውስ አንድ የምኒልክ የደም ቋጠሮ ሀረግ ሳያሠሩ ማለፋቸው ሳያሳዝናቸው እንዳልቀረ መገመቱ ቀላል ነው። ይህንም ሀዘን ለግዞት ወደ እንጦጦ ከመውጣታቸው ጥቂት ጊዜ በፊት ሊሸኟቸው በተሰበሰቡት መኳንንትና ወይዛዝርት ፊት የገጠሙት ግጥም አንጀት የሚበላ ነበር። «ተወዶ ከመኖር ተጠልቶ መውለድ ማን ያይብኝ ነበር ይህን ሁሉ ጉድ» ብለው ባሰሙት ግጥም ነበር። ዋቢ ምንጮች ጳውሎስ ኞኞ፣ «አጤ ምኒልክ» (፲፱፻፹፬ ዓ/ም)፣ ገጽ ፬፻፹፫-፬፻፹፰ አፈወርቅ ገብረ ኢየሱስ፣ «ዳግማዊ አጤ ምኒልክ»፣ (1901 ዓ/ም) ሮማ፣ ሪፖርተር፣ “እቴጌ ጣይቱን በዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ስናስታውሳቸው” ጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ፣ «የ20ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ» አንደኛ መጽሐፍ፣ ፲፱፻፺፮ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሰዎች የኢትዮጵያ ነገሥታት
48570
https://am.wikipedia.org/wiki/Riuadusualihin%28%E1%88%AA%E1%8B%AB%E1%8B%B1%E1%88%B7%E1%88%8A%E1%88%82%E1%8A%95%29
Riuadusualihin(ሪያዱሷሊሂን)
ቅንነትና ታማኝነት ቅንነትና ታማኝነት** (ኢኸላስ) እንዲሁም ተነሳሽነት (ኒያህ በማንኛውም ንግግርና ተግባር ግልፅ ይሁን ድብቅ አላህ እንዲህ ብሉያል አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ አጥሪዎች፣ ቀጥተኞች ኾነው ሊግገዙት፣ ሶላትንም አስተካክለው ሊሰግዱ ዘካንም ሊሰጡ እንጅ ያልታዘዙ ሲኾኑ (ተለያዩ)፡፡ ይህም የቀጥተኛይቱ (ሃይማኖት) ድንጋጌ ነው፡፡ ( አልብይዮነህ) 5 አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጽሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ከእናንተ የሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ (አልሀጅ 37) በደረቶቻችሁ ውስጥ ያለውን ነገር ብትደብቁ ወይም ብትገልፁት አላህ ያውቀዋል፡፡ ( አል ኢምራን 29) 1, ዑመር ኢብኑ አልኸጣብ (ረ,ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልክተኛ (ሶ,ዐ,ወ)እንዲህ ብለዋል ስራ የሚለካው በሀሳብ (በኒይያህ ) ነው። ማንኛውምንም ሰው ያሰበውን ያገኛል ። ስደቱ ወደ አላህና መልክተኛው የሆነ ስደቱ ወደ አላህና መልክተኛው ነው የስደቱ ግብ አለማዊ ጥቅም (ዱንያ) ወይም አንዲት ሴትን ሊያገባት ከሆነ፣ ስደቱ ለተሰደደበት አላማ ነው ። ( ቡኻሪና ሙስሊም) ከሀዲሱ የምንማራቸው ቁምነገሮች አንድ ተግባር ከመከናወኑ በፊት መልካም ተነሳሽነት (ኒይያህ) አስፈላጊ እንደሆነ ዑለሞች ተስማምተውበታል ። የዚያን ተግባር ምንዳ ማግኘት ይቻል ዘንድ ። ግና ማንኛውንም ተግባር ተቀባይነት ይኖረው ዘንድ የግድ ኒይያህ ያስፈልገዋል ወይስ አያስፈልገውም? በሚለው ነጥብ ላይ ተወዛግበዋል የሻፊዒይ መዝሀብ ምሁራን እንደ ውዱእ ባሉ የዒባዳ ዝግጅቶችም ሆነ እንደ ሰላት ባሉ አከባዳወች ላይ ኒይያህ እንደ(ቅድመ መስፈርት) ነው ሲሉ የሀነፊይ መዝሀብ ምሁራን ደግሞ በዒባዳወች ላይ እንጂ ለዒባዳ በሚደረጉ ዝግጁቶች ላይ ኒይያህ እንደማያስፈልግ ይናገራሉ። _ የኒይያ ማእከል ቀልብ (ልቦና)ነው። አንድን ተግባር ለማከናወን በልቦና ማሰቡ ብቻ በቂ ነው።መናገሩ አያስፈልግም ። ተግባርን ለአላህ ብቻ በ"ኢኽላስ" በቅንነት ማከናወንን ለተቀባይነቱ ዋስትና ይሰጣል።አላህ በርሱ ብቻ በቅንነትና በታማኝነት (ኢኽላስ) የተከናወነን ተግባር አንጅ አይቀበልም። 2።የሙእሚኖች እናት አኢሻ (ረአ)እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል የአላህ መልከተኛ ሶ,አ,ወ ካእባን ከማውደም የሚተም አንድ ሰራዊት ይዘምታል ከአንድ ምድረ በዳ መሬት ላይ ሲደርስ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ያሉት ሁሉም በመሬብት መሰንጠቅ ይዋጣሉ በማለት ተናገሩ እንዴት ከመጀመሪያው እሰወከመጨረሻው ያሉት ሁሉም በመሬት መሰንጠቅ ይዋጣሉ በማለት ተናገሩ። እንዴት በመሬት መሰንጠቅ እንዲዋጡ ይደረጋል ? በመካከላቸው የንግድ ሰወችና ሌሎችም (አላማቸው ከእባ ማፍረስ ያልሆኑ ሰወች እያሉ? አልኳቸው ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው (በሁሉም) ይዋጣሉ ከዚያም እንደየኒያቸው ይቀሰቀሳሉ በማለት ገናገሩ ( ቡኻሪ ሙስሊም የሀዲሱም ቃል የቡኻሪ ነው) 3, ዓኢሻ (ረ,ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልክተኛ ሶ,ዐ,ወ እንዲህ ብለዋል ከመካ (በድል) መከፈት ቡሀላ ስደት የለም ።ግና ጂሀድና ፣ኒይያህ ምንግዜም ይኖራሉ ። (ለጂሀድ) እንድትዘምቱ በምትጠየቁበት ጊዜ ዝመቱ።(ቡኻሪና ሙስሊም). ከሀዲሱ የምንማራቸው ቁምነገሮች አንዲት ሀገር ኢስላማዊ (ዳረል ኢስላም) ከሆነች ቡሀላ ወደ ሌላ ሀገር መሰደድ አይፈቀድም አንዲት አገር የኩፍር ሀገር ( ዳረል ኩፍር) እስከሆነችና ሙስሊሞች በዚያች ሀገር ላይ ኢስላምን ተግባራዊ ለማድረግ እስከተሳናቸው ድረስ ስደት ግዴታ እንደሆነ ይቆያል ወደ ጂሀድ ጥሪ በሚመጣበት ወቅት አፋጣኘ ምላሽ መስጠት ይቻል ዘንድ ሁሌም ጂሀድን ማሰብና ለጂሀድ ተገቢውን ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ ተገቢ ነው 4ኛ አቢ አብደላህ ኢብኑ ጃቢር ዐብደላሀደ አል አንሷሪይ (ረ,ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል በአንድ ዘመቻ ላይ ከነብዮ (ሶ,ዐ,ወ )ጋር ነበርን ። እንዲህ አሉ መዲና ውስጥ በሽታ (ከዘመቻ) ያስቀራቸው ሰወች አሉ ።መንገድን አልሄዳችሁም ፣ሸለቆንም አላቋረጣችሁም ከናንተ ጋር ቢሆን እንጂ በሌላ ዘገባ ደግሞ፡-"በምንዳ የተጋሯችሁ ቢሆን እንጂ" የሚል ተመልክቷል፡፡(ሙስሊም ዘግበውታል፡፡)ቡኻሪ አነስን ጠቅሰው እንደዘገቡት፡-"ከተቡክ ዘመቻ ተመለስን፡፡ ከነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር፡፡"ከኋላችን መዲና ውስጥ ችግር (ዑዝር) ከዘመቻያስቀራቸው ሰዎች አሉ፡፡ ጋራ ሸንተረሩን አላቆራረጥንም፥ከኛ ጋር የሆኑ ቢሆን እንጂ" በማለት ተናገሩ፡፡ (ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር- በአንዳች) አስገዳጅ ምክኒያት ከጅሃድ የቀረ ሰውመልካም ኒይያና ፍላጎት እስካለው ድረስ ጅሃድ ያደረጉሰዎችን ምንዳ ያገኛል፡፡ 5. አቡ የዚድ መዕን ኢብኑ የዚድ ኢብኑ አል-አኽነስ(ረ.ዐ) -እርሳቸውም፥ አባታቸውም፥ አያታቸውምሶሐባዎች ነበሩ- እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፡-አባቴ የዚድ ለምፅዋት የተወሰኑ ዲናሮችን አወጣናመስጊድ ውስጥ ለአንድ ሰው መፀወተ። መጣሁናአነሳኋቸው፥ ወደርሱም ይዣቸው መጣሁ፡፡ "በአሏህእምላለሁ! ለአንተ አላሰብኳቸውም ነበር" አለ፡፡መልእክተኛው (ሶ.ዐ.ወ) ዘንድ ሞገትኩ፡፡ "የዚድ ሆይ!ለአንተ ያሰብከው አለህ፥ (የኒይያህን ዋጋ ታገኛለህ፡፡)መዕን ሆይ! ለአንተ ደግሞ የያዝከው አለህ" አሉ፡፡(ቡኻሪና ሙስሊም)ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች- ሱንና የሆነን ምፅዋት ለልጆች መስጠት ይፈቀዳል፡፡ዘካን ግን ለልጆችም ሆነ ለወላጆች መስጠትአይፈቀድም፡፡- ሶደቃን በወኪል ማሰራጨት ይፈቀዳል፡፡ 6. ሰዕድ ኢብኑ አቢ ወቃስ (ረ.ዐ) - ጀነትከተመሰከረላቸው አስር ሰዎች መካከል አንዱ ናቸው-እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፡- የመሰናበቻ ሐጅ ዓመትወቅት ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ሊጠይቁኝ መጡ፡፡ ብርቱ በሽታአሞኝ ነበር፡፡ "በኔ ላይ የምታዩት በሽታ ደርሶብኛል፡፡በርካታ ንብረት አለኝ፡፡ ከአንዲት ሴት ልጅ ሌላ ወራሽየለኝም። የገንዘቤን ሁለት ሶስተኛ ልመፅውትን?"አልኳቸው። "አይሆንም" አሉኝ፡፡ "የአሏህ መልዕክተኛሆይ! ግማሹንስ?" አልኳቸው፡፡ "አይሆንም" አሉኝ፡፡"የአሏህ መልዕክተኛ ሆይ! ሲሶውንስ?" አልኳቸው፡፡"ሲሶ" ሲሶም ብዙ -ወይም ትልቅ- ነው፡፡ ወራሾችህን ሀብታሞች አድርገህ ማለፍህ ድሀዎችና የሰዎችን እጅየሚያዮ አአድርገሀቸው ከሞትህ የበለጠ ነው። የአላህውዴታ በመሻት አንድንም ምፀዋት አትማፀኑም ምንዳያገኝህበት ቢሆን እንጂ። በባሌ ቤትህ አፍበምታስቀምጠው (ጉርሻ) እንኳን ቢሆን ምንዳ ታገኛለህአሉ። ከባልደረቦቼ ተነጥዬ ወደኋላ እቀራለሁኝ አልኳቸውወደ ኃላ ተነጥለህ ቀርተህ የአላህ ውዴታ በመሻትመልካምን ተግባር አትፈፅምም።ደረጃና ልእልናንየጨመርክ ቢሆን እንጂ።ምናልባትም ከፊል ሰዎችእንዲጠቀሙበት ጠላቶች ደግሞ በአንተ (ሰበብ)እንዲጎዱ ወደ ኋላ ትቀር ይሆናል።አላህ ሆይ የባልደረቦቼን ስደት አፅድቅ ወደኃላ አትመልሰቸው አሉ።ነገርግን የሚያሳዝነው ሰአድ ኢብን ኸወይላህ ነው።ኘካውስጥነበር የሞተው ነብዮ (ሰ አ ወ) ዐ ጅግ ያዝኑለትና በሞትየመለየት ነገር ይሰማቸው ነነር።ቡኻሪ ሙስሊም) ።# ከሀዲሱ የምንማራቸው ቁም ነገሮችለመልካም አላማና ተግባር በሽታን ለሌሎች መናገርክልክልነት የለውም ለምሳሌ ፈውስ ወይም ዱአ በመሻት።ገንዘብን ሀላል በሆነ መንገድ መሰብሰብ ይፈቀዳልባለሀብቱ ሀላፊነቱ ጠብቆ እስከተወጣ ድረስ ሃብትማከማቸቱ ከጥፋት ሊቆጠር አየገባም ።አንድ ሰው ወራሽ እስካልፈቀደለት ድረስ ከገንዘቡ ከአንድሶስተኛ በላይ ኑዘዜ ማድረግ አይፈቀድለትም።ሰዎች በመልካም ኒይያን እና ተነሳሽነት ለሚፈፅሙትተግባር ሁለ ምንዳ ያኛሉ።የቤተሰብን ቁሳዊ ፍላጎት ማሟላትም መልካምን ኒይያከታከለበት ምንዳ ያስገኛል 7 •አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ (ሰ አወ) እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል አላህ ውጫዊ ቅርፅናውበታችሁ አይመለከትም ልቦናችሁ ነው የሚመለከተው።(ሙስሊም ዘግበውታል ። # ከሀዲሱ የምንማራቸው ቁም ነገሮችበስራ መጠቀምና አጅር ማግኝት የሚቻለው ተግባሩከመልካም ኒያዎች ጋር የተቆራኘ እንዲሆን ብቻ ነው።ልቦናን የአላህ ቁጣ ሊያስከትሉ ከሚችሉ በሽታዎች ሁሉለማፅዳት ጥረት ማድረግ ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠውየሚገባ ነው።ልቦናን የማፅዳቱ ተግባር ከሌሎች ተግባራት ይልቅቅድሚያ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ።ምክንያቱምለማንኛውም ስራ ና እንቅስቃሴ ተቀባይነት ማግኝትወይም ውድቀት መሆን ወሳኙ የቀልብ በአዳነት ወይምመበከልነውና። 8 አቡ ሙሳ ሙሳ ዐብደላህ ኢብኑ ቀይስ አል አሻሪይ ( ረ.ዐ) እንዳስተላለፊት :-የአላህ የአላህ መልዕክተኛ ሰ.ዐ.ወ ለጀግንነት ስለሚዋጋ ለዘር ክብር ስለሚዋጋ ለይዩልኝ (ለዝናና ክብር ሲል ስለሚዋጋ ሰው የትኛውም በአላህ ጎዳና ላይ እንደሆኑ ተጠየቁ:: "የአላህ ቃል:-ቃል የበላይ ትሆን ዘንድ የሚፋለም፤በአላህ ጎዳና ያለ እርሱ ነው" ሲሉ ተናገሩ:: ቡኻሪና ሙስሊም ከሐዲሱ የምንማረው ቁም ነገር አንድ ተግባር ከአላህ ዘንድ ሊያገኝ የሚችለው በጥሩ ኒይያህ ከተፈፀመ ብቻ ነው:: በአላህ መንገድ ላይ የአላህን ቃል የበላይ ለማስጠበቅ ሲፋለሙ ሰማእት የሆኑ ብቻ ናቸው በቁርአንና በሀዲስ የተጠቀሱ የሰማዕታት እጣዎች ሊጎናፀፉ የሚችሉት ግና ከፍልምያው መስክ ላይ የወደቀ ሁሉ እንደ ሰማዕት ይቆጠራል::አይታጠብም ከፈንም አይለብስም ልብሱ ይቀበራል የ"ኒይያህ"ጉዳይ ለአላህ የተተወ ነው:: 9 አቡ በክረት ኑፈይስ ኢብኑ አል-ሀሪስ ከሥ ሱቀፊይ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል:- ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)"ሁለት ሙስሊሞች ሾተል ከተማዘዙ፥ገዳይም ሟችም፥እሳት ውስጥ ናቸው"በማለት ተናገሩ:"የአላህ መልዕክተኛ ሆይ:ገዳይስ ይሁን የሟች ጥፋት ምን ሆኖ ነው:ለቅጣት የበቃው?::ስል ጠየቅኩ:: ወዳጁን ለመግደል ቋምጦ ነበር ሲሉ መለሱ:: ቡኻሪ ሙስሊም (ከሀዲሱ የምንማራቸው ቁም ነገሮች) ወንጀል ለመፈፀም የአላህን ህግጋት ለመተላለፍ የቆረጠና ለውጊያ የሚያበቁ ቅድመሁኔታዎችን ሁሉ ያሟላ ወንጀሉን ፈፀመም አልፈፀመም ከተጠያቂነት አያመልጥም:: 10. አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል:-"አንድ ሰው በጀመአ በህብረት የሚሰግዳት ሶላት ከስራ ቦታው ወይም ከቤተሰቡ ሶላት ከሀያ ሶስት እስከ ሰላሳ ብልጫ አላት ይህም የሚሆነው በተሟላ መልኩ ውዱዕ ከፈፀመና ከዚያም ሰላትን እንጂ ሌላን ባለመሻት ከቤቱ የወጣበት አላማ ሶላት ብቻ ሆኖ ወደ መስጊድ ከመጣ ነው: ወደ መስጊድ ከመጣ ነው:: ወደ መስጊድ በሚያደርገው ጉዞ በእያንዳንዱ እርምጃ አንድ ደረጃ ከፍ ይደረግለታል::በዚያችው እርምጃ አንድ ኅጥያት ይታበስለታል መስጊድ እስኪገባ ድረስ መስጊድ ከገባ በኋላ መስጊድ ውስጥ ለመቆየቱ ምክንያት ሶላት ብቻ እስከሆነች ድረስ ሶላት ውስጥ እንዳለ ይቆጠርለታል ከእናንተ አንዳቹ የሰገደበትን ቦታ እስካለቀቀ ሰዋችን እስካላወከና ውዱእ እስካልፈታ መላይኮች አላህ ሆይ ምህረትን ለግሰው አላህ ሆይ ጸጸቱን ተቀበለው እያሉ ዱዓ ያደርጉለታል (ቡሀሪና ሙስሊም የሀዲሱ ቃል የሙስሊም ነው) (ከሀዲሱ የምንማራቸው ቁም ነገሮች) - በስራ ቦታ ላይ ሶላት መስገድ ይፈቀዳል ምንም እንኳ ቅልብን ሰብስቦ ለመስገድ ስለማያስችል የሚጠላ - መስጊድ ውስጥ በጀመዓ (በህብረት) የሚሰገድ ሶላት ለብቻ ከሚሰገደው ሶላት በ25፣26 ወይም27 ደረጃዎች
36095
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%A5%E1%89%B5%20%E1%8A%A4%E1%88%8D%E1%88%A3%E1%89%A4%E1%8C%A5%20%E1%8B%B3%E1%8C%8D%E1%88%9B%E1%8B%8A%E1%89%B5
ንግሥት ኤልሣቤጥ ዳግማዊት
(ኤልዛቤት አሌክሳንድራ ሚያዝያ 12, 1919 - ጳጐሜን 3, 2014) የዩናይትድ ኪንግደም ንግሥት እና ከየካቲት 6 ቀን 1952 እስከ ዕለተ ሞቷ ድረስ የ 14 ሉዓላዊ አገሮች ንግሥት ነበረች። ሰባት ወር ከየትኛውም የብሪታንያ ንጉስ ረጅሙ ነበር። ኤልዛቤት የተወለደችው በሜይፌር፣ ለንደን፣ የዮርክ ዱክ እና ዱቼዝ የመጀመሪያ ልጅ (በኋላ ኪንግ ጆርጅ ስድስተኛ እና ንግሥት ኤልዛቤት) የመጀመሪያ ልጅ ስትሆን ነው። አባቷ በ1936 ወንድሙ ንጉስ ኤድዋርድ ስምንተኛ ከስልጣን ሲለቁ ኤልዛቤትን ወራሽ እንድትሆን አድርጓታል። በቤት ውስጥ በግል የተማረች ሲሆን በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ህዝባዊ ተግባራትን ማከናወን ጀመረች, በረዳት ግዛት አገልግሎት ውስጥ አገልግላለች. በኖቬምበር 1947 የግሪክ እና የዴንማርክ ልዑል የነበረውን ፊሊፕ ማውንባተንን አገባች እና ትዳራቸው በ 2021 ፊሊፕ እስከሞተበት ጊዜ ድረስ ለ 73 ዓመታት የዘለቀ ሲሆን አራት ልጆች ወለዱ: ቻርልስ, የዌልስ ልዑል; አን, ልዕልት ሮያል; የዮርክ መስፍን አንድሪው; እና ልዑል ኤድዋርድ፣ የቬሴክስ አርል እ.ኤ.አ. . ኤልዛቤት እንደ በሰሜን አየርላንድ በተከሰቱት ችግሮች፣ በዩናይትድ ኪንግደም የስልጣን ሽግግር፣ የአፍሪካን ከቅኝ ግዛት በመግዛት እና ዩናይትድ ኪንግደም የአውሮፓ ማህበረሰቦችን በመቀላቀል እና ከአውሮፓ ህብረት በመውጣት በመሳሰሉት ትልልቅ የፖለቲካ ለውጦች እንደ ህገ-መንግስታዊ ንጉስ ነግሳለች። ግዛቶች ነፃነት ሲያገኙ፣ እና አንዳንድ ግዛቶች ሪፐብሊካኖች ሲሆኑ የግዛቶቿ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ይለያያል። በርካታ ታሪካዊ ጉብኝቶቿና ስብሰባዎቿ በ1986 በቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ፣ በ1994 የሩስያ ፌዴሬሽን፣ በ2011 የአየርላንድ ሪፐብሊክ፣ እና የአምስት ሊቃነ ጳጳሳት ጉብኝቶች ወይም ጉብኝት ያካትታሉ። እ.ኤ.አ. በ1953 የኤልዛቤት ዘውድ እና የብር፣ የወርቅ፣ የአልማዝ እና የፕላቲኒየም ኢዮቤልዩ ክብረ በዓላት በ1977፣ 2002፣ 2002፣ 2012 እና 2022 እንደቅደም ተከተላቸው ጉልህ ክንውኖች ይገኙበታል። ኤልዛቤት ረጅሙ እና ረጅሙ የብሪታኒያ ንጉሠ ነገሥት ፣ አንጋፋ እና ረጅሙ የስልጣን ርእሰ መስተዳድር እና በዓለም ታሪክ ውስጥ ሁለተኛው ረዥም የግዛት ሉዓላዊ ንጉስ ናቸው። በንጉሣዊው ቤተሰብ ላይ አልፎ አልፎ የሪፐብሊካን ስሜት እና የፕሬስ ትችት ገጥሟታል፣ በተለይም የልጆቿ ትዳር መፍረስ፣ በ1992 የእሷ አንነስ ሆሪቢሊስ እና በ1997 የቀድሞ አማቷ ዲያና፣ የዌልስ ልዕልት ከሞተች በኋላ። ይሁን እንጂ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ለንጉሣዊው አገዛዝ የሚደረገው ድጋፍ ከፍተኛ ነበር እናም አሁንም እንደ ግል ተወዳጅነቷም ጭምር ነው. የመጀመሪያ ህይወት ኤፕሪል 21 ቀን 1926 ኤልዛቤት በ02፡40 (ጂኤምቲ) የተወለደችው በአባቷ በንጉስ ጆርጅ 5ኛ በአባቷ የዮርክ መስፍን (በኋላ ንጉስ ጆርጅ ስድስተኛ) የንጉሱ ሁለተኛ ልጅ ነበር። እናቷ፣የዮርክ ዱቼዝ (በኋላ ንግስት ኤልዛቤት ንግስት እናት)፣ የስኮትላንዳዊው መኳንንት ክላውድ ቦውስ-ሊዮን፣ 14ኛው የስትራትሞር እና የኪንግሆርን ታናሽ ሴት ልጅ ነበረች። በቄሳሪያን ክፍል የተገላገለችው በእናቷ አያቷ ሎንደን ቤት፡ 17 ብሩተን ስትሪት፣ ሜይፋይር ነው። በግንቦት 29 በቡኪንግሃም ቤተ መንግሥት የግል ቤተ ጸሎት ውስጥ በዮርክ የአንግሊካን ሊቀ ጳጳስ ኮስሞ ጎርደን ላንግ ተጠመቀች እና በእናቷ ኤልዛቤት ብላ ጠራች ። አሌክሳንድራ ከአባቷ ቅድመ አያት በኋላ, ከስድስት ወር በፊት ከሞተች በኋላ; እና ማርያም ከአያት ቅድመ አያቷ በኋላ. መጀመሪያ ላይ እራሷን በጠራችው መሰረት "ሊሊቤት" እየተባለች የምትጠራው በአያቷ ጆርጅ አምስተኛ በፍቅር "አያቴ እንግሊዝ" ትላለች እና በጠና ታምሞ በ1929 ዓ.ም. ታዋቂው ፕሬስ እና በኋላ ባዮግራፕ9 የኤልዛቤት ብቸኛ ወንድም ልዕልት ማርጋሬት በ1930 ተወለደች። ሁለቱ ልዕልቶች በእናታቸው እና በገዥታቸው በማሪዮን ክራውፎርድ ቁጥጥር ስር በቤት ውስጥ ተምረው ነበር። በታሪክ፣ በቋንቋ፣ በሥነ ጽሑፍ እና በሙዚቃ ላይ ያተኮሩ ትምህርቶች። ክራውፎርድ የንጉሣዊውን ቤተሰብ አሳዝኖ የኤልዛቤት እና ማርጋሬት የልጅነት ዓመታትን ዘ ትንንሽ ልዕልቶችን በ1950 የሕይወት ታሪክ አሳተመ። መጽሐፉ ኤልዛቤት ለፈረስና ለውሾች ያላትን ፍቅር፣ ሥርዓታማነቷን እና የኃላፊነት ዝንባሌዋን ይገልጻል። ሌሎችም እንደዚህ ያሉትን አስተያየቶች አስተጋብተዋል፡- ዊንስተን ቸርችል ኤልዛቤትን የሁለት ልጅነቷ ጊዜ “ገጸ-ባህሪይ ነች። በጨቅላ ህጻን ውስጥ የሚያስደንቅ የስልጣን እና የማንጸባረቅ አየር አላት። የአጎቷ ልጅ ማርጋሬት ሮድስ እሷን “ደስ የምትል ትንሽ ልጅ ፣ ግን በመሠረቱ አስተዋይ እና ጥሩ ባህሪ ነበረች” በማለት ገልፃዋታል። ወራሽ ግምታዊ በአያቷ የግዛት ዘመን ኤልሳቤጥ ከአጎቷ ኤድዋርድ እና ከአባቷ በመቀጠል የብሪታንያ ዙፋን በመተካት ሶስተኛ ነበረች። ምንም እንኳን ልደቷ የህዝብን ፍላጎት ቢያመጣም ኤድዋርድ ገና ወጣት ስለነበር አግብቶ የራሱ ልጆች ስለሚወልድ ንግሥት ትሆናለች ተብሎ አልተጠበቀም ነበር። በ 1936 አያቷ ሲሞቱ እና አጎቷ እንደ ኤድዋርድ ስምንተኛ ሲተካ ከአባቷ ቀጥሎ በዙፋኑ ላይ ሁለተኛ ሆናለች። በዚያው ዓመት በኋላ ኤድዋርድ ከስልጣን ተወገደ፣ ከተፋታች ሶሻሊስት ዋሊስ ሲምፕሰን ጋር ለመጋባት ካቀደው በኋላ ሕገ መንግሥታዊ ቀውስ አስነሳ። በዚህም ምክንያት የኤልዛቤት አባት ነገሠ፣ የግዛት ስም ጆርጅ ስድስተኛ ወሰደ። ኤልዛቤት ወንድሞች ስላልነበሯት ወራሽ ሆናለች። ወላጆቿ በኋላ ወንድ ልጅ ቢወልዱ ኖሮ, እሱ ወራሽ እና ከእሱ በላይ በሆነው ወራሽ ይሆናል, ይህም በወቅቱ በወንድ ምርጫ ቅድመ ሁኔታ ይወሰናል. ኤልዛቤት በህገ-መንግስታዊ ታሪክ የግል ትምህርት ከኢቶን ኮሌጅ ምክትል ፕሮቮስት ከሄንሪ ማርተን ተቀብላ ፈረንሳይኛ ከተከታታይ የአፍ መፍቻ ተናጋሪ ገዥዎች ተምራለች። ገርል አስጎብኚዎች ድርጅት፣ 1ኛው የቡኪንግሃም ቤተመንግስት ኩባንያ የተቋቋመው በራሷ ዕድሜ ካሉ ልጃገረዶች ጋር እንድትገናኝ ነው። በኋላ፣ እሷ የባህር ጠባቂ ሆና ተመዝግቧል። በ 1939 የኤልዛቤት ወላጆች ካናዳ እና ዩናይትድ ስቴትስ ጎብኝተዋል. እ.ኤ.አ. በ1927፣ አውስትራሊያን እና ኒውዚላንድን ሲጎበኙ ኤልዛቤትም በብሪታንያ ቆይታለች፤ ምክንያቱም አባቷ ህዝባዊ ጉብኝት ለማድረግ በጣም ትንሽ እንደሆነች አድርጎ ስለገመተ። ወላጆቿ ሲሄዱ "እያለቀሰች ትመስላለች።" አዘውትረው ይፃፉ ነበር፣ እና እሷ እና ወላጆቿ በግንቦት 18 የመጀመሪያውን የንጉሣዊ ትራንስትላንቲክ የስልክ ጥሪ አደረጉ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት በሴፕቴምበር 1939 ብሪታንያ ወደ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ገባች። ሎርድ ሃይልሻም ልዕልት ኤልዛቤት እና ማርጋሬት በሉፍትዋፍ ተደጋጋሚ የለንደን የአየር ላይ የቦምብ ጥቃቶችን ለማስቀረት ወደ ካናዳ እንዲሰደዱ ሀሳብ አቅርበዋል ። ይህ በእናታቸው ተቀባይነት አላገኘም እና "ልጆቹ ያለ እኔ አይሄዱም. እ.ኤ.አ. በ1939 የገና በዓል ወደ ሳንሪንግሃም ሃውስ፣ ኖርፎልክ እስከሄዱበት ጊዜ ልዕልቶቹ በባልሞራል ካስትል፣ ስኮትላንድ ቆዩ። ከየካቲት እስከ ግንቦት 1940 በሮያል ሎጅ፣ ዊንዘር ወደ ዊንዘር ቤተመንግስት እስኪሄዱ ድረስ ኖረዋል፣ እና ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አብዛኛውን ኖረዋል። በዊንሶር ልዕልቶች ወታደራዊ ልብሶችን ለመልበስ ክር ገዝተው ለነበረው የንግስት ሱፍ ፈንድ እርዳታ የገና በዓል ላይ ፓንቶሚሞችን አዘጋጁ። እ.ኤ.አ. በ1940 የ14 ዓመቷ ኤልዛቤት የመጀመሪያዋን የሬዲዮ ስርጭት በቢቢሲ የህፃናት ሰአት ላይ አድርጋ ከከተሞች ለተፈናቀሉ ሌሎች ልጆች አነጋግራለች። እሷ እንዲህ አለች: - "እጅግ ጀልባዎቻችንን ፣ ወታደሮቻችንን እና አየር ወታደሮቻችንን ለመርዳት የምንችለውን ሁሉ ለማድረግ እየሞከርን ነው ፣ እናም እኛ ደግሞ የራሳችንን የጦርነት አደጋ እና ሀዘን ለመሸከም እየሞከርን ነው። እያንዳንዳችን እናውቃለን። በመጨረሻ ሁሉም ነገር መልካም እንደሚሆን። እ.ኤ.አ. በ 1943 ኤልዛቤት ባለፈው አመት ኮሎኔል ተብሎ የተሾመችውን የግሬናዲየር ጠባቂዎችን ጎበኘች ። ወደ 18ኛ አመት ልደቷ ሲቃረብ ፓርላማው ህጉን በመቀየር አባቷ አቅመ ቢስነት ወይም ውጭ አገር በሌለበት ሁኔታ ከአምስቱ የመንግስት አማካሪዎች መካከል አንዷ ሆና እንድትሰራ ለምሳሌ በጁላይ 1944 ጣሊያንን ሲጎበኝ በየካቲት 1945 ተሾመች። በረዳት ቴሪቶሪያል አገልግሎት የክብር ሁለተኛ ሱባሌተር ሆና በአገልግሎት ቁጥሩ 230873 በሹፌርነት እና በመካኒክነት የሰለጠነች ሲሆን ከአምስት ወር በኋላ የክብር ጁኒየር አዛዥ (በዚያን ጊዜ ሴት ካፒቴን የምትመስል ሴት) ማዕረግ ተሰጥቷታል። በአውሮፓ ጦርነት ማብቂያ ላይ በአውሮፓ የድል ቀን ኤልዛቤት እና ማርጋሬት በለንደን ጎዳናዎች ላይ ከነበሩት ሰዎች ጋር ማንነትን የማያሳውቅ ነገር ቀላቀሉ። በኋላ ላይ ኤልዛቤት አልፎ አልፎ ባደረገችው ቃለ ምልልስ ላይ “ወላጆቼን ራሳችንን ሄደን ማየት እንደምንችል ጠየቅናቸው። መታወቃችን በጣም ያስፈራን እንደነበር አስታውሳለሁ... ክንድ እያገናኙ በኋይትሆል የሚሄዱ ያልታወቁ ሰዎች መስመር አስታውሳለሁ። በደስታ እና በእፎይታ ማዕበል ላይ ጠራርጎ ወሰድኩ ። " በጦርነቱ ወቅት ኤልዛቤትን ከዌልስ ጋር በቅርበት በማስተሳሰር የዌልስን ብሔርተኝነት ለመቀልበስ ዕቅዶች ተዘጋጅተዋል። የቄርናርፎን ካስትል ኮንስታብልን ወይም የኡርድ ጎባይት ሳይምሩ (የዌልሽ ወጣቶች ሊግ) ጠባቂን መሾም ያሉ ሀሳቦች ብሪታንያ በጦርነት ላይ በነበረችበት ወቅት ኤልዛቤትን በኡርድ ውስጥ ከህሊናቸው ከሚቃወሙት ጋር ማገናኘት መፍራትን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ተጥለዋል። . የዌልስ ፖለቲከኞች በ18ኛ ልደቷ የዌልስ ልዕልት እንድትሆን ጠቁመዋል። የሀገር ውስጥ ፀሐፊ ኸርበርት ሞሪሰን ሃሳቡን ደግፈው ነበር፣ ነገር ግን ንጉሱ አልተቀበሉትም ምክንያቱም እንዲህ ዓይነቱ ማዕረግ የዌልስ ልዑል ሚስት ብቻ እንደሆነ ስለሚሰማቸው እና የዌልስ ልዑል ሁል ጊዜም ወራሽ ነበሩ። እ.ኤ.አ. በ1946፣ በዌልስ ብሔራዊ ኢስቴድድፎድ ወደ ጎርሴድ ኦፍ ባርድስ ገብታለች። ልዕልት ኤልዛቤት በደቡብ አፍሪካ ከወላጆቿ ጋር በመሆን የመጀመሪያውን የባህር ማዶ ጉብኝቷን በ1947 ሄደች። በጉብኝቱ ወቅት፣ በ 21 ኛው ዓመቷ ለብሪቲሽ ኮመንዌልዝ በተላለፈው ስርጭት፣ የሚከተለውን ቃል ገብታለች፡- “መላ ህይወቴ፣ ረጅምም ይሁን አጭር፣ ለአንተ አገልግሎት እና ለአገልግሎት የምታውል መሆኔን በፊትህ አውጃለሁ። ሁላችንም የምንገኝበት ታላቁ ንጉሠ ነገሥት ቤተሰባችን። ንግግሩን የፃፈው የታይምስ ጋዜጠኛ ዴርሞት ሞራህ ነው። ኤልዛቤት የወደፊት ባለቤቷን የግሪክ እና የዴንማርክ ልዑል ፊሊፕን በ1934 እና እንደገና በ1937 አገኘቻቸው። አንድ ጊዜ በዴንማርክ ንጉሥ ክርስቲያን ዘጠነኛ እና ሦስተኛው የአጎት ልጆች በንግስት ቪክቶሪያ ተወግደዋል። በጁላይ 1939 በዳርትማውዝ ሮያል የባህር ኃይል ኮሌጅ ለሶስተኛ ጊዜ ከተገናኘች በኋላ ኤልዛቤት ምንም እንኳን የ13 ዓመቷ ልጅ ቢሆንም—ፊሊፕን እንደወደደች ተናገረች እና ደብዳቤ መለዋወጥ ጀመሩ። እ.ኤ.አ. ጁላይ 9 ቀን 1947 መተጫጫታቸው በይፋ ሲታወቅ 21 ዓመቷ ነበር። ተሳትፎው ያለ ውዝግብ አልነበረም; ፊሊፕ ምንም አይነት የገንዘብ አቋም አልነበረውም፣ የተወለደ የውጭ ሀገር ሰው ነበር (ምንም እንኳን በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በሮያል ባህር ኃይል ውስጥ ያገለገለ የብሪቲሽ ርዕሰ ጉዳይ ቢሆንም) እና ከናዚ ግንኙነት ጋር የጀርመን ባላባቶችን ያገቡ እህቶች ነበሩት። ማሪዮን ክራውፎርድ እንዲህ ሲል ጽፏል፡- “አንዳንድ የንጉሱ አማካሪዎች ለእሷ በቂ አይመስላቸውም ነበር። እሱ ቤት ወይም መንግስት የሌለው ልዑል ነበር። አንዳንዶቹ ወረቀቶች የፊሊፕ የውጭ አገር ምንጭ ላይ ረዥም እና ከፍተኛ ዜማዎችን ተጫውተዋል። በኋላ ላይ የህይወት ታሪኮች እንደዘገቡት የኤልዛቤት እናት ስለ ህብረቱ መጀመሪያ ላይ ጥርጣሬ እንደነበራት እና ፊሊፕን “ዘ ሁን” በማለት አሾፈባት።በኋለኛው ህይወት ግን ንግሥቲቱ እናት ፊልጶስ “እንግሊዛዊ ጨዋ” እንደሆነ ለባዮግራፊው ለቲም ሄልድ ነገረችው። ከጋብቻው በፊት ፊሊፕ የግሪክ እና የዴንማርክ መጠሪያዎቹን ትቷል፣ ከግሪክ ኦርቶዶክስ ወደ አንግሊካኒዝም በይፋ ተለወጠ እና የእናቱን የእንግሊዝ ቤተሰብ ስም በመያዝ ሌተናንት ፊሊፕ ማውንባትተንን ተቀበለ። ከሠርጉ በፊት ብዙም ሳይቆይ የኤድንበርግ መስፍን ተፈጠረ እና የንጉሣዊ ልዕልናን ዘይቤ ሰጠው። ኤልዛቤት እና ፊሊፕ ህዳር 20 ቀን 1947 በዌስትሚኒስተር አቤይ ተጋቡ። ከዓለም ዙሪያ 2,500 የሰርግ ስጦታዎችን ተቀብለዋል. ብሪታንያ ከጦርነቱ ውድመት ገና ሙሉ በሙሉ ስላላገገመች ኤልሳቤጥ ለጋዋን የምትገዛበትን የራሽን ኩፖን ጠይቃ ነበር። ከጦርነቱ በኋላ በብሪታንያ የፊሊፕ የጀርመን ግንኙነት በሕይወት የተረፉትን ሦስት እህቶቹን ጨምሮ ለሠርጉ መጋበዙ ተቀባይነት አልነበረውም። ለዊንዘር መስፍን የቀድሞ ንጉስ ኤድዋርድ ስምንተኛ የቀረበ ግብዣም አልነበረም። ኤልዛቤት የመጀመሪያ ልጇን ልዑል ቻርልስን በህዳር 14 ቀን 1948 ወለደች። ከአንድ ወር በፊት ንጉሱ ልጆቿ የንጉሣዊ ልዑልን ወይም ልዕልትን ዘይቤ እና ማዕረግ እንዲጠቀሙ የሚያስችላቸውን የፓተንት ደብዳቤ አውጥተው ነበር። አባታቸው የንጉሣዊ ልኡል ስላልሆኑ የሚል መብት አላቸው። ሁለተኛ ልጅ ልዕልት አን ነሐሴ 15 ቀን 1950 ተወለደች። ከሠርጋቸው በኋላ ጥንዶቹ በለንደን ክላረንስ ሃውስ እስከ ጁላይ 1949 ድረስ በዊንሶር ቤተመንግስት አቅራቢያ የምትገኘውን ዊንደልሻም ሙርን ተከራዩ። ከ1949 እስከ 1951 ባለው ጊዜ ውስጥ የኤድንበርግ መስፍን በብሪቲሽ ዘውድ ቅኝ ግዛት ማልታ ውስጥ በሮያል ባህር ኃይል መኮንንነት ተቀምጦ ነበር። እሱ እና ኤልዛቤት በማልታ ውስጥ ለብዙ ወራት ያለማቋረጥ ኖረዋል በአንድ ጊዜ በጓርዳማንሻ መንደር ውስጥ በቪላ ፣የፊልጶስ አጎት ጌታ ማውንባተን በተከራዩት ቤት። ሁለቱ ልጆቻቸው በብሪታንያ ቀሩ። መቀላቀል እና ዘውድ በ 1951 የጆርጅ ስድስተኛ ጤና ቀንሷል ፣ እና ኤልዛቤት በሕዝብ ዝግጅቶች ላይ ብዙ ጊዜ ትደግፈው ነበር። በካናዳ ጎበኘች እና በዋሽንግተን ዲሲ በጥቅምት ወር 1951 ፕሬዘዳንት ሃሪ ኤስ.ትሩማንን ስትጎበኝ የግል ፀሃፊዋ ማርቲን ቻርተሪስ በጉብኝት ላይ እያለች የንጉሱን ሞት በተመለከተ ረቂቅ የመግባቢያ መግለጫ ወሰደች። እ.ኤ.አ. በ1952 መጀመሪያ ላይ ኤልዛቤት እና ፊሊፕ በኬንያ በኩል ወደ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ ለመጎብኘት ሄዱ። እ.ኤ.አ. ፌብሩዋሪ 6 ቀን 1952 ወደ ኬንያ ቤታቸው ሳጋና ሎጅ ተመለሱ ፣ በትሬቶፕስ ሆቴል ካደሩ በኋላ ፣ የጆርጅ ስድስተኛ ሞት እና የኤልዛቤት ዙፋን ላይ መውጣቱ ወዲያውኑ ሰማ ። ፊሊጶስ ዜናውን ለአዲሱ ንግስት ተናገረ። ኤልዛቤትን እንደ ንግሥና ስሟ ለመያዝ መረጠች; ስለዚህ እሷ በስኮትላንድ የገዛች የመጀመሪያዋ ኤልዛቤት በመሆኗ ብዙ ስኮቶችን ያስከፋችው ኤልዛቤት ተብላለች። በግዛቶቿ ሁሉ ንግሥት ተባለች እና የንጉሣዊው ፓርቲ በፍጥነት ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ተመለሰ። ኤልዛቤት እና ፊሊፕ ወደ ቡኪንግሃም ቤተ መንግስት ተዛወሩ። ኤልዛቤት ከገባች በኋላ ሚስት የባሏን ስም በትዳር ላይ በምትወስድበት ጊዜ የንጉሣዊው ቤት የኤዲንብራ መስፍን ስም ሊሸከም የሚችል ይመስላል። ሎርድ የ ቤት የሚለውን ስም ደግፏል። ፊሊፕ ከዱካል ማዕረጉ በኋላ የኤድንበርግ ቤትን አቀረበ። የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዊንስተን ቸርችል እና የኤልዛቤት አያት ንግሥት ሜሪ የዊንዘርን ቤት እንዲቆይ ደግፈዋል፣ስለዚህ ኤልዛቤት ሚያዝያ 9 ቀን 1952 ዊንዘር የንጉሣዊው ቤት መጠሪያ ሆኖ እንደሚቀጥል ማስታወቂያ አውጥታለች። ዱኪው "በአገሪቱ ውስጥ ስሙን ለልጆቹ እንዳይሰጥ የተከለከልኩት እኔ ብቻ ነኝ" ሲል ቅሬታ አቅርቧል። እ.ኤ.አ. በ 1960 የንጉሣዊ ማዕረጎችን ለሌላቸው የፊልጶስ እና የኤልዛቤት የወንድ የዘር ሐረግ ስም ተቀበለ። ልዕልት ማርጋሬት ለዘውዳዊ ሥርዓቱ በዝግጅት ላይ እያለች የ16 ዓመት የሞጋጋሬት ከፍተኛ እና ከቀድሞ ጋብቻው ሁለት ወንዶች ልጆች የነበራትን ፒተር ታውንሴንድ የተባለውን ፍቺ ማግባት እንደምትፈልግ ለእህቷ ነገረቻት። ንግስቲቱ ለአንድ አመት እንዲጠብቁ ጠየቃቸው; በግል ፀሐፊዋ አገላለጽ ንግሥቲቱ በተፈጥሮ ለልዕልቷ ርኅራኄ ነበራት ፣ ግን ተስፋ ብላ - ጊዜ ከሰጠች ፣ ጉዳዩ ይቋረጣል ብዬ አስባለሁ ። እንግሊዝ ከፍቺ በኋላ እንደገና ማግባትን አልፈቀደችም። ማርጋሬት የፍትሐ ብሔር ጋብቻ ፈፅማ ብትሆን ኖሮ የመውረስ መብቷን ትታለች ተብሎ ይጠበቃል። ማርጋሬት ከ ጋር ያላትን እቅድ ለመተው ወሰነች። ንግሥተ ማርያም በማርች 24 ቀን 1953 ብትሞትም፣ ማርያም ከመሞቷ በፊት እንደጠየቀችው፣ ንግሥና ሥርዓቱ በሰኔ 2 እንደታቀደው ቀጠለ። በዌስትሚኒስተር አቢ የተካሄደው የዘውድ ሥርዓት ከቅባትና ከቁርባን በስተቀር ለመጀመሪያ ጊዜ በቴሌቪዥን ተላለፈ። በኤልዛቤት መመሪያ፣ የዘውድ ቀሚሷ በኮመን ዌልዝ አገሮች የአበባ አርማዎች ተጠልፏል። የኮመንዌልዝ ዝግመተ ለውጥ ኤልዛቤት ከተወለደችበት ጊዜ ጀምሮ የብሪቲሽ ኢምፓየር ወደ መንግስታት የጋራ ህብረት መቀየሩን ቀጠለ። እ.ኤ.አ. እ.ኤ.አ. በ 1953 ንግስቲቱ እና ባለቤቷ 13 ሀገራትን በመጎብኘት እና ከ 40,000 ማይሎች (64,000 ኪሎ ሜትሮች) በላይ በመሬት ፣ በባህር እና በአየር ተጉዘው የሰባት ወር የአለም ጉብኝት ጀመሩ ። እነዚያን አገሮች ለመጎብኘት የመጀመሪያዋ የአውስትራሊያ እና የኒውዚላንድ ንጉሠ ነገሥት ሆነች። በጉብኝቱ ወቅት ህዝቡ በጣም ብዙ ነበር; ከአውስትራሊያ ህዝብ ሶስት አራተኛው እሷን እንዳያት ተገምቷል። በንግሥናዋ ዘመን ሁሉ ንግሥቲቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ የመንግስት ጉብኝቶችን ወደ ሌሎች ሀገሮች እና የኮመንዌልዝ ጉብኝቶችን አድርጓል; እሷ በጣም የተጓዘች የሀገር መሪ ነች። እ.ኤ.አ. በ 1956 የብሪታንያ እና የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትሮች ሰር አንቶኒ ኤደን እና ጋይ ሞሌት ፈረንሳይ የኮመንዌልዝ ህብረትን ስለምትቀላቀልበት ሁኔታ ተወያይተዋል። ሃሳቡ ፈጽሞ ተቀባይነት አላገኘም እና በሚቀጥለው አመት ፈረንሳይ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ማህበረሰብን የአውሮፓ ህብረት ቀዳሚ የሆነውን የሮማን ስምምነት ተፈራረመች። በኖቬምበር 1956 ብሪታንያ እና ፈረንሳይ ግብፅን ወረሩ በመጨረሻ የስዊዝ ካናልን ለመያዝ አልተሳካም። ሎርድ ንግስቲቱ ወረራውን ትቃወማለች ብሏል ምንም እንኳን ኤደን ቢክድም። ኤደን ከሁለት ወራት በኋላ ስራውን ለቀቀ በኮንሰርቫቲቭ ፓርቲ ውስጥ መሪ የሚመርጥበት መደበኛ ዘዴ አለመኖሩ ኤደን ከስልጣን መልቀቋን ተከትሎ ማንን መንግስት መመስረት እንዳለበት መወሰን በንግስቲቱ ላይ ወደቀ። ኤደን የምክር ቤቱን ጌታ ፕሬዘዳንት ሎርድ ሳልስበሪን እንድታማክር ጠየቀች። ሎርድ ሳሊስበሪ እና ሎርድ ኪልሙየር፣ ጌታቸው ቻንስለር፣ የብሪቲሽ ካቢኔን፣ ቸርችልን፣ እና የ1922 የጓሮ ወንበር ኮሚቴ ሰብሳቢን አማከሩ፣ በዚህም ምክንያት ንግስቲቱ የተመከሩትን እጩ ሃሮልድ ማክሚላን ሾመች። የስዊዝ ቀውስ እና የኤደን ተተኪ ምርጫ እ.ኤ.አ. በ1957 በንግሥቲቱ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የግል ትችት እንዲፈጠር አድርጓቸዋል። ሎርድ አልትሪንቻም በባለቤትነት ባዘጋጀው መጽሄት "ከግንኙነት ውጪ" በማለት ከሰሷት። በሕዝብ ተወካዮች ተወግዟል እና በአስተያየቱ የተደናገጠ የህብረተሰብ አባል በጥፊ ተመታ። ከስድስት ዓመታት በኋላ፣ በ1963፣ ማክሚላን ሥራውን ለቀቀ እና ንግሥቲቱን የተከተለችውን ምክር የተከተለችው የቤት ውስጥ ጆሮን በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንድትሾም መከረቻት። ንግስቲቱ በጥቂት ሚኒስትሮች ወይም በአንድ ሚኒስትር ምክር ጠቅላይ ሚኒስትሩን በመሾሟ እንደገና ትችት ደረሰባት። እ.ኤ.አ. በ 1965 ወግ አጥባቂዎች መሪን ለመምረጥ መደበኛ ዘዴን ወሰዱ ፣ በዚህም እሷን ከተሳትፎ ነፃ አውጥቷታል። እ.ኤ.አ. በ 1957 ኤልዛቤት ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ጎበኘች ፣ እዚያም የኮመንዌልዝ ህብረትን ወክላ ለተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር አቀረበች። በዚሁ ጉብኝት 23ኛውን የካናዳ ፓርላማን ከፍታ የፓርላማ ስብሰባ የከፈተ የካናዳ የመጀመሪያዋ ንጉስ ሆነች። ከሁለት አመት በኋላ የካናዳ ንግስት በመሆኗ ብቻ አሜሪካን ጎበኘች እና ካናዳን ጎበኘች። በ1961 ቆጵሮስን፣ ሕንድን፣ ፓኪስታንን፣ ኔፓልን እና ኢራንን ጎበኘች። በዚያው አመት ጋናን በመጎብኘት ለደህንነቷ ያለውን ፍራቻ ውድቅ አድርጋለች፣ ምንም እንኳን አስተናጋጅዋ ፕሬዝዳንት ክዋሜ ንክሩማህ የገዳዮች ኢላማ ቢሆኑም። ሃሮልድ ማክሚላን እንዲህ ሲል ጽፏል፡- “ንግስቲቱ በሙሉ በፍፁም ተወስኗል… እሷን እንደ የፊልም ተዋናይ እንድትይይላት ያላትን አመለካከት ትዕግስት አጥታለች… በእርግጥ “የሰው ልብ እና ሆድ” አላት ። .. ግዴታዋን ትወዳለች እና ንግሥት መሆን ማለት ነው." እ.ኤ.አ. በ 1964 በኪውቤክ የተወሰኑ ቦታዎችን ከማዘዋወሯ በፊት ፣ ፕሬስ እንደዘገበው በኩቤክ ተገንጣይ እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ ጽንፈኞች የኤልዛቤትን ግድያ እያሴሩ ነበር። ምንም ሙከራ አልተደረገም, ነገር ግን እሷ ሞንትሪያል ውስጥ ሳለ ረብሻ ነበር; ንግስቲቱ "በዓመፅ ፊት መረጋጋት እና ድፍረት" ተስተውሏል. ኤልዛቤት ሶስተኛ ልጇን ልዑል አንድሪውን በየካቲት 19 ቀን 1960 ወለደች ይህም ከ 1857 ጀምሮ በመግዛት ላይ ያለ የብሪታንያ ንጉስ ለመጀመሪያ ጊዜ የተወለደች ሲሆን አራተኛ ልጇ ልዑል ኤድዋርድ መጋቢት 10 ቀን 1964 ተወለደ። ንግስቲቱ ባህላዊ ሥርዓቶችን ከማከናወን በተጨማሪ አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግታለች። የመጀመሪያዋ ንጉሣዊ የእግር ጉዞ፣ ከተራ የህዝብ አባላት ጋር የተገናኘችው፣ በአውስትራሊያ እና በኒውዚላንድ በ1970 ባደረገች ጉብኝት ነበር የቅኝ ግዛት ማፋጠን እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ እና 1970ዎቹ በአፍሪካ እና በካሪቢያን አካባቢ ከቅኝ ግዛት የመግዛት ሂደት መፋጠን ታየ። ራስን በራስ ለማስተዳደር በተደረገው ሽግግር ከ20 በላይ ሀገራት ከብሪታንያ ነፃነታቸውን አግኝተዋል። እ.ኤ.አ. በ 1965 ግን የሮዴዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢያን ስሚዝ ወደ አብላጫ አገዛዝ መሸጋገርን በመቃወም ለኤልዛቤት “ታማኝነት እና ታማኝነት” ሲገልጹ በአንድ ወገን ነፃነታቸውን አወጁ ፣ “የሮዴዥያ ንግሥት” በማለት አወጁ። ምንም እንኳን ንግስቲቱ በይፋ ቢያሰናብተውም እና የአለም አቀፉ ማህበረሰብ በሮዴዥያ ላይ ማዕቀብ ቢያደርግም አገዛዙ ከአስር አመታት በላይ ቆይቷል። የብሪታንያ ከቀድሞ ግዛቷ ጋር የነበራት ግንኙነት እየዳከመ ሲሄድ፣ የብሪታንያ መንግስት በ1973 ዓ.ም ያሳካው ግብ ወደ አውሮፓ ማህበረሰብ ለመግባት ፈለገ። ንግስቲቱ በጥቅምት 1972 ዩጎዝላቪያን ጎበኘች ፣ የኮሚኒስት ሀገርን የጎበኙ የመጀመሪያው የእንግሊዝ ንጉስ ሆነ ። በአውሮፕላን ማረፊያው በፕሬዚዳንት ጆሲፕ ብሮዝ ቲቶ ተቀብላዋለች፣ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቤልግሬድ ተቀብለዋታል። እ.ኤ.አ. በየካቲት 1974 የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤድዋርድ ሄዝ ንግሥቲቱ ወደ ብሪታንያ እንድትመለስ በአስትሮኒያ ፓስፊክ ሪም ጉብኝት መካከል አጠቃላይ ምርጫ እንድትጠራ መክሯታል። ምርጫው የተንጠለጠለ ፓርላማን አስከተለ; የሄዝ ወግ አጥባቂዎች ትልቁ ፓርቲ አልነበሩም፣ ነገር ግን ከሊበራሎች ጋር ጥምረት ከፈጠሩ በስልጣን ላይ ሊቆዩ ይችላሉ። ጥምር መመስረትን በተመለከተ ውይይቶች ሲደረጉ ሄዝ የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚንስትርነቱን ለቀቀ እና ንግስት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የሆነውን የሌበር ሃሮልድ ዊልሰን መንግስት እንዲመሰርቱ ጠየቀች። ከአንድ ዓመት በኋላ፣ በ1975 የአውስትራሊያ ሕገ መንግሥታዊ ቀውስ፣ የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ጎው ዊትላም፣ በተቃዋሚ የሚቆጣጠረው ሴኔት የዊትላምን የበጀት ሐሳብ ውድቅ ካደረገ በኋላ፣ በጄኔራል ገዢው ሰር ጆን ኬር ከሥልጣናቸው ተባረሩ። ዊትላም በተወካዮች ምክር ቤት አብላጫ ድምፅ እንደነበራት፣ አፈ-ጉባዔ ጎርደን ስኮልስ የኬርን ውሳኔ እንድትቀይር ንግስቲቷን ይግባኝ አለች። በአውስትራሊያ ሕገ መንግሥት ለጠቅላይ ገዥው በተቀመጡ ውሳኔዎች ላይ ጣልቃ እንደማትገባ በመግለጽ አልተቀበለችም። ቀውሱ የአውስትራሊያን ሪፐብሊካኒዝም አቀጣጠለ የብር ኢዮቤልዩ እ.ኤ.አ. በ 1977 ኤልዛቤት የመውለጃዋን የብር ኢዮቤልዩ አከበረች። በኮመንዌልዝ ውስጥ ፓርቲዎች እና ዝግጅቶች ተከናውነዋል፣ ብዙዎቹ ከእሷ ጋር ከተያያዙ ብሔራዊ እና የኮመንዌልዝ ጉብኝቶች ጋር ይገጣጠማሉ። ልዕልት ማርጋሬት ከባለቤቷ ሎርድ ስኖዶን ስለመለያየቷ በአጋጣሚ የተገኘ አሉታዊ የፕሬስ ሽፋን ቢሆንም በዓሉ የንግሥቲቱን ተወዳጅነት በድጋሚ አረጋግጧል። እ.ኤ.አ. በ 1978 ንግስቲቱ የሮማኒያ ኮሚኒስት መሪ ኒኮላይ ሴውሼስኩ እና ባለቤታቸው ኤሌና ወደ ዩናይትድ ኪንግደም ያደረጉትን ጉብኝት ተቋቁማለች ፣ ምንም እንኳን በግል “በእጃቸው ደም” እንዳለ ብታስብም ። የሚቀጥለው ዓመት ሁለት ምቶች አመጣ: አንዱ አንቶኒ ብላንት ነበር, የንግስት ሥዕል የቀድሞ ቀያሽ, አንድ ኮሚኒስት ሰላይ ሆኖ; ሌላው በጊዜያዊ የአየርላንድ ሪፐብሊካን ጦር ዘመዷ እና አማቷ ሎርድ ተራራተን መገደል ነው። እንደ ፖል ማርቲን ሲር፣ በ1970ዎቹ መገባደጃ ላይ ንግስት ዘውዱ ለካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ፒየር ትሩዶ “ምንም ትርጉም አልነበራቸውም” ተብላ ተጨነቀች። ቶኒ ቤን ንግስቲቱ ትሩዶን “ይልቁንስ ተስፋ አስቆራጭ” አግኝታዋለች። የትሩዶ ሪፐብሊካኒዝም እንደ በቡኪንግሃም ቤተ መንግስት ውስጥ ያሉትን እገዳዎች ማንሸራተት እና በ 1977 ከንግሥቲቱ ጀርባ መንቀሳቀስ እና የተለያዩ የካናዳ ንጉሣዊ ምልክቶችን በስልጣን ዘመናቸው መወገድ በመሳሰሉት ምኞቱ የተረጋገጠ ይመስላል። እ.ኤ.አ. በ 1980 የካናዳ ፖለቲከኞች የካናዳ ሕገ መንግሥት የአገርን ጉዳይ ለመወያየት ወደ ለንደን ተልከዋል ንግሥቲቱን “ከየትኛውም የብሪታንያ ፖለቲከኞች ወይም ቢሮክራቶች የበለጠ መረጃ ታገኛለች” ። እሷ በተለይ የቢል -60 ውድቀት በኋላ ፍላጎት ነበረው ፣ ይህም እንደ ሀገር መሪነት ሚና ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል። የፕሬስ ምርመራ እና ታቸር ጠቅላይ ሚኒስትርነት እ.ኤ.አ. በ 1981 በ ሥነ-ሥርዓት ላይ ፣ የልዑል ቻርልስ እና ሌዲ ዲያና ስፔንሰር ሠርግ ስድስት ሳምንታት ሲቀረው ፣ ንግሥቲቱ በቅርብ ርቀት ላይ ስድስት ጥይቶች ተተኩሰዋል ፣ ለንደን በፈረስዋ በርማ። ፖሊስ በኋላ ላይ ጥይቶቹ ባዶ መሆናቸውን አረጋግጧል። የ17 አመቱ አጥቂ ማርከስ ሳርጀንት የ 5 አመት እስራት ተፈርዶበት ከሶስት አመታት በኋላ ተፈቷል። የንግስቲቱ መረጋጋት እና ተራራዋን በመቆጣጠር ረገድ ባሳየችው ችሎታ በሰፊው ተመስግኗል።በጥቅምት ወር ንግስቲቱ በኒው ዚላንድ ዱነዲን በጎበኙበት ወቅት ሌላ ጥቃት ደርሶባቸዋል። የ17 አመት ታዳጊ የነበረው ክሪስቶፈር ጆን ሌዊስ .22 ሽጉጥ በመተኮስ ሰልፉን ከሚመለከት ህንጻ አምስተኛ ፎቅ ላይ ተኩሶ ነበር፣ነገር ግን አምልጦታል። ሉዊስ ተይዟል፣ ነገር ግን በግድያ ሙከራ ወይም በአገር ክህደት ክስ ቀርቦ አያውቅም፣ እና የጦር መሳሪያ በህገ-ወጥ መንገድ በመያዙ እና በማውጣቱ የሶስት አመት እስራት ተፈርዶበታል። ከተፈረደበት ሁለት አመት በኋላ ከዲያና እና ከልጃቸው ልዑል ዊሊያም ጋር አገሩን እየጎበኘ ያለውን ቻርለስን ለመግደል በማሰብ ከአእምሮ ህክምና ሆስፒታል ለማምለጥ ሞከረ። ከኤፕሪል እስከ ሴፕቴምበር 1982 የንግስት ልጅ ልዑል አንድሪው በፎክላንድ ጦርነት ከብሪቲሽ ጦር ጋር አገልግሏል፣ ለዚህም ጭንቀት እና ኩራት ተሰምቷታል። እ.ኤ.አ. ጁላይ 9፣ በቡኪንግሃም ቤተ መንግስት ውስጥ በመኝታ ክፍሏ ውስጥ ሚካኤል ፋጋን ሰርጎ ገዳይ ለማግኘት ከእርሷ ጋር ነቃች። በከባድ የጸጥታ ችግር ውስጥ፣ ወደ ቤተመንግስት ፖሊስ መቀየሪያ ሰሌዳ ሁለት ጥሪ ከተደረገ በኋላ እርዳታ ደረሰ። እ.ኤ.አ. በ 1982 የዩኤስ ፕሬዝዳንት ሮናልድ ሬገንን በዊንሶር ካስል ካስተናገደች በኋላ እና በ1983 የካሊፎርኒያ እርባታውን ከጎበኘች በኋላ ፣ ንግስቲቱ አስተዳደሩ ሳያሳውቃት ከካሪቢያን ግዛቶቿ አንዷ የሆነችውን ግሬናዳ እንድትወረር ባዘዘች ጊዜ ተናደደች። በ1980ዎቹ ውስጥ በንጉሣዊው ቤተሰብ አስተያየት እና የግል ሕይወት ላይ ከፍተኛ የሚዲያ ፍላጎት በፕሬስ ውስጥ ተከታታይ ስሜት ቀስቃሽ ታሪኮችን አስገኝቷል ፣ ሁሉም ሙሉ በሙሉ እውነት አይደሉም። የ አዘጋጅ የሆኑት ኬልቪን ማኬንዚ ለሰራተኞቻቸው እንደተናገሩት: "ለሰኞ በሮያልስ ላይ የሚረጭበት እሁድን ስጠኝ. እውነት ካልሆነ አትጨነቅ - ከዚያ በኋላ ስለ ጉዳዩ ብዙ ግርግር እስካልተገኘ ድረስ." የጋዜጣ አርታኢ ዶናልድ ትሬልፎርድ በሴፕቴምበር 21 ቀን 1986 ዘ ኦብዘርቨር ላይ እንዲህ ሲል ጽፏል:- “የሮያል ሳሙና ኦፔራ በአሁኑ ጊዜ የህዝብ ፍላጎት ደረጃ ላይ ደርሷል እናም በእውነታ እና በልብ ወለድ መካከል ያለው ድንበር ጠፍቷል… አንዳንድ ወረቀቶች ብቻ አይደሉም። እውነታቸውን አይፈትሹ ወይም ክህደቶችን አይቀበሉ፡ ታሪኮቹ እውነት ይሁኑ አይሁኑ ግድ የላቸውም። በተለይ በጁላይ 20 ቀን 1986 በወጣው የሰንዴይ ታይምስ ላይ ንግስቲቱ የማርጋሬት ታቸር የኢኮኖሚ ፖሊሲ ማህበራዊ መከፋፈልን እንደሚያሳድግ እና በከፍተኛ ስራ አጥነት ፣በተከታታይ ብጥብጥ ፣በማዕድን ሰራተኞች አድማ እና በታቸርስ እንዳስፈራት ተዘግቧል። በደቡብ አፍሪካ ያለውን የአፓርታይድ አገዛዝ ላይ ማዕቀብ ተግባራዊ ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆን። የወሬው ምንጮች የንጉሣዊው ረዳት ሚካኤል ሺአ እና የኮመንዌልዝ ዋና ፀሐፊ ሽሪዳት ራምፋልን ያካትታሉ፣ ነገር ግን ሺአ ንግግሮቹ ከአውድ ውጪ የተወሰዱ እና በግምታዊ ግምት ያጌጡ ናቸው ብሏል። ታቸር ንግስቲቱ ለሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ -የታቸር የፖለቲካ ተቃዋሚዎች እንደምትመርጥ ተናግራለች። የታቸር የህይወት ታሪክ ጸሐፊ ጆን ካምቤል “ሪፖርቱ የጋዜጠኝነት ጥፋት ነው” ሲል ተናግሯል ።በመካከላቸው የተፈጠረው አለመግባባት የተጋነነ ሲሆን ንግስቲቱ በግል ስጦታዋ ሁለት ክብር ሰጥታለች - የሜሪት ኦፍ ሜሪት እና ዘ ኦርደር አባልነት። ጋርተር - በጆን ሜጀር በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከተተካች በኋላ ወደ ታቸር። በ1984 እና 1993 መካከል የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ብሪያን ሙልሮኒ፣ ኤልዛቤት አፓርታይድን ለማቆም “ከጀርባ ያለው ኃይል” ነች ብለዋል። እ.ኤ.አ. በ 1986 ንግሥቲቱ በቻይና የስድስት ቀናት ጉብኝት አድርጋለች ፣ አገሪቱን የጎበኙ የመጀመሪያ የብሪታንያ ንጉሠ ነገሥት ሆነች። ጉብኝቱ የተከለከለውን ከተማ፣ ታላቁን የቻይና ግንብ እና የቴራኮታ ተዋጊዎችን ያካትታል። በመንግስት ግብዣ ላይ ንግስቲቱ በቻይና የመጀመርያው የእንግሊዝ መልእክተኛ ለንግስት ኤልሳቤጥ ቀዳማዊት ንጉሠ ነገሥት በጻፈችው ደብዳቤ በባህር ላይ ስለጠፋው ቀልዳለች እና "እንደ እድል ሆኖ የፖስታ አገልግሎት ከ1602 ጀምሮ ተሻሽሏል" ስትል ተናግራለች። የንግሥቲቱ ጉብኝት በሆንግ ኮንግ ላይ ሉዓላዊነት ከዩናይትድ ኪንግደም ወደ ቻይና በ 1997 እንደሚተላለፍ የሁለቱም ሀገራት ተቀባይነትን ያሳያል ። እ.ኤ.አ. በ1980ዎቹ መገባደጃ ላይ ንግስቲቱ የሳይት ዒላማ ሆና ነበር። በበጎ አድራጎት ጨዋታ ውስጥ የንጉሣዊው ቤተሰብ ታናሽ አባላት ተሳትፎ መሳለቂያ ነበር በ1987 በካናዳ ኤልዛቤት የፖለቲካ ከፋፋይ የሕገ መንግሥት ማሻሻያዎችን በይፋ ደግፋለች፣ ይህም ለውጦች የታቀዱትን ለውጦች የሚቃወሙትን ፒየር ትሩዶን ጨምሮ ነው። በዚያው አመት የተመረጠው የፊጂ መንግስት በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ከስልጣን ተወገደ። የፊጂ ንጉሠ ነገሥት እንደመሆኗ መጠን፣ ኤልዛቤት ዋና ገዥው ራት ሰር ፔናያ ጋኒላው የአስፈፃሚ ሥልጣንን ለማረጋገጥ እና መፍትሄ ለመደራደር ያደረጉትን ሙከራ ደግፋለች። የመፈንቅለ መንግስቱ መሪ ሲቲቭኒ ራቡካ ጋኒላን ከስልጣን አውርዶ ፊጂን ሪፐብሊክ አወጀ የ1990ዎቹ ሁከት እና አስከፊው አመት በባህረ ሰላጤው ጦርነት በትብብር ድል ምክንያት ንግስቲቱ በግንቦት ወር 1991 በተባበሩት መንግስታት ኮንግረስ የጋራ ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉ የመጀመሪያዋ የብሪቲሽ ንጉስ ሆነች። እ.ኤ.አ. ህዳር 24 ቀን 1992 ኤልዛቤት የዙፋኗን የሩቢ ኢዮቤልዩ በዓልን ለማክበር ባደረገችው ንግግር እ.ኤ.አ. በ1992 አኑስ ሆሪቢሊስ (የላቲን ሀረግ፣ “አስፈሪ አመት” ማለት ነው) ብላ ጠራችው። በብሪታንያ ውስጥ የሪፐብሊካን ስሜት ከፍ ብሏል የንግስት ንግስት የግል ሀብት -በቤተመንግስት በተቃረነ - እና በሰፋፊ ቤተሰቧ መካከል ስላለው የጉዳይ እና የጋብቻ ችግር ዘገባ። በመጋቢት ወር ሁለተኛ ልጇ ልዑል እንድርያስ ከሚስቱ ከሣራ ተለያይተው ሞሪሺየስ ኤልዛቤትን እንደ ርዕሰ መስተዳድር አስወገደ። ልጇ ልዕልት አን በሚያዝያ ወር ካፒቴን ማርክ ፊሊፕስን ፈታች; በድሬዝደን ውስጥ የተናደዱ ተቃዋሚዎች በጥቅምት ወር ወደ ጀርመን ባደረጉት ጉብኝት በንግሥቲቱ ላይ እንቁላሎችን ጣሉ ። እና በህዳር ወር ውስጥ ከኦፊሴላዊ መኖሪያዎቿ አንዱ በሆነው በዊንሶር ካስል ላይ ትልቅ እሳት ተነስቷል። ንጉሣዊው መንግሥት ብዙ ትችት እና የሕዝብ ምልከታ ደርሶበታል። ባልተለመደ የግል ንግግር ንግስቲቱ ማንኛውም ተቋም ትችት መጠበቅ እንዳለበት ተናግራለች ነገር ግን “በቀልድ ፣ ገርነት እና ማስተዋል” ሊደረግ እንደሚችል ጠቁመዋል ። ከሁለት ቀናት በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆን ሜጀር የንጉሣዊው ፋይናንስ ማሻሻያ ዕቅድ አውጀዋል, ባለፈው ዓመት የተዘጋጀው, ንግሥቲቱ ከ 1993 ጀምሮ የገቢ ግብር መክፈልን እና የሲቪል ዝርዝሩን መቀነስን ጨምሮ. በታህሳስ ወር ልዑል ቻርልስ እና ባለቤቱ ዲያና በይፋ ተለያዩ ። በዓመቱ መገባደጃ ላይ ንግስቲቱ የዓመታዊ የገና መልእክቷን ከመተላለፉ ከሁለት ቀናት በፊት ባወጣችበት ወቅት የቅጂ መብት ጥሰት ብላ ዘ ሰን ጋዜጣን ከሰሰች። ጋዜጣው ህጋዊ ክፍያዋን እንድትከፍል የተገደደች ሲሆን 200,000 ፓውንድ ለበጎ አድራጎት ድርጅት ሰጠች። የንግስት ጠበቃዎች የዮርክ ዱቼዝ እና የልዕልት ቢያትሪስ ፎቶግራፍ ካተሙ በኋላ የቅጂ መብት ጥሰትን በተመለከተ ከአምስት ዓመታት በፊት በፀሐይ ላይ እርምጃ ወስደዋል ። ጋዜጣው 180,000 ዶላር እንዲከፍል በማዘዝ ከፍርድ ቤት ውጭ በተደረገ እልባት ጉዳዩ ተፈቷል። እ.ኤ.አ. በጥቅምት 1994 ንግሥቲቱ የሩስያን መሬት የረገጡ የመጀመሪያው የብሪታንያ ንጉሠ ነገሥት ሆነች። በሞስኮ እና በሴንት ፒተርስበርግ ዝግጅቶች ላይ ተገኝተዋል. እ.ኤ.አ. በጥቅምት 1995 ንግስቲቱ የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዣን ቻርቲንን በማስመሰል በሞንትሪያል ሬዲዮ አስተናጋጅ ፒየር ብራሳርድ የውሸት ጥሪ ተታለለች። ክሪቲንን እያናገረች እንደሆነ ያመነችው ንግሥቲቱ የካናዳ አንድነትን እንደምትደግፍ ተናግራለች እናም በኩቤክ ህዝበ ውሳኔ ከካናዳ ለመውጣት በሚቀርቡ ሀሳቦች ላይ ተጽዕኖ ለማድረግ እንደምትሞክር ተናግራለች። በሚቀጥለው ዓመት የቻርለስ እና የዲያና ጋብቻ ሁኔታ ላይ የህዝብ መገለጦች ቀጥለዋል. ከባለቤቷ እና ከጆን ማጆር እንዲሁም ከካንተርበሪ ሊቀ ጳጳስ ጆርጅ ኬሪ እና የግል ጸሃፊዋ ሮበርት ፌሎውስ ጋር በመመካከር በታህሳስ 1995 መጨረሻ ላይ ለቻርለስ እና ለዲያና ደብዳቤ ጻፈች ይህም ፍቺ ጥሩ እንደሆነ ጠቁማለች። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 1997 ከፍቺው ከአንድ ዓመት በኋላ ዲያና በፓሪስ በመኪና አደጋ ሞተች። ንግስቲቱ ከዘመዶቿ ጋር በባልሞራል በበዓል ላይ ነበረች። የዲያና ሁለት የቻርልስ ልጆች - ልኡል ዊሊያም እና ሃሪ - ቤተክርስቲያን መገኘት ፈለጉ እና ስለዚህ ንግስቲቱ እና የኤድንበርግ መስፍን በዚያ ጠዋት ወሰዷቸው። ከዚያም ለአምስት ቀናት ያህል ንግሥቲቱ እና ዱኩ የልጅ ልጆቻቸውን በድብቅ በሚያዝኑበት በባልሞራል በማቆየት ፣ የንጉሣዊው ቤተሰብ ዝምታ እና መገለል ፣ እና ባንዲራውን በግማሽ ጫፍ ላይ ለማውለብለብ አለመቻሉን ለአምስት ቀናት ያህል ከለከሏቸው። የቡኪንግሃም ቤተ መንግስት የህዝብን ስጋት ፈጠረ። በጥላቻ ምላሽ ተገፋፍታ፣ ንግስቲቱ ወደ ለንደን ለመመለስ እና በሴፕቴምበር 5፣ ከዲያና የቀብር ሥነ ሥርዓት በፊት በነበረው ቀን የቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ለማድረግ ተስማማች። በስርጭቱ ላይ ለዲያና ያላትን አድናቆት እና ስሜቷን "እንደ አያት" ለሁለቱ መኳንንት ገልጻለች። በዚህ ምክንያት አብዛኛው የህዝብ ጥላቻ ተንኖ ወጣ። በጥቅምት 1997 ኤልዛቤት እና ፊሊፕ ህንድ ውስጥ የመንግስት ጉብኝት አደረጉ፣ እሱም አወዛጋቢ የሆነውን የጃሊያንዋላ ባግ እልቂት ለማክበር ወደ ስፍራው ጎበኘች። ተቃዋሚዎች "ገዳይ ንግሥት ተመለስ" እያሉ ሲዘምሩ የነበረ ሲሆን ከ78 ዓመታት በፊት የብሪታንያ ወታደሮች ለወሰዱት እርምጃ ይቅርታ እንድትጠይቅ ተጠይቀዋል። በፓርኩ መታሰቢያ ላይ እሷ እና ዱኩ የአበባ ጉንጉን በማስቀመጥ አክብረው ለ30 ሰከንድ ጸጥታ ቆሙ። በዚህም የተነሳ በህዝቡ ዘንድ የነበረው ቁጣ ረጋ ብሎ ተቃውሞው እንዲቆም ተደርጓል። እ.ኤ.አ. በኖቬምበር ላይ ንግስቲቱ እና ባለቤቷ ወርቃማ የሰርግ አመታቸውን ለማክበር በባንኬቲንግ ሀውስ ግብዣ አደረጉ። ንግግር አድርጋ ፊልጶስን “ጥንካሬና መቆያ” ብላ በመጥቀስ በረዳትነት ሚናውን አሞካሽታለች። ዩናይትድ ኪንግደም የአውሮፓ መሪዎች
50703
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8C%82%E1%8A%A6%E1%8D%96%E1%88%8A%E1%88%98%E1%88%AD%20%E1%88%B2%E1%88%9A%E1%8A%95%E1%89%B6
የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ
የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ በክፍል ውስጥ የሙቀት እና ቅዝቃዜ መጠን ለማጠንከር የሚያገለግል የማያያዣ ስርዓት ነው፡፡ ይህም ለፖርትላንድ ሲሚንቶ በአማራጭነት የቀረበ ከአካባቢ ጋር ጥሩ ግንኙነት ያለው ምርት ነው፡፡ በብዙ የሂንዱ ቤተመቅደሶች ውስጥ በአገልግሎት ላይ ውሎ የነበረ ሲሆን እነዚህም ከሺህ አመታት በላይ እድሜ ያላቸው ናቸው ከፍተኛ የካርቦን ምልክት ያላቸውን የሲሚንቶ ምርት ለመቀነስ በተፈጥሮ ካሉት የአፈር አይነቶች ወይም ከኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶች የሚሰራ ሲሆን በብዙ የአርማታ የቆይታ ጊዜ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ተከላካይ ሆኖ የሚያገለግል ነው፡፡ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች ከፖርትላንድ ሲሚንቶ በላይ የሚገኙ እና የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ የፖሊመር ሲሚንቶ ምርት አሉሚኒዮ ሲሊኬትን ለመፍጠር የሚያስፈልጉ እንደ ሜታ ፖሊን ወይም የአፈር ብናኝ የሚያስፈልግ ሲሆን እነዚህም ተጠቃሚ የሚገለገልባቸው እና ጉዳት የማያደርሱ የአልካላይን ሪኤጀንት ናቸው /ለምሳሌ የሶዲየም ወይም ፖታሺየም የሚሟሟ ሲሊኬት ከሞላር ሬሽዎ ሶዲየም ወይም ፖታሺየም የሆነ ኤም/ እንዲሁም ውሃ (ከዚህ በታች ያለውን ተጠቃሚ የሚገለገልበት እና ጉዳት የማያደርስ ሪኤጀንት ፍቺ ይመልከቱ) ፡፡ የክፍል ሙቀት እና ቅዝቃዜ ማጠናከሪያ የካልሺየም ካታዮኖችን በመጨመር ይህም የማቅለጫ ሀይል በመጨመር የሚሳካ ነው፡፡ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች ከፖርትላንድ ሲሚንቶዎች በፍጥነት ለማዳን የተሰሩ ናቸው፡፡ የተወሰኑት ውህዶች በ24 ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ጥንካሬያቸውን ያገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ በመቀላቀያ ፋብሪካ ውስጥ መቀላቀል እንዲችሉ በዝግታ መሰራት አለባቸው፡፡ ይህም ለስራውም ሆነ ወይም በአርማታ ማቀላቀያው ለማቅረብ ነው፡፡ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ በስሊኬት አለት ላይ ከተመሰረቱት ኮረቶች ጋር ጠንካራ የኬሚካል ቦንድ የመፍጠር ችሎታ አለው፡፡ በመጋቢት 2010 በዩኤስ የፌዴራል ትራንስፖርት የፍጥነት መንገድ አስተዳደር መምሪያ ጂኦፖሊመር አርማታ የተሰኘውን ቴክ ብሪፍ ለቅቆ የነበረ ሲሆን ይህም እንዲህ ይላል፡፡ሁለገብ የሆነ፣ ወጪ ቆጣቢ የሆኑ እና እንደ ፖርትላንድ ሲሚንቶ መቀላቀል እና ማጠንከር የሚችሉ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች የትራንስፖርት መሰረተ ልማት እና የግንባታ ኢንዱስትሪውን የግንባታ ደረጃ ማሻሻያ፣ ለውጥ እና ማሳደጊያ ሆኖ ሊወክል ችሏል፡፡ የጂኦፖሊመር አርማታ አጂኦፖሊመር ሲሚንቶ በሚለው እና ጂኦፖሊመር አርማታ በሚሉት ቃላት መካከል ሁልጊዜም ውዝግብ አለ፡፡ ሲሚንቶው መያዣ ሲሆን አርማታ ግን ሲሚንቶውን ከውሃ ጋር በመቀላቀል እና በማጠናከር የሚገኝ የቅልቅል ምርት ውጤት ነው፡፡ (ወይም በጂኦፖሊመር ሲሚንቶ አገላለጽ የአልካላይን) እንዲሁም የድንጋይ ኮረት ውህድ ነው፡፡ የሁለቱ ምርቶች (ጂኦፖሊመር ሲሚንቶ እና ጂኦፖሊመር አርማታ) መሳሪያዎች በተለያዩ በአለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ ገበያዎች ውስጥ ይገኛሉ ኬሚስትሪ፡ የፖርትላንድ ሲሚንቶ እና የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ግራ፡ የፖርትላንድ ሲሚንቶ (ፒሲ) የካልሲየም ስልኬትን ወደ ካልሲየም ስልኬት ሀይድሬት (ሲ-ኤስ-ኤች) እና ፖርትላንዳይት፣ )2 በመቀየር ማጠናከር, )2፡፡ ቀኝ፡ የፖሊመር ሲሚንቶውን (ጂፒ) ፖታሺየም አሊጐ (ሴሊየት ሲሎክሶ) የተባለውን የፖሊ ማቀዝቀዣ እና ማጠንከሪያ ወደ ፖታሺየም ፖሊ (ሲሊየት ሲሎክሶ) በመቀየር በተገናኘ ትስስር በኩል ማጠናከር ነው፡፡ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ውህዱ ሙቀት የሚፈልግ ከሆነ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ የሚባል ሳይሆን የጂኦፖሊመር መያዣ ይባላል፡፡ በአልካላይ የሚሰሩ መሳሪያዎች እና የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች የጂኦፖሊመራይዜሽን ኬሚስትሪ በፖርትላንድ ሲሚንቶ ባለሙያዎች አገልግሎት ላይ እየዋሉ ካሉት ቃላቶች እና ዝርዝሮች በተለየ ሁኔታ ትክክለኛ አገላለፆችን የሚፈልግ ነው፡፡ ጂኦፖሊመር አጠቃልሎ የሚይዘው ዋና ነገር የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች እንዴት በኦርጋኒት ፖሊመር ውስጥ እንደሚመደቡ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የአውስትራሊያዊው ጂኦፖሊመር ባለሙያ የሚከተለውን መግለጫ በድህረ ገፁ ላይ አስቀምጧል፡፡ ጆሴፍ ዴቪዶቪት የፖሊመርን ሀሳብ ፈጥሯል (የሲአይ/ኤኤል ኢንኦርጋኒክ ፖሊመር) ይህም እነዚህን የኬሚካል ሂደቶች እና የመሳሪያዎቹ ውጤቶችን በተሻለ ሁኔታ ለማብራራት ነው፡፡ ይህንን ለማድረግ በአንፃር ከፍተኛ ለውጥ ያስፈልጋል ይህም ከዋናው የክርስቲያላይን ሀይድሬሽን ኬሚስትሪ ማለት የተለመደው የሲሚንቶ ኬሚስትሪ ውጭ ማለት ነው፡፡ እስከዛሬ ድረስ ይህ ለውጥ በአልካላይን በሚሰሩ ሲሚንቶ ውስጥ በሚያገለግሉት ሀኪሞች ቀባይነት ያላገኘ ሲሆን እነዚህ አካላት መሰል ውህድን እስካሁንም በኬሚስትሪ የፖርትላንድ ሲሚንቶ ቃልን በመጠቀም ለማብራራት ይፈልጋሉ፡፡ በእርግጥ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ አንዳንድ ጊዜ በስህተት በአልካላይ የሚሰራ ሲሚንቶ እና አርማታ ተብሎ ይገለፃል፣ ከ50 አመታት በፊት በቪ.ዲ. ግሉሆቭስኪ በዩክሪን በቀድሞ ሶቪየት ህብረት ውስጥ የተሰራ የምርት አይነት ነው እነዚህን በዋናነት የአፈር ስልኬት አርማታዎች እና የአፈር ሲሚንቶዎች ተብለው ይታወቁ ነበር፡፡ ምክንያቱም የፖርትላንድ አርማታ ሲሚንቶዎች በጐጂው የአልካላይ እና ኮረት ውህድ፣ በተቀላቀለ የኤኤአር ወይም ከኤኤስአር ጋር በተቀላቀለ የአልካላይ ሲልካ ውህድ ሊጐድ የሚችሉ ሰለሆነ ነው /ለምሳሌ የሪለም ኮሚቴ 2019- ኤሲኤስ በአርማታ መዋቅር ባለው የኮረት ውህድ የተቀመጠውን ይመልከቱ ፡፡) አልካላይ አክቲቬሽን የሚለው ቃል በሲቪል መሃንዲሶች ላይ አሉታዊ ተጽእኖ አለው፡፡ ይሁን እንጂ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች በጥቅሉ እነዚህን የሚጐዱ ውህዶች አያሳይም (ከዚህ በታች በውህዶች ውስጥ ያለውን ይመልከቱ) ትክክለኛ የመቀላቀያ ኮረት ሲመረት የጂኦፖሊመሮች በአሲዳዊ ምርት ውስጥ ሊሰሩ የሚችሉ ሲሆን ከዚህ በይበልጥም እነርሱን ከኤኤኤም በመለየት ይሰራል፡፡ በተጨማሪም በአልካላይ የሚሰሩ ምርቶች ፖሊመሮች አይደሉም፡፡ስለዚህ ፖሊመር ተብለው ሊጠሩ አይችሉም ወይም ስህተት ሊሆኑ አይችሉም፡፡ በእርግጥ የፖሊመር ኬሚስትሪ ከካልሺየም ሀይሬድት ወይም ፕሪስፒቴት ኬሚስትሪ ጋር ሲነፃፀር በእጅጉ የተለየ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በርካታ የሲሚንቶ ሳይንቲስቶች በአልካላይ ከሚሰሩ መሳሪያዎች ወይም በአልካላይ ከሚሰሩ ፖሊመሮች ጋር የተገናኘውን ቃላት ማስተዋወቃቸውን ቀጥለዋል፡፡ እነዚህ የሲሚንቶ ምፃረ ቃላት ኤኤኤም ሲሆኑ ይህም በአካላይ የሚሰሩ ዝቃጮች፣ በአልካላይ የሚሰሩ የከሰል ብናኝ አፈር እና የተለያዩ የሲሚንቶ አሰራር ስርዓቶችን በተለየ ሁኔታ የያዘ ነው፡፡ (የሪለም ቴክኒካል ኮሚቴ 247-ዲቲኤ ይመልከቱ)፡፡ ተጠቃሚው የሚገለገልባቸው ጉዳት የማያደርጉ የአልካላይን ሪኤጀንቶች ጂኦፖሊመራይዜሽን በመርዛም የኦርጋኒክ ውህዶች ላይ የተመሰረተ አይደለም ነገር ግን በውሃ ላይ ብቻ የተመሰረተ ነው፡፡ አደገኛ ሊሆኑ የሚችሉ የኬሚካል ቅመማ ቅመሞችን የሚፈልግ ሲሆን ስለዚህም የተወሰኑ የደህንነት መጠበቂያ ህጐች ያስፈልጉታል፡፡ የደህንነት መጠበቂያ ሕጐቹ የአልካላይን ምርቶችን በሁለት ጐራ ይመድቡታል፡፡ ይህም የሚያዝጉ ምርቶች (እዚህ ውስጥ ሆስታይል ተብለው የተገለፁ) እና የሚገነፍሉ ምርቶች (እዚህ ውስጥ ጉዳት የማያደርሱ ተብለው የተገለፁ ናቸው) ሁለቱ አይነቶች በአርማዎቻቸው ይታወቃሉ፡፡ ሰንጠረዡ የተወሰኑ የአካላይን ኬሚካሎችን እና የደህንነት መጠበቂያ ደረጃቸውን አስቀምጧል፡፡ የሚያዝጉ ምርቶች በጓንት፣ በመስታወት እና በጭምብል በመጠቀም የምንገለገልባቸው ናቸው፡፡ እነዚህም ተጠቃሚውን ሊጐዱ የሚችሉ እና ትክከለኛ የደህንነት መጠበቂያ ሕጐችን ሳንከተል በብዛት ልንተገብራቸው የማንችላቸው ናቸው በሁለተኛው ምድብ የፖርትላንድ ሲሚንቶ ወይም ሀድሬትድ ላየን የተባሉ አይነተኛ ከፍተኛ ምርቶች ይገኛሉ፡፡ የጂኦፖሊመራዊ አልካላየን ሪኤጀንቶች የተባሉ እና በዚህ ምድብ የሚገኙት ምርቶች ተጠቃሚን የማይጐዱ ተብለው ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ እነዚህም የሚገነፍል ተፈጥሮ ያላቸው የአልካላይን ምርቶች ሲሆኑ የምርቶቻቸውን ዱቄቶች በአየር ወደ ውስጥ እንዳይገቡ ምርጫ እና ትክክለኛ የግል ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያ መልበስን የሚጠይቅ ሲሆን ይህም በማንኛውም ሁኔታ ኬሚካሎች ወይም ዱቄቶች በሚያዙበት አያያዝ መፈፀም ይገባል፡፡ በአልካላየን የሚሰሩ ሲሚንቶች ወይም በአልካላይን የሚሰሩ ፖሊመሮች (በተወሳኑት አካላት በኋላ ላይ ትክክለኛ ያልሆነ ቃል መሆናቸውን አውቀዋል)፡፡ እንዲሁም የተወሰኑ ባለሙያዎች በስነ ጽሑፉ ውስጥ እና በኢንተርኔት የተገኙ የተለያዩ አዘጋጃጀቶች በተለይም በብናኝ ላይ የተመሰረቱ የአልካላይን ስልኬቶችን ከሞላር ሬሽዎች ከ1.20 በታች ከሆነው ጋር ወይም በንፁህ የኤንኤኦኤች (8 ወይም 12) ሲስተሞች ላይ ተመስርቶ የሚያገለግል ሆኖ ተገኝቷል፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ለማንኛውም ሰው አገልግሎት ለማዋል በተጠቃሚው ላይ ጉዳት የማያደርሱ አይደሉም፡፡ ስለዚህ በዚህ የስራ መስክ ላይ ከተቀጠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ እና የግል የአደጋ መከላከያ መሳሪያ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ በእርግጥ የወጡ ሕጐች እና ደንቦች እንዲሁም መመሪያዎች ለሰራተኞች የደህንነት እና የጤና አጠባበቅ እንዲሁም ፕሮቶኮላቸውን ለማስፈፀም የወጡ ናቸው፡፡ ከዚህ በተቃራኒ በመስክ ላይ የተሰማሩ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ አዘገጃጀት ሰራተኞች የአልሪላይን ውህድ ያላቸውን ስልኬቶች ከማስጀመሪያ የሞላር ሬሾ መጠኑ 1.45 እስከ 1.95 ከሆነው ጋር ያካትታሉ፡፡ በተለይም ከ1.60 እስከ 1.85 በሚያህለው በማካተት የሚፈጽሙ ሲሆን ይህም ተጠቃሚውን በማይጐዱ ሁኔታዎች የሚያገለግል ነው፡፡ ለምርምር አላማ የተወሰኑ የላብራቶሪ አዘገጃጀቶች ከ1.20 እስከ 1.45 የሚሆኑ የሞላር ሬሾዎች ያላቸው ናቸው፡፡ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ምድቦች የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ምድቦች በዝቃጭ ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ፡፡ በአለት ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ፡፡ በብናኝ አፈር ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ አይነት 1፡ በአልካላይ የሚሰራ የብናኝ አፈር የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ፡፡ አይነት 2፡ በዝቃጭ/በብናኝ አፈር ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ፡፡ የፌሮ ሴሊየት ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ፡፡ በዝቃጭ ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ የተሰራባቸው ዝርዝሮች፡ ሜታ ኮሊን + የብረት ማቅለጫ ዝቃጭ + አልካላይ ስልኬት (ተገልጋይ የሚጠቀምባቸው እና የማይጐዳ)፡፡ የጂኦፖሊመር ስሪት፡ = 2 በእርግጥ የኤስአይ፡ ኤኤል = 1 ጠጣር ውህድ ነው፣ =1(ዳይ-ስልኬት) (የአኖርታይት አይነት) + - ፖሊ (ሲያሌት - ዳይሲሎክሶ) (ኦርቶ ክላስ አይነት) እና ካልሺየም - ሲሊኬት ሀይድሬት፡፡ የመጀመሪያው የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ የተፈጠረው በ1980ዎቹ ሲሆን አይነቱ (ፓታሺየም፣ ሶዲየም፣ ካልሺየም) - ፖሊ (ሲያሌት) (ወይም በዝቃጭ ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ሆኖ) እንዲሁም በጆሴፍ ዴቭዶቪትስ እና በጄ.ኤል ሳውኢር በሎን ስታር ኢንዱስትሪዎች ዩኤስኤ ውስጥ ከተካሄዱት ምርምሮች የተገኘ ሲሆን እንዲሁም የፓይራሜንት አር ሲሚንቶ የተገኘበት ነው፡ የአሜሪካ የፈጠራ ተግባር የተመዘገበው በ1984 ሲሆን የዩኤስ የፈጠራ ባለቤትነቱ 4,509,985 የሚያህል በሚያዝያ 9/1985// ኢርሊ ሀይ ስትሬንግዝ ሚኒራል ፖሊመር በሚል ስያሜ የተሰጡ ናቸው፡፡ በአለት ያለ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ አየተወሰኑ -750ምርት ከተመረቱት የቮልካኖ ውጤቶች የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ጋር እንዲሁም በቀላል ዝቃጭ ላይ ከተመሰረተው የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ በላይ ዝቅተኛ የካርቦን ልቀት ባላቸው እና የተሳለ ምርት ባላቸው ውጤቶች መተካት፡፡ የማምረቻ ግብአቶች፡ ሜታኮሊን -750፣ የብረት ማቅለጫ፣ የቮልካኖ ውጤቶች (ወደ አመድነት የተቀየሩ ወይም ወደ አመድነት ያልተቀየሩ)፣ የድንጋይ ካቦች እና የአልካላይ ስሊኬት (ተጠቃሚውን የማይጐዱ) ናቸው፡፡ የጂኦፖሊመሪክ ስሪት፡ = 3 በእርግጥ የኤስአይ፡ ኤኤል = 1 ጠጣር ውህድ ነው፣ =1 (ዳይ-ስልኬት) (የአኖርታይት አይነት) + )- ፖሊ (ሲያሌት - ዳይሲሎክሶ) (ኦርቶ ክላስ አይነት) እና ሲ-ኤስ-ኤች ካልሺየም -- ሲሊኬት ሀይድሬት፡፡ በብናኝ አፈር ላይ የተመሰረቱ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች በኋላም በ1997 በዝቃጭ ላይ በተመሰረተው የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች ላይ በተካሄዱ ስራዎች በሌላው በኩል በመገንባት እና እንዲሁም ደግሞ በአንዱ በኩል ከዚኦላይትስ ስሪት በተገኙ በአፈር ብናኝ ላይ በመገንባት እነ ሲሊቨር ስትሪም እና ቫን ጃርስቬልድ እንዲሁም ቫንዴቨንተር በብናኝ አፈር ላይ የተመሰረቱትን የጂኦፖሊመሪክ ሲሚንቶዎችን ለመፍጠር ችሏል፡፡ እነ ሲልቨርስትሪም 5,601,643 የዩኤስ የፈጠራ ባለቤትነት ፍላይ አሽ ሴሜንቲሺየስ ማቴሪያል እና የምርት አሰራር ዘዴ በሚል የተመዘገበ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሁለት አይነት በሲሊከስ ወይም በደረጃ 618) የብናኝ አፈር አይነቶች ላይ የተመሰረቱ ምርቶች አሉ፡፡ ዓይነት 1: -ስለጀመሩ ቅድሚያ በቀዳሚ (የተጠቃሚ-ባለጋራ)፡፡ በብዙ ሁኔታዎች የማሞቂያ ደረጃው ከ60-80 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ላይ ነው፣ እንደ ሲሚንቶ ተለያይቶ የሚመረት ሳይሆን ልክ እንደ ብናኝ አፈር አርማታ በቀጥታ የሚመረት ነው፡፡ ናይትሮጂን ሀይድሬት (በተጠቃሚው ላይ ጉዳት የሚኖረው) + ብናኝ አፈር፡ በከፊል የተዋሀዱ የብናኝ አፈር ሆኖ በአሉሚኖ- ሲሊኬት ጄል የተያያዙ እና ኤስአይ፡ ኤኤል = 1 እስከ 2፣ ከዞሊን አይነት (ቻባዛይት- ናይትሮጂን እና ሶዳላይት) መዋቅሮች ጋር የተያያዘ ነው፡፡ አይነት 2፡ የዝጋጭ/የብናኝ አፈር ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ (ለተጠቃሚው ጉዳት የሌለው)፡፡ በክፍል ሙቀት እና ቅዝቃዜ መጠን የማጠንከር ስራ ለተጠቃሚው ጉዳት የሌለው የስልኬት ውህድ + የብረት ማቅለጫ + ብናኝ አፈር፡ በጂኦፖሊመሪክ ማትሪክስ የተካተቱ የብናኝ አፈር ከ = 2 (ካልሺየም፣ ፖታሺየም) - ፖሊ (ሲሊየት - ሲሎክሶ) በፌሮ - ሲሊየት ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ የማምረቻ ዝርዝሮቹ በአለት ላይ ከተመሰረተው የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ጋር ተመሳሳይነት ያለው ሆኖ ነገር ግን በከፍተኛ ደረጃ የኦክሲጅን ይዘት ባለው አይረን የጂኦለጂካል ኤሌመንቶችን ያካተተ ነው፡፡ የጂኦፖሊመር ስሪት አይነት የፖሊ (ፌሮ - ሲሊየት) (ካልሺየም፣ ፖታሺየም) – (አይረን - ኦክሳይድ) – (ሲልከን - ኦክስጅን - አሉሙኒየም - ኦክስጂን) ናቸው፡፡ ይህ በተጠቃሚው ላይ ጉዳት የሌለው የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ በመመረት እና ለንግድ በማቅረብ ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡ በማምረት ወቅት የሚኖሩ የካርቦን ዳይኦክሳይድ ልቀቶች እንደ አውስትራሊያዊው የአርማታ ባለሙያ ቢ. ቪ. ራንጋን ከሆነ እያደገ ያለው አለም ሁሉም የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ አይነቶችን ለማምረት ያለው የአርማታ ፍላጐት ከፍተኛ እድል ነው፡፡ ምክንያቱም በሚመረቱበት ወቅት ዝቅተኛ የካርቦንዳይኦክሳይድ መጠን ስለሚለቁ ነው፡፡ የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት ንጽጽር የፖርትላንድ ሲሚንቶ ማምረቻው በሚከተሉት ውህዶች መሰረት የካልሺየም ካርቦኔትን ወደ አመድነት የመቀየር አሰራርን አካትቷል፡፡ የአሉሚናን የሚያካትቱ ውህዶች የምርቱን የአሉሚኔት እና ፌሪት ይዘቶች ወደ መፍጠር የሚያመሩ ናቸው፡፡ አንድ ቶን የፖርትላንድ ክሊንከርን ማምረት በግምት 0.55 ቶን የሚያህሉ የካርቦንዳይኦክሳይድ ኬሚካልን በቀጥታ ያወጣል፡፡ ይህም የዚህ ምርት ውህዶች ሆኖ የሚወጣ ሲሆን ስለዚህ ደግሞ ተጨማሪ የ0.40 ቶን ካርቦንዳይኦክሳይድ ምርት ለማምረት የካርቦን ምርት ያለውን ነዳጅ መቀላቀል ያስፈልጋል፡፡ ይህንንም የስራውን ሂደት ብቃት በማግኘት እና ቆሻሻዎችን እንደ ነዳጅ በመጠቀም መቀነስ ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ በአጠቃላይ 1 ቶን የፖርትላንድ ሲሚንቶ ከ0.8 እስከ 1.0 ቶን ካርቦንዳይኦክሳይድ የሚለቅ ይሆናል፡፡ በንጽጽር ሲታይ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች እንደ ቁልፍ ጥሬ እቃ በካልሺየም ካርቦኔት ላይ አይመሰረቱም እንዲሁም በማምረቻ ወቅት ያነሰ የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት የሚያወጡ ሲሆን ይህም ከ40 በመቶ እስከ 80-90 በመቶ መጠን ያለውን የሚቀንስ ነው፡፡ ጆሴፍ ዴቭዶቪትስ በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ በመጋቢት 13/1993 የመጀመሪያ ጽሑፉን ያቀረበ ሲሆን ይህም በአሜሪካ ሲሚንቶ ማህበር በቺካጐ ኢሊኖይስ በተዘጋጀ ሲምፖዚየም ላይ ነው፡፡ የፖርትላንድ ሲሚንቶ ኢንዱስትሪ የሕግ ተቋማትን በማግባባት በስሙ የሚከራከሩ ሲሆን ይህም የሚለቁት የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት ቁጥር ከካልሺየም ካርቦኔት ብስባሴ ጋር የተገናኘውን ክፍል የማያካትት ሲሆን ነገር ግን በውህደቱ ልቀት ላይ ብቻ ትኩረት የሚያደርጉ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ኒው ሳይንቲስት በተባለ ሳይንሳዊ መጽሔት ውስጥ የተፃፈው የ1997 አንቀጽ እንዲህ ይላል …ከሲሚንቶ ማምረቻ የሚለኩ የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት ግምቶች በቀድሞ ምንጭ (የነዳጅ ቅልቅል) ላይ ብቻ ትኩረት ያደረጉ ናቸው፡፡ በመንግስታት መካከል የተደረገው እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የተካሄደው የዩኤን ፓነል ውይይት አጠቃላይ ኢንዱስትሪው የሚለውቀው የካርቦንዳይኦክሳይድ መጠን 2.4 በመቶ መሆኑን እንዲሁም በታናሴ የኦክሪጅ ብሔራዊ ላብራቶሪ ውስጥ የተገኘው የካርቦንዳይኦክሳይድ መረጃ ትንተና ማዕከሉ መጠን 2.6 ካርቦንዳይኦክሳይድ መሆኑን ይገልፃል፡፡ አሁን የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ተቋሙ ጆሴፍ ዶቪዶቪትስ ለመጀመሪያ ጊዜ በሁለቱም ምንጮች ምልክታዎችን አድርጓል፡፡ እርሱም እንዳሰላው ከሆነ በአመት የሚመረተው 1.4 ቢሊየን ቶን የአለም ኤለመንት አሁን ያለው የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት /በአለም/ 7 በመቶ ያህል ያመርታል፡፡ ከ15 አመታት በኋላ /2012/ ሁኔታው በፖርትላንድ ሲሚንቶ የካርቦንዳይኦክሳይድ ይህም በአመት 3 ቢሊየን የሚሆን በመሆኑ የከፋ ሆኗል፡፡ የፖርትላንድ ሲሚንቶ ምርት ከዚህ የበለጠውን ካርቦንዳይኦክሳይድ የሚያወጣ ሲሆን ይህም ወደ አመድነት በሚቀየርበት ጊዜ አገልግሎቱ እና የመቆየት መጠኑ አገልግሎት ላይ በሚውለበት ጊዜ ማለት ነው፡ ስለዚህ የጂኦፖሊመሮች በንጽጽሩ 40 በመቶ ወይም ከዚህ በታች ልቀቶች ሊኖራቸው የሚገባ ሲሆን ይህም ያለቀላቸው ምርቶች ሲታዩ ተመራጭ እንዲሆኑ ማለት ነው፡፡ ንጽጽራዊ የሀይል አገልግሎት ለመደበኛው የፖርትላንድ ሲሚንቶ፣ በአለት ላይ ለተመሰረተው ለጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች ለብናኝ አፈር ላይ ለተመሰረቱን የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች የሚያስፈልገው የሀይል መጠን እና የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀት፡፡ በፖርትላንድ ሲሚንቶ እና በጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች መካከል በተመሳሳይ ጥንቃቄ ያለው ንጽጽር በአማካይ በ28 ቀናት ውስጥ 40 ኤምፒኤ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ በርካታ ጥናቶች የታተሙ ሲሆን ይህም በሚከተለው መንገድ ተጠቃልሏል፡፡ በአለት ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ አመራረት የሚያካትተው፡ በክብደት 70 በመቶ የሆኑ የጂኦሎኪል ኮምፓውንዶች (በ700 ዲግሪ ሴንቲግሬድወደ አመድነት የተቀየረ)፡፡ የብረት ማቅለጫ ዝቃጭ፡፡ የአልካላይን - ስልኬት ውህድ /የኢንዱስትሪ ኬሚካል፣ ተጠቃሚውን የማይጐዳ/፡፡ የብረት ማቅለጫ ዝቃጭ መኖሩ ያለ ክፍል ቴምፕሬቸር ለማጠንከር እና የመካኒካል ጥንካሬውን ለመጨመር ይረዳል፡፡ የኃይል ፍላጎቶች በዩኤስ የፖርትላንድ ሲሚንቶ ማህበር መሰረት ለፖርትላንድ ሲሚንቶ የሚያስፈልገን የሀይል መጠን በአማካይ 4700 ኤምጄ/ቶን ነው፡፡ በአለት ላይ የተመሰረተው የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ስሌት በሚከተሉት ልኬቶች ላይ ተመስርቶ የተሰራ ነው፡፡ - የብረት ማቅለጫ ዝቃጩ ከብረታ ብረት ኢንዱስትሪ በተረፈ ምርት መልክ የሚገኝ ነው (ምንም አይነት ተጨማሪ ሀይል አያስፈልገውም)፡፡ - ወይም መመረት አለበት (ደቃቃ ካልሆነው ዝቃጭ ወይም ከጂኦሎጂካዊ ሀብቶች በድጋሚ የቀለጠ)፡፡ በጣም ተመራጭ በሆነው ሁኔታ - በተረፈ ምርትነት መልክ የሚገኝ ዝቃጭ - በአለት ላይ የተመሰረተውን የፖሊመር ሲሚንቶ ማምረት ከፖርትላንድ ሲሚንቶ ጋር ሲነፃፀር የሚያስፈልገው የሀይል መጠን 59 በመቶ ይቀንሳል፡፡ ዝቅተኛ ተመራጭነት ባለው ሁኔታ ደግሞ የዝቃጭ ማምረቻው - ቅነሳው 43 በመቶ ይደርሳል፡፡. በማምረት ወቅት የሚኖር የካርቦን ልቀት መጠን በጣም ተመራጭ በሆነው ሁኔታ - በተረፈ ምርትነት መልክ የሚገኝ ዝቃጭ - በአለት ላይ የተመሰረተውን የፖሊመር ሲሚንቶ ማምረት ከፖርትላንድ ሲሚንቶ ጋር ሲነፃፀር የሚያስፈልገው የሀይል መጠን 80 በመቶ ይቀንሳል፡፡ ዝቅተኛ ተመራጭነት ባለው ሁኔታ ደግሞ የዝቃጭ ማምረቻው - ቅነሳው 70 በመቶ ይደርሳል፡፡ በብናኝ አፈር ላይ የተመሰረቱ ደረጃ ኤፍ የሆኑ ሲሚንቶዎች እነርሱ ምንም አይነት ተጨማሪ ሙቀት አያስፈልጋቸውም፡፡ ስለዚህም ስሌቱ ቀላል ነው፡፡ ይህም በብናኝ አፈር ላይ ለተመሰረተው የአንድ ቶን ሲሚንቶ የሚለቀው የካርቦንዳይኦክሳይድ መጠን ከ0.09 እስከ 0.25 ቶን ሲሆን ይህም ማለት የካርቦንዳይኦክሳይድ ልቀቱን ከ75 እስከ 90 በመቶ በሚያክል መቶን ይቀንሳል ማለት ነው፡፡ በአለት ላይ ለተመሰረቱ ለጂኦፖሊመር ሲሚንቶ የሚያስፈልጉ ግብአቶች (ካሊሺም፣ ፖታሺየም) – ፖሊ (ሲያሌት-ዳይሲሎክሶ) ይህንን ይመልከቱ በሚሰራበት ጊዜ ያለው የመሸብሸብ መጠን፡ ከ0.05 በመቶ በታች፣ አልተለካም፡፡ ንጽጽራዊ ጥንካሬ (አንድ አክሰስ)፡ በ28 ቀናት ከ90 በላይ (ለከፍተኛ የጥንካሬ ስራ፣ ከ4 ሰዓታት በኋላ 20 ፡፡ የጉብጠት/ልምጠት ጥንካሬ፡ በ28 ቀናት ከ10 እስከ 15 (ለከፍተኛ የጥንካሬ ስራ፣ ከ24 ሰዓታት በኋላ 10 ) ፡፡ የያንግ ሞጁልስ፡ ከ2 በላይ፡፡ የማቀዝቀዣ - ታው፡ የክብደት መቀነስ ከ0.1 በመቶ በታች ፣ የጥንካሬ መቀነስ ከ5 በመቶ በታች ከ180 ኡደቶች በኋላ፡፡ የእርጥብ - ደረቅ ፡ የክብደት መቀነስ ከ 0.1 በመቶ በታች (( በውሃ ውስጥ የመለየት መጠኑ፣ ከ180 ቀናት በኋላ፡ ከ0.015 በመቶ በታች የውሃ መምጠጥ መጠን፡ ከ3 በመቶ በታች፣ ከውሃ ማሳለፍ አቅም ጋር የተገናኘ አይደለም የውሃ ማሳለፍ መጠን፡ 10-10 ሜትር በሰከንድ ሰልፈሪክ አሲድ፣ 10 በመቶ፡ የክብደት መቀነስ 0.1 በመቶ በቀን ሀይድሮክሎሪክ አሲድ፣ 5 በመቶ፡ የክብደት መቀነስ በቀን 1 በመቶ 50 በመቶ፡ የክብደት መቀነስ በቀን 0.02 በመቶ የአሞኒያ ውህድ፡ የክብደት መቀነሱ አልታየም የሰልፌት ውህድ፡ በ28 ቀናት ውስጥ 0.02 በመቶ ተሸብሽቧል የአልካላይ እና የኮረት ውህድ፡ ከ250 ቀናት በኋላ ምንም የተስፋፋ ነገር የለም (ሲቀነስ 0.01 በመቶ) በምስሉ ላይ እንደተመለከተው ከፖርትላንድ ሲሚንቶ (ኤኤስቲኤም ሲ227) ጋር ሲነፃፀር፡፡ እነዚህ ውጤቶች በ1993 የታተሙ ናቸው፡፡ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች እና መያዣዎች ከአልካላይ ይዘቶች ጋር እስከ 10 በመቶ ድረስ ከፍተኛ ሲሆኑ ለመደበኛ ውህደት ከኮረት ጋር ሲጠቀሙ ምንም አይነት የአልካላይ እና የኮረት ውህደት አደገኛነት አያስከትሉም ፡፡ የደረጃዎች አስፈላጊነት በሰኔ 2/2012 እ.ኤ.አ ኤኤስቲኤም ኢንተርናሽናል የተባለው ተቋም (የቀድሞው የአሜሪካ የምርመራ እና የአፈር፣ ኤኤስቲኤም ማህበር) በጂኦፖሊመር መያዣ ሲስተሞች ላይ ሲምፖዚየም አዘጋጅቶ ነበር የሲምፖዚየሙ መግቢያ እንዲህ ይላል፡ ለፖርትላንድ ሲሚንቶ የአፈፃፀም ማብራሪያዎች ሲፃፉ ፖርትላንድ ያልሆኑ መያዣዎች የሚታወቁ አልነበሩም፡፡ እንደ ጂኦፖሊመሮች የመሳሰሉ አዳዲስ መያዣዎች በከፍተኛ ደረጃ ምርምር ተካሂዶባቸው እንደ ልዩ ምርቶች በገበያ ላይ ውሎ በመዋቅራዊ አርማታ ላይ አገልግሎት ላይ ውሏል፡፡ ይህ ሲምፖዚየም የኤኤስቲኤም ተቋም ያሉትን የሲሚንቶ ደረጃዎች አቅርቦት ከግምት እንዲያስገባ ይህም በአንዱ መንገድ ተጨማሪ የጂኦፖሊመር መያዣዎችን ለማግኘት ውጤታማ ስራ እንዲሰራ እንዲሁም በሌላ መንገድ እነዚህን ምርቶች ለሚጠቀሙ አካላት አስተማማኝ ጥበቃ ለማቅረብ እድል እንዲሰጠው ታስቦ የተካሄደ ነው፡፡ ያሉት የፖርትላንድ ሲሚንቶ ደረጃዎች ከጂኦፖሊመር ሲሚንቶ ጋር የሚሄዱ አይደሉም፡፡ በልዩ ኮሚቴ ሊፈጠሩ ይገባል፡፡ ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ደረጃቸውን የጠበቁ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶዎች መገኘት አለባቸው፡፡ በአሁኑ ጊዜ እያንዳንዱ ባለሙያ በሀገር ውስጥ ሕግ ላይ በመመስረት የራሱን አሰራር ዘዴ ማቅረብ ያለበት ሲሆን ይህም በምርቶቹ (ቆሻሻዎች፣ ተረፈ ምርቶች ወይም የተጣሉ ምርቶች) ላይ በመመስረት ነው፡፡ ትክክለኛ የጂኦፖሊመር ሲንቶን ምድብ ለመምረጥ የሚያስፈልግ ነገር አለ የ2012 የጂኦፖሊመር ስቴት ጥናትና ምርምር. ሁለት ስሞቻቸው ከዚህ በታች የተጠቀሱ ምድቦችን እንደ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ የአይነት 2 ዝቃጭ/ በብናኝ አፈር ላይ የተፈሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ፡ የብናኝ አፈር የሚገኙት በዋናነት እያደጉ ባሉ ሀገራት ውስጥ ነው፡፡ በፌሮ - ሲሊየት ላይ የተመሰረተ የጂኦፖሊመር ሲሚንቶ፡ ይህ በገፀ ምድር አይረን የበለፀገው ጥሬ እቃ በአለም አቀፍ ደረጃ በሁሉም ሀገራት ውስጥ የሚገኝ ነው፡፡ ትክክለኛ ተጠቃሚን የማይጐዳ የጂኦፖሊመር ሪኤጀንት
13076
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9D%E1%88%8D%E1%8C%83
ምልጃ
መላእክት የኛን ጸሎት ስለሚያመላልሱ ስለኛ ያውቃሉ ከላይ እንዳየነው , "ባንድ ሀጥያተኛ መዳን " የተነሳ በሰማይ ደስታ እንዳለ ተመልክተናል :: ሉቃስ በወንጌሉ , በዚህ ሳይወሰን , በመላእክት ፊት ደስታ እንዳለ ጠቁሞናል (ሉቅ 15:10) እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል። ይህ ምንባብ እንግዲህ በምንም በማያሻማ መልኩ ስለኛ መዳን "መላእክት እንደሚጨነቁ አስረድቶን አልፏል :: ከመጨነቅ አልፈውም , የኛን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ዙፋን እንደሚያደርሱ እና ስለዚህም ስለኛ እውቀት እንዳላቸው በዮሐንስ ራእይ ተመዝግቦ ይገኛል :- (ራእይ 8:3-4) 3 ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሰዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሰዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ ዕጣን ተሰጠው። 4 የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ። እዚህ ላይ እንደምናየው የቅዱሳን ጸሎት ከመላእክት እጅ ሲያርግ ሲሆን , ይህ ከሆነ ዘንድ እንዴት መላእክት የኛን ጸሎት አያውቁም ማለት እንችላለን ?? በዚህ ትይዩ , አይደለም መላእክት , ሀያ አራቱ ቀሳውስት እንኳን የኛን ጸሎት እንደሚያውቁና እንደሚያሳርጉ መ /ቅዱስ መዝግቧል ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ። (ራእይ 5: ይህ እሚያሳየው ወደ እግዚአብሔር የሚያርገውን የኛን ጸሎት እንድሚያውቁ ነው :: ድጋሚ የተጠየቀ ጥያቄ :- ጻድቃን ሰማእታት ስለምድር ስለሚሆነው ያውቃሉን ከላይ እንዳየነው ቅዱስ ጳውሎስ ሲመሰክር : ሰማይ ያለው እውቀት መሬት ካለው እጅግ የገዘፈ መሆኑን አስረድቷል :: ለዚህ የጳውሎስ ምስክርነት ደጋፊ የመ /ቅዱስ ክፍል አለን ? መልሱ አወ ነው :: በሉቃስ 16 ተመዝግቦ የሚገኘውን አላዛር ስለተባለ ድሀ , ሰለ አንድ ባለጠጋ ጎረቤቱና ስለአብርሀም , የክርስቶስ እየሱስ ምስክርነት እንከታተል :- 23 [ባለጠጋው ] በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ። 24 እርሱም እየጮኸ። አብርሃም አባት ሆይ፥ ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ አለ። 25 አብርሃም ግን። ልጄ ሆይ፥ አንተ በሕይወትህ ሳለህ መልካም እንደ ተቀበልህ አስብ አልዓዛርም እንዲሁ ክፉ፤ አሁን ግን እርሱ በዚህ ይጽናናል አንተም ትሣቀያለህ። ጥያቄ : አብርሀም እንዴት የባለጠጋውን የምድር ላይ ህይወት ሊያውቅ ቻለ :: ጥሩ ነገረስ ገጥሞት እንደ ነበር እንዴት አወቀ ? (ሉቃ 16)27 እርሱም። እንኪያስ፥ አባት ሆይ፥ ወደ አባቴ ቤት እንድትሰደው እለምንሃለሁ፤ አምስት ወንድሞች አሉኝና፤ 28 እነርሱ ደግሞ ወደዚህ ሥቃይ ስፍራ እንዳይመጡ ይመስክርላቸው አለ። 29 አብርሃም ግን። ሙሴና ነቢያት አሉአቸው፤ እነርሱን ይስሙ አለው። 30 እርሱም። አይደለም፥ አብርሃም አባት ሆይ፥ ነገር ግን ከሙታን አንዱ ቢሄድላቸው ንስሐ ይገባሉ አለ። 31 ሙሴንና ነቢያትንም የማይሰሙ ከሆነ፥ ከሙታንም እንኳ አንድ ቢነሣ አያምኑም አለው። ጻድቃን ሰማእታት ምድር ላይ ስለሚሆነው አያውቁም ከተባለ : እንዴት አባታችን አብርሀም ስለ ሙሴና ስለነቢያት ሊያውቅ ቻለ ? ሙሴና ነቢያት ከመወለዳቸው በፊት , አብርሀም በስጋ ሞት ከምድር ከተለየ ዘመናት አላስቆጠረምን ?? ስለዚህስ እንዴት አያውቅም በሚል እልህ እንቀጥላለን :: ቃሉ እንደሚያስረዳን , አብርሀም ያውቃል , ሙሴ ያውቃል , ቅዱስ ሰማእታት ያውቃሉ :: የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ንግግር ሙሉ በሙሉ ምሳሌያዊ ነው። አብርሃም የእግዚአብሔር ምሳሌ፣ ሙሴና ነቢያትም የጌታን ቃል ለህዝብ የሚያስተምሩ አገልጋዮች ወይም የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት እንደ ምሳሌ ሆነው መጠቀሳቸውን ልብ ማለት ይገባል። እንዲያውም መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ "ሙታን አንዳች አያውቁም" ይላል። (መክብብ. 9፡5) ጻድቃን ነፍሳት ምስክርነት 9 አምስተኛውንም ማኅተም በፈታ ጊዜ፥ ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ጠበቁት ምስክር የታረዱትን የሰዎች ነፍሳት ከመሠዊያ በታች አየሁ። 10 በታላቅ ድምፅም እየጮኹ። ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ፥ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም ደማችንንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም ? አሉ። 11 ለእያንዳንዳቸውም ነጭ ልብስ ተሰጣቸው፥ እንደ እነርሱም ደግሞ ይገደሉ ዘንድ ያላቸው የባሪያዎች ባልንጀራዎቻቸውና የወንድሞቻቸው ቍጥር እስኪፈጸም ድረስ፥ ገና ጥቂት ዘመን እንዲያርፉ ተባለላቸው። (ራእይ 6: 9-11) ሰማእታተ , በስጋ ከሞቱ በሗላ , ጌታ ደማቸውን እንዳልተበቀለ እንደሚያውቁ ከላይ የተጠቀሰው የራእይ ክፍል ያስረዳናል :: በምድር የሚካሄደውን ካላወቁ ይህን ጉዳይ እንዴት ሊያውቁ ቻሉ ? የነቢዩ ኤልያስ ደብዳቤ ንጉስ እዮራም , እንዴት ወንድሞቹን እንደገደለና የአይሁድን ዜጎች በሽርሙጥና -ባርነት እንደሸጠ የሚያትት ታሪክ በዜና መዋእል ካልእ ተመዝግቦ ይገኛል :: በዚሁ መጽሀፍ ከብዙ ዘመን በፊት , ከመሬት የተነጠቀው ነቢዩ ኤልያስ ለንጉሱ የጻፈውን ደብዳቤ እንዲህ ሲል ያስነብበናል : 12፤ ከነቢዩም ከኤልያስ እንዲህ የሚል ጽሕፈት መጣባት። የአባትህ የዳዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። በአባትህ በኢዮሣፍጥ መንገድ በይሁዳም ንጉሥ በአሳ መንገድ አልሄድህምና፥ 13፤ በእስራኤል ነገሥታት መንገድ ግን ሄደሃልና፥ የአክዓብም ቤት እንዳደረገ ይሁዳንና በኢየሩሳሌም የሚኖሩትን እንዲያመነዝሩ አድርገሃልና፥ ከአንተም የሚሻሉትን የአባትህን ቤት ወንድሞችህን ገድለሃልና፥ 14፤ እነሆ፥ እግዚአብሔር ሕዝብህንና ልጆችህን ሚስቶችህንም ያለህንም ሁሉ በታላቅ መቅሠፍት ይቀሥፋል። 15፤ አንተም ከደዌው ጽናት የተነሣ አንጀትህ በየዕለቱ እስኪወጣ ድረስ በክፉ የአንጀት ደዌ ትታመማለህ። (2ዜና 21:12-15) እንዴት ነብዩ ኤልያስ በምድር ላይ ስለሚሆነው ሊያውቅ ቻለ ? ደብዳቤውንስ እንዴት ለንጉሱ ሊልክ ቻለ ? የመላእክት ሰለኛ ጣልቃ መግባት ካሁን በፊት እንደተዘረዘረው , መላእክት ካንዴም ሁለት ጊዜ , እንዲሁም ከዚያ በላይ ለሰው ልጆች ሲማልዱ አይተናል :: የጻድቃንንም ጸሎት ሲያሳርጉ , እንዲሁ :: ጥያቄ :: ከላይ ከተዘረዘሩት ማስረጃወች ውጭ , መ /ቅዱስ ስለ መላእክት ምልጃ ተጨማሪ የመዘገበው ንባብ አለን ?? 12፤ የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህ ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው ? አለ። (ዘካ 1:12) እንግዲህ መላእኩ ሳይጠየቅ እንዲህ ሲል ከማለደ , ቢጠየቅማ የቱን ያክል ሊሆን ነው ? በሌላኛው የትንቢተ ዘካርያስ መጽሀፍ ክፍል የእግዚአብሔር መላእክ በሰይጣን ተከሶ በእግዚአብሔር ፊት ለቀረበው ለሊቀ ካህኑ እያሱ እንዲ የሚል ማማለድ /ማጽናናት ሲያቀርብ እናያለን 3፤ ኢያሱም እድፋም ልብስ ለብሶ በመልአኩ ፊት ቆሞ ነበር። እርሱም [መልአኩ ] መልሶ በፊቱ የቆሙትን። እድፋሙን ልብስ ከእርሱ ላይ አውልቁ አላቸው። እርሱንም። እነሆ፥ አበሳህን [ሀጥያትክን ] ከአንተ አርቄአለሁ፥ ጥሩ ልብስም አለብስሃለሁ አለው። ሌላኛው ምሳሌ በኦሪት ዘፍጥረት ተመዝግቦ የሚገኘው ሲሆን , ይህ ክፍል እንዴት የእግዚአብሔር መላእክ , ያእቆብን ከጥፋት እንደታደገው ያስርዳና , ያእቆብ እራሱ ኤፍሬምንና ምናሴን ሲባርክ የተናገራቸውን ምርቃቶች እንዲህ ሲል ይመዘግባል 16፤ ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ፥ እርሱ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ፤ ስሜም የአባቶቼ የአብርሃምና የይስሐቅም ስም በእነርሱ ይጠራ፤ በምድርም መካከል ይብዙ። {ዘፍጥ 48:16) ይህን ደጋፊ ክፍል በእብራውያን 1:14 ላይ በጥያቄ መልክ ተመዝግቦ ይገኛል :: መላእክት ሁሉ መዳንን የሚወርሱትን ለማገልገል የሚላኩ አገልጋይ መናፍስት አይደሉምን :: ይህ ክፍል በማያሻማ መልኩ መላእክት በምድር ላይ ስራ እንዳላቸው አስምሮበት አልፏል :: በቀጣዩ ክፍል የጻድቃንን ታላቅነት , አገልግሎት , የእውቀታቸውን ስፋት , በእግዚአብሔር ዘንድ ያላቸውን ክብር /ሞገስ እናያለን :: ቀጥለንም በምልጃ ላይ የተነሱ ተቃውሞወች እና መልሶቸውን እናያለን :: ከዚያም በሰፊው በክርስቶስ ማማለድ እና በጻ /ሰማእታት , በመላእክት ማማለድ ያለውን ልዩነት አይተን , ለማሳረጊያ የምልጃን መንፈሳዊ ትርጉም አይተን እንዘጋለን :: እስከዛው ህያው እግዚአብሔር ለሁላችንም መባረክን ይስጠን :: መጽሐፍ ቅዱስ
14097
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A8%E1%88%83%E1%8A%93%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A8%E1%88%9B%E1%88%AA%E1%8B%AB%E1%88%9D
ገብረሃና ገብረማሪያም
አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። አለቃ ገብረሃና በቅኔያቸው የሃይማኖት አለቆቻቸውን ወይም የበላዮቻቸውን ብቻ ሳይሆን የገነት ጌታን «ኰንኖ ኃጥአን ኩሎሙ አይደልወከ ምንተ፣ አፍቅሩ ፀላእተከሙ እንዘ ትብል አንተ» ኃጥአንን በገሃነመ እሳት ማሰቃየትና መኰንን አይገባህም፣ ጠላትህንም እንደራስህ አድርገህ ውደደው የሚል ትዕዛዝ እንደሰጠህ ሁሉ ሀጢአተኞችንም ማወገዝና ወደ ሲዖል መላክና ማሰቃየት ይለብህም» በማለት ፈጣሪያቸውን በመፈታተን ብዙ የምርምር ውጤቶችን አበርክተዋል። በዚህ ጥማቸውም የምርምር ቅኔ የሚል ልዩ የመጠየቂያ ወይም የመመርመሪያ መሳሪያ ይጠቀሙ ነበር። በተጨማሪም ግብርና ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተ ክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተ ክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ ነው ተብሎ የሚገመት የአቋቋም ዘዴ ነው። አለቃ ገብረሃና በአጠቃላይ ፈጥኖ መልስ በመስጠት፣ ቃላትን በመሰነጣጠቅ፣ ሁለት ትርጉም በመስጠት፣ እናም ጠለቅ ያለ ትርጉም ያላቸውና ከተናገሩት በኋላ ቆይቶ ሊረዱት የሚቻል አገላለፆችን የሚጠቀሙ ነበሩ። አለቃ ገብረሃና በብዙ ከታወቁ የኢትዮጵያ ነገስታት ዘመን በቅርበት የኖሩና በኢትዮጵያ ሰማይ የምሁራን ሰማይ ላይም እንደ ንጋት ኮከብ ተደርገው ይታዩ ነበር። በመቅደላ ጦርነት ዓፄ ቴዎድሮስ ከሞቱ በኋላ በደጃዝማች ተክለጊዮርጊስና በደጃዝማች ካሳ ኋላ ላይ ዮሐንስ ፬ኛ በተባሉበት መካከል ዙፋኑን ለመያዝ በተደረገው ጦርነት ደጃዝማች ካሳ ጦርነቱን ካሸነፉ በኋላ አለቃ ገብረሃናን ወደ ትግራይ በማስጠራት ፍትህን በፍትሐ ነገስት መሠረት እንዲያስተዳድሩ ጠየቋቸው። በዚህን ጊዜ አለቃ ገብረሃና ጥቂት መጻሕፍትን በብራና ላይ ጽፈው ነበር። እነዚህ የብራና ጽሑፎችም እስካሁን ድረስ በአክሱም ፅዮን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይገኛል። አለቃ ገብረሃና ትልቅ ዝና ያገኙት በዳግማዊ ምኒልክ ፍ/ቤት ነበር። አለቃ ገብረሃና በጊዜያቸው በነበሩት ምሁራን በጣም ይታወቁ ነበር። ከእቴጌ ጣይቱና ከዳግማዊ ምኒልክ ጋር ተባብረው በመስራታቸውም ዝናቸው ተሰራጨ። መጀመሪያ አለቃ ገብረሃና እንጦጦ በሚገኘው ቤተ መንግሥት ከዚያም በቅዱስ ኡራኤልና በቅዱስ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን እንዲቆዩ ተደረጉ። ነገር ግን ሀገራቸው ያለውንና በጣም የሚወዱትን ናበጋ ጊዮርጊስን በጣም ይናፍቁ ነበር። ሆኖም የሀገሩቱ ዋና ከተማ ወደ አዲስ አበባ በመዛወሩ አዲስ አበባ ለመቆየት አሰቡ። ውሎ አድሮ ግን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ነገር ግን በአክሱም በጎንደር የቆዩትን ያህል በአዲስ አበባም እስከማይረሱ ለረጅም ጊዜ ቆይተው ነበር። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት ኤጀንሲ፣ "ብሔራዊ ቢብሎግራፊ (የደራሲያን አጭር የሕይወት ታሪክ)" ፤ ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. (ነሐሴ ፪ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. የተነበበ) የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች
16079
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8D%E1%8A%AB%E1%88%AC%20%E1%8B%9E%E1%88%AB%E1%88%B3%E1%89%B0%E1%88%AD
ፍካሬ ዞራሳተር
'ፍካሬ ዞራስተር: ወደ ሁሉምና ወደ ማንም' በፍሬድሪች ዊልሄልም ኒሺ የተደረሰ የፍልስፍና ልቦለድ* ነው። መጽሐፉ በ1883 እና 1885 (እ.ኤ.አ) መካከል በ4 ክፍል የተደርሰ ሲሆን በጊዜው ይሰራበት ከነበረው የአስተሳሰብ ዘዴ ለየት ባለ መልኩ የፍልስፍናን እና የግብረገብን ጥናቶች መርምሯል። የመጽሃፉ አትኩሮቶች፡ የዘላለማዊ ምልልስ፣ ኃይልን መፍቀድ (*ፈቃድ እዚህ ላይ ጠንካራ ፍላጎት ማለት ነው)፣ የአዳዲስ ዋጋ ወይም ህግጋት አስፈላጊነት፣ የአምላክ በጊዜው በነበሩ አውሮጳውያን ልብ ውስጥ መሞት፣ የበላይ ሰው (*በኒሺ አስተሳሰብ የሰው ልጅ በጦጣወችና በበላይ ሰው መካከል ያለ ፍጡር ነው) መምጣት ትምቢቶች ነበሩ። ጽሁፉ የመጽሐፍ ቅዱስ አጻጻፍ ስልት ይከተል እንጂ የውስጡ ፍሬ ነገር ግን የክርስትናና አይሁድ ሃይማኖቶችን መሰረታዊ እምነቶች የሚጻረር ነበር። ኒሺ ይህን መጽሐፍ " ከሰወችና ከጊዜ 6000 ጫማ" እርቆ እንደጻፈ ይናገራል፣ ማለቱም የመጽሃፉን ሃሳቦች በተራራ ላይ እያለ እንዳገኛቸው ለማስገንዘብ ነበር። ኒሺ ይህን "ፍካሬ ዞራስተር" ብሎ የሰየመውን መጽሃፍ "ስርዓት አልባ"(ጥራዝ ነጠቅ) ወይም ስርዓት ይለሽ በሆነ ዘዴ ስለጻፈው ለተመራማሪወች እጅግ አስቸጋሪ ሆነ። ይሁንና ተመራማሪወች አንድ አንድ ቋሚ የሆኑ የመጽሃፉን ይዘቶች ማስተዋላቸው አልቀረም፦ የበላይ ሰው፡ ለኒሺ የበላይ ሰው ማለት በራሱ ላይ ሙሉ ቁጥጥር ያለው ግለሰብ፣ እምቅ ኃይሉን ወደ ስራ የተርጎመ ሰው ማለት ነው። አሁን ያለው የሰው ልጅ (በኒሺ አሰተያየት) በእንስሳ እና በዚህ በበላይ ሰው መካከል ያለ ፍጡር ነው። የዘላለም ምልልስ፡ ማናቸውም የተከሰቱ ነገሮች እንደገና ይከሰታሉ፣ አሁን የሚከሰቱ ነገሮች ድሮም ተከስተው ነበር ለወደፊቱም እልፍ አዕላፍ ጊዜ ይከሰታሉ! ይህ አለም ልክ እንደምናየው ሆኖ እንደገና ይከሰታል፣ ሰውም ይሞታል ግን ልክ በነበረበት መልኩ በነበረበት አለም ተመልሶ ይመጣል። ኅይል መፍቀድ፡ የሰው ተፈጥሮ መሰረታዊ ባህርይ ነው። ማናቸውም የምንሰራቸው ነገሮች፣ እንደ ኒሺ አስተያየት፣ የዚህ መሪ ሃሳብ መገለጫ ናቸው። ከመራባት፣ ደስታ፣ ሐሴት ጋር ሲነጻጸር የኅይል መፍቀድ ሁሉም የሰው ልጅ ከከባቢው አለም ጋር የሚያደርገውን ትግል ጠቅልሎ የሚይዝ ጽንሰ ሃሳብ ነው። በክፋትና ደግነት በተሰኙ ተቃራኒ የክርስትና ሃሳቦች ላይ ብዙ ትችት መመስረት። በኒሺ አስተያየት እኒህ ነገሮች የሰው ልጅ ፈጠራወች እንጂ በተፈጥሮ የሚገኙ አይደሉም። በሱ አስተያየት የሰው ልጅ ተግባር መለካት ያለበት አስቀድሞ በተቀመጡ የግብረ ገብ ዋጋወች/ህጎች (ጥሩና መጥፎ) ሳይሆን የተግባሩን መዘዝ በመለካት ነው። መጽሐፉ ባጭሩ በመጽሃፉ መግቢያ ላይ ዞራስተር 30 አመት ሲሞላው ወደ ተራራ እንደወጣና በዚያ ከሰወች ተገሎ ብዙ ጥበቦችን እንደሰበሰብ እናነባለን። 40 አመት ሲሞላው ያከማቸውን ጥበብ ለማካፈል ከተራራው ወረደ። የመውረዱ ዋና አላማ "የበላይ ሰው"ን መምጣት ለመስበክ ነበር። የበላይ ሰው፣ በዞራስተር አስተሳሰብ፣ ከሰው በላይ የሆነ ፍጡር ማለት ነው፡ ልክ የሰው ልጅ ከጦጣወች በላይ የሆነ ፍጡር እንደሆነ። በዞራስተር ግምት ዘመናዊው ሰው የሞራል ግሽበት፣ ባዶነትና አጠቃላይ የህይወት ውዥንብር ስለገጠመው አዲስ ትምህርት ያስፈልገዋል። በዞራስተር አስተሳሰብ የዘመናዊው ሰው መንፈሳዊ ግሽበት ምክንያት የአምላክ መሞት ነው። በርግጥ አምላክ ለመሞት አይቻለውም ሆኖም ግን በዞራስቶር አስተሳሰብ አምላክ ሞተ ማለት ዘመናዊው ሰው በአምላክ ላይ ያለው እምነት መሞት ማለት ነው። ስለሆነም የድሮወቹ ሰወች ብዙ አስደናቂ ስራወችን ለአምላክ ሲሉ ቢሰሩም የዘመናዊው ሰው ግን ይህን እመንቱን በማጣቱ አጠቃላይ ዘመናዊ ህብረተሰብ መሪ ሃሳብ የማጣት፣ የመበስበስና ተስፋ የማጣት ምልክቶች አሳየ። ህግን የሚሰጥ በሰው አምሳያ ያለ አምላክ ለአዲሱ ሳይንሳዊና ዘምናዊ ህብረተሰብ እጅግ ኋላ ቀር መስሎ ታየ። ስለሆነም በተማሩ ዘንድ የአለም የህይወት ትርጉምና የግብረገብ ስርዓት እጅግ ዝብርቅርቅ ያለ ሆነ። ዘመናዊ ሰው ባዶነት "ኒሂልዝም"( የህይወት ትርጉም ማጣት) የሚባል ችግር ተጋረጠው፣ የ"ዞራስተር ፍካሬ" ዋና አላማ ይህን ባዶነት ("ኒሂልዝም" -- የህይወት ትርጉም ማጣት) መታገል ነበር። በኒሺ አስተሳሰብ አዲሱ የ"በላይ ሰው" ትምህርት ለዚህ ዘመናዊ ባዶነት ፍቱን መድሃኒት መሆን ነበር። ዞራስተር ከተራራው ወርዶ በሰወች መካከል እንዲህ ሲል ሰበከ፡ የሰው ልጅ በአሁኑ ሰዓት ያለበትን መናኛነት (ተራነት)ና የከሰረ ስልጣኔ በማሸነፍ የ"በላይ ሰው"ን መፍጠር አለበት፡ «የሰው ልጅ ሊሸነፍ የሚገባ ነው። ለማሸነፍ እያንዳንዳችሁ ምን አድርጋችኋል?» ሆኖም ግን ይህ ሰበካው ተቀባይነት አጣ። ህዝቡም መልሶ «የበላይ ሰውህን ለራስህ» ብለውም ተሳለቁበት። የተመቻቸና ጥሩ ኑሮ ከመፈለግ ውጭ የበላይ ሰውን እንደማይፈልጉ ነገሩት። ህይወት ከፍተኛ ትርጉም ከሌለው በርግጥም ከደስታ ውጭ ምንስ ያስፈልጋል? በዚህ ምክንያት የስልጣኔ ዋና ዓላማ "ከፍተኛ ደስታ ለከፍተኛ ቁጥር ላለው ሰው" ሆነ። በዚህ ምክንያት ዞራስተር ለህዝቡ ያለው ጥላቻና ንቀት አደገ ( ምንም እንኳ ከጊዜ ወደጊዜ ሊያዝንላቸውና ሊረዳቸው ህሊናው ቢግደረደርም)። ተማሪውም ሆነ ያልተማረው፣ ፖለቲከኛውም ሆነ ፈላስፋው፣ ሰዓሊውም ሆነ ፕሮፌሰሩ፣ ሁሉም የተደላደለ ህይወት ከመሻት ውጭ ውስጣቸው ያለውን እምቅ ስብዕና ለማሳደግ የማይጥሩ ሆኖ አገኛቸው። ዞራስተር ብዙ ተከታይ ከማፍራት ይልቅ ሊግባባቸው የሚችሉ ጥቂት ፈርጥ የሆኑ ሰወችን ፍለጋ ጀመረ፡ ተራ(መናኛ) ነገሮችን ከህይወት ለማግኘት የሚሞክሩን ሳይሆን፣ ከፍተኛ ነገርን ለማግኘት የሚሞክሩትን። ፍለጋው ጥቂት ሰወችን ስላስገኘለት በዚህ ወቅት ለተመረጡት "ማስተማር" በጥብቅ ጀመረ። ክፍል ፩ በዚህ የመጽሃፉ ክፍል የዞራስተር ዋና ነጥቦች በስድስት ዋና ዋና ሃሳቦች ይጠቃላል። የመጀመሪያው የዞራስተር ነጥብ አጠቃላይ ሜታፊዝክን መካድ ነው። ሜታፊዚክ ማለት በተጨባጩ አለም ጀርባ የማናየው፣ የማንዳሰሰው፣ የማናሸተው እውነተኛ አለም አለ በማለት ይህን አለም ለማግኘት የሚጥር የፍልስፍና ዘርፍ ነው። በዞራስተር አስተያየት አንድ አለም ብቻ አለ፡ እርሱም ተጨባጩ አለም ነው። ሁለተኛው የዞራስተር ነጥብ የአይምሮና አካል ክፍፍልን መካድ ነበረ። በተለምዶ ሰው አካል አለው ብንልም በዞራስተር አስተያየት ሰው እራሱ አካል ነው። የሰው ልጅ ከማይጨበጥ ምናባዊ ነገር (አዕምሮ) እና ከተጨባጭ ነገር (አካል) የተሰራ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ከአካል የተሰራ ነው። በነደካርት የተነሳው ቀልበኛ ፍልስፍና የስውን ልጅ ከሁለት (አዕምሮና ሰወነት) ከከፈለ ወዲህ የስው ልጅ የስራ ውጤቶች ብዙ አመርቂ አልሆኑ፣ ይልቁኑ የጥንቶቹ ከያኒያን በ"ደማቸው የጻፉዋቸው መጽሃፎች" (በአይምሮ ከተጻፉ ዘመናዊ መጽሃፎች) በተለየ መልኩ ስሜት የሚነኩ እንደነበሩ አስተማረ። የሰው ልጅ "አዕምሮ" ከሆነ ወዲህ ስራው ሁሉ በቀመር የተወጠረና ምንም ስሜት የማይቀስቀስ ሆነ። ዞራስተር ሙሉ በሙሉ የግለሰብ ነጻነትን ይደግፋል። ግብረገብ፣ የጋራ ሰላምና፣ ይሉኝታ ለዞራስተር ደንታው አይደሉም። የህይወት ኃይሎች በምንም አይነት መታፈን የለባቸውም። የተመረጡ ነፍሶች የመንጋወችን ግብረ ገብና ስርዓቶች ወደጎን ትተው የራሳቸውን ዋጋ/ህግ አውጥተው የራሳቸውን አላማ ለማስፈጸም ይታገላሉ። ትክክለኛው የህይወት ጣዕም በህግጋትና ግብረገብ የተጋረደ ሳይሆን ከኃጢያትና ጽድቅ ወዲያ ርቆ የሚገኝ ነው። ሙሉው የግለሰብ ነጻነት "ሁሉ በሁሉ ላይ" ጦር እንዲያነሳ ሊያደርግ ይችላል። ይህ ግን በዞራስተር አይን ምንም አይደለም ምክንያቱም ሁሉም ህይወት ያለው ነገር "ኃይልን ይፈቅዳል"፡ ሁሉም ህይወት ያለው ነገር እራሱን ያረጋግጣል፣ ለመኖሩም ምልክት ትግል ያካሂዳል። ሄራክሊተስ እንደጻፈ "ጦርነት የሁሉ ነገር አባት ነው"፣ በዞራስቱራ አስተያየት ያለፍልሚያ ምንም ጥቅም ያለው ነገር አይመጣም። ዞራስተር ለጓደኞቹ የሚመክረውም "በአደጋ ኑር!" እያለ ነበር። ፍቅረኛሞች እንኳ ሳይቀሩ ችግር ሊገጥም እንዲችል መረዳት አለባቸው፣ በፍቅር መጎዳት የሚፈራ ወይም ቂም የሚያሲይዝ ሳይሆን እራስን ለማሳደግና አዳዲስ ነገሮችን ለመረዳት የሚያገልግል ዕድል ነው። ጦርነት ተቀባይነት ያለው መሳሪያ ብቻ ሳይሆን ተቀባይነት ያለው ግብም ነው። እራስን መወሰን ለዞራስተር ፍልስፍና ዋና ቁልፍ ነው። ይህ አለም ከላይም ሆነ ከታች ከጎንም ሳይቀር የተሰጠው ትርጉምም ሆነ ህግጋት የሉትም። ሁሉም ሰው የራሱን ትርጉምና ህግጋት በመፍጠር እራሱን ይወስናል። ሁሉም ሰው ልክ እንደሙሴ የራሱን ጽላት እንዲቀርጽ እንጂ ለሁሉም የሚሰራ ከላይ የተላለፈ ህግ የለም። ከዚህ አንጻር እራስን መወሰን ባንድ በተስተካከል የአለም ስርዓት ውስጥ ራስን መቻል ሳይሆን ከትርምስ ውስጥ የራስን አለምን እንደመፍጠር ነው። ህይወት ሂደት እንጂ ሁኔታ አይደለም። አንድ የሰው ልጅ በሂደት ላይ ያለ እንጂ፣ ቆሞ ያለ የሆነ ነገር አይደለም። እራስን እንደ አንድ ቋሚ ነገር ማሰብ በዞራስተር ስህተት ነው። በመጠበቅ፣ እውቀትንና ሃብትን ዝም ብሎ በማከማቸት ህይወት አይኖርም፣ ይልቁኑ እራስን በየጊዜው በማሸነፍና እራስን በመቀየር ህይወት ይኖራል። ሶስቱ ሽግግሮች ሌላው የዚህ ክፍል ዋና ሃሳብ ሶስቱ ሽግግሮች ናቸው፡፡የሰው መንፈስ እውነቱንና እራሱን ለማወቅ 3 ከባድ ለውጦች እንደሚያካሂድ ዞራስትራ በዚህ ክፍል ሲያስረዳ፦ " እነሆ ነፍሳችሁ ሶስት ጊዜ ይሻገራል፡ እንኪያስ ግመል ነበራችሁ፣ ግመሉ አምበሳ፣ በመጨረሻ አምበሳው ህጻን ልጅ!" ትርጉሙም የመጀመሪያው የመንፈስ ለውጥ ወደ ግመል ሲሆን ይህም "ትሁት መንፈስ"ን ያመላክታል፡ እራስን መካድ፣ በሃብት መቆጠብን፣ መታዘዝንና ችግርን መቋቋምን። ይህም ግመልን እራሷን ዝቅ አድርጋ የጭነት እንስሳ እንደሚያደርጋት ባህርይ ነው። " መጫን ያለበት መንፈስ እንዲህ ይጠይቃል "ከሁሉ ነገር ከባዱ ምንድን ነው?" መልሶም "በጫንቃየ ላይ ጭነቴን አዝየ በጥንካሬየ ሐሴት ማድረግ አይደለምን? እራሴን በማዋረድ ኩራቴን መግደል አይደለምን? የዋህነቴን በማጋነን ጥበቤን መፎተት አይደለምን?" ከዚህ የግመል አለም ወደ አንበሳነት የሰው መንፈስ ለሁለተኛ ጊዜ ይሻገራል። በዚህ ጊዜ ከጭነት ነጻ ይሆናል፣ ከላይ ወደታች በተዘርጋ የሃይል አሰላለፍ ቁንጮውን ለመያዝ ጥረት ያደርጋል፣ ራስ ገዝ ሆኖ ነጻነቱን በራስ ገዝነትና በሃያልነት ይደነግጋል። በታላቁ ዘንዶ ላይ ጦርነት ይክፈታል፣ የቀድሞውን ግብረገብ ጽንሰ ሃሳብ አውልቆ ይጥላል። "ለራሱ ነጻነትን ለመቀዳጀት፣ በህግጋት ላይ ሳይቀር "እምቢ" ለማለት፣ ወንድሞች፣ ለዚያ ለዚያ አንበሳ ያስፈልጋል። አዳዲስ ህግጋትን የመፍጠር መብት እንዳለ ለማወቅ ለተሸካሚና ለአክባሪ ነፍሳት እጅግ አስቸጋሪ ነው። ይህ ተግባር ለነዚህ እንደ ማደን እና የሚታደን እንስሳ ስራ ነው።" አንበሳ እንግዲህ የነበረውን እምቢ በማለት የሚያፈርስ እንጂ አዲስ የሚፈጥር አይደለም። ስለሆነም የሰው መንፈስ አዳዲስ ህግጋትን ለመፍጠር ለ3ኛ ጊዜ መሻገር ይኖርበታል። በዚህ የመጨረሻው ሽግግር መንፈሱ ከአንበሳ ወደ ህጻን ይቀራል። ህጻኑ አዲስ ጅማሬን፣ ንጹህ የዋህነትን የሚወክልና የድሮወቹን ህግጋት ድል ካደረገ በኋላ አዲስ ዋጋወችን ፈጣሪ ይሆናል። "ሕጻን የዋህነት ነው፣ ያለፈውን መርሳትም ነው፣ አዲስ ጅማሬ፣ ጨዋታ፣ እራሱን የሚያሽከረክር ጎማ፣ የመጀመሪያ እንቅስቃሴ፣ ቅዱስ የሆነ "አወ-ማለት"። አወ! ወንድሞች፣ የፈጠራ ጨዋታ ቅዱስ የሆነ "አወ" ማለትን ይጠይቃል፡ መንፈስ የራሱን ፈቃድ ይፈቅዳል፣ አለሙን ያጣ እንግዲህ የራሱን አለም ያገኛል።" ሁሉ ነገር በህጻን ልጅ ተጀምሮ እንደገና በህጻን ማብቃቱ የኒሺን የዘላለም ምልልስ ጽንሰ ሃሳብ የሚያንጸባርቅ ነው። በዚህ የዘላለም ድግግሞሽ የሰው ልጅ እራሱን በማሽነፍ ከነበሩበት ድክመቶች ሁሉ ነጻ በመውጣት አዲስ አይነት ሰው -- የራሱ ህግ/ዋጋ ያለው የበላይ ሰው ይፈጥራል። እኒህን ነጥቦች ለተመረጡ ተከታዮቹ ካስተማረ በኋላ ዞራስተር ወደተራራ ዋሻው እንደተመለሰ መጽሃፉ ያትታል። የዚህ ምክንያቱ ያለሱ ተጽዕኖ ተከታዮቹ በራሳቸው ውሳኔ የራሳቸውን ሃሳብ እንዲያዳብሩ ነው። አስተማሪነቱን ማቆሙም ይህን የፍልስፍናውን ግብ ላለማጣረስ ነበር። ክፍል ፪ በሁለተኛው ክፍል ዞራስተር ከከተማውና ከገበያው በመሸሽ ወደ ተራራው ስለመመለሱ ያትታል። "ዘሩን እንደዘራ ገበሬ ማደጉንም እንደሚጠባበቅ፣ ዞራስተር ከሰወች በማምለጥ ወደአምባው፣ ወደ የብቸኝነት ዋሻው ተመለሰ" ዞራስተር በዚህ ወቅት ከተራራው ወርዶ ስላጋጠመው ሁኔታ ማንሰላሰል ጀመረ፣ በተለይ "ኃይልን መፈለግ" ("ኃይልን መፍቀድ") የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ ተገነዘበ በሄድኩበት ቦታ ሁሉ ያገኘሁት ህይወት ያለው ነገር ሁሉ ኃይልን ይፈቅዳል፣ የሚታዘዙት እንኳ ሳይቀር ጌታ ለመሆን ይፈቅዳሉ! ደካሞች ለጠንካሮች ለመታዘዝ በሌላ ሳይሆን በራሳቸው ፈቃድ ይስማማሉ፣ ደካሞቹ ደግሞ በተራቸው ከነሱ የበለጠ ደካማ ለሆነው ጌትነት ይፈቅዳሉ፡ ይህ ጨርሰው ሊተውት የማይፈቅዱት ደስታቸው ነው! ታናናሾቹ ከነሱ ያነሱት ላይ ኅይል እንዲኖራቸው ለበላዮቻቸው ፈቀቅ እንደሚሉ ሁሉ ከሁሉ የበላይ የሆነው ለአደጋና ከባድ ፈተና እንዲሁ ፈቀቅ ይላል፣ ለኅይል ሲልም ህይወቱን አደጋ ላይ ይጥላል። የሁሉ ታላቅ ፈቀቅ ማለት ለህይወት አስጊ ለሆነ አደጋና በሞትና በህይወት ቁማር ለመጫወት ነው። ይህ የጽሁፍ ክፍል ዞራስቶራ በ3ኛው የመጽሃፍ ክፍል የሚያጋጥመውን ፈተና በመተንበይ ይከናወናል፡ ይህን በምሳሌ እነግራችዋለሁ። ትላንትና ፣ ጸጥታ በሰፈነበት ሰዓት፣ ድንገት ከእግሬ በታች ምድር ተንሸራታ ጠፋች፡ ህልሜም ጀመረ። የጊዜ እጅ ወደፊት በሚነጉድበት፣ የህይወቴ ሰዓት ትንፋሹን በዋጠበት የሰማሁት ጸጥታ ልቤን በፍርሃት ሞላው። በድንገትም ያለምንም ድምፅ አለኝ "ታውቃለህ ዞራስተር?" ሹክሹክታው ስላስፈራኝ ጮኽኩ፣ ፊቴም ገረጣ፣ ግን ካፌ ድምጽም አልወጣም! ቀጠለም "ዞራስተር ታውቃለህ ግን አትናገርም!" በመጨረሻ በሚገዳደር ቃል ተናገርኩ "አወ! አውቃለሁ ግን መናገር አልፈልግም!" ድምጽ የሌለው ሹክሹክታ ግን ጠየቀ " አትፈልግም? ይሄ እውነት ነው? በመገዳደር ቃል እራስክን አትደብቅ!" በዚህ ወቅት አለቀስኩ፣ እንደህጻንም ልጅ ተንቀጠቀጥኩ፣ መለስኩም፡ "ስለእውነትስ እፈልግ ነበር! ግን እንዴት አድርጌ? እባክህ ተወኝ! ይሄ ከኔ በላይ ነው!" ድምጽ የሌለው ሹክሽክታም መለሰ፣ አለም "አንተ ማን ነህ ዞራስተር? ይልቁን የምትናገረውን ተናገርና ሙት!" ክፍል ፫ በዚህ ክፍል ዞራስተር ሃሳቡን ወደታች የሚጎትተውን ጉልበት በማሸነፍ አዳዲስ ሃሳቦችን ያፈልቃል። ብሎም የዘላለም ምልልስን በግልጽ ይናገራል። "ኦ! ዞራስተር" አሉ እንስሳቶቹ "ሁሉም ነገር ይሄዳል፣ ሁሉም ነገር ተመልሶ ይመጣል፣ ለዘላለም የህልውና ጎማ ይሽከረከራል። ሁሉም ይሞታል፣ ሁሉም እንደገና ያብባል፣ የህይወት ቀለበት በንዲህ መልኩ ለዘላለም ይቀጥላል። ሁሉም ይሰበራል፣ ሁሉም እንደገና ይጋጠማል፣ ላለም እስከ ዘላለም አንድ አይነት የኅልውና ቤት ይገነባል። ሁሉም ይለያያል፣ ሁሉም ከሁሉ ጋር እንደገና ይገናኛል፣ ለዘለዓለም የኅልውና ቀለበት በራሱ ላይ እንዲህ ይሽከረከራል።" ይህን በሰማ ጊዜ ዞራስተር የዘላለም ምልልስን ማስተማር የህይወቱ አላማ መሆኑን ተገነዘበ። ስለዚህም ከነበረበት ተራራ ወረደ። ከዘላለም መመላለስ በተጨማሪ ኒሼ ስለ አዳዲስ ህግጋት/ዋጋወች ማውጣት በዚሁ ክፍል አጥብቆ አስተምሯል። "በተሰባበሩና ግማሽ ድረስ በተጻፈባቸው ጽላቶች ተከብቤ ተቀምጨ እጠባበቃለሁ። መቼ ይሆን ጊዜየ የሚመጣው?" ክፍል ፬ በክፍል 4፣ ዞራስተር ከትልልቅ ሰወች ጋር በመገናኘት እራሱን በኒህ ሰወች ይከባል፣ ምግብንም ከነሱ ጋር ይካፈላል፡፡ እነዚህ ታላላቅ ሰወች፡ የግራና የቀኙ ንጉሶች፣ የአረጀው ምትሃተኛ፣ የሮማው ፓፓ፣ ፈቃደኛው ለማኝና ጥላው፣ ንጹህ አዕምሮ፣ በጣም ፉንጋው ሰው ናቸው። እያንዳንዱ ታላቅ ሰው እንግዲህ በአዕምሮው ትክክል ነው ብሎ የተቀበለው ነገር ትክክል ሳይሆን ተጣሞበት (አምላክ፣ እውነት፣ ልብ) ስላገኘ፣ ሆኖም ግን ከዚህ በመነሳት ውሳኔ ላይ መድረስ አቅቷቸው ተስፋ የቆረጡ ነበሩ። በዚህ ምክንያት ድሮ ይሰሩት የነበረውን ስራ መስራት አቅቷቸው የድሮው ስራቸው ተዋናይ/ገጸ ባህርይ ወደ መሆን የወረዱ ነበሩ። ለነዚህ ሰወች ሃዘን ሊገባው የነበረው ዞራስተር ከሃዘኑ ጋር ትንቅንቅ በመፍጠር ሃዘኑን ማሸነፍ እንዳለበት ያሳያል። "የመጨረሻው ጥፋቴ ምን ይሆን?" ከዚህ በኋላ ዞራስተር ወደ ራሱ አዕምሮ አተኮረ፣ ከትልቅ ድንጋይ ላይ ተቀምጦም አንሰላሰለ። በድንገት ተስተካክሎ ተቀመጠ፣ መለሰም፦ "ለታላላቆቹ ሰወች ከንፈር መምጠጥ! " በዚህ ጊዜ ፊቱ ወደ ንሐስ ተቀየረ ከዚህ በኋላ በዚህ ክፍል ዞራስተር እንደ አዲስ ሰው ተቀየረ፣ "አንበሳውም መጥቷል፣ ልጆቸም ተቃርበዋል፣ ዞራስተርም በስሏል፣ ሰዓቴም ተቃርቧል፦ ጎሄ ቀደደ፣ ቀኔ ጀመረ፣ ተነሳ! ተነሳ! አንት ድንቅ ቀትር!" እንዲህ በመናገር ዞራስተር ዋሻውን ለቆ ወጣ፣ ከድቅድቅ ተራራ መካከል እየተፈናጠቀች እንደምትወጣ የጠዋት ጸሓይ እያብረቀረቀ በጥንካሬ ተራመደ። ከፍካሬ ዞራስተር የተወሰዱ ጥቅሶች ህይወትን የምናፈቅር መኖርን ስለተለማመድን ሳይሆን ማፍቀርን ስለተለማመድን ነው። በፍቅር ውስጥ ሁል ጊዜ ዕብደት አለ። በዕብደት ውስጥ ደግሞ ሁልጊዜ ምክንያት አለ። አንቺ ታላቅ ኮከብ! ፍንትው ብለሽ የምታበሪላቸ ባይኖሩ ደስታሽ ምኑ ላይ ነበር? መብረርን የሚማር ሰው መጀመሪያ መቆምን፣ ከዚያም መራመድን፣ ብሎም መሮጥንና ዛፍ መውጣትን እንዲሁም መደነስን መማር አለበት፣ አንድ ሰው ወደ መብረር መብረር አይችልም! እውነትን መናገር - በጣም ጥቂት ሰወች ይችላሉ! ከነዚህ ከሚችሉት ግን የሚፈፅሙት የሉም`! ደፋር፣ ደንታ የሌለው፣ ተሳዳቢ፣ ጸበኛ-- ጥበብ ከኛ እኒህን ትፈልጋለች፡ ሴት ናትና የምትወደውም ጦረኛን ብቻ ነው። እራሱን የማያዝ መታዘዝ አለበት። ብዙወች እራሳቸውን ማዘዝ ይችላሉ፣ ነገር ግን ለራሳቸው ከመታዘዛቸው በፊት ብዙ ይጎላቸዋል! ማህበረሰብ ተኩላውን አላምዶ ውሻ አደረገ። የሰው ልጅ ከሁሉም በላይ ለማዳ እንስሳ ነው! አንድ ትውፊት አጀማመሩ በሩቅ የዘመን ጭጋግ እየተሸፈነ ከሄደ፣ አመሰራረቱም እየተምታታ ከመጣ - በክብር እያደገ ይሄዳል። ክብሩ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየጨመረ ይሄዳል። በመጨረሻ ትውፊት ቅዱስ ይሆንና በሰወች ዘንድ ድንቅ ይሆናል። ሰው በንዴት አይገልም፣ በሳቅ እንጂ። በቁመና ለማደግ፣ ወደብርሃንም ለመጠጋት በተፈለገ ጊዜ፣ ስርን ወደ መሬት መላክ ያስፈልጋል፣ ወደ ድቅድቅ ጨለማው፣ ወደ ጥልቁ - ወደ መጥፎው። እውነተኛ ወንድ ሁለት ነገር ይፈልጋል፡ አደጋና ጨዋታ። ለዚያ ሲልም ሴትን ይፈልጋል፣ ከሁሉ በላይ አደገኛ የሆነች መጫወቻ። "የታላላቆቹ ተራሮች አመጣት ከየት ይሆን?" ብየ ጠይኩ። ከባህር እንደመጡ ደረስኩበት፣ ማስረጃውም በአለቶቻቸውና በከፍተኛ ገጽታቸው ተጽፎ ይገኛል። ታላላቅ ከፍታወች የሚመጡት ከታላላቅ ጥልቀቶች ነው። ነጻ ከምን? ለዞራስተር ደንታ ይሰጠው ይመስል! ይልቁኑ ብሩህ አይኖችህ እንዲህ ይበሉ፡ ነጻ ምን ለማድረግ? ሳንደንስበት ያለፈን ቀን እንደጠፋ ቀን መቁጥር ይገባል። እንዲሁ በሳቅ ያልታጀበን እውነት ውሸት ማለት ይገባል። መተኛት ቀላል ጥበብ አይደለም፡ ለዚህ ሲባል ቀኑን ሙሉ መንቃት ግድ ይላል። መደብ :ፍልስፍና መደብ :ኒሺ ሥነ ጽሁፍ
52695
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A6%E1%88%9E%20%E1%8B%88%E1%8A%95%E1%8B%9D
ኦሞ ወንዝ
በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኘው የኦሞ ወንዝ (ኦሞ-ቦቴጎ ተብሎም ይጠራል) ከአባይ ተፋሰስ ውጭ ትልቁ የኢትዮጵያ ወንዝ ነው። ወሰኑ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ድንበሮች ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ከኬንያ ጋር በሚያዋስነው የቱርካና ሀይቅ ጋር ይዋሃዳል። እንዲሁም ወንዙ የኢንዶራይክ ፍሳሽ ተፋሰስ ዋና ጅረት እና የቱርካና ተፋሰስ ነው። የወንዙ ተፋሰስ በ 1980 በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ መዝገብ ውስጥ እንዲካተት በማድረግ እንደ ቀደምት የድንጋይ መሳሪያዎች ባሉ በርካታ የቅድመ-ሆሚኒድ ቅሪተ አካላት እና በአርኪኦሎጂ ግኝቶች ታዋቂ ነው። የኦሞ ወንዝ ከጊቤ ወንዝ መጋጠሚያ ሲሆን እስከ አሁን ትልቁ የኦሞ ወንዝ ጅረት እና የዋቤ ወንዝ ትልቁ የግራ ባንክ የኦሞ ወንዝ 8°19′ሰ 37°28′ መጋጠሚያዎች፡ 8 °19′ 37°28′′። ከስፋታቸው፣ ከርዝመታቸው እና ከኮርሶቻቸው አንፃር የኦሞ እና የጊቤ ወንዞች አንድ እና አንድ ወንዝ እንደሆኑ ሆነው ነገር ግን የተለያየ ስም አላቸው። በመሆኑም አጠቃላይ የወንዙ ተፋሰስ አንዳንድ ጊዜ የኦሞ-ጊቤ ወንዝ ተፋሰስ ተብሎ ይጠራል። ይህ ተፋሰስ የምዕራብ ኦሮሚያን ከፊል እና የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መካከለኛ ክፍል ያካትታል። የወንዙ ፍሳሽ በደቡብ አቅጣጫ ሆኖም ወደ ምእራብ ይታጠፋል ከ 7° ሰ 37° 30' ም 36° ም ተጉዞ ወደ ደቡብ ተጠምዞ እስከ 5° 30' ደ ከዚያ ትልቅ ደቡብ አቅጣጫ ተጠምዞ ወደ ደቡብ ወደ ቱርካና ሀይቅ ይቀላቀላል፡፡ የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ባሳተመው ጽሁፍ መሰረት የኦሞ ቦቴጎ ወንዝ 760 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው። የኦሞ-ቦቴጎ ወንዝ ፍሳሽ ከጊቢ እና ዋቢ ወንዞች ሙሉ ፋፋቲ 700 ሚትር ሲሆን የ ጊቢ እና የዋቢ ወሰኖች ከ 1060 ሚ እስከ 360 ሚ በሀይቁ ደረጃ ተጉዘው በጥድፊያ ወደ አቀበት ይወጠል ከዚያም ጉዞው በ ኮኮቢ እና ለሎችም ፋፋቲ እየተሰባብረ ከግርጎሪ ሸለቆ አንዱ ቱርካና ሀይቅ ውስጠ ይዘልቃል፡፡ የስፒክትረም መመሪያ ወደ ኢትዮጵያ ምዕሂት ገለጻ መሰረምት ይህ ቦታ በመስከረም እና በትቅምት ከክረምት ወንዙ ከፍተኛ ሳለ ለነጭ ወንዝ ጅልባ ጉዞ ተወዳጅ እንደሆነ ነው፡፡ ጊቢ ወንዝ በጣም አሰፈላጊ ገባር ሲሆን አነስተኛ ገባሪ ወንዞቹ እነ ዋቢ፣ ደንጩያ፣ ጎጅብ፣ ሙኢ እና ኡሰኖ ወንዞች ናችው፡፡ ለቀድሞዎቹ የጃንጄሮ እና የጋሮ ግዛቶች ምስራቃዊ ወሰን ፈጠረ። ኦሞ በዱር አራዊት የሚታወቁትን የማጎ እና የኦሞ ብሄራዊ ፓርኮችንም አልፏል። ብዙ እንስሳት በወንዙ አቅራቢያ እና በጉማሬዎች ፣ አዞዎች እና ፓፍ አዳሮችን ጨምሮ ይኖራሉ። የአርኪኦሎጂ ግኝቶች መላው የኦሞ ወንዝ ተፋሰስ በጂኦሎጂካል እና በአርኪዮሎጂ ረገድም ጠቃሚ ነው። ከታችኛው ሸለቆ ከ50,000 በላይ ቅሪተ አካላት ተለይተዋል፣ ከእነዚህም መካከል 230 የሆሚኒድ ቅሪተ አካላት ከፕሊዮሴን እና ከፕሊስቶሴን ጋር የተገናኙ ናቸው። የአውስትራሎፒተከስ እና ሆሞ ዝርያ ያላቸው ቅሪተ አካላት በተለያዩ የአርኪኦሎጂ ቦታዎች እንዲሁም ከኳርትዚት የተሰሩ መሳሪያዎች የተገኙ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ጥንታዊው የሆነው ከ2.4 ሚሊዮን ዓመታት በፊት ነው። በተገኙበት ጊዜ መሳሪያዎቹ በ ውስጥ ከሚታየው የበለጠ ጥንታዊ የሚባል የቅድመ-ኦልዶዋን ኢንዱስትሪ አካል ሊሆኑ እንደሚችሉ ይታሰብ ነበር. በኋላ ላይ የተደረገ ጥናት እንደሚያሳየው የመሳሪያዎቹ ድፍድፍ ገጽታ በእውነቱ በጣም ደካማ በሆኑ ጥሬ እቃዎች የተከሰተ ነው, እና ጥቅም ላይ የዋሉት ቴክኒኮች እና ቅርፆች በኦልዶዋን ውስጥ እንዲካተቱ ያስችላቸዋል። በአካባቢው የመጀመሪያዎቹ የአርኪኦሎጂ ግኝቶች በ 1901 በፈረንሳይ ጉዞ ነበር. በጣም ጠቃሚ የሆኑት ግኝቶች በ 1967 እና 1975 መካከል በአለም አቀፍ የአርኪኦሎጂ ቡድን ተደርገዋል. ይህ ቡድን 2.5 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ እንዳለው የሚገመተውን የአንድ አውስትራሎፒቴከስ ሰው መንጋጋ አጥንትን ጨምሮ የተለያዩ ነገሮችን አግኝቷል። አርኪኦሎጂስቶች ከጥንት ዘመን እና እስከ ፕሊዮሴን ዘመን ድረስ የ ቅሪተ አካላትን አግኝተዋል። የኳርትዝ መሳሪያዎች በወንዝ ዳርቻ ላይ ከተገኙት ጥቂት በኋላ የሆሞ ሳፒየንስ ቅሪቶች ተገኝተዋል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቁፋሮው የተካሄደው በፈረንሳይ እና በአሜሪካ ጥምር ቡድን ነው። ከቀደምት የሆሚኒድ ቅሪተ አካላት በተጨማሪ በኦሞ ሸለቆ ውስጥ የተለያዩ አጥቢ እንስሳት እና አሳ ቅሪተ አካላት ተገኝተዋል። የሰው ተጽዕኖ የኦሞ የታችኛው ሸለቆ በአሁኑ ጊዜ በሺህዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት የተለያዩ ባህሎች እና ብሄረሰቦች ወደ ክልሉ ሲሰደዱ እንደ መስቀለኛ መንገድ እንደሆነ ይታመናል።እስከ ዛሬ ድረስ የኦሞ የታችኛው ሸለቆ ህዝብ ሙርሲ፣ ሱሪ ጨምሮ። , ኛንጋቶም, ዲዚ እና ሚኤን, በልዩነታቸው የተጠኑ ናቸው። ጣሊያናዊው አሳሽ ቪቶሪዮ ቦቴጎ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰኔ 29 ቀን 1896 በሁለተኛው የአፍሪካ ጉዞው በዚህ ጉዞው በሞተበት በ17 ማርች 1897 ኦሞ ወንዝ ደረሰ። የኦሞ ወንዝ በክብር ስሙ ኦሞ-ቦቴጎ ተባለ። ኸርበርት ሄንሪ ኦስቲን እና ሰዎቹ በሴፕቴምበር 12 ቀን 1898 ኦሞ ዴልታ ደረሱ እና በራስ ወልዳ ጊዮርጊስ የሚመራው የኢትዮጵያ ጉዞ ከዚህ ቀደም ሚያዝያ 7 በቱርካና ሀይቅ ሰሜናዊ ዳርቻ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ እንደሰቀለ እና እንዲሁም የዘረፈ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ወደ ድህነት እንዲቀነሱ አድርጓል[ጥቅስ ያስፈልጋል]. ሌተናንት አሌክሳንደር ቡላቶቪች እ.ኤ.አ. ነሐሴ 21 ቀን 1899 ሀይቅ ላይ የደረሰውን ሁለተኛውን የኢትዮጵያ ጉዞ መርቶ በተመሳሳይ አጥፊ ነበር። ይህ ሆኖ ግን በፓርቲው ውስጥ ያሉት ፈረንሣውያን በኦሞ ወንዝ ዴልታ ውስጥ የሚገኙትን በርካታ አማካኞች ለመጀመሪያ ጊዜ በትክክል ካርታ ሠርተዋል። ይህ የኦሞ ወንዝ አተረጓጎም እስከ 1930ዎቹ ድረስ የኢጣሊያ ቅኝ ገዥዎች ካርቶግራፊዎች ወንዙን እና ደላላው ላይ አዲስ እና ትክክለኛ አተረጓጎም ሲያደርጉ ቆይቷል። የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ጣቢያዎች በኦሞ ወንዝ ተፋሰስ ውስጥ በርካታ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና ግድቦች አሉ እነዚህም በኦሞ ወንዝ ገባር በሆኑት በግልገል ጊቤ ወንዝ እና ጊቤ ወንዝ ስም የተሰየሙ ናቸው። በተወሰነ መልኩ ግራ የሚያጋባ ስያሜ ቢኖርም በኦሞ ወንዝ ላይ የሚገኙ የሃገር በቀል የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና ግድቦች ናቸው። 1998 (ዓም) ጎርፍ በዚህ የአገሪቱ ክፍል ወቅቱን የጠበቀ ከባድ ዝናብ የተለመደ ቢሆንም፣ ልቅ ግጦሽ እና የደን መጨፍጨፍ ለዚህ አደጋ ተጠያቂ ናቸው። በተጨማሪም ተመልከት አባይ ወንዝ (ናይል) የኢትዮጵያ ወንዞች
2451
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%20%E1%8A%A6%E1%88%AD%E1%89%B6%E1%8B%B6%E1%8A%AD%E1%88%B5%20%E1%89%B0%E1%8B%8B%E1%88%95%E1%8B%B6%20%E1%89%A4%E1%89%B0%20%E1%8A%AD%E1%88%AD%E1%88%B5%E1%89%B2%E1%8B%AB%E1%8A%95
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ኃይማኖት ተከታዮች በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ በዓል ነው። መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። የኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት ታሪክ የሚገኘው በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፫ ቁ ፲፫–፲፯ ውስጥ ነው። ጌታ በአገራችን፣ ጥር ፲ ቀን፣ በከተራ፣ በገጠር ወራጅ ውሃ የሚከተርበት፣ ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደሚከበርበት ቦታ በምዕመናን ታጅበው በዝማሬና በሆታ ይሄዳሉ። እዚያም በተዘጋጀ አቡነ ባስልዮስ ከእስክንድርያ ፓትርያርክ አቡነ ዮሳብ 2ኛ የጵጵስና ማዕረግ ተቀበሉ። ኢትዮጵያም፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እራሷን የቻለች ሆነች። ወደ ፶፭-፷ ሚሊዮን የሚቀርቡ ምእመናን ሲኖሩት ከምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነው። «ተዋሕዶ» ከልሣነ ግእዝ የመነጨ ቃል ሲሆን፣ ትርጒሙም "አንድ ሆኖ" ማለት ነው። ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ በተዋሕዶ ከበረ ማለት ነው። ለዚሁም በዐረብኛ ተመሳሳይ ቃል "ታውሒድ" ሲባል፣ በአንድ አምላክ ብቻ ማመን የሚለውን ፅንሰ ኣሳብ ያመለክታል። በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ቃሉ የሚነካ የክርስቶስ ባሕርይ በ"ሰብዓዊ" እና በ"መለኮታዊ" ተለይቶ ሳይሆን አንድ ብቻ እንደሆነ የሚለው ጽኑ እምነት ነው። በ443 ዓ.ም. (451 እ.ኤ.አ.) በሮማው ንጉሥ መርቅያን ዘመነ መንግሥት ፮፻፶ ኤጲስ ቆጶሳት በተገኙበት የተሰበሰበው የኬልቄዶን ጉባኤ ከሮማው ሊቀ ጳጳሳት ቀዳማዊ ልዮን "ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርያት አሉት" የሚል ጽሑፍ አቅርቦላቸው ነበር። ዳሩ ግን የእስክንድርያው ፓትርያርክ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ "ጌታ ሁለት ባሕርያት አሉት" የሚለው ትምሕርት ስሕተት ነው ብሎ ልዮንን አወገዘው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት በእምነት ተለያዩ። የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ትምሕርት የሚከተሉ ዛሬ የአርሜኒያ፣ የሕንደኬ፣ የግብፅ፣ የሶርያ፤ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት ጌታችን መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ከሁለት አካል አንድ አካል በመንሳት ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ ማለት ነው። የቤተ ክርስቲያን መመስረት በኢትዮጵያ የተጀመረው በወንጌል ሰባኪ ቅዱስ ፊልጶስ መሆኑ ይታወሳል (ሐዋርያት ምዕራፍ ፰)፦ «እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሰለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር...» በዚህ ንባብ ዘንድ ፊልጶስ ጃንደረባውን የትንቢተ ኢሳይያስ ክፍል እንዲገባው አስረድቶት በክርስትና አጠመቀው። ንግሥት ግርማዊት ህንደኬ ፯ኛ ከ፴፬ ዓ.ም. እስከ ፵፬ ዓ.ም. ገደማ በኢትዮጵያ የነገሡ ናቸው። በ፬ኛው ምዕት ዘመን በወንድማማቾቹ በንጉሥ ኤዛና እና በንጉሥ ሳይዛና ዘመን በፍሬምናጦስ አማካይነት ክርስትና የግዛቱ ይፋዊ ሃይማኖት ሆነ። ይህ ፍሬምናጦስ በኢትዮጵያ «አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን» ተብሎ ይታወቃል። በወጣትነት ዕድሜው ከአጎቱ ከፈላስፋው ከመሮፔዎስ እና ከወንድሙ ከሲድራኮስ ጋራ መርከባቸው ስለሰመጠች ከወንድሙ ጋር ከሞት ተርፈው ምጽዋ አጠገብ ተገኙ። ወደ ነገሥታቱም ግቢ አመጧቸውና ቀስ በቀስ ከፍተኛ ተጽእኖ ያለበትን ደረጃን አገኙ። ንጉሥ ኤዛናን ደግሞ ወደ ክርስትና ለውጠው እንዲጠመቁ አደረጉ። ኤዛና ፍሬምናጦስን ለኢትዮጵያ አቡን እንዲሾም ለመጠየቅ ወደ እስክንድርያ ላኳቸውና የእስክንድርያ ጳጳስ አትናቴዎስ ፍሬምናጦስን ሾሞ ላከው። ፍሬምናጦስ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ሲሆን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስ ደግሞ ፻፲፩ኛው መሆናቸው ነው። መካከለኛ ዘመን እስላሞች ወደ ግብጽ ከገቡ በኋላ ከእስክንድርያ ጋር የነበረው ግንኙነት ቀጥሏል። ጸሐፊው አቡ ሳሊኅ በ፲፪ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደ ገለጸው፣ ፓትርያርኩ በየዓመቱ ፪ ደብዳቤዎች ለኢትዮጵያና ለኖቢያ ነገሥታት ይጽፉ ነበር። ይህንን አደራረግ ግን አቡ ሃኪም አስቀረ። ፷፯ኛው ፓትርያርክ ቂርሎስ እንደ ኤጲስ ቆሞስ የላኩት ሰቨሩስ ሲሆኑ የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ሁሉ እንዲያስጠበቁ ታዘዙ። በ፲፬፻፴፩ ዓ.ም. በዓጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን አባ ጊዮርጊስ ከአንድ ፈረንሳዊ ጐብኚ ጋራ ስለ ሃይማኖት ስለተነጋገሩ አንድ ተልዕኮ ወደ ሮማ ተላከ። በ፲፭፻ ዓ.ም. ደግሞ ኢትዮጵያ ከአዳል ጋር ስትታገል ማቴዎስ የተባለ አንድ አርሜናዊ ወደ ፖርቱጋል ተልኮ የፖርቱጋል ንጉሥ እርዳታን ለመነ። ስለዚህ በ፲፭፻፲፪ ዓ.ም. የፖርቱጋል ሚሲዮን በኢትዮጵያ ደረሰ። በሚከተለው ክፍለ ዘመን ከፖርቱጋል ኢየሱሳውያን የተባሉ ሚሲዮኖች ቤተ መንግሥቱን ወደ ሮማ ካቶሊክ ሃይማኖት ለማዞር ብዙ ጣሩ። በመጨረሻ በ፲፮፻፲፯ ዓ.ም. ንጉሥ ሱስንዮስ ወደ ሮማ ካቶሊክ እምነት ተቀየሩ። ዳሩ ግን የሮማ ሃይማኖት በተዋሕዶ ፈንታ ይፋዊ መሆኑን ሕዝቡ በጣም አልወደደምና በ፲፮፻፳፭ ዓ.ም ሱስንዮስ ዘውዳቸውን ለልጃቸው ለፋሲለደስ እንዲሰጡ ተደረጉ። ፋሲለደስ ወዲያው አገሩን ወደ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መለሱ። ከዚህ በላይ በ፲፮፻፳፮ ዓ.ም ፋሲለደስ ኢየሱሳውያን አገሩን ለቅቀው እንዲሄዱ አዘዙ። በ፲፮፻፶፰ ዓ.ም. መፃሕፍታቸውም እንዲቃጠሉ አዘዙ። ልዩ ባሕርይ የሚቀበሉ ቅዱሳን መጻሕፍት ኢትዮጵያ ብሉይ ኪዳንን እና ሐዲስ ኪዳንን በሙሉ (ከነዲዩትሮካኖኒካል መፃሕፍት ጋር) በመቀበል ብቸኛ ሃገር ናት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸው ቅዱሳት መፃሕፍት ቁጥራቸው ፹፩ ሲሆን እነዚህም ፴፭ የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትና ፵፮ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ናቸው። ይህ የቅዱሳት መጻሕፍት ቁጥር በቀኖና በ፫፻፲፰ቱ አበው ሊቃውንት የኒቂያ ገባኤ ተደንግጓል። ልሳነ ቅዳሴና ልሳነ ስብከት ሥነ ሕንፃ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሥነ ሕንፃ የቤተክርስቲያናት ትውፊታዊ የሥነ ሕንጻ ጥበቧ አምስት ዓይነት ነው። እነርሱም ክብ፥ መስቀል ቅርፅ፥ ዋሻ፥ ፍልፍል እና ስቀልማ ናቸው። ክብ ሕንጻ አብያተ ክርስቲያናት በብዛት በገጠሪቷ ኢትዮጵያ የሚገኙ ሲሆን፣ መስቀል ቅርጽ ያላቸው ደግሞ በከተማ አካባቢ ይገኛሉ። ዋሻ አብያተ ክርስቲያናት በብዛት በተራራማ አካባቢዎች ሲገኙ፣ ፍልፍል አብያተክርስቲያናት ደግሞ ከአንድ ቋጥኝ ተፈልፍለው የተዘጋጁ ናቸው። ሰቀልማ የሚባለው እንደ ጎንደሩ ደብረ ብርሃን ሥላሴ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። ትምህርት ሃይማኖት (የሃይማኖት ትምህርት) በሁለት ይከፈላል። ይኸውም፦ 1ኛ) ዶግማ፣ 2ኛ) ቀኖና በሚል ነው። 'ዶግማ' ቃሉ የግሪክ ሲሆን ፍችውም እምነት ማለት ነው። 'ቀኖና' ደግሞ ቃሉ የግሪክ ሲሆን ሥርዓት ማለት ነው። ከእነዚህ ከሁለቱ ዶግማ ወይም እምነት አይጨመርበትም፤ አይቀነስበትም፤ አይሻሻልም፤ ችግርና ፈተናም ቢመጣ እስከ ሞት ድረስ አጥብቀን የምንይዘው ነው። ለምሳሌ ያህል፣ ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረ፤ ቢመረምር እንጂ የማይመረመር ሁሉን ቻይ አምላክ፤ የሚሳነው ነገር የሌለ ፈጣሪ፤ የሰማይና የምድር ባለቤት፣ የሠራዊት ጌታ ሕያው እግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔር (ፈጣሪ) የአካል ሦስትነት አለው። በመለኮት፣ በመፍጠር፣ በሥልጣን፣ በአገዛዝ፣ በፈቃድ እና በመሳሰሉት ግን አንድ ነው። በሦስትነቱ አብ፥ ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ ሲባል፣ በአንድነቱ አንድ መለኮት፥ አንድ እግዚአብሔር ይባላል። በአዳም ምክንያት ከመጣው የዘለዓለም ሞትና ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ የወጣነው ከሦስቱ አካላት በአንደኛው አካል ማለትም በወልድ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህ ዶግማ ወይም እምነት ይባላል። ቀኖና ግን በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ያደጉ ክርስቲያኖች የሚመሩበት ሥርዓት ስለሆነ፣ በሃይማኖት አባቶች ወይም በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት እንደጊዜው ሁኔታ የሚሻሻል በመሆኑ የሚጨመርበት፣ የሚቀነስለት ነው። ለምሳሌ ያህል እኛ ኦርቶዶክሳውያን የምንጠመቀው ሴት በተወለደች በሰማንያ ቀን፣ ወንድ በተወለደ በአርባ ቀን ነው። የተወለዱ ሕፃናት፣ ሴቷ ሰማንያ ወንዱም አርባ ቀን ሳይሞላቸው ቢታመሙና በሽታው አስጊ ቢሆን የግድ የተባለው ቀን ሳይጠበቅ በ10፣ በ20፣ በ30…ቀናቸው መጠመቅ ይችላሉ ቀኖና ነውና። በቤተ ክርስቲያናችን የቀዳስያን ብዛት መነሻው አምስት ነው። ምናልባት ከአምስቱ አንዱ፣ ሁለቱ፣ ሦስቱ ቢታጡና ሌላም ተፈልጎ እስከ መጨረሻ የማይገኝ ከሆነ፣ ከአቅም በላይም የሆነ ችግር ከገጠመ፣ ሁለቱ ወይም አንዱ ብቻ ቀድሰው ማቁረብ ይችላሉ፤ ቀኖና ነውና። በቤተ ክርስቲያናችን ታቦት ሲከብር ቤተ ክርስቲያኑን የሚዞረው ሦስት ጊዜ ነው፥ ችግር ካለ አንድ ጊዜ ብቻ ዑደት ተፈጽሞ ሊገባ ይችላል። ቀኖና ነውና፤ ስለቀኖና (ስለሥርዓት) ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ እንዲህ ሲል ጽፏል። 1. "ነገር ግን ሁሉን በአግባብና በሥርዓት አድርጉ" 1ኛ ቆሮ. 14፥40። 2. "ወንድሞች ሆይ በሠራንላቸው ሥርዓት ሳይሆን በተንኮል ከሚሄዱት ወንድሞችን ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን። እኛን ልትመስሉ እንደሚገባችሁ እኛም በእናንተ መካከል ያለ ሥራ እንዳልኖርን ራሳችሁ ታውቃላችሁ" 2ኛተሰ. 3፥6-7። ቀኖና (ሥርዓት) የሚወሰነው በሃይማኖት አባቶች እንደሆነና ወንጌልን የሚያስተምር ሰው ለሚያስተምራቸው ክርስቲያኖች በሃይማኖት አባቶች የተወሰነ ቀኖና ማስተማርና ትምህርት መሰጠት እንዳለበት መፅሐፍ ቅዱስ እንዲህ ሲል ያስረዳል። "በየከተማውም ሲሄዱ፣ ሐዋርያትና ቀሳውስት በኢየሩሳሌም ያዘዙትን (የወሰኑትን) ሥርዓት አስተማሯቸው። አብያተ ክርስቲያናትም በሃይማኖት ፀኑ፤ ዕለት ዕለትም ቁጥራቸው ይበዛ ነበር" ይላል የሐዋ. 16፥4-5። በዚህ የእግዚአብሔር ቃል መሠረት ቅዱስ ጳውሎስ ደርቤንና ልስጥራን በተባሉ ቦታዎች ለነበሩ ክርስቲያኖች ወንጌልን ከሰበከ በኋላ ሐዋርያት የወሰኑትን ቀኖና (ሥርዓት) እንደሰጣቸው እንረዳለን። ስለዚህ ቀኖና ወይም ሥርዓት ቤተ ክርስቲያንን ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም። በመሆኑም ዶግማንና ቀኖናን ወይም እምነትንና ሥርዓትን ጎን ለጎን ይዞ መጓዝ ሐዋርያትን መከተል እንጂ ወደ ኋላ ተመልሶ አይሁድን መከተል አይደለም። እንግዲህ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የሚቃወሙ ሰዎች ሁሉ፣ የሚቃወሙት በቀኖና (በሥርዓት) የሚመሩትን ክርስቲያኖች ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል የሆነ መፅሐፍ ቅዱስን በመሆኑ እንዳይሳሳቱ አደራ እንላለን። አሁን እንግዲህ የዶግማንና የቀኖናን ልዩነት ከተረዳን በቀጥታ ወደ ታቦቱ ጥያቄ እንሄዳለን። ጥያቄ 1፦ ዛሬ በእኛ ቤተ ክርስቲያን ያለው ታቦት ነው? ወይስ በታቦትና በጽላት መካከል ልዩነት አለ? መልስ፦ ታቦት የጽላት ማደሪያ ነው፤ ዘዳ 40፥20። ጽላት ደግሞ ቅዱስ ቃሉ የተጻፈበት ሰሌዳ ማለት ነው፤ ዘዳ 34፥27-28። ስለዚህ እነዚህ ሁለት ነገሮች ዛሬም በሐዲስ ኪዳን አሉ። ሆኖም ግን አሠራሩ ሙሉ በሙሉ በዘጸ 25፥10-18 ያለውን የሙሴን ሕግ የተከተለ አይደለም። ምክንያቱም፦ 1ኛ፦ ታቦት እንደሙሴ ሕግ የሚዘጋጀው ከግራር እንጨት ሆኖ፣ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፣ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል፣ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ይሁን ይልና፣ በውስጥና በውጭም በጥሩ ወርቅ ለብጠው፣ በዙሪያውም የወርቅ አክሊል አድርግለት ይላል። ደግሞም ታቦቱን የሚሸከሙት ከወርቅ በተሠሩ መሎጊያዎች አራት ሰዎች እንደሆኑ እንረዳለን። በአጠቃላይ የብሉይ ኪዳን የታቦት አሠራር እጅግ ከባድ በመሆኑ በሁሉም ዘንድ አይቻልም ነበር። ምናልባት አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን ፍቅር የነበራቸው ነገሥታትና ዛሬም ፍቅረ ቤተ ክርስቲያን ያላቸው አንዳንድ ምዕመናን ይችሉት እንደሆነ ነው እንጂ ቀላል ኣይደለም። 2ኛ፦ ጽላት እንደሙሴ ሕግ ከሆነ መዘጋጀትና መጠረብ ያለበት ከከበረ ድንጋይ ነው። በአንድ ታቦት ውስጥም መቀመጥ ያለባቸው ሁለት ጽላቶች ናቸው፤ ዘዳ 34፥1። በአጠቃላይ እንደ ብሉይ ኪዳኑ ሕግና ሥርዓት ከባድ ነው። የብሉይ ኪዳኑ ሥርዓትም ለሐዲስ ኪዳኑ ሥርዓት ጥላ ሆኖ አልፏል፤ 2ኛ ቆሮ 3፥7-11፤ ቆላ 2፥17፤ ዕብ 10፥1። እንግዲህ እዚህ ላይ የሐዲስ ኪዳኑ ታቦትና ጽላት የብሉይ ኪዳኑን የታቦት አሠራርና ሥርዓት ጠንቅቆና ተከትሎ የማይሄድ ከሆነ፣ "ይህ የብሉይ ኪዳኑን የታቦትና የጽላት አቀራረጽ ሥርዓት ጠንቅቆ ያልሄደ የሐዲስ ኪዳን ታቦትና ጽላት ከየት መጣ?" የሚል ጥያቄም ሳያስነሳ አይቀርም። አንባብያን ሆይ በቀጥታ ወደ ጥያቄው ከመግባታችን በፊት በዚህ ፅሑፍ ስለዶግማና ቀኖና ማብራሪያ የሰጠነው ይህን ለመሰለው ጥያቄ እንዲጠቅም ነው። አሁን ወደ ሐዲስ ኪዳን ታቦትና ጽላት ስንሄድ ቁም ነገሩ እንደሚከተለው ነው። የሐዲስ ኪዳን የታቦትና የጽላት አቀራረጽም ሆነ አጠቃቀሙ የተወሰነውና የሚወሰነው በቀኖና ነው። ቀኖና ደግሞ እንደ ሁኔታው የሚሻሻል ነው። ሲቻል ይጨመርበታል፣ ሳይቻል ደግሞ ይቀነስለታል። እንግዲህ በቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና ካበረከታቸው ነገሮች አንዱ የሐዲስ ኪዳን የታቦትና የጽላት አቀራረጽንና አጠቃቀምን ነው። ስለዚህ በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ለመቅረጽ የግራር እንጨት ባይገኝ በዘፍ 1፥31 ላይ "እግዚአብሔርም የፈጠረውን (ያደረገውን) ሁሉ እጅግ መልካም እንደሆነ አየ" ስለሚልና፣ እግዚአብሔር የፈጠረውን ስለማይንቅ፣ ከግራር ሌላ ከማይነቅዝ እንጨት መቅረጽ እንችላለን። ቁመቱ፣ ወርዱና ዙሪያውም እንደችሎታችን ይሆናል። በውስጥና በውጭ ስለሚሆነው የወርቅ ክብርም እንደችሎታችን ይወሰናል። ከሌለንም ወርቁ ይቀራል፣ ቀኖና ነውና። ስለጽላቱም እንደዚሁ ነው፥ ከቻልን ከከበረ ድንጋይ፣ ከዕብነ በረድ መቅረጽ እንችላለን፤ ካልቻልን ጽላቱን ከማይነቅዝ እንጨት መቅረጽ እንችላለን። በሌላ በኩልም ከቻልን እንደ ብሉይ ኪዳኑ በአንድ ታቦት ሁለት ጽላት ማስቀመጥ እንችላለን፤ ካልቻን በአንድ ታቦት አንድ ጽላት ብቻ ይሆናል። በተጨማሪም ጽላቱን ማስቀመጫ ታቦት ባይኖረን፣ ጽላቱን ታቦት ብለን በመጥራት በጽላቱ ብቻ መጠቀም እችላለን፥ ቀኖና ነውና። በተጨማሪም በኤር 31፥31፤ 2ኛ ቆሮ 3፥1-3፤ በዕብ 8፥8-13፣ የእኛ አካልና ልቡና የርሱ ታቦትና ጽላት ናቸውና "በሐዲስ ኪዳን ለምን ታቦትና ጽላት አስፈለገ? ለምንስ ይህ ሁሉ ተፈጠረ?" የሚሉ አሉ። የክርስቲያኖች አካልና ልቡና በክርስቶስ ደም ታቦት፤ ጽላት፤ ቤተ መቅደስ መሆኑን እናምናለን። ቢሆንም፣ በሐዲስ ኪዳን ታቦትና ጽላት ያስፈለገበት ምክንያት፣ ስለአምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነትና ክብር ሲባል ነው። ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ክብሩን የገለጠበት፣ ቃሉን ያሰማበት፣ ሙሴን እንደባልንጀራ ያነጋገረበት የክብሩ ዙፋን ሆኖ፣ ታቦቱ በውስጡ ለሚቀመጠው ለጽላቱ ማደሪያ በመሆኑ፣ በሐዲስ ኪዳንም የሥጋውና የደሙ የክብር ዙፋን እንዲሆን ሲሆን ስለእኛ በዚህ ዓለም መከራ የተቀበለውን መድኃኔዓለም ክርስቶስን ለማክበር ሲባል ነው። ጥያቄ 2፦ በዘዳ 31፣18፣ 32፣ 15፣ 134፥1-5፣ 2ኛ ዜና 5፥10 ያሉትን ጥቅሶች በመጥቀስ እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠው ሁለት ጽላቶችን ብቻ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እነዚህን እልፍ አእላፋት ጽላት ከየት አመጣቻቸው? አራብታችሁ ቅረጹ የሚል አለ ወይ? መልስ፦ በዘዳ 32፥19 ስንመለከት እግዚአብሔር ራሱ አዘጋጅቶ ለሙሴ የሰጠውን ሁለቱን ጽላት እሥራኤል ጣዖት ሲያመልኩ ስላገኛቸው ሙሴ ተበሳጭቶ ሰብሯቸዋል። ነገር ግን ቸርነቱ ለዘለዓለም የሆነ እግዚአብሔር አምላክ ለሙሴ የመጀመሪያዎቹን አስመስሎ እንዲሠራ ነገረው፤ ሙሴም አስመስሎ ሠራ። በዘዳ 34፥1-5 መሥራት ብቻ ሳይሆን ኣሥሩን የቃል ኪዳን ቃላትም በጽላቱ ላይ እንዲፅፍ ሙሉ ሥልጣን ከእግዚአብሔር ተሰጠው። ሙሴም ተፈቅዶለታልና አሥሩን ቃላት በጽላቱ ላይ ጻፈ። ዘዳ 34፥27-28 ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ጽላትንም ሆነ ታቦትን እያስመሰሉ ለመሥራት ሙሉ ሥልጣንን አግኝተናል። ይህን በተመለከተ አንዳንድ አባቶች፦ "አዳም እንኳን በደለ አዳም ባይበድል ኖሮ አምላክ ሰው ሆኖ በቀራንዮ ስለእኛ የመሰቀሉን፣ ስለኛ የመሞቱን የፍቅር ምስጢር አናውቀውም ነበር" ይላሉ። "እስራኤልም በጥጃ ምስል ጣዖት አምልከው እንኳን በደሉ፣ እሥራኤል ባይበድሉ፣ ሙሴ በእግዚአብሔር የተዘጋጁት ሁለቱ ጽላት፣ የሰው ልጅም እግዚአብሔር የሠራቸውን የፊተኞቹን አስመስሎ ለመሥራት ስልጣን ባልኖረውም ነበር፥ ቢሠራም ለምን ሠራህ ለሚለው መረጃ ባላቀረበም ነበር" ይላሉ። ያም ሆነ ይህ ጽላትን አስመስለን፣ አባዝተን፣ አራብተን ለመሥራት መሠረታችን፣ ሥልጣኑ ለኛ ለልጆቹ የተላለፈልን ከአባታችን ከሙሴ ነው። "ሙሴ የተሰበሩትን አስመስለህ ሁለት ጽላት ቅረጽ ከሚል በቀር ጽላትን አብዝታችሁ፣ አራብታችሁ ተጠቀሙ የሚል ቀጥተኛ ቃል አምጡ" ለሚለው ግን ነገሩ እንዲህ ነው። በብሉይ ኪዳን የጽላትም ሆነ የቤተ መቅደስ ሥርዓት፣ የመስዋዕቱ፣ የዕጣኑ አገልግሎት፣ በኢየሩሳሌም ብቻ ስለነበረና፣ የሌላውም አገር ሕዝብ የሚከተለው የጣዖትን ሥርዓት እንጂ የሙሴን ሥርዓት ባለመሆኑ፣ ጽላቱ ተባዝቶ፣ ተራብቶ ለሌላው አገር ሕዝብ አልተሰጠም። እግዚአብሔርም ከኢየሩሳሌም ውጭ አልፈቀደም፥ የተቀደሰውን ጣዖታውያኑ አሕዛብ ያረክሱታልና። ስለዚህ ስግደቱም፣ የቤተመቅደስ ሥርዓቱም በኢየሩሰሳሌም ብቻ ነበር፤ ዮሐ 4፥18-24። በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩ አሕዛብም "ሰሎሞን ያሠራው ታላቁ ቤተ መቅደስና ሁለቱ ጽላት አንሰውናል፤ በርቀት የምንገኝ እኛ የመንገድ ድካም በዝቶብናል፥ ስለዚህ በያለንበት ቤተ መቅደስ ሠርተን፣ ጽላቱን አክብረን መገልገል እንፈልጋለን እና ይፈቀድልን" ብለው ጠይቀው፣ ከሁለቱ ጽላት በቀር ሌላ አልተፈቀደም ብሎ መልስ የተሰጠበት ቦታ የለም። ያም ሆነ ይህ በሐዲስ ኪዳንም በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በአብ፤ በወልድ፤ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቀው፤ ሁለተኛ የድኅነት ልደት ተወልደው፣ የእግዚአብሔር ልጆች እንዲሆኑ ሥልጣን ሰጣቸው። ለክርስቲያኖችም ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ድረስ እንደሚበዙና በአዲስ ኪዳን በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንጹሕ የሆነውን ቍርባን ከኢየሩሳሌም ውጭ በየቦታው ለእግዚአብሔር ማቅረብ እንደሚችሉ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል። 1. "ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ይከበራልና፤ በየስፍራው ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፤ ንጹሕንም ቍርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና ይላል ሁሉን የሚችል እግዚአብሔር" ሚል 1፥11። 2. "ቤቴ ለአሕዛብ ሁሉ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፎ የለምን? እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችኋት ብሎ አስተማራቸው" ማር11፥17፤ ኢሳ 56 ፥ 7፤ ኤር 7፥11። ይህ ትንቢት በቀጥታ ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች መሆኑ ግልጥ ነው። ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ቤተ መቅደስም ሆነ የዕጣን፣ የቁርባን አገልግሎት እንኳን ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ድረስ ላሉ አሕዛብ፣ በኢየሩሳሌም ከሚኖሩ የእግዚአብሔር ሕዝብ በቀር ለእስራኤል ጎረቤት አገሮች እንኳ አልተፈቀደምና። ነቢዩ ሚልክያስ ንጹሕ ዕጣን ያለው በማቴ 2፥11 ወንጌል እንደተናገረው፣ ከአሕዛብ ወገን የሆኑ ሰብአ ሰገል፣ በቤተልሔም ዋሻ ለክርስቶስ ካቀረቡት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በዓለም ያለን ክርስቲያኖች በክርስቶስ ስም ለክርስቶስ የምናቀርበው ቅዱስ ዕጣን ነው። ንጹሕ ቍርባን የሚለውንም በማቴ 26፥26 ጌታ ኅብስቱን አንሥቶ "ነገ የሚቆረሰው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ወይኑንም አንሥቶ ነገ ስለብዙዎች ኃጢአት የሚፈስሰው ደሜ ይህ ነው" ብሎ ለሐዋርያት የሰጣቸው የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው። ንጹሕ የተባለው ርሱ በባሕርዩ ንጹሕ ሆኖ የእኛን የኃጢአት እድፍ ስለሚያነጻ ነው። በብሉይ ኪዳን በኢየሩሳሌም ብቻ መሆን የሚገባቸው ቤተ መቅደሱ፤ ዕጣኑ፣ ቁርባኑ፣ በክርስቶስ ደም በአዲስ ሕይወት፣ በአዲስ ተፈጥሮ፤ በአዲስ ሥርዓት፣ ክርስቲያኖች ለሆንን ለዓለም ሕዝብ በየሥፍራው (በያለንበት) እንድንጠቀምባቸው ከተፈቀዱልን፣ በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩት ሁለቱ ጽላት ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ተባዝተው በዓለም ያለን ክርስቲያኖች በያለንበት በየቤተ መቅደሳችን ለሥጋውና ለደሙ የክብር ዙፋንነት ብንገለገልባቸውና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ብናከብርባቸው ምን የሚጎዳ ነገር ተገኘ? የሚያስደነግጠውስ ምኑ ነው? ስህተቱስ የቱ ላይ ነው? እንዲሁም ኣሥርቱ ትእዛዛት የተጻፉባቸው ሁለቱ ጽላት መባዛት፣ መራባት የለባቸውም ከተባለ፣ "በጽላቱ ላይ የተጻፉት ኣሥርቱ ትእዛዛት መባዛት የለባቸውም፣ ከኢየሩሳሌምም መውጣት የለባቸውም" ማለት አይደለምን? ትእዛዛቱም ተከለከሉ ማለት ነውና። በጽላቱ ላይ የተጻፉት ትእዛዛት በእግዚአብሔር ፈቃድ ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ድረስ በሚገኙ ክርስቲያኖች እጅ ገብተዋል። ይህም ያስደስታል እንጂ አያሳዝንም። ይህ ከሆነ ለሥጋውና ለደሙ (ለክርስቶስ) ክብር ሲባል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ ጽላት ምን በደል አስከተሉ? እግዚአብሔር ለቀደሙ አባቶቻችን በታቦቱ አድሮ የሠራላቸውን ድንቅ ሥራ እያስታወስን፣ እግዚአብሔርን ከማመስገን ውጭ? ደግሞም ጌታ ስለ ጸሎት ሲያስተምረን "አባታችን ሆይ!..." በሚለው ጸሎት ውስጥ "ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች፣ እንዲሁም በምድር ትሁን..." በሉ ብሏል። በዚህ መሠረት፣ በዮሐንስ ራዕይ 11፥19 ላይ ታቦቱን በሰማይ አሳይቶናል። ስለዚህ የሙሴ የቃል ኪዳኑ ታቦት በሰማይ እንዲገኝ፣ በሰማይ እንዲሆን፣ በሰማይ እንዲታይ ፈቃዱ ከሆነ፣ በምድርም እንዲሆን ፈቃድህ ይሁን ብለን ብንጠቀምበት ስህተቱ ምንድን ነው? ጥያቄ 3፦ የሰሎሞን ቤተ መቅደስ እስኪሠራ ድረስ፣ በርግጥ ታቦቱ ከቦታ ወደ ቦታ ይዘዋወር ነበር፤ ቤተ መቅደሱ ተሠርቶ ታቦቱ ወደ ቤተ መቅደሱ ከገባ በኋላ ግን ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው ስለመውጣታቸው መጽሐፍ ቅዱስ አይናገርም። ታዲያ ዛሬ ክርስቶስ ደሙን ካፈሰሰ በኋላ፣ በብሉይም ሆነ በሐዲስ ኪዳን መመሪያ ሳይኖር፣ ከየት አምጥታችሁ ነው ታቦትን በየጊዜው በማውጣት የክርስቲያኖች ኅሊና ሁሉ ወደተሰቀለው ክርስቶስ መሆኑ ቀርቶ ወደ ታቦቱ የሆነው? መልስ፦ በብሉይ ኪዳን እንኳን አይወጣም ነበር ማለት አንችልም። ምክንያቱም በችግራቸው ጊዜ ለችግራቸው መፍትሔ ያገኙ ዘንድ ከነበረበት ከድንኳኑም ቢሆን ያወጡት ነበርና ለምሳሌ፦ 1. በሙሴ ምትክ የተመረጠ ኢያሱ ሕዝበ እስራኤልን እየመራ ወደ ምድረ ርስት ሲሄድ፣ ድንገት የዮርዳኖስ ወንዝ ሞልቶ ባገኘው ጊዜ፣ ወንዙን ከፍሎ ሕዛቡን ለማሻገር ከእግዚአብሔር በተነገረው መሠረት፣ ካህናቱ ታቦቱን ከነበረበት ቦታ ተሸክመው ወደ ወንዙ በመሄድ፣ ታቦቱን የተሸከሙት ካህናት እግር ወንዙን ሲረግጥ፣ ወንዙ ተከፍሎ ሕዝቡ ሁሉ በሰላም መሻገራቸውን እናገኛለን፤ ኢያሱ 3፥1-17። 2. እስራኤል ምድረ ርስት በደረሱ ጊዜ፣ ምድረ ርስት (ኢያሪኮ) በጠላት እጅ በጽኑዕ ግንብ ታጥራ አገኟት። በዚህም ጊዜ ይህን የጠላት የግንብ አጥር ለማፍረስና ርስታቸውን በእጃቸው ለማድረግ፣ እግዚአብሔር የገለጠላቸው ጥበብ፣ ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው፣ ሕዝቡም እየተከተሉ ሰባት ጊዜ ግንቡን እንዲዞሩት ነው። የታዘዙትን አደረጉ ግንቡም ፈረሰላቸው፤ ኢያሱ 6፥1-17። 3. እስራኤል ጠላት በበረታባቸው ጊዜ ጠላትን ለማሸነፍ ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው ይወጡ ነበር፤ 1ሳሙ 5፥1-ፍ። ስለዚህ በብሉይ ኪዳን ካህናቱ ታቦቱን ከቦታ ወደ ቦታ ሲንቀሳቀሱ ካልሆነ በቀር ለሚፈልጉት ዓላማ ታቦቱን ካለበት ቦታ ተሸክመው አያወጡትም ነበር ማለት አንችልም። ሰሎሞን ቤተ መቅደሱን ሠርቶ ካስገባው በኋላ ቢሆንም ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው እንዳያወጡ የሚል ሕግም የለም። እግዚአብሔር የሠራው ሥራ፣ በብሉይ ኪዳን የተፈጸመው አገልግሎት ሁሉ ሙሉ በሙሉ በመጽሐፍ ቅዱስ አልተጻፈም። በመጽሐፍ ቅዱስም ያልተጻፈ ብዙ ነገር እንዳለ እናምናለን፣ ከዚህ በመነሳት ነው እኛ በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ተሸክመን የምናወጣው፦ በብሉይ ኪዳን በእግዚአብሔር ቸርነት (ትእዛዝ) ካህናቱ ታቦቱን ተሸክመው እንዲወጡ ተደርጎ ካህናቱም ታቦቱን ተሸክመው በመውጣት በታቦቱ ያደረ ኃይለ እግዚአብሔር ለሕዝበ እስራኤል ያደረገውን ድንቅ ሥራ ለማሰብና እግዚአብሔርን ለማመስገን ነው። ዛሬም ለሥጋና ለደሙ የክብር ዙፋን የሆነውን፣ ቅዱስ ስሙም የተጻፈበትን ቅዱስ ታቦት በምናወጣበት ጊዜ፣ በደሙ የባረከን መድኅነ ዓለም ክርስቶስ አሁንም የሥጋውና የደሙ ዙፋን በሆነው በታቦቱ ረቂቅ ኃይሎች በማስተላለፍ በረከቱን ያበዛልናል ብለን በማመን ነው። የተሰቀለው አምላክ መክበሩና መንገሡ ቀርቶ በየጊዜው ታቦት ወጣ እየተባለ፣ ታቦቱ ብቻ ነገሠ፣ ከበረ፣ ሕዝቡም ወደ አምልኮ ባዕድ ኮበለለ ስለሚለው ግን አንድ ሕዝብ የንጉሡን ዙፋን ሲያከብርና ሲፈራ ንጉሡን ማክበሩና መፍራቱ እንደሆነ መዘንጋት የለበትም። እኛ የምናምነው ቅዱስ ስሙ የተጻፈበትን የክርስቶስ ሥጋና ደም፣ የክብር ዙፋን የሆነውን ታቦት ማክበራችን. በኪሩቤል ዙፋን የሚቀመጥ መድኅነ ዓለም ክርስቶስን ማክበራችን መሆኑን ነው። በታቦቱ ፊት መስገዳችንም በታቦቱ ለተጻፈው ለቅዱስ ስሙ ነው። በታቦት ፊት ለእግዚአብሔር ስም ይሰግዱ የነበሩ ኢያሱና የእስራኤል ሽማግሌዎች በረከት አገኙበት እንጂ አልተጎዱበትምና ነው፤ ኢያ 7፥6፣ ዘዳ 33፥10። በሐዲስ ኪዳንም "ድል ለነሣው ስውር መናን እሰጠዋለሁ፤ የብርሃን መጽሐፍንም እሰጠዋለሁ፤ በዚያ መጽሐፍ ውስጥ ላይ ከተቀበለው በቀር ማንም የሚያውቀው የሌለ አዲስ ስም ተጽፎበታል" ራዕ 2፥17። ለዚህ ስም ደግሞ ጉልበት ሁሉ መንበርከክ እንደሚገባው መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ "ይህም በሰማይና በምድር፣ በቀላያትና ከምድርም በታች ያለ ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰግድ ዘንድ ነው። አንደበትም ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር አብ ክብር፣ ጌታ እንደሆነ ያምን ዘንድ ነው"፤ ፊልጵ 2፥10-11። በዚህ መሠረት ቅዱስ ስሙ በተጻፈበት (ከነጭ ድንጋይ፣ ከእብነ በረድ፣ ከእንጨት በተሠራው) በጽላቱ ፊት ለቅዱስ ስሙ መስገድ ታላቅ የመንፈስ ጥበብ እንጂ ሞኝነት አይደለም። ምናልባት ስለታቦት፣ ስለጽላት ባለማወቅ ባጠቃቀሙ በኩል የሚሳሳቱ አባቶችን፣ እናቶችን፣ ወንድሞችንና እህቶችን በተገቢው መንገድ ማስተማር ተገቢ ነው። ከዚህ በላይ ስለ ታቦት ከቤተ መቅደስ መውጣትና አለመውጣት መፅሐፍ ቅዱሳዊ ከመሆኑም በተጨማሪ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሆኑ መታወቅ አለበት። ብዙዎች በሐዲስ ኪዳን ታቦትን ለመቃወም በኤር 3፥16 የተጻፈውን ጠቅሰው “በዚያ ዘመን፦ የእስራኤል ቅዱስ፣ እግዚአብሔር፣ የቃል ኪዳኑ ታቦት፣ እነኋት እያሉም በአፋቸውም አይጠሯትም፣ ከእንግዲህ ወዲህ አይሿትም” ተብሏልና ታቦት አያስፈልግም በማለት ያስተምራሉ። እንደተባለው ታቦት ብሎ መጥራት ካላስፈለገ፣ በኤርምያስ 31፥34 ደግሞ፦ እያንዳንዱ ሰው ባልንጀራውን፣ እያንዳንዱም ወንድሙን፦ "እግዚአብሔርን ዕወቅ ብሎ አያስተምርም” ተብሎ ስለተጻፈ፣ እንግዲህ ሰው ሁሉ በየዘመኑ እግዚአብሔርን እንዲያውቅ ማስተማር አያስፈልግም ማለት ነዋ! ደግሞም ጌታችን በማቴ 28፥19 “እንግዲህ ሒዱና በአብ፣ በወልድና፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው አሕዛብን ሁሉ አስተምሩ” ብሎ መናገሩ ስህተት መሆኑ ነዋ! በአጠቃላይ እንዲህ ነው ብሎ ከመናገር አስቀድሞ በመጽሐፍ የተጻፈው ነገር ለምንና እንዴት ባለ ሁኔታና ጊዜ መፃፉን ማጥናትና መልእክቱን (ምስጢሩን) መመርመር ይገባል እንላለን። በመጨረሻ ግን በኢትዮጵያ ኦርቶኮክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማርያም፣ የቅዱሳን፣ የሰማዕታት፣ የመላዕክት፣ ወዘተርፈ ታቦት እየተባለ የተሰየመበት ምክንያቱና የዚህ ስያሜ ከየት ነው የመጣው? ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ እርግጥ ነው። እንዲህ ተብሎ መሰየሙ በትንቢተ ኢሳይያስ 56፥46 በተገለጸው መሠረት የእግዚአብሔርን ሰንበቱን ለሚጠብቁ፣ ደስ የሚያሰኘውንም ለሚመርጡ፣ ቃል ኪዳኑንም ለሚይዙ ጃንደረቦች (ስለእግዚአብሔር መንግሥት ራሳቸውን ጃንደረባ ያደረጉ ቅዱሳን) ማቴ 19፥12 በእግዚአብሔር ቤትና በቅጥሩ የዘለዓለም መታሰቢያ እንደሚደረግላቸው የተገለጠ በመሆኑ፣ ይህን አብነት በማድረግ ጌታ ሥጋውና ደሙ የሚከብርበት ሆኖ ለቅዱሳኑም መታሰቢያ ለማድረግ ነው፤ (መዝ 111፥7)። እንዲሁም የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነውና፤ ምሳ 10፥7። በዚህ ምክንያት እንጂ በታቦቱ የሚከብረው መድኃኒተ ዓለም ክርስቶስ መሆኑ ግልጽ ሊሆን ያስፈልጋል። እግዚአብሔር አስተዋይ ልቡና ይስጠን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን። “ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ፣ ወንድም የሴትን ልብስ አይልበስ፣ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነው” ዘዳ. 22፡5። ስለ አለባበሳችን እንወያያለን። ዛሬም እህቶቻችን ላይ እናተኩራለን፥ ምነው እኛ ላይ ብቻ እንደማትሉኝ ተስፋአለኝ። ስለአለባበስ መነጋገር ያስፈለገን እውነተኛ ክርስቲያን በአነጋገሩ፣ በአረማመዱ፣ በአመጋገቡ፣ በአለባበሱ፣ ብቻ በሁሉ ነገሩ የተለየ መሆን ስላለበት ነው። ይኸውም ሁሉን በአግባብና በሥርዓት ስለማድረግ ነው። እህቶቻችን ላይ ማተኮር ያስፈለገው ደግሞ፦ በአብዛኛው በዚህ ረገድ ትችት የሚበዛው በእነርሱ ላይ ስለሆነ ነው። እነሆ ውድድሩ ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረና እየከፋ ነው። ለመልካም ነገር መወዳደር ባልከፋ፣ ነገር ግን በከተማችን በተለይም በዋና ዋና መንገዶች ላይ የምናየው የእህቶቻችን አለባበስ፣ አንዷ ከሌላዋ ልቃና በልጣ ለመታየት የሚደረግ ግብግብ እንደሆነ መገመት አያዳግትም። እናቶች ይህንን ጊዜ አታሳየን ብለው ሲጸልዩ በርግጥ እህቶቻችን በዚህ እንደማይስማሙ እናውቃለን፤ አብዛኞቹም ስለተመቸኝና የምወደው ዓይነት አለባበስ ስለሆነ ነው እንዲህ የምለብሰው ይሉናል። ይሁን እንጂ እውነቱ ሌላ ይመስላል ምክንያቱም፦ ብርድ ልብስ ለብሰን እንኳን በማንቋቋመው የብርድ ወቅት ሰውነትን በቅጡ የማይሸፍን ብጣሽ ጨርቅ ጣል አድርጎ መውጣት እንዴት ያለ ምቾት ነው? እጅግ አስጨናቂ ሙቀት ባለበት ሰዓት ሰውነት ላይ ተጣብቆ ሌላ ጭንቀት የሚፈጥር አለባበስ እንደምን ብሎ ያስደስታል? ዓላማችን ምንም ይሁን ርሱ ላይ የመከራከር ፍላጎት የለንም። ነገር ግን አለባበሳችንን እንደ ክርስቲያን እንፈትሸው ዘንድ ይገባልና መሰልጠን ይሁን ወይስ መሰይጠን? ልንለየው ይገባናል። አብዛኞቹ ሴቶች ይህን ተግባር ስልጣኔ እንጂ ስህተት ነው ብለው አያምኑም። ለእነዚህ ሴቶች ከሃይማኖት ብቻ ሳይሆን ከባሕላችን ጭምር ያፈነገጠውን የምዕራባውያንን አለባበስ መልበስ ዘመናዊነት ነው። ☛ላንቺስ?☚ መጽሐፍ ቅዱስስ ምን ይላል? ማንኛዋም ሴት የሰውነቷን ቅርፅ የሚያሳይ ወይም ክፍትፍት ልብስ ለብሳ በመሄዷ የሁሉንም ወንዶች ስሜት መፈታተኗ ርግጥ ከመሆኑም በላይ፣ በመንፈሳዊ ሕይወት ደካማ የሆኑትን ደግሞ ለኃጢኣት አጋልጦ ይሰጣል። እዚህ ላይ የተሳሳተው በራሱ ደካማነት ነው ብሎ ምክንያት መስጠት አይቻልም። እግዚአብሔር የሚጠይቀው "በማን ተሰናከለ?" የሚለውን ጭምር ነውና። በክርስትና ደግሞ ሰውን ማሰናከል እጅግ የከፋ ኃጢኣት ነው። “ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር” ማቴ 18፥6። አንዳንድ ሴቶች እግዚአብሔር "ምን ሠራሽ?" እንጂ "ምን ለበስሽ?" አይለኝም፣ ይላሉ። እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል፦ “እንግዳ ልብስ የሚለብሱትንም ሁሉ እቀጣለው” ትን ሶፎ 1፥18። እንግዲህ የሴቶቹን እንቀበል? ወይስ የእግዚአብሔርን? ምርጫው ያንቺው ነው እህቴ። መፅሐፍ ግን እንዲህ ይላል፦ “ከስው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል” የሐዋ 5፥29። በሴቶችና በወንዶች መካከል የአለባበስ ልዩነት ሊኖር ይገባል። “ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ፣ ወንድም የሴትን ልብስ አይልበስ፣ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነው” ዘዳ 22፥5። ታዲያ ቀሚስን የወንድ፣ ሱሪን የሴት ማን አደረገው? ይህ የሰነፍና ለስህተታቸው ምክንያትን የሚሹ ሴቶች የሚያነሱት ጥያቄ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ እኛ ኦርቶዶክሳውያን የእግዚአብሔርን ቃል ዓውቀን ልንፈፅመው እንጂ በቃሉ ላይ የምንፍቅና ጥያቄ እናነሳ ዘንድ ተገቢ አይደለም። ግን ደግሞ ተፈጥሯችንን ብቻ በማየት ኅሊናችን ራሱ ቢናገር ሱሪ የሴት ነውን? ቀሚስስ የወንድ ነው እንዴ? “ተፈጥሮ እንኳን አያስተምራችሁምን?" 1ኛ ቆሮ 11፥14። “ዳሩ ግን ማንም ሊከራከር ቢፈቅድ እኛ ወይም የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ያለ ልማድ የለንም” 1ኛ ቆሮ 11፥16። ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ስህተት መሆኑን መናገር እንጂ መከራከር አያስፈልግም፣ ክርስትና በምርጫ ነውና። “በፊትህ እሳትና ውኃን አኑሬአለው፥ ወደ ወደድኸው እጅህን ክተት” ሲራ 15፥15። ከዚህ ላይ ግን ቀሚስ ሲባል ከውስጥ ሱሪ የማይሻለውን ብጣሽ ጨርቅ እንዲሁም ቁመቱ ረዥም ሆኖ ከሰውነት ጋር የሚጣበቀውን ዓይነት አለባበስ ማለት እንዳልሆነ ልብ እንበል። እህቶቻችን ሆይ ማስተዋልን ትላበሱ ዘንድ እንለምናችኋለን። መሰልጠንን እና መሰይጠንንም ትለዩ ዘንድ ይሁን። ሰውነትሽ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነውና፣ ሁሉን በአግባብና በሥርዓት አድርጉለት። ደግሞም ክርስትና ራስ ወዳድነትን አብዝታ ትጠላለች፥ ምንም ነገር ስናደርግ ስለ ሌላው ሰው ልናስብ ያስፈልገናል። እኛስ ሰውን ወደ ዝሙት ሊያመራው ስለሚችል አለባበሳችን እጅግ ተጨነቅን፣ ነገር ግን ቅዱስ ጳውሎስ ወንድማችንን ስለማሰናከል ምን አለ? “መብል ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ ወንድሜን እንዳላሰናክለው ለዘለዓለም ከቶ ሥጋ አልበላም” 1ኛ ቆሮ 8፥13። እንግዲህ ክርስትና እዚህ ድረስ ነው፥ ስለራሳችን ብቻ ሳይሆን ስለ ወንድሞችና እህቶች የምናስብባት። ለእነርሱም መሰናከያ እንዳንሆን እየተጠነቀቅን ሁሉን በአግባብና በሥርዓት የምናደርግባት፤ እምነታችንን በምግባር የምንገልጽባት ናት። “በእውኑ ኢትዮጵያዊ መልኩን፣ ነብር ዝንጉርጉርነቱን ይለውጥ ዘንድ ይችላልን?" ትን ኤር 13፥27። እህቴ ሆይ አንቺም ኤርምያስ እንዳለው ኢትዮጵያዊነትሽን ጠብቂ። የምዕራባውያን በዓል ከሆነው አለባበስም ሆነ የምንዝር ጌጥ ራስሽን አርቀሽ በሚያኮራው ኢትየጵያዊ ባሕላችን ትዋቢ ዘንድ እግዚአብሔር ይርዳሽ። ስለእውነት አሁን ማን ነው ተጠያቂ፣ የጡት ካንሰር ቢይዘን? አረ እንዲያው ለመሆኑ ስንቶቻችን የጡት ካንሰር፣ የዲስክ መንሸራተት፣ የማኅፀን ካንሰር፣ እንዲሁም ሌሎች የበሽታ ጠንቆች የሚመጡብን በዚህ አለባበሳችን እንደሆነ አስበነው እናውቅ ይሆን? ሕገ ኦሪት ለምንድነው ኤዲት የሚደረገው የውጭ መያያዣዎች እና ዋቢ መጻሕፍት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንይፋዊ ድረ-ገፅ (እንግሊዝኛና አማርኛ)የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ''' ከሉሌ መልአኩ፤ ሦስተኛ እትም - ፲፱፻፹፮ ዓ.ም.
13591
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%AD%E1%88%AD%E1%8C%8B%20%E1%8B%B1%E1%89%A3%E1%88%88
ይርጋ ዱባለ
ይርጋ ዱባለ የኢትዮጵያ ታዋቂ ዘፋኝ ሲሆን ብዙ ባህላዊ የሙዚቃ ስራወችን በማቅረብ ይታወቃል። የህይወት ታሪክ ይርጋ ዱባለ የተወለደው ጎንደር ከተማ አርባያ በምትባል መንደር ግንቦት 16 ቀን 1922 ዓ.ም ነው። አባቱ ከሌላ የወልዷቸው በርካታ ልጆች ቢኖሩም ከአንድ አባት የተወለዱ አንድ ወንድና አንዲት ሴት ግን ነበሩ። እንዳጋጣሚ ግን ሁለቱም አሁን በህይወት የሉም። ይርጋ ዱባለ የ10 ዓመት ልጅ እያለ፣ ታናሽ ወንድሙ ባዘዘው ዱባለ ደግሞ የ 7 ዓመት ልጆች ሆነው ማሲንቋቸውን ይዘው ሲጫወቱ “እኒያ ልጆች የታሉ?” እየተባሉ እየተጠየቁ ጠረጴዛ ላይ እያወጧቸው ነበር የሚያዘፍኗቸው። ወደ አዲስ አበባ ተወስዳችሁ ትዘፍናላችሁ ሲባሉ እናታቸው “ልጆቼን ሊቀሙብኝ ነው” በሚል ስጋት አባ ጊዮርጊስ የሚባል ቦታ ወስደው የደበቋቸው። ይርጋ እንደሚለው በወቅቱ ደጃዝማች አርአያ ገ/መድህን ወረዳ አስተዳዳሪ ነበሩና ህጻናቱን ድምጻዊያን በደንብ ጠብቀዋቸዋል። ከይርጋ በድምጽም በመሰንቆ ጨዋታም የሚበልጠው ባዘዘው ግን ወደ ስምንተኛ ዓመት ዕድሜው ሊሻገር ሲል ሞተ። “ጥላ ወጊ ገደለብኝ.. ደጃዝማች አርአያ ገ/መድህን ግን ቱልቱላና ጥሩምባ እያስነፉ በክብር አስቀብረውታል” ይላል ይርጋ ስለወንድሙ ሲናገር። እሱ ከሞተ በኋላ ይርጋ ከአባ ጊዮርጊስ ወደ ጎንደር ተመለሰ። ሶስት ልጆች ወልደው አንድ ብቻ የቀራቸው የይርጋ እናት ልጃቸውን ቶሎ ድረው የልጅ ልጆች ማየትን ቸኮሉ። እናም የስድስት ዓመት ልጅ አጩለት። ወዳጅ ዘመድ ተቃውሞ ነበር። “ይህች ህጻን ምን ልትሆን ነው? ይልቅ አንድ ልጅሽ ነውና ቶሎ ለመውለድ የምትበቃውን ሴት ዳሪው” ብለው መከሩ፣ እናት አልሰሙም። ከነ ሞግዚቷ በበቅሎ ተጭና የመጣቸውን ሙሽራ የልጃቸው ሚስት እንድትሆን በአደራ ተቀበሉ። ጎረምሳው ይርጋም እንዴት ይሆናል ብሎ ማሲንቆውን አንጠልጥሎ የቤተሰቡን ሃብት ንብረት ትቶ ከተማ ገባ – እየዘፈነ ሊኖር። ከከተማ ሲመጣ ለዚያች ህጻን ከረሜላ ይዞ ይመጣል። “አያያ መጣ” ትላለች በእናቱ ቤት በሞግዚት የተቀመጠችው የወደፊት ሚስቱ። እሷ ታላቅ ወንድሟ ነበር የሚመስላት። ደስታ ከረሜላውን እየሰጠ፣ እያሻሸ እያጫወተ እንድትለምደው ያደርግ ነበር። እሷም እያደገች መጣች። በመጨረሻም እሱ ሌላ ሴት ሳያውቅ፣ እሷም ሌላ ወንድ ሳታውቅ ተጋቡ። 46 ዓመታትም በትዳር ኖሩ፣ አስር ልጆችም አፈሩ፣ ከነዚያ ውስጥ አራቱ ግን በህይወት የሉም። ስድስት ልጆችና አምስት የልጅ ልጆች ዛሬም አሉ። ከ1955 በኋላ ይርጋ ዱባለ ባለቤቱን ጎንደር ከተማ አስቀምጦ ወደ አዲስ አበባ መጣ። ሽለላና ቀረርቶ ስለሚችልም የምድር ጦር ሰራዊት ሊቀጠር ነበር ሃሳቡ፡ የሚቀጠርበትን ደሞዝ ሲሰማ ግን ሊተወው ፈለገ – 70 ብር በወር ነበር። እምቢ ሲል 300 ብር እንስጥህ አሉት፣ እሱንም አልፈለገም፣ ሌላው ቀርቶ ሠርግ እዚያው ጎንደር ቢሰራ፣ ሽልማቱ ብቻ ከሶስት መቶ ይበልጥ ነበር፣ ስለዚህ አዲስ አበባን ትቶ ወደ ጎንደር ተመለሰ። ጦር ሰራዊቶች ግን ዝም አላሉትም ጎንደር ሄደው አስረው አመጡት። እየጠፋ ሲመለስ፣ እንደገና እያሰሩ ሲያመጡት .. ቀስ በቀስ ለመደውና አዲስ አበባ ቀረ። በቀዳማዊ ሃይለሥላሴ ጊዜ የነበሩ ሚኒስትሮች ይወዱት እንደነበር የሚናገረው ይርጋ፣ በርካታ ጠመንጃና ሽጉጦች በሽልማት መልክ ይሰጡኝ ነበር ይላል። እሱ ግን አንዲት ሽጉጥ ብቻ አስቀርቶ ሌላውን ለነጋዴዎች እንደሸጠ ይናገራል። ይርጋ በጣም የታወቀበት “የፍየል ወጠጤ” ተብሎ የሚጠራው ሽለላ ነበር። ይህን ሽለላ በ1957 ዓ.ም አስመራ ውስጥ ነበር የተጫወተው። ይርጋ አስመራ የሄደው ለሠርግ ሥራ ነበር – ግን ማምሻውን አንድ ቡና ቤት ገብቶ ሳለ፣ ወቅቱ ጦርነት ጦርነት የሚሸትበት ጊዜ ነበረና ይርጋ ይሸልል ጀመር .. በአዳፍኔ ጠመንጃ፣ ወንዝ የሚያሻገር በኤም ዋን ብረት ሰባብሮ የሚጥል ሲመጣ እንደንፋስ የሚወረውር፣ በተላከው ጠረፍ የማያሳፍር፣ ያባ ጠቅል አሽከር .. ..እያለ ይፎክራል። ያን ጊዜም አንድ ሰው በተደጋጋሚ ይርጋን ይሸለም ጀመር። ከዚህ በኋላ የተፈጠረውን ይርጋ እንዲህ ሲል ያስታውሳል “ሰውየው ደጋግሞ ሸለመኝና ፣ መጨረሻ ላይ እፈልግሃለሁ ብሎ ወደ ውጭ አወጣኝ.. ውጭ አንድ ጂፕ መኪና ቆሟል .. ግባ አለኝ፣ ምን አጠፋሁ ብዬ ደነገጥኩ። ሰውየው ግን ሽለላዬን እንደወደደውና ወደፊትም ሊያሰራኝ እንደሚፈልግ ነግሮኝ፣ ሆቴል ተከራየልኝ፣ በማግስቱም ጂፕ መኪና ተላከልኝና ወታደሮች ይዘውኝ ሄዱ – ወስደውም ያ ማታ የሸለመኝ ሰው ፊት አቆሞኝ፣ ደነገጥኩ፣ በሚሊተሪ ልብስ ተንቆጥቁጦ ቆሟል .. ማን መስላችሁ ..ጄኔራል አማን አንዶም!” እናም በማግስቱ ጃንሆይ ምጽዋ ይመጣሉና እዚያም ትሸልላለህ ተባልኩ፣ እኔም አዲስ ግጥም ጽፌ አደርኩ፣ የምጽዋው ዝግጅትም በሬዲዮ ተላለፈ፣ ያኔ ነው ያ ሽለላ የተቀረጸው። የፍየል ወጠጤ፣ ልቡ ያበጠበት፣ እንዋጋ ብሎ ለነብር ላከበት፣ የማትረባ ፍየል ዘጠኝ ትወልዳለች - እነሱም ያልቃሉ እሷም ትሞታለች” አልኩ። ይርጋ እንደሚለው ይህ ዘፈን ለሱዳን እና ለሶማሌ የተዘፈነ ቢሆንም፣ ደርግ ሥልጣን ሲይዝ ለራሱም ተጠቀመበት። ከዚያ በኋላ ለውጥ መጣ፣ ይርጋም ጎንደር ላይ ሰርቷቸው የነበሩት 13 ቤቶች ተወረሱበት። እሱም ጠቅልሎ አዲስ አበባ ገባ። በኋላም በልጅነቱ ከአባቱ የሰማውን ግጥም፦ “የአሳማ ገበሬ የዝንጀሮ ጎልጓይ የጅብ ዘር አቀባይ … ሁሉም እንብላው ባይ የለውም ገላጋይ” የሚለውን ፉከራ ማሰማት ሲጀምር ግን ነገር መጣበት። ያን ጊዜም እስራኤል ኤምባሲ ገብቶ ቪዛ በመጠየቅ ወደ እስራኤል ሄደና መኖር ጀመረ። እስራኤል በገባ በስምንት ወሩ ያለፈው መንግስት ሥርዓት በማብቃቱ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ። ከዚያ ወዲያ አሜሪካም አውሮፓም እያለ “የሰው የለው ሞኝ”ን በመጫወት ቤተስቡን ያስተዳደር ገባ። ይርጋን ለየት የሚያደርገው የምሽት ክበብ ሰርቶ አለማወቁ ነው። ሰርግ ወይም ግብዣ ወይም ትልቅ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ እየሰራ ነው ልጆቹን ያሳደገውና ንብረት ያፈራው። የዛሬ ስምንት ዓመት ታዲያ ይርጋ ዱባለ በነርቭ በሽታ ተይዞ አልጋ ላይ ዋለ። የበሽታውን ምክንያት ሲናገር “22 ማዞሪያ አካባቢ ዮሃንስ ክትፎ ቤት አጠገብ ቤት ለመግዛት የከፈልኩትን 200ሺ ብር የተቀበለኝ ሰው ስለካደኝ በብስጭት በሽተኛ ሆንኩ” ነው ያለው። ከጊዜ ብዛት ግን በተለይ ፕሮፌሰር ጉታ በሚባሉ ሃኪም ድጋፍ እየተሻለው መጥቶ ነበር። ውስኪና ጮማ ትቶ አትክልት ብቻም እየተመገበ ህይወቱ እስካለፈበት ቀን ድረስ ቆይቷል። የጎንደር ልማት ማህበርም ለአገልግሎቱ ትልቅ ዝግጅት አድርጎ ስለሸለመው ሁልጊዜ ምስጋናውን እንዳቀረበ ነበር። ሰው ምንም ቢኖር ከሞት አይቀርምና በተወለደ በ 81 ዓመቱ፣ ግንቦት 8 ቀን 2003 (ሜይ 16/2011) 82 ዓመት ሊሞላው አንድ ሳምንት ሲቀር ከዚህ ዓለም አልፏል። የቀብሩ ሥነ ስር ዓትም በማግስቱ ግንቦት 9 ቀን አዲስ አበባ ከተማ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል። ስለባህል ሙዚቃ ተጫዋች ይርጋ ዱባለ ባለቤቱ ወ/ሮ እናት ምስክር በህይወት እያለ እንዲህ ሲሉ ምስክርነት ሰጥተው ነበር “የጋሼ ይርጋን ባልነት ተዉት፣ ገነት ነው። መድሃኒዓለምን ፣ ብር ሰርቶ አምጥቶ ኪሱ እንኳን አይከትም፣ ሁሉንም እንቺ ነው የሚለኝ፣ እኔንም እንኳ ንፉግ አደረገኝ፣ እንዲህ ሰርቶ አምጥቶ እየሰጠኝ እንዴት ነው የማባክነው እያልኩ አስባለሁ፣ የሚታገዝ ቢሆን በሽታውን ባገዝኩት፣ ይርጋን የመሰለ ባህል አይገኝም፣ አይማታ፣ አይቆጣ፣ አይነዛነዝ፣ አያሳርዘነ፣ አያስርበነ፣ .. እኔንም እንደ ሚሽት፣ እንደ እህት እንደ እናት ነው አንቀባሮ የያዘኝ፣ ምቾተኛ ነኝ፣ ማጣትን አላውቀውም” የስራ ዝርዝር የኢትዮጵያ ዘፋኞች
2068
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%A3%E1%8B%AD
አባይ
ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ() ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል። ግዮን ( ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣የጩኸቱን ግርማ፣ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል።” አባይ ወንዝ ኒል ይባላል(ምናልባት ናይል የሚለውን ከዚህ ወስደው ይሆናል) በግዕዝ ሰማያዊ አይነት፣ወይንም ኑግ ቀለም ኒል ይባላል። ተሰማ ኃብተ ሚካኤል ግፀው፣ ከሣቴ ብርሀን በተባለ በ1947 ዓ.ም. በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት በታተመ መዝገበ ቃላታቸው በገፅ 685 ላይ “ ኒል () ሰማያዊ ቀለምን መስሎ ከጎጃም ምድር መንጭቶ፣ ጎጃምን አካቦ ወርዶ ሱዳንንም አቋርጦ አራት ሺህ ማይል ዐልፎ፣ ከሜዲትራኒያን ባሕር የሚቀላቀል ኒል፣ ዐባይ” ሲሉ ፅፈዋል። ምንም እንኳን ነጮቹ ናይል የሚለው ስም ከሚለው ከግሪክ ቃል መጣ ቢሉም፣ ኒል፣ ከሚለው ጋር ይስማማልና ዐባይ፣ ግዮን፣ ኒል፣ እኛ ያወጣንለት ስም መሆኑን እንመሰክራለን። የዓባይ() ሸለቆ የትውልድ ሐረግ ይህ ነው። ፣ ን ወለደ፣ ፣ ን ወለደ፤ ም የአባይን እናት፣ ታላቁን የአባይ ገደላማ ሸለቆን ን ወለደ። ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው። ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል።የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር። ከ1.8 ሚሊዮን ዓመት በፊት የነበረ ሲሆን ከሰሜን ተራሮች ዝቃጮችን እየጠራረገ ታላቁን ገደል ለአባይ ያሰናዳበት ወቅት ነው። የአባይ አያት ሲሆን ከ400 000 ዓመታት በፊት ነበረ። ፣ የዛሬ 12 500 ዓመት ገደማ ን ተከትሎ የመጣ የአባይ እናት እንደማለት ነው። ከዚህም በኋላ የበረዶ ዘመን ሲጠናቀቅ ለ 6000 ዓመታት የቆየ የዝናብ ዘመን ተከስቶ ነበር።በዚህ ዘመን የነበረው ዶፍ ዝናብ፣ በኢትዮጵያ ከፍታማ ስፍራዎች ቁልቁል መሬቱን እየሸረሸረ አፈሩን እያጠበ፣ኮረቱን እየጠራረገ፣ ቋጥኞችን እየቦረቦረ፣በዘመናት ብዛት የአባይን ወንዝ ከታላቁ የአባይ ሸለቆ ጋር የሚያገናኝ ሸለቆን ፈጠረ። የአባይ ውኃስ ከየት መጣ? ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀት መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል። ከግሸ ተራራ ስር፣ ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ, በግሸ ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል። አባይ () ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል ቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም። የአባይ መነሾን ፍለጋ በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም። በ17ኛው ክፍለ ዘመን ፖርቱጋል ክርስትናን ለመታደግ ሚሲዮናውያንንና ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ ፓድሬ ፔሬዝ የተባለ ሚሲዮናዊ፣ ጢስ እሳትንና የላይኛውን አባይን ለማየቱ ምስክርነቱን ሰጠ። በ18ኛው ክፍለ ዘመን ጄምስ ብሩስ የተባለ የስኮትላንድ ተወላጅ ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባይ መነሾ ጣና ሐይቅ ነው በማለት አወጀ።እስከዚያ ጊዜ ድረስ ማንም የውጭ ዜጋ አባይ () ከጣና እንደሚነሳ አያውቅም ነበር። ሳሙኤል ቤከር ሪቻርድ በርተን ጆን ሀኒንግ ስፔክ የአባይን መነሻ ፈልገው ወደ ታንጋኒካ ሐይቅ አመሩ እንጂ አንዳቸውም ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም። በ1937 ቡክሀርት ባልደክኼር፣የተባለ የጀርመን ተወላጅ፣ የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለአለም አበሰረ።ታሪካችን በነ ባልድክኬርና በብሩስ ሲፃፍ ስታሮቹ እነሱ ናቸው።የታሪካችን ሞተር የሚንቀሳቀሰው በነሱ ነው። ቢሆንም በ1937 ጀርመናዊው ቡርክኸርት ወደ ኢትዮጵያ ሳይመጣ ኢትዮጵያዊው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መፅሐፈ ሰዋሰው ወግስ፡ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው በ1929 ባሳተሙት መፅሐፍ በገፅ 313 313“ ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው፣ ነጭ ኒል፣ ጥቁር ኒል የሚመስሉ፤ በኦሪትም ግዮንና ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቁር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማቾች ወንዞች ከየምንጮቻቸው በኅይል ተነስተው፣ ግርማቸውን ለብሰው፣ተሰልፈው፣በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደመርከብ ሠንጥቀው አልፈው ሠራዊታቸውን ከፊትና ከኋላ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ካርቱም ላይ ሲገናኙ ሁለትነታቸው ይቀርና፣ አንድ ወንዝ ብቻ ይሆናሉ፤ ከካርቱም ደግሞ እስካትባራ ወርደው ከተከዜ ጋር ይገጥማሉ።ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውኃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብፅን ከላይ እስከታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው፣ አልፈው ተርፈው ወደ ሰሜን ጎርፈው ሜዲተራኒ ከሚባለው ከታላቁ ባሕር ይገባሉ።” በማለት መፃፋቸውን ሳንጠቅስ አናልፍም። በ1995 ዓ.ም ግሼ ሜዳ ላይ ከብቶች የሚጠብቅ 11 ዓመት ያልሞላው የውልሰው የተባለ እረኛ አገኘሁና “የአባይ ምንጭ የት ነው ብዬ ስጠይቀው” መሬት ቸክሎ የተደገፈውን በትር ከመሬቱ ላይ ነቅሎ ወደ ግልገል አባይ እያሳየኝ ከዚህ ነዋ አለኝ። አባባሉ ስንት ፈረንጆች የአባይን ምንጭ አገኘን ብለው የቦረቁበት ግኝት አይመስልም። “ እንዴት አወቅክ?” ስለው “ከብቶቼን የማጠጣ ከዚሁም አይደል? የከተማ ሰው አላዋቂ ነውሳ!” ብሎ ሸረደደኝ። በሆዴ ፈረንጆቹ የአባይን ምንጭ ከአንተ በፊት አገኘን እንደሚሉ ባወቅክ ስል፣ ውስጤን ያነበበ ይመስል፣ “ለፈረንጅ ሁሉ የአባይን ምንጭ እጃቸውን ጎትተን የምናሳይ እኛም አይዶለን እንዴ?” ብሎ አስደመመኝ። ግልገል አባይ ጣና ገብቶ መውጣቱን ያጠኑት ፈረንጆች ካልነገሩት ይህ እረኛ በምን ያውቃል ብዬ በጥያቄ ላፋጥጠው፤ ግልገል አባይ ጣና ገብቶ አባይን ሆኖ መውጣቱን ማን ነገረህ? ስለው “ጣና” “ጣና ነገረኝ” ሲለኝ ያው የተለመደውን የጎጃምን ዘፈን “ነገረኝ ጣና ነገረኝ፡አባይ” የሚለውን ዘፈን ሊዘፍን መስሎኝ ነበር። ያ የጎጃም እረኛ “ ማስረጃህ ምንድነው?” ስለው በክረምት አባይ ሲደፈርስ ግልገል አባይ የደፈረሰ ውኃ ይዞ ጣና ይገባና ከጣና ተንሳፎ ሲወጣ ጥርት አርጎ ይታያል።” ብሎ እረኛው ጂኦሎጂስት አስገረመኝ። እዚህጋ ባለቅኔው ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን “ … የጎጃም እረኛ የት ሄዶ ነው እነሱ(ፈረንጆቹ) የአባይን ምንጭ የሚያገኙት?…” ማለቱን አንረሳም። የኛ ቀን ሲመጣ ልጆቻችን ታሪካቸውን ሲፅፉ፣ ጀምስ ብሩስን ወስዶ አባይጋ ያደረሰውን እረኛ ስሙን ይነግሩናል። እነሉሲ ፣ ፣ ፣ ን ምን ብለው ይጠሯቸው እንደነበረ የሚነግረኝ ኢትዮጲያዊው ታሪክ ፀሐፊ ሲመጣ እኔም የታሪክ ሀ ሁን እቆጥራለሁ። እስከዚያው በነአላን ሙር ሄድ ቋንቋ ፣ ን ወለደ፣ ፣ ን ወለደ፤ …. እያልን ወንድማችንን በፈረንጂኛ እንጠራለን። አባይ ወንዝ (ናይል) ጥቁር አባይ ነጭ አባይ
53509
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8B%88%E1%88%8B%E1%88%BD%E1%88%9B%20%E1%88%B5%E1%88%AD%E1%8B%88%20%E1%88%98%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%B5%E1%89%B5
የወላሽማ ስርወ መንግስት
የወላሽማ ስርወ መንግስት አርጎባ የዋላሽማ ስርወ መንግስት በኢፋት (በአሁኑ ምስራቅ ሸዋ ) የተመሰረተ የአፍሪካ ቀንድ የመካከለኛው ዘመን የሙስሊም ስርወ መንግስት ነበር። በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተመሰረተው የዛሬይቱ ሶማሊያ፣ ጅቡቲ እና ምስራቃዊ የኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ የኢፋት እና አዳል ሱልጣኔቶችን አስተዳድሯል። የዘር ሐረግ የኢፋት እና የአደል የዋሽማ መሳፍንት የአረብ የዘር ሐረግ ወጎች እንዳላቸው ይናገራሉ። በዘር ሀረግ የዋሽማ ወጎች ከባኑ መክዙም ጎሳ በኤል መቅሪሲ የተወሰደ ነው። ግን የኢፋት ሱልጣኔት የዘር ሐረግ የከሊፋው አሊ እና የጃፋር ኢብኑ አቢ ጧሊብ ወንድም ከሆነው አቂል ብን አቢ ጣሊብ ነው። የኋለኛው በሀርላ ክልል ውስጥ ከሰፈሩት ቀደምት ሙስሊሞች መካከል አንዱ ነበር። ነገር ግን የዋላስማ ከፊል አፈ ታሪክ እንደሚያረጋግጠው ዑመር ኢብኑ-ዱንያ-ሃውዝ እንደ ቅድመ አያት ኸሊፋ የዓልይ ልጅ አል-ሐሰን ነበር። ይህ በሁለቱም መቅሪዚ አይደገፍም።እና የዋሽማ ዜና መዋዕል። ነገር ግን ሁለቱም የስርወ መንግስት መስራች እንደነበሩ የሚናገሩት ዑመር ኢብኑ-ዱንያ-ሃውዝ የቁረይሽ ወይም የበኑ ሃሺም ተወላጆች ነበሩ። የአስራ አራተኛው ክፍለ ዘመን አረብ የታሪክ ምሁር ኢብን ካልዱን የዋላስማ ቅድመ አያቶች በአንድ ወቅት የዳሞት መንግስት ገባር እንደነበሩ ይጠቅሳሉ። ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የታሪክ ተመራማሪዎች የዋላሽማ ሥርወ መንግሥት የአካባቢው ተወላጆች እንደሆኑ አድርገው ይመለከቱታል። ኤንሪኮ ችሩሊ እና ጄ.ስፔንሰር ትሪሚንግሃም እንደ አርጎባዎች ጎሳ አድርገው ይቆጥሯቸዋል። ዋላስማ በታሪክ ከአርጎባ የዶባ ህዝብ ቅድመ አያቶች ጋር የተሳሰረ ነው። የሀረሪ ህዝብም ከዋልስማ ጋር ተቆራኝተናል ይላሉ። ባህሩ ዘውዴ፣ ሪቻርድ ፓንክረስት ፣ ዲጂብሪል ኒያን እና ሌሎችም የዋላስማ ሱልጣኖች የኢፋት እና የአደል አብላጫ የአርጎባ እና ሀረሪ እንደሆኑ አድርገው ይመለከቱታል። ኤንሪኮ ችሩሊ ከኡመር ኢብኑ ዱንያሁዝ ቅድመ አያቶች አንዱ የ10ኛው ክፍለ ዘመን የሶማሊያዊ " አው " ባርካድሌ ከአረብ ነው። ጄ.ስፔንሰር ትሪሚንግሃም ይህ የማይመስል ነገር እንደሆነ ይቆጥረዋል፣ ምክንያቱም በአካባቢው ወግ መሰረት ከ500 ዓመታት በላይ የኖረ እና በ16ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ስለሞተ የሚል ምክኒያት አስቀምጧል። የኢፋት የዋላስማ ስርወ መንግስት ከአዳል መሪዎች ጋር ተከታታይ የጋብቻ ጥምረት እንደጀመረ በአረብ ፋቂህ “የአቢሲኒያ ወረራ” ዜና መዋዕል እንደገለጸው በመጨረሻው የኢፋት ሰአድ አድ-ዲን የዋላስማ ገዥ የተወለዱ የሃርላ ጌቶች በአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ-አዳል ጦርነት ተሳትፈዋል። በአዳል የመጨረሻው የታወቀው የዋልስማ አባል በአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን የሐረር ሰው ባራካት ኢብን ኡመር ዲን ነው። የሐርላ ካቢርቶ እንዲሁም ከዋላስማ ሥርወ መንግሥት የመነጨው ዶባ በ1769 በሙዳይቶ ሥርወ መንግሥት ተገለበጡ። የአፋር በአውሳ (በአሁኑ አፋር ክልል ) የከቢርቶ ሼክ ከቢር ሀምዛ ዘር በብራና ጽሑፎች ታሪካቸውን ጠብቀዋል። ዋላስማ የሚለው የማዕረግ ስም አሁንም በኢፋት ግዛት እስከ አስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ድረስ የዚያ ክልል ገዥዎች ከአሮጌው ስርወ መንግስት ተወላጆች ነን በሚሉ ሰዎች ይገለገሉበት ነበር። በ1993ዓ.ም መሐመድ ሳሌህ ቅድመ አያቶቻቸው እንደሆኑ የተናገረዉ የኢፋት አርጎባ ዋላስማ ቅድመ አያቶቹ ለዘመናት የሸዋ-ሀረር መንገድ ነጋዴዎች እንደነበሩ ገለፀ። የታሪክ ተመራማሪዎች እንደሚናገሩት የአደል ህዝብ እንዲሁም ገዥዎቹ ኢማሞች እና ሱልጣኖች የሚናገሩት ቋንቋ የወቅቱን የሀረሪ ቋንቋ ይመስላል። የ19ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያዊት የታሪክ ምሁር አስማ ጊዮርጊስ ራሳቸው ዋላሽማ አረብኛ ይናገሩ እንደነበር ይጠቁማሉ። የኢፋት ሱልጣኔት ዋና መጣጥፍ፡ የኢፋትየወላሽማ ስርወ መንግስት በ13ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ሰሜናዊ ሀረርጌ በማክዙሚ ስርወ መንግስት ስር የተሰየመ የሙስሊም ሱልጣኔት መቀመጫ ነበረች። ሱልጣኔቱ በውስጥ ሽኩቻ እየተበጣጠሰ እና ከአጎራባች ሙስሊም መንግስታት ጋር በተደረገው ትግል መዳከሙን የወቅቱ ምንጭ ይገልፃል። በ1278 ከነዚህ አጎራባች ግዛቶች አንዱ በምስራቅ ሸዋ ኢፋት የሚባል በዋላሽማ መሪነት የሸዋ ሱልጣኔትን ወረረ። ከጥቂት አመታት ትግል በኋላ ሱልጣኔቱ ወደ ኢፋት ተጠቃሏል ። ይህ ቁርኝት ብዙውን ጊዜ በዑመር (ረዐ) ነው የሚነገረው ነገር ግን ሸዋ በተቀላቀለበት ጊዜ 50 ዓመታትን አስቆጥሯል። ምናልባትም የልጅ ልጁ ጀማል አድ-ዲን ወይም ምናልባትም የልጅ የልጅ ልጁ አቡድ ሊሆን ይችላል። በ1288 ሱልጣን ዋሊ አስማ ሁባትን በተሳካ ሁኔታ ድል አደረገ። አዳል እና ሌሎች በክልሉ ውስጥ ያሉ ሙስሊም መንግስታት። ኢፋትን በአፍሪካ ቀንድ ውስጥ ካሉት የሙስሊም መንግስታት ሁሉ የላቀ ኃያል መንግሥት ማድረግ። በ1332 የኢፋት ሱልጣን ቀዳማዊ ሃቅ አድ-ዲን በአቢሲኒያ አፄ አምዳ ስዮን ወታደሮች ላይ በወታደራዊ ዘመቻ ተገደለ ። አምዳ ስዮን በመቀጠል ጀማል አድ-ዲንን አዲሱን ንጉስ አድርጎ ሾመ፣ በመቀጠልም የጀማል አድ-ዲን ወንድም ናስር አድ-ዲን ሾመ ። ይህ ውድቀት ቢሆንም የኢፋት ሙስሊም ገዥዎች ዘመቻቸውን ቀጥለዋል። አቢሲኒያው ንጉሠ ነገሥት በአካባቢው ያሉትን ሙስሊሞች “የጌታ ጠላቶች” ብሎ ፈርጀው ነበር፣ አሁንም በ15ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ኢፋትን ወረረ። ከብዙ ተጋድሎ በኋላ የኢፋት ጦር ተሸንፎ የሱልጣኔቱ ገዥ የነበረው ንጉስ ሰአድ አድ-ዲን 2ኛ ወደ ዘይላ ሸሸ። እዚያም በአቢሲኒያ ጦር ተከትለው ገደሉት።
35205
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%99%E1%88%B4
ሙሴ
ሙሴ (ዕብራይስጥ፡ /ሞሼህ/) በብሉይ ኪዳን ከሚጠቀሱት ታላላቅ ነብያት አንዱ ነው። ሙሴ በተወለደበት ዘመን የእስራኤል ልጆች በግብጽ ውስጥ በባርነት ተገዝተው የነበርበት ሆኖም ግን ቁጥራቸው እየበዛና እየተጠናከሩ የነበርበት ጊዜ ነበር። በዚህ ዘመን ግብፅን ያስተዳድር የነበር፣ ስሙ በብሉይ ኪዳን ያልተጠቀሰው የግብፅ ፈርዖን፣ የእስራኤል ልጆች ከውጭ የግብፅ ጠላቶች አግዘው ሊወጉን ይችሉ ይሆናል በሚል ፍራቻ ማናቸው የእስራኤል ወገን የሆኑ ወንድ ልጆች በተወለዱ ጊዜ እንዲገደሉ አዘዘ። ሆኖም የሙሴ እናት፣ ዮካብድ፣ ልጇን ደብቃ ታኖር ነበር። ከሶስት ወር ድበቃ በኋላ ልጁን በደንገል ሳጥን አድርጋ በአባይ (ናይል) ወንዝ አጠገብ አስቀመጠችው። ሳጥኑ እየተንሳፈፈ የፈርዖን ልጅ እምትታጠብበት ስፍራ ደረሰ፣ የፈርዖንም ልጅ ለህጻኑ ስላዘነች በፈርዖን ቤት አደገ። ከስደቱ እስከ እረፍቱ ባጭሩ ካደገ በኋላ አንድ የግብፅ ባሪያ አሳዳሪ እስራኤላዊ አሽከሩን ሲደበድብ አይቶ ሙሴ ግብጻዊውን ገደለው። ሆኖም ይህ ጉዳይ በግብጽ ባለስልጣኖች ዘንድ እየተሰማ ስለሄደ ሙሴ ወደ ምድያም አገር ተሰደደ። በዚያ ለ40 አመት ያክል ሲቀመጥ የካህኑን ዮቶርን በጎች ይጠብቅ ነበር። በዚህ ጊዜ የድሮው ፈርዖን ሞቶ አዲስ ፈርዖን በግብፅ ነግሶ ነበር። በአዲሱ ፈርዖን ዘመን የእስራኤላዊያኑ ጭቆና ባሰ እንጅ አልቀነሰም። ከኮሬብ ተራራ በሚገኝ ቁጥቋጦ ውስጥ በተገለጠለት መልዕክት መሰረት ሙሴ እድሜው 80 ከሞላ በኋላ ወደ ግብፅ ተመለሰ ። የመመለሱም ዋና ዓላማ እስራኤላውያኑ ግብፅን ለቀው እንዲወጡ አዲሱን ፈርዖን ለማስፈቀድ ነበር። አዲሱ ፈርዖን እምቢ ስላለ ሙሴ 10 መቅሰፍቶችን በግብፅ ላይ ከፈፀመ በኋላ ንጉሱ ስለተስማማ እስራኤላውያንን እየመራ ፣ ቀይ ባሕርን በእግዚአብሔር ኃይል ከፍሎ በደረቅ ምድር ላይ አሳልፏቸው ከተገዙበት ግብፅ አውጥቶ በሲናይ (ሲና) በረሃ ብዙ ታአምራትን እያደረገ ፣ ውሀ ከዲንጋይ እያፈለቀ ፣ ከፀሐይ በደመና እየጋረደ ፣ በሌሊት ብርሃን እያደረገ ፣ መና ከሰማይ እያወረደ ሌላም ብዙ ተአምር የሠራ መርቷቸዋል ። በዚህ ወቅት እስራኤላውያኑ በኮሬብ ተራራ ተመስርተው የኤዶምን ደንበሮች ያስሱ ነበር ። አሥርቱ ትዕዛዛትን ሙሴ የተቀበለው በዚህ ወቅት ነበር። በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ሙሴና ህዝቡ ለ40 ዓመት በበረሃው ውስጥ ከዋተቱ በኋላ ሙሴም ወደ ተስፋይቱ ምድር ወደ ከነዓን ሳይገባ እሱን እንዲተካው እያሱን መርጦ በዚሁ በስደት ወራት እድሜው 120 ሲሆን አልፏል። የኖረበት ዘመን አጭር መረጃ በታሪክ አጥኝዎች ዘንድ፣ ሙሴ መቼ እንደኖረ በዕርግጥ አይታወቅም። አንድ አንድ ተመራማሪዎች የኖረበትን ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በ13ኛው ክፍለዘመን ሲያደርጉ ሌሎች ከዛ በፊት ነው ይላሉ። ይህም ግመት በዚያው ክፍለ ዘመን መጨረሻ የገዛው ፈርዖን መርነፕታህ በጽላቱ የእስራኤል ስም መጀመርያው ስለ ጠቀሰው ነው፤ እንዲሁም የአባቱም ስም ራምሴ በኦሪት ዘጸአት ፩፡፲፩ የከተማ ስም ሆኖ ስለ ታየ ነው። ንጉሥ ዳዊት ግን በእስራኤል በ1000 ዓክልበ. ያህል ስለ ገዛ፣ ጸአቱ በመርነፕታህ ዘመን ሆነ ማለቱ ለእብራውያን ዘመነ መሳፍንት አይበቃም። በፈርዖኑ ፪ ራምሴ ሥር የተገነባው ፒ-ራምሴስ በጥንቱ አቫሪስ ሥፍራ ስለ ሆነ፣ የከተማው ኋለኛው ስም በተቀበለው ጽሑፍ እንደ ተገኘ መስሏል። ሌላው የተሰየመው ከተማ ፊቶም (ፒጦት በኩፋሌ) በግብጽኛ ፐር-አቱም ተብሎ ከአቫሪስ ዘመን መኖሩ ታውቋል። በመጽሐፈ ኩፋሌ ዘንድ የእግዚአብሔር መላእክት ለሙሴ በደብረ ሲና ላይ ያቀረቡት ቃል ነው። ይህ የሆነበት ዓመተ ዓለም አዳምና ሕይዋን ከኤዶም ገነት ከወጡ 2,410 ዓመታት በኋላ እንደ ነበር በኢዮቤልዩና በሱባዔ አቆጣጠር ያመለክታል። ዕብራውያንን ከግብጽ ባርነት ወደ ደብረ ሲና የመሩዋቸውም በ2410 ዓ.ዓ. እንደ ሆነ ይነግረናል። የመጽሐፈ ኩፋሌ ዜና መዋዕል አከፋፈል በጠቅላላ ከሥነ ቅርሳዊ መዝገቦች ጋር ሊነጻጽር ይችላል። በዚህ አከፋፈል 2410 ዓ.ዓ. ማለት ከክርስቶስ ልደት በፊት (እንደ ኢትዮጵያዊ አቆጣጠር) 1661 ዓመታት አካባቢ እንደ ነበር ሊገመት ይቻላል። 2149 ዓ.ዓ. (1922 ዓክልበ. ግ.) - የያዕቆብ ልጅ ዮሴፍ ወደ ግብጽ ባርነት ተሸጠ። 2164 ዓ.ዓ. (1907 ዓክልበ. ግ. - ዮሴፍ የፈርዖን ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ። 2171 ዓ.ዓ. (1900 ዓክልበ. ግ.) - የ፯ አመት ታላቅ ረሃብ በመካከለኛው ምሥራቅ ጀመረ 2172 ዓ.ዓ. (1899 ዓክልበ. ግ.) - የተረፉት የእስራኤል ልጆች ከከነዓን ወደ ጌሤም አገር (በአባይ ወንዛፍ) ፈለሱ። 2242 ዓ.ዓ. (1829 ዓክልበ. ግ.) - ዮሴፍ በግብጽ ዓረፈ። 2263 ዓ.ዓ. (1808 ዓክልበ. ግ.) - ዕብራውያን የወንድሞቹን ሬሳዎች ወደ ከነዓን አድርሰው ብዙዎችም ወደ ግብጽ ተመልሰው ጥቂቶቹ ግን ከነሙሴ አባት ዕብራን (ወይም እንበረም እንደ ኦሪት ዘጸአት) በኬብሮን ቀሩ። የከነዓን ንጉሥ መምከሮን ከግብጽ ፈርዖን ጋር ስለ ተዋጋ የግብጽ በር ተዘጋ። 2303 ዓ.ዓ. (1768 ዓክልበ. ግ.) - የሙሴ አባት ዕብራን ከከነዓን ወደ ጌሤም ተመለሰ። 2330 ዓ.ዓ. (1741 ዓክልበ. ግ.) - የዕብራውያን መከራ ዘመን በጨካኝ ፈርዖን ተጀመረ። ሙሴ በጌሤም ተወለደ። 2372 ዓ.ዓ. (1699 ዓክልበ. ግ.) - ሙሴ ከግብጽ ወደ ምድያም ሸሸ። 2410 ዓ.ዓ. (1661 ዓክልበ. ግ.) - ሙሴ ከምድያም ወደ ግብጽ ይመልሳል፣ ፲ የግብጽ መቅሰፍቶች፣ ዕብራውያን ወደ ሲና በረሃ አመለጡ፣ ሕገ ሙሴን በደብረ ሲና ይቀበላሉ። በዚህ አከፋፈል፣ እስራኤል ከነዓንን የወረረበት ወቅት ከ፵ ዓመት በኋላ (2450 ዓ.ዓ. ወይም 1621 ዓክልበ.) ጀመረ፣ ሙሴም ከዮርዳኖስ ወንዝ ምሥራቅ አንዳንድ አሞራዊ አገር አሸንፎ ወንዙን ሳይሻገር ግን በዚያው ዓመት እንዳረፈ በኦሪት ይዘገባል። በ1661 ዓክልበ. የግብጽ ሃይል እጅግ ተደከመ፣ ከመርነፈሬ አይ በኋላ የተከተሉት ፈርዖኖች ከዋና ከተማቸው ከጤቤስ ውጭ ሥልጣን አልነበራቸውም። በዚያም ጊዜ ሂክሶስ የተባለው የአሞራውያን ብሔር ጌሤምን ወረሩ፣ ከግብጻውያንም ጋራ ይዋጉ ጀመር። እነዚህ ሂክሶስ (ወይም «15ኛው ሥርወ መንግሥት») በመጨረሻ በ1548 ዓክልበ. ከግብጽ ተባረሩ፣ የታሪክ ጸሐፊዎች ግን ብዙ ጊዜ ይህን ድርጊት ከጸአቱ ጋራ ይደናገሩ ነበር። ሆኖም በጌሤም የገዛው «14ኛው ሥርወ መንግሥት» (1821-1742 ዓክልበ. ግ.) የተባሉት ነጋዴዎችና እረኞች ለሥነ ቅርስ ታውቀዋል። ደግሞ ይዩ የዕብራውያን ታሪክ ሙሳ (አ.ሰ) - ሙሴ በእስልምና የብሉይ ኪዳን ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ