id
stringlengths
4
5
url
stringlengths
39
537
title
stringlengths
2
65
text
stringlengths
2.04k
162k
45363
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%86%E1%88%9D%E1%8C%AC%20%E1%8A%A3%E1%88%9D%E1%89%A5%E1%8B%8D
ቆምጬ ኣምብው
ቆምጬ አምባው በደርግ ጊዜ የቢቡኝ ወረዳ አስተዳዳሪ የነበሩ ሰው ናቸው ። የቆምጬ አምባው- ቃለ-ምልልስ (በአበባየሁ ገበያው)24 የሶሻሊዝምን ርዕዮተ ዓለም በ1960ዎቹ ማብቂያ ላይ በአገራችን ያስተዋወቁት የደርግ ባለስልጣናት ሶሻሊዝምን የተረዱት የ70 ዓመቱ አዛውንት የጐጃሙ ቆምጬ አምባው በተረዱት መንገድ ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያ ታሪክ አሁን ከምናየው ፍፁም የተለየ ይሆን ነበር፡፡ ለእሳቸው ሶሻሊዝም ማለት ሠርቶ ማሰራት ነበር፤ ሶሻሊዝም ሜዳ ተራራውን አረንጓዴ ማልበስ ነበር፤ ለእሳቸው ሶሻሊዝም ብዙ ት/ቤት፣ ክሊኒክ፣ ወፍጮ ቤት፣ መገንባት ሌባን ማጥፋት ነው፡፡ በደርግ ዘመን ለ13 ዓመት የተለያዩ ወረዳዎችን ያስተዳደሩት ቆምጬ፤ በሠሯቸው በርካታ የልማት ሥራዎችና ብልሃት በታከለበት የአመራር ችሎቻቸው ከመንግስትም ከህዝብም ተወዳጅነት እንዳገኙ ይናገራሉ፡፡ እሳቸው ያልተናገሯቸው ብዙ ነገሮች እየተፈጠሩ በስማቸው እንደሚነገሩ አዛውንቱ ቢናገሩም እራሳቸው በትክክል የፈፀሟቸውም ቢሆኑ ከፈጠራዎቹ የሚተናነሱ አይደሉም፡፡ በሃላፊነት በሚመሩት ወህኒ ቤት የነበሩትን በጣታቸው እየፈረሙ ደሞዝ የሚበሉ ያሏቸውን ፖሊሶች በ60 ቀን ማንበብና መፃፍ እንዲማሩ የፈጠሩት ብልሃት ተጠቃሽ ነው፡፡ ኰሎኔል መንግስቱ ሃ/ማርያም በሥራቸው ተደስተው ሽጉጣቸውን ሲሸልሟቸው አልተቀበሉም - ከሽፍታ ያስፈታሁት 18 ሽጉጥ አለኝ በማለት፡፡ በምትኩ ግን ለህዝቡ መብራትና ውሃ እንዲገባለት ጠይቀዋል፡፡ በትውልድ አገራቸው በጐጃም ያገኘቻቸው የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው ሰፊ ቃለ-ምልልስ ያደረገችላቸው ሲሆን አንባቢያን የእኒህ መለኛ አብዮተኛ ታሪክ ከነለዛቸው ይደርሳቸው ዘንድ ቃለምልልሱን እንደወረደ አቅርበነዋል - ከአነጋገር ዘዬአቸው ጋር፡፡ የት ተወለዱ? መቼ? የተወለድኩት በጠላት ወረራ ዘመን ነው፡፡ በጐዛምን ወረዳ ማያ አንገታም ቀበሌ ገበሬ ማህበር፣ አባላይ በተባለ ቦታ ሜዳ ላይ ተወለድኩ፡፡ እናቴም አባቴም አርበኛ ናቸው፡፡ ስወለድ ማን እንበለው እያሉ ሲመካከሩ ሳለ አንድ አውሮፕላን ትመጣና ክምር ስታቃጥል፣ አባቴ አነጣጥሮ ቢተኩስ ተንከታክታ ወረደች፡፡ ያን ጊዜ ቆምጬአምባው እንበለው፤ ይኼ ልጅ ገዳም ነው ተብሎ ነው ስም የወጣልኝ፡፡ ለትምህርት እንደደረስኩ እዚያው ቀበሌ አንገታም ጊዮርጊስ የቄስ ትምህርት ተምሬ፣ ዳዊት ፆመድጓ ጨርሼ ወደ ቅኔ ቤት ገባሁ፡፡ በሽታ እንደገባ አባቴ ከቅኔ ቤት አውጥተው ወሰዱኝ፡፡ በ15 ዓመቴ የሰባት ደብር የጐበዝ አለቃ ሆንኩኝ፡፡ ቆምጬ ማለት ምን ማለት ነው? ደፋር፣ ጠንካራ፣ ቆራጥ ማለት ነው፡፡ በሸዋ ግን ትርጉሙ ሌላ መሰለኝ. . . አዎ፡፡ በእኔ በኩል ግን ቆምጬ ማለት ታይቶ የሚታለፈውን የሚያውቅ፣ ታይቶ የማይታለፈው ላይ ቆራጥ እርምጃ የሚወስድና ሩህሩህ፣ የዋህ ማለት ነው፡፡ ወጣትነትዎ እንዴት አለፈ? በወጣትነቴ የቤተሰብ ተጽዕኖ ነበረብኝ. . . ሰው ፊት ጠላ መጠጣት አይፈቀድልኝም፤ ውሃ እንኳን ጭልጥ አድርጎ መጠጣት እንከለከላለን፡፡ ስንበላ አፋችሁን ገጥማችሁ አፋችሁን አታጩሁ፤ እየተባልን ነው ያደግነው፡፡ አባቴ ቅዳሴ አስቀድሼ ወጥቼ መሃራ አያስቀምጡኝም ነበር፡፡ ..መሃራ መብላት ያለበት አቅም ያጣ፣ ቤቱ የሚበላው የሌለው ነው፡፡ አንተ ሁሉ ነገር ቤትህ ሞልቶ የተረፈህ ስለሆንክ ምንም እንዳትቀምስ.. እባላለሁ፡፡ ሰርግ ስንሔድ የአባቴን መሣሪያ ይዤ ከበስተጀርባው ነበር የምቀመጠው፡፡ እህል በወሰክንባ(ሞሶብ) ነበር የሚመጣልኝ፡፡ ጨዋታ አምሮኝ ከጉብላሊቱ(ህጻናት) ጋር መደባለቅ አይፈቀድልኝም፡፡ ከፍተኛ ተጽዕኖ ነበረብኝ፡፡ በፆም ቀን ከስምንት ሰዓት በፊት ስንበላ ከተገኘን እንደበደባለን፡፡ የገና ጨዋታ፤ ፈረስ ግልቢያ፣ ዋና፣ አውሬ አደን ምን ልበልሽ ያልተሳተፍኩበት የለም ...ከሁሉም ግን ደስ የሚለኝ አደን ነበር፡፡ ምን አድነዋል? ድኩላው፣ አሳማው፣ ሚዳቋው. . . በለሴ ሆኖ ወደ እኔ ይመጣል፡፡ በቃ ሆ እያልን አገሬ ይዤ እገባለሁ፡፡ ከሰው የተጣላሁ እንደሆን አባቴ አይለቀኝም ነበር፡፡ የደብር አለቃ ሳለሁ ሰው ሲጣላ ባውቀውም ባላውቀውም አስታርቅ ነበር፡፡ በዚያውም የስብሰባን ጥቅምና የአንዳንድ ነገሮችን ሁኔታ ማየት ጀመርኩ፡፡ ስለትዳርና ቤተሰብ ይንገሩኝ. . . አስር ልጆች አሉኝ፡፡ ባለቤቴ አሁን ያለችት የልጆቼ እናት ናት፡፡ ለሷ የእኔ እና የእሷን ስምንት ስምንት የቀንድ ከብት አማተን ደርሰን ሃብታም ሆነን፤ ኋላ ገንዲ በሽታ መጣና ከብቱን ሲፈጀው ተበሳጨሁና ወደ ጐጃም ጠቅላይ ግዛት መጣሁ፡፡ የምክትል ፀሃፊነት ፈተና ተፈተንኩና አለፍኩ - ጃናቢት በተባለች ስፍራ፡፡ ደሞዙ ጥሩ ነበር? 25 ብር ነው፡፡ ማለፌን ከሰማሁ በኋላ አንድ አህያ ተልባ፣ አንድ አህያ ኑግ ጭኜ ወደ ደብረማርቆስ ገበያ ወጣሁና ቦጋለ በረዳ የሚባል ቦታ ሸጥኩት፡፡ ከዚያ ምክትል ፀሃፊነት አለፍኩ አልኩና ሁለት አዝማሪ ጥሩ ብዬ፣ ሹመቴን እያነሳሳ ሲዘፈን ሲጠጣ ሲበላ ታደረ፡፡ ጥቂት ብር ቀረችኝ፡፡ ማለዳ የሹመት ደብዳቤውን ልቀበል አውራጃ አስተዳደሩ ጋ ስሄድ የወረዳው ገዢ ቀኝ አዝማች ረታ ፈረደ ይባላሉ ..አንተ ነህ ምክትል ፀሃፊ የተሾምከው?.. አሉኝ፡፡ አለባበሴም ደህና ነው ያን ጊዜ፤ ንቁ ነኝ፡፡ ..አዎ.. አልኳቸው፡፡ ..አንተማ የዋናው የከበርቴ ልጅ አይደለህ፤ ሰባት ጉልት እያሳረሳችሁ፤ አንተን አንቀጥርም! በል ውጣ ከቢሮዬ.. አሉኝ፡፡ ተበሳጨሁ ገንዘቤን ጨርሻለሁ፤ ሌላ አማራጭ ሳፈላልግ በደብረማርቆስ ወህኒ /ቤት ለወታደርነት ቅጥር የተለጠፈ ማስታወቂያ አየሁ፡፡ ወዲያው እለቱን ተመዝግቤ አለፍኩ፡፡ ሲያዩኝ በቁመትም በክብደትም እኩል መጣሁ፡፡ ወደ ማሰልጠኛ ላኩኝ፡፡ ከማረሚያ ቤት አስተዳደር ወታደሮች አስራ ሰባት፣ ከፖሊስ ሰባት ነበር የተመለመለው፡፡ እዚያ ተደባልቀን ስንማር በፀባይ፣ በተኩስ፣ ህግ በማወቅ አንደኛ ወጣሁ፡፡የዚያን ጊዜው አገረገዥ ደጅአዝማች ፀሃይ እንቁ ኃይለስላሴ፣ የምስክር ወረቀት ሲሰጡ ..በወታደራዊ አቋም፣ በፀባይና በተኩስ ወታደር ቆምጬአምባው ይልማ አንደኛ.. ብለው ሸለሙኝ፡፡ ኮሎኔል አሰፋ ወንድማገኘሁ ከሚባሉ ከወህኒ ቤቱ አዛዥ ጋር ጠሩኝና ..ከአስራ ሰባቱ ወታደር አንተ በጣም ጠንካራ ነህ፤ ወደፊትም እናሳድግሃለን.. አሉና ሃምሳ ብር በግሌ ሰጡኝ፡፡ የወህኒ ቤቱ /ቤት የእስረኞች የህግ አማካሪና የጠቅላይ ግዛቱ ወህኒ ቤት ጠበቃና ነገረ ፈጅ አደረጉኝ፡፡ ኮልት ሽጉጥም ሸለሙኝ፡፡ ከእስረኞች ጋር ስለነበርዎ ግንኙነት ያጫውቱኝ፡፡ እስረኛው አንዳንድ ጊዜ ..ምግብ ጠቆረ.. ይልና ያድማል፡፡ ..እኛ መነገጃ አይደለንም.. ይላል፡፡ የጐጃም ጠቅላይ ግዛት በሙሉ፣ የ35 ወረዳና የሰባቱ አውራጃ እዚሁ ነበር የሚታሰረው - የመተከል፤ የቤንሻንጉል፤ የባህርዳር ሁሉ ማለት ነው፡፡ እስረኛው ሲያድም እኔ ሽጉጥ ታጥቄ በመሃላቸው እገባና ..እናንተን ያሰራችሁ ሰው አይደለም፤ ያሰራችሁ እግዚአብሔር ነው፡፡ እዚህ እኮ የምትፀልዩበት፣ የምትማፀኑበት፣ ፍርድ እናግኝ ብላችሁ የምትለማመኑበት ነው፡፡ የጐጃም ሰው ሆዳም አይደለም ምግብ አነሰኝ ብሎ አይናገርም፡፡ አናንተ ቆሎ፣ በሶ፣ በግም ፍየልም አሳርዳችሁ ትበላላችሁ፤ አገራችን ተሰደበ.. ብዬ ያንን ጠቆረ አንበላም ብለው የተውትን ጥቁር እንጀራ እነሱ መሃል ሆኜ ቆርሼ እበላዋለሁ፡፡ ያንዜ ያጨበጭባሉ፡፡ ከዛ በኋላ አድማው ይበተናል፡፡ ..አሁን ትፈታላችሁ ግማሻችሁ በአመክሮ፤ ግማሾቻችሁ ደግሞ ፀባያችሁ ጥሩ ከሆነ ሚያዚያ 27 በአርበኞች ድል በዓል ወይም ሐምሌ 16 በጃንሆይ ልደትና ጥቅምት 23 በጃንሆይ የዘውድ በአል ትፈታላችሁ፡፡ እንቢ ካላችሁ ግን ችግር ላይ ትወድቃላችሁ.. ስላቸው በጀ ይላሉ፡፡ የጣቢያው አዛዥ ንግግር ስለማያውቅበት ቀጠሮ ስጡኝ ብዬ እኔ ነበርኩ የማናግራቸው፡፡ ለእስረኛው ያወጡት ህግ ነበር ይባላል? ህጉ እያንዳንዱ እስረኛ ሰውነቱን በሳምንት አንድ ቀን ፀጉሩን ዕለት ዕለት እንዲታጠብ የሚል ነው፤ አሽቶ የሚያጥበው በወር 1 ብር ከፍሎ ሰው ራሱ ይቀጥራል፡፡ እስረኛው ገንዘብ ነበረው፡፡ ሞልቶታል፡፡ ከዚያ አሰልፋቸውና ከኪሴ ነጭ መሀረብ አውጥቼ የአንዱን ደረት አሸት አድርጌ ..ይሄው እድፍ አለው ውጣ.. እለዋለሁ፡፡ ንፁህ ሆኖ ያገኘሁትን ደግሞ አንድ ብር አወጣና እሸልመዋለሁ፡፡ ያን ጊዜ እስረኛው ሁሉ ንፁህ ለመሆን መሯሯጥ ነው፡፡ የመኝታቸውን ዳትም ክፍላቸው እየገባሁ እፈትሽ ነበር፡፡ ይሄን አይተው ደጃዝማች ፀሃይ (በ1958) የደ/ማርቆስ ቤተመንግስት ሲሰራ ..ይሄ ጐበዝ ልጅ ነው፤ ጠንካራ ሰራተኛ ነው.. ብለው ወሰዱኝና እንደገና ተሸለምኩ፡፡ ንጽህናውን ያልጠበቀ እስረኛስ? ቅጣት አለው? አዎ ይቀጣል፡፡ አስር የችግኝ ጉድጓድ አስቆፍረዋለሁ፤ በግቢው ውስጥ የፍራፍሬና የአትክልት ስፍራ ስለነበረ እሱንም አስቆፍራቸዋለሁ፡፡ ሰው ገድሎ የታሰረውን ግን ወታደሩ ስራ አናሰራም ብሎ ይቃወመኛል፤ መሳሪያ ነጥቆን ይሄዳል በሚል፡፡ ..በያዝከው መሳሪያ አጨማደህ አትጥለውም፤ እንግዲህ በእግር ብረት ታስሮ አይሞትም.. እልና፤ የገደለውን ሁሉ ሰብስቤ ..ኑ ተንቀሳቀሱ ይሄ ስራ የእናንተ ነው፣ አካልና አእምሮአችሁን አስተባብራችሁ በሞራል የጠነከራችሁ እንድትሆኑ ስሩ.. እላቸዋለሁ፡፡ በጣም ይወዱኛል፡፡ ፍ/ቤት ለስራ ስሄድ ባዶ ወረቀት ካገኘሁ ሰብስቤ አመጣና አንዳንዱን በሽልማት እሰጣቸዋለሁ፤ ለዘመድና ለምሽት ደብዳቤ መጠጣፊያ፡፡ ከዚያ ፊደል ሠራዊት የሚባል መሰረተ ትምህርት ተቋቋመ፡፡ በደጃዝማች ፀሃይ ጊዜ፣ አቶ ሸዋቀና የተባሉ የትምህርት ሚኒስቴር ሃላፊ፣ የጠቅላይ ግዛቱን ወህኒ ቤት እሱ ነው ማስተባበር የሚችለው አሉና እኔን ሾሙኝ፡፡ ማንበብ መፃፍ የማይችል፤ በጣቱ እየፈረመ የሚበላ ፖሊስ ሞልቷል - ያኔ፡፡ አዳራሽ ላይ ሰበሰብኩና እስከ ስልሳ ቀን ድረስ ማንበብና መፃፍ ካልቻላችሁ ሚስጢር ነው የምነግራችሁ ..ትባረራላችሁ.. ተብሏል አልኳቸው፡፡ (ሳቅ) መንግስት አቋም ይዟል፤ ማታ ማታ ልጆቻችሁ ቤት ውስጥ ያስተምሯችሁ አልኳቸው፡፡ ማንበብ መፃፍ የማይችል ሠራዊት በፍፁም አይሆንም፤ እየተባለ ነው ስላቸው. . . ማታ ማታ ጥናት ነው፣ ማንበብ ነው፡፡ ሲፈተኑ ደህና ናቸው፡፡ ..ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዘኢትዮጵያ.. ብዬ ብላክ ቦርዱ ላይ ፃፍኩና ገልብጡ አልኳቸው - እንዳለ ፃፉት፡፡ በዚህም ተሸለምኩ፡፡ አብዮቱ ሲፈነዳ በአንድ ቀበሌ ውስጥ ህዝቡ ስለሚያውቀኝ የአብዮት ጥበቃ የፍርድ ዳኛ ሸንጐ ውስጥ ገባሁ፡፡ በደብረማርቆስ በድሮው ቀበሌ 8 ዳኛ ሆንኩ፡፡ ስራዬ እርቅ ነበር - ይቅር ተባባሉ ማለት፡፡ ፍርድ የሚሻውን ደግሞ ፍርድ እያሰጠሁ እየቀጣሁ በሬድዮ አስነግራለሁ፡፡ ጉልታዊ አገዛዝን እየኮነንኩ፤ የሠራተኛውን መደብ ንቃ እያልኩ የተናገርኩ እንደሆነ መልእክቴ ሁሉ በሬድዮ ይሰማ ነበር፡፡ በአፄ ኃይለስላሴ ጊዜ ከሽፍቶች ጋር ተደራድረሃል ይባላል? የገበሬው አመ በሚባልበት በነ ባምላኩ ጊዜ፣ እነ ደጃዝማች ፀሃይ ከደ/ማርቆስ ይነሱ በሚባል ጊዜ ከብፁዕ አቡነማርቆስ ጋር ደብረወርቅ ሄጃለሁ፡፡ ገበሬው ሰው ቆምጬን ያውቀዋል ብሎ ለከኝ፡፡ በኢሊኮፍተር ነበር የሄድነው፡፡ ከዛ ከኢሊኮፍተሩ ላይ ስንወርድ ከርቀት አነጣጥረው የብፁዕ አቡነ ማርቆስን ቆብ ይመቱታል፤ ..ጐንበስ ይበሉ ጐንበስ ይበሉ.. አልኳቸው፡፡ በኋላ እንደ ምንም ወጣን፡፡ በዚያን ወቅት እንግዲህ ሀገሩ ሁሉ ሸፍቶ ነበር፡፡ ወንበዴ በወንበዴ ሽፍታ በሽፍታ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ማነው አሁን እነሱ ጋ ሄዶ እርቅ የሚለምን ተብሎ አገር ይታመሳል ..እኔ እሄዳለሁ ምን ችግር አለው.. ብዬ ሽጉጡንም፣ ኡዚ አቶማቲክ ጠመንጃም ይዤ በመሃላቸው ገባሁና ..ደህና ዋላችሁ፤ ደህና ዋላችሁ.. ስል ሁሉም ተነስቶ ሰላም አለኝ፡፡ እህሳ! ያ ሁሉ ሽፍታ እኮ ታስሮ የተፈታ ነው፡፡ በእስር ቤት ውስጥ ሁሉም ነበር የሚያውቀኝ፡፡ በኋላ ከፊታቸው ቆሜ ንግግር አደረኩ፡፡ ..እናንተ ብቻችሁን አትችሉም፡፡ ሃገር ልታስደበድቡ ነው፤ ክቡር ዘበኛ መጥቷል፡፡ ዛሬ ምላሻቸውን እንፈልጋለን መልሱን አምጣ ተብዬ ነው.. ስላቸው ..አንተማ የሀገራችን ልጅ ነህ ሌላ ቢሆን በጥሰን በጣልነው ነበር፡፡ በእስር እያለን ከሚስታችን ከዘመዳችን እያገናኘህ ብዙ የረዳኸን ነህ፡፡ አሁንም የምትለንን እንሰማለን፤ ጦርነት አንፈልግም፤ እኛ የምንፈለገው አንድ ብር ከሃምሳ ግብር እንዲነሳልንና ደጃዝማች ፀሃይ እንዲወርዱልን ነው.. አሉኝ፡፡ እዚያው ያሉትን ቁጭ ብዬ ፃፍኩና ..መልስ እስክናመጣላችሁ ወደ ቤታችሁ ግቡ፡፡ እርሻም እረሱ፤ የመጣውም ጦር ይመለስ፤ ጳጳሱም መጥተው ተኩሳችሁ ልትገሏቸው ነበር፡፡ እግዚአብሔር ነው ያወጣቸው፡፡ አሁን እሳቸው ሊያስታርቁ ቢመጡ ሊያስተኩሱ እንደመጡ ሁሉ እንዲህ ታደርጉ? እኔም ደሞ የሀገር ሰው ነህ፤ ወንድም ነህ ተብዬ ተመርጬ ነው የመጣሁ፡፡ የተከበሩ አቶ መኮንን እውነቴን፤ የተከበሩ በከፋ የኔነህን ታውቋቸዋላችሁ አይደል? በአምስት አመት የጠላት ወረራ ዘመን ከደጃዝማች በላይ ዘለቀ ጋር አብረው የነበሩ፣ የደጃዝማች በላይ ዘለቀን ማህተም ይዘው ይፉ የነበሩ ናቸው. . . ጠላትን ያርበደበዱ የነበሩ፡፡ ዛሬ ደግሞ አስታራቂ ሆነው መጡ፡፡ በሉ እነሱ ይምጡና ሰላም በሏቸው.. አልኳቸው፡፡ ..በቃ እሺ...... ወታደር እንዳይመጣ እነሱ ይምጡ.. አሉ፡፡ ይዤአቸው ሄድኩ፡፡ ብቻ ወዲህ ወዲያ ብለን ደጃዝማች ፀሃይ ወረዱ፡፡ ሰላም ሰፈነ፡፡ የደርግ መንግሥት እንዴት ተቀበለህ? በደርግ ሥርዓት ሌባ፣ ሴሰኛ፣ ገንዘብ የሚያታልለው፣ ጥቅም ፈላጊ ፓርቲውን አይቀላቀልም ነበር፡፡ እንጃ! በኋላ አበላሽተውት እንደሆነ አላውቅም፡፡ የመደብ ትግሉን ለመቀላቀል የሚፈልግ ሰው የግል ማህደሩ ይታያል፡፡ እኔ በመጀመርያ በሙሉ ፈቃደኝነት ማመልከቻ የፃፍኩት ..የኢትዮጵያ ብሄራዊ ዲሞክራሲያዊ አብዮት ፕሮግራምን ተቀብያለሁ፤ ከሰፊው ህዝብ ጥቅም ይልቅ የራሴን ጥቅም አላስቀድምም፤ ከራሴ ጥቅም ይልቅ የሰፊውን ህዝብ ጥቅም አስቀድማለሁ፣ እየተማርኩ ከአብዮቱ ጋር ለመቀላቀል ፈቃደኛ ነኝ.. ብዬ፡፡ ማመልከቻዬ ተመረመረ፤ ጀርባዬን አስጠኑኝ - በደህንነቶች፤ በጐረቤት፡፡ በኋላ በቀበሌ የጥናት ክበብ ውስጥ አስገቡኝ፡፡ በመንግሥት ሥራ ተወጥሮ የጥናት ክበቡ ላይ ያልተገኘ እንኳን ይሰረዛል፡፡ መማር ግድ ነበር፡፡ ትምህርቱ ምንድን ነው? የካፒታሊስት ስርዓትና፤ የሶሻሊስት ስርዓት ምንድን ነው? ጠቃሚው የትኛው ነው? በሚል ነበር፡፡ ከዛም የሠራተኛው መደብ ንቅናቄ በጀርመን በአሜሪካ ምን ይመስላል የሚለውን. . . ከዛም የምትበይው፣ አረማመድሽ፣ ንቃትሽ፣ ንግግርሽ ሁሉ ይገመገማል፡፡ የገባው ሁሉ አይዘልቅም፡፡ ልክ መንገድ ላይ መኪና እንደሚጥለው ፌርማታ ላይ እየተራገፈ ይሄዳል፡፡ ከብዙ ምልምሎች ጥቂቶች ቀረን፡፡ . . . እኔ እዚህም ምስጉን ነበርኩ፡፡ ምስጉንነትህን ማን ነገረህ? ጓድ መንግሥቱ ናቸዋ! አፍና ተግባር ይሉኝ ነበር፡፡ አንደዜ እሳቸው በምሠራበት አቸፈር አካባቢ መጥተው ሳለ. . . እኔ አላውቅም ነበር እንደሚመጡ፡፡ የከብቶችን አዛባ እዝቅ ነበር፡፡ ኮረኔል ዘለቀ ..ና ሰላም በል ና ሰላም በል.. አሉኝ፡፡ ሸሚዜን ወደ ላይ ሸበሸብኩና ስጨብጣቸው ..ጓድ ቆምጬ አስተዳድሩ ተባለ እንጂ አዛባ ይዛቁ ተባሉ.. አሉኝ፡፡ ..ጓድ መንግስቱ፤ እኔ ካልሠራሁ ሌላው ስለማይሰራ ነው.. አልኳቸው፤ ዞረው ሁሉን አዩ፡፡ በቆሎው፣ በርበሬው ደርሷል፡፡ በቆሎውን ሸለቀኩና አንዱን ወታደር እንካ ጥበስ አልኩት፡፡ በኋላ ጠብሶ ሲሰጠኝ እንኩ አልኳቸው፤ ሰበር አድርገው እሸቱን በሉ፡፡ ቀሪውን ለአጃቢው ሰጠሁት፡፡ ያሉት ሁሉ አንዳንድ በቆሎ በሉ፤ ቆሎ በኑግ ከመንደር መጣ፡፡ ጠላ በዋንጫ ቀዳሁና እኔ መጀመሪያ ..ፉት.. አልሁና ሰጠኋቸው፡፡ ..ለምን ነው? ለምን ነው? ዝም ብለው ያምጡት አሉኝ.. መቸም ኸዱ ብዬ አላማቸውም፡፡ ..ለምን ቀመሱት ጓድ ቆምጬ ያምጡት በሉ.. አሉኝ ..አይ የጎጃም ባህል ነው፡፡ ማንም እንዲህ ሲሰጥ ቀምሶ ነው ሚሰጥ፤ እንቆቆ ወገርት መድኃኒት ሲሰጥ እንኳን ቢሆን ቀምሶ ነው፤ የሀገሩን ባህል ለማንፀባረቅ ነው.. አልኳቸው፡፡ በኋላ በርበሬ ጧ ብሎ ደርሷል፤ ይዩት ብዬ እሱን አሳየኋቸው፡፡ ጓድ ካሣ ገብሬ የኮንስትራክሽን ሚኒስቴሩ ወፍራም ነበሩ፤ እኔ አላውቃቸውም ነበር፡፡ እንደዛሬው ቴሌቪዥን የለም፡፡ ሳያቸው ሆዳቸው ቦርጫቸው ሌላ ነው ..እስዎም አሁን ኮሚኒስት ተብለው ነውን?.. አልኳቸው፡፡ መሀረባቸውን ከኪሳቸው አውጥተው እምባ በእምባ እስቲሆኑ ድረስ ከት ከት ከት ብለው ሳቁ፡፡ አንተስ ቀጭን ነበርክ? በጣም፡፡ ይኸውልሽ ወንበዴ እየመጣ ሁልጊዜ ተኩስ ነው፡፡ ሀሳብ ነበረብኝ፡፡ በዚያ የተነሳ ሃሳቡ ነው መሰለኝ በጣም ቀጭን ነበርኩ፡፡ በኋላ ጓድ መንግሥቱ ..እስቲ የወረዳውን ተፈጥሯዊ ገታና አጠቃላይ ሁኔታ አምጣ.. አሉኝ፡፡ ..አውራጃ አስተዳዳሪው ጓድ መስፍን አለ አይደል.. አልኳቸው፡፡ ..ከወረዳው መስማት ነው የምንፈልግ.. አሉ - እሳቸው፡፡ ያለውን ነገር ሁሉ ቁጭ አደረኩላቸው፡፡ በመሠረተ ትምህርት ቅስቀሳው አንዳንዶች አትማሩ እያሉ እየቀሰቀሱብን ነው እንዲያውም አስራ ሁለተኛ ክፍል የጨረሰውን ሥራ ሳያሲዙ እያሉ እንደሚያሳምፁና ወረዳውም በከፍተኛ ሁኔታ ኋላ ቀር መሆኑን፣ የመብራትና የውሃ ችግር መኖሩን፣ የአቸፈር ልጅ ለአብዮቱ በየተራራው እንደሚዋጋ ሃቁን ስነግራቸው ..እነዚህ ወረበላዎች ምን እያሉ ነው የሚቀሰቅሱ.. አሉኝ፡፡ አይ ይሄን የነገርኩዎን ነው አልኳቸው፡፡ የወረዳውን ለእኛ ተውት፤ ግን ነገሩ በውይይት ቢፈታ አልኳቸው ..በውይይት ሲሉ ምን ዓይነት ነው?.. አሉኝ፡፡ ..ሰውን የሚያጣላው የስልጣን ጥያቄ ነው ጓድ ሊቀመንበር.. አልኳቸው፡፡ ..ለመሆኑ እርቅና ድርድር ቢጀመር ትኩረት ሰጥተው ይከታተሉታል.. አሉኝ፡፡ ..አዎ.. አልኳቸው፡፡ ..እንዴት.. አሉኝ፡፡ ..በክቡር አቶ አማኑኤል አምደሚካኤል የሚመራ ቡድን ሦስት ጊዜ ሂዶ እርቁ ከሸፈ፡፡ በሬዲዮ የሰማሁትም የኢትዮጵያ መንግሥት እምቢ አለ የሚል ነው.. አልኳቸው፡፡ ..ለማንኛውም ጥሩ ግንዛቤና የሀገር ፍቅር አለህ፡፡ አፍና ተግባር ትክክል ሆኖ ያየሁት ባንተ ነው.. አሉኝ፡፡ ተዚያም ሽጉጥ አውጥተው ..ገንዘብ የለኝም.. አሉና ሊሰጡኝ ሲሉ ..ኧረ እኔ ተሽፍታ ያስፈታሁት አስራ ስምንት ሽጉጥ አለ፡፡ እንደውም ከቸገራችሁ ውሰዱ አልፈልግም.. አልኳቸው፡፡ ..ታዲያ ምንድነው የሚፈልጉት.. ሲሉኝ ..መብራት እና ውሃ ለሰፊው ህዝብ.. አልኳቸው፡፡ ጓድ ፍቅረስላሴ ወግደረስ አብረው ነበሩ፡፡ ..ጓድ ፍቅረሥላሴ፤ ቀን ሰጥቼሀለሁ. . . በተገኘው ገንዘብ ሁሉ መብራትና ውሃ እንዲገባ.. ብለው መመሪያ ሰጡልኝ፡፡ ስልሳ ቀን ሳይሞላ መብራትና ውሃ ገባ፡፡ ለአስተዳዳሪነት የተመደብክበት የመጀመሪያ ቦታ የት ነበር? ቢቡኝ ነበረ፡፡ ቢቡኝ ማለት እስታሁንም አረንጓዴ ትርዒት ማለት ነው፡፡ በሄድኩበት ወረዳ የተፈጥሮ ሀብት እንክብከቤ በማድረግ የደን መራቆት እንዳይኖር ሳልታክት እሠራ ነበር፡፡ ከዚያ ደግሞ ሁለት እጅ እነሴ ወረዳ ነው የሰራሁ፡፡ እዛም እንደዚያው ደብረ ወርቅ ተዛውሬ አበት አለፍ የሚባል ተራራ አለ፤ የሬዲዮ መገናኛ ያለበት ነው፡፡ እዚያ ወጥቼ ሳየው ተራራውን ገበሬው እህል ያበቅልበታል፡፡ አጠናሁና ..እዚህ ላይ ደን እንትከል.. አልኩ. . . ..ከብት ይበላዋል.. አሉ፡፡ ..በፍፁም! እኔ እዚው መሳሪያዬን ይዤ እተኛለሁ እጠብቀዋለሁ ግዴለም.. አልኩ፡፡ በበሬ አረስነ አስተከልነ፡፡ ከዚያ በስብሰባ ላይ ..እንግዲህ ልብ አድርጉ የብሔራዊ አብዮታዊ የምርት ዘመቻን ሳንይዝ መንግሥት ያወጣው መመሪያ ግቡን አይመታም፡፡ ሊመታ የሚችለው እኛ ስንሠራ ነው.. እንደ አሁኑ የ5 ዓመት መርሃ ግብር እንደሚባለው ማለት ነው፡፡ ..በሥራ ቀን ቤት ተቃጥሎብህ፣ ጥይት ተተኩሶብህ ካልሆነ በስተቀር እዚህ ከተማ ሲያወደለድል የሚገኝ ሰው ቢኖር ደን ተከላ ነው የምልከው.. ብዬ አወጅኩ፡፡ ሰው ሲመጣ ይያዛል፤ ደን ተከላ ይላካል፡፡ የዚያንዜ ያስተከልሁት ችግኝ ዛሬ አድጎ መብራት ኃይል ለመላው ኢትዮጵያ ከዚያ እየቆረጠ ነው ሚወስድ፡፡ ወደ 6 ማሊዮን ብር ተሸጧል፡፡ ምን እንደሰሩበት እንጃ! በኋላ ዶ/ር ገረመው ደበሌ ለጉብኝት መጥተው አይተው በጣም ተደሰቱ፡፡ ወደ 50ሺ ብር የሚሆን ለግብርናው ሽልማት ሰጡ፡፡ የቀለም ትምህርት እስከ ስንት ዘልቀሃል? ደብረ ኤልያስ እስከ ስድስተኛ ክፍል ተምሬአለሁ፤ ደብረ ወርቅ እስከ ዘጠኝ ተምሬ በተልዕኮ 12ኛ ጨረስኩ፡፡ ከዛም ፖለቲካ ት/ቤት አስገቡኝ፡፡ ..ይሄን የመሰለ ልማት እየሠራ በትምህርት ቢታገዝ የበለጠ ውጤት ያመጣል.. ተባለ፡፡ ተዚያ ቀደም ይከለክሉኝ ነበር፡፡ የሚልኩኝ ችግር ባለበት ወረዳ ነው፡፡ ችግር ሲኖር እሱ ይሂድ ነው የሚባል፡፡ እኔ ሄጄ እግሬ እንደደረሰ ህዝቡን ሰብስቤ ..ከመንግሥት ጋር ያለህ ፀብ ምንድነው? በል ተናገር.. እለዋለሁ . . . ..ጠባችን ከመንግሥት ጋር አይደለም፤ ከሊቀመንበሩ ጋር ነው.. ይላል፡፡ ..እሱ ነው ጠላትህ ይሄው አወረድኩልህ፤ ሌላ ምረጥ.. እለዋለሁ፡፡ ይኸነዜ አዳሜ ወክ ይላል፡፡ አንድ የማልረሳው ምሳሌ ብነግርሽ አንደዜ የገበሬዎችና አምራቾች የህብረት ሥራ ላይ መሬት ከልለው ገበሬውን ባዶ አስቀርተውት አገኘሁ፡፡ ..ምንድን ነው.. ስላቸው ..ዛሬማ ቅልጥ ያለ ተኩስ አለ.. አሉኝ፡፡ ..ለምን?.. አልኩ፡፡ ..አምራቾች የሚያበሉትን ሳር እናብላ ብለው.. አሉኝ፡፡ አንድ የሚበጠብጥ ካድሬ ነበር ይሄን ሁሉ የሚያደርገው፡፡ የራሴን እርምጃ ወስጄ ወደ ሌላ ቦታ አዛወርሁት፡፡ ሌባን ለማጥፋት ሸፍተህ ነበር ይባላል. . . ዋ! እህሳ! ልክ ነው፡፡ አስር ዓመት ሙሉ የሸፈተ አንድ ኃይለኛ ሽፍታ ነበር፡፡ አንደኛውን በቃ ሃይለኛ ነበር፡፡ ..ግዴለህም ግን.. ብዬ አባብዬ ብልክበት ..እነ ደጃዝማች ደምስ ያልነኩኝ ማን ነው እሱ!.. ብሎ ናቀኝ፡፡ የወረዳውን ህዝብ ሰበሰብኩና ሳበቃ ..የምንሄድበት ቦታ አለ፡፡ ወታደር የሆንክ ወደ ኋላ ሁን.. አልኩ፡፡ ሽማግሌዎች ነበሩ፡፡ የሀገሩ ሰው ለእሱ አብሮ ይተኩስብናል፡፡ ብቻ ተጠንቅቀን ደረስን፡፡ ከሌቱ በ10፡00 ሰዓት ቤቱን ከበብነው ..እታኮሳለሁ.. አለ፡፡ ጠመንጃውን አቀባብሎ ሁለት የጣሊያን ቦምብ ይዞ፤ በሁለት ወታደር ታጅቦ መጣ፡፡ ሰላምታ እየሰጠ. . . እንግዲህ ከበነዋል፡፡ ማምለጫ የለም. . . ሁሉንም እየጨበጠ ሲመጣ እኔ ሰላም እለውና ..ያዝ!.. ስላችሁ በላዩ ላይ ተከመሩ ብዬ ወታደሮችን መክሬያቸው ነበር፡፡ እኔ ጋ ደርሶ ሰላም ሲለኝ ..ያዘው.. ብዬ ስል ያዙት ..ወይኔ ወይኔ!.. አለ፡፡ እጅ እግሩን ጠፍረን አሰርነው፡፡ ..እንግደለው.. አሉ፡፡ ..የለም ይሄ አይደረግም፡፡ እንኳን ይሄንና ሶማሊያ፣ ግብፆች፣ ቱርኮች፣ ጣሊያንና እንግሊዞች አገራችንን ሲወሩ እንደዚህ አድርገው እጃቸውን ሲሰጡ አይገደሉም፡፡ ይሄማ ወንድማችን ነው፤ አስረን ነው የምናስተምረው፤ እሺ ብሎ አንደዜ እጁን ሰጥቷል.. አልኳቸው፡፡ ተዚያማ ምኑን ልንገርሽ፡፡ ሌላ ሆነ . . .ተፎከረ ተሸለለ. . . የተለያዩ መፈክሮች እያፃፍክ ትሰቅል ነበር? መስቀል ነው! . . . ..ከሌባ ጋር እንዳትጋቡ፤ ለሱ የሚድርለት ራሱ ሌባ ነው.. የሚል መፈክር ነበረኝ፡፡ የጦር መሣሪያዬን አነግትና በየኼድኩበት ስለ ጉቦ፣ ስለ ሥርዓቱ አስተምራለሁ፡፡ እና ደግሞ ሰውም ይሰማኛል ..ምን ልታደርግ መጣህ.. ስለው ..ልማር፤ ህግ ላውቅ ነው የመጣሁ.. ይለኛል፡፡ ከሌላው ወረዳ ይልቅስ ብዙ ሽፍቶች እጃቸውን የሚሰጡት በእኔ ወረዳ ነበረ፡፡ በቴሌግራም በሬዲዮ ..እንዲህ ያለ ሽፍታ እጅ ሰጥቷል.. ብዬ አስነግራለሁ፤ ሰላማዊ መሆኔን እነግራለሁ፡፡ የራሴኮ ቴሌግራም ነበረኝ፡፡ ማን ሰጠህ? መንግሥት ነዋ! በዚያን ወቅት እነ ሰልጣን አለሙ የተባሉ ጋዜጠኞች ነበሩ ስራዬን ሁሉ የሚያስተላልፉልኝ፡፡ እናም ..የእሱን ሥራ ተናገሩለት፤ ሌት ተቀን ነው የሚለፋው.. ተብዬ ድጋፍ ተሰጠኝ፡፡ በኋላ አንድ ጊዜ የቡሬ አስተዳዳሪ የነበረ መቶ አለቃ ሙሉ የሚባል ሰው፣ ጓድ ቆምጬ የሚያስተዳድሩት ማቻከል ወረዳ 80ሺ ኩንታል እህል አስገብቶ አንደኛ ወጣ ተብሎ ሲነገር ቢሰማ ..የለም! አፈር ጭኖ ነው እንጂ እህል ጭኖ አይደለም.. ብሎ አስወራብኝ፡፡ ምቀን ይዞት፡፡ በኋላ 4 ወፍጮ ተሸለምን፡፡ በአንተ ስም ነው የተሰየመው ይባላል... አዎ /ሳቅ/ ቆምጬ ወፍጮ ነው የተባለው፤ እንዲያውም ወፍጮው ሲነሳ ሁሉ ..ቆምጬ ተንደቀደቀ.. ይባል ነበር፡፡ ዛፍም አለ ..ቆምጬ ዛፍ.. የሚባል፡፡ ዳቸና ገብርኤል ውስጥ ነው ያለው፡፡ ሰው አይነካውም፡፡ ..ይሄ ከደረቀ ለዚህ እግር አልጠቀመውም.. ብዬ እተክለዋል፡፡ እኔን መስሎ ስለሚታየው ሰው ዛፉን ይንከባከበዋል፤ በምሔድበት ሁሉ መጋቢትም ይሁን የካቲት ቆፍሩ እልና ..ይሄ ዛፍ ይድረቅና እያንዳንዳችሁን አደርቅችኋለሁ.. እያልሁ አስፈራራቸዋለሁ፡፡ የህዝብም ግም የአገርም ግም የለውም፡፡ የትም ወረዳ ሂጂ ..አንድ የሆነ ሰው ክፉ ነው፣ ገዳይ ነው፣ በመሪዎች ላይ አደጋ ይጥላል.. ሲባል ልትሰሚ ትችያለሽ፡፡ ግን ውሸት ነው፡፡ መሣሪያውን ወይም እጮኛውን ካልቀማሽው፣ ሰውየውን ዝቅ ካላደረግሽው፣ ባለሞያውን ካከበርሽው ምንም አይልም፡፡ፖለቲካ ት/ቤት ባለሥልጣኑን ጉድጓድ አስቆፍራቸው ነበር፡፡ መሠረተ ትምህርትን ምሁራኑን ይዤ አቅዳለሁ፡፡ ..እናንተ መሀይምነትን ማጥፋት አለባችሁ.. እላቸዋለሁ፡፡ ለመምህራኑ ስኳር፣ ብርድ ልብስ የሚያስፈልጋቸውን እሰጣቸዋለሁ፡፡ ከሊቀመንበሩ በላይ የገጠሩ መሪ የማደርገው መምህሩን ነበረ፡፡ ባለሙያውን ልዩ ሥልጣን እሰጠዋለሁ፡፡ በደብረ ምጥማጥ አንድ መምህር ነበረ፡፡ ወጥሮ ያዛቸው፡፡ ትምህርት ላስተምራችሁ ባለ ያላደረገውን ..በሬ ሰረቀን . . .እንዲህ አደረገን.. አሉና ከበው ይዘው አመጡት፡፡ ..ነው? ሰረቀ?.. አልኳቸው፡፡ ..አዎ.. አሉኝ፡፡ ..በአለም ላይ መምህር መቼ ነው ሌባ ሲሆን ያያችሁት?.. አልኩና ይዘውት የመጡትን ሰዎች አሰርኳቸው፡፡ መምህሩን ይዤው ወደ ከሰሱት ሀገር ሄጄ ..እውነቱን አውጡ! ካልሆነ በጊዜ ቀጠሮ እያንዳንድህን ወህኒ ቤት ነው ምለቅህ.. አልኳቸው፡፡ ጎጃም ዱር የሚባል ቦታ አለ፡፡ አካፋና ዶማ አስያዝኩና ማስቆፈር ጀመርኩ፡፡ ሲቆፍሩ ውለው አዳራሽ ውስጥ እንዲያድሩ አደረግሁ፡፡ ተዚያማ . . . . . . ..አያ! ጌታችን ተሳስተናል.. አሉኝ፡፡ ..ጌታ እግዚአብሔር ነው፡፡ አቶ ቆምጬ (ጓዱ ቆምጬ) ብለህ ጥራኝ፡፡ ጌታህ እየሱስ ክርስቶስ እንጂ እኔ አይደለሁም.. አልኳቸው፡፡ ..አንተም እርፍ ይዘህ ታርሳለህ፣ እኔም አርሳለሁ፡፡ አንተ የምታጭደውን እኔም አጭዳለሁ፡፡ እኔ ህይወትህንና ንብረትህን ለማስጠበቅ መንግሥት የላከኝ ሰው ነኝ እንጂ አንተንና እኔን የሚለየን የለም.. አልኳቸው፡፡ ..ውሸታችንን ነው፡፡ መሠረተ ትምህርት እያስተማረ አላስቀምጥ ስላለን ነው ይቅርታ.. አሉ፡፡ ዋና ቀንደኞችንና ሊቀመንበሩን ወህኒ ሰደድኩና ..ይህንን መምህር አክብረህ መሪነቱን፣ መምህርነቱን፣ ሰው የሚለውጥ መሆኑን፣ ለብሔራዊ አብዮታዊ የምርት ዘመቻ ከፍተኛ እድገት አዋጭ መምህሩ መሆኑን አውቀህ አክብረው፡፡ እኔን በትምህርት ይበልጠኛል.. አልኩ፡፡ ሰው እንዲማርና መሠረተ ትምህርት እንዲያድግ ህዝቡን ሌላ ያሳመኑበት መንገድም ነበር . . .? አይሄ (ሳቅ). . . ይኼውልሽ አንድ ዮናስ የሚባል ልዥ ነበር፡፡ የወረዳ አስተዳዳሪ ነው፡፡ እና ገጠር አይወድም፡፡ ገጠር ከሄደ አተር አስቆልቶ ሲበላ ነው የሚከርም፡፡ የገበሬውን ቦሃቃ፤ ምግቡን ንፁህ አይደለም እያለ ያነውራል፡፡ እኛ ደግሞ ገበሬ የበላውን ነው የምንበላ፡፡ ድንችም ቆሎም የተገኘውን እንበላለን፡፡ ዶ/ር ፋሲል ናሆም የጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ህግ አማካሪ፤ ቀደምም የመንግሥቱ ኃ/ማርያም አማካሪ የነበሩ በሄሊኮፕተር ወደ ፓዊ ሲሄዱ ..ቆምጫ አምባው ማለት ወታደር ነው እንጂ መምህር አይደለም፤ እንዴት ነው ነገሩ? በመሠረተ ትምህርት አንደኛ ወጥቷል፤ በፀረ ስድስት ክትባት ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሸልሞታል፡፡ ሽልማት በሽልማት ነው ስልቱ ምንድን ነው?.. ሲሉ ይሄ ዮናስ ያልኩሽ ሰው ..እሱማ ቢቡኝ ወረዳ ሂዶ፤ መሠረተ ትምህርት ያልተማረ መፃፍ ማንበብ ያልቻል ቡዳ ነው፤ ቡዳ ስለሆነ እንዳትድሩለት፤ ውሃም እንዳታስቀዱት ብሎ አወጀ.. ብሎ ነገራቸው፡፡ በቃ ያን ይዘው እንዲህ አለ ይሉኛል፡፡. . . ..ያው እኔ በእቅድና በስልት ነበር የምመራ፡፡ በእርስዎ ስም የሚነገሩ ብዙ ቀልዶች አሉ... የሶሻሊዝም አፍቃሪ ነበሩ ይባላል? ያ ሥርዓት ተለውጧል ብዬ የምተወው አይደለም፡፡ በተመስጥኦ ነበር የተቀበልኩት፡፡ ግንባር ቀደምትነት የሚሰጠው ለሠራተኛው ስለነበር በጣም ነበር ያራመድኩት፡፡ በሠራተኛውም በዕደ ጥበባቱም፡፡. . . ..ሦስቱ ጣምራ ጠላቶቻችን እነማን ናቸው.. ብላችሁ ቆምጬን ብትጠይቁት ..ያው አብዮት አደባባይ ተሰቅለውላችኋል!.. ይላል ይላሉ - የግልብጥ ሲወራ፡፡ (ሌኒን፣ ማርክስና ኤንግልስ ለማለት ነው) ፈተና ቀርቦ ..የብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ፕሮግራም ለምን አስፈለገ? ለምን ቀጥታ ሶሻሊዝም አልሆነም?.. ተብሎ ሲጠየቅ ..ታዲያ ቆምጬ አምባው ነው የከለከላችሁ ከሆነ አታደርጉትም!.. ብሎ መለሰ ይላሉ፡፡ ሊቢያና ቻድ ተጣልተው ነበረ፡፡ ፕሬዚዳንት ሊቀመንበር ጓድ መንግሥቱ ሊያስታርቁ ሄደው ሳይሳካ ቀረ፤ ..አንተ በፖለቲካ መጥቀኸል ሌት ተቀን ታነባለህ፡፡ ንባቡን አንበልብለኸዋል፡፡ እንግዲህ በአንተ አተያይ ሊቢያና ቻድ እንዴት ናቸው?.. ብለው አቶ ካሣዬ አራጋው ሲጠይቀው ..አይ! ለምን ሥራ ያስፈቱኛል? ሊቢያና ቻድን ሊቀመንበር መንግሥቱ ያልሆነለትን ከደብረወርቅ ቆምጬ አምባው ሄጄ ላስታርቅ ነው?.. ብሎ አለ አሉኝ፡፡ አንደዜ ደሞ እኔ ራሴ ዝርፊያ ትተው አገር እንዲጠብቁ ያስታጠኳቸው ሌቦች ነበሩ፡፡ እኔ ከማስተዳድረው አካባቢ ለቀው ሌላ ቦታ ሲዘርፉ ተገኙ፡፡ በኋላ ጠራሁና አረቄ እያጠጣሁ ..እንዴት ነው . . . እኔ በማህበር በሰንበቴ በእድር እከታተላችኋለሁ፡፡ ግን ስርቆውን አልተዋችሁምና.. አልኳቸው፡፡ ..አይ እስዎን መደበቅ ማለት እግዚአብሔርን መደበቅ ማለት ነው፡፡ ከቢቡኝ ህዝብ እኮ አንሰርቅም ከዳሞት ነው የምንሰርቀው.. አሉኝ፡፡ ..እንግዲህ ያ ህዝብ አይደለም? እነማናችው አብረዋችሁ ያሉ?.. ብዬ ስጠይቃቸው ነገሩኝ፡፡ . . . የተባሉትን ጠራሁና መከርኳቸው፡፡ ሌላው ደሞ በትምህርት ቤት ጎበዝ የሆነ ተማሪ ወደ ጦር ሜዳ አልክም፡፡ መምህር አላዘምትም ..ስብጥር አድርገው.. ስባል ..አልክም! ማን ያስተምር? ህዝቡ ይነሳብኛል.. እላቸዋለሁ፡፡ ሌባውን ነው መርጬ የምልከው፤ ..ሌባው ህዶ ሰልጥኖ ሞያ ቀስሞ ይመጣል.. ነው የምል፡፡ አንድዜ ደሞ የአንዱ የአውራጃ አስተዳዳሪ ከነበሩ አቶ መስፍን አበረ ጋር አንግባባም ነበር፡፡ ምክንያቱ ፖለቲካ ነው፡፡ ማልሬድ የተባለ የፖለቲካ ድርጅት አባል ነበሩ፡፡ እኔ ደግሞ አብዮታዊ ሰደድ ለተባለው ድርጅት አባል ነበርኩ፡፡ በምልመላ ተጣላነ፡፡ ታክቲክና ስትራቴጂ በመቀየስ የፖለቲካ ሥራውን አቀላጥፈው ነበርና በርካታ አባላቱን ወሰድኩበት፡፡ ኋላ ነደደዋ! ጠላኝ፡፡ ኋላ ምን ልበልሽ አጥረገረገኝ፡፡ ..ከሃምሳ ጦር በላይ ቢቡኝ አብሮህ ውሏል፡፡ ፖለቲካ ሰውን ሥራ እያስፈቱ እንደዚህ ማድረግ አይደለም፡፡ አንተ ያልተማርክ መሀይም... . . ስድብ በስድብ ተዚያ በቴሌግራም ጻፈለኝ፡፡ ሳየው ንዴቱ ገባኝ፡፡ ፖለቲካ ደግሞ ወንድማማች ያጋድላል እንኳን ስድብ፡፡ ኋላ. . . ማንነቱን ጠቅሼ ተንትኜ አሳየሁታ!! ምን ብለው? ስፍለት. . . ..አባቴ ፊታውራሪ አምባው ይባላል፡፡ ግራዝማች ናቸው፡፡ የርስዎ አባት ደሞ ደጃዝማች አበራ ይማም ይባላሉ፡፡ ሚያዚያ 30 ቀን 1942 ዓ.ም. ዳንግላ (ሸፍተው) ወረራ አካኸዱ፡፡ ዳንገላንም የወረሩበት ምክንያት ሹመት ቀረብኝ ብለው ነው፡፡ አባትዎ ሲሸፍቱ የእኔ አባት ፊታውራሪ አምባ በሽማግሌ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ወርጠዋቸው ..አቸፈርን በአውሮፕላን አታስደብድብ እጅህን ስጥ.. ብለው መክረዋቸው እጃቸውን ሰጡ፡፡ እጃቸውን ሲሰጡ ጃንሆይ አስረው አሰቃዩዋቸው፡፡ ፊውዳል እኔ አይደለሁም፤ እስዎ ነዎት፡፡ እሰዎስ ቢሆኑ የጃንሆይ መንግሥት እንዳይቀለበስ በፓርላማ ሲሟገቱ አልነበረ? እኔ የአንዱ ጉልት ገዢ ልጅ ነኝ፡፡ ደሞስ ማህይም ማለትዎ?! ማህይምስ እስዎ፡፡ በእጅ መፃፍ አቅቶዎት በታይፕ የሚጽፉ.. ብዬ ስልክባቸው ወከክ አሉያ፡፡ ብቻ እንዲያ እንዲያ ተብሎ ታረቅነ፡፡ በሥልጣን ዘመንዎ ያሰሯቸው ት/ቤቶች፣ ጤና ጣቢያዎች እስቲ ንገሩን? በተለያዩ አካባቢዎች የተለያየ ሥልጣን ነበረኝ፡፡ በአውራጃ አስተዳዳሪነት ብትይ በወረዳ አስተዳዳሪነት. . . ቢቡኝ አስር ት/ቤት አሰርቻለሁ፤ ከሕዝቡ ጋር ነው የምሠራው፡፡ ከመንግሥት የምፈልገው ቆርቆሮና ሚስማር ብቻ ነው፡፡ ጤና ጣቢያ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ አሰርቻለሁ፡፡ ቆንተር ስላሴ (ወይን ውሃ ከተማ ት/ቤት ጤና ጣቢያ) የሚባል አገር አለ፡፡ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት የጓድ ብርሃኑ ባየህ አገር ናት፡፡ እነሱ እንኳን በሄሊኮፕተር ወርደው አይተዋታል፡፡ አንደዜ ወባ ህዝቡን ፈጀው፡፡ ክሊኒክ ሠራን በዚያ ወቅት ወባ ጠፋች፡፡ በቢቡኝ ወረዳ ኮረብታ አማኑኤል ክሊኒክ ተሠርቷል፡፡ ጎማጣ (የጎልማሶች ማሰልጠኛ ጣቢያ) ገነባን፡፡ ሁለት እጁ አነሴሞ ሌላ ጎማጣ፣ አስራ አምስት ት/ቤቶች፣ አስራ አምስት የአገልግሎት የህብረት ሥራ ማህበራት አንደኛ ደረጃ ት/ቤት፤ የመንግሥታዊና የሕዝባዊ ድርጅቶች ቢሮ ስፖርት ሜዳ አሠራሁ፡፡ ቢቡኝ ዘጠኝ የህብረት ሥራ አገልግሎት ማህበራት፤ ሁለት የበግ ማርቢያ አዳራሾች፣ የደን ተከላ፣ ጎማጣ አሰርቻለሁ፡፡ እናርጅ እናውጋ ወደ ዘጠኝ የአገልግሎት የህብረት ሥራ ማህበር፤ አንድ የስፖርት ሜዳ አሰርቼ ..ኢትዮጵያ ትቅደም.. የተባለውን ውድድር፣ ሰባቱን አውራጃዎች 35 ወረዳዎችን አስተናግዷል፡፡ መብራት፣ ንፁህ የመጠጥ ውሃ፣ ጤና ጣቢያ፣ ደን፣ አስር ት/ቤት፣ ጤና ጣቢያ፣ ሦስት ክሊኒክ፤ ፈለገ ብርሃን የተባለ ቦታም አንድ ት/ቤት፣ አንድ ጤና ጣቢያ፣ ክሊኒክ አሰርቻለሁ፡፡ አቸፈር ውስጥ የህዝብ መድኃኒት ቤት፤ አምስት ት/ቤት፣ ሦስት ጤና ጣቢያ፣ መብራትና ውሃ፣ ደን ልማት ይህን ሁሉ ሠርቻለሁ፡፡ ትምህርትን በተመለከተ በኢትዮጵያ ከነበሩት ከአምስት መቶ ሰባ ስድስት ወረዳዎች ደብረ ወርቅ አንደኛ፣ ፈለገ ብርሃን ሁለተኛ ወጣ፡፡ ማቻከል በፀረ ስድስት ክትባት አንደኛ ወጥቶ ከጤና ጥበቃ ተሸልሟል፡፡ በደን አያያዝም ከግብርና ሚኒስትሩ ከዶ/ር ገረመው ደበሌ ተሸልመናል፡፡ በ13 ዓመት ጊዜ ይሄን ሠራን፡፡ በሠራነው ስቴዲየም ስፖርት ኮሚሽን 30ሺ ብር ሸልሞን በሥራ ብዛት ሳንወስደው ቀርተናል፡፡ ስቴዲየሙ ደረጃውን የጠበቀ ነበር? ምን ማለትሽ ነው? ራሴ እኮ ነኝ ቆሜ ያሰራሁት፡፡ ወረዳ አስተዳዳሪ ነበርኩ፡፡ ህዝቡን ሰብስቤ በጉልበትና በዶዘር አስተካከልኩት፡፡ ራሴ ነኝ ዶዘሩን እየነዳሁ መሬቱን እደለድል የነበረ፡፡ ጓድ ካሳዬ አራጋው መጥተው አዩንና ..በአጠቃላይ ከሁሉም ወረዳ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ በማህበራዊ እንቅስቃሴ ተወዳዳሪ የለህም.. ተባልኩ፡፡ /ሳቅ/ ስብሰባ ላይ ምን ይናገራል ብለው የተገላቢጦሽ የሚፈሩኝ እኔን ነው፡፡ ..ኮከብ ወረዳ አስተዳዳሪ!.. ተብዬ ነው አልኩሽ የተሸለምኩት፡፡ ብዙ ጊዜ ስለሚሸለሙ አንዳንድ ባለሥልጣናት እርስዎን የሚያኮስስ ነገር በአደባባይ ይናገሩ ነበር የሚባለው እውነት ነው? የነበረው መንግሥት ወዳጅም ጠላትም ነበረው፡፡ ጠላቶች በጦርነት አይደለም የሚያሸንፉ፡፡ ማዳከም፣ መቦርቦር፣ የሚወጣውን እቅድና ፕሮግራም አለመፈም፣ ማንኮላሸት ነበር ሞያቸው፡፡ ምን ሆነ መሰለሽ? . . . እናርጅ እናውጋ ወረዳ ውስጥ ነው፡፡ ብዙ ህዝብ ተሰብስቧል፡፡ የቅባት፣ የጥራጥሬ እህል አለ፡፡ እና ይህን የሚያነሳልን መኪና አጣን፡፡ ብጮህ ብጮህ የሚሰማኝ አጣሁ፡፡ ..የተሰበሰበውን እህል ምስጥና አይጥ እየበላው ስለሆነ ይታሰብበት.. የሚል መረጃ በጋዜጣ ላይ አስወጣሁ፡፡ ንግድ ሚኒስትሩ ሰው ልከው ሲያዩት ሌላ ሆኖ ተከምሮአል፡፡ ለጓድ ካሳዬ አራጋው ነገሯቸው፡፡ በአንድ በኩል ህዝቡ እየተራበ ነው፤ አዲስ አበባ ህዝቡ ምግብ አምጡልን እያለ ነው፡፡ ..ለምን አይነሳም.. ብዬ በጋዜጣ ሳወጣ ጠሉኝ. . . እዚያ ያለው የቀጠና ኃላፊ ..እንደዚህ አድርገህ ስም ታጠፋለህ.. አለኝ፡፡ ..እናንተ ናችሁ ፀረ ህዝብ.. አልኩት፡፡ ማቻከል ወረዳ ተዛውሬ እንደዚሁ በጋዜጣ አስወራሁ፡፡ የመንግሥት ማዕከላዊነት አልጠብቅም ሪፖርት አደርጋለሁ፡፡ ካሳዬ አራጋው ..እኔ ብሰማው.. አሉኝ፡፡ ..እስዎ ምን መኪና አለዎት.. አልኳቸው፡፡ ..ቢፈልጉ ያባሩኝ አርሼ መብላት የምችል ነኝ.. ስላቸው ..ስለሠራህ ለምን አባርርሃለሁ?.. አሉኝ፡፡ ..እንግዲያስ ለእኔ ለምን አትነግረኝም አይበሉኝ፡፡ ቢፈልጉ ይጥሉኝ በማስተዋወቂያ ክፍሉ እቀበቅባቸዋለሁ.. አልኳቸው፡፡ አንደዜ ደሞ የቤተ መንግሥቱ ጋዜጠኛ አሰፋ ሽበሸ ደውሎ ..ጓድ መንግሥቱ በጣም ይወዱሃል፡፡ ቆራጥ መሪ ነው የሚሉህ፡፡ አይዞህ በርታ፤ ሁሉ ሰው እንዳንተ ቆራጥ ቢሆን ነው የሚሉ ጋዜጣውን እያነበቡ.. አለኝ፡፡ እንዲያውም አንደዜ . .. ባህርዳር ቤዛዊት ቤተመንግስት ጓድ ሊቀመንበር አስጠሩኝና ..እስቲ ንገረኝ ህዝቡ ምንድን ነው የሚል?.. አሉኝ ..አይ . . . ህዝቡ መዋጮ በዝቶበታል፡፡ የልዩ መዋጮ ሃያ ብር፣ ግብር ሃያ ብር፣ በዛብን እያለ ነው፡፡ በርግጥ ህዝቡ እስዎን ይወድዎታል.. አልኳቸው፡፡ ..ሚኒስትሮችም ነገሩን አለባብሰው ምንም ችግር የለም ነው የሚሉዎት፡፡ መረጃ ቢያገኙ ጥሩ ነው.. አልኳቸው፡፡ ..እንደዚህ ደፍሮ የሚነግረኝ የለም.. አሉኝ ይሄን አልረሳውም፡፡ በሌላ ጊዜ ደሞ ጓድ ካሳዬ ሲነግሩኝ ፕሬዚዳንቱ ..ጓድ ቆምጬ ደህና ናቸው?.. ነው የሚሉ እንጂ ..ጐጃም ደህና ነው ወይ.. አይሉም አሉ፡፡ እሳቸውን የሚጠላ እኔን አይወደኝም፡፡ ሬዲዮና ጋዜጣ ላይ ስምዎት በየጊዜው ይጠቀስ ነበር የሚባለውስ? ቢቡኝ ወፍጮ የለም፡፡ ርዕሰ ከተማው ወፍጮ አያውቅም፡፡ ከህዝቡ ላይ 15ሺ ብር አወጣሁና ..እስኪ አንድ ወፍጮ ከተማው ላይ እናድርግ፡፡ ሴቶች፣ እርጉዞች፣ ደካሞች፣ እየለፉ ነው.. ብዬ ካስማማሁ በኋላ ወፍጮውን ከአዲስ አበባ የሚያመጣልኝ አጣሁ፡፡ በዚያን ሰዓት ችግሬን በሬዲዮ አስነግሬ ያንን 15ሺ ብር ባንክ አገባንና አንድ ግለሰብ ወፍጮውን ከአዲስ አበባ ገዝቶ አመጣልን፡፡ በኋላ ሬዲዮው ..ወፍጮ ተተከለ . . . ወፍጮውን መርቀው የከፈቱት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ጓድ ቆምጬ ናቸው.. ብሎ አወራ፡፡ ያኔ አርስዎ የት ነበሩ? /ሳቅ/ እዚያው ቢቡኝ፡፡ ኋላ . . . ምን አሉ መሰለሽ . . . ..ቆምጬ አምባው ከአዲስ አበባ ወደ ቢቡኝ በመኪና ሲመጣ ..ስማ አንተ ሹፌር አንደዜ አቁም.. ህዝቡን ደሞ አንደዜ ጫ በሉ እሻ. . . እሻ.. ብሎ ..ጓድ ቆምጫምባው ማለት እኔ ነኝ.. አለ አሉ፡፡ ኩራት፣ ትቢት፣ ጉበኛ፣ ምቀኛ፣ መዝባሪ አትሁኝ ብቻ፡፡ ህዝቡ ይወድሻል፡፡ አንድ ጊዜ እናርጅ እናውጋ ወረዳ ፈለገ ብርሃን ከተማ ክሊኒኩን ጓድ ቆምጬ አምባው መርቀው ከፈቱ ይልና እኔ በማላስተዳድርበት በቡሬ ሽኩዳድ መረቀ ብሎ ጋዜጠኛው ተሳስቶ አወራ፡፡ አስተዳዳሪው ለነጓድ ካሳዬ ስልክ ደወለና ..ይኼ እንዴት ይሆናል.. ብሎ አበደ፡፡ ..አይ! ጓድ ቆምጬ በሬድዮ ሁልጊዜ ይናገራል፤ የልማት ሰው ነው፤ እንግዲህ ጋዜጠኞች ይወዱታል እሱም ይወዳቸዋል፤ ጋዜጠኞች ተሳስተዋል ቆምጬን አንከስም.. ይሉታል፡፡ ባህርዳር ስብሰባ ላይ ስንገናኝ ..አምባገነን.. አለኝ፡፡ ..ዋ! አምባገነን የሚለውን ትርጉም እወቅ አንተ! እኔ እንደ አንተ ምስኪን አስተዳዳሪ ነኝ! የሚሰጠኝን መመሪያ፣ እቅድና ፕሮግራም አቀላጥፌ እሰራለሁ፡፡ ቆምጬ አምባው መረቀ አለና እኔ ምን ላድርግህ?.. አልሁት፡፡ በአንድ ወቅት ደግሞ ቢቡኝ ውስጥ የራሴን ቢሮ ወረዳውን አስተባብሬ አብሬ ጭቃ እያቦካሁ እመርጋለሁ፡፡ አያየኝም መስሎታል አንዱ ሌላውን ጐተት አድርጐ ..እህ! ይሄ ከማርቆስ የመጣው ውራጌ አስተዳዳሪ አይደለ . . ... ብሎ ሲያወራ ሰማሁ... ..አንተ በመጨረሻ ስትሄድ እኔን እንድታገኘኝ.. ብዬ አንዱን እንዲጠብቀው አዘዝሁበት፡፡ ..ስራ መሥራት ውራጌ ያስብላል አንተ? እኔ የተንጠራራሁ የአንዱ ፊታውራሪ ልጅ ነኝ፤ በል ወዲህ ና!.. አልኩና መቶ ጉድጓድ አስቆፈርሁት፡፡ በሌላ በኩል ደሞ እኔ በዛ አካባቢ ስሾም በኢህአፓም በሌብነትም ተይዞ እስር ላይ የነበረውን ሁሉ ጠራሁና እየጠየቅሁ ፈታሁ... ግን ያን ሳደርግ ቅ እያስሞላሁ ስለማንነቱ እንዲገል እየጠየቅሁ ነበር፡፡ ከዚያ ወደ ሁለት መቶ የሚሆን ኢህአፓ ቆምጬ ሊጨመድደኝ አይደል ብሎ እርሻውን እየተወ ሄደ፡፡ በኢህአፓ ጊዜ የገጠመዎት ችግር ነበር አሉ. . .? አዎ! ወረዳውን አልነግርሽም፡፡ ብቻ በዚያ አካባቢ የጠነጠነ አንድ ሽፍታ አለ፤ አንዱ ቤት ገባሁ፡፡ ከዚያ ነገሩ ደስ ስላላለኝ ወታደር ልኬ ሌላ ቤት እንዲዘጋጅልኝ አድርጌ ወደ ሌላ ቤት ተዛወርሁ፡፡ መጀመሪያ የነበርኩበትን ቤት ..ቆምጬ አምባው.. ብሎ ፎክሮ ያን ሳር ቤት በእሳት አጋየው፡፡ በኋላ ግን ሰነባብቶ ያው ሰውዬ ሌላ ቦታ ተይዞ ተቀጣ፡፡ አንድዜ ደሞ ሽፍቶቹ መከሩ እኔን ለመግደል...፡፡ በስብሰባው ላይ ከሽፍቶች ጋር አብሮ የዋለው ሰውዬ... ቢሮዬ መጥቶ ሰላም አለኝ፡፡ ..ላይህ ነው የመጣሁ እንዲያው ግን ደና ሰንብተሃል . . . ደህና ነህ ደህና ነህ?.. ሲለኝ ቆይቶ ..ስብሰባ ተደርጐ ሽፍቶች እንግደለው ብለው መክረዋል.. አለኝ፡፡ ሰማሁት፡፡ ሚኒሽር ጠበንጃ ሸለምኩት፡፡ እነዚያን የሽፍታ አለቆች ሁለቱን በሚኒሽር! አይላቸው መሰለሽ. . . (ሳቅ)፡፡ ገዳዩ እኔ ነኝ አላለኝም፤ ይሄን ያደረገው እስር ቤት ሳለ የሰራሁለትን ውለታ ቆጥሮ ኖሯል፡፡ ... ግን መጥቶ ..ተደመሰሱኮ.. አለኝ፤ ..እኔ ገደልኳቸው.. አላለኝም፡፡ እኔም አንስቼ 50 ጥይት ሰጠሁት፡፡ የየካቲት 66 የፖለቲካ ትምህርቱስ? እዛማ ስድስት ወር ነው የተማርኩ፡፡ ..ለምንድነው እኔ የማልማር? . . . አርሶ አደሮች እረዳለሁ፡፡ ሠራተኛ መደብ እረዳለሁ፤ ልማት ሠራሁኝ ምን ቸገራችሁ ት/ቤት ብትልኩኝ.. አልኩ፡፡ እላይ ድረስ ጮህኩ፡፡ እውነትም ለምን አይገባም? ይገባዋል ትምህርት . . . ተብዬ ገባሁ፡፡ የጎንደር፣ የወሎ፣ የጎጃም ሁሉ የትምህርት ቤቱ የልማት ኮሚቴ አስተባባሪ አደረጉኝ፡፡ ጄነራሉን ባለሥልጣኑን ሳይቀር አበባ መትከያ ጉድጓድ ጠዋት ጠዋት አስቆፍረዋለሁ፡፡ ዳይሬክተሩ ጋር ሂደው ..በቁፋሮ ፈጀን.. ብለው ተናገሩ፡፡ ..ይሄ ሪሰርች ነው.. ተባሉ፡፡ እኔ ቱታ ለብሼ ውሃ ነበር የማጠጣ፡፡ እነሱ ወርቃቸውን ሌዘራቸውን ለብሰው ይሸልላሉ፡፡ አቶ በጋሻው አታላይ ለእያንዳንዱ ካድሬ ሁለት ሁለት ኩንታል ቡና ለስንቅ ሰጥተዋቸው ነበር፡፡ እኔ ያችው ደሞዜ ናት፡፡ እና እነሱ ቢራቸውን ይጠጣሉ፡፡ ቆፍሩ ስላቸው መች ሚሰሙኝ ሆኑ. . . ደግሞ በትምርቱስ የዋዛ መሰልሁሽ? ሌት ተቀን አጠና ነበር፡፡ ትምህርቱ አይከብድም ነበር? ኧሯ አይከብድም! የሚታወቅ አይደል፡፡ በጣም ቀላል ነበር፡፡ የኢንፔሪያሊስቱና የሶሻሊስቱን ሁኔታ ነው፡፡ ይሄ ቄስ ትምህርት ረድቶኛል፡፡ በኋላ ምርቃቱ ላይ ለገሠ አስፋው መጡና ተህዝቡ ፊት ቆመው ..ጓድ ቆምጬ አምባው አንደኛ.. ብለው የኮምኒስቶች መጽሐፍት /የቼኮዝላቫኪያ፣ የሶቬት ሕብረት/ ሽልማት በሽልማት . . . አያረጉኝ መሰለሽ! ውጭ አገር ሄደዋል? ኧሯ! ማን ሰዶኝ፡፡ መቼም መላ አለው ብለው ችግር ባለበት እኮ ነው የሚልኩኝ! በኢህአዴግ ስርዓትስ? ... አቶ ታምራት ላይኔ ደሞ ምን አለኝ መሰለሽ? ..አቶ ቆምጬ ጥፋት የለብዎትም፡፡ የልማት ሰው ነዎት፡፡ ወደፊትም ልማት ይስሩ.. ብለው እስዎ ዲግሪ የለዎትም አዲስ አበባ በዲግሪና ዲፕሎማ ነው የምንመድብ፤ ቢሆንም እዚህ ይሁኑ ሲሉኝ እኔ አገሬ ጐጃም ናፍቆኛል ልሄድ አልኩቸው... በኢህአዴግ ታስሬ ስፈታ... እሰራበት ወደነበረው አካባቢ ስሜን ወስደው ህዝቡን ጠየቁት፤ ህዝቡ ጥሩ አስተያየት ሰጠልኝ፡፡ ..ኧረ እንዲያውም . . . አሁንም ይምጣልን . . . ይኼ ሁሉ ልማት የሱ ነው.. አሉ፡፡ አሁንም ተህዝቡ ጋር ነኝ፡፡ የቀይ መስቀል የቦርድ አባል እኮ ነኝ - በህዝብ ተመርጬ፡፡ እንዴት ከእስር ተፈቱ? የደርግ ባለስልጣናት በሙሉ ማህደራችን ተሰብስቦ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ተልኮ ነበር፡፡ ..በቃ ቀልጬ ቀረሁ.. አልኩኝ፡፡ የጠ/ሚ /ቤት ብዙ ብሄራዊና አለማቀፋዊ ስራ አለበት... የእኔ የአንድ ተራ ሰው ጉዳይ ልብ ተብሎ አይታይም ብዬ አስቤ ነበር፡፡ 3 ዓመት ከ7 ወር ታስሬ ተፈትቻለሁ፡፡ ጉዳዩን እንዲያዩልኝ ስጠይቅ ለረጅም ጊዜ ሲያደርጉብኝ ጊዜ እንዴት አልኩና የጡረታዬን ጉዳይ ልጠይቅ የማህበራዊ ዋስትና ሃላፊውን ሳናግር ..አቶ ቆምጬ እንኳን እግዚአብሄር አስፈታዎት... ይቀመጡ... በሉ ወተት ሻይ.. ሲለኝ ፆም ነበር ..አይ ይቅርብኝ.. ስለው... ..ምነው ያን ጊዜ ሳይበሉ ኑረው ነው?.. አለኝ... ..ኧረ እኔስ በልቻለሁ.. አልኩ፡፡ ተሳሳቅን፡፡ ጉዳዩን እንዲያዩልኝ ስል... ወዲያው ተፎ ተሰጠኝ፡፡ ..ወደፊት ምን ይሰራሉ?.. ሲሉኝ ..እርሻ . . ሹመኞች ሁሉ ሞጣዎች ናቸው፡፡ ያውቁኛል.. አልኳቸው፡፡ ..አያሳርስዎትም.. አሉኝ፡፡ ..ዋ!ምን ብለው? ምን በሰራሁ... ? አልኳቸው፡፡ ..መጓጓዣ ገንዘብ ልስጥዎት?.. አሉኝ... ..ጐጃም ሞልቶ የል ባዲሳባ? አልኳቸው፡፡ ሦስት መቶ ብር... እምቢ ብለው ሰጡኝ፡፡ አሁን በምን ሙያ እየተተዳዳሩ ነው? አሁን በጡረታ ስገለል ..ነገረ ፈጅ ነበርኩ የጥብቅና ፈቃድ ስጡኝ.. አልኳቸው፡፡ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት. . . የጥብቅና ፈቃድ ሰጠኝ፡፡ መቼም ለጡረታ መደጐሚያ ይበቃል፡፡ ጎጃምማ ..እሱም ወንድ፣ እኔም ወንድ፣ ከማን አንሼ ነው ጠበቃ ምገዛ?.. ይላል፡፡ ለጥብቅና ሥራ ሸጋ አዲስ አበባ ነው፡፡ የኛ ሰው ነገር አዋቂ ነኝ ብሎ ጠበቃ ማቆም ዝቅተኛነት ይመስለዋል፡፡ እና እንዳልሁሽ እርቅ ሥሠራ ነው የምውለው፡፡ በአኩሪው ባህላችን መሠረት ስናስታርቅ ነው የምውል፡፡ አሁን በእድር በማህበራዊም ሆነ በተለያየ የማህበራት አስተባባሪና መሪ ነኝ፡፡ በኢህአዴግስ አልተሸለሙም? ምክትል ጠ/ሚ አዲሱ ለገሠ ..የመልካም አስተዳደር የሰላምና የዲሞክራሲ እድሮችን በመምራት ባደረጉት አስተዋጽኦ ተሸላሚ.. የተባለ ጊዜ አግኝተውኝ ..አቶ ቆምጬ፣ ከሦስት መንግሥት የሚበሉ፤ በሃይለ ሥላሴ፣ በደርግ፣ በኢህአዴግም . . ... አሉ፡፡ እኔስ ምኔ ሞኝ!. . . ..ሁሉም እኮ የኢትዮጵያ ተወላጅ ናቸው፡፡ መንግሥት ይለወጣል፣ አገር ነው የማይለወጥ.. አልኳቸው፡፡ ሳቁ፡፡ ..ሰምቻለሁ ሥራዎትን፡፡ ጥሩ ነው፡፡ ሰውን አስተምሩት፡፡ ሽማግሌ ነዎት፡፡ ትልቅ ሰው ነዎት፡፡ ይለፋሉ፡፡ አይዞዎት.. አሉኝ፡፡ እንዲሁ አንደዜ የደ/ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ሲመረቅ ንግግር እንዳደርግ ተጋብዤ ተናገርኩ፡፡ ..ብሔር ብሔረሰቦች የሚተዋወቁበት ኮሌጅ ተሰራልነ፡፡ የሠራችሁልን መማሪያ ቤት የኛ ነው፡፡ ቧንቧው መስኮቱ እንዳይሰበር እንጠብቃለን፡፡ ከሌላ አገር የመጣ ደባል ፀባይ ካለ እኛ ጎጃሞች አንፈልግም፤ ጉሮሮውን አንቀን ለፍርድ እናቀርባለን.. አልኳቸው፡፡ በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ስላለው የፖለቲካ ሁኔታ ምን ይላሉ? ኢትዮጵያ ውስጥ የማያባራ ጦርነት ነበር፡፡ ያኔ ፕሬዚዳንቱን ..ሥልጣን አጋሩ፤ ተደራደሩ.. ብያቸው ነበር ግን ..ድርድር የለም.. ብለው እምብኝ አሉ ፕሬዚዳንቱ፡፡ የሚገርምሽ በደርግ ወቅት ጦሩ እንዳይዋጋ የሚቀሰቅስ ሙዚቃ ነበር፡፡ ..አሁን የእኔ መኖር፤ መኖሩ ነው ወይ፤ ጉች ጉች ያለ ጡት አንድ ቀን ሳላይ.. የሚል ቅስቀሳ ወጣቱ ይሰማ ነበር፡፡ ጦር ሜዳ? እህሳ፡፡ በጦር ሜዳ ቅስቀሳ ሲደረግበት ወጣቱ በቃ እዚያ መቆየት አይፈልግም፡፡ በቃ እየተወ መምጣት ጀመረ፡፡ ሽንፈቱ አየለ፡፡ ሌላው ጦርነቱ ደግሞ የአንድ አገር ጦርነት ነበረ፡፡ ያው አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት አሸንፏል፡፡ ነገር ግን ያንዜ የነበረው ጦርነት ታሪካዊ ተብሎ አይያዝም፡፡ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ የተቃመሱ፡፡ የእርስ በርስ ጦርነት ስለሆነ፡፡ ታሪካዊ ጦርነት የምትይው ከኤርትራ፣ ከሱማሌ፣ ከጣልያን፣ ቱርኮች፣ ግብፆች፣ እንግሊዞች ጋር የነበረው ጦርነት ማለት ነው፡፡ አንድ ጦርነት ታሪካዊ የሚባለው ጦርነት በሚያውቁ ሳይንቲስቶች፣ የጦር ጠበብቶች ሲገመገም ነው፡፡ አሁን ያለው ለሰላም ለዲሞክራሲ፣ ለመልካም አስተዳደር የቆመ አስተዳደር ነው ቢባልም ከላይ የወጣው መመሪያ ትክክል ሆኖ ሳለ ከታች ግን ይሸራረፋል፡፡ ከታች ያየሽ እንደሆን መመሪያዎች፣ ህገ መንግሥቱ፣ ሌሎች ነገሮች እየተሸራረፉ ይገኛሉ፡፡ ተቆጣጥሮ ለማስተካከል ጥብቅ ክትትል ያስፈልጋል፡፡ በኢህአዴግ ዘመን በምርጫ ለምን አልተወዳደሩም? አይ!. . . መንግሥታት በሥልጣናቸው የሚመጣባቸው አይወዱም፡፡ እኔም ደሞ ከእንግዲህ የአገር ሽማግሌ ነኝ፡፡ ተመርጠሽ ፓርላማ በምትገቢበት ጊዜ ቢያንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ሊኖርሽ ይገባል፡፡ ለነገሩ ለተሳትፎም መማር ጥሩ ነው፡፡ ግን ትምህርቱን ለምን እስከ ዲግሪ አልገፉበትም? እህ እንግዲያ! እኔ በተልዕኮ በህግ የጥብቅና ዲፕሎማ ይዣለሁ፡፡ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊን አግኝተዋቸው ያውቃሉ? ኧረ የለም፡፡ ጠ/ሚኒስትሩን የማመሰግናቸው የኢትዮጵያና የኤርትራን ጦርነት በአሸናፊነት በመወጣታቸው ነው፡፡ የቀድሞ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ በሚያስተዳድሩ ጊዜ የሶማሌ ጦር ..አዋሽ ነው ድንበሬ.. ብሎ መጥቶ ነበረ፡፡ ለወሬ ነጋሪ ሳይቀር እንደ አገዳ ክምር ተቃጠሏ! ጠ/ሚ መለስም ቢሆኑ ጦርነት ባይፈልጉም ጦረኞችን ለመከላከል የሚያደርጉት የሚደንቅ ነው፡፡ ይህም ደግሞ አፄ ቴዎድሮስ፣ አፄ ዮሐንስ ህይወታቸውን የሰውት ንብረት ጠፍቷቸው ንብረት ፍለጋ ሳይሆን ሀገር ለመጠበቅ ነው፡፡ ያው በእኔ በኩል ጠ/ሚኒስትሩን ባገኛቸው ግን ጎጃም ውስጥ እነ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ ደራሲ ዮፍታሔ ንጉሴ፣ ደራሲ ዶ/ር ሃዲስ አለማየሁ፣ የቅኔው ባለቤት በአለም የታወቀው አድማሱ ጀምበሬ. . . የተወለዱበት አገር ደብረ ኤልያስ ይባላል፡፡ በደብረ ኤልያስ ..አባይ ፍል ውሃ.. 44 ዓይነት ምንጭ ውሃ የሚፈልቅባት ናት - ለብለብ፣ ሙቀት፣ እሳት አለንጋ፡፡ ታዲያ ሰው ለመፈወስ በበረሃው እየሄደ በውሃ ጥም እስከ 300 ሰዎች ሞተዋል፡፡ በጫካ ገብተው መንገዱ ጠፍቷቸው፡፡ እና ጠ/ሚኒስትሩ እግዚአብሔር ከዚያ ሁሉ ሽምቅ ውጊያ፤ አሁንም ቢሆን አንዳንድ ከፍተኛ መሰናክሎች አጋጥሟቸው የተወጡት በእግዚአብሔር ሃይል ስለሆነ . . . የእነዚህን ታላላቅ ሰዎች አገር ..አባይ ፍልውሃን.. ባለችዎት አቅም በእግዚአብሔር ብየዋለሁ ያሰሩልን፡፡ ..አባይ ፍልውሃ.. መንገዱ ቢሠራ ከፍተኛ የእምነበረድ ክምችት፣ ከፍተኛ የብረት ምርት፤ የቅባትና የሰሊጥ እንዲሁም፣ የበርበሬ ምርት በብዛት ያለበት ነው፡፡ ከደ/ኤልያስ አባይ ፍል ውሃ 17 ኪ.ሜ ርቀት ነው ያለ፡፡ እና እባክዎ ይሄንን ያሰሩልን . . . በፃድቃን በሰማዕታት በደናግል በመነኮሳት . . . ይዠዋለሁ፡፡ በመጨረሻ ምን ይላሉ? መልካም ዘመን ለኢትዮጵያ ሕዝብ፡፡ ከአዲስ አበባ ድረስ ደ/ማርቆስ በመምጣት ቃሌን ተቀብላችሁ በጋዜጣችሁ ስላስተላለፋችሁ አዲስ አድማሶችን አመሰግናለሁ፡፡ ይህ ቃለ-ምልልስ በሁለት ክፍሎች በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ታትሟል፡፡ ቃለ-ምልልሱን ያገኘነው በጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው መልካም ፈቃድ ነው፡፡ እናመሰግናለን፡፡ የኢትዮጵያ ሰዎች
18583
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8D%B3%E1%8D%BB%E1%8D%AB%20%E1%8B%93.%E1%88%9D.%20%E1%8B%A8%E1%88%8A%E1%89%A2%E1%8B%AB%20%E1%88%95%E1%8B%9D%E1%89%A3%E1%8B%8A%20%E1%8A%A0%E1%89%A5%E1%8B%AE%E1%89%B5
የ፳፻፫ ዓ.ም. የሊቢያ ሕዝባዊ አብዮት
የ፳፻፫ ዓ.ም. የሊቢያ ሕዝባዊ አብዮት በሊቢያ ውስጥ የተከሰተ እና በሰሜን አፍሪቃ በተከታታይ ከተደረጉ የተለያዩ ሀገራት ፀረ መንግስታዊ አብዮቶች አንዱ ነው። ይህ አብዮት የተጀመረው በእ.አ.አ. 15 ፌብሩዋሪ 2011 ሲሆን በዚሁ ወር መጨረሻ አካባቢ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ተባብሶ ታይቷል። አብዮቱ በዋናነት የኮለኔል ሞአመር ጋዳፊን የ42 ዓመታት የስልጣን ላይ ቆይታ በመቃወም ነው። ፀረ መንግስታዊ አገዛዙን በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰቱ አብዮቶች ጋር እንዲያያዝ የሚያደርገው ዋናው ነገር በቱኒዚያ እና ግብፅ የተደረጉ ሕዝባዊ አብዮቶች ተከትሎ መደረጉ ነው። የኋላ ታሪክ ሞአማር ጋዳፊ ቀድሞ የነበረውን አሃዳዊ አገዛዝ በመገርሰስ የስልጣን መንበሩን የተቆናጠጠው እ.አ.አ. በ1969 ነበር። የኡመር ቦንጎን በእ.አ.አ. 2009 መሞት እና የፊደል ካስትሮን በእ.አ.አ. 2008 ከስልጣን መውረድ ተከትሎ የሊቢያው ሞአማር ጋዳፊ በህይወት የሚገኝ እና ለረዥም ጊዜ ሥልጣን ላይ የቆየ ኢ-ንጉሳዊ መሪ ነው። የህትመት ነፃነት ሥርዓት እንደ የህትመት ነፃነት ማውጫ መሰረት ሊቢያ በህትመት ነፃነት በኩል ከመካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪካ በከፍተኛ ሁኔታ የከበደ ቁጥጥር የሚደረግባት ሀገር ናት። በአብዛኸኛው የሀገሪቱ ፍርድ ከውጭ ሀገር ዜጋ ጋር ስለፖለቲካ ጉዳዮች መነጋገር እስከ ሶስት ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ሲያስጥል ቆይቷል። ጋዳፊ በሀገሪቱ ውስጥ የውጭ ቋንቋዎች እንዲጠፉ አድርጓል። ከነዚህም እ.አ.አ. 1986 ከአሜሪካ እና እንግሊዝ ጋር ዲፕሎማሲያዊ እንዲሁም ሌሎች ግንኙነቶች ሲቋረጡ እንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት እንዳይሰጥ ከልክሎ ነበር። ቅድመ አነሳስ አቡ ሳሊም ፕሪሰን የተባለው የሊቢያ ከፍተኛ የጠበቃ ባለስልጣን በሀገሪቱ ለተደረጉ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተጠያቂ መሆን አንዱ ለአብዮቱ መነሳት እንደዋነኛ ምክንያትነት ይጠቀሳል። ይህ ግለሰብ በከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በአለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ለ1,270 ያህል እስረኞች መገደል እንደዋነኛ ተኘያቂ ነው። የክስተቶች ቅደምተከተል ከፌብሩዋሪ 15-21 ፌብሩዋሪ 15 ቀን መጀመሪያ ወደ 200 የሚጠጉ ሰልፈኞች የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ የሆነውን የፋትሂ ተርቢልን መታሰር በመቃወም በተለያዩ የቤንጋዚ ፖሊስ ጣቢያዎች ፊት አደረጉ። በኋላም ከ500 እስከ 600 የሚጠጉ ሌሎች ሰልፈኞች ጋር በመቀላቀል ተቃውሞ ሲያደርጉ ፖሊስ ሰልፉን ለመበተን ባደረገው ጥረት ከሰልፈኞቹ መካከል 40 የሚሆኑት ጉዳት ደረሰባቸው። ከፌብሩዋሪ 22-28 የየዓይን እማኞች ፌብሩዋሪ 22 ጋዳፊ ከአሜሪካ ወደ ሀገሪቱ በአውሮፕላን ቅጥር ነብሰ-ገዳዮችን አስመጥቷል ሲሉ ተናገሩ። ጋዳፊም ለብጥብጡ መነሳት የውጭ መንግስታትን እና የውጭ ሃይሎችን ተጠያቂ እንደሆኑ በዚህም ተቃውሞ ሰልፈኞቹ እንዲወጡ መገደዳቸውን በዚሁ እለት አስታወቁ። ከማርች 1-4 በማርች አንድ የአውስትራልያው መከላከያ ሚኒስትር የጋዳፊ መንግስት በፍቃደኝነት ስልጣኑን እንደማይለቅ በማስገንዘብ የኃይል አማራጭ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል። ከማርች 5-8 በማርች 5 ቀን ከጋዳፊ ሃይሎች ጋር በተደረገ ከባድ ውጊያ ራስ ላኑፍየተባለችዋን የሀገሪቱን ከተማ በተቃዋሚ ሃይሎች እጅ ስር ማስገባት ተችሏል። የጋዳፊ ሃይሎች ሁኔታ እንደ የጋዳፊ ከተማ ሲርት ባሉ ከተሞች የሚኖሩ ሰዎች በጥሩ የኑሮ ደረጃ ያሉ እና ለአገዛዙ ታማኞች ናቸው። ከእንደዚህ ያሉ ከተሞች ሃይሎችን ማስወጣት ለተቃዋሚ ሃይሎች ፈተና ሁኗል። ሞት እና አካል ጉዳት በገለልተኛነት እስካሁን የሞቱትን እና የተጎዱትን በትክክል ለማወቅ አልተቻለም። ሆኖም አንዳንድ ምንጮች 1000 አካባቢ ሰዎች እንደሞቱ በመዘገብ አቋርጠዋል። እንደ የአለም የሰብዓዊ መብት ፌዴሬሽን መረጃ ደግሞ ከ3000 የማያንሱ ሰዎች እንደሞቱ ተዘግቧል። ነገር ግን የተቃዋሚ ኃይሎች ይህን አሃዝ በማጣጣል የሟቾች ቁጥር ከ6500 በላይ እንደሆኑ አስታውቀዋል። የተጎጅዎችንም ብዛት የሚገልፅም ቢሆን ይህ ነው የሚባል ታማኝ መረጃ የለም። የግብፅ ሕዝባዊ አብዮት የቱኒዚያ ሕዝባዊ አብዮት የመካከለኛው ምስራቅ አብዮቶች
15324
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8D%8B%E1%88%B2%E1%88%8D%20%E1%8C%8D%E1%89%A2
ፋሲል ግቢ
ፋሲል ግቢ ወይንም ነገሥታት ግቢ በጎንደር ከተማ የሚገኝ የቤተመንግስታት ግምቦች ስብስብ ነው። ግቢው የተመሰረተው በ1628ዓ.ም. በዓፄ ፋሲለደስ ነበር። ማቀባበያ የሚሰኘው የግቢው አጥር 900ሜትር ርዝመት ሲኖረው በውስጡ 70፣000 ስኩየር ሜትር የመሬት ይዞታ ያካልላል። አጼ ፋሲለደስ የመጀመሪያውንና ታላቁን ግንብ ያሰሩ እንጂ፣ ከርሳቸው በኋላ የተነሱት ነገሥታትም ለ220 ዓመታት የየራሳቸውን ህንጻ በመስራት ቦታው በቅርስ እንዲዳብር አድርገዋል። በግቢው የመጨረሻውን ህንጻ ያሰራችው ንግሥት ብርሃን ሞገስ ነበርች። ግቢው ገናና በነበረበት ዘመን በሽወች የሚቆጠሩ ቤቶችና ሱቆችን በውስጡ ያቅፍ ነበር። በጥንቱ ዘመን የአስተዳደር ስርዓት ተቀርጾለት በጥንቃቄ የሚመራ ነበር። ስርዓቱም ስርዓተ መንግስት በመባል ሲታወቅ በመጽሃፍ መልኩ በግዕዝና በድሮው አማርኛ የተመዘገበ ነበር። የግቢው ይዘት ፋሲል ግቢ፣ የውሃ እጥረት እንዳይገጥመው በማሰብ በአንገርብ እና ቃሃ በተሰኙ ሁለት ምንጮች መካከል ነበር የተመሰረተው። ከግቢው በስተደቡብ የጎንደር አደባባይ ሲገኝ፣ ቦታው ለገበያነት፣ ለአዋጅ መንገሪያነት እና ለወንጀለኛ መቅጫነት ያገለግል ነበር ። በአሁኑ ወቅት የጎንደር ከተማ መናፈሻ በመሆነ ያገልግላል። ማቀባበያ የሚሰኘው የግቢው አጥር ግምብ በዙሪያው 12 በሮች ሲኖሩት፣ እኒህ በሮች ግልጋሎታቸውን የሚወክሉ ስያሜ ነበሯቸው። አንዳንዶቹ በሮች ከውጨኛው አለም ጋር ይገናኙ የነበሩት በትላልቅ ድልድዮች ነበር። ምንም እንኳ አብዛኞቹ የግቢው ቤቶች በጦርነትና እሳት ቢወድሙም ዋና ዋናዎቹ ህንጻዎች ግን እስከ አሁኑ ዘመን ዘልቀው ይታያሉ። ከነዚህ ጉልህ ህንጻዎች መካከል የፋሲለደስ ግምብ፣ ትንሹ የፋሲል ግምብ፣ የታላቁ እያሱ ግምብ፣ የዳዊት ፫ ዙፋን ቤት፣ ምንትዋብ ግምብ፣ የየምንትዋብ ቱርክ መዋኛ፣ የፈረሶች ቤት፣ የፈረሰኞች አለቃ ቤት፣ አንበሶች ቤት፣ የበካፋ ግምብ፣ የበካፋ ሰገነት፣ የቀዳማዊ ዮሐንስ ጽሕፈት ቤት፣ ዮሐንስ ቤተ መጻሕፍት፣ አዋጅ መንገሪያን፣ ክረምት ቤት፣ ቋል ቤት(የሰርግ ቤት) እና ግምጃ ቤት ማርያም፣ አጣጣሚ ሚካኤል የሚሰኙ አብያተ ክርስቲያናት የግኙበታል። በተጨማሪ ከፋሲል ግቢ ወጣ ብሎ በስተሰሜን ራስ ግምብ ይገኛል። ትንሹ የፋሲል ግምብ ትንሹ የፋሲል ግምብ ሌሎች ህንጻዎች ከመገንባታቸው በፊት ለሙከራ ያክል የተገነባ የፋሲል ግቢ የመጀመሪያው አንስተኛ ህንጻ ነው። ዋናው የፋሲል ግምብ እስኪገነባ ድረስ ዓፄ ፋሲለደስ ተቀምጠዉበት የነበር ህንጻ ነው። የፋሲል ግቢን ዙሪያ ጥምጥም የያዘው የግምብ አጥር ማቀባበያ በመባል ይታወቃል። ስሙ ከጥንት ጀምሮ የነበር ሲሆን በዓፄ በዕደማርያም ዜና መዋዕልም መቀባበያ የሚባል ህንጻ ተጠቅሶ ይገኛል። ትርጎሜውም መዘጋጃ፣ ወይም መከላከያ ምሽግ መሆኑ ነው። በዚህ የግምብ አጥር ዙሪያ 12 በሮችና ከፍ ብለው የተሰሩ መተላለፊያ ድልድዮች ይገኛሉ። የፋሲል ግቢ እንደሐዋርያት ብዛት 12 በሮች አሉት፣ 12ቱም እንደየተግባራቸው ስም ወጥቶላቸው ያገልግሉ ነበር። ልዕልት እንኳየ በር፣ በንግሥት ብርሃን ሞገስ እናት ስም የተሰየመ ነበር። ግምጃ ማርያም በር ወደ ግምጃ ቤት ማርያም ቤተክርስቲያን ግቢ የሚያሻግር ሲሆን ጃን ተከል በር(ፊት በር) የሚባለው ዋናው በር ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የጎብኚዎች መግቢያ ነው፡፡ ከአደባባይ ፊት ለፊት ይገኛል። ወምበር በር (የዳኞች በር) የፍርድ መስጫ በር ሆኖ ዳኞች የሚገቡበትም ነው ፣ ተዝካር በር በድሮ ጊዜ ድልድይ የነበረው፣ ሆኖም ግን በዳግማዊ ኢያሱ ጊዜ በተነሳ ጦርነት የፈረሰበት በር ነው።የቀብርና የሙታን ሥርዓት ለማስፈጸም የሚገባበት ነው። አዛዥ ጥቁር በር በድሮ ጊዜ ከአደባባይ ተክለ ሃይማኖት ጋር በድልድይ ይገናኝ ነበር፡፡ አደናግር በር እንዲሁ በድሮ ጊዜ ቅዱስ ሩፋኤል ተብሎ ከሚታወቀው የሸማኔዎች ሰፈር ቤተክርስቲያን ጋር በድልድይ ይገናኝ ነበር።የፈትል ባለሙያዎች የሚገቡበት ነበር። ቋሊ በር ከእልፍኝ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ዘመናዊ መግቢያ አጠገብ የሚገኝ ሲሆን ስሙ የወጣው የንግሥት ደንገጡሮች በር መሆኑን ለመግለጽ ነበር። እምቢልታ በር የአዝማሪዎች በር ሲሆን እልፍኝ በር ወደ የግቢው የግል ህንጻዎች የሚወስድ ነበር። ባልደራስ በር እሚያመለክተው የፈረሰኞች አለቃ በር መሆኑን ሲሆን፣ ራስ በር በሌላ ስሙ ቋረኞች በር ተብሎ ይታወቅ ነበር። እርግብ በር ደግሞ ቀጭን አሸዋ በር በመባል በሁለተኛ ስም ይታወቅ ነበር– ለነገሥታት እጅ መንሻ የሚገባበት በር ነው።። ፋሲል ግምብ ፋሲል ግምብ ፋሲል ግቢ ውስጥ ካሉት ግምቦች ትልቁና የመጀመሪያው ዋና ህንጻ ነው። ቤተመንግሥቱ 32 ሜትር ቁመት እና 25 ሜትር በ25 ሜትር የሆነ የጎንና ጎን ርዝመት አለው። ባለ ሦስት ፎቅ ሕንፃ ሲሆን 123 ደረጃዎች አሉት።አጼ ፋሲለደስ የአገሪቱ መዲናን ከቦታ ቦታ መዛወር በመሰልቸት በመጨረሻ ጎንደር ከተማ ላይ የረጋ ማዕከል በ1628ዓ.ም. አቋቋሙ። በ1640ወቹ መጀመሪያ ፋሲል ግምብን በከተማው ማዕከል አሰርተው አስጨረሱ። ከጣሪያው ላይ ባለው መመልከቻ በረንዳ እስከ ጣና ሐይቅ ድረስ መመልከት ይቻላል። በውስጡ 20 ክፍሎች አሉት። ግድግዳው ላይ የተሰሩ ብዙ ጌጦች የነበሩት ሲሆን እንደ ጣሊያናዊው አመዶ የ1930 ጥናት የማግኔት ኮምፓስ ወደ ግድግዳዊ ሲጠጋ ኮምፓሱ በሃይል ዘውሮ ወደ 80 ዲግሪ እንደሚጠጋ ይጠቃሳል። ከዚህ ተነስቶ ግድግዳው ከማግኔታይት ባዛልት እንደተሰራ ይዘግባል (ገጽ 26)። የየመኑ አምባሳደር ሃሰን ኢብን አል-ሃያሚ ይህን ግምብ በ1640ዓ.ም. ተመልክቶ «ድንቅ ህንጻ፣ ውብ የሆነ የድንጋይና ኖራ ውጤት» በማለት እንደሚገልጸው ታሪክ አጥኝው ስቱዋርት ሞንሮ-ሄይ ዘግቦት ይገኛል። ከቤተ መንግሥቱ ጫፍ ላይ የንጉሡ- የአፄ ፋሲል የቅኝት ማማ ይገኛል። በሦስተኛው ፎቅ ላይ የንጉሡ መኝታ ክፍል አለ። በሁለተኛው ፎቅ ላይ ደግሞ ፊት ለፊት የአክሊል ቅርጽ ያለው በረንዳ ይገኛል። ይህ በረንዳ የንጉሡ አዋጅ መንገሪያ፤ ሕግና ትእዛዛት ማሳወቂያ ነው። አንደኛው ፎቅ በረንዳ ላይ እንደየማዕረጋቸው የሚቀመጡ ሹማምንትና አፈ- ቀላጤዎች ከንጉሡ አንደበት ተቀብለው በተዋረድ አዋጁን ያሰማሉ። እንዲህ እያለም- ነጋሪት እየተጎሰመ፣ እምቢልታ እየተነፋ፣ ከበሮ እየተደለቀ አዋጁ ከሕዝቡ ጆሮ ይደርሳል። በቤተ መንግሥቱ አራቱም ማዕዘናት የክብ ቅርጽ ያላቸው እና ላቅ ብለው የሚታዩ ግምቦች አሉ። እነዚህም አራቱን ወንጌላውያን- ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስን ወክለው የተገነቡ ናቸው። የማዕዘን ግንቦቹ እያንዳንዳቸው ሦስት ሦስት መስኮቶች አላቸው ( በአንደኛ ፎቅ ላይ አንድ፣ በሁለተኛ ፎቅ ላይ አንድ፣ በሦስተኛ ፎቅ ላይ አንድ መስኮት ማለት ነው) የመስኮቶቹ ብዛትም 12 ሲሆን፤ ሐዋሪያትን ይወክላል። ወደ አንደኛ ፎቅ ለመውጣት 32 ደረጃዎች አሉ። ደረጃዎቹም አፄ ፋሲል በ17ኛው ክፍለ ዘመን በ32ኛው ዓመት (በ1632 ዓ.ም) በትረ-ንግሥና መጨበጣቸውን ያጠይቃል። በአንደኛው ፎቅ የእንግዳ መቀበያ ክፍልን ጨምሮ የሴትና የወንድ ማዕድ ቤቶች፣ በወርሃ ክረምት የእሳት መሞቂያ፣ ንጉሱ ከእንግዶች ጋር የሚነጋገሩበት ክፍል እና መፀዳጃ ቤቶች ይገኛሉ። ክፍሎቹ በዚያን ዘመን በተሰሩና ውበታቸው ባልጠወለገ ጠንካራ የእንጨት በሮች የተከፋፈሉ ናቸው። የቤተ መንግሥቱ መግቢያ በርም እንዲሁ ከግዙፍ ጣውላ የተሠራ ሁለት ተካፋች በር ነው። ቤተ መንግሥቱ ከጥቁር እና ከቀይ ጥርብ ድንጋዮች የተሰራ ነው። ግድግዳው ለዓመታት በሚቦካ ኖራ የተለሰነና የተጣበቀ ሲሆን እስከ አንድ ሜትር ተኩል ውፍረት አለው። ይህ የኖራ ማጣበቂያ በየጊዜው እየጠነከረ የሚሄድ እንጅ የሚላላ አይደለም። ከቤተ መንግሥቱ ጀርባ ከግንቡ ጋር ተያይዘው የተገነቡ ሌሎችም ቅርሶች አሉ። የመታጠቢያ ቤቶች፣ የእስረኞች ማቆያ፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ገንዳ ይጠቀሳሉ። ግን አብዛኞቹ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጉዳት ደርሶባቸዋል። የፋሲል ገንዳ ከፋሲል ግምብ አጠገብ ውሃ የነበረበት ገንዳ ይገኛል። ይሄ ገንዳ በጊዜው ለዋና እና ዓሣ ለማርቢያነት ያገለግል ነበር። ፋሲለደስ ዓሣ ተመጋቢ እንደነበር ይዘገባል (ገጽ 27)። ታላቁ እያሱ ግምብ ታላቁ እያሱ ግምብ (አድያም ሰገድ ግምብ)፣ በንጉሱ ታላቁ እያሱ ዘመን ተገንብቶ በ1677 (ዘመነ ማቲዎስ) የተጠናቀቀ ነበር። የአናጢዎች መሪ ወልደ ጊዮርጊስ ግምቡን የሰራው ሲሆን በጊዜው ከጠቢቡ ሰለሞን ቤት የብለጠ ያምር ነበር በመባል የተደነቀ ነበር። የግምቡ ጣሪያ በወርቅና በከበሩ ደንጊያወች ያጌጠ ነበር። ግድግዳዎቹ ከዝሆን ጥርስና ከቅጠላቅጥል ጌጦች የተሰራ ነበር። ግምቡ በ2ኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ በእንግሊዝ የአውሮፕላን ቦምብ ድብድባ የተጎዳ ቢሆም አብዛኛው ክፍሉ ግን አሁን ድረስ ሳይፈርስ ይገኛል። ዮሐንስ ቤተመጻሕፍት ዮሐንስ ቤተመጻሕፍት በፋሲልደስ ልጅ በቀዳማዊ አጼ ዮሐንስ የተገነባ ቤተ መጻሕፍት ሲሆን በፋሲል ግቢ ይገኛል። አማዶ በ1930 ብዙ ጌጣጌጥ እንደነበረውና ውጭውም ጥሩ መልክ ባለው፣ ከኑግ ዘይት በተሰራ ቢጫ ፕላስተር የተለጠፈ እንደነበር ይዘግባል። በዚሁ ወቅት የዚህ ህንጻ ሁለት ጎኖች የመፍረስ አደጋ ገጥሟቸው እንደነበርም ጽፎት ይገኛል (ገጽ 27)። አንድ ፎቅ ያለው ይሄ ህንጻ ምድር ቤቱ 3 ሰፋፊ ክፍሎች አሉት ። ከነዚህ ውስጥ አንዱ ክፍል ከሁሉ የሚሰፋ የነበር ሲሆን ይህን ክፍል ከሁለት የሚከፍል ቅስት ነበረው። በተረፈ የፎቁ ክፍል ከሁለት የተከፈለ የነበር ሲሆን፣ ወደ ፎቁ የሚያወጣው ደረጃ ከቤተመጻህፍቱ በስተ ውጭ(ገጽ 27)። ዮሐንስ ጽሕፈት ቤት ዮሐንስ ጽሕፈት ቤት በፋሲልደስ ልጅ በቀዳማዊ አጼ ዮሐንስ የተገነባ በፋሲል ግቢ የሚገኝ ያስገነባው ንጉስ ጽህፈት ቤት የነበር ነው። እንደቤተመጻሕፍቱ ሁሉ፣ ይሄም ህንጻ አንድ ፎቅ አለው። የምድሩ ክፍል እንግዶችን ለመቀበልና ሌሎች ህዝባዊ በዓላትን ለማክበር ይጠቅም ነበር። ፎቅ ቤቱ በአንጻሩ እንደ መዝገብ ቤት ሲያገለግል የግብር እና የፍርድ ቤት መዝገቦችን ይይዝ ነበር (ገጽ 28)። ትንሽ አንስተኛ በር ወደ አንስተኛ ሰገነት መወጣጫ ደረጃ ስታመራ፣ ሌላ ሰፊ በር ደግሞ ወደ ውጭ ያመራል። የፈረሰኞች አለቃ ቤት የፈረሰኞች አለቃ ቤት በፋሲል ግቢ ዋና በር ጎንና ጎን ያሉ ባለ አንድ ፎቅ ግንቦች ናቸው። እኒህ ፎቆች ከሌሎቹ ህንጻዎች ለየት ባለ መልኩ ሳይፈርሱ ብዙ ዘመን አሳልፈዋል። ጣሊያናዊው አሌሳንድሮ ኮርቴ በ1930 ጥናቱን ሲያካሂድ በእኒህ ህንጻዎች የአጣጣሚ ሚካኤል ቄስ ይኖሩ እንደነበር ሳይዘግብ አላለፈም (ገጽ 38)። ወደ ላይ የሚያወጣ የውጭ ደረጃ አለው። አጣጣሚ ሚካኤል አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ፋሲል ግቢ ውስጥ በስተ ሰሜን ምስራቅ ክፍል ሲገኝ፣ ሰኔ ፲፪ ቀን ፲፯፻፰ ዓመተ ምሕረት ተመርቆ የተከፈተ ቤተ ክርስቲያን ነው። ወደቤተክርስቲያኑ የሚገባው በእልፍኝ በር አድርጎ ነው። በዓፄ ዳዊት ዘመን ይተገነባው ይሄ ቤተክርስቲያን የአራት ማዕዘን ቅርጽ የነበረውና መልካም ውድርን የተከተለ ነበር። ሁለት ሰገነቶች የነበሩት ሲሆን አንዱ ግን ወድቋል። ውስጡ ከ3 ክፍሎች ነበሩት (ገጽ 38)። የአጣጣሚ ሚካኤል ቄሶች በአለቃ ገነት ማዕረግ እስካሁን ይታወቃሉ። በካፋ ግምብ በካፋ ግምብ ፋሲል ግቢ ውስጥ የሚገኝ በአጼ በካፋ የታነጸ ነው። ግምቡ በግቢው በስተሰሜን በኩል ሲገኝ፣ ከፈረሶች ቤት ጋር የተያያዘ ነው። ይህ የዓፄ በካፋ ቤተ መንግሥት ነው። በ '' ቅርጽ የተሠራ ሲሆን 30 ሜትር ርዝመትም አለው። መሲህ ሰገድ በካፋ በፋሲል አምባ ያኖሩት ቅርስ ለግቢው አምስተኛው ቤተ መንግሥት ነው፡፡ በጣም ረዥም ሲሆን ከሁሉም የአምባው አብያተ መንግሥታት የተለየ ቅርጽ አለው። በዚህ ህንጻ በስተግራ በኩል ረዥም ግድግዳ ይታያል። በስተቀኝ ደግሞ ዋናው የቤተመንግሥቱ ክፍል አለ። ብቻውን የቆመው ግድግዳውና ዋናው ቤተ መንግሥት በ30 ሜትር ርዝመት ላይ ይገናኛሉ። ከመግቢያው ጀምሮ ግድግዳዎቹ እስከሚገናኙበት ድረስ ያለው ክፍተት እየጠበበ ሄዶ የ'' ቅርጽ ይኖረዋል። ብቻውን በቆመው ግድግዳና በዋናው የቤተ መንግሥቱ ግድግዳ መካከል የ'' ቅርጽ ያለው ክፍት ቦታ አለ። ይህ ክፍት ቦታም ጣሪያ የሌለውና በልምላሜ የተሸፈነ ነው። በዘመኑ የነበሩ መኳንንትና የፈረሰኛ አዛዦች እንደየማዕረጋቸው ፈረሶቻቸውን የሚያቆሙት- በዚሁ ክፍት ቦታ ላይ ነበር። የቤተ መንግሥቱ በርና መስኮቶች እስካሁን ያሉ ጣውላዎች ናቸው፣ ከሁለት ተከፋች ናቸው። የቤተ መንግስቱ እልፍኝ ከጫፍ እስከ ጫፍ የተዘረጋ ነው። እስከ 300 ሰዎችንም የማስተናገድ አቅም አለው። አምበሶች ቤት አምበሶች ቤት በአጼ ሳልሳዊ ዳዊት የተሰራ በፋሲል ግቢ የሚገኝ አንበሶች ይኖሩበት የነበር ነው። እስከ 1984 ዓ.ም. አምበሶች ይኖሩበት የነበር ሲሆን በዚሁ አመት የመጨረሻው አንበሳ በሞት አለፈ። ምንትዋብ መታጠቢያ የምንትዋብ መዋኛ ወይም የምንትዋብ መታጠቢያበእቴጌ ምንትዋብ የተሰራ በፋሲል ግቢ ውስጥ ከምንትዋብ ግምብ አጠገብ የሚገኝ ቱርክ መታጠቢያ (ሐማም) ነበር። ስለሆነም ከህንጻው ስር ምድጃ ሲኖር፣ ውሃ በቱቦ ይገባለትና እንፋሎት እያተነነ የተለያዩ የሚሸቱ ቅጠሎች በላዩ ላይ እየተደረጉ ለህመም ፈውስ የሚገኝበት ክፍል ነበር። በዚህ መታጠቢያ ቤት የመጀመሪያው ክፍል እራቁትን ሆኖ ሰውነትን ለማሞቅ የሚያገለግል ሲሆን፣ ሁለተኛ የበለጠ ሰውነትን በማጋል ላብ የሚያስወጣ ነበር። ከዚህ ቀጥሎ በቅዝቃዛ ውሃ መታጠቢያ ክፍል ውስጥ መታጠብ ሂደቱን ያጠናቅቃል። ምንትዋብ ግምብ ምንትዋብ ግምብ ወይንም አልፎ አልፎ ትንሹ ኢያሱ ግምብ በእቴጌ ምንትዋብ የተሰራ ሲሆን በፋሲል ግቢ ይገኛል። ዳዊት ፫ ዙፋን ቤት የዳዊት ፫ኛ ዙፋን ቤት በቀዳማዊ እያሱ ልጅ በዳዊት ፫ኛ የተሰራ ነበር። የቀዳማዊ ዮሐንስ ግንቦች ከተገነቡ ከ15 ዓመታት በኋላ መሆኑ ነው። የዙፋን ቤቱ በግቢው በስተሰሜን በበበካፋ ግምብ እና በአጣጣሜ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን መካከል ይገኛል። ይህ ሕንጻ በእርግጥ ቤተ መንግሥት ሳይሆን በዘመኑ የሚደረጉ ጉባኤዎች፣ ክብረ በዓላት የመዝሙርና የዝማሬ መርሐ ግብሮች፣ የሹመትና የሽረት ስነ ሥርዓቶች፣ የኪ ጥበብና የባሕል መዝናኛ ዝግጅቶችም የሚካሔዱት አዳራሽ ነው። ይህ አዳራሽ ሰፊና ጣሪያ አልባ ነው። አጼ ዳዊት ሦስተኛ አዳራሹን ሲያስገነቡት ለመዝሙርና ለዝማሜ አገልግሎት ይውል ዘንድ አስበው ነበር። ጣሪያ አልባ አድርገው ማሠራታቸው ዘማሪያን ሲያመሰግኑ ወደ ሰማይ ሲያንጋጥጡ -ሲመለከቱ የሚከልላቸው ጣሪያ እንዳይኖር ነው የሚሉ አሉ። የአጼ ዳዊት መዝሙር ቤት በአብዛኛው በዓመታዊ የንግሥና ክብረ በዓላት፣ በዓውደ በዓላትና በሌሎችም ጊዜያት ዝማሬና ዝማሜ ይቀርብበት ነበር። ንጉሱም ፊት ለፊት ከሚገኘው ባለፎቅ መድረክ ላይ ሆነው ይህንኑ መንፈሳዊ ሥርዓት ይታደማሉ። የአቋቋም የቅኔና ሌሎች ሊቃውንት በንጉሱ እና በታዳሚው ፊት ሆነው በያሬዳዊው ዝማሬና ዝማሜ ይሳተፋሉ። አጼ ዳዊት መዝሙር ቤቱን ያስገነቡት በዋናነት ለመንፈሳዊው ዝማሬና ዝማሜ የነበረ ቢሆንም ቅሉ አዳራሹ ለሌሎችም ግልጋሎቶች ይውል እንደነበር፤ ከእነዚህ አገልግሎቶቹ ውስጥ ደግሞ አንዱ የሙዚቃ እና የሌሎችም ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶችን ማቅረቢያነትም ነበር። ኋላ መንፈሳውያኑ ዘማርያን እና ዓለማውያኑ ሙዚቀኞች ሊጣጣሙ ስላልቻሉ አዳራሹ ለሁለት እኩል እንደተከፈለ ይጠቀሳል። እንደሚወጣላቸው መርሐ ግብር መንፈሳውያኑ በቀኝ ሙዚቀኞቹም በግራ የአዳራሹ ክፍል ኪናቸውን ማቅረብ ጀመሩ። በእንግሊዝ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች የተመታው ይኸው አዳራሽ የተወሰነው ግድግዳው ፈርሷል። መንፈሳዊውን ከዓለማዊው ሙዚቃ የሚለየው የመካከል ግድግዳ ፈርሷል። ፋሲል ግቢ ቀዳማዊ ዓፄ ዮሐንስ የኢትዮጵያ ታሪክ
52580
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%89%A2%E1%88%B2%E1%8A%92%E1%8B%AB%20%E1%8B%B5%E1%88%98%E1%89%B5
አቢሲኒያ ድመት
የአቢሲኒያ ድመት የድመት ዝርያ ነው ፡፡ በአካላዊ ገጽታ እና በባህሪው ምክንያት ተወዳጅ ዝርያ ነው። በእረፍትም ሆነ በእንቅስቃሴ ላይ ይህ እንስሳ በእንቅስቃሴዎቹ ውስጥ ትልቅ ውበት እና ስምምነት ያሳያል ፡፡ እሱ ወዳጃዊ ፣ ግን ጠንካራ የቤት እንስሳ ፣ በጣም ተጫዋች ነው። ዘሩ የተሰየመው የቀድሞው የኢትዮጵያ ግዛት ስም በነበረው “አቢሲኒያ” ነው. ሌላው የብዙዎቹ የአቢሲኒያ ባህሪዎች ቡችላ ባህሪቸውን በከፍተኛ ደረጃ መያዛቸው ነው ፣ ይህ ማለት ብዙ ፍልስጤሞች እያደጉ ሲሄዱ በባህሪያቸው ውስጥ የበለጠ ብስለት እና የጎልማሳነት ዝንባሌን የሚያሳዩ ቢሆኑም አቢሲኒያውያንም ለመናገር ይዳረጋሉ ፡ በእሱ ስብዕና ውስጥ. እሱ በአካል እና በስሜታዊነት ያድጋል ነገር ግን እሱ ማራኪ ቡችላ እያለ ያሳየውን ተንኮል እና የጨዋታ ባህሪ በጭራሽ አያጣም። አቢሲኒያን ሁል ጊዜ በፍላጎት የሚነዳ እና ማንኛውንም ጨዋታ ለመጫወት ዝግጁ ሆኖ የሚሰማው ዕድሜው ብቻ ነው እናም ሁል ጊዜም ከልቡ እንደ ወጣት ይቆጥረዋል ፡፡ ከሌሎች ድመቶች ጋር ሲወዳደር ረዥም ፣ ዘንበል ያለ እና ጥሩ ቀለም ያለው የዝርያው ልዩ ገጽታ ከሰው ፋሽን ሞዴሎች ጋር ተመሳስሏል ፡ ስብእና ያላቸው ፣ ድመቶች በባህላዊ ንቁ እና የማወቅ ጉጉት ያላቸው ባህሪያትን ያሳያሉ ፣ እነሱም ደጋግመው ባለቤቶቻቸውን የሚከታተሉ እና ጨዋታን የሚያበረታቱ ሲሆን እንደ “የድመት መንግሥት ቅጥረኞች” ይቆጠራሉ ፡ ተጫዋች መሆናቸው ይታወቃል ፡ የእነሱ ውሻ መሰል ባህሪዎችም የተወሰነ የፍቅር ስሜት እና የመግባባት ፍላጎት ያካትታሉ። የስሙ እንደሚያመለክተው አቢሲኒያውያን የቀደሙት የኢትዮጵያ ኢምፓየር ስም ከሆነው አቢሲኒያ ነው።አቢሲኒያ ድመት ዛሬ እንደሚታወቀው በታላቋ ብሪታንያ ታርዳ ነበር ፡፡ በአስራ ዘጠነኛው ክፍለዘመን ወደ ሰሜን አፍሪካ የተሰማሩት የእንግሊዝ ወታደሮች ከአከባቢው ነጋዴዎች የተገዙትን ድመት ይዘው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ ተብሏል ፡ አቢሲኒያውያን ቀጭን ፣ ጥሩ አጥንት ያላቸው ፣ መካከለኛ መጠን ያለው ድመት ናቸው ፡፡ ጭንቅላቱ በመጠነኛ የሽብልቅ ቅርጽ ያለው ፣ በምስሉ ላይ ትንሽ ብልሽት ያለው ሲሆን ፣ አፍንጫ እና አገጭም በመገለጫ ሲታዩ ቀጥ ያለ ቀጥ ያለ መስመር ይፈጥራሉ ፡፡ እነሱ ንቁ ፣ በአንጻራዊነት ትላልቅ ሹል ጆሮዎች አሏቸው ፡፡ ዓይኖቹ የአልሞንድ ቅርፅ ያላቸው እና በአለባበሱ ቀለም ላይ በመመርኮዝ ወርቅ ፣ አረንጓዴ ፣ ሀዘል ወይም ናስ ናቸው ፡፡ እግሮች ከፀጋው አካል ጋር ተመጣጣኝ ረዘም ያለ አዝማሚያ ይኖራቸዋል ፣ በትንሽ ሞላላ ጥፍሮች; ጅራቱም እንዲሁ ረጅምና ታፔር ነው ፡፡ ካፖርት እና ቀለሞች የአቢሲኒያ ድመቶች የተወለዱት በጨለማ ካፖርት ሲሆን ቀስ በቀስ እየበሰለ ሲሄድ አብዛኛውን ጊዜ ከብዙ ወራት በላይ ነው ፡፡ የአዋቂው ካፖርት ከመጠን በላይ አጭር መሆን የለበትም ፣ እና በጥሩ ሁኔታ ጥሩ ፣ ጥቅጥቅ ያለ እና ቅርብ-ውሸት ፣ ለመንካት ለስላሳ ነው። ምንም እንኳን የአከርካሪ እና የጅራት ፣ የኋላ እግሮች ጀርባ እና የእግሮቻቸው ንጣፎች ሁል ጊዜ ቢሆኑም የዝርያዎቹ የንግድ ምልክት የሆነው የቲክ ወይም የአቱቲ ውጤት በሰውነቱ ላይ ተመሳሳይ መሆን አለበት ፡ ይበልጥ ጨለማ። እያንዳንዱ ፀጉር ወደ ጫፉ እየጠቆረ የሚጨምር ተጨማሪ ቀለም ያላቸው ሦስት ወይም አራት ባንዶች ያሉት ቀለል ያለ መሠረት አለው ፡፡ የመሠረቱ ቀለም በተቻለ መጠን ግልጽ መሆን አለበት; ከግራጫ ጋር ማንኛውንም ሰፊ መጠላለፍ እንደ ከባድ ስህተት ይቆጠራል ፡፡ በአገጭ ላይ ነጭ የመሆን ዝንባሌ የተለመደ ነው ግን በተመሳሳይ መልኩ ዝቅተኛ መሆን አለበት ፡፡ የተለመደው የታብያ ኤም ቅርጽ ያለው ምልክት ብዙውን ጊዜ በግንባሩ ላይ ይገኛል ፡፡ የዘርው የመጀመሪያ ቀለም መስፈርት በአውስትራሊያ ውስጥ በዩናይትድ ኪንግደም ታውኒ ውስጥ “የተለመደ” በመባል የሚታወቅ እና በሌላ ቦታ ደግሞ “ሩዲ” ተብሎ የሚጠራ ጥቁር መዥገር ያለው ሞቃታማ ጥልቅ ቀይ ቡናማ ቀለም ያለው መሠረት ነው ፡፡ ከቸኮሌት ቡናማ መዥገር ጋር ቀለል ያለ የመዳብ መሠረት የሆነው ሶርል (ቀረፋም ወይም ቀይም ይባላል) የዚህ የመጀመሪያ ዘይቤ ልዩ ሚውቴሽን ነው። ሌሎች ተለዋጮች ወደ በርማ እና ሌሎች አጫጭር ዘሮች በተለይም ሰማያዊ (በሞቃት የቢች መሠረት ላይ) እና ፋውንዴሽን (ለስላሳ ለስላሳ የፒች መሠረት) በማስተዋወቅ አስተዋውቀዋል ፡ ዩናይትድ ኪንግደም በተጨማሪ ለብር አቢሲኒያን እውቅና ታደርጋለች ፣ በዚህ መሠረት የመሠረቱ ካፖርት ጥቁር (“የተለመደ ብር” ተብሎ ይጠራል) ፣ ሰማያዊ ፣ ክሬም ወይም የሶረል መዥገር ያለ ንፁህ የብር ነጭ ነው ፡፡ የተለያዩ ሌሎች የቀለም ድብልቅ የሆነ የተጠቀመም ውስጥ የ "" ጨምሮ, ልማት ውስጥ ናቸው የኤሊ ድመት እነዚህ ቀለማት በማናቸውም መንገድ የመጠቀሙ ታቢ በብረትና ስር የሚታይ ነው. ዘሩ ልዩ መለያቸውን ኮ በመባል በሚታወቀው አውራ ዘራፊ ዕዳ አለባቸው ፡፡ መላው ጂኖ የታተመችው የመጀመሪያዋ ድመት ቀረፋ የምትባል አቢሲኒያ ናት ፡፡ አቢሲኒያውያን ባልተለመደ የማሰብ ችሎታቸው እና በአጠቃላይ በተዘዋዋሪ ፣ በጨዋታ ፣ በፈቃደኝነት ስብእናቸው በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ የዝርያዎች ምስጋና ናቸው ፡፡ ያለማቋረጥ እንቅስቃሴ እና የባለቤቶቻቸው ትኩረት ሳይጨነቁ ይነገራል ፡፡ የአቢሲኒያ እና የበርማ ድመቶች “ውሻ የመሰሉ አባሪዎች ” የእንስሳት ሐኪሙ ጆአን ኦ ጆሹ እንደፃፈው “በሰው ግንኙነት ላይ የበለጠ ጥገኛ” ነው ፡ ይህ በርካታ ሌሎች ዘሮች ከሚያሳዩት “ምቾት” ጋር ከተመሠረተው “የሰዎች ኩባንያ ታጋሽነት ተቀባይነት” ጋር ሲነፃፀር ተቃራኒ ነው ፡፡ አቢሲኒያውያን ከባለቤቶቻቸው ጋር ለመጫወት ካላቸው ፍላጎት ጋር የማወቅ ጉጉት ካላቸው የማሰብ ችሎታ ጋር ተደምረው “የድመት መንግሥት ክላውንስ” በመባል ይታወቃሉ ፡፡ እነሱ ንቁ ፣ ተግባቢ ተፈጥሮ አላቸው ፣ ግን ፀጥ ያሉ ድመቶች ናቸው ፡፡ እንደሚጠበቀው “መዎ” የማይመስል ለስላሳ የቺርፕ መሰል ድምፆች አላቸው። እነሱ ለሰዎች ፍቅር እና ወዳጃዊ ናቸው ፡፡ ዘሩ ለድድ በሽታ የተጋለጠ ሊሆን ይችላል ፣ ይህ ደግሞ በጣም ከባድ ወደሆነ የያስከትላል ፡ በአአ አሚሎይድ የፕሮቲን ዘረ-መል (ጅን) ውስጥ በሚከሰት ለውጥ ምክንያት የኩላሊት መታወክ የቤተሰብ የኩላሊት አሚሎይዶስ ወይም አሚሎይዶስ በአቢሲኒያ ውስጥ ታይቷል ፡ አቢሲኒያውያኑጂን ውስጥ በሚውቴሽን ምክንያት በዘር የሚተላለፍ ሬቲና መበላሸት በሚያስከትለው ዓይነ ስውርነት ላይ ከባድ ችግሮች አጋጥመውታል ፡፡ ሆኖም በስዊድን ሀገር በ ስርጭቱ ከነበረበት 45% ወደ 4% በታች ሆኗል ፡፡ እንደ ዩሲ ዴቪስ የእንሰሳት ጄኔቲክስ ላቦራቶሪ የሚሰጡት እንደ ሚውቴሽን ርመሪያ ምርመራዎች እና አገልግሎቶች በስፋት በመገኘታቸው በሁሉም የአቢሲኒያ ህዝብ ውስጥ የበሽታውን ድሞሽ መቀነስ ይቻላል ፡፡ የዘረመል ልዩነት እ.ኤ.አ. በ ር ሌሴ ሊዮን በተመራው ቡድን በዩሲ ዴቪስ የተካሄደው አቢሲኒያውያን የዘረመል ብዝሃነት ዝቅተኛ ደረጃ ያለው ፣ ለሁሉም ጥናት የተደረጉ ዘሮች በሙሉ ከ 0.34-0.69 ባለው ክልል ውስጥ 0.45 የሆነ የሂትሮይዚጎሴቲዝም እሴት እንዳለውና የጄኔቲክ ጠቋሚዎችም አሉት ፡፡ የደቡብ ምሥራቅ እስያም ሆነ የምዕራባውያን ዝርያዎች የእስያም ሆነ የአውሮፓ ድመቶች ዝርያውን ለመፍጠር እንደዋሉ ያመለክታሉ ፡፡ ተዛማጅ ዝርያ የሶማሊያ ድመቶች እንደ አቢሲንያውያን ተመሳሳይ የዘር ውርስ ናቸው ነገር ግን ለረጅም ፀጉር ኃላፊነት ላለው ጂን ሪሴስ ናቸው ፡ ኦሴሎትድመቶች አቢሲኒያ ድመቶች እና መካከል በአጋጣሚ በማዳቀል ከ ስለ መጣ የተዳቀሉ. የድመት ዝርያዎች ዝርዝር ድመት ቡችላ ውጫዊ አገናኞች
37092
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%B3%E1%89%A6%E1%88%AD%20%E1%89%B0%E1%88%AB%E1%88%AB
የታቦር ተራራ
ደብረ ታቦር እስራኤል ውስጥ የሚገኝ ተራራ ሲሆን በአዲስ ኪዳን ታሪክ መሰረት ሕዋርያት ጴጥሮስ፣ ዮሐንስና ያዕቆብ እያዩ የኢየሱስ ክርስቶስ መልክ እንደጸሐይ ያበራበት ቦታ እንዲሁም ሙሴንና ኤልያስን በተዓምር ከሙታን አንስቶ ያሳያቸውበት ቦታ (ማቴ ፤ማርቆስ ፤ ሉቃ ነው ተብሎ ይታመናል። ስለሆነም ለደብረ ታቦር (ዓመት በዓል) መሰረት የሆነ ቦታ ነው። ኢትዮጵያም ውስጥ ደብረ ታቦር (ከተማ) የተሰየመው በከተማው ሰሜን የሚገኘው ተራራ የዚህን ኮረብታ ቅርጽ ስለያዘ ነው። ደብረ ታቦር እስራኤል በመጽሐፈ መሳፍንት 4 መሠረት የምድያምን ውድቀት የነበየችው ነቢይት ዲቦራ በምድያም ሃያላት ያሸነፈችባቸው አምባ ነበረ። ስሙም ከዲቦራ አምባ ሊሆን ይችላል። በኋላም በነጌዴዎን ዘመን ያሕል በፈርዖኑ 2 ራመሠስ መዝገቦች ወደ ሶርያ ለዘመቻ ሲሄድ ሥራዊቱ «ደብረ ዳፑር» አምባን እንደ ከበበ ሲገልጽ፣ በአንዳንድ አስተሣሰብ ይሄ ማለት የደብረ ታቦር አምባ ሳይሆን አይቀርም። ሥርወ ቃል የዕብራይስጡ ስም፣ ታቦር፣ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ “እምብርብር” ከሚለው ስም ጋር ተቆራኝቷል፣ ታብቡር፣ ይህ ግን ምናልባት በታዋቂው ሥርወ-ቃል ምክንያት ነው። "በሴፕቱጀንት ኤርምያስ ምዕራፍ 26፣ ኢታቢሪየም () የሚለው ስም ለደብረ ታቦር ጥቅም ላይ ውሏል። ጆሴፈስ ከጥቂት መቶ ዓመታት በኋላ ተመሳሳይ ቃል ተጠቅሟል።" ከኢየሱስ መገለጥ ጋር ካለው ግንኙነት፣ ተራራው በታቦር ብርሃን በክርስቲያናዊ ሥነ-መለኮት ፣ በታቦራውያን የቦሔሚያ ክፍል እና የበርካታ ሰፈሮች እና ተቋማት ስም ሆነ። የስሙ አረብኛ ቅፅ ጀብል ታቦር ጃባል አቲ-ታቡር ወይም ጀብል አልጦር ጃባል አ ነው። የመሬት አቀማመጥ የታቦር ተራራ ልክ እንደ ግማሽ ሉል ቅርጽ ያለው ነው ፣ በድንገት ከጠፍጣፋው አከባቢ ተነስቶ 575 ሜትር (1,886 ጫማ) ከፍታ ላይ ደርሷል ፣ ስለሆነም በጥሩ 450 ሜትሮች በታች ባለው ሜዳ ላይ ያለችውን ከተማ ክፋር ታወርን ተቆጣጠረ። ከተራራው ጫፍ ላይ ሁለት የክርስቲያን ገዳማት ይገኛሉ አንድ የግሪክ ኦርቶዶክስ በሰሜን ምስራቅ እና አንድ የሮማ ካቶሊክ በደቡብ ምስራቅ በኩል. ከላይ ያለው የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከሩቅ በቀላሉ ይታያል. ተራራው ሞናድኖክ ነው፡ ገለል ያለ ኮረብታ ወይም ትንሽ ተራራ በቀስታ ከተዳፋት ወይም ከዙሪያው ከፍታ በድንገት የሚወጣ ሲሆን እሳተ ገሞራም አይደለም። ለናዝሬት ተራሮች ቅርበት ቢኖረውም የተለየ የጂኦሎጂካል ቅርፅ ይይዛል። ከሥሩ ከሞላ ጎደል በዳቡሪያ፣ ሺብሊ እና ኡሙ አል-ጋናም የአረብ መንደሮች የተከበበ ነው። የታቦር ተራራ ከሀይዌይ 65 ወጣ ብሎ የሚገኝ ሲሆን ጫፉም በሺብሊ በኩል በመንገድ ይገኛል። የእግረኛ መንገድ የሚጀምረው ከቤዱዊን መንደር ሺብሊ ሲሆን አምስት ኪሎ ሜትር ያህል ይረዝማል። የእስራኤል ብሔራዊ መንገድ አካል ነው። ተራራው ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰው በዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ፣ በኢያሱ 19፡22፣ የሶስት ነገድ ድንበር ሆኖ ዛብሎን፣ ይሳኮር እና ንፍታሌም ነው። የተራራው ጠቀሜታ ከኢይዝራኤል ሸለቆ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ሀይዌይ ያለው የገሊላ ሰሜን-ደቡብ መንገድ መገናኛ ላይ ካለው ስትራቴጂካዊ ቁጥጥር ነው። በመጽሐፈ መሳፍንት መሠረት አሶር የከነዓን ንጉሥ የያቢን መቀመጫ ነበረች፤ አዛዡ ሲሣራ በእስራኤላውያን ላይ የከነዓናውያንን ጦር እየመራ ነበር። ዲቦራ የተባለች አይሁዳዊት ነቢይት የንፍታሌም ወገን የሆነውን ባርቅን ጠርታ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ሰጠችው፡- “ሂድ ወደ ተራራ ታቦርም ቅረብ ከንፍታሌምም ልጆች ከዛብሎንም ልጆች አሥር ሺህ ሰዎች ከአንተ ጋር ውሰድ” (መሳ. 4፡6)። . እስራኤላውያን ከተራራው ሲወርዱ ሲሣራንና ከነዓናውያንን ወረሩ። በሁለተኛው ቤተ መቅደስ ዘመን (በ516 ዓክልበ. - 70 ዓ.ም.) የደብረ ታቦር ተራራ በሰሜናዊ የአይሁድ የተቀደሱ ቀናት እና አጀማመሩን ለማሳወቅ መብራቶችን ማብራት ከተለመዱት የተራራ ጫፎች አንዱ ነበር። ደብረ ታቦር
9571
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%85%E1%88%8A%E1%8A%93%20%E1%8A%90%E1%8D%83%E1%8A%90%E1%89%B5
የኅሊና ነፃነት
የኅሊና ነፃነት ማለት ማንኛውም ግለሠብ ምንምን ሀሣብ፣ እምነት ወይም አስተያየት በጽናት ለመያዝ የሚረጋገጥበት ነጻነት ነው። የሌላ ሰዎች እምነት ምንም ቢሆንም፣ ይህ ነጻነት ለየግለሠቡ ጽኑእ ሆኖ ይቆጠራል። የኅሊና ነጻነት ለሰዎች ለመከልከል ቢሞከር ኖሮ ይህ የሰው ልጆች መሠረታዊ መብት (ሰው ለራሱ ለማሰብ) እንደ መከልከል ይቆጠራል። የኅሊና ነጻነት ፍሬ ነገር እያንዳንዱ ግለሠብ ለራሱ የቱን እምነት ለመምረጥ ስለሚሰጥ፣ 'የሃይማኖት ነጻነት' ጽንሰ ሐሳብ ከዚህ ጋር ተያይዟል። በአንዳንድ ህብረተሠብ ወይም መንግሥት በተግባር የሃይማኖት ነጻነት ወይም የእምነት ነጻነት ባይከበርም፣ በሌሎች ህብረተሠብ ወይም ሕገ መንግሥታት ግን በተለይ በምእራቡ አለም ይህ ነጻነት በታሪክ እጅግ ተከብሯል። ለምሳሌ በአሜሪካ ሕገ መንግሥት 1ኛ ማሻሻያ አንቀጽ መሠረት ሃይማኖት ወይም ንግግር የሚከለክል ሕግ እንደማይጸና ይረጋገጣል። ዛሬ በአለም ዙሪያ ደግሞ አብዛኛው ሕገ መንግሥታት የእምነት ነጻነት የሚያረጋግጡ ናቸው። በ1948 ዓ.ም. በኢትዮጵያ የወጣ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 40 አባባል እንዲህ ነው፦ «የሕዝቡን መልካም ጠባይ ወይም ፀጥታን ወይም በፖለቲካ ረገድ የሚያውክ ካልሆነ በቀር በንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ግዛት የሚኖሩ ሰዎች በሕግ መሠረት የሃይማኖታቸውን ሥርዓት አክብረው በነፃ ከመፈጸም አይከለከሉም።» «የሰብዓዊ መብት አቀፋዊ መግለጽ» አንቀጽ ፲፰ ደግሞ እንደሚለው፣ «እያንዳንዱ ሰው፡ የሃሳብ የሕሊናና የሃይማኖት ነጻነት መብት አለው። ይህም መብት ሃይማኖቱን ወይም እምነቱን የመለወጥ ነጻነትንና ብቻውን ወይም ከሌሎች ጋር በኀብረት በይፋ ወይም በግል ሆኖ ሃይማኖቱን ወይም እምነቱን የማስተማር፣ በተግባር የመግለጽ የማምለክና የማክበር ነጻነትን ይጨምራል።» እንዲሁም በአንቀጽ ፲፱ ዘንድ፣ «እያንዳንዱ ሰው የሐሳብና ሐሳቡን የመግለጽ መብት አለው። ይህም መብት ያለጣልቃ ገብነት በሐሳብ የመጽናትንና ዜናን ወይም ሐሳቦችን ያላንዳች የድንበር ገደብ የማግኘትን የመቀበልን ወይም የማካፈልን ነጻነትም ይጨምራል።» የኅሊና ነጻነት ስለ መከልከል አንድ ተራ ሰው ልጅ ሌሎቹ ሁሉ በእውነት ምን ምኑን እንደሚያሥቡ ለማወቅ ስንኳ ይሁንና ለማስተዳደር በፍጹም አለመቻሉ ግልጽ ስለሚሆን፣ ይህ ኹኔታ የህሊና ነጻነትን ለመከልከል ለሚያስቡ ሰዎች ጽኑ መሰናከል ነው። የሰውን ሀሣብ ለማስተዳደር በፍጹም እንደማይቻል መጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፈ መክብብ 8፡8 እንዲህ ያስተምራል፦ «በመንፈስ ላይ ሥልጣን ያለው ሰው የለም፤ በሞቱም ቀን ሥልጣን የለውም...» ተመሳሳይ አስተያየት በኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ይገኛል። እዚህ የባልንጀሮቻቸውን ስሜት ለማስተዳደር በከንቱ የሚጣሩ ሰዎች «በገበያ የሚቀመጡትን ልጆች»ን ያስመስላቸዋል፤ ደስታ በእምቢልታ ልቅሶም በሙሾ ለማስገኘት ይሞክራሉና ባለመቻላቸው በቅሬታ ይጮሃሉ። (ማቴ. 11፡16)። ጽንሰ ሃሳቡ እንደገና በቅዱስ ጳውሎስ የተለማ ሲታይ ውሏል። («አርነቴ {ኤለውጠሪያ} በሌላ ሰው ሕሊና {ሱነይዴሰዮስ} የሚፈረድ ኧረ ስለ ምንድር ነው?» 1 ቆሮ. 10፡29) በሰው ጭንቅላት ውስጥ ምን እንደሚታሠብ ለመወሰን የሚሞክሩ ድንጋጌዎች በታሪክ አጠያያቂ ሆነዋል። ለምሳሌ የእንግሊዝ ንግሥት 1 ኤልሳቤጥ (16ኛው ክፍለ ዘመን) እንዲህ አይነት ሕግ በሠረዙት ጊዜ፣ 'በሰዎች ነፍስና ግል ሀሣብ ላይ መስኮት ለመስራት አልወድም' ብለዋል። የኅሊና ነጻነት ለዴሞክራሲ መሠረታዊ መርኅ ሲባል፣ የኅሊና ነጻነት የሚከለከልበት ሙከራ የፈላጭ ቁራጭ ወይም አምባገነን መንግሥት ባኅርይ ሆነዋል። አፈና፣ ማሳደድ፣ መጽሐፍ መቃጠል፣ ወይም ፕሮፓጋንዳ ሁሉ የንግግር ነጻነት ሲወስኑ ይህ ሁናቴ ለኅሊና ነጻነት ጤነኛ አይደለም። ለምሳሌ በሂትለር ዘመን በጀርመን ባለሥልጣናቱ ያልወደዱት ብዙ መጻሕፍት ተቃጥለው ነበር። ዛሬም ባንዳንድ አገራት ውስጥ የንግግር ነጻነት ለመቆጣጠር ሲያስቡ በኢንተርኔት ላይ ማገጃ የሚጣሉ መንግሥታት አሉ። በአንዳንድ ክርክር ዘንድ ደግሞ፣ አደንዛዥ ዕጽ የተለወጠ ሀሣብ ሊፈጥር ስለሚችል፣ እንግዲህ ሕገ ወጥ መሆኑ የኅሊና ነጻነት እንደ መከልከል ሊባል ይችላል። በመጋቢት 2006 ዓ.ም. የሚከተሉት አገራት ፌስቡክ፣ ትዊተር ወይም ዩ ቱብ ላይ ማገጃ ጥለዋል፦ የቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ። ፌስቡክ፣ ትዊተርና ዩ-ቱብ ከ2001 ዓ.ም. ጀምሮ ተከለክለዋል። ከመስከረም 2006 ዓም ጀምሮ ግን በሻንግሃይ ከተማ ብቻ ተፈቀዱ። ኢራን። ከ2001 ዓ.ም. ጀምሮ ፌስቡክ፣ ትዊተርና ዩ ቱብ አብዛኛው ጊዜ ተከለክለዋል። ኤርትራ። ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ ዩ ቱብ ተከለክሏል። ቬት ናም። ከ2004 ዓ.ም. ፌስቡክ እንደ ተከለከለ ተብሏል፤ ዜጎች ግን በቀላሉ ሊደርሱት ይችላሉ። በመስከረም 2006 ደግሞ ዜጎች መንግሥትን በፌስቡክ እንዳይተቹ የሚል ሕግ ወጣ። ፓኪስታን። ከመስከረም 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ዩ ቱብ ተከለክሏል። በ2002 ዓ.ም. ደግሞ ለጊዜው ፌስቡክን ከለከለ። ቱርክ። በመጋቢት 2006 ዓ.ም. ትዊተርንና ዩ ቱብን ከለከለ። ስሜን ኮርያ። ኢንተርነት በሙሉ በስሜን ኮርያ ለባላሥልጣናት ብቻ ይፈቀዳል። ባለፉት ጊዜ የሚከተሉት አገራት ለጊዜው ድረ ገጾቹን ተክለክለው አሁን ግን እንደገና ፈቀደዋል። ሶርያ ከ2000 እስከ 2003 ዓ.ም. ድረስ ዩቱብን ከለከለ። ባንግላዴሽ - በመጋቢት 2001ና እንደገና በ2005 ዓ.ም. ዩ ቱብን ከለከለ። ሊብያ ከ2002 እስከ 2003 ዓ.ም. ድረስ ዩቱብን ከለከለ። አልጄሪያ፣ ቱኒዚያ፣ ግብጽ፣ ካሜሩን፣ ማላዊ፣ ቤላሩስ - ትዊተር በ2003 ዓ.ም. ተከለከለ። ታጂኪስታን በ2005 ዓ.ም. አንዳንዴም ዩቱብን ከለክሏል። አፍጋኒስታን ከመስከረም እስከ ጥር 2005 ዓ.ም. ድረስ ዩ ቱብን ከለከለ። ምየንማ - አንዳንዴ ፌስቡክን ከለክሏል። ብዙ ሌሎች አገራት እነዚህንና ሌሎች ድረ ገጾች ለጊዜው አግደዋል። ደግሞ ይዩ። የመንግሥት ሃይማኖት የፖለቲካ ጥናት
1523
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%89%B1%E1%8A%AB%E1%8A%95%20%28%E1%8D%8D%E1%88%AC%29
ብርቱካን (ፍሬ)
ብርቱካን (ወይም ኦሬንጅ) ማለት የዛፍ አይነትም ሆነ በተለይ የዚሁ ዛፍ ፍሬ ማለት ነው። የሌሎች አትክልት ክልስ ሆኖ ከጥንት እንደ ለማ ይታሥባል። እርዝማኔው እስከ 10 ሜትር ድረስ ቢደርስም ዛፉ ትንሽ ይባላል፤ ቡቃያው እሾህ አለበትና ቅጠሎቹ ከ4 እስከ 10 ሳንቲሜትር ድረስ የሚዘረጉ እንደ ጥድም ወገን መቸም የማይረግፉ ናቸው። የፍሬው መጀመርያ ትውልድ በደቡብ-ምሥራቃዊ እስያ በህንደኬ፣ በቬትናም ወይም በደቡብ ቻይና ተገኘ። ስለ እርሻና ስለጥቅም የብርቱካን እርሻ በብዙ አገሮች ምጣኔ ሀብት በጣም ታላቅ የንግድ ሥራ ነው። እዚህ ማለት በአሜሪካ፣ በሜዲቴራኔያን አገሮች፣ በሮማንያ፣ በደቡብ አፍሪካ፣ በቻይና፣ በአውስትራልያም ይከትታል። ብርቱካን በዓለሙ ውስጥ ሙቅ አየር በሚገኝበት በሰፊ ይበቅላል፤ የብርቱካንም ጣዕም ከጣፋጭ እስከ ኮምጣጣ ድረስ ይለያል። ፍሬው በተለመደ ይላጣል ጥሬም ሆኖ ይበላል፤ አለዚያ ለጭማቂው ይጨመቃል። ወፍራምና መራራ ልጣጩ በተለመደ ወደ ቆሻሻ ይጣላል፤ ነገር ግን በክብደትና በሙቀት አማካኝነት ውሃውን በማስወግድ፣ ለመኖ ሊጠቅም ይችላል። ባንዳንድ የምግብ አሠራር ዘዴ ደግሞ፣ እንደ ጣዕም ወይም እንደ መከሸን ይጨመራል። የልጣጩ አፍአዊው ቆዳ በልዩ መሣርያ በቀጭን ይፋቃልና ይሄ ጣዕሙ ለወጥ የሚወደድ ቅመም ያስገኛል። ከልጣጩ በታች ያለው ነጭና ሥሥ ሽፋን ስለማይረባ ይጣላል። ደግሞ የብርቱካን ዘይት አስታጋሽ መዓዛ ስላለው በሕክምና ይጠቅማል። ከብርቱካን የተሠራ ሌላ ውጤት እንደሚከተለው ነው፦ የብርቱካን ጭማቂ በኒው ዮርክ ሸቀጣሸቅጥ ገበያ ላይ የሚነገድ የንግድ ዕቃ ነው። የዓለሙ አንደኛ ብርቱካን ጭማቂ የምታስገኝ ሀገር ብራዚል ስትሆን ሁለተኛዋ ፍሎሪዳ ክፍለሀገር በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ትሆናለች። የብርቱካን ዘይት ልጣጩን በመጭመቅ ይሠራል። የዕንጨት ዕቃ መልክ ለማሳምር የጠቅማል፤ ደግሞ የእጅ ማጽዳት ቅባት ያደርጋል። የሚረጭ አይነት በሱቅ ሲሸጥ በጣም ኃይለኛ ማጽደጃ ነውና ለአካባቢ አይጎዳም አይመርዝምም። የብርቱካን አበባ የፍሎሪዳ ክፍለሀገር ብሄራዊ ምልክት ቢሆን እንዲሁም በአንዳንድ ባሕል እምነት ውስጥ የመልካም ዕድል ምልክት ሆኛልና ለሙሽሪት እቅፍና ለጌጥ በሠርግ ጊዜ ለረጅም ዘመን ባሕላዊ ነበር። ያበባው ቅጠል ደግሞ መልካም መዓዛ ያለበት ሽቶ ሊሠራ ይችላል። የብርቱካን አበባ ማር የሚሠራ የንብ ቀፎ በብርቱካን ደን ውስጥ በማበቡ ጊዜ በማስቀመጥ ነው። ይህ አደራረግ ደግሞ ዘር ያለባቸው ሌሎች አበቦች እንዲራቡ ያደርጋል። የብርቱካን አበባ ማር እጅግ የወደዳል ጣእሙም እንደ ብርቱካን ይመስላልና። እንዲያውም ብርቱካን፣ ሎሚ፣ መንደሪን ወዘተ. ሁሉ የአንድ ወገን ናቸው ሁላቸው እርስ በርስ ማራባት ይችላሉ ማለት ነው። በተግባር እነኚህ አይነቶች እንጆሪ ይባላሉ ምክንያቱም ብዙ ዘር እያላቸው ሥጋቸውም ወፍራምና ለስላሳ ሆኖ ከአንድ ዕንቁላል ብቻ ያፈራሉ። በምድር ላይ ጥቂት አይነቶች ይታረሳሉ። ለምሳሌ ጣፋጭ ብርቱካን የምትባል መጀመርያ በእስፓንያ አገር በቀለች፤ ይቺ ከሁሉ የምትወደድ አይነት ሆናለች። ጣፋጭ ብርቱካን እንደ አየሩ ሁኔታ በልዩ ልዩ መጠኖችና ቀለሞች ትገኛለች፤ አብዛኛው 12 ክፍሎች ውስጥ አሉባቸው። የሴቪል ብርቱካን በሰፊ የምትታወቅ አሁንም በሜዲቴራኔያን አቅራቢያ በኩል የምትበቀል እጅግ ኮምጣጣ ብርቱካን ናት። ቆዳዋ ወፍራምና ስርጉዳት ያለው ነውና ማርማላታም ሆነ የብርቱካን አረቄ ለመስራት በጣም ትከብራለች። "ይብራ በብርቱካን ወጥ" ሲበሉ ብርቱካን የዚች አይነት ናት። ባጋጣሚ በብራሲል አገር ውስጥ በ1812 ዓ.ም. በአንድ ገዳም በነበረ የብርቱካን እርሻ ከሆነ ድንገተኛ ለውጥ የተነሣ፤ "የእምብርት ብርቱካን" የሚባል አይነት መጀመርያ ተገኘ። ከዚያ በ1862 ዓ.ም. ነጠላ ቁራጭ ወደ ካሊፎርንያ ተዛዉሮ አዲስ የዓለም አቀፍ ብርቱካን ገበያ የዛኔ ተፈጠረ። ድንገተኛ ለውጡ "መንታ ፍሬ" ያደርጋልና ታናሹ መንታ በታላቁ ውስጥ ተሠውሮ ይገኛል። የእምብርት ብርቱካን ዘር ስለሌለው በእፃዊ ተዋልዶ ይባዛል፤ የፍሬውም መጠን ከጣፋጭ በርቱካን ይበልጣል። ቫሌንሲያ ወይም ሙርሲያ ብርቱካን በተለይ ለጭማቂ የሚመች ጣፋጭ አይነት ነው። መንደሪን ትመስለዋለች፣ ነገር ግን ይልቁን ትንሽና ጣፋጭ ናት፤ በመጨራሻም፣ "ድፍን ቀይ እምብርት" የተባለው የዚህ አይነት ከነመንታው ለውጥ እንደ እምብርት በርቱካን ነው። የቃል ታሪክ በድሮ ጊዜ ፖርቱጋል የምትባል አገር ለምሥራቅ አገሮች የጣፋጭ ብርቱካን ዋና አስገቢ ነበረች። ስለዚህ በብዙ ቋንቋዎች የፍሬው ስም ከዚያው መነሻ ተወስዷል። ለምሳሌ፦ ዓረብኛ - ቡርቱቃል ፋርስ - ፖርተግሐል ቱርክ - ፖርታካል አዘርኛ - ፖርታጃል ዘመናዊ ግሪክ - ፖርቶካሊ ሩማንኛ - ፖርቶካላ ቡልጋርኛ - ፖርቶካል ጂዮርጂያ - ፖርቶቃሊ ተብሎ ይሰየማል። ባብዛኛው ቋንቋዎች ግን ያለባቸው ቃል ከሳንስክሪት «ናራንጋ» የወጣ ነው፤ በሌሎችም «የቻይና ቱፋህ» (አፕል) ወይም «የወርቅ ቱፋህ» የሚተረጎሙ ቃሎች ለብርቱካን ለማለት የጠቅማቸዋል።
14636
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A3%E1%88%85%E1%88%AD%20%E1%8B%9B%E1%8D%8D
ባህር ዛፍ
ባህር ዛፍ () በተፈጥሮው ከአውስትራሊያ የሚገኝ አበባ ሚያብብ የዛፍ ወገን ነው። በአለም ላይ 700 አይነት የባህር ዛፍ ዝርያዎች አሉ፣ ከነዚህ ውስጥ 15ቱ ከአዉስትራሊያ ውጭ በተፈጥሮ ሲገኙ ከ700ው 9ኙ ዘር ብቻ አውስትራሊያ ውስጥ በተፈጥሮ አይገኝም። በኢትዮጵያ በተለይ የታወቁት፦ ነጭ ባሕር ዛፍ ቀይ ባሕር ዛፍ በአዲስ አበባ ከተማ ዳግማዊ ምኒልክ የባህር ዛፍ ፍሬ አስመጥተው ካስተከሉ በኋላ ይሄ አዲስ ዕጽ ዓየሩ ተስማምቶት ለከተማዋ የአረንጓዴ መቀነት ይመስል በጥቂት ዓመታት አሸበረቃት። በ፲፱፻፵ ዎቹ ይሄ መቀነት እስከ አርባ ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት በመያዙ ከተማዋን በሰፊው "" (የባህር ዛፍ ከተማ) የተባለ ቅጽል ስምን አትርፎላት ነበር። በአሁኑ ወቅት ባህር ዛፍ አለም አቀፍ ተፈላጊነት አግኝቷል። ይህም የሆነበት ምክንያት ቶሎ በማደግ አስፈላጊ እንጨት ይሰጣል የዛፉ ዘይት ለጽዳት እና እንዲሁም በራሪ ትንኞችን ለማባረር እንዲሁም ለመግደል ይረዳል አልፎ አልፎ ለወባ ትንኝ ማደግ ምቹ የሆኑ አረንቋወችን ለማድረቅ ይረዳል። ሆኖም ግን ባህር ዛፍ ከላይ ለተጠቀሱት አላማወች ቢያገለግልም ትልቁ ችግሩ ውሃ በጣም ይወዳል። ስለሆንም እርሱ በተተከለበት ሌሎች አትክልቶች የማደግ እድላቸው ዝቅተኛ ነው። ኢትዮጵያም ውስጥ በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ምንጮችን እንዳደረቀ መረጃ አለ። አፄ ምኒልክ አዲስ አበባ የመንግሥታቸው መቀመጫ እንድትሆን መወሰን የቻሉት ከአውስትራሊያ የመጣው ባህር ዛፍ ለማገዶ ችግር አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥ ሆኖ በመገኘቱ ነበር፡፡ ባህር ዛፍን ጨምሮ የደን ልማት ለአገርና ለሕዝብ ያለውን ጠቀሜታ የተረዳው የአፄ ኃይለሥላሴም መንግሥት ከሐምሌ 9 ቀን 1948 ዓ.ም ጀምሮ በየዓመቱ የደን በዓል ቀን ሆኖ እንዲከበር ወስኖ እንደነበር “ፍሬ ከናፍር 3ኛ መፅሐፍ” በሚል ርእስ በ1957 ዓ.ም የታተመው ጥራዝ ውስጥ ታሪኩ ተዘግቧል፡፡ በዘመኑ በሆለታ ከተማ በተከበረው የደን በዓል ቀን ላይ ንግግር ያደረጉት የእርሻ ሚኒስትሩ ባላምባራስ ማህተመሥላሴ ወልደመስቀል ለበዓሉ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ችግኝ መዘጋጀቱን፣ ችግኞቹን መትከያ 120,000 ሜትር ካሬ መሬት መሰናዳቱን፣ ከሚተከሉትም ችግኞች የሚበዙት ከውጭ አገር የመጡ መሆናቸውን፣ ለፕሮጀክቱ መሳካት የተባበሩት መንግሥታት የእርሻና የምግብ ድርጅት እገዛ ማድረጉን ገልፀዋል፡፡ የደን በዓል ቀን ተቆርጦለት መከበር ከመጀመሩ በፊት በተሰራው ሥራም ወደ አንድ ሚሊዮን የሚደርሱ እፅዋት መተከላቸውን ያመለከቱት አፄ ኃይለሥላሴ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር “አስፈላጊውን ችግኝ ምንም እንኳን የእርሻ ሚኒስቴር እንዲሰጥ ቢታዘዝ ከእርሻ ሚኒስቴር እየተወሰዱ የሚተከሉት ዛፎች ሁሉ የባለርስቱ ንብረት ናቸውና ይህን ሥራ ያለማቋረጥ በትጋት መፈፀም ግዴታ ነው፡፡” የእርሻ ሚኒስትሩና ንጉሠ ነገሥቱ “በሆለታ ዛፍ ተክል መፈተኛ ጣቢያ” ተገኝተው ካደረጉት ንግግር መረዳት እንደሚቻለው ካለፈው ብቻ ሳይሆን ዛሬ ከሚታየውም እውነታ ጋር እያያዝን ብዙ ጥያቄ እንድናነሳ ግድ የሚሉ መረጃዎች ሰፍረዋል፡፡ ለሐምሌ 9 ቀን 1948 ዓ.ም የደን በዓል ቀን እንዲተከሉ የቀረቡት እፅዋት የሚበዙት ከውጭ የመጡ ከሆነ አሁን ባህር ዛፍን በአገር በቀል እፅዋት የመተካቱ ተግባር በዚያ ዘመን በብዛት ወደ አገር ውስጥ የገቡትንም ያካትት ይሆን? “የሆለታ ዛፍ ተክል መፈተኛ ጣቢያ” ጥናትና ምርምር ዛሬ ተግባራዊ እየሆነ ላለው ተግባር ምን አስተዋፅኦ አድርጓል? ለ1948 ዓ.ም የደን በዓል ቀን የተባበሩት መንግሥታት የእርሻና የምግብ ድርጅት እገዛ ዛሬም ለተመሳሳይ ዓላማ እያገኘናቸው ካሉ እርዳታዎች ጋር ስናነፃፅረው ስለነገ መድረሻችን ምን ያሳየናል? በዘመኑ አፄ ኃይለሥላሴና የእለቱ የክብር እንግዶች የተከሏቸው ችግኞች አሁን ይኖሩ ይሆን? ዛፍ እንደ ቅርስ፣ እንደ ሐውልት ታሪክ ማስተላለፊያ ሆኖም አገልግሏል፡፡ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሕንፃ ፊት ለፊት በ”አፍሪካ ፓርክ” ውስጥ ያሉት እፅዋት በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት ለአፍሪካ አንድነት ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ የመጡ የአህጉሪቱ መሪዎች የተከሏቸው ናቸው፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይሆን በክልል ከተሞችም በታዋቂ ሰዎች የተተከሉ እፅዋት እንዳሉ መረጃ ከሚሰጡን መፃሕፍት አንዱ የሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው “ዐፈር ያነሳ ሥጋ” የግጥም ስብስብ መድብል ነው፡፡ በ1964 ዓ.ም የታተመው ይህ መፅሐፍ ጥር 24 ቀን 1961 ዓ.ም የተፃፈና “አንድ ያልታደለ ዛፍ” የሚል ርእስ ያለው ግጥምን ይዟል፡፡ በዘመኑ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ሆነው ያገለግሉ የነበሩት ኡ፡ታንት በኢትዮጵያ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት በደብረዘይት ከተማ የዛፍ ተከላ ሥነ ሥርዓት አከናውነዋል የቅጠሉ ጥቅሞች የቅጠሉ ተናኝ ዘይት ለጉንፋን ይረዳል። ትንኞችንም ለማባረር ይረዳል። ቅጠሎቹ በወለሎች ላይ የሚዘረጉ ናቸው። የቅጠሉም ውጥ ለማጅራት ገትር ተጉመጠመጠ። በአውስትራሊያ ለቅጠሉ ሱስነት ያለ ኪሴ እንስሳ ወይም «ኮዋላ» ይገኛል።
51566
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%A0%E1%8C%8C%E1%88%9D%E1%8B%B5%E1%88%AD
በጌምድር
የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግስት ውስጥ የተለያዪ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ያሉበት ክልል ነው። የአማራ ክልል መንግስትም አማራን፣ የአገውአዊን፣ የኦሮሞን፣ የዋግእምራን፣ የአርጐባንና የቅማንትን ብሄር ብሔረሰቦች ወክሎ የተዋቀረ የክልል መንግስት ነው።በክልሉ የሚገኙት ሁሉም ብሔረሰቦች የራሳቸው ቋንቋ፣ባህልና ታሪክ እምነት ያላቸው ብሄረሰቦች ናቸው። በአብዛኛው ሁሉም በክልሉ የሚገኙ ብሄረሰቦች የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፈው ይናገራሉ፤የጋራ ማህበራዊ ህይወታቸውን ስንመለከት አጠቃላይ ማህበራዊ ክንዋኔዎችን የሚያደርጉ እና በአንድ አይነት ማህበራዊ ክንዋኔዎች የሚገለጹ ህዝቦች ናቸው፡፡በእምነት፣ በጥቃት ፣ በመልከ አምድራዊ አኗኗራቸው… ወዘተ ተከባብረውና ተደጋግፈው የሚኖሩ ሕዝቦች ናቸው። በጠቃላይ የክልሉ ህዝቦች በአብሮነት የክልሉን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ በጋራ ና በአንድነት እኩል ተሳትፎ ያደርጋሉ። #የአማራ_ክልል_ብሔር_ብሄረሰቦችናሕዝቦችን አጠር አድርገን ዘርዝረን እንመልከት፦ "አማራ" የአማራ ክልል ብሄር አንድ አካል ነው፡፡ አብዛኛውን የክልሉን ህዝብ በመልከ ኣምድራዊ አቀማመጡ፣በቋንቋው ተናጋሪ ብዛት፣በሰፊው የሚሸፍን በመሆኑ የአጠቃላይ የክልሉ መጠሪያ ሆኗል፡፡"አማራዎች በአብዛኛው የክርስትና እምነት ተከታዮች ናቸው።በሸዋ፣በወሎ፣ በጐጃምና በጐንደር በስፋት ይገኛሉ። የራሳቸው ባህል ታሪክና ቋንቋ ያላቸው ብሔረሰቦች ናቸው። ከሁሉም ብሄረሰብ ጋር በአብሮነት ተቻችለው የሚኖሩ ህዝቦች ሲሆኑ የአማራ ብሔር እንደኔ እንደኔ ሁለት ተጨማሪ ተደራቢ ማንነቶች አሉት እነሱም፦ #ቤተ_እስራኤል_አማራ(#ፈላሻ)ቤተ እስራኤል የአማራ ብሄር አንዱ ክፍል ነው፡፡ሆኖም ወደእስራኤል አገር ከመሄዳቸው በፊት #ፈላሻ ወይም ቤተ እስራኤል የሚል መጠሪያ ነበራቸው፡፡ የድሮ ቋንቋቸው ግን አማርኛ ነበር፡፡ አሁን ወደእስራኤል ከሄዱ በኋላ ግን የኋላኛው ትውልድ "እብራይስጥኛን" እንደ በዋና ቋንቋነት ይናገራል፡፡ ታሪካቸው የተወሳሰበ ቢሆንም ከአማራ ብሄር የተለዩ አይደሉም። #ወይጦ_አማራ "ወይጦ አማራ" ከመባሉ ውጭ በማንኛውም መስፈርት በህይማኖትም በባህልም አማራ እንደሆኑ ይገልፃሉ የታሪክ ፃሀፊዎች፡፡ ስለሆነም የአማራ ብሄር ነገድ አካል ነው፡፡ ኦሮሞ በክልሉ መዋቅር ስር ከጥንት ጀምሮ በወሎ ምድር የሚኖሩ ማህበረሰቦች ናቸው።የራሳቸው ባህል ታሪክና ቋንቋ ያላቸው የእስልምና እምነት ተከታይ ማሕበረሰቦች ናቸው። የራስ አስተዳደራቸውን "የኦሮሚያ ልዩ ዞን" በሚል መስረተው ራሳቸውን በራሳቸው እያስተዳደሩ ይገኛሉ። "ዋግእምራ" በአማራ ክልል ከሚገኙት ብሄር ብሄረሰቦች አንዱ ነው።በሰሜን ምስራቅ አማራ የሚገኙ ብሄረሰቦች ሲሆኑ የራሳቸው ልዩ የሆነ ባሕል፣ ቋንቋ ና ታሪክ ያላቸው ብሔረሰቦች ናቸው።በአሁኑ ሰአት የራስ አስተዳደር ዋግእምራ ልዩ ዞን መስርቶ ራሳቸውን በራሳቸው እያስተዳደሩ ይገኛል። "አገውአዊ "የአማራ ብሄራዊ ክልል አንዱ ክፍል ነው፡፡ በምዕራብ አማራ የሚገኙ ብሔረሰቦች ሲሆኑ "የአገውኛ ቋንቋ" ን የሚናገሩ ና የራሳቸው ባህል ና ታሪክ ያላቸው ሕዝቦች ናቸው፡፡ የራሳቸው አስተዳደር "አዊ ልዩ ዞን" መስርተው ራሳቸውን በራሳቸው እያስተዳደሩ ይገኛሉ። "ቅማንት" የአማራ ብሄራዊ ክልል መንግስት አንዱ ክፍል ነው፡፡ የቅማንት ማሕበረሰቦች የራሳቸው ባሕል ታሪክና ቋንቋ ያላቸው የክርስትና እምነት ተከታይ ማሕበረሰቦች ናቸው። ከአማራ ሕዝብ ጋር በአብሮነትና በፍቅር ተሰሳስረው በመተሳሰብ የሚኖሩ ማሕበረሰቦች ናቸው።ራስን በራስ ለማስተዳደር ጥያቄ አቅርበው በ2007 ዓ.ም በሰሜን ጐንደር ዞን "የቅማንት ልዩ ወረዳን" መስርተው ራስን በራስ እያስተዳደሩ ይገኛሉ።የልዩ ወረዳዋ ህዝቦች ህገ መንግስታዊ መብታቸው ተከብሮ ቋንቋቸውን ለማሳደግ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።ሙሉ በሙሉ መብታቸው ተከብሯል። ነገር ግን ከወረዳው ውጭ ባሉ አጐራባች ወረዳዎች የሚኖሩ የብሄረሰቡ አባላቶች የራስ አስተዳደር ጥያቄ አቅርበው ምላሽ እየጠበቁ ይገኛሉ። "የአርጎባ ማሕበረሰብ"ከጥንት ዘመን ጀምሮ በአማራ ውስጥ ከሚገኙት ብሄሮች አንዱ ነው፡፡ የራሳቸው ባህል፣ ቋንቋ ናታሪክ ያላቸው የእስልምና እምነት ተከታይ ማህበረሰቦች ናቸው። ቋንቋቸውም "አርጐብኛ" ይባላል። በተለያዩ የአፄ ገዢዎች ምክኒያት ቋንቋቸው ቢዳከምም ዛሬ ድርስ የአርጐብኛ ቋንቋን በጥቂት አካባቢዎቻቸው ላይ ይናገራሉ። ራስን በራስ ለማስተዳደር ለክልሉ ምክር ቤት ጥያቄ አቅርበው በ1998 ዓ.ም በደቡብ ወሎ ዞን የሚገኙት የብሄረሰቡ አባላቶች "የአርጐባ ልዩ ወረዳን" መስርተው ራሳቸውን በራሳቸው በከፊል እያስተዳደሩ ነው። የብሄረሰቡ ተወላጆች በወረዳው ብዙም ደስተኛ አይደሉም ምክኒያቱም የይምሰል ልዩ ወረዳ ነው……። በብሄረሰቡ ጥቂት ተወላጆች አማካኝነት ቋንቋቸውን ለማሳደግ የተለያዩ መፅሀፍትንና ብሮሸሮችን በማዘጋጀት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ከወረዳው ወጭ ያሉ በወረዳው አጎራባች ቀበሌ የሚገኙት የብሄሩ አባላት የራስ አስተዳደር ጥያቄ አቅርበው ምላሽ በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ።በኦሮሚያ ልዩ ዞንና በሰሜን ሸዋ ዞን በ12 ወረዳዎች ከ92 ቀበሌዎች በላይ የሚገኙት የብሄረሰቡ አባላትም ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ ራስን በራስ ለማስተዳደር ጥያቄ አቅርበው ምላሽ መጠበቅ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። የአርጐባ ብሔረሰቦች ከማንኛውም ብሄር ብሄረሰብ ጋር በአብሮነት፣ በሰላምና በፍቅር ተቻችሎ በመኖር ከሚጠቀሱት የኢትዮዽያ ብሔር ብሔረሰቦችና ኅዝቦች ግንባር ቀደሞቹ ናቸው።ወሬ ላማሳመር ብዬ ሳይሆን በታሪክም ተግባርም የሚታወቅና የሚታይ ነገር ነው። በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በሐረሪና በአፋር ክልል በብዛትና በስፋት በሚኖሩበት ሑሉ ከማንኛውም ብሄር ብሄረሰብ ጋራ ቋንቋውን፣ባህሉን ወረሰው የጋራ ማህበራዊ ትስስር ፈጥረው የሚኖሩ ብሔረሰቦች ናቸው። እነዚህ ከላይ ከ①/፩ኛ እስከ⑥/፮ኛ የተዘረዘሩት ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በአማራ ብሔረሰብ ስር በጋራ የሚኖሩ የአንድ ምድር ህዝቦች ናቸው።ሑሉም ባለፉት የአፄ መንግስታቶች ተፅዕኖ ቀንበር ውስጥ የነበሩ ብሔር ብሔረሰቦች ናቸው። ከሌሎች ብሔር ብሔረሶች ጋር በመሆን ባደረጉት ትግል በ1983 ዓ.ም አምባገነን መንግስት ድል አደረጉ። የፌደራሊዝም ስርዓት ተገንብቶ የሀገራችን ህገ መንግስት በህዝቦች ውሳኔ ከፀደቀ ቡሃላ ራስን በራስ የማስተዳደር የእኩልነት መብት ለሁሉም ለብሄር ብሄረሰቦች በሚል ፍትህ አገኙ። ይሁን እንጂ ይህን ስርኣት የሚጠሉት የአምባገነኑ ርዝራዦች ኢህአዴግን እንደጠላት አድርገው ይቆጥሩታል። ጭቁን የነበሩ ብሄር ብሄረሰቦች ግን ኢህአዴግን እያመሰገኑት እንደሆነ እርገጠኛ ነኝ። የአርጎባ ማህበረሰቦች ራስን በራስ ለማስተዳደር በድርጅታቸው አሕዴድ ኢህአዴግ አማካኝነት ከ1986ዓ.ም ጀምረው በኦሮሚያ ልዩ ዞን፣ በደቡብ ወሎና ሰሜን ሸዋ ዞኖች ራስን በራስ የማስተዳደር የመብት ጥያቄያቸውን አቅርበው «በደቡብ ወሎ ዞን ጥቂት ቀበሌዎችን ብቻ» እንዲያስተዳድር ወሰኖ የተቀሩት ደግሞ ከሌሎቹ ብሄረሰቦች በተለየ ሁኔታ ለህዝብ በማይታወቅና ግልፅ ባልሆነ ምክኒያት ምላሽ አላገኙም። ይሁን እንጂ የአርጐባ ብሔረሰቦች መብታቸውን በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ጥያቄያቸው አቅርበው አሁንም ምላሽ በመጠበቅ ላይ ናቸው! ግን ለምን? አባት ልጁን ድሮ ጎጆ እንደሚያወጣው ሁሉ…… ሑሉንም ብሔረሰቦች በእኩል አይኑ ሊመለከታቸው ይገባል። #ማስታወሻ፦ በፅሁፌ ላይ ስህተት ካለበት ይቅርታ እየጠየቅኩ አስተያዬታችሁን እሻለሁ ይገነባኛልና በተመቻችሁ ሁኔዎች ሁሉ ልትገልፁልኝ ትችላላችሁ እወዳችሗለሁ ደህና ሁኑ! 3,ከአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ቢሮ ብሮሸር "የጣና ሐይቅን እንታደግ! የ"እቦጭ" አርምን ተባብረን እናስወግድ!" "የብሔር ብሔረሰቦች መብት ተከብሮ በአንድነት፣በፍቅር፣ከሌሎች ሕዝቦች ጋር እኩል ተከባብረን የጋራ ኢትዮዽያችንን እንገንባ!" የጋራ ጠላታችን ድህነትን እንዋጋ! ©በሰዒድ አል ጀበርቲ ተፃፈ አዲስ አበባ-ኢትዮዽያ
2867
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%A9%E1%88%B2%E1%8B%AB
ሩሲያ
ሩሲያ (መስኮብኛ፦ /ሮሲያ/) ወይም የሩሲያ ፌዴሬሽን (መስኮብኛ፦ /ሮሲስካያ ፍየድየራትሲያ/) በአውሮፓ እና እስያ አህጉሮች ውስጥ የምትገኝ አገር ናት። በ17,075,200 ካሬ ኪ.ሜ. ከዓለም በመሬት ስፋት አንደኛ ስትሆን በሕዝብ ብዛትም ከዓለም ስምንተኛ ናት። ሩስያ ከኖርዌ፣ ፊንላንድ፣ ኤስቶኒያ፣ ሌትላንድ (ላቲቪያ)፣ ሊትዌኒያ፣ ፖላንድ፣ ቤላሩስ፣ ዩክሬን፣ ጆርጂያ፣ አዘርባይጃን፣ ካዛኪስታን፣ የቻይና ሕዝባዊ ሬፑብሊክ፣ ሞንጎሊያ እና ሰሜን ኮሪያ ጋር ድንበር አላት። ሞስኮ ዋና እና ትልቅ ከተማዋ ሲሆን ሴንት ፒተርስበርግ ሁለተኛው ትልቅ ከተማ ናት በምስራቃዊ አውሮፓ ክፍል የሚኖሩ የስላቭ ህብረተሰብ ወደ አሁኗ ሩስያ ከሶስት እስከ ስምንተኛው ክፍል ዘመን ተሰደዱ። ኬይቫን ረስ የሩስያ ህዝብ ማንነት እንዲኖሮ በማድረግ ከ9ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበረ ትልቅ ግዛት ነው። በተጨማሪም፣ የሩስያ ኦርቶዶክስ መነሳት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በ988 ዓም፣ ክርስትና ከቢዛንታይ ወደ ሩስያ ተስፋፋ። ልክ የረስ ስልጣን በሞንጎል ወረራ ሲዳከም፣ ምስራቃዊ ክፍሏ በልዕልና እስከ 13ተኛው ክፍለ ዘመን ይመራ ነበር። እስከ 18ተኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ምዕራባዊው ግዛት በፍጥነት ድንበሯን ወደ ምስራቅ በማስፋፋት የሩስያ ኢምፓየር መመረት ችላለች። በ1917 የተነሳው የሩስያ አብዮት የመንግስቱን ስርአት ወደ ሶሻሊስት በመቀየር የሶቬት ህብረትን በ1922 አቋቋመች። ሰፊውን የምስራቃዊ አውሮፓና መካከለኛ እስያ ክፍልን የሚይዘው የሶቬት ህብረት በሁለተኛው የአለም ጦርነት አክሲስ ሀያላንን በመዋጋት ጎልህ ሚና ነበራት። ነገር ግን ከጆሴፍ ስታንሊን አመራር ጀምሮ፣ የሶቬት ህብረት አምባገነናዊ እየሆነ ሄደ። ብዙ ቤት ክርስቲያኖች ወደሙ፣ ብዙ ሰዎች ተገደሉ፣ ብዙ አይሁዶች ከቀያቸው ተፈናቀሉ። የሶቬት ህብረት ከአሜሪካ ጋር የቀዝቃዛውን ጦርነት ስታስጀምር ብዙ ደባና ጭካኔ አድርሳለች። ለምሳሌ፣ የቬትናም ጦርነት ላይ ከአሜሪካ ጋር የውክልና ጦርነት በማድረግ ሰብዕዊ መብት ጥሳለች። በተቃራኒው ሶቬት በሳይንስና ቴክኖሎጂ እጅግ በጣም መበልፀግ የጀመረችበት ጊዜ ነበር። በማርክሲዝ ሌኒንዝም አብዮት የተሞላችው ሶቬት ህብረት በ1991 በህዝበ ውሳኔ ልትፈርስ ችላለች። ሩስያ በ1993 መንግስቷን ወደ ፌድራል ልትቀይር ችላለች፤ እስካሁንም ትመራለች። ሩስያ ሀያላን ሀገር ናት። በተጨማሪም በጦርና በማዕድን የምትታወቅ ናት። ሩሲያ የሚለው ስም በዋነኝነት በምስራቅ ስላቭስ የሚኖር የመካከለኛው ዘመን ግዛት ከሆነው ሩስ' የተገኘ ነው። ይሁን እንጂ ትክክለኛው ስም በኋለኛው ታሪክ ውስጥ ጎልቶ የወጣ ሲሆን አገሪቷ በተለምዶ በነዋሪዎቿ "የሩሲያ ምድር" ተብላ ትጠራ ነበር.ይህን ግዛት ከእሱ ከተገኙት ሌሎች ግዛቶች ለመለየት በዘመናዊ የታሪክ አጻጻፍ ኪየቫን ሩስ ተብሎ ይገለጻል. ሩስ የሚለው ስም እራሱ የመጣው ከጥንት የመካከለኛው ዘመን የሩስ ሰዎች ፣ የኖርስ ነጋዴዎች እና ተዋጊዎች ቡድን ከባልቲክ ባህር ማዶ በኖቭጎሮድ ላይ ያተኮረ ግዛት በመመሥረት በኋላ ኪየቫን ሩስ ሆነ። የመካከለኛው ዘመን የላቲን ስም ሩስ' የሚለው ስም ሩተኒያ ነበር፣ እሱም ለምስራቅ ስላቪክ እና ለምስራቅ ኦርቶዶክስ ክልሎች ከበርካታ ስያሜዎች አንዱ እና በተለምዶ ለሩሲያ መሬቶች መጠሪያነት ያገለግል ነበር። የወቅቱ የአገሪቱ ስም ሩሲያ (ሮስሲያ) ) የመጣው ከባይዛንታይን ግሪክ የሩስ ስያሜ ነው፣ – ፊደል ተባለ በዘመናዊ ግሪክ።የሩሲያ ዜጎችን ለማመልከት መደበኛው መንገድ በእንግሊዝኛ “ሩሲያውያን” ነው። ሁለት ቃላት አሉ። በሩሲያኛ በተለምዶ ወደ እንግሊዘኛ "ሩሲያውያን" ተብሎ የሚተረጎመው - አንደኛው "ሩስስኪ" (ሩስስኪ) ነው, እሱም ብዙውን ጊዜ ሩሲያውያንን የሚያመለክት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ "ሮሺያኔ" (ሮስሲያኔ) ነው, እሱም የሩሲያ ዜጎች ምንም ቢሆኑም. ብሄረሰብ። «ሩሲያ» ወይም ከእንግሊዝኛ አጠራሩ «ራሺያ» የሩስኛ ስም «ሮሲያ» ያንጸባርቃሉ። በሀገሩ ዜና መዋዕሎች ዘንድ፣ «ሩስ» የተባለ የቫይኪንግ ወገን ከስዊድን በስላቮች ለማስተዳደር 830 ዓም ገደማ ተጋበዙ። የዛሬውን ኪየቭ መቀመጫቸውን አድርገው ኪየቫን ሩስ የተባለ መንግሥት በ874 ዓም መሠረቱ። በፊንኛ /ርዎጺ/ የሚለው መጠሪያ ማለት ሩስያ ሳይሆን የስዊድን መጠሪያ እስካሁን ነው፤ እንዲሁም ለፊንኛ የተዛመዱት ቋንቋዎች ስዊድንን በተመሳሳይ ስያሜዎች ይሉታል። የስዊድንም ባልቲክ ባሕር ዳር «ሮስላግን» ይባል ነበር፤ የ«ሮስ» ትርጓሜ «መርከብ ቀዛፊዎች» እንደ ሆነ ይታስባል። ዳሩ ግን ሌሎች ራሻዊ ሊቃውንት የ«ሩስ» ስም ከስዊድን እንደ መጣ አይቀበሉም። በተለይ አንድ የሳርማትያ ወይም እስኩቴስ ወገን ሮክሶላኒ ተብሎ ከ100 ዓክልበ. እስከ 350 ዓም ግድም በአካባቢው ይገኝ ነበር። በአንድ አስተሳሰብ የሮክሶላኒ ስም ከ«ሮስ» እና ከ«አላኒ» (አላኖች) ውሑድ ይሆናል። እንዲሁም ከ90 እና 550 ዓም መካከል «ሩጊ» (ሩጋውያን) የተባለ ምሥራቅ ጀርመናዊ ወገን ይጠቀስ ነበር፤ በኋላ በኪዬቫን ሩስ ዘመን የሮማይስጥ ሰነዶች ብዙ ጊዜ ለሩስ «ሩጊ» ይሉዋቸው ነበር። በ1275 ዓም የሞስኮ ግዛት ተመሠረተ፤ በኋላም የሞስኮ ታላቅ መስፍን በሌሎቹ ሩስያ ግዛቶች ላዕላይነት አገኘ። እስከ 1714 ዓም ድረስ ታላቁ ፕዮትር የሩስያ ግዛት (1714-1909 ዓ.ም.) እስካዋጀ ድረስ፣ መንግሥቱ በሮማይስጥ «ሞስኮቪያ»፣ በእንግሊዝኛም /መስኮቪ/ ይባል ነበር። በአማርኛ ይህ ስም «መስኮብ» ተጽፎ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሲቆይ ቋንቋውም ሩስኛ ደግሞ «መስኮብኛ» በመባል ይታወቃል። የጥንት ታሪክ ዘላን አርብቶ አደርነት በፖንቲክ-ካስፒያን ስቴፔ ከቻኮሊቲክ ጀምሮ ጎልብቷል። የእነዚህ የእርከን ሥልጣኔ ቅሪቶች እንደ አይፓቶቮ፣ ሲንታሽታ፣ አርቃይም እና ፓዚሪክ ባሉ ቦታዎች ተገኝተዋል፤ እነዚህም በጦርነት ውስጥ በጣም የታወቁትን የፈረስ አሻራዎች በሚይዙባቸው ቦታዎች። , የጥንት ግሪክ ነጋዴዎች በጣና እና ፋናጎሪያ ውስጥ ወደሚገኙት የንግድ ቦታዎች ክላሲካል ስልጣኔን አመጡ። በ 3 ኛው እስከ 4 ኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም, የጎቲክ ኦይየም ግዛት በደቡብ ሩሲያ ውስጥ ይኖር ነበር, እሱም በኋላ በሃንስ ተሸነፈ. በ 3 ኛው እና 6 ኛው መቶ ዘመን ዓ.ም መካከል ፣ የግሪክ ቅኝ ግዛቶችን የተከተለው የሄለናዊ ፖለቲካ የነበረው የቦስፖራን መንግሥት ፣ እንደ ሁንስ እና ዩራሺያን አቫርስ ባሉ ተዋጊ ጎሳዎች በተመራ ዘላኖች ወረራ ተጨናንቋል። በካስፒያን እና በጥቁር ባህር መካከል ያለውን የታችኛውን የቮልጋ ተፋሰስ ስቴፕ እስከ 10 ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ይገዛ ነበር። የሩስያውያን ቅድመ አያቶች በአውሮፓ ሰሜናዊ ምስራቅ ክፍል ከታዩት ከፕሮቶ-ኢንዶ-አውሮፓውያን ከተለዩት የስላቭ ጎሳዎች መካከል ናቸው. ከ 1500 ዓመታት በፊት. የምስራቅ ስላቭስ ቀስ በቀስ ምዕራብ ሩሲያን በሁለት ማዕበል ሰፈሩ፡ አንደኛው ከኪየቭ ወደ ዛሬው ሱዝዳል እና ሙሮም እና ሌላው ከፖሎትስክ ወደ ኖቭጎሮድ እና ሮስቶቭ ሄደ። ከ 7 ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ, የምስራቅ ስላቭስ በምእራብ ሩሲያ ውስጥ ከፍተኛውን ህዝብ ያቀፈ ሲሆን ቀስ በቀስ ግን ሰላማዊ በሆነ መንገድ የፊንላንድ ተወላጆችን አዋህዷል. ኪየቫን ሩስ በ9ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የመጀመሪያዎቹ የምስራቅ ስላቪክ ግዛቶች መመስረት ከምስራቃዊ ባልቲክ እስከ ጥቁር እና ካስፒያን ባህሮች ድረስ ባሉት የውሃ መስመሮች ላይ የተሳፈሩት ቫይኪንጎች ቫራንግያውያን ከመጡበት ጊዜ ጋር ተገጣጠመ። በአንደኛ ደረጃ ዜና መዋዕል መሠረት ሩሪክ የተባለ ከሩስ ሕዝብ የመጣ ቫራንጂያን በ 862 የኖቭጎሮድ ገዥ ሆኖ ተመረጠ። በ 882 ተተኪው ኦሌግ ወደ ደቡብ በመዞር ቀደም ሲል ለካዛርስ ግብር ይከፍል የነበረውን ኪየቭን ድል አደረገ። የሩሪክ ልጅ ኢጎር እና የኢጎር ልጅ ስቪያቶላቭ በመቀጠል ሁሉንም የአካባቢውን የምስራቅ ስላቪክ ጎሳዎች በኪየቫን አገዛዝ አሸንፈው የካዛርን ካጋኔትን አወደሙ እና ወደ ባይዛንቲየም እና ፋርስ ብዙ ወታደራዊ ዘመቻዎችን ጀመሩ። በ 10 ኛው እስከ 11 ኛው ክፍለ ዘመን ኪየቫን ሩስ በአውሮፓ ውስጥ ካሉት ትላልቅ እና በጣም የበለጸጉ ግዛቶች አንዱ ሆነች. የታላቁ የቭላድሚር ዘመን እና ልጁ ያሮስላቭ ጠቢብ የኪየቭ ወርቃማ ዘመንን ይመሰርታል ፣ እሱም የኦርቶዶክስ ክርስትና ከባይዛንቲየም ተቀባይነት ያገኘ እና የመጀመሪያው የምስራቅ ስላቪክ የጽሑፍ የሕግ ኮድ ተፈጠረ። , የሩስካያ ፕራቭዳ. የኪየቫን ሩስን በጋራ ይመራ በነበረው የሩሪክ ሥርወ መንግሥት አባላት መካከል የማያቋርጥ የእርስ በርስ ግጭት የሚታይበት የፊውዳሊዝም እና ያልተማከለ አስተዳደር ዘመን መጥቷል። የኪየቭ የበላይነት እየቀነሰ በሰሜን-ምስራቅ ለቭላድሚር-ሱዝዳል፣ በሰሜን-ምዕራብ ኖቭጎሮድ ሪፐብሊክ እና በደቡብ-ምዕራብ ውስጥ ጋሊሺያ-ቮልሂኒያ ጥቅም ላይ ይውላል። የኪየቫን ሩስ በመጨረሻ ተበታተነ፣ የመጨረሻው ምት የሞንጎሊያውያን ወረራ በ1237–40 ሲሆን ይህም ኪየቭን ተባረረ እና የሩስ ህዝብ ዋና ክፍል ሞተ። በኋላ ላይ ታታር በመባል የሚታወቁት ወራሪዎች የወርቅ ሆርዴ ግዛትን መሰረቱ፣ እሱም የሩሲያን ርዕሳነ መስተዳድሮች የዘረፈ እና የሩሲያ ደቡባዊ እና መካከለኛ ቦታዎችን ከሁለት መቶ ዓመታት በላይ ያስተዳድር ነበር። ጋሊሺያ-ቮልሂኒያ በመጨረሻ በፖላንድ መንግሥት የተዋሃደች ሲሆን በኪዬቭ ዳርቻ ላይ የሚገኙት ኖቭጎሮድ ሪፐብሊክ እና ቭላድሚር-ሱዝዳል የተባሉት ሁለት ክልሎች ለዘመናዊው የሩሲያ ሕዝብ መሠረት ሆኑ። በልዑል አሌክሳንደር ኔቪስኪ እየተመራ ኖቭጎሮድያውያን በ1240 በኔቫ ጦርነት ወራሪዎቹን ስዊድናውያን እንዲሁም በ1242 የጀርመናዊ የመስቀል ጦረኞችን በበረዶው ጦርነት አባረሩ። የሞስኮ ግራንድ ዱቺ ከኪየቫን ሩስ ጥፋት በኋላ የተፈጠረው በጣም ኃይለኛው የሞስኮ ግራንድ ዱቺ በመጀመሪያ የቭላድሚር-ሱዝዳል አካል ነበር። አሁንም በሞንጎሊያውያን ታታሮች ግዛት ሥር እና ከነሱ ጋር በመሆን ሞስኮ በ 14 ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ በአካባቢው ተጽእኖውን ማረጋገጥ ጀመረች, ቀስ በቀስ የሩስ አገሮችን እንደገና በማዋሃድ እና ሩሲያን በማስፋፋት ሂደት ውስጥ ግንባር ቀደም ኃይል ሆናለች. የሞስኮ የመጨረሻ ተቀናቃኝ የሆነው ኖቭጎሮድ ሪፐብሊክ እንደ ዋና የፀጉር ንግድ ማእከል እና የሃንሴቲክ ሊግ ምስራቃዊ ወደብ ሆነች ። በሞስኮ ልዑል ዲሚትሪ ዶንኮይ የሚመራው እና በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የታገዘው የተባበሩት መንግስታት ጦር በ 1380 በኩሊኮቮ ጦርነት በሞንጎሊያውያን ታታሮች ላይ ትልቅ ሽንፈትን አድርሷል ። ሞስኮ ቀስ በቀስ ወላጇን ቭላድሚር-ሱዝዳልን ወሰደ ፣ ከዚያም በዙሪያው እንደ እና ኖቭጎሮድ ያሉ ቀደምት ጠንካራ ተቀናቃኞችን ጨምሮ ርዕሰ ጉዳዮች። ኢቫን ("ታላቅ") በመጨረሻ ወርቃማው ሆርዴ ቁጥጥርን ጥሎ መላውን ሰሜናዊ ሩስን በሞስኮ ግዛት አዋህዶ "የሩስ ሁሉ ታላቅ መስፍን" የሚል ማዕረግ የወሰደ የመጀመሪያው የሩሲያ ገዥ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1453 ከቁስጥንጥንያ ውድቀት በኋላ ፣ ሞስኮ የምስራቅ ሮማን ኢምፓየር ቅርስ መሆኗን ተናግራለች። ኢቫን የመጨረሻው የባይዛንታይን ንጉሠ ነገሥት ቆስጠንጢኖስ የእህት ልጅ የሆነችውን ሶፊያ ፓላይኦሎጂን አገባ እና የባይዛንታይን ባለ ሁለት ጭንቅላት ንስርን የራሱ እና በመጨረሻም የሩሲያን ኮት ኦፍ-ክንድ አደረገው። ሳርዶኤም የሩሲያ የሦስተኛው ሮም ሀሳቦች እድገት ፣ ታላቁ መስፍን ኢቫን አራተኛ ("አስፈሪው") በ 1547 የሩሲያ የመጀመሪያ ንጉስ ዘውድ በይፋ ተቀበለ ። ዛር አዲስ የሕግ ኮድ አወጀ (የ 1550 ሱዲቢኒክ) ፣ የመጀመሪያውን የሩሲያ ፊውዳል ተወካይ አቋቋመ ። አካል (ዘምስኪ ሶቦር)፣ ወታደሩን አሻሽሎ፣ የቀሳውስቱን ተጽእኖ ገድቦ የአካባቢ አስተዳደርን አደራጀ። ኢቫን በረዥም የግዛት ዘመኑ ሦስቱን የታታር ካናቶችን ማለትም ካዛን እና አስትራካንን በቮልጋ እና በደቡብ ምዕራብ ሳይቤሪያ የሚገኘውን የሲቢርን ኻኔትን በማካተት ቀድሞውንም ትልቅ የነበረውን የሩሲያ ግዛት በእጥፍ ለማሳደግ ተቃርቧል። በመጨረሻም በ 16 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ሩሲያ ከኡራል ተራሮች በስተ ምሥራቅ ተስፋፍቷል. ሆኖም የዛርዶም የፖላንድ መንግሥት እና የሊቱዌኒያ ግራንድ ዱቺ ጥምረት (በኋላ የተባበሩት የፖላንድ-ሊቱዌኒያ ኮመንዌልዝ)፣ የስዊድን መንግሥት፣ እና ዴንማርክ–ኖርዌይ ጥምረት ላይ በተደረገው ረጅም እና ያልተሳካ የሊቮኒያ ጦርነት ተዳክሟል። የባልቲክ የባህር ዳርቻ እና የባህር ንግድ በ 1572 የክራይሚያ ታታሮች ወራሪ ጦር ወሳኝ በሆነው የሞሎዲ ጦርነት ሙሉ በሙሉ ተሸንፏል። የኢቫን ልጆች ሞት በ1598 የጥንቱ የሩሪክ ሥርወ መንግሥት ማብቃቱን የሚያመለክት ሲሆን በ1601–03 ከደረሰው አስከፊ ረሃብ ጋር ተዳምሮ የእርስ በርስ ጦርነት፣ የአስመሳዮች አገዛዝ እና የውጭ ጣልቃገብነት በችግር ጊዜ አስከትሏል። 17 ኛው ክፍለ ዘመን. የፖላንድ-ሊቱዌኒያ ኮመንዌልዝ የሩስያን ክፍሎች በመቆጣጠር ወደ ዋና ከተማዋ ሞስኮ ዘልቋል። በ1612 ፖላንዳውያን በነጋዴ ኩዝማ ሚኒን እና በልዑል ዲሚትሪ ፖዝሃርስኪ ​​የሚመራው በሩሲያ በጎ ፈቃደኞች ጓዶች ለማፈግፈግ ተገደው ነበር። የሮማኖቭ ሥርወ መንግሥት በ 1613 በዜምስኪ ሶቦር ውሳኔ ዙፋኑን ተቀበለ እና ሀገሪቱ ከችግር ቀስ በቀስ ማገገም ጀመረች ። ሩሲያ በ 17 ኛው ክፍለ ዘመን የግዛት እድገቷን ቀጥላለች, እሱም የኮሳክስ ዘመን ነበር. እ.ኤ.አ. በ 1654 የዩክሬን መሪ ቦህዳን ክሜልኒትስኪ ዩክሬንን በሩሲያ ንጉስ አሌክሲስ ጥበቃ ስር ለማድረግ አቅርበዋል ። የዚህ አቅርቦት ተቀባይነት ወደ ሌላ የሩስያ-ፖላንድ ጦርነት አመራ. በመጨረሻም ዩክሬን በዲኒፐር በኩል ተከፈለች, ምስራቃዊውን ክፍል (ግራ-ባንክ ዩክሬን እና ኪየቭ) በሩሲያ አገዛዝ ስር ትተው ነበር. በምስራቅ, ፈጣን የሩሲያ ፍለጋ እና ሰፊ የሳይቤሪያ ቅኝ ግዛት, ጠቃሚ የሆኑ ፀጉራሞችን እና የዝሆን ጥርስን ማደን ቀጠለ. የሩስያ አሳሾች በዋነኛነት በሳይቤሪያ ወንዝ መስመሮች በኩል ወደ ምሥራቅ ገፍተው ነበር፣ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ፣ በምሥራቃዊ ሳይቤሪያ፣ በቹክቺ ባሕረ ገብ መሬት፣ በአሙር ወንዝ እና በፓስፊክ ውቅያኖስ ዳርቻ ላይ የሩስያ ሰፈሮች ነበሩ። እ.ኤ.አ. በ 1648 ሴሚዮን ዴዥኒቭ በቤሪንግ ስትሬት ውስጥ ለመጓዝ የመጀመሪያው አውሮፓዊ ሆነ። አስያኢዊ ራሽያ በታላቁ ፒተር ሩሲያ በ 1721 ኢምፓየር ተባለች እና ከአውሮፓ ታላላቅ ሀይሎች አንዷ ሆነች። ከ1682 እስከ 1725 የገዛው ፒተር ስዊድንን በታላቁ ሰሜናዊ ጦርነት በማሸነፍ የሩሲያ የባህር እና የባህር ንግድ መዳረሻን አስገኘ። እ.ኤ.አ. በ 1703 ፣ በባልቲክ ባህር ፣ ፒተር ሴንት ፒተርስበርግ የሩሲያ ዋና ከተማ አድርጎ መሰረተ። በእሱ አገዛዝ ዘመን ሁሉ፣ ሰፊ ማሻሻያዎች ተደርገዋል፣ ይህም የምዕራብ አውሮፓውያን ባሕላዊ ተጽዕኖዎች በሩሲያ ላይ አመጡ። በ1741-62 የጴጥሮስ አንደኛ ሴት ልጅ ኤልዛቤት የግዛት ዘመን ሩሲያ በሰባት ዓመታት ጦርነት ውስጥ ተሳትፎዋን ተመልክቷል። በግጭቱ ወቅት የሩሲያ ወታደሮች ምስራቅ ፕራሻን አሸንፈዋል, አልፎ ተርፎም የበርሊን በር ደረሱ. ነገር ግን፣ ኤልዛቤት ስትሞት፣ እነዚህ ሁሉ ወረራዎች የፕሩሺያን ደጋፊ በሆኑት ሩሲያዊው ፒተር ሳልሳዊ ወደ ፕሩሺያ ግዛት ተመለሱ። በ 1762-96 የገዛው ካትሪን ("ታላቅ") የሩስያ የእውቀት ዘመንን ይመራ ነበር. በፖላንድ-ሊቱዌኒያ ኮመንዌልዝ ላይ የሩሲያ የፖለቲካ ቁጥጥርን አራዘመች እና አብዛኛዎቹን ግዛቶቿን ወደ ሩሲያ በመቀላቀል በአውሮፓ በሕዝብ ብዛት ቀዳሚ አድርጋለች። በደቡብ ከኦቶማን ኢምፓየር ጋር ከተካሄደው ስኬታማ የሩሶ-ቱርክ ጦርነቶች በኋላ ካትሪን የክሬሚያን ካንትን በማፍረስ እና ክራይሚያን በመቀላቀል የሩስያን ድንበር እስከ ጥቁር ባህር አድርጋለች። በሩሲያ-ፋርስ ጦርነቶች ቃጃር ኢራን ላይ ባደረገችው ድል በ19ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ ሩሲያ በካውካሰስ ከፍተኛ የግዛት እመርታ አስመዝግባለች። የካተሪን ተተኪ ልጇ ፖል ያልተረጋጋ እና በዋነኝነት የሚያተኩረው በቤት ውስጥ ጉዳዮች ላይ ነበር። አጭር የግዛት ዘመኑን ተከትሎ ካትሪን የ1ኛ አሌክሳንደር በ1809 ከተዳከመችው ስዊድን እና በ1812 ከኦቶማን ከቤሳራቢያን ፊንላንድ በመታጠቅ የካትሪን ስትራቴጂ ቀጥሏል። አላስካ በ 1803-1806 የመጀመሪያው የሩሲያ ሰርቪስ ተደረገ. በ 1820 አንድ የሩሲያ ጉዞ የአንታርክቲካ አህጉርን አገኘ. በናፖሊዮን ጦርነት ወቅት ሩሲያ ከተለያዩ የአውሮፓ ኃያላን መንግሥታት ጋር ኅብረትን በመቀላቀል ከፈረንሳይ ጋር ተዋግታለች። እ.ኤ.አ. በ 1812 በናፖሊዮን የስልጣን ከፍታ ላይ የፈረንሳይ ሩሲያን ወረራ ወደ ሞስኮ ደርሶ ነበር ፣ ግን በመጨረሻ ከቀዝቃዛው የሩሲያ ክረምት ጋር ተቀናጅቶ የነበረው ግትር ተቃውሞ በወራሪዎች ላይ አስከፊ ሽንፈት አስከትሏል ፣ ይህም የፓን-አውሮፓዊው ግራንዴ አርሜይ ፍጹም በሆነ ሁኔታ ገጥሞታል ። ጥፋት። በሚካሂል ኩቱዞቭ እና ሚካኤል አንድሪያስ ባርክሌይ ደ ቶሊ የሚመራው ኢምፔሪያል የሩሲያ ጦር ናፖሊዮንን አስወግዶ በስድስተኛው ጥምረት ጦርነት በመላው አውሮፓ በመንዳት በመጨረሻ ፓሪስ ገባ። አሌክሳንደር 1ኛ የሩስያ ልዑካንን በቪየና ኮንግረስ ተቆጣጠረ፣ ይህም የድህረ-ናፖሊዮን አውሮፓን ካርታ ይገልጻል። ናፖሊዮን ከሞስኮ ማፈግፈግ በአልብሬክት አዳም ። ናፖሊዮንን አሳድደው ወደ ምዕራብ አውሮፓ የገቡት መኮንኖች የሊበራሊዝም ሃሳቦችን ወደ ሩሲያ አመጡ እና እ.ኤ.አ. በአውሮፓ ውስጥ ያለው የሩሲያ ኃይል እና ተጽዕኖ በክራይሚያ ጦርነት ሽንፈት ተስተጓጎለ። የኒኮላስ ተተኪ አሌክሳንደር 2ኛ በ1861 የተካሄደውን የነፃ ማውጣት ማሻሻያ ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ ከፍተኛ ለውጦችን አድርጓል።እነዚህ ማሻሻያዎች ኢንደስትሪላይዜሽን አነሳስተዋል እና ከ1877 በኋላ ብዙ የባልካን ግዛቶችን ከኦቶማን አገዛዝ ነፃ ያወጣውን ኢምፔሪያል የሩሲያ ጦርን ዘመናዊ አድርጓል። -78 የሩስያ-ቱርክ ጦርነት. በአብዛኛው በ19ኛው እና በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ሩሲያ እና ብሪታንያ በአፍጋኒስታን እና በመካከለኛው እና በደቡብ እስያ በሚገኙ አጎራባች ግዛቶች ላይ ተስማሙ። በሁለቱ ዋና ዋና የአውሮፓ ግዛቶች መካከል የነበረው ፉክክር ታላቁ ጨዋታ በመባል ይታወቃል። በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በሩሲያ ውስጥ የተለያዩ የሶሻሊስት እንቅስቃሴዎች መነሳት ታይቷል. አሌክሳንደር 2ኛ በ1881 በአብዮታዊ አሸባሪዎች ተገደለ።የልጃቸው አሌክሳንደር የግዛት ዘመን ብዙም ሊበራል ግን የበለጠ ሰላማዊ ነበር። የመጨረሻው የሩሲያ ንጉሠ ነገሥት ኒኮላስ እ.ኤ.አ. በ 1905 በተካሄደው የሩሲያ አብዮት የተከሰቱትን ክስተቶች መከላከል አልቻለም ፣ በአዋራጅ የሩሶ-ጃፓን ጦርነት እና የደም እሑድ በመባል በሚታወቀው ማሳያ ክስተት የተነሳ። ህዝባዊ አመፁ ተቀምጧል፣ ነገር ግን መንግስት የመናገር እና የመሰብሰብ ነፃነቶችን መስጠትን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ህጋዊ ማድረግ እና የተመረጠ የህግ አውጭ አካል መመስረትን ጨምሮ ትላልቅ ማሻሻያዎችን (የ 1906 የሩሲያ ህገ-መንግስት) ለመቀበል ተገደደ። አብዮት እና የእርስ በርስ ጦርነት እ.ኤ.አ. በ 1914 ሩሲያ ወደ አንደኛው የዓለም ጦርነት የገባችው ኦስትሪያ-ሀንጋሪ በሩሲያ አጋር በሆነችው ሰርቢያ ላይ ጦርነት ባወጀችበት ወቅት ነው ፣ እና ከሦስትዮሽ ኢንተንቲ አጋሮች ስትገለል በተለያዩ ግንባሮች ተዋግታለች። እ.ኤ.አ. የኦስትሮ-ሃንጋሪ ጦር. ነገር ግን በጦርነቱ ዋጋ እየናረ በመምጣቱ፣ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳትና በሙስና እና የሀገር ክህደት ወሬዎች ቀድሞውንም የነበረው ህዝባዊ አመኔታ የጎደለው ነበር። ይህ ሁሉ በ 1917 የሩስያ አብዮት የአየር ንብረትን አቋቋመ, በሁለት ዋና ዋና ተግባራት ተከናውኗል. በ 1917 መጀመሪያ ላይ ኒኮላስ ለመልቀቅ ተገደደ; በሩሲያ የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት እሱ እና ቤተሰቡ በየካተሪንበርግ ታስረው ተገድለዋል. ንጉሣዊው ሥርዓት ራሱን ጊዜያዊ መንግሥት ብሎ ባወጀው በተናወጠ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥምረት ተተካ። ጊዜያዊ መንግሥት በመስከረም ወር የሩሲያ ሪፐብሊክን አወጀ. እ.ኤ.አ. ጥር 6 1918 የሩሲያ ሕገ-መንግሥታዊ ምክር ቤት ሩሲያ ዴሞክራሲያዊ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ (የጊዜያዊ መንግሥት ውሳኔን በማፅደቅ) አወጀ። በማግሥቱ የሕገ መንግሥት ጉባኤ በሁሉም የሩሲያ ማዕከላዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ፈረሰ። ቭላድሚር ሌኒን፣ ሊዮን ትሮትስኪ እና ሌቭ ካሜኔቭ በሶቪየት-ፖላንድ ጦርነት፣ ግንቦት 1 ቀን 1920 ወታደሮችን እንዲዋጉ አነሳሱ። ተለዋጭ የሶሻሊስት ተቋም በዴሞክራሲያዊ መንገድ በተመረጡት የሰራተኞች እና የገበሬዎች ምክር ቤቶች ፣ሶቪየትስ በሚባለው የፔትሮግራድ ሶቪየት ፣ ሥልጣኑን ይቆጣጠር ነበር። የአዲሶቹ ባለስልጣናት አገዛዝ ችግሩን ከመፍታት ይልቅ በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ቀውስ አባባሰው እና በመጨረሻም በቦልሼቪክ መሪ ቭላድሚር ሌኒን የሚመራው የጥቅምት አብዮት ጊዜያዊ መንግስትን አስወግዶ የሶቪዬት መንግስት ሙሉ የአስተዳደር ስልጣንን ሰጠ ፣ ይህም ለሶቪዬቶች መፈጠር ምክንያት ሆኗል ። በዓለም የመጀመሪያው የሶሻሊስት መንግሥት. የሩሲያ የእርስ በርስ ጦርነት በፀረ-ኮሚኒስት ነጭ እንቅስቃሴ እና በአዲሱ የሶቪየት አገዛዝ በቀይ ጦር መካከል ተከፈተ። ከአንደኛው የዓለም ጦርነት ማዕከላዊ ኃያላን ጋር ጦርነቱን ያጠናቀቀውን የብሬስት-ሊቶቭስክ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ; ቦልሼቪስት ሩሲያ 34% ህዝቧን ፣ 54% የኢንዱስትሪዎቿን ፣ 32% የእርሻ መሬቷን እና 90% የሚሆነውን የድንጋይ ከሰል ማዕድን የሚስተናገዱትን አብዛኛዎቹን ምዕራባዊ ግዛቶች አስረከበች። የተባበሩት መንግስታት ፀረ-ኮምኒስት ኃይሎችን ለመደገፍ ያልተሳካ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ጀመሩ። እስከዚያው ድረስ ሁለቱም የቦልሼቪኮች እና የነጭ ንቅናቄዎች ቀይ ሽብር እና ነጭ ሽብር በመባል የሚታወቁትን የማፈናቀል እና የሞት ቅስቀሳዎችን አድርገዋል። በአመጽ የእርስ በርስ ጦርነት ማብቂያ ላይ የሩሲያ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት በከፍተኛ ሁኔታ ተጎድቷል እና በጦርነቱ ወቅት 10 ሚሊዮን የሚደርሱት ጠፍተዋል, በአብዛኛው ሲቪሎች. ሚሊዮኖች ነጭ ኤሚግሬስ ሆነዋል, እና በ 1921-22 የሩስያ ረሃብ እስከ አምስት ሚሊዮን የሚደርሱ ተጎጂዎችን አጠፋ. ሶቪየት ህብረት በታህሳስ 30 ቀን 1922 ሌኒን እና ረዳቶቹ የሶቪየት ህብረትን አቋቋሙ ፣ የሩሲያ ኤስኤፍኤስአርን ከባይሎሩሺያን ፣ ትራንስካውካሲያን እና የዩክሬን ሪፐብሊኮች ጋር አንድ ነጠላ ግዛት ውስጥ በመቀላቀል ። በመጨረሻም የውስጥ የድንበር ለውጦች እና መቀላቀል በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የ 15 ሪፐብሊኮች ህብረት ፈጠረ ። በብዛቱ እና በሕዝብ ብዛት ትልቁ የሩስያ ኤስኤፍኤስአር ነው፣ እሱም ህብረቱን በሙሉ ታሪኩ በፖለቲካ፣ በባህላዊ እና በኢኮኖሚ የበላይ አድርጎታል። በ1924 የሌኒን ሞት ተከትሎ፣ ትሮይካ እንዲቆጣጠር ተሾመ። በመጨረሻም የኮሚኒስት ፓርቲ ዋና ፀሀፊ ጆሴፍ ስታሊን ሁሉንም ተቃዋሚዎች በማፈን ስልጣኑን በእጁ በማጠናከር በ1930ዎቹ የሀገሪቱ አምባገነን ለመሆን ችሏል። የዓለም አብዮት ዋነኛ አራማጅ የሆነው ሊዮን ትሮትስኪ በ1929 ከሶቭየት ኅብረት ተሰደደ።የስታሊን የሶሻሊዝም ሃሳብ በአንድ ሀገር ውስጥ ይፋዊ መስመር ሆነ።በቦልሼቪክ ፓርቲ ውስጥ የቀጠለው የውስጥ ትግል በታላቁ ጽዳት ተጠናቀቀ። በስታሊን መሪነት፣ መንግስት የዕዝ ኢኮኖሚ፣ አብዛኛው የገጠር ሀገሪቱን ኢንዱስትሪያላይዜሽን እና የግብርናውን መሰብሰብ ጀመረ። በዚህ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ለውጥ ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የስታሊንን አገዛዝ በመቃወም ወይም በተጠረጠሩበት ወቅት ብዙ የፖለቲካ ወንጀለኞችን ጨምሮ ወደ ቅጣት የጉልበት ካምፖች ተላኩ። እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩት ተፈናቅለው ወደ ሶቪየት ዩኒየን ርቀው ወደሚገኙ አካባቢዎች ተወሰዱ።የሀገሪቱ የግብርና ሽግግር ሽግግር፣ከአስቸጋሪ የመንግስት ፖሊሲዎች እና ድርቅ ጋር ተዳምሮ በ1932–1933 የሶቪየትን ረሃብ አስከተለ። ይህም እስከ 8.7 ሚሊዮን ገደለ።ሶቭየት ኅብረት በመጨረሻ ከግብርና ኢኮኖሚ ወደ ትልቅ የኢንዱስትሪ ሃይል በአጭር ጊዜ ውስጥ ውድ የሆነ ለውጥ አደረገ። ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሶቪየት ኅብረት መስከረም ፲፯ ቀን ፲፱፻፴፱ ዓ.ም ፖላንድን በመውረር ወደ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት የገባችው በሞሎቶቭ – ሪበንትሮፕ ከናዚ ጀርመን ጋር በተደረገው ሚስጥራዊ ፕሮቶኮል መሠረት ነው። ሶቪየት ኅብረት በኋላ ፊንላንድን ወረረ፣ እናም የባልቲክ ግዛቶችን፣ እንዲሁም የሮማኒያን አንዳንድ ክፍሎች ተቆጣጠረ።፡ 91–95 ሰኔ 22 ቀን 1941 ጀርመን ሶቪየት ኅብረትን ወረረች፣ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ትልቁን የምስራቅ ግንባርን ከፈተች።: በመጨረሻም 5 ሚሊዮን የሚጠጉ የቀይ ጦር ወታደሮች በናዚዎች ተማርከዋል፤፡ 272 የጄኔራል ፕላን ኦስትን ለመፈጸም እንደፈለገ የኋለኛው 3.3 ሚሊዮን የሶቪዬት ጦር ኃይሎች እና እጅግ በጣም ብዙ ሰላማዊ ዜጎችን ገደለ። 175–186 ዌርማችቶች ቀደምት ስኬት ቢኖራቸውም ጥቃታቸው በሞስኮ ጦርነት ቆመ። በመቀጠልም ጀርመኖች በ1942-43 ክረምት መጀመሪያ በስታሊንግራድ ጦርነት እና በኩርስክ ጦርነት በ1943 የበጋ ወቅት ትልቅ ሽንፈት ደርሶባቸዋል።ሌላኛው የጀርመን ውድቀት ከተማዋ ሙሉ በሙሉ የነበረችበት የሌኒንግራድ ከበባ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1941 እና በ 1944 መካከል በጀርመን እና በፊንላንድ ኃይሎች መሬት ላይ ተከልክሏል ፣ እናም በረሃብ እና ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሞተ ፣ ግን በጭራሽ እጅ አልሰጠም። በ1944–45 የሶቪየት ጦር በምስራቅ እና በመካከለኛው አውሮፓ ተዘዋውሮ በርሊንን በግንቦት 1945 ያዘ። በነሐሴ 1945 የሶቪየት ጦር ማንቹሪያን ወረረ እና ጃፓናውያንን ከሰሜን ምስራቅ እስያ በማባረር በጃፓን ላይ ለተካሄደው ድል አስተዋጽኦ አድርጓል። የ 1941-45 የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ በሩሲያ ውስጥ እንደ ታላቁ የአርበኝነት ጦርነት ይታወቃል. በሶቪየት ኅብረት ከዩናይትድ ስቴትስ፣ ዩናይትድ ኪንግደም እና ቻይና ጋር በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ውስጥ እንደ ትልቅ አራት የሕብረት ኃይሎች ተደርገው ይቆጠሩ ነበር ፣ እና በኋላ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት መሠረት የሆነው አራቱ ፖሊሶች ሆነዋል።: 27 ጦርነት፣ የሶቪየት ሲቪል እና ወታደራዊ ሞት ከ26-27 ሚሊዮን ገደማ ሲሆን ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሰለባዎች ግማሹን ይይዛል።፡ 295 የሶቪየት ኢኮኖሚ እና መሰረተ ልማት ከፍተኛ ውድመት ደርሶባቸዋል፣ ይህም የሶቪየትን ረሃብ በ1946–47 አስከተለ። ይሁን እንጂ ብዙ መስዋዕትነት በመክፈል የሶቪየት ኅብረት ዓለም አቀፍ ልዕለ ኃያል ሆና ተገኘች። ቀዝቃዛ ጦርነት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የፖትስዳም ኮንፈረንስ እንደገለፀው የምስራቅ እና መካከለኛው አውሮፓ ክፍሎች ፣ምስራቅ ጀርመን እና ምስራቃዊ የኦስትሪያ ክፍሎች በቀይ ጦር ተይዘዋል ። በምስራቅ ብሎክ ሳተላይት መንግስታት ላይ ጥገኛ የሆኑ የኮሚኒስት መንግስታት ተተከሉ።የአለም ሁለተኛዋ የኒውክሌር ሃይል ከሆነች በኋላ፣ሶቭየት ህብረት የዋርሶ ስምምነትን በመመስረት፣ቀዝቃዛው ጦርነት እየተባለ ከሚጠራው እና ከተቀናቃኙ አሜሪካ እና ኔቶ. እ.ኤ.አ. ክሩሽቼቭ ታው. በተመሳሳይ የዩናይትድ ስቴትስ ጁፒተር ሚሳኤሎች ወደ ቱርክ እና የሶቪየት ሚሳኤሎች በኩባ ስለመዘርጋቷ ሁለቱ ተቀናቃኞች ሲጋጩ የቀዝቃዛው ጦርነት ውጥረቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። እ.ኤ.አ. በ 1957 የሶቭየት ኅብረት በዓለም የመጀመሪያውን ሰው ሰራሽ ሳተላይት ስፑትኒክ 1 አመጠቀች ፣ በዚህም የጠፈር ዘመን ተጀመረ። እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 12 ቀን 1961 ቮስቶክ 1 ሰው በያዘው የጠፈር መንኮራኩር በመሳፈር ምድርን በመዞር የመጀመሪያው ሰው የሆነው ሩሲያዊው ኮስሞናዊት ዩሪ ጋጋሪን ሆነ። እ.ኤ.አ. የ1970ዎቹ እና የ1980ዎቹ መጀመሪያ ዘመን ከጊዜ በኋላ የመቀዛቀዝ ዘመን ተብሎ ተሰየመ። እ.ኤ.አ. በ 1965 የተካሄደው የ ተሃድሶ የሶቪዬት ኢኮኖሚን ​​በከፊል ያልተማከለ ነው ። እ.ኤ.አ. በ 1979 በአፍጋኒስታን በኮሚኒስት መሪነት አብዮት ከተካሄደ በኋላ የሶቪየት ኃይሎች አገሪቱን ወረሩ ፣ በመጨረሻም የሶቪየት-አፍጋኒስታን ጦርነት ጀመሩ ። በግንቦት 1988 ፣ ሶቪየቶች ከአፍጋኒስታን መውጣት ጀመሩ ፣ በአለም አቀፍ ተቃውሞ ፣ የማያቋርጥ ፀረ-ሶቪየት የሽምቅ ጦርነት ፣ እና የሶቪየት ዜጎች ድጋፍ እጦት. እ.ኤ.አ. ከ1985 ጀምሮ በሶቭየት ሥርዓት ውስጥ ሊበራል ማሻሻያዎችን ለማድረግ የፈለጉት የመጨረሻው የሶቪየት መሪ ሚካሂል ጎርባቾቭ የ (ክፍትነት) እና የፔሬስትሮይካ (መዋቅር) ፖሊሲዎችን በማስተዋወቅ የኤኮኖሚው መቀዛቀዝ ጊዜን ለማቆም እና መንግሥትን ወደ ዴሞክራሲ ለማምጣት በመሞከር ነበር። . ይህ ግን በመላ ሀገሪቱ ጠንካራ ብሔርተኝነት እና ተገንጣይ እንቅስቃሴዎች እንዲነሱ አድርጓል። ከ 1991 በፊት የሶቪየት ኢኮኖሚ በዓለም ሁለተኛ ደረጃ ላይ ነበር, ነገር ግን በመጨረሻዎቹ ዓመታት ውስጥ, ቀውስ ውስጥ ገባ. እ.ኤ.አ. በ 1991 የባልቲክ ግዛቶች ከሶቪየት ኅብረት ለመገንጠል በመረጡበት ወቅት ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ውዥንብር መቀቀል ጀመረ ። እ.ኤ.አ. መጋቢት 17 ቀን ህዝበ ውሳኔ ተካሂዷል፣ አብዛኞቹ ተሳታፊ ዜጎች ሶቭየት ህብረትን ወደ አዲስ ፌዴሬሽን ለመቀየር ድምጽ የሰጡበት። እ.ኤ.አ ሰኔ 1991 ቦሪስ የልሲን የሩስያ ኤስኤፍኤስአር ፕሬዝዳንት ሆነው ሲመረጡ በሩሲያ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው በቀጥታ የተመረጠ ፕሬዝዳንት ሆነ።በነሐሴ 1991 በጎርባቾቭ መንግስት አባላት መፈንቅለ መንግስት ሙከራ በጎርባቾቭ ላይ ያነጣጠረ እና ሶቭየትን ለመጠበቅ ያለመ ነው። ዩኒየን በምትኩ የሶቪየት ዩኒየን ኮሚኒስት ፓርቲ ፍጻሜ አደረሰ። እ.ኤ.አ. በታህሳስ 25 ቀን 1991 የሶቪዬት ህብረት መፍረስ ፣ ከዘመናዊቷ ሩሲያ ጋር ፣ ከሶቪየት-ሶቪየት በኋላ አስራ አራት ሌሎች መንግስታት ብቅ አሉ። ድህረ-ሶቪየት ሩሲያ (1991-አሁን) የሶቭየት ህብረት ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ውድቀት ሩሲያን ወደ ጥልቅ እና ረዥም የመንፈስ ጭንቀት ዳርጓታል. በሶቪየት ኅብረት መፍረስ ወቅት እና በኋላ፣ የፕራይቬታይዜሽን እና የገበያ እና የንግድ ነፃነትን ጨምሮ ሰፊ ማሻሻያዎች ተካሂደዋል፣ በ"" መስመር ላይ ሥር ነቀል ለውጦች ተካሂደዋል። ወደ ፕራይቬታይዜሽን መሸጋገሩ በዋነኛነት የኢንተርፕራይዞችን ቁጥጥር ከመንግስት ኤጀንሲዎች ወደ በመንግስት ውስጥ ውስጣዊ ግንኙነት ወደሌላቸው ግለሰቦች ቀይሮታል፣ይህም አስነዋሪዎቹ የሩሲያ ኦሊጋርቾች እንዲነሱ አድርጓል። ብዙዎቹ አዲስ ሀብታሞች በከፍተኛ የካፒታል በረራ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ጥሬ ገንዘብ እና ንብረቶችን ከአገሪቱ ውጭ አንቀሳቅሰዋል። በኢኮኖሚው ውስጥ ያለው ጭንቀት የማህበራዊ አገልግሎቶች ውድቀትን አስከትሏል-የልደት መጠን አሽቆለቆለ የሞት መጠን ሲጨምር እና ሚሊዮኖች ወደ ድህነት ገቡ; ከፍተኛ ሙስና፣ እንዲሁም የወንጀለኞች ቡድኖች እና የተደራጁ ወንጀሎች በከፍተኛ ሁኔታ ጨምረዋል። እ.ኤ.አ. በ 1993 መገባደጃ ላይ በየልሲን እና በሩሲያ ፓርላማ መካከል የነበረው አለመግባባት በሕገ መንግሥታዊ ቀውስ ተጠናቀቀ ይህም በወታደራዊ ኃይል በኃይል አብቅቷል ። በችግር ጊዜ ዬልሲን በምዕራባውያን መንግስታት የተደገፈ ሲሆን ከ 100 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ። በታህሳስ ወር ህዝበ ውሳኔ ተካሂዶ ጸድቋል ፣ ይህም አዲስ ሕገ መንግሥት በማውጣት ለፕሬዚዳንቱ ትልቅ ስልጣን ሰጠ ። እ.ኤ.አ. በ1990ዎቹ በሰሜን ካውካሰስ በትጥቅ ግጭቶች ፣በአካባቢው የጎሳ ግጭቶች እና ተገንጣይ እስላማዊ አመጾች ታመው ነበር። በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ የቼቼን ተገንጣዮች ነፃነታቸውን ካወጁበት ጊዜ አንስቶ ጊዜያዊ የሽምቅ ውጊያ በአማፂ ቡድኖች እና በሩሲያ ጦር መካከል ተካሄዷል። በንፁሀን ዜጎች ላይ የሽብር ጥቃት በቼቼን ተገንጣዮች የተፈፀመ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ የሩሲያ ንፁሀን ዜጎች ህይወት ቀጥፏል። ከሶቪየት ኅብረት መፍረስ በኋላ ሩሲያ የኋለኛውን የውጭ ዕዳዎች ለመፍታት ኃላፊነቷን ወሰደች. እ.ኤ.አ. በ 1992 አብዛኛው የሸማቾች የዋጋ ቁጥጥሮች ጠፍተዋል ፣ ይህም ከፍተኛ የዋጋ ግሽበትን አስከትሏል እና የሩብልን ዋጋ በእጅጉ አሳንሷል። ከፍተኛ የበጀት ጉድለቶች ከካፒታል በረራ መጨመር እና ዕዳዎችን ለመክፈል አለመቻል በ 1998 የሩሲያ የፋይናንስ ቀውስ አስከትሏል, ይህም ተጨማሪ የሀገር ውስጥ ምርት ማሽቆልቆልን አስከትሏል. የፑቲን ዘመን እ.ኤ.አ. በታህሳስ 31 ቀን 1999 ፕሬዝዳንት የልሲን ባልተጠበቀ ሁኔታ ሥልጣናቸውን ለቀው በቅርቡ ለተሾሙት ጠቅላይ ሚኒስትር እና ለተመረጡት ቭላድሚር ፑቲን ሹመት ሰጥተዋል። ዬልሲን ቢሮውን በሰፊው ተወዳጅነት ያላገኘ ሲሆን በአንዳንድ ግምቶች 2% ዝቅተኛ የማጽደቅ ደረጃ ተሰጥቶታል። ከዚያም ፑቲን እ.ኤ.አ. በ 2000 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸንፈዋል ፣ እናም የቼቼን አማፂያን አፍኑ። ፑቲን እ.ኤ.አ. በ 2004 ለሁለተኛ ጊዜ የፕሬዝዳንትነት ጊዜ አሸንፈዋል ። በከፍተኛ የነዳጅ ዋጋ ፣ የውጭ ኢንቨስትመንት መጨመር እና ጥንቃቄ የተሞላበት ኢኮኖሚያዊ እና የፊስካል ፖሊሲዎች ፣ የሩሲያ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ሁኔታ አደገ ። በከፍተኛ ደረጃ የሩሲያን የኑሮ ደረጃ ማሻሻል እና በአለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ ያለውን ተጽእኖ ማሳደግ. የፑቲን አገዛዝ መረጋጋትን ጨምሯል፣ ሩሲያን ወደ ፈላጭ ቆራጭ ሀገርነት ሲቀይር። እ.ኤ.አ. መጋቢት 2 ቀን 2008 ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ ፑቲን ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሆኑ ህገ መንግስቱ ፑቲንን ለሶስተኛ ተከታታይ የፕሬዝዳንታዊ የስልጣን ዘመን እንዳያገለግሉ ከልክሏል። እ.ኤ.አ. በ2012 የተካሄደውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ተከትሎ ፑቲን ወደ ፕሬዝዳንትነት የተመለሱ ሲሆን ሜድቬዴቭ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። ይህ የአራት አመት የጋራ አመራር በሁለቱ ሀገራት መካከል "ታንድ ዲሞክራሲ" በውጭ ሚዲያዎች የተቀረፀ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2014 ፑቲን የክሬሚያን ፓርላማ ለመያዝ የሩሲያ ወታደሮችን ወደ ዩክሬን በማሰማራቱ ክሬሚያን እንድትቆጣጠር አድርጓል። ከዚህ በኋላ ሩሲያ ክሪሚያን መግዛቷ እና ከዚያ በፊት የተካሄደው ህዝበ ውሳኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ሳይሰጠው ቆይቶ በምዕራቡ ዓለም ሀገራት ማዕቀብ እንዲጣል ምክንያት ሆኗል፤ ይህን ተከትሎም የሩሲያ መንግስት በሁለተኛው ላይ የጸረ-ማዕቀብ ምላሽ ሰጥቷል። እ.ኤ.አ. በማርች 2018 ፑቲን በአጠቃላይ ለአራተኛው የፕሬዝዳንት ጊዜ ተመርጧል። እ.ኤ.አ. በጥር 2020 በህገ-መንግስቱ ላይ ጉልህ ማሻሻያዎች ቀርበዋል ፣ ከሀምሌ ወር ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ፣ ይህም ፑቲን አሁን ያለው የስልጣን ጊዜ ካለቀ በኋላ ለሁለት ተጨማሪ የስድስት ዓመታት ፕሬዝዳንታዊ የስልጣን ዘመን እንዲወዳደር አስችሎታል። እ.ኤ.አ. የካቲት 24 ቀን 2022 ሩሲያ በዩክሬን ላይ ወረራ ጀመረች። በ 06:00 በሞስኮ ሰዓት ፑቲን በዩክሬን ወታደራዊ ዘመቻ እንደሚካሄድ አስታውቋል; ከደቂቃዎች በኋላ የዩክሬን ከተሞች በሚሳኤል ጥቃት ደረሰባቸው። የመሬት አቀማመጥ ሩሲያ በአውሮፓ ምሥራቃዊ ክፍል እና በእስያ ሰሜናዊ ጫፍ ላይ በስፋት የተዘረጋች አህጉር አቋራጭ ሀገር ነች። የዩራሺያ ሰሜናዊውን ጫፍ ይሸፍናል; እና ከ37,653 ኪሜ (23,396 ማይል) በላይ የሚሸፍነው በዓለም አራተኛው ረጅሙ የባህር ዳርቻ አለው። ሩሲያ በኬክሮስ 41° እና 82° ፣ እና ኬንትሮስ 19° እና 169°፡ 9,000 ኪሜ (5,600 ማይል) ከምስራቅ ወደ ምዕራብ እና ከ2,500 እስከ 4,000 ኪሜ (ከ1,600 እስከ 2,500 ማይል) ከሰሜን ወደ ደቡብ ትዘረጋለች። በመሬት ስፋት፣ ከሶስት አህጉራት የሚበልጥ ሲሆን ከፕሉቶ ጋር ተመሳሳይ የሆነ የገጽታ ስፋት አለው። ሩሲያ ዘጠኝ ዋና ዋና የተራራ ሰንሰለቶች ያሏት ሲሆን እነሱም በካውካሰስ ተራሮች ላይ ጉልህ የሆነ ክፍል የሚጋሩት በደቡብ ምዕራብ ክልሎች ይገኛሉ (በሩሲያ እና በአውሮፓ 5,642 ሜትር (18,510 ጫማ) ከፍታ ያለው የኤልብሩስ ተራራን ይይዛል); በሳይቤሪያ ውስጥ የአልታይ እና የሳያን ተራሮች; እና በምስራቅ የሳይቤሪያ ተራሮች እና በሩሲያ ሩቅ ምስራቅ ውስጥ በካምቻትካ ባሕረ ገብ መሬት (, በ 4,750 ሜትር (15,584 ጫማ) በዩራሲያ ውስጥ ከፍተኛው ንቁ እሳተ ገሞራ ነው) የያዘ. የኡራል ተራሮች ከሰሜን ወደ ደቡብ በሀገሪቱ ምዕራብ በኩል የሚጓዙት በማዕድን ሀብት የበለፀጉ እና በአውሮፓ እና በእስያ መካከል ባህላዊ ድንበር ይመሰርታሉ። ሩሲያ ከሶስት ውቅያኖሶች ጋር ከሚዋሰኑ የአለም ሁለት ሀገራት አንዷ እንደመሆኗ መጠን ከብዙ ባህር ጋር ትስስር አላት። ዋና ደሴቶቹ እና ደሴቶቹ ኖቫያ ዘምሊያ፣ ፍራንዝ ጆሴፍ መሬት፣ ሰቬርናያ ዘምሊያ፣ አዲሱ የሳይቤሪያ ደሴቶች፣ ፣ የኩሪል ደሴቶች እና ሳክሃሊን ያካትታሉ። በሩሲያ እና በዩናይትድ ስቴትስ የሚተዳደረው የዲዮሜድ ደሴቶች በ3.8 ኪሜ (2.4 ማይል) ልዩነት አላቸው። እና ኩናሺር ደሴት የኩሪል ደሴቶች ከሆካይዶ፣ ጃፓን 20 ኪሜ (12.4 ማይል) ብቻ ይርቃሉ። ከ100,000 በላይ ወንዞች መኖሪያ የሆነችው ሩሲያ ከአለም ትልቁ የገጸ ምድር የውሃ ሃብት አንዱ ያላት ሲሆን ሀይቆቿ በግምት አንድ አራተኛ የሚሆነውን የአለም ፈሳሽ ውሃ ይይዛሉ። የባይካል ሀይቅ ትልቁ እና ከሩሲያ ንጹህ የውሃ አካላት መካከል በጣም ታዋቂው የአለም ጥልቅ ፣ ንፁህ ፣ ጥንታዊ እና በጣም አቅም ያለው ንጹህ ውሃ ሀይቅ ነው ፣ ከአለም ንፁህ የገጽታ ውሃ ከአንድ አምስተኛ በላይ ይይዛል። በሰሜን ምዕራብ ሩሲያ የሚገኙት ላዶጋ እና ኦኔጋ በአውሮፓ ከሚገኙት ትላልቅ ሀይቆች መካከል ሁለቱ ናቸው። በአጠቃላይ ታዳሽ የውሃ ሀብቶች ሩሲያ ከብራዚል ቀጥሎ ሁለተኛ ነች። በምዕራብ ሩሲያ የሚገኘው ቮልጋ፣ እንደ ሩሲያ ብሔራዊ ወንዝ በሰፊው የሚነገርለት በአውሮፓ ውስጥ ረጅሙ ወንዝ ነው። በሳይቤሪያ የሚገኙት የኦብ፣ የኒሴይ፣ የሌና እና የአሙር ወንዞች ከአለም ረዣዥም ወንዞች መካከል ናቸው። 2 ጥንታዊ መድረኮችን የሚለየው የኡራል-ሞንጎሊያ ኤፒፓልዮዞይክ የታጠፈ ቀበቶ መዋቅር ውስጥ የ ሪፊን ፣ ባይካል ሳላይር, ካሌዶኒያኛ እና ሄርሲኒያን የታጠፈ ቦታዎች አሉ. የየኒሴይ-ሳያን-ባይካል የሪፊያን እና የባይካል ማጠፍያ የሳይቤሪያ መድረክን ያዘጋጃል። ከምስራቃዊ አውሮፓ መድረክ ጋር ባለው ድንበር ላይ፣ በፔርሚያን ስትራታ የተሞላው የሲስ-ኡራል የኅዳግ ገንዳ በሰሜን ውስጥ ጠንካራ የድንጋይ ከሰል እና በገንዳው መካከለኛ ክፍል ውስጥ የፖታስየም ጨዎችን (ኡራልን ይመልከቱ)። በሩሲያ ግዛት ላይ ያለው የፓሲፊክ የታጠፈ ቀበቶ በከፍተኛ ሰሜናዊ ምዕራብ ክፍል ይወከላል ፣ በውስጡም ጥንታዊ የቅድመ-ሪፊያን ግዙፍ ፣ የሜሶዞይክ እና የሴኖዞይክ ማጠፍያ አካባቢዎች እና ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ንቁ ዞኖች ይገኛሉ። በቬርኮያንስክ-ቹኮትካ ክልል ውስጥ የወርቅ ክምችቶች ከጁራሲክ እና የታችኛው ክሪቴሴየስ ግራናይት ወረራዎች እንዲሁም ከቲን፣ ከተንግስተን እና ከሜርኩሪ ጋር ተያይዘው ይታወቃሉ። ትላልቅ የድንጋይ ከሰል ክምችቶች በ ገንዳ እና በዚሪያንስክ የመንፈስ ጭንቀት ውስጥ በሚገኙ ሞላሰስ ውስጥ ይገኛሉ. የምእራብ ካምቻትካ የታጠፈ ስርዓት የላይኛው ክሪታሴየስ ጂኦሳይክሊናል ውስብስብ ነው፣ እሱም በግራናይት-ግኒዝ እና ሼል-ማፊክ ምድር ቤት ላይ ተደራርቦ ነበር፣ እና ከታጠፈ በኋላ በፓሊዮጂን-ኒኦጂን ዓለቶች ተሸፍኗል። የምስራቃዊው ዞን በተደራረቡ ዘመናዊ እሳተ ገሞራዎች (28 ንቁ እሳተ ገሞራዎች) ይታወቃል. የኩሪል ደሴት አርክ ታላቁ እና ትንሹ ሪጅስ 39 ንቁ እሳተ ገሞራዎች ያሉት ሲሆን ክሪታሴየስ እና ኳተርንሪ የእሳተ ገሞራ- ደለል እና የእሳተ ገሞራ ፍጥረታት ናቸው። የ ቅስት ወጣት ሥርዓት የተከፋፈለ ነው, እና ፊት ለፊት, እንዲሁም በካምቻትካ ምሥራቃዊ ክፍል ፊት ለፊት, ጥልቅ-የውሃ ቦይ አለ. የሳክሃሊን ሴኖዞይክ የታጠፈ ክልል በማዕከላዊ ሳክሃሊን ግራበን ተለያይቶ ወደ ምስራቃዊ እና ምዕራባዊ ዞኖች የተከፈለ ነው። የነዳጅ እና የጋዝ ክምችቶች ከሰሜን ሳካሊን ዲፕሬሽን ጋር የተቆራኙ ናቸው, እና የድንጋይ ከሰል ክምችቶች በደሴቲቱ ላይ ከሚገኙት የመካከለኛው ሚዮሴን ድንጋዮች ጋር የተቆራኙ ናቸው. የአየር ንብረት የሩሲያ ስፋት እና የብዙዎቹ አከባቢዎች ከባህር ርቀው የሚገኙት ከታንድራ እና ከደቡብ ምዕራብ ጽንፍ በስተቀር በአብዛኛዎቹ የአገሪቱ ክፍሎች እርጥበት ያለው አህጉራዊ የአየር ንብረት የበላይነትን ያስከትላል። በደቡብ እና በምስራቅ የሚገኙት የተራራ ሰንሰለቶች ከህንድ እና ፓሲፊክ ውቅያኖሶች የሚነሳውን የሞቀ አየር ፍሰት ያደናቅፋሉ ፣ የአውሮፓ ሜዳ በምእራብ እና በሰሜን በኩል በአትላንቲክ እና በአርክቲክ ውቅያኖሶች ላይ ተጽዕኖ እንዲያሳድር ይከፍታል። አብዛኛው የሰሜን ምዕራብ ሩሲያ እና ሳይቤሪያ የከርሰ ምድር አየር ንብረት አላቸው፣ በሰሜን ምስራቅ ሳይቤሪያ ውስጣዊ ክልሎች እጅግ በጣም ከባድ ክረምት (በአብዛኛው ሳካሃ፣ ቀዝቃዛው ሰሜናዊ ዋልታ የሚገኝበት እና ዝቅተኛ የሙቀት መጠን -71.2 ° ሴ ወይም -96.2 °) እና የበለጠ መጠነኛ ክረምት በሌላ ቦታ። በአርክቲክ ውቅያኖስ አቅራቢያ ያለው ሰፊ የሩሲያ የባህር ዳርቻ እና የሩሲያ አርክቲክ ደሴቶች የዋልታ የአየር ንብረት አላቸው። በጥቁር ባህር ላይ ያለው የክራስኖዶር ክራይ የባህር ዳርቻ ክፍል በተለይም ሶቺ እና አንዳንድ የሰሜን ካውካሰስ የባህር ዳርቻ እና የውስጥ ክፍልፋዮች እርጥብ እና እርጥብ ክረምት ያለው እርጥብ የአየር ንብረት አላቸው። በብዙ የምስራቅ ሳይቤሪያ እና የሩሲያ ሩቅ ምስራቅ ክልሎች ክረምቱ ከበጋ ጋር ሲወዳደር ደረቅ ነው; ሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች በየወቅቱ የበለጠ ዝናብ ያጋጥማቸዋል። በአብዛኛዎቹ የአገሪቱ ክፍሎች የክረምት ዝናብ እንደ በረዶ ይወርዳል። የምዕራባዊው የካሊኒንግራድ ክልል ክፍሎች እና በደቡባዊ ክራስኖዶር ክራይ እና በሰሜን ካውካሰስ አንዳንድ ክፍሎች የውቅያኖስ የአየር ንብረት አላቸው። በታችኛው ቮልጋ እና ካስፒያን ባህር ዳርቻ ያለው ክልል እንዲሁም አንዳንድ ደቡባዊ የሳይቤሪያ ቁንጮዎች በከፊል ደረቃማ የአየር ጠባይ አላቸው። በአብዛኛዎቹ ክልሎች ውስጥ ሁለት የተለያዩ ወቅቶች ብቻ ናቸው, ክረምት እና በጋ; እንደ ጸደይ እና መኸር በአብዛኛው በጣም ዝቅተኛ እና እጅግ በጣም ከፍተኛ በሆነ የሙቀት መጠን መካከል አጭር የለውጥ ወቅቶች ናቸው. በጣም ቀዝቃዛው ወር ጥር (የካቲት በባህር ዳርቻ ላይ); በጣም ሞቃት ብዙውን ጊዜ ሐምሌ ነው። ከፍተኛ የሙቀት መጠኖች የተለመዱ ናቸው። በክረምት ወቅት የሙቀት መጠኑ ከደቡብ እስከ ሰሜን እና ከምዕራብ ወደ ምስራቅ ይበርዳል። በሳይቤሪያ ውስጥ እንኳን ክረምቱ በጣም ሞቃት ሊሆን ይችላል. ብዝሃ ህይወት ሩሲያ ግዙፍ በሆነ መጠንዋ ምክንያት የዋልታ በረሃዎች፣ ታንድራ፣ የደን ታንድራ፣ ታይጋ፣ የተቀላቀለ እና ሰፊ ደን፣ የደን ስቴፔ፣ ስቴፔ፣ ከፊል በረሃ እና የሐሩር ክልልን ጨምሮ የተለያዩ ስነ-ምህዳሮች አሏት። ከሩሲያ ግዛት ውስጥ ግማሽ ያህሉ በደን የተሸፈነ ነው, እና በዓለም ላይ ትልቁ የደን ክምችት አለው, እሱም "የአውሮፓ ሳንባ" በመባል ይታወቃል; በሚወስደው የካርቦን ዳይኦክሳይድ መጠን ከአማዞን ደን ቀጥሎ ሁለተኛ ነው። የሩስያ ብዝሃ ህይወት 12,500 የቫስኩላር ተክሎች, 2,200 የብሪዮፊት ዝርያዎች, 3,000 የሚያህሉ የሊች ዝርያዎች, 7,000-9,000 የአልጌ ዝርያዎች እና 20,000-25,000 የፈንገስ ዝርያዎችን ያጠቃልላል. የሩሲያ እንስሳት ከ 320 በላይ አጥቢ እንስሳት ፣ ከ 732 በላይ የአእዋፍ ዝርያዎች ፣ 75 የሚሳቡ እንስሳት ፣ ወደ 30 የሚጠጉ የአምፊቢያን ዝርያዎች ፣ 343 የንፁህ ውሃ ዓሳ ዝርያዎች (ከፍተኛ ኤንደምዝም) ፣ በግምት 1,500 የጨው ውሃ ዓሳ ፣ 9 የሳይክሎስቶማታ ዝርያዎች እና በግምት 100-150,000 ኢንቬርቴብራቶች (ከፍተኛ የደም መፍሰስ). በግምት 1,100 የሚሆኑ ብርቅዬ እና ሊጠፉ የተቃረቡ የእፅዋት እና የእንስሳት ዝርያዎች በሩሲያ ቀይ መረጃ መጽሐፍ ውስጥ ተካትተዋል። የሩስያ ሙሉ በሙሉ ተፈጥሯዊ ስነ-ምህዳሮች ወደ 15,000 የሚጠጉ ልዩ ጥበቃ በሚደረግላቸው የተፈጥሮ ግዛቶች ውስጥ የተጠበቁ ናቸው የተለያዩ ደረጃዎች , ከጠቅላላው የሀገሪቱ ክፍል ከ 10% በላይ ይዘዋል. እነሱም 45 የባዮስፌር ክምችቶች፣ 64 ብሄራዊ ፓርኮች እና 101 የተፈጥሮ ክምችቶችን ያካትታሉ። ሩሲያ እስካሁን ድረስ በሰው ያልተነኩ ብዙ ሥነ-ምህዳሮች አሏት። በዋነኛነት በሰሜናዊ ታይጋ አካባቢዎች እና በሳይቤሪያ ንዑስ ታንድራ ውስጥ። ሩሲያ በ2019 የደን መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ አማካኝ ነጥብ 9.02 ያስመዘገበች ሲሆን ከ172 ሀገራት 10ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያ ደረጃ ዋና ሀገር። መንግስት እና ፖለቲካ ሩሲያ ያልተመሳሰለ ፌዴሬሽን እና ከፊል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ነው, እሱም ፕሬዚዳንቱ ርዕሰ መስተዳድር ናቸው, እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስት መሪ ናቸው. በመሠረታዊነት የተዋቀረው የመድበለ ፓርቲ ተወካይ ዴሞክራሲ ሲሆን ፌዴራል መንግሥት በሶስት ቅርንጫፎች የተዋቀረ ነው፡- ህግ አውጪ፡- 450 አባላት ያሉት የግዛት ዱማ እና 170 አባላት ያሉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌደራል ህግን ያፀደቀው ፣ ጦርነት አውጀዋል ፣ ስምምነቶችን ያፀድቃል ፣ የቦርሳውን ስልጣን እና የፕሬዚዳንቱን የመክሰስ ስልጣን ያለው የሩሲያ የሁለት ምክር ቤት ፌዴራል ምክር ቤት . ሥራ አስፈፃሚ: ፕሬዚዳንቱ የጦር ኃይሎች ዋና አዛዥ ነው, እና የፌዴራል ህጎችን እና ፖሊሲዎችን የሚያስተዳድሩ እና የሚያስፈጽም የሩሲያ መንግስት (ካቢኔ) እና ሌሎች መኮንኖችን ይሾማል. ዳኝነት፡- በፕሬዚዳንቱ አቅራቢነት በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሾሙ ዳኞች ሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የሥር ፌዴራል ፍርድ ቤቶች ሕጎችን ተርጉመው ሕገ መንግሥታዊ ናቸው የሚሏቸውን ሕጎች መሻር ይችላሉ። ፕሬዚዳንቱ የሚመረጠው በሕዝብ ድምፅ ለስድስት ዓመታት የሥራ ዘመን ሲሆን ከሁለት ጊዜ በላይ ሊመረጥ አይችልም። የመንግስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ምክትሎቻቸው፣ ሚኒስትሮች እና ሌሎች የተመረጡ ግለሰቦችን ያቀፈ ነው። ሁሉም በፕሬዚዳንቱ የተሾሙት በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት ነው (የኋለኛው ሹመት ግን የግዛቱን ዱማ ፈቃድ ይጠይቃል)። ዩናይትድ ሩሲያ በሩሲያ ውስጥ የበላይ የፖለቲካ ፓርቲ ሲሆን "ትልቅ ድንኳን" ተብሎም ተገልጿል. የፖለቲካ ክፍሎች በሕገ መንግሥቱ መሠረት የሩስያ ፌዴሬሽን 85 የፌዴራል ርዕሰ ጉዳዮችን ያቀፈ ነው. እ.ኤ.አ. በ 1993 አዲሱ ሕገ መንግሥት ሲፀድቅ 89 የፌዴራል ጉዳዮች ተዘርዝረዋል ፣ ግን የተወሰኑት በኋላ ተዋህደዋል። የፌዴራል ርዕሰ ጉዳዮች በፌዴሬሽን ምክር ቤት, በፌዴራል ምክር ቤት የላይኛው ምክር ቤት ውስጥ እኩል ውክልና አላቸው-ሁለት ተወካዮች እያንዳንዳቸው. እነሱ ግን በሚደሰቱት የራስ ገዝ አስተዳደር ደረጃ ይለያያሉ። በ 2000 የሩስያ ፌዴራል አውራጃዎች በ 2000 በፑቲን የተመሰረቱት የማዕከላዊ መንግስት የፌዴራል ርዕሰ ጉዳዮችን ለመቆጣጠር ነው. በመጀመሪያ ሰባት፣ በአሁኑ ጊዜ ስምንት የፌደራል ወረዳዎች አሉ፣ እያንዳንዳቸው በፕሬዚዳንቱ በተሾሙ መልእክተኞች የሚመሩ ናቸው። የውጭ ግንኙነት ሩሲያ እ.ኤ.አ. በ2019 ከአለም አምስተኛዋ ትልቁ የዲፕሎማሲያዊ ትስስር ነበራት። ከ190 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል ሀገራት፣ ሁለት በከፊል እውቅና ካላቸው ሀገራት እና ከሶስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ታዛቢ መንግስታት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን ትጠብቃለች። ከ144 ኤምባሲዎች ጋር ሩሲያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ከአምስቱ ቋሚ አባላት አንዷ ስትሆን ልዕለ ኃያል ሀገር ነች። በታሪክ ውስጥ ትልቅ ኃይል እና ጉልህ የሆነ የክልል ኃይል ነበር. ሩሲያ የ 20፣ የአውሮፓ ምክር ቤት፣ እና አባል ነች። እንደ ሲአይኤስ፣ ኢኤኢዩ፣ ፣ እና ባሉ ድርጅቶች ውስጥ የመሪነት ሚና ይጫወታል። ሩሲያ ከጎረቤት ቤላሩስ ጋር የቅርብ ግንኙነት ትኖራለች ፣ እሱም በዩኒየን ግዛት ውስጥ ፣ ከሩሲያ ጋር የኋለኛው ኮንፌዴሬሽን ነው። ሁለቱም ሀገራት ጠንካራ የባህል፣ የጎሳ እና የሃይማኖት ዝምድና ስለሚኖራቸው ሰርቢያ ከሩሲያ ጋር በታሪካዊ የቅርብ አጋር ነበረች። ህንድ ከሩሲያ ወታደራዊ መሳሪያዎች ትልቁ ደንበኛ ስትሆን ሁለቱ ሀገራት ከሶቪየት ዘመነ መንግስት ጀምሮ ጠንካራ ስልታዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አላቸው። ሩሲያ በጂኦፖለቲካዊ ጠቀሜታ በደቡብ ካውካሰስ እና በመካከለኛው እስያ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድራል። እና ሁለቱ ክልሎች እንደ ሩሲያ "ጓሮ" ተገልጸዋል. በ 21 ኛው ክፍለ ዘመን በሩሲያ እና በቻይና መካከል ያለው ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ በሁለትዮሽ እና በኢኮኖሚ ተጠናክሯል; በጋራ የፖለቲካ ፍላጎቶች ምክንያት. ቱርክ እና ሩሲያ ውስብስብ ስትራቴጂካዊ፣ ጉልበት እና የመከላከያ ግንኙነት አላቸው። ሩሲያ ስትራቴጂካዊ እና ኢኮኖሚያዊ አጋር በመሆኗ ከኢራን ጋር ጥሩ ግንኙነት አላት። ሩሲያ በአርክቲክ፣ በእስያ-ፓሲፊክ፣ በአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅ እና በላቲን አሜሪካ ተጽእኖዋን ለማስፋት እየገፋች ነው። በተቃራኒው ሩሲያ ከምዕራቡ ዓለም ጋር ያለው ግንኙነት; በተለይም ዩናይትድ ስቴትስ, የአውሮፓ ህብረት እና ኔቶ; ቀስ በቀስ እየተባባሱ መጥተዋል.
12159
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB%20%E1%8D%95%E1%88%AA%E1%88%9A%E1%8B%A8%E1%88%AD%20%E1%88%8A%E1%8C%8D
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
በስፖንሰር አድራጊነት ምክንያቶች ቤቲኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተብሎ የሚጠራው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በኢትዮጵያ ከፍተኛው የማኅበር እግር ኳስ ክፍል ነው። ሊጉን የሚቆጣጠረው በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር (ቀድሞ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከ 1997 እስከ 2020 ቁጥጥር ስር ነበር) ነው። እ.ኤ.አ. በ 1997 (በ 1990 ) የተቋቋመ ሲሆን የቀደመውን የመጀመሪያውን ምድብ (ኢ. 19444) ተክቷል። በአስራ ስድስት ክለቦች ተወዳድሮ በኢትዮጵያ ከሌሎች የሁለተኛና የከፍተኛ ሊጎች ጋር በማሳደግና በመውረድ ሥርዓት ላይ ይሠራል። ሊጉ ከ 1997–98 የውድድር ዘመን ጀምሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲ.ሲ በዚህ ዘመን የሀገሪቱ መሪ ክለብ ሆኖ በ 14 ማዕረጎች (በአጠቃላይ 29 የመጀመሪያ ዲቪዝዮን) የመጀመሪያው በይፋ እውቅና የተሰጠው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ሊግ ስሪት እ.ኤ.አ. በ 1944 ተቋቋመ። በመጀመሪያ አምስት ቡድኖችን የሚወክሉ አምስት ቡድኖች እና የብሪታንያ ወታደራዊ ተልእኮ በኢትዮጵያ (ቢኤምኤም) በቢኤምኤም አሸናፊነት ለመወዳደር ተወዳድረዋል። የኢትዮጵያ ዋንጫ በቀጣዩ ዓመት ተጨምሮበት ከተወሰኑ ክፍተቶች ዓመታት በስተቀር በየጊዜው እየተፎካከረ ይገኛል። የኢትዮጵያ ከፍተኛ ዲቪዚዮን እግር ኳስ የመጀመሪያዎቹ ዓመታት በአብዛኛው የሜጫል (የአሁኑ የመከላከያ ኃይል አ.ማ) የበላይነት ነበረባቸው። ክለቡ በ 40 ዎቹ እና በ 50 ዎቹ ውስጥ 6 ርዕሶችን አሸን ል። ቅዱስ ጊዮርጊስ አክሲዮን ማኅበር በ 60 ዎቹ መገባደጃ ላይ የተወሰነ የበላይነትን አግኝቶ ከዚያ በኋላ ሊጉ በ 70 ዎቹ እና በ 80 ዎቹ አንጻራዊ የእኩልነት ጊዜን አሳል ል። ሊጉ በ 1990 ዎቹ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ 1997 የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ኢኤፍኤፍ) እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ከፍተኛ ምድብ ባቋቋሙት ቡድኖች ውስጥ ለውጦችን አሳይል። የፕሪሚየር ሊግ ዘመን የ 1997-98 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን መብራት ኃይል ዋንጫውን ያነሳበት ነበር። በቀጣዩ ዓመት ሊጉ የቡድኖቹን ቁጥር ወደ 10 ለማሳደግ ወስኗል ፣ ዓመቱን ሙሉ ተወዳጆች ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲ. ቅዱስ ጊዮርጊስ በቀጣዩ ዓመት (1999-00 የውድድር ዘመን) ሻምፒዮን ሆኖ ይደጋግማል። የመብራት ኃይል አጥቂ ዮርዳኖስ አባይ ባሳየው የጥቃት ማሳያ የ 2000–01 የውድድር ዘመን በሊጉ ልዩ ነበር። አባይ በሊጉ ዘመቻ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ለሁለተኛ ጊዜ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ (3 ኛ አጠቃላይ ማዕረግ) በመርዳት በሊጉ ዘመቻ በወቅቱ 24 ግቦችን አስቆጥሯል። በ 2016-17 የውድድር ዘመን 25 ግቦችን በማስቆጠር የደደቢቱ አጥቂ ጌታነህ ከበደ እስኪያልፍ ድረስ የእሱ ሪከርድ 16 ዓመታት ይቆማል። በቀጣዩ የውድድር ዘመን (2001-02 የውድድር ዘመን) ኢትዮ ኤሌክትሪክ በብዙዎች ዘንድ ሻምፒዮን ሆኖ ለመድገም ቢመረጥም በመጨረሻ ሻምፒዮን ከሆነው ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጀርባ በመጨረስ ተስፋውን አጣ። የ 2002–03 የውድድር ዘመን ከአዲስ አበባ ውጭ የመጀመሪያዎቹ እውነተኛ ተፎካካሪዎች የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለማግኘት ሲገፋፉ ነበር። የቅዱስ ጊዮርጊስ 4 ኛ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን (19 ኛውን አጠቃላይ ዋንጫ) ለማረጋገጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተፎካካሪዎቹ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ድል ማድረግ ሲያስፈልገው የመጨረሻው ቀን ወርዷል። በደቡብ አርባ ምንጭ ከተማ የሚገኘው የሁለተኛው ደረጃ አርባ ምንጭ ጨርቃጨርቅ የመጀመሪያውን ማዕረግ ለማሸነፍ ቢፈልግም ቅዱስ ጊዮርጊስ አ.ማ. በመጨረሻ ግን ቅዱስ ጊዮርጊስ ግጥሚያቸውን ማሸነፍ እና ሻምፒዮንነቱን ለመያዝ ችሏል ነገር ግን በአርባ ምንጭ ጨርቃጨርቅ የተደረገው ጠንካራ ማሳያ ከዋና ከተማው ውጭ ያሉ ቡድኖች እንደገና በከፍተኛ ሊግ ለመወዳደር ዝግጁ መሆናቸውን ያሳያል። በካፒቴን ካማል አህመድ የሚመራው ሀዋሳ ከተማ አ.ማ በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ማንሳት በመቻላቸው የ 2003–04 የውድድር ዘመን ከአዲስ አበባ ውጪ ላሉ ቡድኖች የእድገት ዓመት ሆኖ ነበር። ለፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ቡና አ.ማ እና ትራንስ ኢትዮጵያ የመሳሰሉትን ለመከላከል ሀዋሳ ከተማ ኒያላ አ.ሲን ማሸነፍ ነበረበት። 5 ኛውን እና 6 ኛውን የፕሪሚየር ሊግ (20 ኛ እና 21 ኛ ዋንጫዎችን በአጠቃላይ) ማንሳት በመቻላቸው ቀጣዮቹ ሁለት የውድድር ዘመናት በቅዱስ ጊዮርጊስ አ.ሲ፡፡ የ 2006 - 07 የውድድር ዘመን መጀመሪያ ሊጉ ወደ 16 ክለቦች አድጓል። ቅዱስ ጊዮርጊስ አ.ማ ሶስት አተርን በመከልከል በበርካታ ዓመታት ውስጥ ሀዋሳ ከተማ ለሁለተኛ ጊዜ ዋንጫውን በማሸነፍ የውድድር ዘመኑ ተጠናቀቀ። ሆኖም ቀጣዮቹ ሶስት ተከታታይ ወቅቶች እንደገና በቅዱስ ጊዮርጊስ የበላይነት የሚቆጣጠሩ ሲሆን በአሰልጣኙ መንቾ መሪነት ቅዱስ ጊዮርጊስ 7 ኛ ፣ 8 ኛ እና 9 ኛ የፕሪሚየር ሊግ ማዕረጎቻቸውን (በአጠቃላይ 22 ኛ ፣ 23 ኛ እና 24 ኛ ማዕረጎቻቸውን) ይጨምራል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ከፍተኛ ተፎካካሪዎቹ ኢትዮጵያ ቡና የ 2010-11 ዋንጫውን የመጀመሪያውን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ (በአጠቃላይ ሁለተኛውን ዋንጫ) በማሸነፍ ታላቅ ሩጫቸውን ያቆማሉ። ሆኖም ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ተመልሶ በ 2011-12 እንደገና ዋንጫውን ያነሳ ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ ለመድገም ያደረገው ሙከራ እንደ ቀጣዩ የውድድር ዘመን ደደቢት ኤፍ. በምትኩ በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ የዘውድ ሻምፒዮን ይሆናሉ። ከ2013-14 የውድድር ዘመን እስከ 2016-17 የውድድር ዘመን ቅዱስ ጊዮርጊስ አ.ማ በኢትዮጵያ ውስጥ በአንደኛው ዲቪዚዮን እግር ኳስ አንድ ጊዜ ብቻ የተከናወነ እና በተከታታይ 4 ርዕሶችን ያሸነፈ አንድ ነገር ያደርጋል። በተለይ የ 2016-17 የውድድር ዘመን 16 ክለቦችን ያካተተ ሲሆን ፌደሬሽኑ ሊጉን ከቀድሞው 14 ክለቦች ለማስፋት ከወሰነ በኋላ ነው። በተራው ደግሞ ባለፈው የውድድር ዘመን መጨረሻ ከሊጉ የወረዱት ሁለት ክለቦች ብቻ ሲሆኑ አዲሱን 16 ክለቦች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ለማቋቋም ከከፍተኛ ሊግ ባደጉ አራት ክለቦች ተተክተዋል። በግንቦት 2 ቀን 2018 በወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ እና በመከላከያ መካከል በተደረገው ጨዋታ ዳኛ ጥቃት ከተሰነዘረበት በኋላ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሊግ ተቋረጠ። የሊግ ጨዋታ ከሁለት ሳምንት በኋላ ዳኞች በቅርብ ጊዜ ውስጥ የመድን ሽፋን እንደሚቀበሉ እና ቀደም ሲል የህክምና ወጪዎች በተጠያቂ ክለቦች እንደሚሸፈኑ ለአርቢተሮች ማህበር ዋስትና እስከሚሰጥ ድረስ አይቀጥልም። የ 2017-18 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ጅማ አባ ጅፋር ኤፍ.ሲ በመሆን በአስደናቂ ሁኔታ ተጠናቋል። በመጨረሻው ቀን በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን አንስተዋል። ጅማ አባ ጅፋር እና ቅዱስ ጊዮርጊስ በነጥብ እና በግብ ልዩነት ተለያይተው ወደ መጨረሻው ቀን የገቡ ቢሆንም በጅማ አባ ጅፋር 5 ለ 0 እና በቅዱስ ጊዮርጊስ አ.ሲ 2 ለ 0 ውጤት ማሸነፍ የርዕሱ ጅማ ምስጋና ይገባዋል ማለት ነው +3 የግብ ልዩነት ከቅዱስ ጊዮርጊስ አ.መ. የደመወዝ ጭማሪ እና የቤት ውስጥ ያደጉ ተጫዋቾች ቸልተኝነት እርምጃው የተወሰደባቸው አንዳንድ ምክንያቶች ተደርገዋል። በግንቦት 5 ቀን 2020 የ 2019-20 ወቅት በ -19 ወረርሽኝ ምክንያት ተሰረዘ። በውጤቱም በዚህ የውድድር ዘመን ምንም ሻምፒዮን አልተሸለመም እንዲሁም ክለቦች ከሊጉ ወርደው አልወጡም። በታህሳስ 12 ቀን 2020 የ 2020-21 ወቅት በይፋ ተጀመረ። ግንቦት 6 ቀን 2021 ፋሲል ከነማ የ2020-21 የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ፣ የክለቡ የመጀመሪያ አንደኛ ዲቪዥን ማዕረግ መሆኑ ተረጋገጠ። የውድድር ቅርጸት በፕሪሚየር ሊጉ 16 ክለቦች አሉ። በአንድ ወቅት (ከኖቬምበር እስከ ግንቦት) እያንዳንዱ ክለብ ሌሎቹን ሁለት ጊዜ (ባለ ሁለት ዙር ሮቢን ስርዓት) ፣ አንድ ጊዜ በቤታቸው ስታዲየም እና አንድ ጊዜ በተቃዋሚዎቻቸው ላይ በአጠቃላይ ለ 30 ጨዋታዎች ይጫወታል። ቡድኖች ለማሸነፍ ሶስት ነጥብ እና ለአንድ ነጥብ አንድ ነጥብ ይቀበላሉ። ለኪሳራ ምንም ነጥብ አይሰጥም። ቡድኖች በጠቅላላው ነጥብ ፣ ከዚያም በግብ ልዩነት ፣ ከዚያም ግቦች ተቆጥረዋል። ሦስቱ ዝቅተኛ ደረጃ ያላቸው ቡድኖች ወደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ሁለተኛ ደረጃ) ዝቅ ተደርገዋል እና ከከፍተኛ ሊግ የመጡ ከፍተኛ ሶስት ቡድኖች በቦታቸው ከፍ ብለዋል። ለአፍሪካ ውድድሮች ብቃት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ በቀጣዩ ዓመት ለካፍ ቻምፒየንስ ሊግ በቀጥታ ይሳተፋል። የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊው ለካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ ዙር ብቁ ይሆናል። ከፍተኛ ግብ አግቢዎች ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በወቅቱ ብዙ ጊዜ ማሸነፍ ሊጉን በተደጋጋሚ በማሸነፍ ደረጃውን የያዙት ክለቦች የሚከተሉት ናቸው፡ 20 (ሃያ) ጊዜ..............................ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ 6 (ስድስት) ጊዜ..........................መቻል የእግር ኳስ ክለብ 5 (አምስት) ጊዜ..........................ጦር የእግር ኳስ ክለብ ጦር የእግር ኳስ ክለብ እ.አ.አ. ከ 1951 እስከ 1954 በተከታታይ 4 (አራት) ጊዜ በማሸነፍ ታሪክ ያለው ክለብ ነው። ይህ ክለብ በአሁኑ ጊዜ የለም። አሁን ካሉት ክለቦች ደግሞ ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ እ.አ.አ. ከ 1994 እስከ 1996 በተከታታይ ለ3 (ሶስት) ጊዜ ያህል በማሸነፍ ብቸኛው ክለብ ነው። በደጋፊ ብዛትም ቢሆን ብልጫውን እንደሚይዝ ብዙዎች ይናገራሉ። ድረ ገጽ ያላቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ክለቦች የራሳቸው የድረ ገጽ አድራሻ ያላቸው ክለቦች 2 (ሁለት) ብቻ ናቸው። እነርሱም፡ ኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ክለብ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ ናቸው። እነሱም:- የቅዱስ ጊዮርጊስ እንዲሁም የኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ክለብ ድረ ገጽ ናቸው ። የሊጉ ተሳታፊ ክለቦች በሊጉ ውስጥ በ፳፻፫ ዓ.ም. የሚሳተፉ ክለቦች 18 (አስራ ስምንት) ናቸው። እነዚህም፦ ሐረር ቢራ የእግር ኳስ ክለብ መብራት ኃይል የእግር ኳስ ክለብ መተሓራ ስኳር የእግር ኳስ ክለብ መከላከያ የእግር ኳስ ክለብ መድን የእግር ኳስ ክለብ ሙገር ሲሚንቶ ሜታ አቦ የእግር ኳስ ክለብ ሰበታ የእግር ኳስ ክለብ ሲዳማ ቡና የእግር ኳስ ክለብ ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ቡድን ባንኮች የእግር ኳስ ክለብ ትራንስ የእግር ኳስ ክለብ ኒያላ የእግር ኳስ ክለብ አዋሳ ከተማ የእግር ኳስ ክለብ አዳማ ከተማ የእግር ኳስ ክለብ የኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ክለብ ደቡብ ፖሊስ የእግር ኳስ ክለብ ደግሞ ይዩ የ፳፻፫ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እግር ኳስ
43708
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D
ማርያም
ድንግል ማርያም በክርስትናና፣ በእስልምና እምነቶች መሠረት የከበረችው የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነች። በክርስትና እምነት የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ማለትም የወልድ እናት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ግብር ኃይል በሥላሴ ምርጫ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንደ ወለደችው ይታመናል ። በእግዚአብሔር ህሊና ከፍጥረት በፊት እንደነበረች ኦዘ-ም፡፫ ቁ፡፲፭ ያስረዳል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማርያምን በጣም ከመወደዷ የተነሳ ከ፻ በላይ በሰየመቻት ስሞቿ ትጠራታለች (የቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች):: አንዱ የእመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም አስደናቂ አባባል ደሞ "ትውልድ ሁሉ ብፅእት ይሉኛል" ሉቃ.ም፣፩ ቁ.፵፯ ፶፭ ብላ ከ፪ሺ ዓመት በፊት የጸለየቸው ወይም የተናገረቻችው ቃላቶች ናቸው ። ሙስሊሞች ደግሞ መሪማ የኢየሱስ (ኢሳ) እናት ይልዋታል። በአለም ላይ ፫ ታላላቅ እምነቶች ዘንድ እስዋም ልጅዋም ትልቅ ክብርና ቅድስና በተለይ ለልጇ መመለክ ገንዘባቸው ነው። >ውዳሴ ማርያም እንድምታ >ቅዳሴ ማርያም እንድምታ >ከድረገጾችዎ አንዱን ለማየት እዚህላይ ይጫኑ ወይም ይህን ይጫኑ በክርስትና እምነት ድንግል ማርያም ሰው ሁኖ የመጣዉ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነች። ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ከእግዚአብሔር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንዱ ተወላዲ ማለትም (ወልድ) ሲሆን ፣ ወላዲ ደግሞ (አብ) ነው ፣ ቀጥሎም ሰራጺ (መንፈስ ቅዱስ) ይሆናል ፤ በተጨማሪ ወልድ ጌታ ወይም ክርስቶስ፡መሢሕ ይባላል። እናቱ ማርያም እግዚአብሔር የተባለውን ወልድ ለመውለድ ስለ ተመረጠች እና ብቁ ሆና ስለተገኘች ከሴቶች ሁሉ ይልቅ ብጹዕት ፣ ቅድስት ፣ በግሪክ ቴዎቶከስ ማለትም የእግዚአብሔር እናት ትባላለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከ 34 ዓ.ም ጀምራ ክርስትናን በኢትዮጵያ ምድር የሰበከች ጥንታዊት ቤተክርስቲያን ሥትሆን ምድቧም ከ ኦርዮንታል አብያተ ክርስቲያናት ነው:: እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥላሴ አካላት አንዱ ወልድ፣ አምላክ ነው::ይህ አምላክም ወይም እግዚአብሔር ወልድ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ተወለደ::በሌላ አገላለጽ አምላክ ሰው ሆነ::በዚህም ምክንያት ቅድስት ድንግል ማርያምን የጌታ እናት ወይም የእግዚአብሔር እናት(ወላዲተ አምላክ) ትባላለች:: ቤተክርስቲያኗ ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስንም አምላክ ፣ ወልደ አምላክ ፣ ወልደ ማርያም ፣ ወልድ፣ ቃል ብላ ትጠራዋለች:: ድንግል ማርያምን ደግሞ እመቤት ፣ ቅድስተ ቅዱሳን ፣ እግዝእትነ ማርያም ፣ የጌታ እናት ፣ ወላዲተ አምላክ ፣ ቅድስት፣እመ ብርሃን ፣ እመ አምላክ፣ንጽሕተ ንጹሃን ቅድስተ ቅዱሳን፣ጽዮን ወዘተ በማለት ትጠራታለች::ቅድስት ድንግል ማርያምን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከአዳም በደል ወይም ከጥንተ አብሶ ነጻ ሆና በአዳም ባህርይ እንደ እንቁ ስታበራ የኖረች አደፍ ጉድፍ የሌለባት ፣ ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ የነጻች ፣ እንደሆነች ታምናለች። በሌላው ወገን ጥንተ አብሶ ነበራት ለዚህም ማስረጅያ "ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም" ተብሎ የሚጠራው በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ቁጥር 47 እግዚአብሔርን "መድኃኒቴ" ብላ ማመስገነዋ ነው የሚሉም አሉ ። ሁለቱም ወገን ግን እግዚአብሔር ወልድ ሥጋዋን ከተዋሃደ በፊት እንዳነጻት ማደሪያው እንድትሆን እንዳስጌጣት ከወለድችሁም በኋላ በድንግልኗና በንፅህኗ እንደኖረች፣ ለዘለዓለም በዚሁ ሁኔታ ጸንታ እንደምትኖር ያምናሉ። ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች የሆነች፣ የሰማይ የምድር ንግስት ፣ እንደሆነች ቤተክርስቲያን ታስተምራለችና ። አንዱ የእመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም አስደናቂ አባባል ደሞ "ትውልድ ሁሉ ብፅእት ይሉኛል" ሉቃ.ም፣፩ ቁ.፵፯ ፶፭ ብላ ከ፪ሺ ዓመት በፊት የጸለየቸው ወይም የተናገረቻችው ቃላቶች ናቸው ። ይህም መንፈስ ቅዱስ የሞላባት ወልድ የተዋሀዳት አብ የመረጣት ፍፁምነት የተገለፀባት ከሰው ሁሉ ተለይታ መከበር የሚገባት መሆኑዋን አረጋግጦ ያስረዳል ። ጸሎተ ማርያም ሉቃስ ም፩ ፣ ፵፯ - ፶፭ ነፍሴ፡ጌታን፡ታከብረዋለች፥መንፈሴም፡በአምላኬ፡በመድኀኒቴ፡ሐሴት፡ታደርጋለች፤ የባሪያዪቱን፡ውርደት፡ተመልክቷልና።እንሆም፥ከዛሬ፡ዠምሮ፡ትውልድ፡ዅሉ፦ብፅዕት፡ ይሉኛል፤ ብርቱ፡የኾነ፡ርሱ፡በእኔ፡ታላቅ፡ሥራ፡አድርጓልና፤ስሙም፡ቅዱስ፡ነው። ምሕረቱም፡ለሚፈሩት፡እስከ፡ትውልድና፡ትውልድ፡ይኖራል። በክንዱ፡ኀይል፡አድርጓል፤ትዕቢተኛዎችን፡በልባቸው፡ዐሳብ፡በትኗል፤ ገዢዎችን፡ከዙፋናቸው፡አዋርዷል፤ትሑታንንም፡ከፍ፡አድርጓል፤ የተራቡትን፡በበጎ፡ነገር፡አጥግቧል፤ባለጠጋዎችንም፡ባዷቸውን፡ሰዷቸዋል። ለአባቶቻችን፡እንደ፡ተናገረ፥ለአብርሃምና፡ለዘሩ፡ለዘለዓለም፡ምሕረቱ፡ትዝ፡እያለው፡ የቅድስት ድንግል ማርያም ትውልድ ቅድስት ድንግል ማርያም አባቷ ኢያቄም እናቷ ደግሞ ሃና ይባላሉ::የተፀነሰቸው በእለተ እሁድ ነሐሴ ፯ ቀን ሲሆን የተወለደቸውም ግንቦት ፩ ነው::እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም የተወለደችበት እለት በአባት እናቷ ቤት ፍስሃ ደስታ ተደረገበት ፤ ቤቱንም ብርሃን መላው ፤ በ፰ኛውም ቀን ማርያም ብለው አወጡላት::ስለምን ማርያም ብለው አወጡላት ቢሉ:እነሆ በዚህ አለም ከሚመገቡት ሁሉ ምግብ ለአፍ የሚጥም ለልብ የሚመጥን ማር ነው:በገነትም በህይወት የተዘጋጁ ጻድቃን ቅዱሳን ያም የሚባል ምግብ አላቸው ::ከዚ ሁሉ የበለጥሽ የከበርሽ ነሽ ሲሉ ስለዚህ ማርያም ብለው አወጡላት:: እመቤታችን ማርያም ለእናት ለአባቷ አንዲት ስትሆን የተወለደቸው በጸሎት በመሆኑና የስለት ልጅ በመሆኗ እናትና አባቷ ለእግዚአብሔር በተሳሉት መሰረት ፫ ዓመት ሲሞላት ወደ ቤተመቅደስ ወሰደው ለካህኑ ለዘካርያስ አስረከቧት::እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደች በሦስት ዓመቷ እናቷ ሐና አባቷ ኢያቄምን፡- “ይህች ብላቴና ሆዷ ዘመድ ሳይወድ፣ አፏ እህል ሳይለምድ “ለእግዚአብሔር በገባነው ቃል መሠረት ወስደን ለቤተ መቅደስ አንሰጣትምን?” ‘የሰጠ ቢነሣ የለበት ወቀሳ’ እንዲሉ አንዳች ነገር ብትሆንብን ከልጃችንም ከእግዚአብሔርም ሳንሆን እንዳንቀር” አለችው፡፡ እርሱም፡- “ፍቅርሽ ይለቅልሽ ብዬ ነው እንጂ እኔማ ፈቃዴ አይደለምን?” አላት፡፡ወላጆቿ ይህን ተነጋግረው እንዳበቁ ሕጻን ልጃቸውን ማርያምን ወስደው ለቤተ መቅደስ ሰጧት፡፡ በዚያን ጊዜ የነበረው ሊቀ ካህናት ዘካርያስ ይባላል፤ እርሱም ስለ ምግቧ ነገር ሊያስወስን መጥቅዕ (ደወል) ደውሎ ሕዝቡን ሰብስቦ እየተወያዩ ሳለ የእግዚአብሔር መልአክ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል የሰማይ ኅብስትና የሰማይ ጽዋ ይዞ ከሰማይ ወርዶና ረብቦ ታየ፡፡ብላቴናይቱንም መልአኩ ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ደግሞ ጋርዶ በሰው ቁመት ያህል ከምድር አስለቅቆ ከፍ አድርጓትና መግቧት ዐረገ፡፡ ከዚህ በኋላ ካህናቱና ሕዝቡ “የምግቧ ነገር ከተያዘልንማ ከሰው ጋር ምን ያጋፋታል” ብለው ሕጻን ማርያምን ከወላጆቿ ተቀብለው ወደ ቤተ መቅደስ አግብተዋት በዚያ ፲፪ ዓመት ኖራለች፡፡ይህም ሲደመር ጠቅላላ ፲፭ ዓመት ሆናት ማለት ነው::በዚህ ስዓት አይሁድ ከበተመቅደስ ትውጣልን ብለው አመለከቱ ፤ ለጻድቁ ለቅዱስ ዮሴፍም እንዲጠብቃት ታጨች ፤ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አበሰራት::በ ፲፭ አመቷ እግዚአብሔር ወልድን ፀነሰች:: የቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች:- የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን «እስመ ስሙ ይመርህ ኀበ ግብሩ» በማለት ስም ግብርን ሁኔታን ማንነትን ይገልጻል ይላሉ፡፡በዚህም መሰረት ቤተክርስቲያኗ ለስመ ድንግል ማርያም ዘርፍ /ቅጽል/ አልያም ምትክ አድርጋ የምትጠቀምባቸው ምሥጢራዊና ረቂቅ ትርጉም ያላቸው ንጽሕናዋን፣ ቅድስናዋን፣ ድንግልናዋን፣ ብፅእናዋን ወዘተ የሚመሰክሩ በርካታ ስሞች ሰይማላታለች፡፡ከነዚህም መካከል ከብዙ በጥቂቱ:ምልዕተ ጸጋ ፣ እምነ /«ም» ጠብቆ ይነበብ/ ጽዮን ፣እመ ብርሃን ሰአሊተ ምሕረት ፣እመቤታችን ፣ቤዛዊተ ዓለም፣ ወላዲተ አምላክ ፣ኪዳነ ምሕረት ወዘተ.. ቅድስት ድንግል ማርያም በ 64 ዓመቷ ካረፈች በኋላ እንደ ልጇ በሦስተኛው ቀን ማረጓን ቤተክርስቲያኑ ታስተምራለች:: ቅድስት ድንግል ማርያም በኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተአምረ ማርያም በሚባለው የጸሎት መጽሓፍ ቅድስት ድንግል ማርያም በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው በሕፃንነቱ ልጇን ጌታ ኢየሱስን እንዳይገድሉባት ከምድረ እስራኤል ስትሸሽ በግብጽ አልፋ ወደ ኢትዮጵያ ምድር ደርሳለች። ጌታ ኢየሱስ በእግሩ በመረገጡ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ከአረጋዊው ከቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ከዘመዳቸው ከቅድስት ሰሎሜ ጋር በእንግድነት በመቀመጡ ምድረ ኢትዮጵያን ባርኳታል። እመቤታችንን በጭንቀቷ ሰዓት ይቺ ምድርና ሕዝቦቿ ስለተቀበሏት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአደራነት ወይም በአሥራትነት ኢትዮጵያን ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደሰጣት ቤተ ክርስቲያኒቷ ታስተምራለች። በዚህ ምክንያት በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ዘንድ እጅግ በጣም ልዩ ተወዳጅነትና ፍቅር ያላት በተለምዶ እንኳን እምዬ እናታችን እመቤታችን ወይም በመዓረግ ስሞቿ ኪዳነ ምሕረት ወላዲተ አምላክ እመብርሃን ተብላ ትጠራለች። ከኃይማኖትም ባሻገር በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ባህልም ቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ ቦታ አላት። ለምሳሌ አንዲት እርጉዝ ሴት ልትወልድ ስትል «ድንግል ማርያም ትቅረብሽ» ስትወልድም «እንኳን ማርያም ማረችሽ» በአራስ ቤትም ሳለች «ድንግል ማርያም በሽልም ታውጣሽ» ትባላለች። አንድ ሰው ገላው ላይ ሲወለድ የነበረ ጥቁር ምልክት ቢኖረው «ድንግል ማርያም እዚህ ስምሃለች» ይባላል። >ጾመ ፍልሰታ ፍልሰታ የሚለው ቃል የሚገልጸው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለቆ መሔድን መሰደድን መፍለስን ያመለክታል። ይህም የእመቤታችንን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን በኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ስር ከነበረበት መነሳቱን ለማመልከት ይነገራል። ጾመ ፍልሰታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፷፬ ዓመት በዚች ምድር ኖራ እንደ አንድ ልጇ መሞቷን መነሳቷንና ማረጓን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት የጾሙት ጾም ነው። ጾሙ ከነሐሴ 8 ቀን አስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን ሲጾም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዋጅ ከደነገገቻቸው ሰባቱ አጽዋማትም አንዱ ነው። ኃይማኖታዊ መሠረት እመቤታችን ከአባቷ ከኢያቄም እና ከናቷ ከሐና ነሐሴ ፯ ቀን ተጸንሳ ግንቦት ፩ ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች# <እምሊባኖስ ትወጽዕ መርአት : ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች > እንደተባለ ። እምቤታችን በእናት አባቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ አሥራ ሁለት ዓመት፤ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር : ዮሐንስ ወልደዘብዴዎስ ዘንድ አሥራ አራት ዓመት ከዘጠኝ ወር ቆይታ በ ፷ ዓመት ዕድሜዋ በ፱ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። የእመቤታችንን ስም የሚገልጹ የውዳሴ ጽሑፎችም በእድሜዋ ልክ ተደርሰዋል። ለምሳሌ የውዳሴ ማርያም ቁጥር ፰ ነው የመልክአ ማርያም ቁጥርም ፷ ነው። ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰባስበው አስከሬኗን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ለማሳረፍ ሲሄዱ አይሁድ ለተንኮል አያርፉምና ተተናኮሏቸው። ቀድሞ ልጇ ሞቶ ተነሳ፣ አረገ እያሉ ሲያስቸግሩን ይኖራሉ፡ ደግሞ አሁን እሷም ተነሳች፣ አረገች ሊሉ አይደል በማለት አይሁድ ተሰባስበው አስከሬኗን ለማቃጠል ሲተናኮሉ እግዚአብሔር በተአምር ከነዚያ አይሁዶች አድኗቸዋል :: የእመቤታችንንም አስከሬን ነጥቆ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር በገነት በዕፀ ህይወት ስር አኑሯቸዋል ። ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በአረፈች በስምንተኛው ወር ከነሐሴ ፩ ጀምሮ ስከ ነሐሴ ፲ ቀን ድረስ ሁለት ሱባዔ ይዘው በአሥራ አራተኛው ቀን ሥጋዋን ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በምህላ በፍጹም ደስታ በጌቴሰማኔ አሳረፉት ። በ ሦስተኛውም ቀን ተነስታ ስታርግ ከሰኡቃዊያን ወገን የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አያት። እርሱም በቀብር ስርዓቱ ጊዜም አልነበረም። ሀገረ ስብከቱ ህንድ ስለነበር ሊያስተምር ወደዛው ሂዶ ነበርና። በዚያም ሲያስተምር ሰንብቶ በደመና ተጭኖ ሲመጣ ያገኛታል። ትንሳኤዋን ከርሱ ሰውራ ያደረገች መስሎት አዝኖ «ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀርቼ ነውን ?» ብሎ ቢያዝንባት እመቤታችንም ከርሱ በቀር ማንንም ትንሳኤዋን እንዳላየ ነግራ አጽናናችው። ለሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲነግራቸው ለምልክትም /ለምስክርም እንዲሆነው ሰበኗን /መግነዟን ሰጥታው አረገች። ቶማስም ኢየሩሳሌም ደርሶ ሐዋርያትን የእመቤታችን ነገርስ እንደምን ሆነ?» ሲል ቢጠይቅ «አግኝተን ቀበርናት እኮ» አሉት። እርሱ ምስጢሩን አዉቆ ደብቆ «ሞት በጥር በነሐሴ መቃብ» እንዴት ይሆናል ? አይደረግም ይላቸዋል። ሊያሳያቸውም መቃብሩ ዘንድ ሂደው ቢከፍቱት አጧት። እርሱም «አታምኑኝም ብዬ እንጂ እርሷስ ተነስታ አርጋልች» በማለት ሁኔታውን ተረከላቸውና ለምስክር ይሁንህ ብላ የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው። ከዚህ በኋላ ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ ሰበኑን ተካፍለው ወደየአህገረ ስብከታቸው ሄዱ። ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የዚያ ሰበን ምሳሌ ነው። በዓመቱ ሐዋርያት ከያሉበት ተሰባስበው ቶማስ ትንሳኤሽን አይቶ እኛስ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምርው ሱባዔ ቢይዙ ከሁለት ሱባዔ በኋላ እንደገና ትንሳኤዋንና እርገቷን ለማየት በቅተዋል። ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናም ምእመኖቿ ከእመቤታችን በረከትን እንዲያገኙ ይጾሙ ዘንድ ይህን ሐዋርያት የጾሙትን ጾም እንዲጾሙ አዉጃለች። ምእመናንም በተለየ መልኩ በጾም በጸሎት በሱባዔ ጽሙድ ሆነው ይህን ወቅት ያሳልፋሉ። የእመቤታችን ትንሳኤ ድንገት እንደእንግዳ ደራሽ እንደ ዉሀ ፈሳሽ የተደረገ ሳይሆን በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት የተገለጸ ነው። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር ፻፴፩ ቁጥር ፲ ላይ «አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነስ አንተና የመቅደስህ ታቦትም» ይላል። በዚህም ምዕመናንን ወደ ምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህ ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነስ አለ። ታቦት የጽላት ማደርያ እንደሆነ ሁሉ እምቤታችንም ለክርስቶስ ማደርያ በመሆኗ አማናዊት ታቦት ትባላለች። ንጉስ ሰሎሞንም በመኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፩ ላይ «ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ፤ ወዳጄ ሆይ ተነሽ፡ ውብቴ ሆይ ነይ» ብሏል። እዚህ ላይ ወዳጄ ...ዉበቴ»" የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት # ክቡር ዳዊት መዝሙር ቁጥር ፱ ላይ «በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች» እንደሚል ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛነቱን ከፈጸመ በኋላ ወደ ቀደመ ክብሩ እንዳረገ እመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም በቀኙ ትቀመጥ ዘንድ «ተነሽ ነይ» አላት ። እንግዲህ ይህንና የመሰለዉን ሁሉ ይዘን የእናታችንን እረፍቷን ትንሳኤዋን እንዘክራለን እንመሰክራለንም። የማርያምን ድንግል ሁና እየሱስን ወይንም እነሱ እንደሚሉት ኢሳ (አ.ሰ)ን እንደወለደች ብሎም በነሱ እምነት አራት ተብለዉ ከተጠቀሱ ምርጥ ሴቶች ዉስጥ አንድዋ ነች። ነገር ግን ኢሳን የአላህ መልዕክተኛ ነዉ ሲሉት፣ አላህም ፈጣሪዉ እንጅ ልጁ አይደለም ባዮች ናቸው። በቁርአን ምክንያት አምላክ አይወልድም አይወለድም፤ ይህም ለአላህ የማይገባው ሥራ ነው ይላሉ።
8418
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A5%E1%88%B5%E1%8D%93%E1%8A%95%E1%8B%AB
እስፓንያ
ስፔን (ስፓኒሽ: ፣ ወይም የስፔን መንግሥት (ስፓኒሽ ሬይኖ ዴ እስፓኛ)፣[] በደቡብ ምዕራብ አውሮፓ የምትገኝ አገር ነች፣ በአትላንቲክ ውቅያኖስ እና በማዶ ላይ የተወሰነ ግዛት ያለው። የሜድትራንያን ባህር፡ የስፔን ትልቁ ክፍል የሚገኘው በአይቤሪያ ባሕረ ገብ መሬት ላይ ነው። ግዛቱ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የሚገኙትን የካናሪ ደሴቶችን ፣ በሜዲትራኒያን ባህር ውስጥ የሚገኙትን የባሊያሪክ ደሴቶችን ፣ የራስ ገዝ ከተሞችን ሴኡታ እና ሜሊላን እና በርካታ ትናንሽ የባህር ማዶ ግዛቶችን በሞሮኮ የባህር ዳርቻ በአልቦራን ባህር ተበታትነዋል ። የሀገሪቱ ዋና መሬት ከ ድንበር ደቡብ በጅብራልታር; ወደ ደቡብ እና ምስራቅ በሜዲትራኒያን ባህር; ወደ ሰሜን በፈረንሳይ, አንዶራ እና የቢስካይ የባህር ወሽመጥ; እና ወደ ምዕራብ በፖርቱጋል እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ. ስፋቷ 505,990 ኪሜ 2 (195,360 ስኩዌር ማይል)፣ ስፔን በደቡባዊ አውሮፓ ትልቁ ሀገር፣ በምዕራብ አውሮፓ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለች ሀገር እና የአውሮፓ ህብረት እና በአውሮፓ አህጉር አራተኛዋ ትልቅ ሀገር ነች። ከ 47.4 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ስፔን በአውሮፓ ውስጥ በህዝብ ብዛት ስድስተኛዋ እና በአውሮፓ ህብረት አራተኛዋ በህዝብ ብዛቷ ሀገር ነች። የስፔን ዋና ከተማ እና ትልቁ ከተማ ማድሪድ ነው; ሌሎች ዋና ዋና የከተማ አካባቢዎች ባርሴሎና ፣ ቫለንሲያ ፣ ሴቪል ፣ ዛራጎዛ ፣ ማላጋ ፣ ሙርሲያ ፣ ፓልማ ዴ ማሎርካ ፣ ላስ ፓልማስ ዴ ግራን ካናሪያ እና ቢልባኦ ያካትታሉ። አናቶሚ ዘመናዊ ሰዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አይቤሪያ ባሕረ ገብ መሬት የደረሱት ከ 42,000 ዓመታት በፊት አካባቢ ነው። በአሁኑ ስፓኒሽ ግዛት ውስጥ ያደጉ የመጀመሪያዎቹ ባህሎች እና ህዝቦች የቅድመ-ሮማን ህዝቦች እንደ የጥንት አይቤሪያውያን፣ ሴልቶች፣ ሴልቲቤሪያውያን፣ ቫስኮን እና ቱርዴታኒ ያሉ ናቸው። በኋላ፣ እንደ ፊንቄያውያን እና የጥንት ግሪኮች ያሉ የውጭው የሜዲትራኒያን ሕዝቦች የባሕር ዳርቻ የንግድ ቅኝ ግዛቶችን አዳበሩ፣ እና የካርታጊናውያን የስፔን የሜዲትራኒያን የባህር ዳርቻን የተወሰነ ክፍል ለአጭር ጊዜ ተቆጣጠሩ። ከ218 ዓ.ዓ. ጀምሮ የሮማውያን የሂስፓኒያ ቅኝ ግዛት ተጀመረ እና ከአትላንቲክ ኮርኒስ በስተቀር የአሁኗን የስፔንን ግዛት በፍጥነት ተቆጣጠሩ። ሮማውያን በ206 ዓ.ዓ. የካርታጊናውያንን ከአይቤሪያ ባሕረ ገብ መሬት አውጥተው ለሁለት አስተዳደራዊ ግዛቶች ከፈሉት፣ እና ። በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የምዕራቡ የሮማ ኢምፓየር እስኪወድቅ ድረስ ስፓኒያ በሮማውያን አገዛዝ ሥር ቆየ፣ ይህም የጀርመን የጎሳ ኮንፌዴሬሽን ከአውሮፓ እስከ ፈጠረ። በዚህ ጊዜ ውስጥ ባሕረ ገብ መሬት እንደ ሱቪ ፣ አላንስ ፣ ቫንዳልስ እና ቪሲጎትስ በመሳሰሉት ይገዛ ነበር ፣ የኋለኛው ደግሞ ከሮም ጋር በፎኢዱስ በኩል ያለውን ጥምረት ጠብቆ ነበር ፣ የሜዲትራኒያን የባህር ዳርቻ ክፍል የባይዛንታይን ግዛት ነበር። በመጨረሻም፣ ቪሲጎቶች በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የበላይ ኃይል ሆነው ብቅ አሉ፣ የቪሲጎቲክ መንግሥት አብዛኛው የአይቤሪያን ባሕረ ገብ መሬት ይሸፍናል እና ዋና ከተማውን አሁን የቶሌዶ ከተማ አቋቋመ። በቪሲጎቲክ ጊዜ ውስጥ ሊበር ኢዲሲዮረም የሕግ ኮድ መፍጠር በስፔን መዋቅራዊ እና ህጋዊ መሠረት እና ከሮማ ግዛት ውድቀት በኋላ የሮማን ሕግ ሕልውና ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል። በስምንተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የቪሲጎቲክ መንግሥት በኡመያድ ኸሊፋነት ወረራ፣ በደቡብ ኢቤሪያ ከ700 ዓመታት በላይ የሙስሊም አገዛዝ አስከትሏል። በዚህ ጊዜ ውስጥ፣ አል-አንዳሉስ ዋና የኢኮኖሚ እና የእውቀት ማዕከል ሆነ፣ የኮርዶባ ከተማ በአውሮፓ ውስጥ ካሉት ትላልቅ እና ሀብታም አንዷ ነች። በሰሜን አይቤሪያ ውስጥ በርካታ የክርስቲያን መንግስታት ብቅ አሉ ከነዚህም መካከል ሊዮን፣ ካስቲል፣ አራጎን፣ ፖርቱጋል እና ናቫሬ ናቸው። በሚቀጥሉት ሰባት መቶ ዓመታት ውስጥ፣ እነዚህ መንግሥታት ወደ ደቡብ አቅጣጫ መስፋፋት— እንደ ወይም —የመጨረሻው በ1492 ባሕረ ገብ መሬት ናስሪድ የግራናዳ መንግሥት ክርስትያኖች በተያዙበት ጊዜ ነበር። ኮሎምበስ የካቶሊክ ንጉሶችን በመወከል ወደ አዲስ አለም ደረሰ፣የካስቲል ዘውድ እና የአራጎን ዘውድ ስርወ መንግስት ህብረት በተለምዶ እንደ አንድ የተዋሃደች ስፔን እንደ አንድ ሀገር ይቆጠራል። አይሁዶች እና እስላሞች ወደ ካቶሊክ እምነት እንዲቀየሩ ተገደዱ እና የኋለኛው ደግሞ በመጨረሻ በመንግስት ተባረሩ። በተለወጡ ሰዎች መካከል ሃይማኖታዊ ኦርቶዶክሳዊነትን ማስጠበቅ ለምርመራው ተልእኮ ተሰጥቶ ነበር። የስፔን አሜሪካን ቅኝ ግዛት ተከትሎ፣ ዘውዱ ትልቅ የባህር ማዶ ግዛት ለመያዝ መጣ፣ ይህም በአለም አቀፍ ደረጃ በአዲስ አለም በተመረተው ብር በዋናነት የሚቀጣጠለው የአለም የንግድ ስርዓት መፈጠሩን መሰረት ያደረገ ነው። ስፔን ያደገች አገር፣ ዓለማዊ ፓርላሜንታሪ ዲሞክራሲ እና ሕገ መንግሥታዊ ንጉሣዊ ሥርዓት ነች፣ ንጉሥ ፌሊፔ 6ኛ በርዕሰ መስተዳድሩ። ከፍተኛ ገቢ ያላት ሀገር እና የላቀ ኢኮኖሚ ያላት፣ በአለም አስራ አራተኛው ትልቅ ኢኮኖሚ በስም እና አስራ ስድስተኛ-ትልቁ በፒ.ፒ.ፒ. እ.ኤ.አ. በ 2019 ስፔን በ 83.5 ዓመታት ውስጥ በዓለም ላይ ካሉት ረጅም ዕድሜዎች አንዱ ነው ። በተለይም በጤና አጠባበቅ ጥራት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች ፣ የጤና አጠባበቅ ስርዓቷ በዓለም ዙሪያ በጣም ቀልጣፋ ነው ተብሎ ይታሰባል። የአካል ክፍሎች ንቅለ ተከላ እና የአካል ልገሳ የዓለም መሪ ነው። ስፔን የተባበሩት መንግስታት ()፣ የአውሮፓ ህብረት (ኢ.ዩ) አባል ነች
14684
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%BD%E1%88%98%E1%8A%93
ሽመና
የሽመና ጥበብ አጀማመር ታሪክ በአዲስ አበባ (በአምሳሉ መላከ ብርሃን) ኢትዮጵያ ከምትታወቅባቸው በርካታ ባህላዊ አና ታሪካዊ እሴቶች መካከል የሕዝቦች ባህላዊ አለባበስ አንዱ ነው። ይህ ባህላዊ አለባበስ ደግሞ በአመዛኙ የሽመና ሥራ ውጤት ነው። የሽመና ሥራ በሀገራችን መቼና እንዴት እንደተጀመረ በትክክል የሚገልጽ የጽሑፍ መረጃ ባይኖርም ከሺ ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳለው አንዳንድ ጽሑፎች ይጠቁማሉ። በሀገራችን የሺ ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የሽመና ሥራ በአዲስ አበባ በስፋት የተዋወቀው ከጋሞ ተራራማ ቦታዎች ወደ አዲስ አበባ በተለያዩ ምክንያቶች በመጡ የጋሞ ማሕበረሰብ አባላት አማካይነት ከ፲፰፻፺፰ ዓ.ም. ጀምሮ ነው። በዚህ ዓመተ ምሕረት ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ጋሞ ጎፋን የግዛታቸው አካል ከማድረጋቸው ጋር ተያይዞ ንጉሡ ከማሕበረሰቡ አባላት መካከል ወታደሮችን እና አገልጋዮችን መልምለው ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸውን የተለያዩ ጥናቶች ይጠቁማሉ። በተጨማሪም በአዲስ አበባ ውስጥ በርካታ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እየተስፋፉ መምጣታቸው ከርዕሰ ከተማዋ የገበያ ፍላጎት ጋር ተዳምሮ ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የጉልበት ሠራተኞች ወደ አዲስ አበባ መጥተዋል። ከእነዚህም መካከል የጋሞ ተወላጆች ይገኙበታል። ሦስተኛው ምክንያት የጋሞ ተወላጆች ለዓፄ ምኒልክ ግብር ለማስገባትና አቤቱታቸውን ለማቅረብ ወደ መዲናዋ በብዛት መምጣት ነበር። በሌላ በኩል በቀለ ዘለቀ (፲፱፻፸፫ ዓ/ም) እንዳስገነዘቡት ከሰላሳ እስከ ሃምሳ ሺህ የሚሆኑ የጋሞ ተወላጆች በ፲፱፻ ዓ/ም. ጋሞጎፋን የጎበኙትን የዳግማዊ ምኒልክን እንደራሴ ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ዲናግዴን አጅበው ወደ አዲስ አበባ መጥተዋል። ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች ወደ አዲስ አበባ የመጡ የጋሞ ማሕበረሰብ አባላት የሽመና ሥራን ከጀመሩባቸው ምክንያቶች መካከል በመሠረተ ልማት ግንባታው የሚከፈላቸው ገንዘብ በቂ አለመሆኑ እና ይዘው የመጡትን ግብርና አቤቱታ የሚያስተናግድ የቤተ-መንግሥት ባለሙያ ማጣታቸው ይጠቀሳሉ። በዚህም ምክንያት ለብዙ ጊዜ በቤተ-መንግሥት አካባቢ በዛፍ ሥርና በሜዳ ላይ በመቀመጥ በደጅ ጥናት ጊዜያቸውን ያሳልፉ ነበር። በኋላም ችግሩ ሲጠናባቸው ከትውልድ ቀያቸው ይዘውት በመጡት የሽመና መሣሪያ አማካይነት የሽመና ሥራ መስራት ጀመሩ። /ጋሞዎች ከትውልድ ቀያቸው ለቀው ወደ ተለያየ ቦታ ሲንቀሳቀሱ የሽመና መሣሪያቸውን ይዘው መሄድ የለመዱት ባህል ነው። በዚህ ወቅት ጋሞዎች የሽመና ሥራን በሁለት መንገድ ያከናውኑ ነበር። አንደኛ ሸማ ማሠራት በሚፈልጉ ግለሰቦች መኖሪያ ቤት አጥር / በረንዳ ውስጥ መሣሪያቸውን በመትከል ይሰሩ ነበር። ለሥራቸውም የሚከፈላቸው የዕለት ምግብ ነበር። ከሥራቸውም በኋላ አመሻሽ ላይ አሁን የአሜሪካ ኤምባሲ በሚገኝበት አካባቢ በመሄድ ያድሩ ነበር። ሁለተኛው ለቤተ-መንግሥት ባለሟሎች ተቀጥረው የሚሠሩ ናቸው። የሥራቸውንም ውጤት ለቤተ-መንግሥት ባለሟሎች ያቀርባሉ። ከእነዚህ ባለሙያዎች መካከልም አምሳ /፶/ የሚሆኑት ወደ አንኮበር ተልከው የሸዋን የአሸማመን ጥበብ ተምረው እንደመጡ ጋሪሰን (፲፱፻፸፬ ዓ/ም) ያስረዳሉ። በዚህ ሁኔታ የሽመና ሥራቸውን በአዲስ አበባ የጀመሩ ጋሞዎች ታዋቂ የሆኑት ከ፲፰፻፺፰ ዓ.ም. እስከ በ፲፱፻ ዓ/ም. ባለው የጊዜ ክልል ውስጥ በአዲስ አበባ በተከሰተው ማሕበራዊና ምጣኔ ሀብታዊ ክስተቶች ምክንያት ነው። በዚህ ወቅት ጋሞዎች እና ከጋሞ ውጭ የሆኑ የሽመና ባለሙያዎች በሌሎች የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ዘንድ የሚሰጣቸው ማሕበራዊ ደረጃ ዝቅተኛ ነበር። ሙያውም የተናቀ ነበር። በመሆኑም በወቅቱ ከከተማ ዕድገት ጋር በተፈጠረው የሥራ ዕድል በመጠቀም ከጋሞ ማሕበረሰብ ውጭ የሆኑ ብዛት ያላቸው ሸማኔዎች ሽመናን ሥራ በመተው ወደ ሌላ ሥራ ተሰማርተዋል። አንዳንድ የጋሞ ማሕበረሰብ አባላትም «በቂ» ነው ብለው የሚያስቡትን ገንዘብ ከአጠራቀሙ በኋላ ወደ ትውልድ ቀያቸው ይመለሳሉ። ምክንያቱም በጋሞ ተራራማ ቦታዎች የሽመና ሥራ እና ባለሙያው ከፍተኛ ማሕበራዊ ከበሬታ የተሰጠው ነበርና። በተጨማሪም በዚህ የጊዜ ክልል ውስጥ ከውጭ ሀገር በተለይም ከእንግሊዝ ወደ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገባ የጥጥ ምርት የአዲስ አበባን ገበያ ተቆጣጥሮት ነበር። የከተማዋ ነዋሪም ፊቱን ወደ ዘመን አመጣሾቹ የፋብሪካ ምርቶች አዙሯል። በዚህም ሰበብ በሽመና ሥራ የሚተዳደሩ ባለሙያዎች ገቢ አሽቆልቁሏል። ለችግርም ተጋልጠዋል። በመሆኑም ከጋሞ ውጭ የሆኑ ሌሎች የሽመና ባለሙያዎች በተፈጠረው የምጣኔ ሀብት ቀውስ ምክንያት ወደ ሌላ ሥራ ተሰማርተዋል። የጋሞ ማሕበረሰብ አባላት ግን የተፈጠረውን ማሕበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ ችግር በጽናት በመቋቋም የአዲስ አበባ ምርጥ የሽመና ባለሙያዎች የሚያስብል ደረጀ ላይ መድረሳቸውን የተለያዩ ምሁራን መስክረውላቸው። ከ፲፱፻፭ ዓ/ም ጀምሮ የሸማ ተፈላጊነት የገነነበት ወቅት ነው። የቤተ-መንግሥት ባለሙያዎች እና ፊቱን ወደ ዘመን አመጣሹ የፋብሪካ ምርት አዙሮ የነበረው የአዲስ አበባ ነዋሪ ለተለያዩ ክብረ በዓላት / ለፋሲካ፣ ለጥምቀት፣ ለገና፣/ የማንነቱ መግለጫ አድርጎ በማሰቡ «የአበሻ ልብስ» የሚል ስያሜ ሰጥቷቸዋል። እንዲሁም ሸማዎች በሚለበሱበት የተለያዩ አጋጣሚዎች እና ዓውዶች ላይ የተጠቃሚዎችን ማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዋ፣ ባህላዊና ፖለቲካዊ ደረጃ ማሳየት የጀመሩበት ወቅት ነው። የሸማ ሥራ በአዲስ አበባ በስፋት ከተዋወቀበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ፲፱፻፹፭ ዓ/ም አካባቢ ድረስ በብዛት የሚመረቱ ምርቶች ጋቢ፣ ነጠላ፣ ቀሚስ፣ ጥበብ ልብስ፣ ሙሉ ልብስ ፣ ቡልኮ፣ መጠምጠሚያ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በዝማሬ የሚለብሱት ጥንግ ድርብ ነበሩ። ለሽመናም የሚጠቀሙበት ጥሬ ዕቃ ድር ፣ ማግ እና ጥለት ነበር።እንደ አካባቢው ባህል ይለያይ እንጅ(ስሙ) ድግር መወርወሪያ እና የመሳሰሉትም የሽመና እቃ ውጤቶች ናቸው። የሽያጭ አገልግሎቱሎም በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ ነበር ማለት ይቻላል። በእርግጥ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን የሽመና ውጤቶችን ወደ ውጭ ሀገር ይዘው ይሄዱ ነበር። ይህ ሁሉ ሲሆን ግን በሽመና ዙሪያ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ለእደ ጥበብ ባለሞያዎች ያለን ምልከታ ትንሽ መስተካከል ያለበት ይመስለኛል። ምክንያቱም እንደተናቀ ስራ የመቁጠር አባዜ ስላለብን ነው። ይሄ ደግሞ አንዱን ጥሎ አንዱን አንጠልጥሎ ይሆናል። ነጮች ከብረት ቅጥቀጣ ተነስተው ወደ አውሮፕላን ሲያድጉ እኛ ግን....ነጮች ከሽመና ተነስተው ወደ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ሲያድጉ እኛ ግን...."ብቻ ብዙ የቤት ስራ አለብን። ሸማና ሥልጣኔ ከ፲፱፻፹፭ ዓ.ም. በኋላ ለአዲስ የአሸማመን ስልት፣ ጥሬ ዕቃ፣ አልባሳት እና ጌጣጌጦች መታየት ጀምረዋል። በተለይም በውጭ ሀገር (በአውሮፓና በአሜሪካ) ባሉ «የፋሽን»፣ «የዲዛይን» እና «የስታይል» ማሠልጠኛ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰው በሽመና ሥራ ውጤቶች ላይ መሳተፋቸው አስተዋጽኦው ቀላል አይደለም። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ጥናት ተቋም ከዩኔስኮ ጋር በመተባበር ለሽመና ባለሙያዎች የተለያዩ ተከታታይ ሥልጠናዎች መስጠታቸው እና የመንግስት አካላት የሸማ ባለሙያዎችን በማህበር እንዲደራጁ ማድረጋቸው ለለውጡ የሚጠቀሱ ምክንያቶች ናቸው። እንዲሁም የባህል ልብስ ዓውደ ርዕይ /ፋሽን ሾው/ አዘጋጆች፣ የግል እና የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን አዳዲስ የሽመና ሥራዎችን በማስተዋወቅ በተጠቃሚዎችና በአምራቾች መካከል የመገናኛ ድልድይ ፈጥረዋል። በዚህ ሁኔታ የተለያዩ የለውጥ አሻራ የታተመባቸው የሽመና ውጤቶች የዘመኑን ወጣት ቀልብ ለመሳብ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል። ወጣቱም ከዘመኑ ፋሽን እና ከፍላጎቱ ጋር የሚሄዱ አልባሳት፡- ሸሚዝ፣ ቀሚስ፣ ጉርድ ቀሚስ፣ ሚኒ ፓሪ፣ የአንገት ልብስ፣ ቦርሳ፣ የተለያዩ ጌጣጌጦች… ወዘተ በሽመና ሥራ መመረታቸው ፊቱን ወደ ሽመና ሥራ ውጤቶች እንዲመለስ ጋብዞታል። ይህም ሁኔታ ሰዎች የሀገራቸውን ምርት እንዲጠቀሙ እና በሀገራቸው ምርት እንዲኮሩ መንገድ ከፍቷል። በባዕድ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና አፍቃሪ ኢትዮጵያ የሽመና ውጤቶችን በመጠቀም የኢትዮጵያን ሕዝቦች ባህላዊ አለባበስ ለሌላው ዓለም ሕዝብ ከማስተዋወቅ በተጨማሪ ለውጭ ንግድ በር ከፍተዋል። ያም ሆኖ ሀገራችን ወደ ውጭ ከሚላኩ አልባሳት በቀጥታ ተጠቃሚ አይደለችም። አልባሳቱ ወደ ውጭ የሚወጡት በመደበኛ የንግድ እንቅስቃሴ ሳይሆን በግለሰቦች አማካይነት በሻንጣ ተይዘው ነው። በመሆኑም ከዘርፉ የበለጠ ተጠቃሚ ለመሆን በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የብሔር ብሔረሰቦችን አልባሳት እና የዘመኑን የሽመና ውጤቶች የሚያሳይና የሚያስተዋውቅ ዓውደ ርዕይ / ፋሽን ሾው/ በማዘጋጀት ረገድ የበለጠ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል። ሆኖም የዘመናዊው ትውልድ ጥንት ኢትዮጵያ ጥጡን አብቅላ፣ ፈልቅቃ ነድፋ፣ ፈትላ፣ ሸምና በመልበስ ራሷን በራሷ የምታለብስ እንደነበረና ሠለጠኑ የሚባሉት አገሮች እንኳን በዚህ ረገድ ችሎታ ቢስ እንደነበሩ በመዘንጋት ባህሉ ሲጠፋ፣ ዕውቀቱ ሲያወድም፣ ያችውም በስንት መባተል መድከም የምትገኘው የውጭ ምንዛሪ ለጨርቃ ጨርቅ መግዣ ወደ ሕንድ እና ቻይና ስትገበር እያየ ዝም ብቻ ነው ስሜቱ። ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም ከብዙ ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደአገራቸው ሲመለሱ የገጠማቸውንና የተሰማቸውን «የሕይወቴ ታሪክ» በተባል መጽሐፋቸው ላይ እንዲህ ይሉናል፦ «አዲስ አበባ የገባሁ ዕለት ያገሬን ልብስ ለብሼ ነበር። በማግሥቱ ዘመዶቼ አስለወጡኝ። የፈረንጅ ልብስ ያስከብርሃል፤ ያማራው ያዋርድሃል እያሉ መከሩኝ። ስለዚህ ሐዘን ተሰማኝ፤ የተወልዶየን መምሰል አምሮኝ ነበር፤ ተሣቀቅሁ።.....በማግሥቱ ወደ ግቢ ሄድኩ፤ እንደአውሮፓውያን ለብሻለሁ፤ ልብሴ ሁሉ ፓሪስ የተሰፋ ዘመናይ ነው። ወደ ግቢ ስገባ እስከ ውስጠኛው በር ድረስ ከበቅሎ እንዳልወርድ ዘመዶቼ አስጠንቅቀውኛል። ገና ወደ በሩ ቀረብ ስል በረኛው ጮኸ። ዞር በሉ እያለ መንገዱን አስለቀቀልኝ። (እንደአማራ ለብሼ ቢሆን መመታት አይቀርልኝም ነበር)፤ በገዛ አገሬ ውስጥ ለመከበሪያየ የሰው ልብስ መከታ ስለሆነኝ ልቤ ተቃጠለ።» ዛሬስ ምን ለውጥ አለ? ዋቢ ምንጭ ፊታውራሪ ተክለ ሐዋርያት ተክለ ማርያም፣ "ኦቶባዮግራፊ (የሕይወቴ ታሪክ)፣ (፲፱፻፺፰ ዓ/ም)፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ባህል፣ ቋንቋና ጥበብ ፦ አዲስ አበባ ባለፈውና በአዲሱ ሚሌኒየም የኢትዮጵያ ታሪክ
15722
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%89%85%E1%8B%B0%E1%88%8B
መቅደላ
መቅደላ ወይም በአሁኑ ስሙ አምባ ማርያም የሚባለው አምባ፣ ወሎ ውስጥ የሚገኝ በአጼ ቴወድሮስ ዘመን ለዋና ከተማነት ታጭቶ በመካከሉ በእንግሊዞች ጦርነት ወቅት የተቃጠለ ከተማ ነው። በአሁኑ ወቅት በአካባቢው 1899 ሰወች ይኖራሉ። መቅደላ አምባ እና ዓፄ ቴዎድሮስ መቅደላ አምባ ለመድረስ ከደሴ ከተማ በስተምዕራብ ፻፳፰ ኪ/ሜ ርቀት ላይ ከምትገኘው የተንታ ከተማ በስተሰሜን ምስራብ ፳፱ ኪ/ሜ መጓዝን ይጠይቃል፡፡ ጥንት ከመቅደላ ደብረ ታቦር ከዚያም ወደጣና ሐይቅ ዳርቻ የሚያዘልቅ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ጐብኝዎች የሚታወቅ የእግር መንግድ ነበር፡፡ ግን ልክ እንደ ጥንታዊው የላሊበላ ሰቆጣ መንገድ ሁሉ መስመሩ ከተዘጋ ዘመናት ተቆጥረዋል። መቅደላ ሲነሳ ዓፄ ቴዎድሮስ መታወሳቸው የማይቀር ነው፡፡ የመቅደላ አምባ ዙሪያ ገባውን ከርቀት ለመቆጣጠር የሚያስችል በመሆኑና በዘመኑ የፖለቲካ ከርሰ-ምድር ሁነኛ ሥፍራ ላይ በመገኘቱ ከፍተኛ ቁልፋዊ ጥቅም ነበረው፡፡ ይህ ጠቀሜታ ደግሞ በወቅቱ ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ ለሚጥር ንጉሥና ባለሟሎቹ የሚሰወር አልነበረም። በንጉሠ ነገሥቱ የፖለቲካ ሥልጣን መባቻ ለሰባት ወራት የተካሄደው የወሎ ዘመቻ የተጠናቀቀውም በመቅደላ መያዝ ነበር፡፡ ዓፄ ቴዎድሮስ ከጎንደር በኋላ የሥልጣን ማእከላቸውን ለጊዜው ወደ ደብረ ታቦር ከዚያም ወደመቅደላ በማዞር ለተቀረው ግዛት ዓርዓያ ሊሆን የሚችል የአስተዳደር ሥርዓት ለማቆም ጥረት የጀመሩት በዚሁ ሥፍራ ነበር፡፡ በርካታና የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች፣ ብዛት ያላቸው ገድሎች፣ መጻሕፍትና ድርሳናት እንዲሁም የንጉሠ ነገሥቱ የግል የክብር ዕቃዎች በሥርዓት ተሰድረው ይቀመጡ የነበረው በመቅደላ ግምጃ ቤት ነበር። በዘመኑ ፲፭ መድፎች፣ ፯ ሞርታሮች፣ ፲፩ ሺ ፷፫ የተለያዩ ጠመንጃዎች፣ ፰፻፸፭ ሽጉጦችና ፬፻፹፩ ሳንጃዎች፣ ፭፻፶፭ የመድፍና የሞርታር አረሮች እንዲሁም ፹፫ ሺ ፭፻፷፫ የተለያዩ ጥይቶች በመቅደላው ግምጃ ቤት እንደነበሩ መረጃዎች ይገልፃሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን ለታሪክ መዘክርነት በቦታው ከሚገኙት ቅርሶች አንዱ ‘ሴባስቶፖል’ የተባለው የንጉሠ ነገሥቱ ትልቅ መድፍ እና ዓፄ ቴዎድሮስ ጊዜያዊ ቤተ መንግሥት ፍርስራሽና የመቃብር ቦታዎች ናቸው፡፡ መጽሐፍቱ፣ ድርሳናቱ፣ የወርቅና ብር ዋንጫዎች፣ አክሊሎችና ሌሎች የንጉሠ ነገሥቱ የግል ሀብቶች የነበሩ ቅርሶች ሁሉ ከመቅደላው ጦርነትና ከዓፄ ቴዎድሮስ እረፍት በኋላ በደላንታ ሜዳ ለጨረታ ተሰጥተው በ ናፒዬር የተመራው የእንግሊዝ ሠራዊት ተቀራምቷቸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ከንጉሠ ነገሥቱ አናት ላይ የተሸለተውን ሹሩባ ፀጉር ጨምሮ ሌሎች ቅርሶች በእንግሊዝ አገር የተለያዩ የሥነ-ቅርስ መዘክሮች ውስጥ ተቀምጠው ይገኛሉ። ከዓርዓያዊ የአስተዳደር ማዕከልነትና ግምጃ ቤትነት ባሻገር የንጉሠ ነገሥቱ ወህኒ ቤትም የሚገኘው በመቅደላ ነበር፡፡ በእጅ ተይዘው በሞት ያልተቀጡ ጠንካራ የሥልጣን ተቀናቃኞች፣ ምርኮኞችና አማጽያን ከመቅደላ ነዋሪዎች ጥቂቶቹ ነበሩ። ከእነዚህም አንዱ የኋላው ንጉሠ ነገሥት የያኔው ደጃዝማች ምኒሊክ ናቸው። ምኒልክ ለ አሥራ አንድ ዓመታት የመቅደላ እስረኛ ነበሩ። አጼ ቴዎድሮስ ከእንግሊዝ መንግሥት ጋር በነበራቸው ጠብ እልህ ውስጥ ገብተው በጎንደር ይኖሩ የነበሩ የውጭ ዜጎችን ሰብስበው ያጎሩት በመቅደላው ወህኒ ቤት ነበር፡፡ በመጨረሻም የመቅደላ አምባ የአጼ ቴዎድሮስ ሥልጣን መደላደል ምልክት የመሆኑን ያህል የፍጻሜያቸውም ተምሳሌት ሆኗል። ሁሉም ነገር አብቅቶ የማይቀረው ፍፃሜ ሲቀርብ ራሳቸውን በክብር ያጠፉት በዚሁ በቅደላ አምባ ነው፡፡ የመቅደላ አምባ ከአጼ ቴዎድሮስ ሞት በኋላም እስረኞች የሚታገቱበት ሥፍራ መሆኑ አልቀረም። ከሰገሌ ጦርነት አምስት ዓመት ቀደም ብሎ በታኅሣሥ ወር ፲፱፻፫ ዓ/ም የወሎው ራስ ሚካኤል አልጋ ወራሽነት ታጭተው የነበሩትን የልጃቸውን የልጅ ኢያሱን ሥልጣን ለማጠናከርና ሁኔታዎችን ለመቆጣጠር ወደ ስምንት ሺህ የሚደርስ የወሎ ሠራዊትን አስከትለው ወደ አዲስ አበባ ከዘመቱ በኋላ ይደርሳል ተብሎ የተፈራው ግጭት በአቡኑ እና በእጨጌው ገላጋይነት በርዶ ራስ ሚካኤል ወደ ወሎ ሲመለሱ ከአመጹት መካከል አንዱ ናቸው ያሏቸውን ራስ አባተ ቧ ያለውን ወደ መቅደላ በመውሰድ ለአምሥት ዓመታት በእስር አቆይተዋቸዋል፡፡ ከሰገሌ ጦርነትም በኋላ ልጅ ኢያሱ እራሳቸው ከማዕከላዊው መንግሥት በሸሹበት ጊዜ እዚሁ መቅደላ ላይ ለጥቂት ጊዜ መሽገው እንደነበር ታሪክ ይዘግባል። ታሪኩን ለሚያውቅ የመቅደላ ጉብኝት ልዩ ስሜት ይፈጥርበታል፡፡ ሁሉም ጐብኝ ግን የቴዎድሮስን ፍፃሜ በዓይነ ህሊናው ማስተዋሉ አይቀርም፡፡ በመቅደላ አምባ አካባቢ ሊጐበኙ ከሚችሉ ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርሶች መካከል በ፬ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአብርሐ ወአጽብሐ ዘመነ መንግሥት መተከሉ የሚነገርለት የሰላምጌ ሥላሴ፣ በአጼ ላሊበላ ዘመን ከአንድ አለት ተፈልፍሎ የተሠራው የፉል አምባ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን፣ በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዓፄ ይስሐቅ ዘመነ መንግሥት መመሥረቷ የሚታመነው የመቅደላ ማርያምና በ፳ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በንጉሥ ሚካኤል የተሠራው የተንታ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት ዋናዎቹ ናቸው፡፡ በውስጣቸውም የኢትዮጵያን ጥንታዊነት የሚዘክሩና በርካታ ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን ይዘዋል። ዋቢ ምንጭ “አማራ ክልልና መስህቦቿ” የኢትዮጵያ ተራሮች የኢትዮጵያ ከተሞች አጼ ቴዎድሮስ
51110
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8A%A4%E1%88%8D
ኢትኤል
አባታችን አዳም በዕለተ አርብ በነግህ ከተፈጠረ በኋላ እናታችን ሔዋን በሳምንቱ አርብ በዘመናችን አነጋገር 3 ሰዓት ላይ ከግራ ጎኑ ተፈጠረች። በገነትም 7 ዓመት ከ3 ወር ከ 17 ዕለታት ካሳለፉ በኋላ ሕግን ተላልፈው እፀ በለስን በመብላታቸው ከገነት ተባረሩ። በዚህ ግዜ አምላካችን እግዚአብሔር ለአዳም የተስፋ ቃል ሰጠው፤ እርሱም ከልጅ ልጅህ ተወልጀ ከ5 ቀን ከመንፈቅ በኋላ አድንሃለሁ የሚል ቃል ነበረ። ይህ የተስፋ ቃልና ከመላእክት ለአዳም የተሰጡትን ስጦታዎች አዳምና የልጅ ልጆቹ ሲቀባበሉት ቆይቶ ከካሕኑ መልከጼዴቅ እጅ ላይ ደረሰ። ከመልከጼዴቅ አንዳንዶቹ ለአብርሃም ተሰጠ ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ለኢት-ኤል ተሰጠ ይላሉ። 🔰መልከጼዴቅም ኢት-ኤልን እንዲህ አለው፦ “ ይህን የዕንቁ እንክብል ውሰድ፤ ሄደህም በአባይ ወንዝ መነሻ ኑሮህን መስርት። እንክብሉ በርሃብና በመከራ ወቅት ይጠቁራል፤ በጥጋብና በመልካም ወቅቶች ደግሞ ያበራል፤ ኢትዮጵያውያን የሚሆኑ ትውልዶችህ ይህን ዕንቁ ተንከባክበው እንዲጠብቁ እዘዛቸው። የሰላሙ ንጉሥ መወለዱንም አንድ ብሩህ ኮከብ ከሰማይ ያመላክታቸዋል፤ ጨረሮቹም ንጉሡ ወደ ሚወለድበት አቅጣጫ ይፈነጥቃሉ። በተወለደበት ቦታ ላይ ሲደርሱ ኮከቡ ንቅናቄውን ያቆማል። ነግሥታቱ ልጆችህም በዚያ ለንጉሡ ‘አንተ የዘላለም አምላክ ነህ’ ብለው ይስገዱለት። ልዩ የሆነውንም የኢትዮጵያ ‘ዮጵ’ የተባለውን ቢጫ ወርቅ፤ እንዲሁም ዕንጣንና ከርቤ ለሰላሙ ንጉሥ ገጸ-በረከት ያቅርቡለት። ” 🔰ከዚህ በኋላ ደሸት(ዘረ ደሸት) 1400-1600 ቅ.ል.ክ ላይ በጣና ዳር ሆኖ ሲጸልይና ከዋክብትን ሲመራመር ድንግል ከነልጅዋ በራእይ ተመለከተ፤ እርሱንም በወርቅና በብር ሰሌዳ ላይ ጽፎ ለትውልድ አስተላለፈ። ከነሸምሸልና ከነ ቀራሚድ በኋላ ደሸት ጣና አከባቢ ጎጃም ውስጥ ደሸት በተባለ ስፍራ ላይ ይኖር ነበረ። ሰብአ ሰገሎች ማን ናቸው ? ( ስለ ሰብአ ሰገሎች ከማብራራታችን በፊት የስማቸውን አንድምታ ማወቅ ይኖርብናል። #ሰብእ ማለት በግእዝ ቋንቋ #ሰው ማለት ሲሆን #ሰገል ማለት ደግሞ #ጥበብ ፈላስፋ እንደማለት ነው። በእንግሊዘኛው ሐዲስ ኪዳን ‘’ ይላቸዋል፤ በብዙ ቁጥር ሲሆን ደግሞ ‘’ ይላቸዋል። እነዚህ ነገሥታት በሥነ-ከዋክብት እውቀት ላይ የተራቀቁ እንደነበሩ ሁሉም ተመራማሪዎች ይስማሙበታል። በቀደምቱ ዓለም ደግሞ ሥነ-ጠፈር፥ ሥነ-ከዋክብትንና ሥነ ሕክምናን ከዓለም አስቀድማ ያጠናችና ጥበቡን ያስተላለፈች ቅድስት ምድር ኢትዮጵያ እንደነበረች ብዙዎች ይስማማሉ። 🔰ተመራማሪው ሉስያን “ ” በማለት ኢትዮጵያ በሥነ ከዋክብትና በተለያዩ ዘርፎች ገናና ጥበብ ከነበራቸውን ሀገራት ውስጥ ተጠቃሽ ናት። 🔰መምሕር መስፍን ሰሎሞን “7 ቁጥር” በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “ ባቢሎን፥ ግሪክ፥ ሕንድ፥ ኢትዮጵያ፥ ሮም፥ ቻይናና ፋርስ በቀደመው ዓለም 7 የሥነ-ጠፈር አጥኚ ሀገራት ናቸው” በማለት አስፍረዋል። ነገር ግን ስለ ሰብአ ሰገል መነሻ ስፍራ አንድ ወጥ የሆነ አስተሳሰብ የለም፤ ትልቅ ጥናት የሚያስፈልገው የታሪክ ክስተት ነው። አንዳንዶቹ በፋርስ ከነበረ “” ማኅበረሰብ የመጡ ናቸው ይላሉ፤ ይሄም “” የሚለው ስያሜ የመጣበት ማኅበረሰብ እንደሆነ ይገመታል። አንዳንዶቹ የፋርስ ሰዎች ናቸው በማለት ዘረ-ደሸት የተባለ ሰው በፋርስ ይኖር ነበረ ይላሉ፤ ይህ ግን በጣም አስቂኝ ነገር ነው ዘረ-ደሸትን ከዞሮአስተር ጋር እያየያዙት ነው። በሀገራችን ደሸት የተባለ ቦታ አሁን ድረስ ጣና አከባቢ ይገኛል። ታዲያ ይህንን ታሪክ ከኢትዮጵያ በማውጣት ለሌላ ዓለም እየሰጡ ነው፤ ልክ የትሮይ ጦርነትን ኢትዮጵያውያን ተዋግተው ታሪኩ ግን ለግሪክ እንደተሰጠው የታሪክ መዛባትና ስርቆት ማለት ነው። 🔰ታላቁ የቤተ-ክርስቲያናችን ሊቅ አለቃ አያሌው ታምሩ ሰብአ ስገል 3 ሲሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነበሩ ብለው “የኢትዮጵያ እምነት በ፫ቱ ሕግጋት” በተባለው መጽሐፋቸው ላይ አስፍረው አልፈዋል። በርካታ የታሪክ ተመራማሪዎች ቁጥራቸው 3 ናቸው በማለት ስማቸውን እንዲህ በማለት ይዘረዝራሉ። ሜልኩ[ሜልኪዮር]- የፐርሽያ ንጉሥ ፥ ማንቱሲማር[ጋስፓር]- የሕንድ ንጉሥና በዲዳስፋ የኢትዮጵያ ንጉሥ በሚለው ስያሜ በርካታ ተመራማሪዎች ይስማማሉ። ተመራማሪዎቹ ሰብአ ሰገል 3 ናቸው ያሉበት ዋና ምክንያት ወርቅ፥ ዕጣንና ከርቤን በመገበራቸው ነው። 🔰ከምዕራባውያን ተመራማሪዎች ውስጥ ዊልያም ሊዮ ሀንስበሪና ኢሀርፐር ጆንሰን “” በተባለው ጽሁፋቸው ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ናቸው ቁጥራቸውም 3 ናቸው ይላሉ። አንዳንድ ተመራማሪዎች 3 ፤ አንዳንዶቹ ደግሞ 12 ናቸው እያሉ የየራሳቸውን ማስረጃዎች ያቀርባሉ። ☑️ሰብአ ሰገል ኢትዮጵያዊ ለመሆናቸው ማስረጃዎች ( ሰብአ ሰገሎች ኢትዮጵያዊ ናቸው ከሚሉት ውስጥ አለቃ አያሌው ታምሩ፥ አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ፥ ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ፥ መሪ ራስ አማን በላይ እንዲሁም ከላይ የተጠቀሱት ዊልያም ሊዮ ሀንስበሪና ኢሀርፐር ጆንሰን ተጠቃሽ ናቸው። እኒህ መረጃ አድርገው የሚያቀርቧቸው ማስረጃዎች ውስጥ ትንቢተ ኢሳያስ 60፥ 6 ላይ ያለው ቃል ዋነኛው ነው፤ ነገሥታቱ የሳባ ነገሥታት ናቸው ብቻ ስለሚል ነገሥታቱ የሳባ ነገሥታት ናቸው ማለት እኒህ ነገሥታት የተነሱት ከኢትዮጵያ ነው ማለት ነው። እንዲሁም መዝ. 71፥ 9-10 ላይ “በፊቱም ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ፤ ጠላቶቹም አፈር ይልሳሉ” በሚለው ቃል ላይ “ኢትዮጵያ” ብሏልና እነዚህ ሰብአ ሰገል ኢትዮጵያዊ ናቸው ብለው ማስረጃ ያቀርባሉ። ከላይ የተጠቀሰው የደሸት ታሪክም አንዱ ማስረጃ ሲሆን ዋናው ማስረጃ ደግሞ ኢትዮጵያ ከዓለም ብቸኛዋ ወርሃ ተኅሣሥን ከሰብአ ሰገል ጋር አያይዛ የሰየመች መሆኑ ነው። ታኅሣሥ ትርጉሙ የማሰስ የመፈለግ ወር ማለት ነውና። ስለ ሰብአ ሰገል በመጽሐፍ ቅዱስ በማቴ. 2 ላይ የተነገረ ሲሆን ከምሥራቅ መጡ ይላል እንጂ ስማቸውን አይዘረዝርም። ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳና መሪ ራስ አማን በላይ በሰብአ ሰገል ዙሪያ ተመሳሳይ አመለካከቶች ሲኖራቸው ሰብአ ሰገል 12 ናቸው የተነሱትም ከኢትዮጵያ ነው ይላሉ። 🔰የእያንዳንዱን ነገሥታት ስምም በመጽሐፋቸው ላይ እንዲህ ብለው አስፍረዋል። 1- የጎንጂ ንጉሥ አጎጃ ጃቦን ዮጵ ወርቅ ይዞ ተነሣ 2- አቦል 3- ቶና 4- በረካን 3ቱ የአጎጃ ጃቦን ወንድም የዳጋ ነገሥታት ነበሩ። 5- የሱዳንና የአረብ ንጉሥ መሊ አቡሰላም 6- የሰገልና የማጂ ንጉሥ መጋል 7- የኤውላጥ[ኦጋዴን]ና የሶማሊያ ንጉሥ መቃዲሽ ከርቤ ይዞ ተነሣ 8- የአዳል ንጉሥ አውርና 9- የአፋር ንጉሥ ሙርኖ ዕጣን ይዘው። 10- የአዘቦ ንጉሥ አጋቦን 11- የኑባው ንጉሥ ሀጃቦንና 12- በሳባ ከተማ በሃማሴን ይቀመጥ የነበረው አርስጣ ናቸው። ሰብአ ሰገል 12 መሆናቸው ከ12ቱ ሐዋርያት ጋር የተያያዘ መለኮታዊ ምስጢር አለው በማለት 2ቱ ተመራማሪውች የኢትዮጵያ ትንሣኤ ታሪክና ስውሩና ያልተነገረው የኢትዮጵያውያንና የአይሁዳውያን ታሪክ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ አስፍረዋል።አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ በመጽሐፋቸው ላይ ሰብአ ሰገል 3 ነገሥታትና 2 ልዑላን ናቸው በማለት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ናቸው ይሉንና እኒህ ነገሥታት ኢትዮጵያዊ ናቸው፤ ቀለማቸው ግን ነጭ ሊኖር ይችላል። ያ ኢትዮጵያዊነታቸውን አይፍቅም። ኢትዮጵያዊ ከአንድ እናትና አባት 4 አይነት ቀለም ያላቸው የተለያዩ አበባ የመሰሉ ልጆችን ይወልዳሉና ይላሉ በጥናታቸው ላይ። 🔰አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ የነገሥታቱን ስምና የትውልድ ቦታ እንዲህ በማለት ያብራሩታል። 1- ናሁ አዳም(ከወንድሙ ጋር) ተነሳ ከኢትዮጵያ 2- ራይናስ(ከወንድሙ ጋር) ከምሥር 3- አሕራም ከየመን ኮከቡን ያዩት በነገሡ በ13ኛው ዕለት ሲሆን የጉዞው መሪ ከ3ቱ ኢትዮጵያውያን ውስጥ እስከ መካከለኛው ምሥራቅ ይገዛ የነበረው ናሁ አዳም ነው ይላሉ። ~ በአጠቃላይ በሰብአ ሰገል ማንነት ላይ ሁሉም ተመራማሪዎች ቢያንስ ከ3 ወይንም ከ12 አንዱ ኢትዮጵያዊ ነው በማለት ይስማማሉ። 🔰ከላይ የጠቀስናቸው የመጽሐፍ ቅዱስ የትንቢተ ኢሳያስና የመዝሙረ ዳዊት አገላለጾችና አንድምታዎች በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሥነ-ጠፈር ምርምር የተራቀቀች መሆኗ ሰብአ ሰገል ኢትዮጵያዊ ናቸው ወደሚለው ጥናት ይወስደናል። በዚያም ሆነ በዚህ ሰብአ ሰገል ውስጥ አንዱ ወይንም ከዚያ በላይ የሆኑት ኢትዮጵያዊ ናቸው የሚለው ሃሳብ ሁሉንም ተመራማሪዎች ያስታርቃል። ☑️ሰብአ ሰገል የተመለከቱት ኮከብ ምን አይ ከጠዋቱ ፀሐይ እንደወጣች ልክ ሦስት ጫማ በዘመናችን አነጋገር ከጠዋቱ 3 ሰዓት እንደሆነ ጂራቱ 13 ክንድ የሚያህል 7 ሕብረ ቀለማት ያለው በጣም የሚያምር ጂራታም ኮከብ ከምሥራቅ በኩል ወጥቶ በኢትዮጵያና በዓለም ላይ አበራ፤ ይህንን ኮከብ የሚያዩት ለማየት ከአምላካችን #ሥላሴ የተፈቀደላቸው ብቻ ናቸው። ይላሉ አባ ተስፋ ሥላሴ ሞገስ። 🔰በተመሳሳይ የታኅሣሡ ስንክሳር “ልውጥ ኮከብ” ይለዋል፤ ይህም የሚቀያየር የሚሰወር ኮከብ ለማለት ሲሆን አንድም ሕብረ ቀለሙን ለመግለጽም ነው። ሰብአ ሰገል በመሃል ከተማ በሚገቡበት ጊዜ ኮከቡ ይሰወራቸው ነበር ይላል። ኮከቡ አንዴ ሕጻን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን አንዴ ደግሞ ራስ፥ እጅና እግር ያለውን ሰው ይመስል ነበረ። ይህ ኮከብ የታየው ክርስቶስ ከመወለዱ ከ2 ዓመታት በፊት ነበረ፤ ይሄም ቀድሞ በቅድስት ሥላሴ ፈቃድ የተከናወነ ጎዞ መሆኑን ያመለክተናል። ምክንያቱም ከ2 ዓመት በኋላ በቤተልሔም ስለሚደርሱ ነው። 🔰ስለ ኮከቡ ምንነት በቤተክርስቲያን አስተምሕሮ መሰረት ሁሉም አንድ ወጥ ሃሳብ አላቸው፤ ‘ኮከቡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ነው’ የሚል። ለዚህም ማስረጃ የሚሆነን ኮከብ በቀን አይታይምና ኮከብ ዝቅ ብሎ እነርሱ ባሉበት ደረጃ አይጓዝም የሚል ነው። ኮከብ የተባለው በምስጢራዊ አነጋገር ነው ይላሉ መተርጉማነ መጻሕፍት። ☑️የሰብአ ሰገል ጉዞ[ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም] ( ሰብአ ሰገል ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም የሄዱት ስዊዝ ካናል ከመከፈቱ በፊት መንገድ ነበረ በዚያ ነው። ከቦታው ለመድረስም 2 ዓመት ፈጅቶባቸዋል። በትርክቶች መሰረት ሲነሱ 12 ነገሥታት ሲሆኑ ኢየሩሳሌም ግን የደረሱት 3ቱ ናቸው ይባላል፤ ምክንያቱም ስንቅ ስላለቀባቸውና ጦር ስለ ተነሳባቸው ነው ይላሉ። ይህ ግን በኢትዮጵያ መዛግብት ዘንድ ተቀባይነት የለውም። ሰብአ ሰገል ኢየሩሳሌም ሲደርሱ ከተማዋ ተሸበረች እነ ሄሮድስ ደነበሩ፤ ለወረራ የመጡ መስሏቸው ነበረና ኢትዮጵያውያን ሮማውያንን ከጥንት ጀምሮ አይቀጡ ቅጣት ይቀጧቸው ነበረና። እነርሱም ለንጉሡ ልንሰግድለትና ሥጦታ ልንሰጥ መጣን ሲሉ ሄሮድስ ተደሰተ ለርሱ መስሎት ነበረና፤ ለርሱ አለመሆኑን ሲረዳ ግን ተበሳጨ ከእኔ ውጭ የይሁዳ ንጉሥ አለ እንዴ በሚል ተናደደ። እነርሱንም ንጉሡን ስታገኙት ንገሩኝ እኔም መጥቼ እንድሰግድለት አላቸው። 🔰ሰብአ ሰገል ከበረቱ በደረሱ ጊዜ ኮከቧ ቆመች[ ከላይ መልከጼዴቅ ያለውን ይመልከቱ] ወደ ውስጥም ገብተው ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስና ለእናቱ ለድንግል ማርያም ሰግደው ዮጵ ወርቅ፥ ዕጣን፥ ከርቤ፥ ቅባት፥ አክሊል፥ ዘውድ፥ በትረ መንግሥት፥ በትረ መስቀልና ሽቶ ሥጦታ አበረከቱ። ☑️ሰብአ ሰገል ከዚህ ሁሉ በኋላ አስቀድሞ የአምላክን ሰው መሆን ለድንግል ማርያም ባበሰራት በሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ትእዛዝ በነፋስ ኃይል በብርሃን ሰረገላ በስውር ዓለምን ዙረው ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ከተመለሱ በኋላ የአምላክን ሰው መሆን የምስራች ለኢትዮጵያ ሕዝቦች በሙሉ አበሰሩ የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች በመሆን ሰበኩ። ከዚህ በኋላ ዋልድባ[አርምኃ ደጋ] በመግባት ከአበው ጋር በመቀላቀል አምላክን ሲያገለግሉ ኖሩ። 😲ሰብአ ሰገል በሕይወት ይኖራል እንጂ አልሞቱም፥ ቅዱስ ገብርኤል ጌታን ዳግም እስከምታዩት ድረስ አትሞቱም ብሏቸዋልና አሁን እንደነ ነብዩ ሄኖክ፥ ቅዱስ ኤልያስ፥ ቅዱስ ያሬድ፥ ቅዱስ ነአኩቶለአብ፥ አቡነ አረጋዊ እንዲሁም ሌሎች ቅዱሳን ተሰውረው ይገኛሉ። ፨ኢትኤል ኢትዮጵያን የሰራ ድንቅ ጥበበኛ መሪ ነበር። ተጻፈ በኃይለሚካኤል ደሣለኝ - - መንገደ ጥበብ / ዩቲዩብ ቻናል።
11754
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B6%E1%89%AA%E1%8B%AC%E1%89%B5%20%E1%88%95%E1%89%A5%E1%88%A8%E1%89%B5
ሶቪዬት ሕብረት
ሶቪየት ዩኒየን፣[] በይፋ የሶቪየት ሶሻሊስት ሪፐብሊካኖች ህብረት ከ1922 እስከ 1991 ድረስ ዩራሺያንን ያቀፈ የሶሻሊስት ግዛት ነበር። [] በተግባር መንግሥቱ እና ኢኮኖሚው እስከ መጨረሻዎቹ ዓመታት ድረስ በጣም የተማከለ ነበር። ሀገሪቱ የአንድ ፓርቲ መንግስት ነበረች (ከ1990 በፊት) በሶቭየት ዩኒየን ኮሚኒስት ፓርቲ የሚተዳደር ሲሆን በሞስኮ ዋና ከተማዋ በትልቁ እና በሕዝብ ብዛት በሩስያ ኤስኤፍኤስአር. ሌሎች ዋና ዋና የከተማ ማዕከሎች ሌኒንግራድ (የሩሲያ ኤስኤስአር)፣ ኪየቭ (የዩክሬን ኤስኤስአር)፣ ሚንስክ (ባይሎሩሺያ ኤስኤስአር)፣ ታሽከንት (ኡዝቤክ ኤስኤስአር)፣ አልማ-አታ (ካዛክኛ ኤስኤስአር) እና ኖቮሲቢርስክ (የሩሲያ ኤስኤስአር) ነበሩ። ከ22,402,200 ስኩዌር ኪሎ ሜትር በላይ (8,649,500 ስኩዌር ማይል) የሚሸፍን እና አስራ አንድ የሰዓት ሰቆችን የሚሸፍን ትልቁ ሀገር ነበረች። የሶቪየት ኅብረት ሥሮቿ በ1917 የጥቅምት አብዮት የመሠረቱት በቭላድሚር ሌኒን የሚመራው ቦልሼቪኮች ቀደም ሲል የሩስያን ኢምፓየር የሮማኖቭን ቤት የተካውን ጊዜያዊ መንግሥት ገልብጠው ነበር። የሩስያ ሶቪየት ሬፐብሊክ ሪፐብሊክን መስርተዋል, በአለም የመጀመሪያው በህገ-መንግስታዊ ዋስትና ያለው የሶሻሊስት መንግስት ነው.[] ውጥረቱ ተባብሶ በቦልሼቪክ ቀይ ጦር እና በቀድሞው ኢምፓየር ውስጥ ባሉ በርካታ ፀረ-ቦልሼቪክ ኃይሎች መካከል ወደ እርስ በርስ ጦርነት ተለወጠ፣ ከእነዚህም መካከል ትልቁ ክፍል ነጭ ዘበኛ ነበር። የነጩ ጠባቂው በቦልሼቪኮች እና በተጠረጠሩ ሰራተኞች እና ገበሬዎች ቦልሼቪኮች ላይ ነጭ ሽብር በመባል የሚታወቀውን የጸረ-ኮሚኒስት ጭቆና ላይ ተሰማርቷል። የቀይ ጦር አስፋፍቶ የአካባቢውን ቦልሼቪኮች ሥልጣን እንዲይዙ፣ ሶቪዬቶችን በማቋቋም፣ የፖለቲካ ተቃዋሚዎቻቸውን እና ዓመፀኛ ገበሬዎችን በቀይ ሽብር ጨቋኙ። እ.ኤ.አ. በ 1922 የኃይል ሚዛኑ ተቀይሯል እና ቦልሼቪኮች በድል ወጡ ፣ የሩሲያ ፣ ትራንስካውካሲያን ፣ ዩክሬን እና ባይሎሩሺያን ሪፐብሊኮችን በማዋሃድ ሶቪየት ህብረትን አቋቋሙ ። የእርስ በርስ ጦርነቱ ሲያበቃ የሌኒን መንግስት የነጻ ገበያ እና የግል ንብረት በከፊል እንዲመለስ ያደረገውን አዲስ የኢኮኖሚ ፖሊሲ አስተዋወቀ። ይህም የኢኮኖሚ ማገገሚያ ወቅት አስከትሏል. በ1924 የሌኒን ሞት ተከትሎ ጆሴፍ ስታሊን ወደ ስልጣን መጣ። ስታሊን በኮሚኒስት ፓርቲ ውስጥ ያለውን አገዛዝ የሚቃወሙትን ሁሉንም የፖለቲካ ተቃዋሚዎች አፍኖ የዕዝ ኢኮኖሚን ​​አስመረቀ። በዚህ ምክንያት ሀገሪቱ ፈጣን የኢንደስትሪላይዜሽን እና የግዳጅ ስብስብ ሂደት ውስጥ ገብታ ከፍተኛ የኢኮኖሚ እድገት ያስመዘገበች ቢሆንም በ1932-1933 ሰው ሰራሽ የሆነ ረሃብ አስከተለ። የጉላግ የሠራተኛ ካምፕ አሠራርም በዚህ ጊዜ ውስጥ ተስፋፋ። በተጨማሪም ስታሊን የፖለቲካ ፓራኖይያን በማነሳሳት ተቃዋሚዎቹን ከፓርቲው ለማስወገድ ወታደራዊ መሪዎችን፣ የኮሚኒስት ፓርቲ አባላትን እና ተራ ዜጎችን በጅምላ በማሰር ወደ ማረሚያ ካምፖች ተላኩ ወይም ሞት ተፈረደባቸው። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 23 ቀን 1939 ፀረ ፋሺስት ከምዕራቡ ዓለም ኃይሎች ጋር ፀረ-ፋሺስት ጥምረት ለመመሥረት ያልተሳካ ሙከራ ካደረጉ በኋላ ፣ ሶቪየቶች ከናዚ ጀርመን ጋር ጠብ የለሽ ስምምነት ተፈራረሙ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት መጀመር በኋላ የፖላንድ፣ ሊትዌኒያ፣ ላትቪያ እና ኢስቶኒያ ምስራቃዊ ክልሎችን ጨምሮ መደበኛ ገለልተኛ ሶቪየቶች የበርካታ የምስራቅ አውሮፓ ግዛቶች ግዛቶችን ወረሩ እና ያዙ። ሰኔ 1941 ጀርመኖች ወረሩ ፣ በታሪክ ትልቁ እና ደም አፋሳሹ የጦርነት ቲያትር ከፈቱ ። እንደ ስታሊንግራድ ባሉ ኃይለኛ ጦርነቶች በአክሲስ ኃይሎች ላይ የበላይነትን በማግኘቱ ሂደት የሶቪዬት ጦርነቶች ሰለባዎች አብዛኞቹን በግጭቱ የተጎዱትን ሰለባዎች አድርሰዋል። የሶቪየት ኃይሎች በመጨረሻ በርሊንን ያዙ እና ግንቦት 9 ቀን 1945 በአውሮፓ ሁለተኛውን የዓለም ጦርነት አሸንፈዋል። በቀይ ጦር የተቆጣጠረው ግዛት የምስራቅ ብሎክ የሳተላይት ግዛቶች ሆነ። የቀዝቃዛው ጦርነት በ 1947 ብቅ አለ ፣ የምስራቅ ብሎክ የምእራብ ብሎክን ተጋፍቷል ፣ እሱም በ 1949 በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት ውስጥ አንድ ይሆናል ። እ.ኤ.አ. በሚሊዮን የሚቆጠሩ ገበሬዎች በኢንዱስትሪ የበለጸጉ ከተሞች ውስጥ በመውደቃቸው አገሪቱ በፍጥነት አደገች። ዩኤስኤስአር በጠፈር ውድድር ቀዳሚውን ስፍራ የወሰደው በመጀመርያው የሳተላይት እና የመጀመሪያውን የሰው ልጅ የጠፈር በረራ እና የመጀመሪያውን ፕላኔት ቬነስ ላይ ለማረፍ ነው። እ.ኤ.አ. በ1970ዎቹ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የነበረው ግንኙነት አጭር ነበር፣ ነገር ግን እ.ኤ.አ. በ1979 የሶቭየት ህብረት ወታደሮቿን በአፍጋኒስታን ስታዘምት ውጥረቱ እንደገና ቀጠለ። ጦርነቱ ኢኮኖሚያዊ ሃብቱን ያሟጠጠ እና የአሜሪካ ወታደራዊ እርዳታ ለሙጃሂዲን ተዋጊዎች መባባስ ነበር። እ.ኤ.አ. በ 1980 ዎቹ አጋማሽ ላይ የመጨረሻው የሶቪየት መሪ ሚካሂል ጎርባቾቭ በግላኖስት እና በፔሬስትሮይካ ፖሊሲዎች ኢኮኖሚውን የበለጠ ለማሻሻል እና ነፃ ለማድረግ ፈለገ። ግቡ የኢኮኖሚ ድቀት እየቀለበሰ የኮሚኒስት ፓርቲን መጠበቅ ነበር። የቀዝቃዛው ጦርነት በእርሳቸው የስልጣን ዘመን ያበቃ ሲሆን በ1989 የዋርሶ ስምምነት በመካከለኛው እና በምስራቅ አውሮፓ የየራሳቸውን የማርክሲስት ሌኒኒስት አገዛዞችን ገለበጡ። በዩኤስ ኤስ አር አር ላይ ጠንካራ የብሔርተኝነት እና የመገንጠል እንቅስቃሴ ተከፈተ። ጎርባቾቭ በሊትዌኒያ፣ ላትቪያ፣ ኢስቶኒያ፣ አርሜኒያ፣ ጆርጂያ እና ሞልዶቫ የተቃወሙትን ህዝበ ውሳኔ አስጀመረ - ይህም አብዛኞቹ ተሳታፊ ዜጎች ህብረቱን እንደታደሰ ፌዴሬሽን እንዲጠብቅ ድምጽ ሰጥተዋል። እ.ኤ.አ. ነሐሴ 1991 በኮሚኒስት ፓርቲ ጠንካራ ታጋዮች መፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተደረገ። መፈንቅለ መንግስቱን በመጋፈጥ ረገድ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቦሪስ የልሲን ትልቅ ሚና በመጫወት አልተሳካም። ዋናው ውጤት የኮሚኒስት ፓርቲ እገዳ ነበር። በሩሲያ እና በዩክሬን የሚመሩት ሪፐብሊካኖች ነፃነታቸውን አወጁ። በታህሳስ 25 ቀን 1991 ጎርባቾቭ ሥልጣናቸውን ለቀቁ። ሁሉም ሪፐብሊካኖች ከሶቪየት ኅብረት መፍረስ የወጡ ነፃ የድህረ-ሶቪየት መንግሥታት ናቸው። የሩስያ ፌደሬሽን (የቀድሞው የሩስያ ኤስ.ኤፍ.አር.ኤስ.አር.ኤስ.አር.) ​​የሶቪየት ህብረትን መብቶች እና ግዴታዎች ወስዶ በአለም ጉዳዮች ውስጥ እንደ ቀጣይ ህጋዊ አካል እውቅና አግኝቷል። የሶቪየት ኅብረት ወታደራዊ ኃይልን በሚመለከት ብዙ ጉልህ የሆኑ የማህበራዊ እና የቴክኖሎጂ ስኬቶችን እና ፈጠራዎችን አፍርቷል። በዓለም ሁለተኛዋ ትልቁ ኢኮኖሚ እና በዓለም ላይ ትልቁን የጦር ሰራዊት ትኮራለች። ዩኤስኤስአር ከአምስቱ የኑክሌር ጦር መሳሪያዎች አንዱ እንደሆነ ታወቀ። የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት መስራች ቋሚ አባል እንዲሁም የ፣ የ አባል እና የጋራ ኢኮኖሚ ድጋፍ ምክር ቤት እና የዋርሶ ስምምነት መሪ አባል ነበር። የዩኤስኤስአር ከመፈረሱ በፊት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ለአራት አስርት አመታት ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመሆን እንደ ልዕለ ኃያልነት ደረጃውን ጠብቆ ቆይቷል። አንዳንድ ጊዜ "የሶቪየት ኢምፓየር" እየተባለም በምስራቅ-መካከለኛው አውሮፓ እና በአለም አቀፍ ደረጃ በወታደራዊ እና በኢኮኖሚ ጥንካሬ, በውክልና ግጭቶች እና በማደግ ላይ ባሉ ሀገሮች ተጽእኖ እና በሳይንሳዊ ምርምር የገንዘብ ድጋፍ, በተለይም በህዋ ቴክኖሎጂ እና የጦር መሳሪያዎች. ሥርወ ቃል ሶቪየት የሚለው ቃል ሶቬት (ሩሲያኛ፡ ) ከሚለው የሩስያ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም "ምክር ቤት"፣ "መሰብሰቢያ"፣ "ምክር" [ዎች] በመጨረሻ ከፕሮቶ-ስላቪክ የቃል ግንድ ("ለማሳወቅ") ከስላቪክ ("ዜና")፣ እንግሊዘኛ "ጥበበኛ"፣ በ"ማስታወቂያ-ቪስ-ኦር" (በፈረንሳይኛ ወደ እንግሊዘኛ የመጣው) ስርወ ወይም ከደች ("ማወቅ"፤ ትርጉም "ሳይንስ"). ሶቪዬትኒክ የሚለው ቃል "መማክርት" ማለት ነው። በሩሲያ ታሪክ ውስጥ አንዳንድ ድርጅቶች ምክር ቤት (ሩሲያኛ: ) ተብለው ይጠሩ ነበር. በሩስያ ኢምፓየር ከ1810 እስከ 1917 ሲሰራ የነበረው የመንግስት ምክር ቤት ከ1905 ዓ.ም አመጽ በኋላ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ተብሎ ተጠርቷል። በጆርጂያ ጉዳይ ወቅት፣ ቭላድሚር ሌኒን በጆሴፍ ስታሊን እና በደጋፊዎቹ የታላቋን የሩሲያ የጎሳ ጎሣዊነትን አገላለጽ አስቦ ነበር፣ እነዚህ ብሔር ብሔረሰቦች ሩሲያን እንዲቀላቀሉ በመጀመሪያ የሶቪየት ሪፐብሊኮች ህብረት ብሎ የሰየመውን ታላቅ ህብረት ከፊል ገለልተኛ ክፍሎች እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል። የአውሮፓ እና እስያ (ሩሲያኛ: ). ስታሊን መጀመሪያ ላይ ሃሳቡን ተቃውሟል ነገር ግን በመጨረሻ ተቀበለው። ምንም እንኳን በሌኒን ስምምነት የሶቭየት ሶሻሊስት ሪፐብሊኮች ህብረት (ዩኤስኤስአር) ስም ቢቀየርም ሁሉም ሪፐብሊካኖች በሶሻሊስት ሶቪየትነት ቢጀምሩም እስከ 1936 ድረስ ወደ ሌላኛው ስርዓት አልተቀየሩም። በበርካታ ሪፐብሊካኖች ብሔራዊ ቋንቋዎች ውስጥ ፣ ምክር ቤት ወይም ኮንሲሊያር የሚለው ቃል በቋንቋው ውስጥ በጣም ዘግይቶ ወደ ሩሲያ ሶቪዬት መላመድ ተቀይሯል እና በሌሎች ውስጥ በጭራሽ አልተለወጠም ፣ ለምሳሌ የዩክሬን ኤስኤስአር. (በላቲን ፊደላት፡ ) በሲሪሊክ ፊደላት እንደተጻፈው የዩኤስኤስአር የሩስያ ቋንቋ ኮኛቴት ምህጻረ ቃል ነው። ሶቪየቶች ይህንን ምህፃረ ቃል ደጋግመው ስለተጠቀሙ በአለም ዙሪያ ያሉ ታዳሚዎች ትርጉሙን ጠንቅቀው ያውቁ ነበር። በሩስያኛ ለሶቪየት ግዛት ሌሎች የተለመዱ አጫጭር ስሞች (ትርጓሜ፡ ሶቬትስኪ ሶዩዝ) ትርጉሙም ሶቭየት ዩኒየን እና (ትርጓሜ፡ ሶዩዝ ኤስኤስአር) የሰዋሰው ልዩነቶችን ካሣ በኋላ በመሰረቱ ወደ ኤስኤስአርኤስ ህብረት ተተርጉሟል። እንግሊዝኛ. በእንግሊዘኛ ቋንቋ ሚዲያ ግዛቱ እንደ ሶቪየት ዩኒየን ወይም ዩኤስኤስአር ይባል ነበር። በሌሎች የአውሮፓ ቋንቋዎች፣ በአገር ውስጥ የተተረጎሙት አጫጭር ቅጾች እና አህጽሮተ ቃላት አብዛኛውን ጊዜ እንደ ዩኒየን ሶቪዬቲክ እና ዩአርኤስኤስ በፈረንሳይ፣ ወይም በጀርመን እና ያገለግላሉ። በእንግሊዘኛ ተናጋሪው ዓለም፣ ሶቪየት ኅብረት መደበኛ ባልሆነ መንገድ ሩሲያ እና ዜጎቿ ሩሲያውያን ተብላ ትጠራ ነበር፣ ምንም እንኳን ሩሲያ ከዩኤስኤስ አር ሪፐብሊካኖች አንዷ ብቻ በመሆኗ ያ በቴክኒካል ስህተት ነበር። ሩሲያ ከሚለው ቃል ጋር ተመሳሳይ የሆኑ የቋንቋ አቻዎች እንደዚህ ያሉ የተሳሳቱ አተገባበር በሌሎች ቋንቋዎችም ተደጋጋሚ ነበሩ። የመሬት አቀማመጥ የሶቪየት ህብረት ከ22,402,200 ስኩዌር ኪሎ ሜትር በላይ (8,649,500 ስኩዌር ማይልስ) ስፋትን ሸፈነች እና የአለም ትልቁ ሀገር ነበረች፣ ይህ ደረጃም በተተኪዋ ሩሲያ ተይዛለች። ከምድር ገጽ ስድስተኛውን ይሸፍናል፣ እና መጠኑ ከሰሜን አሜሪካ አህጉር ጋር ሊወዳደር ይችላል። በአውሮፓ ውስጥ ያለው ምዕራባዊ ክፍል የአገሪቱን ሩብ የሚሸፍን ሲሆን የባህል እና የኢኮኖሚ ማዕከል ነበር። በእስያ ያለው ምስራቃዊ ክፍል በፓስፊክ ውቅያኖስ በምስራቅ እና በአፍጋኒስታን ወደ ደቡብ የተዘረጋ ሲሆን በመካከለኛው እስያ ከሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎች በስተቀር በሕዝብ ብዛት ያነሰ ነበር። ከ10,000 ኪሎ ሜትር በላይ (6,200 ማይል) ከምስራቅ ወደ ምዕራብ በአስራ አንድ የሰዓት ሰቆች እና ከ 7,200 ኪሎ ሜትር በላይ (4,500 ማይል) ከሰሜን ወደ ደቡብ ተዘርግቷል። አምስት የአየር ንብረት ቀጠናዎች ነበሩት፡ ታንድራ፣ ታጋ፣ ስቴፕስ፣ በረሃ እና ተራሮች። ሶቪየት ኅብረት ከሩሲያ ጋር በሚመሳሰል መልኩ ከ60,000 ኪሎ ሜትር በላይ (37,000 ማይል) ወይም 1+1⁄2 የምድር ክብ ስፋት ያለው የአለማችን ረጅሙ ድንበር ነበራት። ሁለት ሦስተኛው የባህር ዳርቻ ነበር. አገሪቷ ድንበር (ከ1945 እስከ 1991)፡ ኖርዌይ፣ ፊንላንድ፣ የባልቲክ ባህር፣ ፖላንድ፣ ቼኮዝሎቫኪያ፣ ሃንጋሪ፣ ሮማኒያ፣ ጥቁር ባህር፣ ቱርክ፣ ኢራን፣ ካስፒያን ባህር፣ አፍጋኒስታን፣ ቻይና፣ ሞንጎሊያ እና ሰሜን ኮሪያ። የቤሪንግ ስትሬት አገሪቷን ከአሜሪካ ስትነጠል፣ ላ ፔሩዝ ስትሬት ደግሞ ከጃፓን ለያት። የሶቪየት ኅብረት ከፍተኛው ተራራ ኮሙኒዝም ፒክ (አሁን ኢሞኢል ሶሞኒ ፒክ) በታጂክ ኤስኤስአር፣ በ7,495 ሜትር (24,590 ጫማ) ላይ ነበር። በተጨማሪም በዓለም ትልቁ ሐይቆች መካከል አብዛኞቹ ያካትታል; የካስፒያን ባህር (ከኢራን ጋር የተጋራ)፣ እና በሩሲያ የባይካል ሀይቅ፣ በአለም ትልቁ እና ጥልቅ ንጹህ ውሃ ሀይቅ። የአውሮፓ ታሪካዊ አገሮች የእስያ ታሪክ
22829
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%B8%E1%88%88%E1%88%9D%E1%8C%A5%E1%88%9B%E1%8C%A5
ሸለምጥማጥ
ሸለምጥማጥ ኢትዮጵያና ሌላ አገር ውስጥ የሚገኝ አጥቢ እንስሳ ነው። የእንስሳው ሳይንሳዊ ጸባይ ሸለምጥማጦች አጫጭር ቅልጥም ያላቸውና ሽንጠ ረጅም የሆኑ፣ በከፊል ዛፍ ላይ የሚኖሩ ሥጋ-በሎች ናቸው። በሙሉ ጀርባቸው በረጃጅም ተርታዎች ነጠብጣብ አላቸው። ረጅም ጅራታቸው ቀለበቶች የመሳሰሉ ጥቋቁር ክቦች አለው። ሁሉም እግሮቻቸው አምስት አምስት ጣቶች አሏቸው። ክብደታቸው ፪ ኪሎ ግራም ገደማ ነው። ዓይኖቻቸው ከፊት ለፊት ይገኛሉ። አፋቸው ጋ ረጃጅም ፀጉር አላቸው። ኮኮኔዎቻቸው የጎበጡና ስል፣ የሚወጡና የሚገቡ ናቸው። ሸለምጥማጦች ቀልጣፋና በዛፍ ላይ ሆነ በምድር ብቁ አካላዊ እንቅስቃሴ ያላቸው አዳኞች ናቸው። አንዳንዴ አድፍጠው፣ አንዳንዴ አሯሩጠው ያድናሉ። የሌሊት እንስሳት ናቸው። ደማቅ የጨረቃ ብርሃን ሲኖርም ተግባራቸውን በቅልጥፍና ያካሂዳሉ። በኢትዮጵያ፣ በኦሞ ፓርክ በተደረገ ጥናት፣ ‹‹›› ብዙ ተግባሮቻቸውን የሚያካሂዱት፣ ፀሐይ ከጠለቀች ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት መሆኑ ተረጋግጧል። ሸለምጥማጦች እጅጉን የተለያዩ ዓይነት ምግቦች ይበላሉ። አይጥ፣ የሌሊት ወፍ፣ ሜንጦዎች፣ አእዋፍ (ዶሮ የሚያህሉት ድረስ)፣ እንሽላሊት፣ እባብ፣ እንቁራሪት፣ የእግዜር-ፈረስ፣ ጢንዚዛ፣ ሸረሪት፣ አርባ እግር፣ ጊንጥ፣ የሳት ራት የመሳሰሉትን ሁሉ ይበላሉ፡፡ ፍራፍሬና የአበባ ወለላም ይበላሉ። የታወቀ የዶሮ ሌባ ነው። ሸለምጥማጦች የማሽተት ኃይላቸው እጅግ የዳበረ ነው። ሽንት፣ ዓይነ ምድር እና ከተለያዩ የአካል ክፍሎች ከሚወጡ እዦች፣ የአካባቢው ኗሪ ሸለምጥማጥ ወይንስ የእንግዳ መሆኑን መለየት ይችላሉ። በዓይነ ምድር መውጫና በቆለጥ (ወይም ሴት ከሆነች በብልቷ) መካከል ዘይትነት ያለው ብጥብጥ እዥ የሚያወጣ ዕጢ አላቸው። በዚህ እዥ ነው ወይ ከኋላቸው ዝቅ ብለው፣ አሊያም ከቆመ ነገር ጋር ተሻሽተው ምልክት የሚያደርጉበት። መለስተኛ መዓዛ ያለው ይህ እዥ፣ ሲደርቅ ቡናማ ጥቁር ይሆናል። ተደጋግሞ የተጠረገበት ግንድ ከአራት ዓመት በኋላም የሸለምጥማጥ ጠረን ይኖረዋል። ማኅበራዊ አደረጃጀታቸው፣ ግለኛ፣ ዋነኞቹ ወንዶች የአያሌ ሴቶችን መኖርያ የሚጠብቁበት፣ ማለትም አንድ ወንድ ብዙ ሴቶችን የሚቆጣጠርበት ነው። ምንም እንኳ አንዳንዴ ወንድና ሴት ከልጆቻቸው ጋር እንደ አንድ ቡድን ሊታዩ ቢችሉም፣ ሸለምጥማጦች ግለኛ ቢባሉ ትክክል ነው። ትልቁ ቡድን እናትና ቡችሎቿ ናቸው። ይኸም የሚዘልቀው፣ ቢበዛ መንፈቅ ሞልቷቸው ጡት እስኪጥሉ ነው። ሆኖም የዳበረ አካል የሚኖራቸው በሁለት ዓመታቸው ግድም ነው። ወንዶቹ እስከ አምስት ካሬ ኪሎ ሜትር በሆነ ሥፍራ የሚዘዋወሩ ሲሆኑ፣ ሴቶቹ እጅግ በጠበበ ሥፍራ የተወሰኑ ናቸው። ሆኖም ግን ተይዘው፣ ከተጠመዱበት ሥፍራ ፴፭ ኪሎ ሜትር ርቀት የተለቀቁ ሴት ሸለምጥማጦች፣ በጥቂት ቀናት ከመኖርያ ሥፍራቸው ተመልሰዋል። ወንዶቹ በክልላቸው በሚዘዋወሩበት ጊዜ፣ የርምጃቸው ፍጥነት በሰዓት ሦስት ኪሎ ሜትር ይሆናል። ሴቶቹ በዓመት ሁለት ጊዜ በአማካይ በአንድ ጊዜ ከሁለት እስከ ሦስት ግልገሎች ይወልዳሉ። የሚያረግዙት ከ፸ እስከ ፸፯ ቀናት ነው። በስሪያ ወቅት የሴቷን ብልት ወይም ሽንት ወይም እዥ ያሸተተ ወንድ፣ ሽቅብ ያንጋጥጣል። የደራች መሆኑን ይገነዘባል። ከዚያ እያጉረመረመና የጉንፋን የመሰለ ድምፅ እያሰማ ይከተላታል። በመጀመርያ ታፋና ጭራዋን ዝቅ አድርጋ ትሸሸዋለች። በኋላ ግን እንዲጠጋት ትፈቅዳለች። ፊታቸውንና ብልቶቻቸውን ተሸታትተው፣ ጉንጮቻቸውን ይተሻሻሉ። ሴቷ ጭራዋን ከፍ አድርጋና ወደ ጎን ብላ፣ ከታፋዋ ከፍ ብላ ትጋብዘዋለች። ደረትና ሆዱ ከታፋዋ ላይ አርፎ፣ በእጆቹ ከላይ በኩል ጭኖቿን ይዞ፣ ግንኙነቱን ይፈጽማል። አንዳንዴ አምስት ደቂቃ በሚፈጀው ስሪያ በመጨረሻዎቹ ሰኮንዶች፣ የአንገቷን ፀጉር ይነክሳል። ከዚያ ሴቷ በቂጧ ትንፏቀቅና በጀርባዋ ትንከባለላለች። በመጨረሻ ሁለቱም የየራሳቸውን ብልቶች ይልሳሉ። ሸለምጥማጦች የሚወልዱት በጉድጓድ ውስጥ ወይም ከቅጠሎች በተሠራ ጎጆ ነው። እናቲቱ እየላሰቻቸውና ዓይነምድራቸውን እየበላች፣ ከግልገሎቿ ጋር ብዙ ቀናት ትቆያለች። ከቦታ ቦታ ስታዘዋውራቸው የጀርባቸውን ቆዳ ነክሳ አንጠልጥላ ነው። የግልገሎቹ ፀጉር ግራጫና ምልክቶቹ የማይለይ ነው። ዓይንና ጆሯቸው የሚከፈተው ወደ አሥረኛው ቀን ገደማ ነው። ከወተት ሌላ መመገብ የሚጀምሩት ከስድስት ሳምንቶች በኋላ የመንጋጋ ጥርሳቸው ሲወጣ ነው። አዳኝነቱን የሚማሩት ቀስ በቀስና ደረጃ በደረጃ ነው። ለማደን ጥረት የሚያደርጉት አሥራ-አንድ ሳምንት ገደማ ከሞላቸው በኋላ ነው። አደን ማደን ከጀመሩ በኋላ በእዥ ምልክት ማድረግም ይጀምራሉ። ሸለምጥማጦች ሲጣሉ፣ ንክሻቸው የሚያነጣጥረው ራስ፣ አንገትና ደረት ላይ ነው። ባይቋሰሉም ፀጉር ይነጫጫሉ። ከዚያም ተሸናፊው ይጮሃል፣ ይሸናል፣ ቂጡ ጋ ካለው ከረጢት ውስጥ ያለውን ግም ፈሳሽ ይለቃል። በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር እና ብዛቱ የተለያዩ ብቸኛ ዝርያዎች፣ የተለያዩ ሥነ ምህዳራዊ ሁኔታዎች ስለሚፈቅዱ፣ ተለያይተው ይኖራሉ። በደን ውስጥ የሚገኙ የሸለምጥማጥ ብቸኛ ዝርያዎች ቢኖሩም፣ ‹‹,›› የተባሉት የሚገኙት ዛፍ በሌለባቸው ገላጣ ሥፍራዎች ነው። ‹‹›› ሰው በሚኖርባቸው አካባቢዎች ይኖራል። በኢትዮጵያ የተለያዩ የሸለምጥማጥ ብቸኛ ዝርያዎች ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ሽለምጥማጦች፣ በዝርዝር የተጠኑት ሁለቱ ብቻ ናቸው። ጀኒታ ቲግሪና () እና ጀኒታ ጀኒታ ()። የሸለምጥማጦች ምንጭ የኮንጎ የዝናብ ደን ነው ቢባልም፣ ከሰሃራ በረሃ በስተቀር በአፍሪካ የሌሉበት ሥፍራ የለም። ከዚህም አልፈው በደቡባዊ ምዕራብ አውሮፓና በዐረብ ባሕር ሰርጥም ይገኛሉ። መደበቂያና ምግብ በሚያገኙባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ይገኛሉ። ገና በቂ ጥናት የተደረገባቸው ባይሆኑም፣ የተለያዩት ብቸኛ ዝርያዎች በመልክና በምግባር የተመሳሰሉ መሆናቸው ግልጽ ነው። ‹‹›› እና ‹‹›› ከሌሎቹ ሁሉ ሰፊ ስርጭት ያላቸው ከመሆናቸው በላይ ያሉበት ቦታ ተደራራቢ ነው። በአንድ ሥፍራ እየኖሩም ግን አንዱ ዓይነት ከሌላው የማይዋለዱ ናቸውና የተለያዩ ብቸኛ ዝርያዎች ለመሆናቸው የሚያጠራጥር ነገር የለም። ዋቢ ምንጭ ሪፖርተር (የካቲት ፫ ቀን ፳፻፭ ዓ/ም)፤ “ሸለምጥማጥ ‹‹)”፤ በሰሎሞን ይርጋ (ዶር.) ‹‹አጥቢዎች›› የኢትዮጵያ አጥቢ እንስሳት የዱር አራዊት
17440
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%83%E1%88%AA%20%E1%8D%96%E1%89%B0%E1%88%AD%20%E1%8A%AD%E1%8D%8D%E1%88%8D%20%E1%88%B5%E1%8B%B5%E1%88%B5%E1%89%B5%20%28%E1%8D%8A%E1%88%8D%E1%88%9D%29
ሃሪ ፖተር ክፍል ስድስት (ፊልም)
ሃሪ ፖተር ክፍል ስድስት (; ጥሬ ትርጉሙ: ሃሪ ፖተርና የግማሽ ደም ልዑሉ) እኤአ ፳፻፱ ዓም ለዕይታ የበቃ የብሪቲሽ ፊልም ነው። ፊልሙ በሃሪ ፖተር ተከታታይ ፊልሞች ውስጥ ስድስተኛው ክፍል ሲሆን በዴቪድ የትስ ዳይሬክት ተደርጎ በስቲቭ ክሎቭስ ተፅፎ እንዲሁም በዋርነር ብሮስ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው። ሃሪ ፖተር የአሜሪካ ፊልሞች ይህ ፊልም "" በተሰኘው በፀሀፊ ጄ.ኬ ሮውሊንግ የተፃፈውና እ.ኤ.አ በ፳፻፭ ዓም ለህትመት በበቃው መፅሀፍ ተመስርቶ የተሰራ ሲሆን ፊልሙ የሚተርከውም ሃሪ ፖተር ስድስተኛ የትምህርት አመቱን በሆግዋርትስ የአስማተኛ ትምህርት ቤት የሚያሳልፈውን ጊዜንና የሎርድ ቮልድሞርትን የመርቻ ቁልፍ ስራ የሚሰራበትን ኩነት ነው። እ.ኤ.አ በ፲፭ ጁላይ ፳፻፱ ዓም ሲኒማ ቤትን የረገጠው ይህ ፊልም በተመልካቾችና በሐያስያን ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝቷል። የዚህ ተከታይ ፊልም ሃሪ ፖተር ክፍል ሰባት በኖቬምበር ፳፻፲ ዓም ለዕይታ በቅቷል። ሎርድ ቮልድሞርት በተራው አለም()ና በአስማተኛው አለም የሽብር እጆቹን አሁንም እየዘረጋ ነው። ፕሮፌሰር ዳምብልዶ ሃሪን ከፕሮፌሰር ስለጎርን አስተዋውቆት እንዲቀርበው ያዘዋል። በዚህም ጊዜ ዳምብልዶ ግራ እጁ እንደገረጣና እንደጠቆረ ሃሪ ያስተውላል። ምን እነደሆነ ሃሪ ቢጠይቀውም ዳምብልዶ ሊመልስለት አልፈለገም። ከጥቂት ጊዜ በኋላም ሃሪ ድራኮ ማልፎይን ከእናቱ ጋር ወደ አንድ የእንጨት መደብር ሲያመራ ይመለከተዋል። እሱም ማልፎይ የአባቱ የሉሲየስ ማልፎይ መታሰርን ተከትሎ የሎርድ ቮልድሞርት ተከታይ ወይም ዴዝ ኢተር() እንደሆነ ጠረጠረ። ይህ ሀሳብ ቅዠት ነው ብለው ጓደኞቹ ሄርመኒና ሮን ቢነግሩትም ሊሰማቸው አልፈለገም። በድብቅም እሱን መከታተልም ጀመረ። በሆግዋርትስም ፕሮፌሰር ስለጎርን አስተማሪያቸው እንደሚሆን በዳምብልዶ ተበሰረ። ሃሪም በፕሮፌሰር ስለጎርን ትምህርቶች ላይ በግማሽ ደም ልዑሉ() መፅሐፍ አጋዥነት ጥሩ ተሳትፎ እያሳየ የፕሮፌሰሩን ቀልብ ሳበ። ይህን የተመለከተችው ጓደኛው ሄርሞኒም የባለመፅሐፉን ማንነት እንዲያጣራ ደጋግማ ለመነችው እሱ ግን አሻፈረኝ ብሎ ይበልጥኑ ከመፅሐፉ ጋር ያለውን ቁርኝት አጠበቀው። አንድ ጊዜ ዳምብልዶ ሃሪን ቢሮው ጠርቶ ያለፉትን ትዝታዎችን እንደ መስታወት በሚያሳየው ፔንሲቭ() በሚባለው አስማተኛ እቃ በመጠቀም ከሎርድ ቮልድሞርት ወይም በዛን ጊዜ ቶም ሪድል ተብሎ የሚጠራበትና እሱን ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቀበት ወቅት አሳየው። ዳምብልዶም አክሎ ቶም በሆግዋርትስ ተማሪ ሳለ ከፕሮፌሰር ስለጎርን ጋር የጠበቀ ዝምድና እንዳላውና ለሱ ምስጢር እንደሚያካፍለው ገለፀለት። በመቀጠልም በአንድ ሰሞን ለእሱ የነገረውን ምስጢር የያዘ ትዝታ() እንዲቀበለው አዘዘው ለዚህም ቀድሞ እንዳስተዋወቀውና እንዲቀርበው እንደጠየቀው ነገረው። ሃሪም ይህን ተከትሎ ብዙ ጊዜ ሊያወጣጣው ሞከረ ግን አልቻለም። የማልፎይ ነገር አሁንም አልዋጥለት ያለው ሃሪ ክትትሉን አላቆመም። በአንድ ወቅትም ለዳምብልዶ በተላከ እቃ ውስጥ የሚገል አስማተኛ ቃል() ተያዘ። ሃሪም ቀጥታ ማልፎይን ጠረጠረ። በማልፎይና በፕሮፌሰር ስኔፕ ድብቅ ንግግርም ማልፎይ ዳምብልዶን እንዲገል በቮልድሞርት እንደተላከ ሰማ። ስኔፕም እሱን ሊረዳው ለእናቱ ቃል እንደገባ ነገረው። ይህንንም ለኦርደር ኦፍ ፎኒክስ() አባል ለሆኑት ለሉፒንና ለሮን አባት አርተር ገለፀላቸው እነሱም ስኔፕ የኦርደር ኦፍ ፎኒክሱ አባል እንደሆነና ዳምብልዶም እንደሚያምነውም ነገሩት። በነገሩ ግራ የተጋባው ሃሪ አይኑን ከሁለቱ ማለትም ስኔፕና ማልፎይ ሊነቅል አልፈለገም። ከጥቂት ጊዜ ቆይታ በኋላም እውነቱን ለማወጣጣት ማልፎይን ተጋፈጠው። ማልፎይም በንዴት ሃሪ ላይ ጥቃት ማድረስ ሞከር። ሃሪ ከግማሽ ደም ልዑሉ የተማረውን አስማተኛ ቃል() ተጠቀመበት። ይህም አደገኛ ጉዳት ማልፎይ ላይ አደረሰ ስኔፕም በቦታው ተገኝቶ ማልፎይን ከአደጋው አተረፈው በዚህ የተደናገጠው ሃሪ መፅሐፉ መጥፎ ነገር እንዳስተማረው ተረድቶ ከጂኒ ጋር እቃዎች በሚደበቅበት ክፍል ውስጥ ደበቁት። በዛውም ጂኒ ለእሱ ያላትን ፍቅር ገለፀችለት። ከብዙ ካልተሳኩ ሙከራዎች በኋላ ሃሪ በስለጎርን ትምህረቶች ጥሩ አቋም በነበረበት ጊዜ ላይ የተሸለመውን ጥሩ እድል አምጪ ፈሳሽ() በመጠቀም ከስለጎርን ቮልድሞርት የነገረውን ትዝታ ሰጠው። ዳምብልዶና ሃሪም ተመለከቱት። ከሱም ቮልድሞርት ሆክሮክስ() የተባለ አስማት የተጠቀመ እንደሆነና ነፍሱንም ሰባት ቦታ ከፍሎት በተለያዩ እቃዎች እንዳስቀመጠው ተረዱ። ዳምብልዱ የጠረጠረው ልክ እንደነበርና የመጀመሪያው ነፍሱ ያየዘው እቃ የእሱ ዲያሪ እንደነበርና ሃሪም ከአራት አመት በፊት እንዳጠፋው ሁለተኛው ደግሞ የእናቱ ቀለበት ሲሆን እሱን ለማጥፋት ሲል ግራ እጁ እንደጠቆረና እንደገረጣ ነገረው። በመጨመርም ሶስተኛውን እንዳገኘና አብረው ማጥፋት እንደሚሻ ገለፀለት። ሃሪም ተስማማ። ሃሪና ዳምብልዶ የቮልድሞርት ሶስተኛ ነፍስ የተቀመጠበትን እቃ ለመፈለግ ወደ አንድ ዋሻ ያመራሉ በዚያም ዳምብልዶ አድካሚ ፈሳሽ የመጠጣት ክፍያ አስከፍሎት ሶስተኛውን ወይም የአንገት ሃብሉን አገኙት። ሀብሉን አግኝተውት እንደተመለሱም ዳምብልዶ በመድከሙ ስኔፕን እንዲጠራለት ሃሪን አዘዘው። ሃሪም ስኔፕን ለመጥራት ልክ ሲሄድ ማልፎይ ዳምብልዶን ሊገለው መጣ። ዳምብልዶም ማልፎይ ገዳይ እንዳልሆነና ሊገለው እንደሚፈልግ ከብዙ ጊዜ በፊት ያውቅ እንደ ነበር በእርጋታ ነገረው። ማልፎይን ተከትሎም ለሌሎች የቮልድሞርት ተከታዮች በቦታው ተገኙ። ዳምብልዶም ትምህርት ቤቱ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገለት እንዴት ተከታዮቹ ወደ ውስጥ እንደዘለቁ ጠየቀው እሱም አንድ እንጨት መደብር ውስጥ ያለ ቁም ሳጥን ትምህርት ቤቱ ውስጥ ሌላ መንታ ቁምሳጥን እንዳለውና ሰውን አንዱ ቁምሳጥን ካለበት ቦታ ወደሌላኛው ቁምሳጥን እንደሚያዘዋውር ነገረው። ዳምብልዶም ደጋግሞ እንዳይገለው ቢጠይቀውም ማልፎይ እንደፈራና ካልገደለው ቮልድሞርት እንደሚገለው እንባ እየተናነቀው ነገረው። ይህንን ሁኔታ በድብቅ የሚከታተለው ሃሪ ስኔፕ ከቦታው እንዳይነቃነቅ ምልክት ሰጠው። ስኔፕም በቦታው በማምራት የዳምብልዶን አይን እየተመለከተ ዳምብልዶን ገድሎት ከቦታው ሸሸ። ይህንን አይቶ የደረቀው ሃሪ ስኔፕን በሩጫ ተከተለው። ሊጎዳውም ስለፈለገ ከመፅሐፉ የወሰደውን ቃል ተጠቀመበት። ስኔፕም በቀላሉ ጥቃቱን ተከላከለ ቀርቦም ይህንን አስማተኛ ቃል እራሱ እንደፈጠረና የመፅሀፉ ባለቤት(ባለግማሽ ደም ልዑል) እሱ እንደሆነ ነገረው። በመጨረሻም ሃሪ ዳምብልዶ ሲገደል እያየ ምንም አለማድረጉ እንደቆጨውና እሱ የጀመረውን ስራ ማለትም ነፍሶቹን እንደሚፈልግ ለጓደኞቹ ነገራቸው እነሱም እንደሚረዱት ቃል ገቡ። ተዋንያንና ገፀባህሪያት ዳንኤል ራድክሊፍ እንደ ሃሪ ፖተር ሃሪ ፖተር ገና ልጅ ሳለ ጨካኑ አስማተኛ ቮልድሞርት እናትና አባቱን የገደለበትና በእሱም ላይ የግድያ ሙከራ ያመለጠ ሲሆን በዚህም ሰበብ ቮልድሞርትና ሃሪ ቀንደኛ ጠላት ናቸው። በዚህ ክፍል ውስጥ ባለ፲፭ቱ ታዳጊ ሃሪ ቮልድሞርትን ለመርታት ከዳምብልዶ ጋር ሆኖ ሲፋለም እናየዋለን። ዳንኤል ራድክሊፍም ከመጀመሪያው ክፍል ጀምሮ ሃሪን ሆኖ የተወነው አሁንም ለሰባተኛው ክፍል አንደሚተውነው ፈርሟል። ኤማ ዋትሰን እንደ ሄርሞኒ ግሬንጀር የሃሪ ፖተር ጓደኛና የበሰለ አስተሳሰብ ያላት ልጅ ናት። በዚህ ፊልም ላይም ከጓደኛዋ ሮን ጋር ፍቅር እንደያዛት እንመለከታለን። ሩፔርት ግሪንት እንደ ሮን ዊዝሊ የሃሪና የሄርሞኒ ጓደኛ። ሮን የአስማተኞች ጨዋታ ላይ ተካፋይ ሆኖ ድል ተቀዳጅቷል። ሚካኤል ጋምበን እንደ ፕሮፌሰር ዳምብልዶ በአስማተኛው አለም ውስጥ በጣም ብልጥና ብልህ አስማተኛ ነው። ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ቮልድሞርትን ሲዋጋ እንደነበርና እሱን ለመዋጋትም ኦርደር ኦፍ ፊኒክስ የተባለ ቡድን አቋቁሟል። በዚህ ክፍልም በባልደረባው በስኔፕ ተክዶ ሞቷል። አላን ሪክማን እንደ ፕሮፌሰር ስኔፕ የሆግዋርትስ ትምህርት ቤት መምህርና በፊት ቮልድሞርት ተከታይ። ሃሪ አሁንም ቢሆን ለቮልድሞርት እንደሚሰራ ቢጠረጥርም ጥርጣሬው በጓደኞቹ ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም። በመጨረሻም ስኔፕ ዳምብልዶን ገድሎት ጥርጣሬው ልክ እንደነበር እንመለከታለን። ቶም ፌልተን እንደ ድሬኮ ማልፎይ ማልፎይ ከድሮ ጀምሮ ከሃሪ ጋር አይስማሙም ነበር። አሁንም ጠላትነታቸው ጣሪያ ነክቷል። በቮልድሞርት ዳምብልዶን እንዲገል ቢታዘዝም ሊያሳካ አልቻለም። ጂም ብሮድቤንት እንደ ፕሮፌሰር ስለጎርን የሆግዋርት ትምህርት ቤት መምህርና በአንድ ጊዜ የቮልድሞርት መምህር። ሃሪ ከስለጎርን ቮልድሞርት የነገረውን ምስጢር ለማወቅ ይሞክራል። ከብዙ ሙከራ በኋላም ተሳክቶለታል። ራልፍ ፊንስ እንደ ሎርድ ቮልድሞርት ስሙ በፊልሙ ቢጠቀስም በአካል አልታየም። ቮልድሞርት ከመቼውም በላይ ሀይሉ እየጨመረ መጥቷል። ሃሪም እሱን መውጊያ ምስጢር አውቋል። ሃሪ ፖተር (ተከታታይ ፊልሞች)
1569
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%8D%E1%8A%AD%E1%8D%94%E1%8B%B2%E1%8B%AB
ውክፔዲያ
ውኪፒዲያ የባለ ብዙ ቋንቋ የተሟላ ትክክለኛና ነጻ መዝገበ ዕውቀት (ኢንሳይክሎፒዲያ) ነው። ማንኛውም ሰው ለውኪፒዲያ መጻፍ ይችላል። ውኪፒዲያ፣ ውኪሚዲያ የተባለ ግብረ ሠናይ ድርጅት ከሚያካሂዳቸው ፕሮግራሞች አንዱ ነው። ወደ 272 በሚጠጉ የተለያዩ ቋንቋዎች ፅሁፎች አሉት። ውኪፒዲያ በኢንተርኔት ከሚገኙ ታዋቂ መዛግብተ ዕውቀት አንዱ ነው። ውኪፒዲያ ድረ-ገፅን መሰረት ያደረገና ማንም ሰው በቀላሉ እንዲያስተካክለው ተደረጎ የተዘጋጀ፣ በብዙ ቋንቋዎች የሚቀርብ ነጻ የኢንተርኔት መዝገበ እውቀት ወይም ኢንሳይክሎፒድያ ነው። ውኪፒዲያ የሚለውን ስያሜ ያገኘው “ዊኪ” (ትርጉሙ ፈጣን ማለት ነው) የሚለውን ቃል ከሀዋይኛ ቋንቋ በመወሰድና “ኢንሳይክሎፒድያ” ከሚልው የእንግሊዘኛ ቃል ጋር በማዳቀል ሲሆን እያንዳንዱ የውኪፒዲያ ገጽ እራሱ ከሚይዘው መረጃ በተጨማሪ አንባቢን ይበልጥ ግነዛቤ ለማስጨበጥ ከሚረዱ ሌሎች ተዣማጅ ገፆች ጋር ያለውን የትስስር መረጃም በተጨማሪነት አካቶ የያዘ ነው። ውኪፒዲያ የተመዘገበ (የሚታወቅ) አድራሻ ሳይኖራቸው ኢንተርኔት ላይ ያለምንም ክፍያ በፈቃደኝነት የሚጽፉ የበርካታ ግለሰቦች የጋራ የትብብር ውጤት ነው። ስለሆነም ከአንዳንድ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ገደብ ከተጣለባቸው ገጾች በስተቀር ማንኛውም የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚና ፈቃደኛ የሆነ ሰው፤ በብዕር ስም፣ ትክለኛ ስምን በመጠቀም ወይም ደግሞ ያለምንም ስምና አድራሻ፣ ውኪፒዲያ ላይ የፈለገውን ሀሳብ የማስፈርና አስተዋጾ የማድረግ አሊያም ቀድሞ በሰፈረ ጽሁፍ ላይ ተጨማሪ መረጃን የማካታት፣ ስህተትን የማረምና የማስተካከል ፈቃድ ተሰጥቶታል። ውኪፒዲያ ከተመሰረተበት ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በፍጥነት በማደግ ላይ ያለና በብዛት ከሚጎበኙና ኢንተርኔት ላይ ከሚገኙ በረካታ የማጣቀሻ ድረ-ገጾች መካከል አንዱ ሲሆን 2011 እ.ኤ.አ. መጋቢት ወር ብቻ ከ400 ሚሊዎን በላይ አዳዲስ ጎብኝዎች ድረገጹን እንደጎበኙት ኮም ስኮር ያካሄደው የጥናተ ዘገባ ያመለክታል። ውኪፒዲያ ከ82,000 በላይ አርታኢዎች፣ ከ270 በላይ በሚሆኑ ቋንቋዎች ያጠናቀሯቸውን ከ19,000,000 በላይ የሚሆኑ መጣጥፎችን አካቶ የያዘ ድረ-ገጽ ነው። ውኪፒዲያ በአሁኑ ጊዜ 3,874,529 የእንግሊዘኛ መጣጥፎችን የያዘ ሲሆን በየቀኑ ከመቶ ሺህ በላይ ጎብኝዎች እንደሚጎበኙትም ይገመታል። በተጨማሪም በተለያዬ የአለም ክፍል የሚኖሩ ግለሰቦች በሚያደርጉት የጋራ አስተዋጽኦ በየቀኑ ከአስር ሺህ በላይ መጣጥፎች የተለያዩ ማስተካከያዎች የሚደረግባቸው ሲሆን ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ መጣጥፎች ደግሞ ውኪፒዲያን በየቀኑ ይቀላቀላሉ። ምንም እንኳን መሰረታዊ የውኪፒዲያ መርሆች የሚባሉት አምስት ቢሆኑም ይህንኑ መዝገበ-ዕውቀት (ኢንሳይክሎፒዲያ) ይበልጥ ለማሻሻልና ለማጎልበት የሚያግዙ ሌሎች በርካታ ፖሊሲዎችና መመሪያዎች በውኪፒዲያ ማህበረሰብ ተቀርጸው ተግባር ላይ የዋሉ ሲሆን ነገር ግን እነዚህን መሰረታዊ መመሪያዎችና ደንቦች አስተዋጾ ማድረግ ካልጀመረ በስተቀር ማንኛውም ሰው የማወቅ ግደታ የለበትም። በሌላ በኩል፣ ውኪፒዲያ አንድ ሰው ካለው የሙያ ችሎታ ይልቅ ለሚያበረክተው አስተዋፆ ትልቅ ግምት የሚሰጥ በመሆኑ፣ በተለያየ የእድሜ ክልል፣ ባህልና መነሻ (ዳራ) የሚገኝ ማንኛውም ሰው የውኪፒዲያ አስገዳጅ ፖሊሲዎችን አሟልቶ እስከተገኘ ድረስ፣ ውኪፒዲያ ላይ የፈለገውን መጣጥፍ እንዳንድስ የመጨመር አሊያም ማንኛውም ውኪፒዲያ ላይ የሚገኝ ሌላ ጽሑፍ፣ ማጣቀሻና ምስል የማየት የማሻሻልና የማረም አንዳደም ሙሉ ለሙሉ የመለዎጥና ፈቃድ አለው። በመሆኑም ውኪፒዲያ በተለያዩ አስተዋጾ አድራጎዎች በየጊዜው ማሻሻያ የሚደረግበት እንደመሆኑ መጠን፣ አዲስ ከሚካተቱት መጣጥፎች ይልቅ ቀደም ሲል በድረ ገጹ የተካተቱ መጣጥፎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየታረሙና እየተሻሻሉ የሚሄዱ በመሆናቸው የተሻለ የሐሳብ ጥራት፣ የመረጃ ሚዛናዊነትና ምሉእነት እንደሚኖራቸው ይታመናል። የውክፔዲያ አመሰራረት ዊክፔዲያ ነፃ ኦንላይን መዝገበ-ዕውቀትን () ለመፍጠር አላማ አድርጎ የተመሰረተና ቀደም ሲል ኑፔዲያ () በመባል የሚታወቅ ፕሮጀክት ውጤት ነው። ኑፔዲያ ምንም እንኳን የተሻሻለ የዕርስ-በርዕስ መገማገሚያ () መንገዶችን አካቶ የያዘና ሙያዊ ብቃት ያላቸው መጣጥፍ አቅራቢዎችን የሚጠይቅ ፕሮጀክት የነበረ ቢሆንም መጣጥፎችን አትሞ ለማውጣት ረጅም ጊዜን ይጠይቅ ነበር። በመሆኑም ይንንም ችግር ለመቅረፍ፣ በ2000 እ.ኤ.አ. የኑፔዲያ መስራቹ ጂሚ ዌልስና በዚሁ ፕሮጀክት ተቀጥሮ ይሰራ የነበረ ላሪ ሳንገር የተባለ ሌላ ግለሰብ ኑፔዲያን እንደት ማሻሻልና ሌሎች ተጨማሪ ገፅታዎችን አካቶ የሚይዝ ፕሮጀከት ማደረግ እንሚቻል የጋራ ውይይት አደረጉ። በውይይታቸውም ወቅት እንደ ግብአት የተጠቀሟቸው አብዛሐኛዎቹ ምንጮች አንድ የዊኪ ድረ-ገጽ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የየራሳቸውን አስተዋፆ ማበረከት የሚችሉበት መዳረሻ ተደርጎ ድዛይን ሊደረግ እንደሚችል አመላከቱዋቸው። በዚህም መሰረት ማንኛውም ሰው የራሱን አድስ አስተዋፆ ማበርከትና ብሎም ሌሎች የቀረቡ መረጃዎችን ማስተካክልና ማረም እንዲያስችል ተደርጎ ዲዛይን የተተደረገው የመጀመሪያው የኑፔዲያ የዊኪ ገፅ እ.ኤ.አ ጥር 10 ቀን 2001 ዓ.ም. አየር ላይ ዋለ። ነገር ግን ሌሎች የኑፔዲያ ፕሮጀክት አካል የነበሩ አርታኢዎችና ሀያሲዎች በኑፔዲያ ፕሮጀክት ላይ የተደረገውን የማሻሻያ ለውጥ በተለየም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የየራሳቸውን አስተዋሶ ማበርከት የሚያስችልን ድረ ገፅ(ዊኪ) ቅርፅ እዲይዝ ተደርጎ መሻሻሉን በመቃዎማቸው፣ የተሻሻለው የኑፔዲያ ፕሮጀክት አድስ የስያሜ ለውጥ በማድረግና “ዊክፔዲያ” በመባል በራሱ አድራሻ () አንዳንዶች ዛሬ “የዊክፔዲያ ቀን” እያሉ በሚጠሩት ጥር 15 ቀን በይፋ ስራውን ጀመረ። ለውክፔዲያ ሳንዲዬጎ የሚገኘውንና የመጀመሪያው የድረ-ገፁ መቀመጫ በመሆን ያገለገለውን ሰርቨር ኮምፒውተርና የመረጃ ማስተላለፊያ መስመሩን () በርዳታ የለገሰው ጂሚ ዌልስ ነበር። በተጨማሪም በራሱ በጂሚ ዌልስ እና በሌሎች ሁለት ጓደኞቹ የተቋቋመውና በአነስተኛ የኢንተርኔት የማስታዎቂያ ስራዎች ላይ የተሰማራ ቦሚስ () የሚባል ድርጅት ሰራተኞች የነበሩና ባሁኑ ጊዜም እየሰሩ የሚገኙ ሌሎች ግለሰቦችም የራሳቸውን አስተዋፆ ለዊክፔዲያ አበርክተዋል። በዚህ ረገድ ከሚጠቀሱት፣ የቦሚስ ተባባሪ መስራችና በአሁኑ ጊዜ የድርጂቱ ዋና ስራ አስኪያጅ በመሆን እያገለገለ የሚገኘው ቲም ሸልና ፕሮገራመሩ ጃሰን ሪቺ ይጠቀሳሉ። በሌላ በኩል ዊክፔዲያ አሁን ወደ ሚታወቅበት የአድራሻ ለውጥ ያደረገው ለትርፍ የማይንቀሳቀሰውና የራሱ የዊክፔዲያ እህት ኩባኒያ የሆነው “ዊክፔዲያ ፋውንደሽን” ከተቋቋመ በሗላ ነበር። ውክፔዲያ ምንም እንኳ መጀመሪያ የተመሰረተው እንግሊዘኛ ቋንቋን መሰረት አድርጎ ቢሆንም እ.ኤ.አ ከግንቦት 2001 ዓ.ም. ጀምሮ ሌሎች አዳድስ ቋንቋዎችን በማካተት የበርካታ ቋንቋዎች መዳረሻ ለመሆን ችሏል። ከነዚህም መካከል ካታልኛ፣ ቻይንኛ፣ ጀርመንኛ፣ ሞስኮብኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ ዕብራይስጥ፣ ጣሊያንኛ፣ ጃፓንኛ፣ ፖርቹጋልኛና ስፓንሽኛ በግንባር ቀደምትነት ዊክፔድያን የተቀላቀሉ ቋንቋዎች ሲሆኑ፣ አረብኛ፣ ሀንጋሪኛ፣ ፖሎንኛና ሆላንድኛ ከላይ የተጠቀሱትን ቋንቋዎች በቅርብ እርቀት ተከትለው የተቀላቀሉ ሌሎች ቋንቋዎች ናቸው። በሌላ በኩል በጥር 2012 እ.ኤ.አ. በተደረገ ጥናት ዊክፔድያ ከ31 ሚሊዎን በላይ በሚሆኑ የተመዘገቡ የዊኪፒዲያ አስተዋፆ አድራጎዎችና በመላው አለም በሚገኙ ሌሎች ስፍር ቁጥር የሌላቸው ያልተመዘገቡ (የማይታወቁ) አስተዋፆ አድራጎዎች በ283 ቋንቋዎች ከ20 ሚሊዎን በላይ የሚሆኑና ማንምሰው በነፃ ሊገልባቸው የሚችሉ መጣጥፎችን አካቶ መያዙ ተረጋግጧል። በተጨማሪም ከጠቅላላው የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ውስጥ 14.5% ዊክፔዲያን እንደሚጎበኙ ተረጋግጧል። የንግድ ምልክትና የኮፒራይት ህግ ውክፔድያ ንብረትነቱ ዊክሜዲያ ፋውንደሽን የሚባል ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት የተመዘገበ ህጋዊ የንግድ ምልክት ነው። የውክፔዲያ አስተዋፆ አድራጊዎች ማንኛውም የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚና ፈቃደኛ የሆነ ሰው ከአንዳንድ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ገደብ ከተጣለባቸው ገጾች በስተቀር ውክፔዲያ ላይ ስለተለያዩ ጉዳዮች (በህዎት ያሉ ሰዎችን ስም የሚያጠፉና ሌሎች የተከለከሉ ይዘት ያላቸውን ጽሁፎች ሳይጨምር) የፈለገውን ጽሁፍ የማስፈር አሊያም ስህተት የሆነን ጽሑፍ የማረምና የማስተካከል ፈቃድ ተሰጥቶታል። ይህም ያልተገደበ ፈቃድ ዊክፔዲያ በርካታ መጣጥፎችን እንዲኖሩት ያስቻለው ሲሆን፣ ከቀላል የድረ-ገጹ ተጠቃሚዎች (አንባቢዎች) ጨምሮ እስከ 91000 የሚደርሱ የተለያዩ የሙያ ባለቤት የሆኑ ግለሰቦችና በቋሚነት ዊክፔዲያን አርትኦት የሚያደርጉ ፈቃደኛ አስተዋፆ አድራጊዎችን አሉት። በመሆኑም ምንም እንኳን የድረገፁ ባለቤት ዊክፔዲያ ፋውንደሽን ቢሆንም ብዙውን ጊዜ በድረ-ገፁ ላይ በሚዎጡ የፅሁውፍ ስራዎችና የድረ-ገፁን የቀን ተቀን እንቅስቃሴዎችን በመቆጣጠሩ ረገድ የላቀ ተሳትፎ አይታይበትም። በተጨማሪም ይህንንም የበለጠ ለማጎልበት ይረዳ ዘንድ፣ የተለያዩ የዊክፔዲያ ተጠቃሚዎችና አባሎች ግለሰባዊ ማንነታቸው/ሙያቸው/ እንደተጠበቀ ሆኖ የተሻሻለና ጥራት ያላቸው ስራ ማበርከት ይችሉ ዘንድ የተለያዩ መፍትሔዎች ተነድፈው ተግባራዊ ሆነዋል። ከነዚህም መካከል አርታኢዎች የተላያዩ ገፆችን ማስተካከልና መፍጠር የሚችሉ ሲሆን ፕሮገራመሮች ደግሞ የአርትኦት ችግር ያለባቸውን ገፆች በቀላሉ ለመከታተል የሚያስችሉ ፐፕሮገራሞችን በየጊዜው ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም በመረጃዎች አቀራረብ ዙሪያ አንዳንድ አለመግባባቶች በአርታኢዎች መካከል ሲፈጠሩ፣ አርታኢዎች በጋራ በመሰባስብና በመወያየት ተጨባጭና የተሻለ የነገሩን/ሀሳቡን እውነታ ይወክላል የሚሉትን በመርጥ እንዲያፀድቁ የሚደረግበት አሰራርም አለ። የአስተዋፆ ማስታወሻዎች በተለያዩ የዊክፔዲያ ገፆች ላይ የሚገኙ ጽሑፎች የበርካታ አስተዋፆ አድራጊ ሰዎች የጋራ የትብብር ውጤቶች ናቸው። በመሆኑም ማንኛውም ለውክፔዲያ ገፅ አስተዋፆ ያደረገ ግለሰብ ፣ ገፁን በመፍጠር ሂደት ውስጥ አስተዋፆ ያበረከቱ ግለሰቦች በሚመዘገቡበት የገፁ ታሪክ መዝገብ ውስጥ የሚካተትና ያደረገው አስተዋፆም የሚመዘገብ ሲሆን ይህም ለማንኛውም ሰው በግልፅ እንዲታይ ተደርጎ ከገፁ ጋር ተያያዥ ሆኖ የሚቀርብ ነው። ምስሎችንና ሌሎች ሜዲያዎችን በተመለከተ የተመዘገበን የአስተዋፆ አድራጊነት፣ የባለቤትነት ድርሻን ወይም ደግሞ ሌሎች የመረጃ ምንጮችን በተመለከተ መረጃን ለማዎቅ ካስፈለገ፣ የተፈለገው ምስል ላይ በኮምፒውተራችን ማውስ ጠቅ በማድረግ ወይም ደግሞ በአቅራቢያው የሚገኝን የመረጃ መስጫ ምልክት () በመጫን መመልከት (ማግኘት) ይቻላል። ውክፔዲያን በተሻለ መጠቀም ውክፔዲያን በመጠቀም መረጃን በተሻለ ማግኘት ውክፔዲያን በቀን ከሚጎበኙ የድረ-ገጹ ተጠቃሚዎች መካከል ብዙዎቹ በድረ-ገጹ ላይ ሌሎች እንዲጎበኙ ያስቀመጡዋቸውን (ያጋሩዋቸውን) መረጃዎች ለማገኘት ሲሆን ሌሎች በርካቶች ደግሞ ያላቸውን መረጃ/እውቀት በዚሁ ድረ-ገጽ በመታገዝ ለሌሎች ተጠቃሚዎች ለማጋራት ነው። በዚሁ ተመሳሳይ ቅፅበት ደግሞ ሌሎች በርካታ መጣጥፎች ማሻሻያ ሲደረግባቸው፣ ሌሎች ስለ በርካታ ጉዳዮች የሚዳስሱ መጣጥፎች ደግሞ እንደ አድስ እየተጻፉ ውክፔዲያን ይቀላቀላሉ። በመሆኑም እስካሁን ውክፔዲያን ከተቀላለቀሉ መጣጥፎችም መካከል ከ3000 በላይ የሚሆኑ መጣጥፎች በዊክፔዲያ ማህበረሰብ “የምንጊዜም ምርጥ መጣጥፎች” በሚል የተመረጡ ሲሆን ከ13000 በላይ የሚሆኑት ደግሞ «የተሻሉ መጣጥፎች» በሚል የተመረጡ ናቸው። በተጨማሪም ውክፔዲያ ላይ የሚገኙ መረጃዎች በተለያዩ የመረጃ የደረጃ ክፍልፍሎሽ (ዝርዝሮች) ስር እየተጠናቀሩ የሚቀርቡ ሲሆን ከነዚህም መካከል የተሻለ የመረጃ የክፍፍሎሽ ይዘት ያላቸው መጣጥፎች “የምንጊዜም ምርጥ ዝርዝር” በሚል ጠመርጠዋል። በሌላ በኩል ውክፔዲያ የተለያዩ አርዕስቶች/ጉዳዮችን በተመሳሳይ ቦታ ለማጋራት የሚያስችል አስራርን የሚከተል በመሆኑ ተመሳሳይ ሃሳቦችን በተመሳሳይ አርዕስቶች ዙሪያ በማደራጀትና የተለያየ ይዘት ያላቸውን መረጃዎችን በተመሳሳይ መዳረሻ በማቅረብ ረገድ ውክፔዲያ “የምንግዜም ምርጥ መዳረሻ” በሚል የተመረጠ ድረ-ገጽ ነው። በተለያዩ መጣጠፎች ላይ የተደረጉ የመረጃ ማሻሻያዎችን በሁለት መንገድ መከታተል ይቻላል። በተለያዩ ገፆች በቅርብ ጊዜ የተደረጉ ማሻሻያዎችን ለመመልከት በዋናው ገፅ የሚገኘውና «በቅርብ ጊዜ የተለወጡ» የሚል ርዕስ ያለውን ጽሁፍ በመጫን መመልከት ይቻላል። ማንኛውንም ለውጥ ለመመልከት ከተፈለገ ደግሞ በዋናው ገፅ የሚገኘውን “ማንኛውንም ለማየት” የሚል ርዕስ ያለውን ጽሁፍ በመመጫን መመልከት ይቻላል። በሌላ በኩል ውክፔዲያ ከእንግሊዘኛ ቋንቋ በተጨማሪ አማርኛን ጨምሮ በሌሎች ቋንቋዎችም አገልግሎት ከመስጠቱ ባሻገር፣ የተሻሻለና ቀላል የእንግሊዝኛ ቋንቋን ጨምሮ ሌሎች ተመሳሳይ ይዘት ያላቸውን ፕሮጀክቶች ማለትም፤ መዝገበ-ቃላት፣ ጥቅሶች፣ መጸሐፍት፣ መመሪያዎች፣ ሳይንሳዊ የመረጃ ምንጮችና የዜና አገልገሎትና ሌሎች መሰል አገልገሎቶችን ከሁለት መቶ በላይ በሚሆኑ ቋንቋዎች ያቀርባል። እነዚህም የተለያዩ አግልግሎቶች፣ ከውክፔዲያ ማህበረሰብ በተጨማሪ በተናጥል በሚገኙ ሌሎች ማህበረሰቦች ክትትል፣ ቁጥጥርና ማሻሻያዎች የሚደረጉባቸው ሲሆኑ አብዛሀኛዎቹ መጣጥፎችም በሌሎች የመረጃ መጋሪያ ድረ-ገጾች በቀላሉ የማይገኙ ናቸው። ውክፔድያ በኢትዮጵያ ቋንቋዎች የሚከተሉት ዋና የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የውክፔድያ ድረ-ገጽና መርሀገብር ለተናጋሪዎቻቸው አላቸው። አማርኛ ውክፔድያ - አሁኑ የሚያነቡት ኦሮምኛ ውክፔድያ - : ትግርኛ ውክፔድያ - : ሶማልኛ ውክፔድያ - : አፋርኛ ውክፔድያ - :: (ተዘግቷል ።) የአፋርኛ ውክፔድያ የተዘጋበት ምክንያት የአፋርኛ ዕውቀት ያላቸው ሰዎች ጉድለት በኢንተርኔት ላይ ስላለ ነው። (ደግሞ ኢንተርኔት በኢትዮጵያ ይዩ።) ዳሩ ግን ጊዜያዊ የአፋርኛ ማዘጋጀት ቦታ በ: ተደርጓል። ሌሎች የዓለም ልሳናት «ጊዜያዊ» ውክፔድያዎች ወዘተ. በዚህ ይዘረዘራሉ፦ :። መዝገበ ዕውቀት ለመጽሐፍ የሚችሉ ለቋንቋውም ቅልጥፍና ያላቸው አዛጋጆች በኖሩበት ጊዜ፣ እነዚህ «ጊዜያዊ» መርሃግብሮች ደግሞ የገዛ ድረ-ገጾቻቸውን ሊያገኙ ይችላሉ። ከዚህ በቀር በማንኛውም ሌላ ቋንቋ «ጊዜያዊ» ውክፔድያ በጥያቄ መጀምር ቀላል ነው። መሰረታዊ የውክፔዲያ የገፅ ለገፅ ዝውውር ሁሉም በውኪፔዲያ የሚገኙ መጣጥፎች እርዕስ በርሳቸው እንዲገናኙ ተደርገዋል። ማንኛውም የተሰመረና ሰማያዊ ቀለም ያለው ጽሁፍ ስለተሰመረው አርዕስት የተሻለና የተብራራ መረጃ ሊሰጥ ከሚችል ሌላ ገፅ ጋር እንደተሳሰረ የሚያመለክት ሲሆን የኮምፒውተራችን ማውስ በዚህ በተሰመረና ሰማያዊ ቀለም ባለው ማንኛውም ጽሁፍ ላይ በመጠቆም የተቀመጠው ትስስር ከየትኛው ገፅ ጋር እንደሆነ መመልከት ይቻላል። አንባቢው እንደዚህ አይነት ትስስር ያላቸውን ሀሳቦች ለበለጠ ለመረዳት ከፈለግ በማንኛውም በተሰመረና ሰማያዊ ቀለም ባላው አርዕስት ላይ ክሊክ በማድረግ ተጨማሪ ማብራሪያ ማግኝት ይችላል። ከዚህ አይነት የገጽ-ለገጽ ትስስሮሽ በተጨማሪ አንባቢን ከሌሎች ከተለያዩ ጉዳዮች ጋር እንዲያገናኙ ሆነው የተፈጠሩ ሌሎች ትስስሮች ይኖራሉ። ለምሳሌ ያክል ከቀረበው መጣጥፍ ላይ ወደሚገኘው የመጨረሻ ገጽ የሚዎስዱ፣ ከሌሎች ውጭያዊ ጠቃሚ ድረገፆች ጋር የሚያገናኙ፣ ወደ ማጣቀሻ ምንጮች የሚወስዱና በተለያዩ ደረጃዎች/አርዕስቶች በተዋቀረ ገፅ ላይ በቀላሉ ከአንድ አርዕስት ወደ ሌላ አርዕስት ለመንቀሳቀስ የሚያገዙ ትስስሮች ይገኙበታል።ከዚህ በተጨማሪም አንዳንድ መጣጥፎች እንደ መዝገበቃላት መፍቻዎች፣ የድምፅ የመፀሐፍ ንባብ፣ ጥቅሶችን፣ የቀረበው መጣጥፍ በሌላ ቋንቋ ወደ ተጻፈ የመጣጥፉ ግልባጭ (ኮፒ) የሚወስዱና ከሌሎች ተጨማሪ መረጃዎችን ከያዙ እህት ፕሮጀክቶች ጋር የሚያሰተሳስሩ ይገኙበታል። ውኪፔዲያን ለምርምር መሳሪያነት መጠቀም እንደ ዊኪ (ፈጣን) የመረጃ ፍይልነታቻው በውኪፔዲያ ውስጥ የሚገኙ መጣጥፎች በሁሉም ረገድ የተሟሉ ናቸው ብሎ ለመገመት ያዳግታል። ከዚህ ይልቅ የዊኪፔዲያ የተለያዩ መጣጥፎች፣ በተከታታይ አርትኦትና ማሻሻያዎች እየተደረገባቸው ስለሚሄዱ ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ የተሻሻለንና ትክክለኛ የሆነ መረጃን እየያዙ እንደሚመጡ ይታመናል። ስለሆነም ማንኛው የውኪፔዲያ ተጠቃሚ፤ ሁሉም መጣጥፎች ከመነሻቸው አንድ ኢንሳክሎፔዲያ ሊያሟላው የሚገባውን የጥራት ደረጃ ሊያሟሉ እንደማይችሉና ምናልባትም የተሳሳተ ይዘት ያላቸው ወይም አከራካሪ የሆኑ መረጃዎችን ሊይዙ እንደሚችሉ መገንዘብ ይኖርበታል። በርገጥም ብዙ መጣጥፎች ከመነሻቸው አጭርና የአንድዮሽ ምልከታን ብቻ በመያዝ የሚጀመሩ ሲሆን ቀስ በቀስ ግን የተለያዩ ምልከታዎችንና መረጃዎችን በማካተት ሁሉንም ሊያስማማ በሚችል ደረጃ ሙሉና ሁለገብ እየሆኑ የሚሄዱ ናቸው። ለዚህም እንደምከንያትነት የሚጠቀሰው፣ በርካታ የመጣጥፍ አርታኢዎችና አዘጋጆች፣ የሚያቀርቡትን መጣጥፍ ሁለገብ ይዘት እንዲኖረው ከማድረግ ይልቅ ብዙውን ጊዜ የሚያጠነጥኑት በራሳቸው የግል ፍላጎትና የአንድዮሽ ምልከታ ላይ ብቻ በመሆኑ እንደዚህ አይነት የይዘት ችግር ያለባቸውን መጣጥፎች እንደገና ላማሻሻልና ሚዛናዊ መረጃን እንዲይዙ ለማድረግ ረዘም ያለ ጊዜ የሚጠይቁ ሲሆን ምናልባትም እስከ አንድ ወር ጊዜ ድረስ የሚያስፈልጋቸው ይኖራሉ። በሌላ በኩል ደግሞ የዚህ አይነት ችግር ያላባቸውን መጣጥፎች ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት የተለያዩ አርታኢዎች የየራሳቸውን ድርሻ ስለሚያበረክቱ መጣጥፎቹን ሁለገብ እና ሚዛናዊ ለማድረግ የሚድረገውን ጥረት በቀላሉ ለማሳካት ክፍተኛ አስተዋፆ አላቸው። በተለይም ደግሞ በተለያዩ የመጣጥፍ አርታኢዎች መካከል የሚፈጠርን አልመገባባት በቀለላሉ ለመምፈታት የሚያሰችሉ የውክፔዲያ የራሱ የሆኑ ብዛት ያላቸው ውስጣዊ የድርጅት አሰራሮች ያሉት በመሆኑ በዝህ ረገድ ያሉ አላስፈላጊ ችግሮችን በቀላሉ ማስወገድ ይቻላል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ቢያንስ በመርህ ደረጃ አንድ የዊክፔዲያ መጣጥፍ ሊያሟላ ከሚገባቸው መሰረታሢ ነጥቦች መካከል፣ የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል። በጥራት የተጻፈ፣ ሚዛናዊ የሆነ መረጃን የያዘ መሆን፣ ከዎገናዊነት የፀዳና መዝገባዊ ይዘት ያለው ሲሆን በተጨማሪም፣ የተሟላ፣ ሊጠቀስና ሊረጋገጥ የሚችል መረጃን የያዘ የሚሉት ይገኙበታል። በዚህም ረገድ ይህንን ስታንዳርድ ያሟሉና ከጊዜ ወደ ጊዜ በሟሟላት ላይ የሚገኙ በርካታ መጣጥፎች ያሉ ሲሆን እነዚህንም የተለያዩ የመጣጥፍ ደረጃ መለኪያ ስታንዳርዶችን አሟልተው የተገኙ በረካታ መጣጥፎች “የምንግዜም ምርጥ መጣጥፎች” በሚል ስያሜ ይታወቃሉ። ይህንንም ለማመልከት መጣጥፉ በሚገኝበት ገጽ የላይኛው የቀኝ ጥግ ላይ ትንሽ የኮኮብ ምልክት እንዲቀመጥ ይደረጋል። ነግርግን ሌሎች በረካታ መጣጥፎች፣ የተሟላ የመረጃ ማጣቀሻ ያላስቀመጡ፣ በበቂ ሁኔታ ያልተብራሩ አሊያም በፊት ከነበራቸው የተሻለ ይዘት በተጨማሪ ሌሎች ገና ያልተብራሩ አዳድስ ክፍሎችን ያካተቱ ስለሚሆኑ ይህንን “የምንግዜም ምርጥ መጣጥፎች “ የሚል ደረጃ ለማግኘት ከአንድ ወር እስከ አንድ አመት ጊዜን የሚጠይቅ የማሻሻል ስራና ያላሰለሰ ጥረትን የሚጠይቁ ናቸው። ስለሆነም ምንም እንኳን ውክፔዲያ በብዙ ረገድ እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም የተለያዩ መጣጥፎች የተለያየ የሀሳብ ጥልቀትና ጥራት ሊኖራቸው ስለሚችል ዊክፔዲያን እንደ አንድ የምርምር ማጣቀሻነት ከመጠቀም ጎን ለጎን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ይመከራል። በዚህ ረገድ መረጃ በመስጠት ተጠቃሚን የሚያግዙ ገፆች የተዘጋጁ ሲሆን፣ ከነዚህም መካክል የማመላከቻና የመረጃ ገጽንና ስለ ውክፔዲያ አስተማማኝ የመረጃ ምንጭነት የተደረጉ የሶስተኛ ወገን ጥናቶችን መመልከት ይቻላል። ውክፔዲያ ከሌሎች የህትመት ኢንሳይክሎፕዲያዎች ጋር ሲነፃጸር ውክፔዲያ ቀደም ሲል በስፋት ይውሉ ከነበሩ የህትመት ኢንሳይክሎፕዲያዎች ጋር ሲነፃጸር ከፈተኛና የራሱ የሆነ ጠቀሜታ አለው። በመጀመሪያ ደረጃም አነስተኛ የህትመትና የማስፋፋት ወጭና የሚጠይቅ መሆኑና ዝቀተኛ የሆነ የጎንዮሽ አካባቢያዊ ተፅኖች ያሉት መሀኑን ማንሳት ይቻላል። በሌላ በኩል ምንም አይነት የህትመት ስራ የማይፈለግ በመሆኑ ኮምፒውተሮች የራሳቸው የሆነ አካባቢያዊ ተጽኖ ይኖራቸዋል። በተጨማሪም ሁሉንም አይነት መግለጫዎችን በአንድ ገጽ አካቶ ከመያዝ ይልቅ እርስበርስ የሚዛመዱና በሌሎች የተለያዩ ገጾች የተብራሩ ጉዳዮችን ከአጫጭር ማጠቃለያዎች ጋር አጣምሮ በማቀረብ በቀላሉ መረጃን ለማግኘት ይረዳል። በመጨረሻም እንዴ ሌሎች የህትመት ኢንሳይክሎፕዲያዎች የተወሰነ የአርትኦትና የማሻሻያ ጊዜን የማይጠይቅ በመሆኑ፣ ውክፔዲያ ከሌሎች የህትመት ኢንሳይክሎፕዲያዎች ጋር ሲነጻጸር አጭር የአርትኦት ጊዜን የሚጠይቅና በማንኛውም ጊዜና ሰአት መሻሻሎችን በማደረግ መጣጠፎች ወቅታዊና ጊዜውን የተበቀ መረጃን ይዘው እንዲቀጥሉ የሚያስችል ዘመናዊ አሰራርን ይፈቅዳል እና መረጃ ለማንበብ አደገኛ ጣቢያ። የውጭ መያያዣ ውክፔዲያ ኹኔታ ከ10 አመት በኋላ - አጭር ቪዲዮ በዩ ቱብ ላይ
4132
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%89%A3%E1%89%A0%E1%88%A9%E1%89%B5%20%E1%8B%A8%E1%88%80%E1%8C%88%E1%88%AD%20%E1%8A%95%E1%8C%89%E1%88%B3%E1%8B%8A%20%E1%8A%A0%E1%8C%88%E1%8B%9B%E1%8B%9D
የተባበሩት የሀገር ንጉሳዊ አገዛዝ
የታላቋ ብሪታንያ እና የሰሜን አየርላንድ ዩናይትድ ኪንግደም በተለምዶ ዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) ወይም ብሪታንያ በሰሜን-ምዕራብ አውሮፓ በሰሜን-ምእራብ አውሮፓ የባህር ዳርቻ ላይ የምትገኝ ሉዓላዊ ሀገር ነች። ዩናይትድ ኪንግደም ደሴትን ያጠቃልላል። ታላቋ ብሪታንያ፣ የአየርላንድ ደሴት ሰሜናዊ ምስራቅ ክፍል እና በብሪቲሽ ደሴቶች ውስጥ ያሉ ብዙ ትናንሽ ደሴቶች። ሰሜን አየርላንድ ከአየርላንድ ሪፐብሊክ ጋር የመሬት ድንበር ትጋራለች። ያለበለዚያ ዩናይትድ ኪንግደም በአትላንቲክ ውቅያኖስ የተከበበ ሲሆን በምስራቅ ሰሜን ባህር ፣በደቡብ የእንግሊዝ ቻናል እና የሴልቲክ ባህር በደቡብ-ምዕራብ ፣በአለም ላይ 12 ኛውን ረጅሙ የባህር ዳርቻ ይሰጣታል። የአየርላንድ ባህር ታላቋን ብሪታንያ እና አየርላንድን ይለያል። የዩናይትድ ኪንግደም አጠቃላይ ስፋት 93,628 ስኩዌር ማይል (242,500 ኪ.ሜ.) ነው፣ በ2020 ከ67 ሚሊዮን ህዝብ ይገመታል። ዩናይትድ ኪንግደም አሃዳዊ ፓርላማ ዲሞክራሲ እና ሕገ መንግሥታዊ ንጉሣዊ ሥርዓት ነች። ንጉሥ ቻርለስ ሣልሳዊ ከ ሴፕቴምበር 8 2022 ጀምሮ ነገሡ። ዋና ከተማዋና ትልቁ ከተማ ለንደን ናት፣ 14 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርባት ዓለም አቀፍ ከተማ እና የፋይናንስ ማዕከል ናት። ሌሎች ዋና ዋና ከተሞች በርሚንግሃም ያካትታሉ, ማንቸስተር, ግላስጎው, ሊቨርፑል እና ሊድስ. ዩናይትድ ኪንግደም አራት አገሮችን ያቀፈ ነው-እንግሊዝ ፣ ስኮትላንድ ፣ ዌልስ እና ሰሜን አየርላንድ። ከእንግሊዝ በቀር፣ የተካተቱት አገሮች የራሳቸው የተከፋፈሉ መንግስታት አሏቸው፣ እያንዳንዳቸው የተለያየ ሥልጣን አላቸው። ዩናይትድ ኪንግደም ለበርካታ መቶ አመታት ከተከታታይ መቀላቀል፣ ማኅበራት እና መከፋፈያዎች የተሻሻለ ነው። በእንግሊዝ መንግሥት (እ.ኤ.አ. በ1542 የተካተተውን ዌልስን ጨምሮ) እና የስኮትላንድ መንግሥት በ1707 መካከል የተደረገው የሕብረት ስምምነት የታላቋ ብሪታንያ መንግሥት ፈጠረ። በ 1801 ከአየርላንድ መንግሥት ጋር ያለው ህብረት የታላቋ ብሪታንያ እና የአየርላንድ ዩናይትድ ኪንግደም ፈጠረ። አብዛኛው አየርላንድ በ1922 ከእንግሊዝ ተለየች፣ የአሁኑን የታላቋ ብሪታኒያ እና የሰሜን አየርላንድ ዩናይትድ ኪንግደም ትቶ በ1927 ይህን ስም በይፋ ተቀብሏል። በአቅራቢያው ያለው የሰው ደሴት፣ ጉርንሴይ እና ጀርሲ የዩናይትድ ኪንግደም አካል አይደሉም፣ የዘውድ ጥገኝነት ከብሪቲሽ መንግስት ጋር ለመከላከያ እና ለአለም አቀፍ ውክልና ሀላፊነት ያለው። እንዲሁም 14 የብሪቲሽ የባህር ማዶ ግዛቶች አሉ፣ የብሪቲሽ ኢምፓየር የመጨረሻ ቅሪቶች በ1920ዎቹ ከፍታ ላይ ሲደርሱ፣ የአለምን መሬት ሩብ የሚጠጋውን እና ከአለም ህዝብ አንድ ሶስተኛውን ያቀፈ እና በታሪክ ውስጥ ትልቁ ኢምፓየር ነበር። የብሪታንያ ተጽእኖ በብዙዎቹ የቀድሞ ቅኝ ግዛቶቿ ቋንቋ፣ ባህል እና የሕግ እና የፖለቲካ ሥርዓቶች ውስጥ ይስተዋላል። ዩናይትድ ኪንግደም በአለም አምስተኛው ትልቁ ኢኮኖሚ በስም ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒ) እና አስረኛው ትልቁን በግዢ ሃይል እኩልነት () ነው። ከፍተኛ ገቢ ያለው ኢኮኖሚ እና በጣም ከፍተኛ የሰው ልጅ ልማት መረጃ ጠቋሚ ደረጃ አላት፤ ከአለም 13ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ዩናይትድ ኪንግደም በዓለም የመጀመሪያዋ በኢንዱስትሪ የበለጸገች ሀገር ሆነች እና በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የአለም ቀዳሚ ሃይል ነበረች።ዛሬ እንግሊዝ ከአለም ታላላቅ ሀይሎች አንዷ ሆና ቀጥላለች፣በኢኮኖሚ፣ባህላዊ፣ወታደራዊ፣ሳይንሳዊ፣ቴክኖሎጂ እና ፖለቲካዊ ተፅእኖዎች። እውቅና ያለው የኒውክሌር መንግስት ሲሆን በአለም አቀፍ ደረጃ በወታደራዊ ወጪ በአራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በ 1946 ከመጀመሪያው ስብሰባ ጀምሮ ቋሚ አባል ነው. ዩናይትድ ኪንግደም የኮመንዌልዝ ኦፍ ኔሽን፣ የአውሮፓ ምክር ቤት፣ 7፣ ቡድን አስር፣ 20፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ኔቶ፣ ፣ የኢኮኖሚ ትብብርና ልማት ድርጅት ()፣ ኢንተርፖል አባል ነች። ፣ እና የዓለም ንግድ ድርጅት ()። እ.ኤ.አ. በ2016 የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገር እና ተከታዩ የአውሮፓ ህብረት እ.ኤ.አ. ሥርወ-ቃላት እና ቃላት የተባበሩት መንግስታት 1707 ወይም አቦር 1700 ወይም 1699 በኢትዮጵያ የቀን አቆጣጠር የእንግሊዝ መንግሥት እና የስኮትላንድ መንግሥት “በታላቋ ብሪታንያ ስም ወደ አንድ መንግሥት የተዋሐዱ ናቸው” በማለት አውጇል። “ዩናይትድ ኪንግደም” የሚለው ቃል አልፎ አልፎ ጥቅም ላይ ውሏል ። ከ 1707 እስከ 1800 ያለው ኦፊሴላዊ ስም በቀላሉ "ታላቋ ብሪታንያ" ቢሆንም ለቀድሞው የታላቋ ብሪታንያ መንግሥት መግለጫ። የ 1800 የሕብረት ሥራ በ 1801 የታላቋ ብሪታንያ እና የአየርላንድ መንግስታትን አንድ አደረገ ፣ የታላቋ ብሪታንያ እና የአየርላንድ ዩናይትድ ኪንግደም ፈጠረ። በ1922 የአየርላንድ ክፍፍል እና የአይሪሽ ነፃ ግዛት ሰሜን አየርላንድ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የአየርላንድ ደሴት ብቸኛ አካል ሆና ከቀረችው በኋላ በ1922 ዓ.ም. . ምንም እንኳን ዩናይትድ ኪንግደም ሉዓላዊ ሀገር ብትሆንም፣ እንግሊዝ፣ ስኮትላንድ፣ ዌልስ እና ሰሜን አየርላንድ እንደሀገር በስፋት ይጠራሉ።የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ድረ-ገጽ ዩናይትድ ኪንግደምን ለመግለጽ "በሀገር ውስጥ ያሉ ሀገራት" የሚለውን ሀረግ ተጠቅሟል። አንዳንድ ስታቲስቲካዊ ማጠቃለያዎች፣ እንደ ዩናይትድ ኪንግደም ለአስራ ሁለቱ 1 ክልሎች ስኮትላንድ፣ ዌልስ እና ሰሜን አየርላንድ እንደ “ክልሎች” ሰሜን አየርላንድ ደግሞ “አውራጃ” ተብሎም ይጠራል። አወዛጋቢ፣ ምርጫው ብዙውን ጊዜ የአንድን ሰው የፖለቲካ ምርጫ ያሳያል። "ታላቋ ብሪታንያ" የሚለው ቃል በተለምዶ የታላቋ ብሪታንያ ደሴትን ወይም በፖለቲካዊ መልኩ ወደ እንግሊዝ፣ ስኮትላንድ እና ዌልስ በጥምረት ይመለከታል። አንዳንድ ጊዜ ለዩናይትድ ኪንግደም በአጠቃላይ እንደ ልቅ ተመሳሳይ ቃል ያገለግላል። "ብሪታንያ" የሚለው ቃል ለሁለቱም ለታላቋ ብሪታንያ እና ለዩናይትድ ኪንግደም ተመሳሳይ ቃል ጥቅም ላይ ይውላል. አጠቃቀሙ ድብልቅ ነው፡ የዩናይትድ ኪንግደም መንግስት በእሱ ላይ "ብሪታንያ" ወይም "ብሪቲሽ" ከሚለው ቃል ይልቅ "ዩኬ" የሚለውን ቃል መጠቀም ይመርጣል. ሁለቱም ቃላቶች ዩናይትድ ኪንግደምን እንደሚያመለክቱ እና በሌላ ቦታ "የብሪታንያ መንግስት" ቢያንስ እንደ "የዩናይትድ ኪንግደም መንግስት" ጥቅም ላይ እንደሚውል በማመን የራሱ ድረ-ገጽ (ከኤምባሲዎች በስተቀር)። የዩናይትድ ኪንግደም የጂኦግራፊያዊ ስሞች ቋሚ ኮሚቴ "ዩናይትድ ኪንግደም", "ዩኬ" እና "ዩኬ" እውቅና ሰጥቷል. በታላቋ ብሪታንያ እና በሰሜን አየርላንድ ለዩናይትድ ኪንግደም እና በሰሜን አየርላንድ በቶፖኖሚክ መመሪያዎች ውስጥ እንደ አጠር እና አጠር ያለ የጂኦፖለቲካ ቃላት; “ብሪታንያ”ን አልዘረዘረም ነገር ግን “ሰሜን አየርላንድን የማይለዋወጥ ብቸኛዋ “ታላቋ ብሪታንያ” የሚለው መጠሪያ ቃል ብቻ እንደሆነ ልብ ይሏል። ቢቢሲ በታሪክ "ብሪታንያን" ለታላቋ ብሪታንያ ብቻ መጠቀምን ይመርጣል፣ ምንም እንኳን የአሁኑ የአጻጻፍ መመሪያ "ታላቋ ብሪታንያ" ሰሜን አየርላንድን ከማስወጣቱ በስተቀር አቋም አይወስድም። "ብሪቲሽ" የሚለው ቅጽል በተለምዶ ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል እና በህግ የዩናይትድ ኪንግደም ዜግነት እና ከዜግነት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ለማመልከት ያገለግላል. የዩናይትድ ኪንግደም ሰዎች ብሄራዊ ማንነታቸውን ለመግለጽ የተለያዩ ቃላትን ይጠቀማሉ እና እራሳቸውን እንደ ብሪቲሽ፣ እንግሊዘኛ፣ ስኮትላንዳዊ፣ ዌልሽ፣ ሰሜናዊ አይሪሽ ወይም አይሪሽ መሆናቸውን ሊገልጹ ይችላሉ። ወይም የተለያዩ ብሄራዊ ማንነቶችን በማጣመር። የዩናይትድ ኪንግደም ዜጋ ኦፊሴላዊ ስያሜ "የብሪታንያ ዜጋ" ነው. ከኅብረት ስምምነት በፊት ዩናይትድ ኪንግደም ለመሆን በነበረችው በሰውኛ ዘመናዊ ሰዎች የሰፈሩት ከ30,000 ዓመታት በፊት ጀምሮ በማዕበል ነበር።በክልሉ ቅድመ ታሪክ ዘመን መጨረሻ ህዝቡ በዋነኛነት ኢንሱላር ሴልቲክ ከሚባለው ባህል የመጣ እንደሆነ ይታሰባል። ብሪቶኒክ ብሪታንያ እና ጌሊክ አየርላንድን ያቀፈ። ከሮማውያን ወረራ በፊት ብሪታንያ ወደ 30 የሚጠጉ የአገሬው ተወላጆች መኖሪያ ነበረች። ትልልቆቹ ቤልጌ፣ ብሪጋንቶች፣ ሲልረስ እና አይስኒ ነበሩ። የታሪክ ምሁር የሆኑት ኤድዋርድ ጊቦን ስፔን፣ ጋውል እና ብሪታንያ በ‹‹ሥነ ምግባር እና ቋንቋዎች›› መመሳሰል ላይ ተመስርተው ‹‹በተመሳሳይ ጠንካራ አረመኔዎች ዘር›› እንደሚኖሩ ያምናል። በ43 ዓ.ም የጀመረው የሮማውያን ወረራ እና የደቡብ ብሪታንያ የ400 ዓመት አገዛዝ በኋላ በጀርመናዊው የአንግሎ-ሳክሰን ሰፋሪዎች ወረራ የብሪቶኒክ አካባቢን በዋነኛነት ወደ ዌልስ፣ ኮርንዋል እና እስከ መጨረሻው ደረጃ ድረስ እንዲቀንስ አድርጓል። የአንግሎ-ሳክሰን ሰፈር፣ ሄን ኦግሌድ (ሰሜን እንግሊዝ እና የደቡባዊ ስኮትላንድ ክፍሎች)። በአንግሎ-ሳክሰኖች የሰፈረው አብዛኛው ክልል በ10ኛው ክፍለ ዘመን እንደ እንግሊዝ መንግሥት አንድ ሆነ። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ በሰሜን ምዕራብ ብሪታንያ የሚገኙ የጌሊክ ተናጋሪዎች (ከአየርላንድ ሰሜናዊ ምስራቅ ጋር ግንኙነት ያላቸው እና በተለምዶ በ 5 ኛው ክፍለ ዘመን ከዚያ ተሰደዱ ተብሎ የሚታሰበው) በ9ኛው ክፍለ ዘመን የስኮትላንድን መንግስት ለመፍጠር ከፒክቶች ጋር ተባበሩ።በ1066 ኖርማኖች እና ብሬተን አጋሮቻቸው እንግሊዝን ከሰሜን ፈረንሳይ ወረሩ። እንግሊዝን ከያዙ በኋላ፣ ሰፊውን የዌልስ ክፍል ያዙ፣ ብዙ አየርላንድን ያዙ እና በስኮትላንድ እንዲሰፍሩ ተጋብዘው ወደ እያንዳንዱ ሀገር በሰሜን ፈረንሳይ ሞዴል እና በኖርማን-ፈረንሣይ ባህል ላይ ፊውዳሊዝምን አመጡ። የአንግሎ-ኖርማን ገዥ መደብ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል፣ነገር ግን በመጨረሻ ከእያንዳንዱ የአካባቢ ባህሎች ጋር ተዋህዷል። ተከታዩ የመካከለኛው ዘመን የእንግሊዝ ነገሥታት የዌልስን ወረራ አጠናቀቁ እና ስኮትላንድን ለመቀላቀል ሙከራ አድርገው አልተሳኩም። እ.ኤ.አ. በ1320 የአርብራት መግለጫ ነፃነቷን ስታረጋግጥ፣ ስኮትላንድ ከእንግሊዝ ጋር የማያቋርጥ ግጭት ብታደርግም ከዚያ በኋላ ነፃነቷን አስጠብቃለች። የእንግሊዝ ነገሥታት፣ በፈረንሳይ ከፍተኛ ግዛቶችን በመውረስ እና የፈረንሣይ ዘውድ ይገባኛል በሚል፣ በፈረንሳይ በተፈጠሩ ግጭቶች፣ በተለይም የመቶ ዓመታት ጦርነት፣ የስኮትላንዳውያን ነገሥታት በዚህ ጊዜ ውስጥ ከፈረንሣይ ጋር ኅብረት ፈጥረው ነበር። የጥንቷ ብሪታንያ ሃይማኖታዊ ግጭቶች የተሐድሶ ተሃድሶ እና የፕሮቴስታንት መንግሥት አብያተ ክርስቲያናት በየሀገሩ መጀመራቸውን ተመለከተ። ዌልስ ሙሉ በሙሉ ወደ እንግሊዝ ግዛት ተቀላቀለች እና አየርላንድ ከእንግሊዝ ዘውድ ጋር በግላዊ አንድነት እንደ መንግስት ተመስርታ ነበር ። ሰሜናዊ አየርላንድ በምትሆንበት ወቅት ፣ የነፃው የካቶሊክ ጋሊሊክ መኳንንት መሬቶች ተወስደው ከእንግሊዝ ለመጡ ፕሮቴስታንት ሰፋሪዎች ተሰጡ። እና ስኮትላንድ. እ.ኤ.አ. በ 1603 የእንግሊዝ ፣ የስኮትላንድ እና የአየርላንድ መንግስታት የስኮትስ ንጉስ ጄምስ ስድስተኛ የእንግሊዝ እና የአየርላንድ ዘውዶችን ወርሶ ፍርድ ቤቱን ከኤድንበርግ ወደ ለንደን ሲያንቀሳቅስ በግል ህብረት ውስጥ አንድ ሆነዋል ። ሆኖም እያንዳንዱ አገር የተለየ የፖለቲካ አካል ሆኖ ቆይቶ የተለየ የፖለቲካ፣ የሕግ እና የሃይማኖት ተቋማትን እንደያዘ ቆይቷል። በ 17 ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ሦስቱም መንግስታት በተከታታይ በተያያዙ ጦርነቶች (የእንግሊዝ የእርስ በርስ ጦርነትን ጨምሮ) ንጉሣዊው አገዛዝ በጊዜያዊነት እንዲገለበጥ፣ በንጉሥ ቻርልስ ቀዳማዊ መገደል እና የአጭር- በእንግሊዝ ኮመንዌልዝ ፣ ስኮትላንድ እና አየርላንድ አሃዳዊ ሪፐብሊክ ኖረ። በ 17 ኛው እና በ 18 ኛው ክፍለ ዘመን የብሪቲሽ መርከበኞች በአውሮፓ እና በካሪቢያን የባህር ዳርቻ ላይ መርከቦችን በማጥቃት እና በመስረቅ የባህር ላይ የባህር ላይ የባህር ላይ ዝርፊያ (የግል ንብረትነት) ተግባር ላይ ተሰማርተዋል ። ንጉሣዊው ሥርዓት ቢታደስም፣ ኢንተርሬግኑም (እ.ኤ.አ. ከ 1688 የከበረ አብዮት እና ተከታዩ የሕግ ድንጋጌ 1689 እና የይገባኛል ጥያቄ 1689) ከሌሎች የአውሮፓ አገሮች በተለየ መልኩ የንጉሣዊው አብሶልቲዝም እንደማያሸንፍ አረጋግጠዋል። ካቶሊክ ነኝ ባይ ወደ ዙፋኑ መቅረብ አይችልም። የብሪታንያ ሕገ መንግሥት የሚገነባው ሕገ መንግሥታዊ ንጉሣዊ ሥርዓትንና የፓርላማ ሥርዓትን መሠረት በማድረግ ነው። በ1660 የሮያል ሶሳይቲ ሲመሰረት፣ ሳይንስ በጣም ተበረታቷል። በዚህ ጊዜ ውስጥ በተለይም በእንግሊዝ የባህር ኃይል ማደግ እና ለግኝት ጉዞዎች ፍላጎት የባህር ማዶ ቅኝ ግዛቶችን በተለይም በሰሜን አሜሪካ እና በካሪቢያን አካባቢዎች እንዲሰፍሩ አድርጓል. እ.ኤ.አ. በ1606፣ 1667 እና 1689 በታላቋ ብሪታንያ ሁለቱን መንግስታት አንድ ለማድረግ ቀደም ሲል የተደረገው ሙከራ ባይሳካም፣ በ1705 የተጀመረው ሙከራ የ1706 የኅብረት ስምምነት በሁለቱም ፓርላማዎች እንዲስማማና እንዲፀድቅ አድርጓል። የታላቋ ብሪታንያ መንግሥት ግንቦት 1 ቀን 1707 (ኤውሮጳ) የታላቋ ብሪታንያ መንግሥት ተመሠረተ ፣ የሕብረት ሥራ ውጤት በእንግሊዝ እና በስኮትላንድ ፓርላማዎች የ 1706 የሕብረት ስምምነትን ለማፅደቅ እና ሁለቱን መንግስታት አንድ ለማድረግ። በ18ኛው ክፍለ ዘመን የካቢኔ መንግስት በሮበርት ዋልፖል ስር ተቋቋመ፣ በተግባር የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ። ተከታታይ የያዕቆብ አመፅ የፕሮቴስታንት ሃኖቨርን ቤት ከብሪቲሽ ዙፋን ላይ ለማስወገድ እና የካቶሊክን የስቱዋርትን ቤት ለመመለስ ፈለገ። በመጨረሻ በ1746 በኩሎደን ጦርነት ያቆባውያን ተሸነፉ፣ከዚያም የስኮትላንድ ሀይላንድ ነዋሪዎች በጭካኔ ተጨፈኑ። በሰሜን አሜሪካ የእንግሊዝ ቅኝ ግዛቶች በአሜሪካ የነጻነት ጦርነት ከብሪታንያ ተገንጥለው በ1783 በብሪታንያ እውቅና ያገኘችው ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ሆነች። የእንግሊዝ ኢምፔሪያል ምኞት ወደ እስያ በተለይም ወደ ህንድ ዞረ። ብሪታንያ በአትላንቲክ የባሪያ ንግድ ውስጥ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውታለች፣ በተለይም እ.ኤ.አ. በ 1662 እና 1807 መካከል የብሪታንያ ወይም የእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ባሪያ መርከቦች ከአፍሪካ ወደ 3.3 ሚሊዮን የሚጠጉ ባሪያዎችን ሲያጓጉዙ ነበር። ባሪያዎቹ በብሪቲሽ ይዞታዎች በተለይም በካሪቢያን ግን በሰሜን አሜሪካ በሚገኙ እርሻዎች ላይ እንዲሠሩ ተወስደዋል። ባርነት ከካሪቢያን የስኳር ኢንዱስትሪ ጋር ተዳምሮ በ18ኛው ክፍለ ዘመን የብሪታንያ ኢኮኖሚ በማጠናከር እና በማደግ ረገድ ትልቅ ሚና ነበረው። ነገር ግን ፓርላማው በ1807 ንግዱን አግዷል፣ በ1833 በብሪቲሽ ኢምፓየር ባርነትን ታግዶ፣ ብሪታንያም በአፍሪካ በመገደብ ባርነትን ለማስወገድ በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ ግንባር ቀደም ሚና ነበራት እና ሌሎች ሀገራት የንግድ ንግዳቸውን በተከታታይ ስምምነቶች እንዲያቆሙ ግፊት አድርጋለች። አንጋፋው አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ፀረ-ባርነት ኢንተርናሽናል በ1839 በለንደን ተቋቋመ። ከአየርላንድ ጋር ከነበረው ህብረት እስከ አንደኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ ድረስ በ1801 የታላቋ ብሪታንያ እና የአየርላንድ ፓርላማዎች እያንዳንዳቸው ሁለቱን መንግስታት አንድ በማድረግ እና የታላቋ ብሪታንያ እና የአየርላንድ ዩናይትድ ኪንግደም ሲፈጥሩ “ዩናይትድ ኪንግደም” የሚለው ቃል ይፋ ሆነ። በፈረንሣይ አብዮታዊ ጦርነቶች እና የናፖሊዮን ጦርነቶች መጨረሻ የፈረንሳይ ሽንፈት ከደረሰ በኋላ ዩናይትድ ኪንግደም የ19ኛው ክፍለ ዘመን ዋና የባህር ኃይል እና የንጉሠ ነገሥት ኃይል ሆና ብቅ አለች (ከ1830 ገደማ ጀምሮ ለንደን በዓለም ላይ ትልቁ ከተማ ነበረች) በባህር ላይ ያልተፈታተነው የብሪታንያ የበላይነት ከጊዜ በኋላ ፓክስ ብሪታኒካ ("የብሪቲሽ ሰላም") ተብሎ ተገልጿል ይህም በታላላቅ ሀይሎች መካከል አንጻራዊ ሰላም የሰፈነበት ጊዜ የብሪቲሽ ኢምፓየር አለም አቀፋዊ ግዛት የሆነበት እና የአለም አቀፍ ፖሊስነትን ሚና የተቀበለበት ወቅት ነበር. . እ.ኤ.አ. በ 1851 ታላቁ ኤግዚቢሽን ወቅት ብሪታንያ “የዓለም አውደ ጥናት” ተብላ ተገልጻለች። እ.ኤ.አ. ከ 1853 እስከ 1856 ብሪታንያ ከሩሲያ ግዛት ጋር በተደረገው ጦርነት ከኦቶማን ኢምፓየር ጋር በመተባበር በቦንኒያ ባሕረ ሰላጤ እና በፊንላንድ ባሕረ ሰላጤ የአላንድ ጦርነት ተብሎ በሚታወቀው የባልቲክ ባህር የባህር ኃይል ጦርነቶች ውስጥ በመሳተፍ በክራይሚያ ጦርነት ተሳትፋለች። , ከሌሎች ጋር. የብሪቲሽ ኢምፓየር ተስፋፍቷል ህንድ፣ ትላልቅ የአፍሪካ ክፍሎች እና ሌሎች በአለም ዙሪያ ያሉ ሌሎች ግዛቶችን ይጨምራል። በቅኝ ግዛቶቿ ላይ ከወሰደችው መደበኛ ቁጥጥር ጎን ለጎን፣ ብሪታንያ በአብዛኛዎቹ የአለም ንግድ የበላይነት የበርካታ ክልሎችን እንደ እስያ እና ላቲን አሜሪካ ያሉ ኢኮኖሚዎችን በብቃት ተቆጣጥራለች። በአገር ውስጥ፣ የፖለቲካ አመለካከቶች የነጻ ንግድን እና የላይሴዝ-ፋይር ፖሊሲዎችን እና ቀስ በቀስ የድምፅ መስጫ ፍራንቺስ እንዲስፋፋ አድርጓል። በክፍለ ዘመኑ የህዝቡ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል፣ከተሜነት መስፋፋት ታጅቦ ከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጭንቀቶችን አስከትሏል።አዲስ ገበያዎችን እና የጥሬ ዕቃ ምንጮችን ለመፈለግ፣በዲስራኤሊ ስር ያለው ወግ አጥባቂ ፓርቲ በግብፅ፣ደቡብ አፍሪካ የኢምፔሪያሊስት መስፋፋትን ጀምሯል። , እና ሌላ ቦታ. ካናዳ፣ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ ራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳድሩ ገዢዎች ሆኑ። ከመቶ አመት መባቻ በኋላ የብሪታንያ የኢንዱስትሪ የበላይነት በጀርመን እና በዩናይትድ ስቴትስ ተገዳደረ። ከ 1900 በኋላ የአየርላንድ ማህበራዊ ማሻሻያ እና የቤት ውስጥ ህግ አስፈላጊ የቤት ውስጥ ጉዳዮች ነበሩ ። የሌበር ፓርቲ በ 1900 ከሰራተኛ ማህበራት እና ትናንሽ የሶሻሊስት ቡድኖች ጥምረት ወጣ ፣ እና ከ 1914 በፊት የሴቶች ድምጽ የመምረጥ መብት እንዲከበር የምርጫ ቅስቀሳ አድርጓል ።ብሪታንያ ከፈረንሳይ፣ ሩሲያ እና (ከ1917 በኋላ) ዩናይትድ ስቴትስ፣ ከጀርመን እና አጋሮቿ ጋር በአንደኛው የዓለም ጦርነት ተዋግታለች። የብሪቲሽ ጦር ኃይሎች በአብዛኛው የብሪቲሽ ኢምፓየር እና በተለያዩ የአውሮፓ ክልሎች በተለይም በምዕራቡ ግንባር ላይ ተሰማርተው ነበር። በትሬንች ጦርነት ምክንያት የሞቱት ሰዎች ቁጥር ብዙ ትውልድ እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል፣ በሀገሪቱ ውስጥ ዘላቂ የሆነ ማህበራዊ ተፅእኖ እና በማህበራዊ ስርዓቱ ላይ ትልቅ መስተጓጎል አስከትሏል። ከጦርነቱ በኋላ ብሪታንያ በበርካታ የቀድሞ የጀርመን እና የኦቶማን ቅኝ ግዛቶች ላይ የመንግስታቱን ሊግ ስልጣን ተቀበለች። የብሪቲሽ ኢምፓየር ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፣ ከአለም አንድ አምስተኛውን የመሬት ገጽታ እና ከህዝቡ አንድ አራተኛውን ይሸፍናል። ብሪታንያ 2.5 ሚሊዮን ጉዳት ደርሶባታል እናም ጦርነቱን በከፍተኛ ብሄራዊ ዕዳ ጨርሳለች። የእርስ በርስ ጦርነት ዓመታት እና ሁለተኛው የዓለም ጦርነት በ1920ዎቹ አጋማሽ አብዛኛው የብሪታንያ ህዝብ የቢቢሲ የሬዲዮ ፕሮግራሞችን ማዳመጥ ይችላል። የሙከራ የቴሌቭዥን ስርጭቶች በ1929 ጀመሩ እና የመጀመሪያው የቢቢሲ ቴሌቪዥን አገልግሎት በ1936 ተጀመረ። የአየርላንድ ብሔርተኝነት መነሳት፣ እና በአየርላንድ ውስጥ በአይሪሽ የቤት ህግ ውሎች ላይ በአየርላንድ ውስጥ አለመግባባቶች፣ በመጨረሻም በ1921 ወደ ደሴቲቱ መከፋፈል ምክንያት ሆነዋል። የአየርላንድ ነፃ ግዛት ነፃ ሆነ፣ መጀመሪያ ላይ በ1922 የዶሚኒየን ደረጃ ያለው፣ እና በ1931 በማያሻማ ሁኔታ እራሱን የቻለ። አየርላንድ የዩናይትድ ኪንግደም አካል ሆና ቆይታለች። እ.ኤ.አ. የ1928 ህግ ለሴቶች ከወንዶች ጋር እኩልነት እንዲኖረው በማድረግ የምርጫውን ምርጫ አስፋፍቷል። እ.ኤ.አ. በ 1920 ዎቹ አጋማሽ ላይ የምሽት ማዕበል በ 1926 አጠቃላይ አድማ ። ብሪታንያ ታላቁ የኢኮኖሚ ድቀት በተከሰተበት ጊዜ ከጦርነቱ ውጤቶች አላገገመችም ። ይህ በቀድሞው የኢንዱስትሪ አካባቢዎች ከፍተኛ ሥራ አጥነት እና ችግር፣ እንዲሁም በ1930ዎቹ የፖለቲካ እና የማህበራዊ አለመረጋጋት፣ የኮሚኒስት እና የሶሻሊስት ፓርቲዎች አባልነት እየጨመረ መጥቷል። ጥምር መንግሥት በ1931 ዓ.ም. ቢሆንም፣ "ብሪታንያ በጣም ሀብታም ሀገር ነበረች፣ በጦር መሣሪያ የምትፈራ፣ ጥቅሟን ለማስከበር ርህራሄ የሌላት እና በአለም አቀፍ የምርት ስርአት እምብርት ላይ የተቀመጠች ሀገር ነበረች።" ናዚ ጀርመን ፖላንድን ከወረረ በኋላ ብሪታንያ በ1939 በጀርመን ላይ ጦርነት በማወጅ ወደ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ገባች። ዊንስተን ቸርችል በ1940 ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጥምር መንግሥት መሪ ሆነ። በጦርነቱ የመጀመሪያ አመት የአውሮፓ አጋሮቿ ሽንፈት ቢያጋጥሟትም ብሪታንያ እና ግዛቱ በጀርመን ላይ ብቻውን ጦርነቱን ቀጠለ። ቸርችል በጦርነቱ ወቅት ለመንግስት እና ለጦር ኃይሉ ለመምከር እና ለመደገፍ ኢንዱስትሪ፣ ሳይንቲስቶች እና መሐንዲሶች ተሰማሩ። እ.ኤ.አ. በ 1940 የሮያል አየር ሀይል በብሪታንያ ጦርነት ሰማዩን ለመቆጣጠር በተደረገው ትግል የጀርመኑን ሉፍትዋፍን ድል አደረገ። በ ወቅት የከተማ አካባቢዎች ከባድ የቦምብ ጥቃት ደርሶባቸዋል። እ.ኤ.አ. በ 1941 የተቋቋሙት የብሪታንያ ፣ የዩናይትድ ስቴትስ እና የሶቪየት ህብረት ግራንድ ህብረት በአክሲስ ሀይሎች ላይ አጋሮችን እየመራ ። በአትላንቲክ ውቅያኖስ ጦርነት፣ በሰሜን አፍሪካ ዘመቻ እና በጣሊያን ዘመቻ ውሎ አድሮ ከባድ የተፋለሙ ድሎች ነበሩ። እ.ኤ.አ. በ 1944 በኖርማንዲ ማረፊያ እና አውሮፓን ነፃ በማውጣት የብሪታንያ ኃይሎች ከአጋሮቻቸው ከአሜሪካ ፣ ከሶቪየት ኅብረት እና ከሌሎች አጋር አገሮች ጋር ትልቅ ሚና ተጫውተዋል ። የብሪቲሽ ጦር በጃፓን ላይ የበርማ ዘመቻን ሲመራ የብሪቲሽ ፓሲፊክ የጦር መርከቦች ጃፓንን በባህር ላይ ተዋጉ። የብሪታንያ ሳይንቲስቶች ለጃፓን እጅ እንድትሰጥ ምክንያት የሆነውን የማንሃተን ፕሮጀክት አስተዋፅዖ አድርገዋል። የመሬት አቀማመጥ የዩናይትድ ኪንግደም አጠቃላይ ቦታ በግምት 244,820 ካሬ ኪሎ ሜትር (94,530 ካሬ ማይል) ነው። አገሪቷ የብሪቲሽ ደሴቶችን ዋና ክፍል ትይዛለች እና የታላቋ ብሪታንያ ደሴት ፣ የአየርላንድ ደሴት ሰሜናዊ ምስራቅ አንድ ስድስተኛ እና አንዳንድ ትናንሽ ደሴቶችን ያጠቃልላል። በሰሜን አትላንቲክ ውቅያኖስ እና በሰሜን ባህር መካከል የሚገኝ ሲሆን በደቡብ ምስራቅ የባህር ዳርቻ ከሰሜን ፈረንሳይ የባህር ዳርቻ በ 22 ማይል (35 ኪሜ) ርቀት ላይ ይገኛል ፣ ከሱም በእንግሊዝ ቻናል ይለያል ። እ.ኤ.አ. በ 1993 10 በመቶው የዩናይትድ ኪንግደም በደን የተሸፈነ ነበር ። 46 በመቶው ለግጦሽ አገልግሎት የሚውል ሲሆን 25 በመቶው ደግሞ ለግብርና ነው የሚመረተው። በለንደን የሚገኘው ሮያል ግሪንዊች ኦብዘርቫቶሪ በ1884 በዋሽንግተን ዲሲ የጠቅላይ ሜሪዲያን መለያ ነጥብ ሆኖ ተመረጠ። 100 ሜትር ወደ ኦብዘርቫቶሪ በስተምስራቅ. ዩናይትድ ኪንግደም በኬክሮስ 49° እና 61° ፣ እና ኬንትሮስ 9° እና 2° . ሰሜን አየርላንድ ከአየርላንድ ሪፐብሊክ ጋር 224 ማይል (360 ኪሜ) የመሬት ወሰን ትጋራለች። የታላቋ ብሪታንያ የባህር ዳርቻ 11,073 ማይል ነው። (17,820 ኪሜ) ርዝመት. 31 ማይል (50 ኪሜ) (24 ማይል (38 ኪሜ) በውሃ ውስጥ) ላይ ባለው የቻናል ቱነል ከአህጉር አውሮፓ ጋር የተገናኘ ሲሆን በአለም ላይ ካሉት የውሃ ውስጥ ረጅሙ ዋሻ ነው። እንግሊዝ ከጠቅላላው የዩናይትድ ኪንግደም ስፋት ከግማሽ በላይ ብቻ (53 በመቶ) ይሸፍናል፣ ይህም 130,395 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (50,350 ካሬ ማይል) ይሸፍናል። አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል የቆላማ መሬትን ያቀፈ ነው፣ ከ መስመር በስተሰሜን ምዕራብ የበለጠ ደጋማ እና አንዳንድ ተራራማ መሬት ያለው። የሐይቅ አውራጃን፣ ፔኒኒስን፣ ኤክስሞርን እና ዳርትሞርን ጨምሮ። ዋናዎቹ ወንዞች እና ወንዞች ቴምዝ ፣ ሰቨርን እና ሀምበር ናቸው። የእንግሊዝ ከፍተኛው ተራራ በሐይቅ አውራጃ ውስጥ ስካፌል ፓይክ (978 ሜትር (3,209 ጫማ)) ነው። ስኮትላንድ ከጠቅላላው የዩናይትድ ኪንግደም አጠቃላይ ስፋት ከአንድ ሶስተኛ (32 በመቶ) በታች ነው የሚይዘው፣ 78,772 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (30,410 ካሬ ማይል) ይሸፍናል። በተለይም ሄብሪድስ፣ ኦርክኒ ደሴቶች እና ሼትላንድ ደሴቶች። ስኮትላንድ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ በጣም ተራራማ አገር ነች እና የመሬት አቀማመጥ በሃይላንድ ድንበር ጥፋት - የጂኦሎጂካል አለት ስብራት - ስኮትላንድን በምዕራብ ከአራን አቋርጦ በምስራቅ እስቶንሃቨን ይለያል። ስህተቱ ሁለት ልዩ ልዩ ክልሎችን ይለያል; ማለትም በሰሜን እና በምዕራብ በኩል ሀይላንድ እና ዝቅተኛ ቦታዎች በደቡብ እና በምስራቅ. በጣም ወጣ ገባ የሆነው ሃይላንድ ክልል ቤን ኔቪስን ጨምሮ 1,345 ሜትሮች (4,413 ጫማ) በብሪቲሽ ደሴቶች ውስጥ ከፍተኛው ቦታ የሆነውን አብዛኛው የስኮትላንድ ተራራማ መሬት ይይዛል። ቆላማ አካባቢዎች - በተለይም በፈርዝ ክላይድ እና በፈርት ኦፍ ፎርዝ መካከል ያለው ጠባብ የመሬት ወገብ ሴንትራል ቤልት በመባል የሚታወቀው - የስኮትላንድ ትልቁ ከተማ ግላስጎው እና ዋና እና የፖለቲካ ማእከል የሆነችው ኤድንበርግ ጨምሮ የአብዛኛው ህዝብ መኖሪያ ነው። ምንም እንኳን ደጋማ እና ተራራማ መሬት በደቡባዊ አፕላንድ ውስጥ ይገኛል። 20,779 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (8,020 ስኩዌር ማይል) የሚሸፍነው ዌልስ ከጠቅላላው የዩናይትድ ኪንግደም አካባቢ ከአንድ አስረኛ (9 በመቶ) ያነሰ ነው። ዌልስ በአብዛኛው ተራራማ ነው፣ ምንም እንኳን ሳውዝ ዌልስ ከሰሜን እና ከመሃል ዌልስ ያነሰ ተራራማ ነው። ዋናው የህዝብ ብዛት እና የኢንዱስትሪ አካባቢዎች በሳውዝ ዌልስ ውስጥ የሚገኙት የካርዲፍ፣ ስዋንሲ እና ኒውፖርት የባህር ዳርቻ ከተሞችን እና በሰሜን በኩል የደቡብ ዌልስ ሸለቆዎችን ያቀፈ ነው። በዌልስ ውስጥ ከፍተኛዎቹ ተራሮች በስኖዶኒያ ውስጥ ሲሆኑ ስኖውዶን (ዌልሽ፡ ይር ዋይድፋ) በ1,085 ሜትር (3,560 ጫማ) ላይ ያለው፣ በዌልስ ውስጥ ከፍተኛው ጫፍ ነው። ዌልስ ከ2,704 ኪሎ ሜትር በላይ (1,680 ማይል) የባህር ዳርቻ አላት። ብዙ ደሴቶች ከዌልሽ ዋና መሬት ርቀው ይገኛሉ፣ ትልቁ ደሴቶች በሰሜን ምዕራብ የሚገኘው አንግልሴይ (ይኒስ ሞን) ነው። ሰሜን አየርላንድ፣ ከታላቋ ብሪታንያ በአይሪሽ ባህር እና በሰሜን ቻናል የተነጠለች፣ 14,160 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (5,470 ካሬ ማይል) ስፋት ያላት ሲሆን በአብዛኛው ኮረብታ ነው። በ388 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (150 ስኩዌር ማይል) በብሪቲሽ ደሴቶች ውስጥ በአከባቢው ትልቁ ሀይቅ የሆነውን ን ያጠቃልላል። በሰሜን አየርላንድ ከፍተኛው ጫፍ ስሊቭ ዶናርድ በሞርኔ ተራሮች በ852 ሜትር (2,795 ጫማ) ነው። ዩናይትድ ኪንግደም አራት የመሬት አከባቢዎችን ይዟል፡ የሴልቲክ ሰፊ ጫካዎች፣ የእንግሊዝ ዝቅተኛላንድስ የቢች ደኖች፣ የሰሜን አትላንቲክ እርጥበታማ ድብልቅ ደኖች እና የካሌዶን ኮኒፈር ደኖች። አገሪቷ የ2019 የደን መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ኢንቴግሪቲ ኢንዴክስ 1.65/10 አማካይ ነጥብ ነበራት፣ ይህም በአለም ከ172 ሀገራት 161ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። የአየር ንብረት አብዛኛው የዩናይትድ ኪንግደም ሞቃታማ የአየር ንብረት አለው፣ በአጠቃላይ ቀዝቀዝ ያለ የሙቀት መጠን እና ዓመቱን ሙሉ ብዙ ዝናብ። የሙቀት መጠኑ ከ0°) በታች እየቀነሰ ወይም ከ30°) በላይ በሚጨምር ወቅቶች ይለያያል። አንዳንድ ክፍሎች፣ ከባህር ዳርቻ ርቀው፣ ደጋማ እንግሊዝ፣ ዌልስ፣ ሰሜናዊ አየርላንድ እና አብዛኛው ስኮትላንድ፣ የከርሰ ምድር ውቅያኖስ የአየር ንብረት () ያጋጥማቸዋል። በስኮትላንድ ውስጥ ያሉ ከፍታ ቦታዎች አህጉራዊ ንዑስ-አርክቲክ የአየር ንብረት (ዲኤፍሲ) እና ተራሮች የ የአየር ንብረት () ያጋጥማቸዋል። ነፋሱ ከደቡብ ምዕራብ ሲሆን መለስተኛ እና እርጥብ የአየር ሁኔታን ከአትላንቲክ ውቅያኖስ በተደጋጋሚ ይሸከማል፣ ምንም እንኳን የምስራቃዊው ክፍል በአብዛኛው ከዚህ ንፋስ የተከለለ ቢሆንም አብዛኛው ዝናብ በምዕራባዊ ክልሎች ላይ ስለሚወድቅ የምስራቃዊው ክፍል በጣም ደረቅ ነው። በባህረ ሰላጤው ጅረት የሚሞቅ የአትላንቲክ ሞገዶች መለስተኛ ክረምትን ያመጣሉ፤በተለይ በምእራብ ክረምት ክረምት እርጥብ በሆነበት እና በከፍታ ቦታ ላይ። ክረምቱ በደቡብ ምስራቅ እንግሊዝ በጣም ሞቃታማ ሲሆን በሰሜን ደግሞ በጣም ቀዝቃዛ ነው። በከፍታ ቦታ ላይ በክረምት እና በፀደይ መጀመሪያ ላይ ከባድ የበረዶ ዝናብ ሊከሰት ይችላል, እና አልፎ አልፎ ከኮረብታዎች ርቆ ወደ ከፍተኛ ጥልቀት ይሰፍራል. ዩናይትድ ኪንግደም ከ180 ሀገራት 4ቱን በአከባቢ አፈፃፀም መረጃ ደረጃ ላይ ትገኛለች። እ.ኤ.አ. በ2050 የዩናይትድ ኪንግደም በካይ ጋዝ ልቀቶች ዜሮ ዜሮ እንደሚሆን ህግ ወጣ መንግስት እና ፖለቲካ ዩናይትድ ኪንግደም በህገ-መንግስታዊ ንግስና ስር ያለ አሃዳዊ መንግስት ነው። ንግሥት ኤልዛቤት የእንግሊዝ ንጉሠ ነገሥት እና ርዕሰ መስተዳድር፣ እንዲሁም 14 ሌሎች ነፃ አገሮች ናቸው። እነዚህ 15 አገሮች አንዳንድ ጊዜ "የጋራ ግዛቶች" ተብለው ይጠራሉ. ንጉሠ ነገሥቱ "የመመካከር፣ የማበረታታት እና የማስጠንቀቅ መብት" አላቸው። የዩናይትድ ኪንግደም ሕገ መንግሥት ያልተስተካከሉ እና በአብዛኛው የተለያዩ የተፃፉ ምንጮች ስብስቦችን ያቀፈ ነው, እነሱም ደንቦች, ዳኛ ሰጭ የክስ ህግ እና ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከህገመንግስታዊ ስምምነቶች ጋር. የዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ የሕገ-መንግስታዊ ማሻሻያ የፓርላማ ስራዎችን በማፅደቅ ማካሄድ ይችላል, እና ስለዚህ ማንኛውንም የሕገ-መንግስቱን የተፃፈ ወይም ያልተፃፈ ነገር የመቀየር ወይም የመሻር የፖለቲካ ስልጣን አለው. ማንም ተቀምጦ ፓርላማ ወደፊት ፓርላማዎች ሊለወጡ የማይችሉትን ህግ ሊያወጣ አይችልም። ዩናይትድ ኪንግደም የፓርላማ ዲሞክራሲ እና ሕገ መንግሥታዊ ንጉሣዊ አገዛዝ ነች። የእንግሊዝ ፓርላማ ሉዓላዊ ነው። እሱ ከኮመንስ, ከጌቶች ቤት እና ከዘውድ ጋር የተዋቀረ ነው.የፓርላማ ዋና ሥራ የሚከናወነው በሁለቱ ምክር ቤቶች ውስጥ ነው, ነገር ግን ህጉ የፓርላማ ህግ (ህግ) እንዲሆን የንጉሣዊ ፈቃድ ያስፈልጋል. ለጠቅላላ ምርጫ (የጋራ ምክር ቤት ምርጫ)፣ ዩናይትድ ኪንግደም በ650 የምርጫ ክልሎች የተከፋፈለ ሲሆን እያንዳንዱም በፓርላማ አባል () ይወከላል። የፓርላማ አባላት እስከ አምስት አመታት ድረስ ስልጣንን ይይዛሉ እና ሁልጊዜም ለጠቅላላ ምርጫዎች ይወዳደራሉ. የወግ አጥባቂ ፓርቲ፣ የሌበር ፓርቲ እና የስኮትላንድ ብሄራዊ ፓርቲ እንደቅደም ተከተላቸው፣ አሁን ያሉት አንደኛ፣ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ትላልቅ ፓርቲዎች (በፓርላማ አባላት ቁጥር) በኮመንስ ሃውስ ውስጥ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የመንግስት መሪ ናቸው ። ሁሉም ጠቅላይ ሚኒስትሮች ማለት ይቻላል የግምጃ ቤት የመጀመሪያ ጌታ ሆነው አገልግለዋል ሁሉም ጠቅላይ ሚኒስትሮች ከ 1905 ጀምሮ የግምጃ ቤት የመጀመሪያ ጌታ ፣ ከ 1968 ጀምሮ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር እና ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል ። ህብረቱ ከ 2019 ጀምሮ (አውሮፓ). በዘመናችን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በሕገ መንግሥት ኮንቬንሽን፣ የፓርላማ አባል ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚሾሙት በንጉሠ ነገሥቱ ሲሆን ሹመታቸውም በሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎች የሚመራ ነው። ነገር ግን፣ በመደበኛነት በፓርላማው ውስጥ ብዙ መቀመጫዎች ያሉት የፖለቲካ ፓርቲ መሪ ናቸው እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እምነትን በማዘዝ ስልጣንን ይይዛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕግ የተደነገጉ ተግባራት (ከሌሎች ሚኒስትሮች ጋር) ብቻ ሳይሆን የንጉሣዊው ዋና አማካሪ ናቸው እና ንጉሣዊውን ከመንግሥት ጋር በተገናኘ የንጉሣዊ ሥልጣናቸውን ተግባራዊ ለማድረግ ለእነሱ ምክር መስጠት አለባቸው። በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚኒስትሮችን ሹመት እና የካቢኔ ሰብሳቢዎችን ይመራሉ ። የአስተዳደር ክፍሎች የዩናይትድ ኪንግደም ጂኦግራፊያዊ ክፍፍል በካውንቲ ወይም በሺርስ የጀመረው በመካከለኛው ዘመን መጀመሪያ ላይ በእንግሊዝ እና በስኮትላንድ ውስጥ ሲሆን በዘመናዊው ዘመን መጀመሪያ በመላው በታላቋ ብሪታኒያ እና አየርላንድ ተጠናቀቀ። በዩናይትድ ኪንግደም በእያንዳንዱ ሀገር አስተዳደራዊ ዝግጅቶች በተናጥል ተዘጋጅተዋል፣ መነሻቸውም ብዙውን ጊዜ ዩናይትድ ኪንግደም ከመፈጠሩ በፊት ነበር። ዘመናዊ የአካባቢ አስተዳደር በከፊል በጥንታዊ አውራጃዎች ላይ በመመስረት በተመረጡ ምክር ቤቶች ፣ በእንግሊዝ እና በዌልስ በ 1888 ፣ በስኮትላንድ በ 1889 እና በአየርላንድ በ 1898 ሕግ ፣ ይህ ማለት ወጥነት ያለው የአስተዳደር ወይም የጂኦግራፊያዊ አከላለል ስርዓት የለም ማለት ነው ። በመላው ዩናይትድ ኪንግደም. እስከ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በእነዚያ ዝግጅቶች ላይ ትንሽ ለውጥ አልተደረገም ፣ ግን ከዚያ በኋላ የሚና እና የተግባር ለውጥ አለ በእንግሊዝ ውስጥ የአከባቢ መስተዳድር አደረጃጀት ውስብስብ ነው, የተግባሮች ስርጭት እንደ አካባቢያዊ ዝግጅቶች ይለያያል. የእንግሊዝ የላይኛው-ደረጃ ንዑስ ክፍልፋዮች ዘጠኙ ክልሎች ናቸው ፣ አሁን በዋነኝነት ለስታቲስቲክስ ዓላማዎች ያገለግላሉ። አንድ ክልል ታላቋ ለንደን ከ2000 ጀምሮ በቀጥታ የተመረጠ ጉባኤ እና ከንቲባ ነበረው በህዝበ ውሳኔ የቀረበውን ሀሳብ ህዝባዊ ድጋፍ ተከትሎ። ሌሎች ክልሎችም የራሳቸው የተመረጡ የክልል ምክር ቤቶች እንዲሰጡ ታቅዶ ነበር፣ ነገር ግን በሰሜን ምስራቅ ክልል ሊካሄድ የታቀደው ስብሰባ በ2004 በህዝበ ውሳኔ ውድቅ ተደርጓል። ከ2011 ጀምሮ በእንግሊዝ አስር ጥምር ባለስልጣናት ተቋቁመዋል። ከእነዚህ ውስጥ ስምንቱ ከንቲባዎችን መርጠዋል፣ የመጀመሪያው ምርጫ በግንቦት 4 ቀን 2017 ተካሄዷል። ከክልል ደረጃ በታች፣ አንዳንድ የእንግሊዝ ክፍሎች የካውንቲ ምክር ቤቶች እና የአውራጃ ምክር ቤቶች ሲኖራቸው ሌሎች ደግሞ አሃዳዊ ባለስልጣናት ሲኖራቸው ለንደን 32 የለንደን ወረዳዎችን እና ከተማዋን ያቀፈ ነው። የለንደን. የምክር ቤት አባላት የሚመረጡት በአንደኛው-ያለፈው-ፖስት ሥርዓት በነጠላ-አባል ቀጠናዎች ወይም በባለብዙ-አባላት የብዙነት ሥርዓት በብዙ-አባል ቀጠናዎች ውስጥ ነው። ለአካባቢ አስተዳደር ዓላማ፣ ስኮትላንድ በ32 የምክር ቤት አካባቢዎች የተከፋፈለ ሲሆን ይህም በመጠን እና በሕዝብ ብዛት ሰፊ ልዩነት አለው። የግላስጎው፣ የኤድንበርግ፣ አበርዲን እና ዳንዲ ከተሞች የተለያዩ የምክር ቤት አካባቢዎች ናቸው፣ እንደ ሃይላንድ ካውንስል ሁሉ፣ የስኮትላንድን አንድ ሶስተኛ የሚያካትት ግን ከ200,000 በላይ ሰዎች ብቻ። የአካባቢ ምክር ቤቶች በተመረጡ የምክር ቤት አባላት የተዋቀሩ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 1,223; የትርፍ ሰዓት ደመወዝ ይከፈላቸዋል. ምርጫዎች የሚካሄዱት ሶስት ወይም አራት የምክር ቤት አባላትን በሚመርጡ ባለ ብዙ አባላት ባሉበት በአንድ የሚተላለፍ ድምጽ ነው። እያንዳንዱ ምክር ቤት የምክር ቤቱን ስብሰባዎች የሚመራ እና የአከባቢው ዋና መሪ ሆኖ የሚሰራ ፕሮቮስት ወይም ሰብሳቢ ይመርጣል። በዌልስ ውስጥ የአካባቢ አስተዳደር 22 አሃዳዊ ባለስልጣናትን ያቀፈ ነው። ሁሉም አሃዳዊ ባለስልጣናት የሚመሩት በምክር ቤቱ በራሱ በተመረጠ መሪ እና ካቢኔ ነው። እነዚህም የካርዲፍ፣ ስዋንሲ እና ኒውፖርት ከተሞችን ያጠቃልላሉ፣ እነሱም በራሳቸው መብት አሃዳዊ ባለስልጣናት ናቸው። ምርጫዎች በየአራት አመቱ የሚካሄደው በአንደኛ-ያለፈው-ፖስት ስርዓት ነው። በሰሜን አየርላንድ ያለው የአካባቢ አስተዳደር ከ1973 ጀምሮ በ26 የዲስትሪክት ምክር ቤቶች ተደራጅቷል፣ እያንዳንዳቸው በአንድ በሚተላለፍ ድምፅ ተመርጠዋል። ሥልጣናቸው እንደ ቆሻሻ መሰብሰብ፣ ውሾችን መቆጣጠር እና ፓርኮችን እና የመቃብር ቦታዎችን በመንከባከብ ላይ ባሉ አገልግሎቶች ላይ ብቻ የተገደበ ነው። በ 2008 ሥራ አስፈፃሚው 11 አዳዲስ ምክር ቤቶችን ለመፍጠር እና አሁን ያለውን አሰራር ለመተካት በቀረቡት ሀሳቦች ላይ ተስማምቷል የተደራጁ መንግስታት ስኮትላንድ፣ ዌልስ እና ሰሜን አየርላንድ እያንዳንዳቸው የራሳቸው መንግሥት ወይም ሥራ አስፈፃሚ አላቸው፣ በአንደኛ ሚኒስትር የሚመራ (ወይንም በሰሜን አየርላንድ ጉዳይ፣ የዲያስትሪክት የመጀመሪያ ሚኒስትር እና ምክትል ተቀዳሚ ሚኒስትር) እና የተወከለ አንድነት ያለው የሕግ አውጭ አካል። የእንግሊዝ ትልቋ ሀገር የሆነችው እንግሊዝ ምንም አይነት ስልጣን አስፈፃሚ ወይም የህግ አውጭ አካል የላትም እና በሁሉም ጉዳዮች ላይ በቀጥታ በእንግሊዝ መንግስት እና ፓርላማ የምትተዳደረው እና የምትተዳደር ናት። ይህ ሁኔታ ከስኮትላንድ፣ ዌልስ እና ሰሜን አየርላንድ የተውጣጡ የፓርላማ አባላት እንግሊዝን ብቻ በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ አንዳንድ ጊዜ በቆራጥነት ድምጽ መስጠት የሚችሉበትን እውነታ የሚመለከት የምእራብ ሎቲያን ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል። እንግሊዝን ብቻ የሚመለከቱ ህጎች ከአብዛኞቹ የእንግሊዝ የፓርላማ አባላት ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።የስኮትላንድ መንግስት እና ፓርላማ ለዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ በተለየ ሁኔታ ትምህርትን፣ የጤና አጠባበቅን፣ የስኮትላንድ ህግን እና የአካባቢ መንግስትን ጨምሮ በማንኛውም ጉዳይ ላይ ሰፊ ስልጣን አላቸው። በ2020 የዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ ባፀደቀው ድርጊት በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ያላቸው ስልጣን በከፍተኛ ሁኔታ የተገደበ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2012 የእንግሊዝ እና የስኮትላንድ መንግስታት የኤድንበርግ ስምምነትን በ2014 የስኮትላንድ ነፃነት ህዝበ ውሳኔ 55.3 በመቶ የተሸነፈበትን ስምምነት ተፈራርመዋል። ወደ 44.7 በመቶ - በዚህም ምክንያት ስኮትላንድ የዩናይትድ ኪንግደም የተከፋፈለ አካል ሆና እንድትቀር አድርጓልየዌልስ መንግስት እና ሴንድድ (የዌልስ ፓርላማ፤ የቀድሞ የዌልስ ብሔራዊ ምክር ቤት) ወደ ስኮትላንድ ከተሰጡት የበለጠ የተገደበ ሥልጣን አላቸው። ሴኔድ ለዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ በተለየ መልኩ በሌለበት በማንኛውም ጉዳይ በሴኔድ ሳይምሩ የሐዋርያት ሥራ በኩል ሕግ ማውጣት ይችላል። የሰሜን አየርላንድ ስራ አስፈፃሚ እና ምክር ቤት ለስኮትላንድ ከተሰጡት ጋር ተመሳሳይ ስልጣን አላቸው። ሥራ አስፈፃሚው የአንድነት እና የብሔራዊ ምክር ቤት አባላትን በሚወክል ዲያቢሲ ይመራል ። የሰሜን አየርላንድ ዲቮሉሽን በሰሜን አየርላንድ አስተዳደር በሰሜን-ደቡብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውስጥ በሰሜን አየርላንድ አስተዳደር ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ ነው ፣ የሰሜን አየርላንድ ሥራ አስፈፃሚ በመተባበር እና በጋራ እና በጋራ ፖሊሲዎች ያዘጋጃል ። የአየርላንድ መንግስት. የብሪቲሽ እና የአየርላንድ መንግስታት የሰሜን አየርላንድ አስተዳደር በማይሰራበት ጊዜ የሰሜን አየርላንድን ሀላፊነት በሚወስደው በብሪቲሽ-አይሪሽ በይነ መንግስታት ኮንፈረንስ ሰሜን አየርላንድን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ይተባበራሉ።ዩናይትድ ኪንግደም የተቀናጀ ሕገ መንግሥት የላትም እና ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮች ለስኮትላንድ፣ ዌልስ ወይም ሰሜን አየርላንድ ከተሰጡት ሥልጣኖች መካከል አይደሉም። በፓርላማ ሉዓላዊነት አስተምህሮ፣ የዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ በንድፈ ሀሳብ፣ የስኮትላንድ ፓርላማን፣ ሴኔድን ወይም የሰሜን አየርላንድ ጉባኤን ማጥፋት ይችላል። በእርግጥ፣ በ1972፣ የዩኬ ፓርላማ የሰሜን አየርላንድ ፓርላማን በአንድ ወገን መራመዱ፣ ይህም ለወቅታዊው ከስልጣን ተቋማት ጋር ተዛማጅነት ያለው ምሳሌ ነው። በተግባር፣ በሪፈረንደም ውሳኔዎች የተፈጠረውን የፖለቲካ መሠረተቢስነት ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ ለስኮትላንድ ፓርላማ እና ለሴኔድ ውክልና መስጠትን መሰረዝ በፖለቲካ ረገድ ከባድ ነው። በሰሜን አየርላንድ ያለው የስልጣን ክፍፍል ከአየርላንድ መንግስት ጋር በተደረገው አለም አቀፍ ስምምነት ላይ የተመሰረተ በመሆኑ በዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ በሰሜን አየርላንድ የስልጣን ክፍፍልን ለማደናቀፍ በዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ ላይ የሚኖረው ፖለቲካዊ ገደብ ከስኮትላንድ እና ዌልስ ጋር ካለው ግንኙነት የበለጠ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2020 በፀደቀው ሕግ የፓርላማዎችን የሕግ አውጭ ብቃት በኢኮኖሚ መስክ አሳልፏል ዩናይትድ ኪንግደም የዩናይትድ ኪንግደም እራሷ አካል ያልሆኑ በ17 ግዛቶች ላይ ሉዓላዊነት አላት፡ 14 የብሪቲሽ የባህር ማዶ ግዛቶች እና ሶስት የዘውድ ጥገኞች። 14ቱ የብሪቲሽ የባህር ማዶ ግዛቶች የብሪቲሽ ኢምፓየር ቅሪቶች ናቸው፡ አንጉዪላ; ቤርሙዳ; የብሪቲሽ አንታርክቲክ ግዛት; የብሪቲሽ ህንድ ውቅያኖስ ግዛት; የብሪቲሽ ቨርጂን ደሴቶች; የካይማን ደሴቶች; የፎክላንድ ደሴቶች; ጊብራልታር; ሞንትሴራት; ሴንት ሄለና, ዕርገት እና ትሪስታን ዳ ኩንሃ; የቱርኮች እና የካይኮስ ደሴቶች; የፒትካይርን ደሴቶች; ደቡብ ጆርጂያ እና ደቡብ ሳንድዊች ደሴቶች; እና አክሮቲሪ እና ዴኬሊያ በቆጵሮስ ደሴት ላይ። የብሪታንያ የይገባኛል ጥያቄ በአንታርክቲካ ዓለም አቀፍ እውቅና የተገደበ ነው። በአጠቃላይ የብሪታንያ የባህር ማዶ ግዛቶች 480,000 ስኩዌር ናቲካል ማይል (640,000 ስኩዌር ማይልስ፣ 1,600,000 ኪ.ሜ.2) የሚሸፍን ሲሆን በአጠቃላይ ወደ 250,000 የሚጠጋ ህዝብ ያለው። የባህር ማዶ ግዛቶች 6,805,586 ኪ.ሜ (2,627,651 ስኩዌር ማይል) ላይ በአለም አምስተኛው ትልቁን ብቸኛ የኢኮኖሚ ዞን ሰጥተውታል። የ1999 የዩናይትድ ኪንግደም መንግስት ነጭ ወረቀት እንዲህ ይላል፡ "[ ብሪቲሽ ሆነው ለመቀጠል እስከፈለጉ ድረስ ብሪቲሽ ናቸው። ብሪታንያ ነፃነቷን በተጠየቀችበት ቦታ በፈቃደኝነት ሰጥታለች ፣ እናም ይህ አማራጭ ከሆነ ይህንን ማድረጋችንን እንቀጥላለን። የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት በበርካታ የባህር ማዶ ግዛቶች ሕገ-መንግስቶች የተደነገገ ሲሆን ሦስቱ በተለይ በብሪታንያ ሉዓላዊነት (ቤርሙዳ በ1995፣ ጊብራልታር በ2002 እና በፎክላንድ ደሴቶች 2013) ስር እንዲቆዩ ድምጽ ሰጥተዋል። የዘውድ ጥገኞች ከእንግሊዝ የባህር ማዶ ግዛቶች በተቃራኒ የዘውዱ ንብረቶች ናቸው። በገለልተኛነት የሚተዳደሩ ሶስት ስልጣኖችን ያቀፉ፡ የጀርሲ ቻናል ደሴቶች እና በእንግሊዝ ቻናል ውስጥ ጉርንሴይ እና በአይሪሽ ባህር ውስጥ የሰው ደሴት። በጋራ ስምምነት፣ የእንግሊዝ መንግስት የደሴቶቹን የውጭ ጉዳይ እና መከላከያ ያስተዳድራል እና የዩኬ ፓርላማ እነርሱን ወክሎ ህግ የማውጣት ስልጣን አለው። በአለምአቀፍ ደረጃ፣ እንደ “ዩናይትድ ኪንግደም ተጠያቂ የሆነችባቸው ክልሎች” ተደርገው ይወሰዳሉ። ደሴቶቹን የሚመለከቱ ህግ የማውጣት ስልጣን በመጨረሻ በየራሳቸው የህግ አውጭ ስብሰባዎች ላይ የተመሰረተ ነው፣ በዘውዱ ፍቃድ (የግላዊነት ምክር ቤት ወይም በጉዳዩ ላይ የሰው ደሴት፣ በአንዳንድ ሁኔታዎች ሌተና ገዥው)። እ.ኤ.አ. ከ2005 ጀምሮ እያንዳንዱ የዘውድ ጥገኝነት ዋና ሚኒስትር የመንግስት መሪ ሆኖ ቆይቷል ህግ እና የወንጀል ፍትህ የ1706 የኅብረት ስምምነት አንቀጽ 19 የስኮትላንድ የተለየ የሕግ ሥርዓት እንዲቀጥል እንደደነገገው ዩናይትድ ኪንግደም አንድም የሕግ ሥርዓት የላትም። ዛሬ ዩናይትድ ኪንግደም ሶስት የተለያዩ የህግ ሥርዓቶች አሏት፡ የእንግሊዝ ህግ፣ የሰሜን አየርላንድ ህግ እና የስኮትስ ህግ። በጥቅምት 2009 የጌቶች ምክር ቤት ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴን ለመተካት አዲስ የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተፈጠረ። የፕራይቪ ካውንስል ዳኞች ኮሚቴ፣ ከጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር ተመሳሳይ አባላትን ጨምሮ፣ የበርካታ ነጻ የኮመንዌልዝ ሀገራት፣ የብሪቲሽ የባህር ማዶ ግዛቶች እና የዘውድ ጥገኞች ከፍተኛው የይግባኝ ፍርድ ቤት ነው።በእንግሊዝ እና በዌልስ ውስጥ የሚሰራው ሁለቱም የእንግሊዝ ህግ እና የሰሜን አየርላንድ ህግ በጋራ ህግ መርሆዎች ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የጋራ ሕግ ፍሬ ነገር በሕገ-ደንብ መሠረት ሕጉ በፍርድ ቤት ዳኞች ተዘጋጅቷል ፣ ሕግን ፣ ቅድመ ሁኔታን እና ምክንያታዊ ዕውቀትን በፊታቸው ያሉትን እውነታዎች በመተግበር ለወደፊቱ ሪፖርት የሚደረጉ እና አስገዳጅ የሕግ መርሆዎችን አግባብነት ያላቸውን የሕግ መርሆዎች የማብራሪያ ፍርዶች መስጠቱ ነው። ተመሳሳይ ጉዳዮች () .የእንግሊዝ እና የዌልስ ፍርድ ቤቶች በእንግሊዝ እና ዌልስ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የሚመሩ ናቸው, የይግባኝ ፍርድ ቤት, የፍትህ ከፍተኛ ፍርድ ቤት (የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች) እና የዘውድ ፍርድ ቤት (የወንጀል ጉዳዮች) ያካተቱ ናቸው.ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእንግሊዝ፣ በዌልስ እና በሰሜን አየርላንድ ለሁለቱም የወንጀል እና የፍትሐ ብሔር ይግባኝ ጉዳዮች በምድሪቱ ውስጥ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ነው እናም የሚወስነው ማንኛውም ውሳኔ በተመሳሳይ ችሎት ውስጥ ባሉ ሌሎች ፍርድ ቤቶች ላይ አስገዳጅ ነው፣ ብዙ ጊዜ በሌሎች ስልጣኖች ውስጥ አሳማኝ ተጽእኖ ይኖረዋል። የስኮትስ ህግ በሁለቱም የጋራ ህግ እና በሲቪል ህግ መርሆዎች ላይ የተመሰረተ ድቅል ስርዓት ነው። ዋና ፍርድ ቤቶች የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች እና የወንጀል ጉዳዮች ከፍተኛ ፍርድ ቤት የክፍለ ጊዜ ፍርድ ቤት ናቸው. የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ፍርድ ቤት በስኮትስ ህግ መሰረት ለፍትሐ ብሔር ጉዳዮች ከፍተኛው የይግባኝ ፍርድ ቤት ሆኖ ያገለግላል። የሸሪፍ ፍርድ ቤቶች ከአብዛኛዎቹ የሲቪል እና የወንጀል ጉዳዮች ጋር የወንጀል ችሎቶችን ከዳኞች ጋር፣ የሸሪፍ ልዩ ፍርድ ቤት በመባል የሚታወቁትን፣ ወይም ከሸሪፍ እና ከዳኞች ጋር፣ የሸሪፍ ማጠቃለያ ፍርድ ቤት በመባል የሚታወቁትን ጨምሮ ይመለከታል። የስኮትላንድ የህግ ስርዓት ለወንጀል ችሎት ሶስት ሊሆኑ የሚችሉ ብይን ሲኖረው ልዩ ነው፡ "ጥፋተኛ ያልሆነ" እና "ያልተረጋገጠ"። ሁለቱም “ጥፋተኛ አይደሉም” እና “ያልተረጋገጠ” ጥፋተኛ አይደሉም። በእንግሊዝ እና በዌልስ በ 1981 እና 1995 መካከል ባለው ጊዜ ውስጥ ጨምሯል ፣ ምንም እንኳን ከዚያ ከፍተኛ ደረጃ ጀምሮ ከ 1995 እስከ 2015 በተመዘገበው የወንጀል አጠቃላይ የ 66 በመቶ ውድቀት ታይቷል ፣ እንደ የወንጀል ስታቲስቲክስ። የእንግሊዝ እና የዌልስ ወህኒ ቤቶች ቁጥር ወደ 86,000 ከፍ ብሏል ይህም በምዕራብ አውሮፓ እንግሊዝ እና ዌልስ ከ100,000 ሰዎች 148 እስራት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሰዋል። ለፍትህ ሚኒስቴር ሪፖርት የሚያደርገው የግርማዊቷ ወህኒ ቤት አገልግሎት በእንግሊዝ እና በዌልስ ውስጥ የሚገኙትን አብዛኛዎቹን እስር ቤቶች ያስተዳድራል። በእንግሊዝ እና በዌልስ ያለው የግድያ መጠን በ2010ዎቹ የመጀመሪያ አጋማሽ መረጋጋት ችሏል ከ100,000 1 ሰው ግድያ ሲሆን ይህም በ2002 ከፍተኛው ግማሹ ነው እና በ1980ዎቹ በስኮትላንድ የተፈጸመው ወንጀል በ2014–2015 በመጠኑ ቀንሷል። በ 39 ዓመታት ውስጥ ዝቅተኛው ደረጃ በ 59 ግድያዎች ከ 100,000 1.1 ግድያ ጋር። የስኮትላንድ እስር ቤቶች ተጨናንቀዋል ነገር ግን የእስር ቤቱ ቁጥር እየቀነሰ ነው። የውጭ ግንኙነት እንግሊዝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባል፣ የኔቶ አባል፣ ፣ የኮመንዌልዝ ኦፍ ኔሽን፣ የ 7 የገንዘብ ሚኒስትሮች፣ የ7 ፎረም፣ 20፣ ፣ ፣ የአውሮፓ ምክር ቤት እና ነች። ዩናይትድ ኪንግደም ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር "ልዩ ግንኙነት" እና ከፈረንሳይ - "ኢንቴቴ ኮርዲያል" ጋር የቅርብ አጋርነት እንዳላት ይነገራል - እና የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ቴክኖሎጂን ከሁለቱም ሀገራት ጋር ትጋራለች; የአንግሎ-ፖርቱጋል ህብረት በዓለም ላይ እጅግ ጥንታዊው አስገዳጅ ወታደራዊ ትብብር ተደርጎ ይቆጠራል። ዩናይትድ ኪንግደም ከአየርላንድ ሪፐብሊክ ጋር በቅርበት የተሳሰረ ነው; ሁለቱ ሀገራት የጋራ የጉዞ አካባቢን በመጋራት በብሪቲሽ-አይሪሽ በይነ መንግስታት ኮንፈረንስ እና በብሪቲሽ-አይሪሽ ካውንስል በኩል ትብብር ያደርጋሉ። የብሪታንያ ዓለም አቀፋዊ ህላዌ እና ተፅእኖ የበለጠ እየጨመረ የሚሄደው በንግድ ግንኙነቷ፣ በውጭ ኢንቨስትመንቶች፣ በይፋ የልማት ዕርዳታ እና በወታደራዊ ተሳትፎ ነው። ካናዳ፣ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ፣ ሁሉም የቀድሞ የብሪቲሽ ኢምፓየር ቅኝ ገዥዎች ሲሆኑ፣ ንግሥት ኤልዛቤት ን እንደ ርዕሰ መስተዳድር የሚጋሩት፣ በብሪታንያ ሕዝብ ዘንድ በዓለም ላይ በጣም የሚወደዱ አገሮች ናቸው። የግርማዊቷ ጦር ኃይሎች ሶስት የባለሙያ አገልግሎት ቅርንጫፎችን ያቀፈ ነው-የሮያል ባህር ኃይል እና ሮያል ማሪን (የባህር ኃይል አገልግሎትን ይመሰርታሉ) ፣ የብሪቲሽ ጦር እና የሮያል አየር ሀይል ። የዩናይትድ ኪንግደም ጦር ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር የሚተዳደሩ እና የሚቆጣጠሩት የመከላከያ ካውንስል, በመከላከያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሚመራ. ዋና አዛዡ የብሪታኒያ ንጉሠ ነገሥት ነው, የሠራዊቱ አባላት የታማኝነት ቃለ መሃላ የፈጸሙበት. የጦር ኃይሎች ዩናይትድ ኪንግደምን እና የባህር ማዶ ግዛቶቿን በመጠበቅ፣ የዩናይትድ ኪንግደም ዓለም አቀፍ የጸጥታ ጥቅሞችን በማስተዋወቅ እና ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ጥረቶችን በመደገፍ ተከሷል። የ የተባበሩት ፈጣን ምላሽ ጓድአምስት የኃይል መከላከያ ዝግጅቶች, እና ሌሎች የአለም አቀፍ ጥምረት ስራዎችን ጨምሮ በኔቶ ውስጥ ንቁ እና መደበኛ ተሳታፊዎች ናቸው. የባህር ማዶ ሰፈሮች እና መገልገያዎች በአሴንሽን ደሴት፣ ባህሬን፣ ቤሊዝ፣ ብሩኔይ፣ ካናዳ፣ ቆጵሮስ፣ ዲዬጎ ጋርሺያ፣ የፎክላንድ ደሴቶች፣ ጀርመን፣ ጊብራልታር፣ ኬንያ፣ ኦማን፣ ኳታር እና ሲንጋፖር ይገኛሉ። በ18ኛው፣ በ19ኛው እና በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የብሪቲሽ ኢምፓየር አውራ የዓለም ኃያል መንግሥት እንዲሆን የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። ከግጭቶች አሸናፊ በመሆን ብሪታንያ ብዙውን ጊዜ በዓለም ክስተቶች ላይ በቆራጥነት ተጽዕኖ ማሳደር ችላለች። ከብሪቲሽ ኢምፓየር መጨረሻ ጀምሮ ዩናይትድ ኪንግደም ዋና ወታደራዊ ሃይል ሆና ቆይታለች። የቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት ተከትሎ፣ የመከላከያ ፖሊሲ እንደ አንድ ጥምር አካል “በጣም የሚጠይቁ ተግባራት” እንደሚካሄድ ግምቱን አስቀምጧል። የስቶክሆልም ዓለም አቀፍ የሰላም ምርምር ኢንስቲትዩት እና ዓለም አቀፍ የስትራቴጂ ጥናት ተቋምን ጨምሮ ምንጮች እንደሚሉት፣ ዩናይትድ ኪንግደም አራተኛው ወይም አምስተኛው ከፍተኛ ወታደራዊ ወጪ አላት። አጠቃላይ የመከላከያ ወጪ ከብሔራዊ የሀገር ውስጥ ምርት ውስጥ 2.0 በመቶ ይደርሳል ዩናይትድ ኪንግደም በከፊል ቁጥጥር የሚደረግበት የገበያ ኢኮኖሚ አላት። በገበያ ምንዛሪ ተመኖች ላይ በመመስረት፣ እንግሊዝ ዛሬ በዓለም አምስተኛዋ ኢኮኖሚ እና በአውሮፓ ከጀርመን ቀጥላ ሁለተኛዋ ናት። ኤች ኤም ግምጃ ቤት፣ በቻንስለር ኦፍ ኤክስቼከር የሚመራ፣ የመንግስትን የህዝብ ፋይናንስ ፖሊሲ እና የኢኮኖሚ ፖሊሲን የማዘጋጀት እና የማስፈፀም ሃላፊነት አለበት። የእንግሊዝ ባንክ የዩናይትድ ኪንግደም ማዕከላዊ ባንክ ሲሆን በሀገሪቱ ምንዛሪ ፓውንድ ስተርሊንግ ኖቶች እና ሳንቲሞች የማውጣት ሃላፊነት አለበት። በስኮትላንድ እና በሰሜን አየርላንድ ያሉ ባንኮች ጉዳያቸውን ለመሸፈን በቂ የእንግሊዝ ባንክ ኖቶች እንዲቆዩ በማድረግ የራሳቸውን ማስታወሻ የማውጣት መብት አላቸው። ፓውንድ ስተርሊንግ በዓለም አራተኛው ትልቁ የመጠባበቂያ ገንዘብ ነው (ከአሜሪካ ዶላር፣ ዩሮ እና የጃፓን የን በኋላ)።ከ1997 ጀምሮ በእንግሊዝ ባንክ ገዥ የሚመራ የእንግሊዝ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ​​ኮሚቴ ወለድ የማዘጋጀት ኃላፊነት ነበረበት። በየአመቱ በቻንስለር የተቀመጠውን አጠቃላይ የኢኮኖሚ ግሽበት ግብ ለማሳካት አስፈላጊ በሆነው ደረጃ ተመኖች። የዩናይትድ ኪንግደም የአገልግሎት ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 79 ከመቶ ያህሉን ይይዛል። ለንደን ከአለም ትልቁ የፋይናንሺያል ማእከላት አንዷ ነች፣ በአለም 2ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፣ ከኒውዮርክ ከተማ በመቀጠል፣ በአለምአቀፍ የፋይናንሺያል ማእከላት ማውጫ በ2020። በአውሮፓ. በ2020 ኤዲንብራ በአለም 17ኛ፣ እና በምዕራብ አውሮፓ 6ኛ ደረጃ ላይ በግሎባል የፋይናንሺያል ማእከላት መረጃ ጠቋሚ በ2020። ቱሪዝም ለብሪቲሽ ኢኮኖሚ በጣም አስፈላጊ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2004 ከ 27 ሚሊዮን በላይ ቱሪስቶች የገቡት ፣ ዩናይትድ ኪንግደም በዓለም ላይ ስድስተኛ ዋና የቱሪስት መዳረሻ ሆና ትገኛለች እና ለንደን በዓለም ላይ ካሉ ከማንኛውም ከተማዎች የበለጠ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አላት። በ 1997 እና 2005 መካከል በአማካይ 6 በመቶ በዓመት. ዩናይትድ ኪንግደም ከአውሮፓ ህብረት መውጣቷን ተከትሎ፣ የዩናይትድ ኪንግደም የውስጥ ኢኮኖሚ ገበያ ተግባር በዩናይትድ ኪንግደም የውስጥ ገበያ ህግ 2020 የተደነገገ ሲሆን ይህም የሸቀጦች እና አገልግሎቶች ንግድ በዩናይትድ ኪንግደም አራት ሀገራት ውስጥ ያለ ውስጣዊ እንቅፋት መቀጠሉን ያረጋግጣል ።የኢንዱስትሪ አብዮት በዩኬ ውስጥ የጀመረው በጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ላይ ትኩረት በመስጠት ነው ፣ ከዚያም እንደ የመርከብ ግንባታ ፣ የድንጋይ ከሰል ማዕድን ማውጣት እና ብረት ማምረቻዎች ያሉ ሌሎች ከባድ ኢንዱስትሪዎች ተከትለዋል ። የብሪታንያ ነጋዴዎች ፣ ላኪዎች እና የባንክ ባለሙያዎች ዩናይትድ ኪንግደም በዓለም አቀፍ ደረጃ የበላይ እንድትሆን በሚያስችላቸው ከሌሎች ብሔሮች የላቀ ጥቅም አዳብሯል። በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ንግድ. ሌሎች አገሮች በኢንዱስትሪ ሲበለጽጉ፣ ከሁለት የዓለም ጦርነቶች በኋላ ከኢኮኖሚ ውድቀት ጋር ተዳምሮ፣ ዩናይትድ ኪንግደም የፉክክር ጥቅሟን ማጣት ጀመረች እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በሙሉ ከባድ ኢንዱስትሪ በዲግሪ እያሽቆለቆለ ነበር። ማኑፋክቸሪንግ የኢኮኖሚው ወሳኝ አካል ቢሆንም በ2003 ከብሔራዊ ምርት 16.7 በመቶውን ብቻ ይይዛል።የአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው ወደ 800,000 የሚጠጉ ሰዎችን የሚቀጥር ሲሆን በ2015 በ70 ቢሊዮን ፓውንድ ገቢ 34.6 ቢሊዮን ፓውንድ (ከዩናይትድ ኪንግደም አጠቃላይ የወጪ ንግድ ዕቃዎች 11.8 በመቶ) አስገኝቷል። እ.ኤ.አ. በ 2015 እንግሊዝ ወደ 1.6 ሚሊዮን የመንገደኞች ተሽከርካሪዎች እና 94,500 የንግድ ተሽከርካሪዎችን አምርታለች። ዩናይትድ ኪንግደም ለኤንጂን ማምረቻ ዋና ማዕከል ናት፡ በ2015 ወደ 2.4 ሚሊዮን የሚጠጉ ሞተሮች ተመርተዋል። የዩናይትድ ኪንግደም የሞተር ስፖርት ኢንዱስትሪ ወደ 41,000 የሚጠጉ ሰዎችን ይቀጥራል፣ ወደ 4,500 የሚጠጉ ኩባንያዎችን ያቀፈ እና ዓመታዊ ገቢ ወደ 6 ቢሊዮን ፓውንድ ይደርሳል። የዩናይትድ ኪንግደም የኤሮስፔስ ኢንደስትሪ በአለም ላይ ሁለተኛው ወይም ሶስተኛው ትልቁ ብሄራዊ የኤሮስፔስ ኢንደስትሪ ነው እንደ የመለኪያ ዘዴ እና አመታዊ ትርፋማ 30 ቢሊዮን ፓውንድ አለው ሲስተምስ በአንዳንድ የአለም ታላላቅ የመከላከያ ኤሮስፔስ ፕሮጀክቶች ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በዩኬ ውስጥ ኩባንያው የታይፎን ዩሮ ተዋጊ ትላልቅ ክፍሎችን ይሠራል እና አውሮፕላኑን ለሮያል አየር ኃይል ይሰበስባል። እንዲሁም በ ላይ ዋና ንዑስ ተቋራጭ ነው -የአለም ትልቁ ነጠላ የመከላከያ ፕሮጄክት - የተለያዩ አካላትን እየነደፈ። በተጨማሪም ሃውክ የተባለውን የአለማችን በጣም ስኬታማ የሆነውን የጄት ማሰልጠኛ አውሮፕላኖችን ያመርታል። ኤርባስ ዩኬ ደግሞ ለኤ 400 ሜትር ወታደራዊ ማጓጓዣ ክንፉን ያመርታል። ሮልስ ሮይስ የዓለማችን ሁለተኛው ትልቁ የኤሮ-ሞተር አምራች ነው። የእሱ ሞተሮች ከ 30 በላይ የንግድ አውሮፕላኖችን ያመነጫሉ እና ከ 30,000 በላይ ሞተሮችን በሲቪል እና በመከላከያ ዘርፎች ውስጥ ያገለግላሉ ። የዩናይትድ ኪንግደም የጠፈር ኢንዱስትሪ በ2011 £9.1 እና 29,000 ሰዎችን ቀጥሯል። እንደ ጃንጥላ ድርጅቱ የዩኬ የጠፈር ኤጀንሲ እንደገለጸው በየዓመቱ በ7.5 በመቶ እያደገ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2013 የብሪታንያ መንግስት ለስካይሎን ፕሮጀክት 60 ሚ. የመድኃኒት ኢንዱስትሪው በዩኬ ኢኮኖሚ ውስጥ ትልቅ ሚና የሚጫወት ሲሆን ሀገሪቱ ከዓለም አቀፍ የመድኃኒት ወጪዎች ሦስተኛው ከፍተኛ ድርሻ አላት። ግብርናው የተጠናከረ፣ በከፍተኛ ሜካናይዜድ እና በአውሮፓ ደረጃዎች ቀልጣፋ ሲሆን 60 በመቶ የሚሆነውን የምግብ ፍላጎት ከ1.6 በመቶ ያነሰ የሰው ኃይል (535,000 ሠራተኞች) በማምረት ነው። ሁለት ሦስተኛው የሚሆነው ምርት ለከብቶች፣ አንድ ሦስተኛው ለእርሻ ሰብሎች ይውላል። ምንም እንኳን በጣም የቀነሰ የአሳ ማጥመድ ኢንዱስትሪ ዩናይትድ ኪንግደም ጉልህ ስፍራን ይይዛል። በተጨማሪም የድንጋይ ከሰል፣ፔትሮሊየም፣ የተፈጥሮ ጋዝ፣ ቆርቆሮ፣ የኖራ ድንጋይ፣ የብረት ማዕድን፣ ጨው፣ ሸክላ፣ ኖራ፣ ጂፕሰም፣ እርሳስ፣ ሲሊካ እና የተትረፈረፈ የሚታረስ መሬትን ጨምሮ በተለያዩ የተፈጥሮ ሃብቶች የበለፀገ ነው።እ.ኤ.አ. በ 2020 የኮሮና ቫይረስ መቆለፊያ እርምጃዎች የዩኬ ኢኮኖሚ በተመዘገበው ትልቁ ውድቀት በሚያዝያ እና ሰኔ መካከል በ 20.4 በመቶ በዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ጋር ሲነፃፀር በ 20.4 በመቶ ቀንሷል ፣ ይህም በይፋ በ 11 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ውድቀት እንዲገባ አድርጓታል ። . ዩናይትድ ኪንግደም 9.6 ትሪሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ አለባት፣ ይህም ከአሜሪካ ቀጥላ በአለም ሁለተኛዋ ነው። እንደ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት መጠን የውጭ ዕዳ 408 በመቶ ሲሆን ይህም ከሉክሰምበርግ እና አይስላንድ ቀጥሎ በሦስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። የሳይንስ እና የቴክኖሎጂ እድገት እንግሊዝ እና ስኮትላንድ ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የሳይንሳዊ አብዮት ማዕከላት ግንባር ቀደም ነበሩ። ዩናይትድ ኪንግደም ከ 18 ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የኢንዱስትሪ አብዮትን መርታለች, እና ጠቃሚ እድገቶች የተመሰከረላቸው ሳይንቲስቶች እና መሐንዲሶችን ማፍራቷን ቀጥላለች. የ17ኛው እና 18ኛው ክፍለ ዘመን ዋና ንድፈ ሃሳቦች የእንቅስቃሴ እና የስበት ብርሃን ህግጋት የዘመናዊ ሳይንስ ቁልፍ ድንጋይ ሆነው ይታዩ የነበሩት አይዛክ ኒውተን ይገኙበታል። ከ19ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በተፈጥሮ ምርጫ የዝግመተ ለውጥ ንድፈ ሃሳብ ለዘመናዊ ባዮሎጂ እድገት መሰረታዊ የሆነው ቻርለስ ዳርዊን እና ክላሲካል ኤሌክትሮማግኔቲክ ቲዎሪ የፈጠረው ጄምስ ክለርክ ማክስዌል፤ እና በቅርብ ጊዜ በኮስሞሎጂ, በኳንተም ስበት እና በጥቁር ጉድጓዶች ምርመራ ውስጥ ዋና ዋና ንድፈ ሐሳቦችን ያዳበረው ስቴፈን ሃውኪንግ.ከ 18 ኛው ክፍለ ዘመን ዋና ዋና ሳይንሳዊ ግኝቶች በሄንሪ ካቨንዲሽ ሃይድሮጅን ያካትታሉ; ከ 20 ኛው ክፍለ ዘመን ፔኒሲሊን በአሌክሳንደር ፍሌሚንግ, እና የዲኤንኤ መዋቅር, በፍራንሲስ ክሪክ እና ሌሎች. ታዋቂ የእንግሊዝ መሐንዲሶች እና የኢንዱስትሪ አብዮት ፈጣሪዎች ጄምስ ዋት፣ ጆርጅ እስጢፋኖስ፣ ሪቻርድ አርክራይት፣ ሮበርት እስጢፋኖስ እና ኢሳባርድ ኪንግደም ብሩነል ያካትታሉ። ከእንግሊዝ የመጡ ሌሎች ዋና ዋና የምህንድስና ፕሮጀክቶች እና አፕሊኬሽኖች በሪቻርድ ትሬቪቲክ እና አንድሪው ቪቪያን የተሰራውን የእንፋሎት ሎኮሞቲቭን ያካትታሉ።ከ19ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ኤሌክትሪክ ሞተር በሚካኤል ፋራዳይ፣በቻርልስ ባባጅ የተነደፈው የመጀመሪያው ኮምፒውተር፣የመጀመሪያው የንግድ ኤሌክትሪክ ቴሌግራፍ በ ዊልያም ፎዘርጊል ኩክ እና ቻርለስ ዊትስቶን በጆሴፍ ስዋን የበራ አምፖል እና የመጀመሪያው ተግባራዊ ስልክ በአሌክሳንደር ግራሃም ቤል የፈጠራ ባለቤትነት; እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በአለም የመጀመሪያው የሚሰራው የቴሌቭዥን ስርዓት በጆን ሎጊ ቤርድ እና ሌሎች፣ የጄት ሞተር በፍራንክ ዊትል፣ የዘመናዊው ኮምፒዩተር መሰረት የሆነው በአላን ቱሪንግ እና የአለም አቀፍ ድር በቲም በርነርስ ሊ። ሳይንሳዊ ምርምር እና ልማት በብሪቲሽ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስፈላጊ ሆኖ ይቆያል፣ ብዙዎቹ የሳይንስ ፓርኮችን በማቋቋም ምርትን እና ከኢንዱስትሪ ጋር መተባበርን ያመቻቻሉ። እ.ኤ.አ. በ 2004 እና 2008 መካከል ዩናይትድ ኪንግደም 7 በመቶውን የአለም ሳይንሳዊ የምርምር ወረቀቶችን አዘጋጅታለች እና 8 በመቶ የሳይንሳዊ ጥቅሶች ድርሻ ነበራት ፣ ይህም በዓለም ላይ ሶስተኛ እና ሁለተኛ ደረጃ (ከአሜሪካ እና ከቻይና ፣ በቅደም ተከተል)። በዩኬ ውስጥ የሚዘጋጁ ሳይንሳዊ መጽሔቶች ተፈጥሮ፣ ብሪቲሽ ሜዲካል ጆርናል እና ላንሴት ይገኙበታል። ዩናይትድ ኪንግደም እ.ኤ.አ. በ2020 እና 2021 በአለምአቀፍ ኢኖቬሽን ኢንዴክስ 4ኛ ሆናለች፣ በ2019 ከ5ኛ ደረጃ እ.ኤ.አ. በ 2006 ዩናይትድ ኪንግደም በዓለም ዘጠነኛዋ ትልቁ የኃይል ፍጆታ እና 15 ኛ-ትልቁ አምራች ነበረች። ዩናይትድ ኪንግደም የበርካታ ትላልቅ የኢነርጂ ኩባንያዎች መኖሪያ ነች፣ ከእነዚህም ውስጥ ሁለቱን ከስድስት ዘይት እና ጋዝ "ሱፐርሜጆሮች" - ቢፒ እና ሼል ጋር። እ.ኤ.አ. በ 2013 ዩናይትድ ኪንግደም በቀን 914 ሺህ በርሜል (ቢቢሊ / ዲ) ዘይት በማምረት 1,507 ሺህ በላ። ምርቱ አሁን እያሽቆለቆለ ነው እና ዩናይትድ ኪንግደም ከ 2005 ጀምሮ የተጣራ ዘይት አስመጪ ነች። በ2010 እንግሊዝ 3.1 ቢሊዮን በርሜል የተረጋገጠ የድፍድፍ ዘይት ክምችት ነበራት ይህም ከማንኛውም የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ትልቁ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2009 ዩናይትድ ኪንግደም በዓለም ላይ 13 ኛ-ትልቁ የተፈጥሮ ጋዝ አምራች እና በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ትልቁ አምራች ነበረች። ምርት አሁን እያሽቆለቆለ ነው እና ዩናይትድ ኪንግደም ከ 2004 ጀምሮ የተፈጥሮ ጋዝ የተጣራ አስመጪ ነች። በ 19 ኛው እና በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን የድንጋይ ከሰል ማምረት በዩኬ ኢኮኖሚ ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል. እ.ኤ.አ. በ 1970 ዎቹ አጋማሽ 130 ሚሊዮን ቶን የድንጋይ ከሰል ይመረት ነበር ፣ እስከ 1980 ዎቹ መጀመሪያ ድረስ ከ 100 ሚሊዮን ቶን በታች አልወደቀም። እ.ኤ.አ. በ1980ዎቹ እና 1990ዎቹ ውስጥ ኢንዱስትሪው በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ኋላ ተመልሷል። እ.ኤ.አ. በ2011 እንግሊዝ 18.3 ሚሊዮን ቶን የድንጋይ ከሰል አምርታለች። እ.ኤ.አ. በ 2005 የተረጋገጠ 171 ሚሊዮን ቶን የድንጋይ ከሰል ክምችት ተገኝቷል። የዩናይትድ ኪንግደም የድንጋይ ከሰል ባለስልጣን ከ 7 ቢሊዮን ቶን እስከ 16 ቢሊዮን ቶን የድንጋይ ከሰል በከርሰ ምድር ውስጥ በከሰል ጋዝ ማምረቻ () ወይም 'ፍራኪንግ' የማምረት አቅም እንዳለ ገልጿል, እና አሁን ባለው የዩኬ የድንጋይ ከሰል ፍጆታ ላይ በመመስረት, እንዲህ ዓይነቱ ክምችት በ 200 መካከል ሊቆይ ይችላል. እና 400 ዓመታት. ኬሚካሎች ወደ ውሃ ወለል ውስጥ መግባታቸው እና አነስተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ቤቶችን ስለሚጎዱ የአካባቢ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ተነስተዋል። እ.ኤ.አ. በ 1990 ዎቹ መገባደጃ ላይ የኑክሌር ኃይል ማመንጫዎች በዩኬ ውስጥ ከጠቅላላ አመታዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች 25 ከመቶ ያህሉ አስተዋፅዖ አድርገዋል፣ ነገር ግን አሮጌ እፅዋት በመዘጋታቸው እና ከእርጅና ጋር የተያያዙ ችግሮች በእጽዋት አቅርቦት ላይ ተጽዕኖ ስለሚያሳድሩ ይህ ቀስ በቀስ ቀንሷል። እ.ኤ.አ. በ 2012 ዩናይትድ ኪንግደም 16 ሬአክተሮች በመደበኛነት 19 በመቶውን የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያመነጩ ነበሯት። ከአንዱ ሬአክተሮች በስተቀር ሁሉም በ 2023 ጡረታ ይወጣሉ ከጀርመን እና ከጃፓን በተለየ መልኩ ዩናይትድ ኪንግደም ከ 2018 ገደማ ጀምሮ አዲስ የኑክሌር ተክሎችን ለመገንባት አስባለች. በ2011 ሩብ ዓመት ውስጥ በዩናይትድ ኪንግደም ከሚፈጠረው የኤሌክትሪክ ኃይል 38.9 ከመቶ የሚሆነው የሁሉም ታዳሽ የኤሌክትሪክ ምንጮች 28.8 የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርበዋል ። ዩናይትድ ኪንግደም በአውሮፓ ውስጥ ለንፋስ ሃይል በጣም ጥሩ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ነው፣ እና የንፋስ ሃይል ምርት በጣም ፈጣን እድገት ያለው አቅርቦት ነው ፣ በ 2019 ከጠቅላላው የዩኬ 20 ከመቶ የሚሆነውን ኤሌክትሪክ አመነጨ። የውሃ አቅርቦት እና የንፅህና አጠባበቅ በዩኬ የተሻሻለ የውሃ አቅርቦት እና የንፅህና አጠባበቅ ተደራሽነት ሁለንተናዊ ነው። 96.7 በመቶ የሚሆኑ አባወራዎች ከቆሻሻ ማስወገጃ መረብ ጋር የተገናኙ እንደሆኑ ይገመታል። የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ እንደገለጸው፣ በዩናይትድ ኪንግደም ለሕዝብ ውሃ አቅርቦት አጠቃላይ የውሃ ማጠቃለያ በ2007 በቀን 16,406 ሜጋሊተር ነበር። በእንግሊዝ እና በዌልስ የውሃ እና የፍሳሽ አገልግሎት የሚሰጡት በ10 የግል የክልል የውሃ እና ፍሳሽ ኩባንያዎች እና 13 በአብዛኛው ትናንሽ የግል "ውሃ ብቻ" ኩባንያዎች ናቸው። በስኮትላንድ የውሃ እና የፍሳሽ አገልግሎት የሚሰጠው በአንድ የህዝብ ኩባንያ ስኮትላንድ ውሃ ነው። በሰሜን አየርላንድ የውሃ እና የፍሳሽ አገልግሎቶች በአንድ የህዝብ አካል በሰሜን አየርላንድ ውሃ ይሰጣሉ። የስነ ሕዝብ አወቃቀር በየ10 አመቱ በሁሉም የዩኬ ክፍሎች ቆጠራ በአንድ ጊዜ ይከናወናል። በ2011 በተደረገው ቆጠራ የዩናይትድ ኪንግደም አጠቃላይ የህዝብ ብዛት 63,181,775 ነበር። በአውሮፓ አራተኛው ትልቅ ነው (ከሩሲያ ፣ ከጀርመን እና ከፈረንሣይ በኋላ) ፣ በኮመንዌልዝ ውስጥ አምስተኛው-ትልቁ እና በዓለም ላይ 22 ኛ-ትልቅ ነው። በ 2014 አጋማሽ እና በ 2015 አጋማሽ ላይ የተጣራ የረዥም ጊዜ ዓለም አቀፍ ፍልሰት ለሕዝብ እድገት የበለጠ አስተዋፅዖ አድርጓል. እ.ኤ.አ. በ2012 አጋማሽ እና በ2013 አጋማሽ ላይ የተፈጥሮ ለውጥ ለሕዝብ ዕድገት ከፍተኛውን ድርሻ አበርክቷል። በ 2001 እና 2011 መካከል ያለው የህዝብ ቁጥር በአማካይ በ 0.7 በመቶ ገደማ ጨምሯል. ይህም ከ 1991 እስከ 2001 ባለው ጊዜ ውስጥ 0.3 በመቶ እና ከ1981 እስከ 1991 ባለው 0.2 በመቶ ጋር ይነጻጸራል። የ2011 የሕዝብ ቆጠራም እንደሚያሳየው ካለፉት 100 ዓመታት ውስጥ ከ0-14 ዕድሜ ያለው የህዝብ ብዛት ከ31 ቀንሷል። ከመቶ ወደ 18 በመቶ፣ እና 65 እና ከዚያ በላይ የሆናቸው ሰዎች መጠን ከ 5 ወደ 16 በመቶ ከፍ ብሏል። እ.ኤ.አ. በ 2018 የዩኬ ህዝብ አማካይ ዕድሜ 41.7 ዓመታት ነበር። እ.ኤ.አ. በ 2011 የእንግሊዝ ህዝብ 53 ሚሊዮን ነበር ፣ ይህም ከዩናይትድ ኪንግደም አጠቃላይ 84 በመቶውን ይወክላል። በ2015 አጋማሽ ላይ በአንድ ካሬ ኪሎ ሜትር 420 ሰዎች የሚኖሩባት፣ በተለይ በለንደን እና በደቡብ-ምስራቅ የሚገኙ ህዝቦች በብዛት ከሚኖሩባቸው የአለም ሀገራት አንዷ ነች። እ.ኤ.አ. በ 2011 የተካሄደው ቆጠራ የስኮትላንድን ህዝብ 5.3 ሚሊዮን ፣ ዌልስ በ 3.06 ሚሊዮን እና ሰሜን አየርላንድ 1.81 ሚሊዮን ። እ.ኤ.አ. በ 2017 በዩናይትድ ኪንግደም አማካይ አጠቃላይ የወሊድ መጠን () በሴት የተወለዱ 1.74 ልጆች ነበሩ። እየጨመረ የሚሄደው የወሊድ መጠን ለሕዝብ ዕድገት አስተዋፅዖ እያደረገ ቢሆንም፣ በ1964 በሴቷ 2.95 ሕፃናት ከነበረው የሕፃን ዕድገት ጫፍ በእጅጉ በታች፣ ወይም በ1815 ከሴቷ የተወለዱት 6.02 ሕፃናት ከፍተኛ፣ ከ2.1 የመተካካት መጠን በታች፣ ነገር ግን ከፍ ያለ ነው። የ 2001 ዝቅተኛው 1.63. እ.ኤ.አ. በ 2011 በዩኬ ውስጥ 47.3 በመቶው የተወለዱት ላላገቡ ሴቶች ነው። የብሔራዊ ስታትስቲክስ ቢሮ እ.ኤ.አ. በ 2015 በዩናይትድ ኪንግደም 16 እና ከዚያ በላይ የሆናቸው ህዝብ 1.7 በመቶው ግብረ ሰዶማዊ ፣ ሌዝቢያን ወይም ሁለት ሴክሹዋል መሆናቸውን ያሳያል (2.0 በመቶው ወንድ እና 1.5 በመቶ) ። 4.5 ከመቶ የሚሆኑት ምላሽ ሰጪዎች "ሌላ"፣ "አላውቅም" በማለት ምላሽ ሰጥተዋል ወይም ምላሽ አልሰጡም። በ2001 እና 2008 መካከል በተደረገው ጥናት በዩኬ ውስጥ የትራንስጀንደር ሰዎች ቁጥር ከ65,000 እስከ 300,000 መካከል እንደሚሆን ተገምቷል። የጎሳ ቡድኖች በታሪክ፣ የብሪቲሽ ተወላጆች ከ12ኛው ክፍለ ዘመን በፊት እዚያ ሰፍረው ከነበሩት ከተለያዩ ጎሳዎች የተውጣጡ ናቸው ተብሎ ይታሰባል፡- ኬልቶች፣ ሮማውያን፣ አንግሎ ሳክሰኖች፣ ኖርስ እና ኖርማኖች። የዌልስ ሰዎች በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ በጣም ጥንታዊው የጎሳ ቡድን ሊሆኑ ይችላሉ። እ.ኤ.አ. በ 2006 የተደረገ የዘረመል ጥናት እንደሚያሳየው ከ50 በመቶ በላይ የሚሆነው የእንግሊዝ የጂን ገንዳ ጀርመናዊ ክሮሞሶም አለው። ሌላ እ.ኤ.አ. በ 2005 የዘረመል ትንታኔ እንደሚያመለክተው “ከዘመናዊቷ ብሪታንያ ህዝብ ሊመረመሩ ከሚችሉት ቅድመ አያቶች ውስጥ 75 በመቶው የሚሆኑት ከ6,200 ዓመታት በፊት ፣ በብሪቲሽ ኒዮሊቲክ ወይም የድንጋይ ዘመን መጀመሪያ ላይ ወደ ብሪቲሽ ደሴቶች ደርሰው ነበር” እና እንግሊዞች በሰፊው ይጋራሉ። ከባስክ ሰዎች ጋር የጋራ የዘር ግንድ. ዩናይትድ ኪንግደም በአፍሪካ የባሪያ ንግድ ወቅት ቢያንስ ከ1730ዎቹ ጀምሮ በሀገሪቱ ውስጥ ጥንታዊው ጥቁር ህዝብ ያለው ሊቨርፑል ነጭ ያልሆነ የኢሚግሬሽን ታሪክ አላት። በዚህ ጊዜ ውስጥ የታላቋ ብሪታንያ አፍሮ-ካሪቢያን ህዝብ ከ 10,000 እስከ 15,000 ይገመታል እና በኋላ ላይ ባርነት በመጥፋቱ ምክንያት ቀንሷል ። በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን ቻይናውያን መርከበኞች ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ በአውሮፓ ውስጥ እጅግ ጥንታዊ የቻይና ማህበረሰብ አላት ። እ.ኤ.አ. በ1950 በብሪታንያ ከ20,000 ያነሱ ነጭ ያልሆኑ ነዋሪዎች ነበሩ፣ ሁሉም ማለት ይቻላል በባህር ማዶ የተወለዱ ናቸው። እ.ኤ.አ. በ 1951 በደቡብ እስያ ፣ ቻይና ፣ አፍሪካ እና ካሪቢያን የተወለዱ በግምት 94,500 ሰዎች በብሪታንያ ይኖሩ ነበር ፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ህዝብ ከ 0.2 በመቶ በታች። እ.ኤ.አ. በ 1961 ይህ ቁጥር ከአራት እጥፍ በላይ ወደ 384,000 አድጓል ፣ ይህም ከዩናይትድ ኪንግደም ህዝብ ከ 0.7 በመቶ በላይ ብቻ ነው። ከ1948 ጀምሮ ከአፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ደቡብ እስያ ከፍተኛ የሆነ የኢሚግሬሽን በብሪቲሽ ኢምፓየር የፈጠሩት ትሩፋት ናቸው። እ.ኤ.አ. ከ2004 ጀምሮ ከመካከለኛው እና ምስራቃዊ አውሮፓ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ፍልሰት በእነዚህ የህዝብ ቡድኖች ውስጥ እድገት አስከትሏል ፣ ምንም እንኳን አንዳንድ የዚህ ፍልሰት ጊዜያዊ ነው። እ.ኤ.አ. ከ1990ዎቹ ጀምሮ የስደተኞች ቁጥር ከፍተኛ ልዩነት ነበረው ፣ ወደ እንግሊዝ የሚመጡ ስደተኞች ካለፉት ማዕበሎች በጣም ሰፋ ያሉ ሀገራት ይመጣሉ ፣ ይህም በአንጻራዊ ሁኔታ ሲታይ አነስተኛ ቁጥር ካላቸው ሀገራት የሚመጡ ስደተኞችን ይጨምራል ። ምሁራን አሉ ። ለመጀመሪያ ጊዜ በ1991 የሕዝብ ቆጠራ ላይ የተዋወቁት በብሪቲሽ ብሔራዊ ስታቲስቲክስ ውስጥ የተቀጠሩት የጎሳ ምድቦች በጎሳ እና በዘር ጽንሰ-ሀሳቦች መካከል ግራ መጋባትን ያካትታሉ ሲል ተከራክሯል። እ.ኤ.አ. በ 2011 ከዩናይትድ ኪንግደም 87.2 በመቶው የዩናይትድ ኪንግደም ህዝብ እራሳቸውን ነጭ ብለው ለይተዋል ይህም ማለት 12.8 በመቶው የዩናይትድ ኪንግደም ህዝብ እራሳቸውን ከቁጥር አናሳ የጎሳ ቡድኖች መካከል እንደ አንዱ ይለያሉ ። በ 2001 ቆጠራ ፣ ይህ አሃዝ ከዩኬ ህዝብ 7.9 በመቶው ነው። . በእንግሊዝ እና በዌልስ፣ በስኮትላንድ እና በሰሜን አየርላንድ ጥቅም ላይ በሚውሉት የህዝብ ቆጠራ ቅጾች የቃላት አገባብ ልዩነት የተነሳ የሌላ ነጭ ቡድን መረጃ ለዩናይትድ ኪንግደም በአጠቃላይ አይገኝም፣ ነገር ግን በእንግሊዝ እና በዌልስ ይህ በመካከላቸው በፍጥነት እያደገ ያለው ቡድን ነበር። የ 2001 እና 2011 ቆጠራ, በ 1.1 ሚሊዮን (1.8 በመቶ ነጥብ) ጨምሯል. ለሁሉም የዩናይትድ ኪንግደም ክፍሎች ተመጣጣኝ መረጃ ከሚገኙ ቡድኖች መካከል, ሌላው የእስያ ምድብ በ 2001 መካከል ከ 0.4 በመቶ ወደ 1.4 ከመቶ የህዝብ ብዛት ጨምሯል. እና 2011፣ የተቀላቀለው ምድብ ከ1.2 በመቶ ወደ 2 በመቶ ከፍ ብሏል።በ ንግሊዝ ገር ውስጥ የብሔር ልዩነት በከፍተኛ ሁኔታ ይለያያል። 30.4 ከመቶው የለንደን ህዝብ እና 37.4 ከመቶው የሌስተር ህዝብ በ2005 ነጭ እንዳልሆኑ ሲገመት ከ5 በመቶ ያነሱ የሰሜን ምስራቅ እንግሊዝ ፣ዌልስ እና ደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ከአናሳ ጎሳዎች የተውጣጡ ነበሩ ፣በ2001 መሰረት የሕዝብ ቆጠራ. እ.ኤ.አ. በ 2016 በእንግሊዝ ውስጥ 31.4 ከመቶ የመጀመሪያ ደረጃ እና 27.9 ከመቶ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የአናሳ ጎሳ አባላት ነበሩ።የ1991 ቆጠራ የጎሳ ቡድንን በተመለከተ ጥያቄ ያለው የመጀመሪያው የእንግሊዝ ቆጠራ ነው። እ.ኤ.አ. በ 1991 በዩኬ በተደረገው የህዝብ ቆጠራ 94.1 በመቶ የሚሆኑት እራሳቸውን ነጭ ብሪቲሽ ፣ ነጭ አይሪሽ ወይም ነጭ ሌላ እንደሆኑ ዘግበዋል ፣ 5 የዩናይትድ ኪንግደም ኦፊሴላዊ ቋንቋ እንግሊዝኛ ነው። ከዩናይትድ ኪንግደም 95 በመቶው ህዝብ አንድ ቋንቋ ተናጋሪ እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች እንደሆኑ ይገመታል።[5.5 ከመቶው ህዝብ ወደ እንግሊዝ የመጡ ቋንቋዎች እንደሚናገሩ ይገመታል በአንፃራዊነት በቅርብ ጊዜ በስደት ምክንያት። የደቡብ እስያ ቋንቋዎች ፑንጃቢ፣ ኡርዱ፣ ቤንጋሊ፣ ሲልሄቲ፣ ሂንዲ እና ጉጃራቲ የሚያካትቱ ትልቁ ቡድን ናቸው። እ.ኤ.አ. በ 2011 የሕዝብ ቆጠራ መሠረት ፖላንድ በእንግሊዝ ውስጥ ሁለተኛው ትልቁ ቋንቋ ሆኗል እና 546,000 ተናጋሪዎች አሉት። በ2019 ሦስት አራተኛው ሚሊዮን ሰዎች እንግሊዘኛ የሚናገሩት ትንሽ ወይም ምንም አልነበሩም። በዩኬ ውስጥ ሶስት ሀገር በቀል የሴልቲክ ቋንቋዎች ይነገራሉ፡ ዌልሽ፣ አይሪሽ እና ስኮትላንዳዊ ጌሊክ። በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ እንደ መጀመሪያ ቋንቋ የጠፋው ኮርኒሽ፣ ለተሃድሶ ጥረቶች ተገዥ ነው፣ እና አነስተኛ ቁጥር ያለው ሁለተኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች አሉት። በ2011 የሕዝብ ቆጠራ፣ በግምት አንድ አምስተኛ (19 በመቶ) የሚሆነው የዌልስ ሕዝብ ዌልሽ መናገር እንደሚችሉ ተናግረዋል፣ ይህም ከ1991 የሕዝብ ቆጠራ (18 በመቶ) ጭማሪ። በተጨማሪም ወደ 200,000 የሚጠጉ የዌልስ ተናጋሪዎች በእንግሊዝ እንደሚኖሩ ይገመታል። በሰሜን አየርላንድ በተካሄደው ተመሳሳይ ቆጠራ 167,487 ሰዎች (10.4 በመቶ) “የአይሪሽ የተወሰነ እውቀት እንዳላቸው” (በሰሜን አየርላንድ ውስጥ የአየርላንድ ቋንቋን ተመልከት) በብሔረተኛ (በዋነኛነት በካቶሊክ) ሕዝብ ውስጥ ብቻ ማለት ይቻላል ብለዋል። በስኮትላንድ ውስጥ ከ92,000 በላይ ሰዎች (ከህዝቡ ከ2 በመቶ በታች) 72 በመቶውን በውጪ ሄብሪድስ ውስጥ የሚኖሩትን ጨምሮ አንዳንድ የጌሊክ ቋንቋ ችሎታ ነበራቸው። በዌልስም ሆነ በስኮትላንድ ጌሊክ እየተማሩ ያሉ ልጆች ቁጥር እየጨመረ ነው። ከተሰደዱ ሰዎች መካከል አንዳንድ ስኮትላንዳዊ ጌሊክ አሁንም በካናዳ (በተለይ ኖቫ ስኮሺያ እና ኬፕ ብሪተን ደሴት) እና ዌልስ በፓታጎንያ፣ አርጀንቲና ይነገራል። ስኮትስ፣ ከመጀመሪያዎቹ ሰሜናዊ መካከለኛው እንግሊዘኛ የተወለደ ቋንቋ፣ ከክልላዊው ልዩነቱ፣ በሰሜን አየርላንድ የሚገኘው አልስተር ስኮት፣ ለመጠበቅ እና ለማስተዋወቅ ልዩ ቁርጠኝነት ሳይኖረው ዕውቅና ውሱን ነው። ከኤፕሪል 2020 ጀምሮ በዩኬ ውስጥ ወደ 151,000 የሚጠጉ የብሪቲሽ የምልክት ቋንቋ (ቢኤስኤል)፣ መስማት የተሳናቸው ሰዎች የሚጠቀሙበት የምልክት ቋንቋ ተጠቃሚዎች እንዳሉ ይነገራል። በእንግሊዝ ውስጥ ተማሪዎች እስከ 14 አመት እድሜ ድረስ ሁለተኛ ቋንቋ መማር አለባቸው። በእንግሊዝ እና በስኮትላንድ በብዛት የሚማሩት ፈረንሳይኛ እና ጀርመንኛ ሁለቱ ሁለተኛ ቋንቋዎች ናቸው። በዌልስ ውስጥ ያሉ ሁሉም ተማሪዎች ዌልሽ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ እስከ 16 አመት ይማራሉ ወይም በዌልሽ እንደ መጀመሪያ ቋንቋ ይማራሉ በአሁኑ ጊዜ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ከ1,400 ለሚበልጡ ዓመታት የክርስትና ዓይነቶች ሃይማኖታዊ ሕይወትን ሲቆጣጠሩ ኖረዋል። ምንም እንኳን አብዛኛው ዜጋ አሁንም በብዙ ጥናቶች የክርስትና እምነት ተከታይ ቢሆንም ከ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ መደበኛ የቤተክርስትያን መገኘት በእጅጉ ቀንሷል፣ የኢሚግሬሽን እና የስነ-ህዝብ ለውጥ ግን ለሌሎች እምነቶች በተለይም ለእስልምና እድገት አስተዋጽኦ አድርጓል።ይህም አንዳንድ ተንታኞችን አድርጓል። ዩናይትድ ኪንግደም እንደ ባለ ብዙ እምነት፣[ሴኩላራይዝድ ወይም ድህረ-ክርስቲያን ማህበረሰብ እንደሆነ ለመግለጽ። እ.ኤ.አ. በ 2001 በተደረገው የህዝብ ቆጠራ 71.6 በመቶው ምላሽ ከሰጡት ሰዎች መካከል 71.6 በመቶው ክርስቲያን መሆናቸውን አመልክተዋል ፣ ቀጣዩ ትላልቅ እምነቶች እስልምና (2.8 በመቶ) ፣ ሂንዱይዝም (1.0 በመቶ) ፣ ሲኪዝም (0.6 በመቶ) ፣ ይሁዲዝም (0.5 በመቶ) ናቸው። ቡዲዝም (0.3 በመቶ) እና ሁሉም ሌሎች ሃይማኖቶች (0.3 በመቶ)።[15 በመቶው ምላሽ ሰጪዎች ምንም ዓይነት ሃይማኖት እንደሌላቸው ገልጸዋል፣በተጨማሪ 7 በመቶው ሃይማኖታዊ ምርጫን አልገለጹም። እ.ኤ.አ. በ2007 የተደረገ የ ጥናት እንደሚያሳየው ከ10 ብሪታንያውያን መካከል አንዱ ብቻ በየሳምንቱ ወደ ቤተክርስትያን እንደሚሄድ ያሳያል። እ.ኤ.አ. በ 2001 እና 2011 መካከል ባለው የህዝብ ቆጠራ መካከል በ12 በመቶ ክርስቲያን ብለው የታወቁ ሰዎች ቁጥር ቀንሷል ፣ ምንም ዓይነት ሃይማኖታዊ ግንኙነት እንደሌለው የሚናገሩት በመቶኛ በእጥፍ ጨምሯል። ይህ ከሌሎቹ ዋና ዋና የሀይማኖት ቡድኖች እድገት ጋር ተቃርኖ፣ የሙስሊሞች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ በድምሩ 5 በመቶ ገደማ ደርሷል። የሙስሊሙ ህዝብ በ2001 ከነበረበት 1.6 ሚሊዮን በ2011 ወደ 2.7 ሚሊዮን በማደግ በዩናይትድ ኪንግደም ሁለተኛው ትልቅ የሃይማኖት ቡድን አድርጎታል። በ 2016 በ (የብሪቲሽ ማህበራዊ አመለካከት) በሃይማኖታዊ ግንኙነት ላይ የተደረገ ጥናት; ምላሽ ከሰጡት 53 በመቶዎቹ 'ሃይማኖት የለም' ሲሉ 41 በመቶው ክርስቲያን መሆናቸውን ሲገልጹ 6 በመቶው ደግሞ ከሌሎች ሃይማኖቶች (ለምሳሌ እስልምና፣ ሂንዱይዝም፣ ይሁዲነት፣ ወዘተ) ጋር ግንኙነት ያላቸው ናቸው። በክርስቲያኖች መካከል፣ የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች 15 በመቶ፣ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን 9 በመቶ እና ሌሎች ክርስቲያኖች (ፕሬስባይቴሪያንን፣ ሜቶዲስቶችን፣ ሌሎች ፕሮቴስታንቶችን፣ እንዲሁም የምስራቅ ኦርቶዶክስን ጨምሮ) 17 በመቶ ናቸው። ከ18–24 አመት የሆናቸው ወጣቶች 71 በመቶው ሃይማኖት እንደሌላቸው ተናግረዋል። የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን በእንግሊዝ ውስጥ የተመሰረተ ቤተ ክርስቲያን ነው። በዩኬ ፓርላማ ውስጥ ውክልና ይይዛል እና የብሪቲሽ ንጉሠ ነገሥት ጠቅላይ ገዥው ነው። በስኮትላንድ፣ የስኮትላንድ ቤተ ክርስቲያን ብሔራዊ ቤተ ክርስቲያን በመባል ይታወቃል። በመንግስት ቁጥጥር ስር አይደለም፣ እና የብሪቲሽ ንጉሠ ነገሥት ተራ አባል ነው፣ እሱ ወይም እሷ በመጡበት ጊዜ “የፕሮቴስታንት ሃይማኖትን እና የፕሪስባይቴሪያን ቤተ ክርስቲያን መንግሥትን ለመጠበቅ እና ለመጠበቅ” መሐላ እንዲገባ ያስፈልጋል። የዌልስ ቤተክርስቲያን በ1920 ተቋረጠ እና አየርላንድ ከመከፋፈሏ በፊት በ1870 የአየርላንድ ቤተ ክርስቲያን እንደተበታተነች፣ በሰሜን አየርላንድ ምንም የተቋቋመ ቤተ ክርስቲያን የለም። ምንም እንኳን እ.ኤ.አ. በ 2001 በተደረገው የህዝብ ቆጠራ የግለሰብን የክርስቲያን ቤተ እምነቶች ስለመከተል በዩኬ ውስጥ ሰፊ መረጃ ባይኖርም ፣ 62 በመቶው ክርስቲያኖች አንግሊካን ፣ 13.5 በመቶው ካቶሊክ ፣ 6 በመቶው ፕሬስባይቴሪያን እና 3.4 በመቶ የሜቶዲስት እንደሆኑ ተገምቷል ። እንደ ፕሊማውዝ ወንድሞች እና የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ያሉ ሌሎች የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች ዩናይትድ ኪንግደም በተከታታይ የስደት ማዕበል አጋጥሟታል። በአየርላንድ የተከሰተው ታላቁ ረሃብ፣ በወቅቱ የዩናይትድ ኪንግደም አካል፣ ምናልባትም አንድ ሚሊዮን ሰዎች ወደ ታላቋ ብሪታንያ እንዲሰደዱ አድርጓል። ለንደን ከዚህ ህዝብ ግማሽ ያህሉን ይዛለች፣ እና ሌሎች ትናንሽ ማህበረሰቦች በማንቸስተር፣ ብራድፎርድ እና ሌሎችም ነበሩ። የጀርመን ስደተኛ ማህበረሰብ እስከ 1891 ድረስ ከሩሲያ አይሁዶች ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ቡድን ነበር። ከ 1881 በኋላ ሩሲያውያን አይሁዶች መራራ ስደት ደርሶባቸዋል እና በ 1914 2,000,000 የሩስያን ኢምፓየር ለቀው ወጡ ። 120,000 ያህሉ በብሪታንያ በቋሚነት ተቀምጠዋል ፣ ከብሪቲሽ ደሴቶች ውጭ ካሉ አናሳ ጎሳዎች ትልቁ ። ይህ ሕዝብ በ1938 ወደ 370,000 አድጓል። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ ወደ ፖላንድ መመለስ ባለመቻሉ ከ120,000 በላይ የፖላንድ አርበኞች በእንግሊዝ በቋሚነት ቆይተዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ፣ ብዙ ሰዎች በካሪቢያን እና በህንድ ክፍለ አህጉር ከነበሩት ቅኝ ግዛቶች እና የቀድሞ ቅኝ ግዛቶች፣ እንደ ኢምፓየር ውርስ ወይም በሠራተኛ እጥረት ተገፋፍተው ተሰደዱ። እ.ኤ.አ. በ 1841 ከእንግሊዝ እና ከዌልስ ህዝብ 0.25 በመቶው በውጭ ሀገር የተወለዱ ሲሆን በ 1901 ወደ 1.5 በመቶ ፣ በ 1931 2.6 በመቶ እና በ 1951 4.4 በመቶ። እ.ኤ.አ. በ 2014 የኢሚግሬሽን የተጣራ ጭማሪ 318,000 ነበር ፣ ኢሚግሬሽን በ 641,000 ነበር ፣ በ 2013 ከ 526,000 ፣ ከአንድ አመት በላይ የለቀቁት ስደተኞች ቁጥር 323,000 ነበር። የቅርብ ጊዜ የፍልሰት አዝማሚያ በምስራቅ አውሮፓ ከሚገኙት አዲሶቹ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ሰራተኞች መምጣት 8 ሀገራት በመባል ይታወቃል። እ.ኤ.አ. በ 2011 የአዲሱ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ዜጎች 13 በመቶው ስደተኞች ናቸው። ዩናይትድ ኪንግደም በጥር 2007 የአውሮፓ ህብረትን የተቀላቀለው የሮማኒያ እና የቡልጋሪያ ዜጎች ላይ ጊዜያዊ እገዳዎችን ተጠቀመች ። በስደት ፖሊሲ የእኩልነት እና የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የተደረገ ጥናት እንደሚያመለክተው ከግንቦት 2004 እስከ መስከረም 2009 ባለው ጊዜ ውስጥ 1.5 ሚሊዮን ሰራተኞች ከ አዲስ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ወደ ዩኬ፣ አብዛኛዎቹ የፖላንድ ናቸው። በኋላ ብዙዎች ወደ አገራቸው ተመለሱ፣ በዚህም ምክንያት በዩኬ ውስጥ የአዲሶቹ አባል ሀገራት ዜጎች ቁጥር ጨምሯል። በ 2000 ዎቹ መገባደጃ ላይ በዩኬ ያለው የኢኮኖሚ ውድቀት ፖልስ ወደ እንግሊዝ ለመሰደድ ኢኮኖሚያዊ ማበረታቻን ቀንሷል [ስደትን ጊዜያዊ እና ሰርኩላር አድርጎታል። በ ንግሊዝ ገር ውስጥ የውጭ ተወላጆች ድርሻ ከብዙ ሌሎች የአውሮፓ ሀገሮች ትንሽ ያነሰ ነው. በ1991 እና 2001 መካከል ካለው የህዝብ ቁጥር ግማሹን ያህሉ የጨመሩት ከ1991 እስከ 2001 ድረስ ስደተኞች እና እንግሊዝ የተወለዱ ልጆች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ኢሚግሬሽን በአሁኑ ጊዜ እየጨመረ ነው ። እ.ኤ.አ. በ 2015 ይፋዊ ስታቲስቲክስ ተለቋል። ኦኤንኤስ እንደዘገበው የተጣራ ፍልሰት ከ2009 ወደ 2010 በ21 በመቶ ወደ 239,000 ከፍ ብሏል። እ.ኤ.አ. በ 2013 ወደ 208,000 የሚጠጉ የውጭ ሀገር ዜጎች እንደ ብሪታንያ ዜጋ ተሰጥተዋል ፣ ከ 1962 ጀምሮ ከፍተኛው ቁጥር ። ይህ አሃዝ በ 2014 ወደ 125,800 ዝቅ ብሏል ። እ.ኤ.አ. በ 2009 እና 2013 መካከል ፣ በየዓመቱ የሚሰጠው አማካኝ የእንግሊዝ ዜግነት 195,800 ነበር። እ.ኤ.አ. በ 2014 ዜግነት የተሰጣቸው በጣም የተለመዱት የቀድሞ ብሄረሰቦች ህንድ ፣ ፓኪስታን ፣ ፊሊፒንስ ፣ ናይጄሪያ ፣ ባንግላዲሽ ፣ ኔፓል ፣ ቻይና ፣ ደቡብ አፍሪካ ፣ ፖላንድ እና ሶማሊያ ናቸው። በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ የሚሰጥ ነገር ግን ዜግነት የሌለው የሰፈራ ጠቅላላ የገንዘብ ድጋፍ በ2013 በግምት 154,700 ነበር ይህም ካለፉት ሁለት ዓመታት የበለጠ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2008 ፣ የብሪቲሽ መንግስት የስኮትላንድ መንግስት ትኩስ ታለንት ተነሳሽነትን ጨምሮ የቀድሞ እቅዶችን ለመተካት ከአውሮፓ ኢኮኖሚ ክልል ውጭ ለሚመጡ ስደተኞች ነጥብ ላይ የተመሠረተ የኢሚግሬሽን ስርዓት አስተዋውቋል። በሰኔ 2010 ከአውሮፓ ህብረት ውጭ የሚመጡ ስደተኞች ጊዜያዊ ገደብ ተጀመረ፣ ይህም በሚያዝያ 2011 ቋሚ ካፕ ከመጣሉ በፊት ማመልከቻዎችን ተስፋ ለማስቆረጥ ነው። በ19ኛው ክፍለ ዘመን ስደት የብሪቲሽ ማህበረሰብ አስፈላጊ ገጽታ ነበር። ከ1815 እስከ 1930 ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ 11.4 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ከብሪታንያ እና 7.3 ሚሊዮን ከአየርላንድ ተሰደዱ። ግምቶች እንደሚያሳዩት በ20ኛው መቶ ዘመን መገባደጃ ላይ 300 ሚሊዮን የሚያህሉ የብሪታንያና የአየርላንድ ዝርያ ያላቸው ሰዎች በዓለም ዙሪያ በቋሚነት ሰፍረዋል። ዛሬ ከ5.5 ሚሊዮን ያላነሱ የእንግሊዝ ተወላጆች በውጭ የሚኖሩ ሲሆን በተለይም በአውስትራሊያ፣ ስፔን፣ አሜሪካ እና ካናዳ ይኖራሉ። በዩናይትድ ኪንግደም የከፍተኛ ትምህርት በዩኒቨርሲቲዎች እና ዩኒቨርሲቲ ባልሆኑ ተቋማት (ኮሌጆች, ተቋማት, ትምህርት ቤቶች እና አካዳሚዎች) የሚሰጥ ሲሆን ሁለቱንም በጥናት ላይ የተመሰረተ እና ከፍተኛ ሙያዊ ትምህርት ይሰጣል. ዩንቨርስቲዎች በዲግሪ (ባችለር፣ ማስተርስ ወይም ዶክትሬት ዲግሪ) የሚጨርሱ የዲግሪ መርሃ ግብሮችን እና የዲግሪ ያልሆኑ ፕሮግራሞችን እንደ ሰርተፍኬት ወይም ዲፕሎማ ያሉ የሙያ መመዘኛዎችን ይሰጣሉ። የብሪቲሽ ከፍተኛ ትምህርት በጥራት እና በጠንካራ የአካዳሚክ ደረጃዎች በአለም ዙሪያ ከፍተኛ ዋጋ ያለው ነው። በየመስካቸው ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ ታዋቂ ሰዎች የብሪቲሽ ከፍተኛ ትምህርት ውጤቶች ናቸው። ብሪታንያ በዓለም ላይ በጣም ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መገኛ ነች እና በዓለም ላይ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች አንደኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። እንደ ካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፣ ኢምፔሪያል ኮሌጅ ለንደን እና ዩሲኤል ያሉ ተቋማት በተከታታይ ከአለም ምርጥ አስር ዩኒቨርሲቲዎች ተርታ ይመደባሉ። ለ የሚቀመጡ ተማሪዎች ከ20 እስከ 25 ፈተናዎችን ይወስዳሉ እና አብዛኛውን ጊዜ 9 ይወስዳሉ። አብዛኛው ተማሪ የሂሳብ፣ የእንግሊዘኛ ስነጽሁፍ፣ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ድርብ ሳይንስ ይወስዳሉ፣ ይህም በአጠቃላይ 5 ፣ ተማሪዎች በመደበኛነት በተለያዩ የትምህርት ዓይነቶች ተጨማሪ 4 ዎችን ይወስዳሉ። በፈተና ላይ መቀመጥ የ 11 ዓመታት የግዴታ ትምህርት ያበቃል. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት አጠቃላይ ሰርተፍኬት () ለእያንዳንዱ ለሚያልፍ የትምህርት አይነት የሚሰጥ ሲሆን የአለም ትምህርት አገልግሎት ቢያንስ ሶስት ጂሲኤስዎች ከተገመገመ በኋላ የሁለተኛ ደረጃ ዲፕሎማ ይሰጣል። በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የቅድመ-ዩኒቨርሲቲ ትምህርት የሁለት ዓመት ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ መርሃ ግብር ነው, ይህም ወደ አዲስ ዙር ፈተናዎች የሚያመራ አጠቃላይ የትምህርት የምስክር ወረቀት, ከፍተኛ ደረጃ (በተጨማሪም በመባል ይታወቃል). እንደ ሁሉ ለፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች የትምህርት ዓይነቶችን እና የፈተናዎችን ብዛት ይመርጣሉ (የተወሰዱት አማካይ ቁጥር ሶስት ነው)። የ ሽልማቶች ባሳለፉት የትምህርት ዓይነቶች ተፈጥሮ እና ብዛት ላይ በመመስረት የመጀመሪያ ዲግሪ ክሬዲት ነው። እያንዳንዱ ዩኒቨርሲቲ የራሱ የሆነ የመግቢያ ፖሊሲዎች እና ለእያንዳንዱ የተለየ የከፍተኛ ትምህርት መርሃ ግብር ዝቅተኛ የመግቢያ መስፈርቶች አሉት።የአጠቃላይ የትምህርት የላቀ ደረጃ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ላሉ ዩኒቨርሲቲዎች የመግቢያ ብቃት እና ብዙ ነው በዓለም ዙሪያ ያሉ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ። የከፍተኛ ትምህርት ለመከታተል ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ብዙውን ጊዜ በቅድመ-ዩኒቨርስቲ እና ተጨማሪ የትምህርት ፕሮግራሞች ውስጥ ይመዘገባሉ. የቅድመ-ዩኒቨርስቲ ትምህርት እስከ ሁለት አመት የሚፈጅ ሲሆን ይህም በአዲስ የፈተናዎች ስብስብ ይጠናቀቃል, አጠቃላይ የትምህርት የምስክር ወረቀት, የላቀ ደረጃ (-ደረጃዎች). በተመሳሳይ ከጂሲኤስኢ ጋር፣ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች የፍላጎት ርእሶቻቸውን እና የፈተናዎችን ብዛት ይመርጣሉ። አብዛኛዎቹ ተማሪዎች በአማካይ ሶስት የትምህርት ዓይነቶችን ይወስዳሉ እና ባሳለፉት የትምህርት ዓይነቶች ተፈጥሮ እና ብዛት ላይ በመመርኮዝ የቅድመ ምረቃ ክሬዲት ይሰጣል። የባችለር ዲግሪዎች በባዶ ዝቅተኛው በተለምዶ ከሁለት እስከ ሶስት የ ደረጃ ማለፊያዎች ያስፈልጋሉ ፣ እና ዝቅተኛው የ ብዛት በ ወይም ከዚያ በላይ ያልፋል "የብሪቲሽ ሥነ ጽሑፍ" ከዩናይትድ ኪንግደም፣ ከማን ደሴት እና ከቻናል ደሴቶች ጋር የተያያዙ ጽሑፎችን ያመለክታል። አብዛኛው የብሪቲሽ ሥነ ጽሑፍ በእንግሊዝኛ ነው። በ2005 በዩናይትድ ኪንግደም 206,000 የሚያህሉ መጽሐፎች የታተሙ ሲሆን በ2006 በዓለም ላይ ትልቁን መጽሐፍ አሳታሚ ነበር። እንግሊዛዊው ፀሐፌ ተውኔት እና ገጣሚ ዊልያም ሼክስፒር የ20ኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የወንጀል ፀሐፊ አጋታ ክሪስቲ የዘመኑ ምርጥ ሽያጭ ደራሲ ናቸው። በቢቢሲ የዓለም ተቺዎች አስተያየት ከተመረጡት 100 ልብ ወለዶች ውስጥ 12 ቱ ምርጥ 25 በሴቶች የተፃፉ ናቸው። እነዚህ በጆርጅ ኤሊዮት፣ ቨርጂኒያ ዎልፍ፣ ሻርሎት እና ኤሚሊ ብሮንት፣ ሜሪ ሼሊ፣ ጄን አውስተን፣ ዶሪስ ሌሲንግ እና ዛዲ ስሚዝ የተሰሩ ስራዎችን ያካትታሉ። የዩናይትድ ኪንግደም ባህል በብዙ ምክንያቶች ተጽዕኖ አሳድሯል-የሀገሪቱ ደሴት ሁኔታ; እንደ ምዕራባዊ ሊበራል ዲሞክራሲ እና ትልቅ ኃይል ያለው ታሪክ; እንዲሁም እያንዳንዱ ልዩ ወጎች, ልማዶች እና ተምሳሌታዊ ባህሪያትን የሚጠብቅ የአራት አገሮች የፖለቲካ አንድነት ነው. በብሪቲሽ ኢምፓየር የተነሳ የብሪታንያ ተጽእኖ በብዙዎቹ የቀድሞ ቅኝ ግዛቶቿ ቋንቋ፣ ባህል እና ህጋዊ ስርአቶች አውስትራሊያ፣ ካናዳ፣ ህንድ፣ አየርላንድ፣ ኒውዚላንድ፣ ፓኪስታን፣ ደቡብ አፍሪካ እና ዩናይትድ ስቴትስ፣ ዛሬ እንደ አንግሎስፌር የጋራ ባህል ተፈጠረ። የዩናይትድ ኪንግደም ከፍተኛ የባህል ተጽእኖ እንደ "የባህል ልዕለ ኃያል" እንድትባል አድርጓታል። ለቢቢሲ በተደረገው ዓለም አቀፍ የሕዝብ አስተያየት ዩናይትድ ኪንግደም በዓለም ላይ (ከጀርመን እና ካናዳ ጀርባ) በሦስተኛ ደረጃ በአዎንታዊነት የሚታይባት ሀገር ሆናለች። የስኮትላንድ አስተዋፅዖዎች አርተር ኮናን ዶይል (የሼርሎክ ሆልምስ ፈጣሪ)፣ ሰር ዋልተር ስኮት፣ ጄ ኤም ባሪ፣ ሮበርት ሉዊስ ስቲቨንሰን እና ገጣሚው ሮበርት በርንስ ይገኙበታል። በቅርብ ጊዜ ሂዩ ማክዲያርሚድ እና ኒል ኤም.ጉንን ለስኮትላንድ ህዳሴ አስተዋፅዖ አድርገዋል፣ ከኢያን ራንኪን እና ከአይን ባንክስ ገራሚ ስራዎች ጋር። የስኮትላንድ ዋና ከተማ ኤዲንብራ በዩኔስኮ የመጀመሪያዋ የአለም የስነ-ጽሁፍ ከተማ ነበረች። የብሪታንያ አንጋፋው የታወቀው ግጥም የተቀናበረው ምናልባትም በ6ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ ነው። የተጻፈው በከምብሪክ ወይም በብሉይ ዌልሽ ሲሆን የንጉሥ አርተርን ጥንታዊ ማጣቀሻ ይዟል። የአርተርሪያን አፈ ታሪክ የበለጠ የተገነባው በሞንማውዝ ጂኦፍሪ ነው። ገጣሚ ዳፊድ አፕ ግዊሊም (እ.ኤ.አ. 1320-1370) በዘመኑ ከነበሩት ታላላቅ የአውሮፓ ገጣሚዎች አንዱ ተደርጎ ይወሰዳል።ዳንኤል ኦወን በ1885 ን ያሳተመው የመጀመሪያው የዌልስ ልቦለድ ደራሲ እንደሆነ ይነገርለታል። የዌልስ ገጣሚዎች ዲላን ቶማስ እና አር ኤስ ቶማስ ሲሆኑ፣ በ1996 ለኖቤል ሽልማት በሥነ ጽሑፍ የታጩት። የ20ኛው ክፍለ ዘመን መሪ የዌልስ ደራሲያን ሪቻርድ ሌዌሊን እና ኬት ሮበርትስ ይገኙበታል። ሁሉም አየርላንድ የዩናይትድ ኪንግደም አካል በነበረችበት ጊዜ የሚኖሩ የአየርላንድ ፀሐፊዎች ኦስካር ዋይልዴ፣ ብራም ስቶከር እና ጆርጅ በርናርድ ሻው ይገኙበታል። መነሻቸው ከዩናይትድ ኪንግደም ውጭ የሆኑ ግን ወደ እንግሊዝ የተዛወሩ በርካታ ደራሲያን ነበሩ። እነዚህም ጆሴፍ ኮንራድ፣ ቲ.ኤስ.ኤልዮት፣ ካዙኦ ኢሺጉሮ፣ ሰር ሳልማን ራሽዲ እና ኢዝራ ፓውንድ ያካትታሉ። የእንግሊዝ፣ የዌልስ፣ የስኮትላንድ እና የሰሜን አየርላንድ አገር በቀል ሙዚቃዎችን ጨምሮ የተለያዩ የሙዚቃ ስልቶች በእንግሊዝ ታዋቂ ናቸው። ከ16ኛው እና 17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የመጡ ልዩ የህዳሴ እና ባሮክ አቀናባሪዎች ቶማስ ታሊስ፣ ዊልያም ባይርድ፣ ኦርላንዶ ጊቦንስ፣ ጆን ዶውላንድ፣ ሄንሪ ፐርሴል እና ቶማስ አርን ያካትታሉ። በንግሥት አን የግዛት ዘመን ወደ ለንደን ከተዛወረ በኋላ፣ ጆርጅ ፍሪደሪክ ሃንዴል በ1727 የጆርጅ 2ኛ ዘውድ የንግሥና ሥርዓተ ንግሥ ለሆነው ቄስ ሳዶቅ የተሰኘውን መዝሙር ባቀናበረ ጊዜ፣ በ1727 የብሪቲሽ ዜጋ ሆነ። ሁሉንም የወደፊት ነገሥታትን የመቀባት ባህላዊ ሥነ ሥርዓት ሙዚቃ ሆነ። ብዙዎቹ የሃንደል ታዋቂ ስራዎች፣ ለምሳሌ መሲህ፣ የተፃፉት በእንግሊዝኛ ነው። ታዋቂው የ19ኛው እና የ20ኛው ክፍለ ዘመን የብሪቲሽ አቀናባሪዎች ኤድዋርድ ኤልጋር፣ ሁበርት ፓሪ፣ ጉስታቭ ሆልስት፣ አርተር ሱሊቫን (ከሊብሬቲስት ጊልበርት ጋር በመስራት በጣም ታዋቂ)፣ ራልፍ ቮን ዊሊያምስ፣ ዊልያም ዋልተን፣ ሚካኤል ቲፕት እና ቤንጃሚን ብሪተን፣ የዘመናዊቷ ብሪታንያ አቅኚ ናቸው። ኦፔራ ከጦርነቱ በኋላ ከነበረው ትውልድ፣ ፒተር ማክስዌል ዴቪስ፣ ማልኮም አርኖልድ፣ ሃሪሰን ቢርትዊስትል፣ ጆን ሩትተር፣ ጆን ታቨርነር፣ አሉን ሆዲኖት፣ ቲያ ሙስግሬድ፣ ጁዲት ዌር፣ ጄምስ ማክሚላን፣ ማርክ-አንቶኒ ተርኔጅ፣ ጆርጅ ቤንጃሚን፣ ቶማስ አዴስ እና ፖል ሜሎር ነበሩ። ከዋነኞቹ አቀናባሪዎች መካከል። ዩናይትድ ኪንግደም በዓለም የታወቁ የሲምፎኒ ኦርኬስትራዎች እና እንደ የቢቢሲ ሲምፎኒ ኦርኬስትራ እና የለንደን ሲምፎኒ ቾረስ ያሉ መዘምራን መኖሪያ ነች። ታዋቂ የብሪቲሽ መሪዎች ሰር ሄንሪ ውድ፣ ሰር ጆን ባርቢሮሊ፣ ሰር ማልኮም ሳርጀንት፣ ሰር ቻርለስ ግሮቭስ፣ ሰር ቻርለስ ማከርራስ እና ሰር ሲሞን ራትል፣ በተመሳሳይ ጊዜ እንደ ጆርጅ ሶልቲ እና በርናርድ ሃይቲንክ ያሉ የብሪታንያ ተወላጆች ሳይሆኑ ዓለም አቀፍ መሪዎች በሲምፎኒክ ሙዚቃ እና ኦፔራ በብሪታንያ ግንባር ቀደም ሆነዋል። ከታወቁት የፊልም ውጤቶች አቀናባሪዎች መካከል ጆን ባሪ፣ ክሊንት ማንሴል፣ ማይክ ኦልድፊልድ፣ ጆን ፓውል፣ ክሬግ አርምስትሮንግ፣ ዴቪድ አርኖልድ፣ ጆን መርፊ፣ ሞንቲ ኖርማን እና ሃሪ ግሬግሰን-ዊሊያምስ ያካትታሉ። አንድሪው ሎይድ ዌበር የሙዚቃ ቲያትር አቀናባሪ ነው። ስራዎቹ ከ20ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ጀምሮ የለንደንን ዌስት ኤንድ ተቆጣጥረውታል እና በአለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ስኬት ሆነዋል። ዘ ኒው ግሮቭ ዲክሽነሪ ኦፍ ሙዚቃ እና ሙዚቀኞች ድረ-ገጽ እንደገለጸው፣ “ፖፕ ሙዚቃ” የሚለው ቃል የመጣው በ1950ዎቹ አጋማሽ ላይ ከብሪታንያ የሮክ እና ሮል ውህደትን ከ“አዲሱ የወጣቶች ሙዚቃ” ጋር ለመግለጽ ነው። የኦክስፎርድ ሙዚቃ መዝገበ ቃላት እንደ ዘ ቢትልስ እና ሮሊንግ ስቶንስ ያሉ አርቲስቶች በ1960ዎቹ መጀመሪያ ላይ የፖፕ ሙዚቃን በታዋቂ ሙዚቃዎች ግንባር ቀደም አድርገው እንደነበሩ ይገልጻል። በሚቀጥሉት ዓመታት ብሪታንያ በሮክ ሙዚቃ እድገት ውስጥ አንድ ክፍል ነበራት ፣ የብሪታንያ ድርጊቶች የሃርድ ሮክ ፈር ቀዳጅ በመሆን; ራጋ ሮክ; አርት ሮክ; ከባድ ብረት; የጠፈር ድንጋይ; ግላም ሮክ አዲስ ሞገድ; ጎቲክ ሮክ እና ስካ ፓንክ። በተጨማሪም, የብሪታንያ ድርጊቶች ተራማጅ ዓለት አዳብረዋል; ሳይኬደሊክ ሮክ; እና ፓንክ ሮክ. ከሮክ ሙዚቃ በተጨማሪ የብሪቲሽ ድርጊቶች ኒዮ ነፍስን አዳብረዋል እና ዱብስቴፕን ፈጠሩ።ቢትልስ ከ1 ቢሊዮን በላይ ዩኒቶች አለምአቀፍ ሽያጮች አላቸው እና በታዋቂ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ሽያጭ እና ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪ ባንድ ናቸው። ሌሎች ታዋቂ የብሪቲሽ አስተዋጽዖ አበርካቾች ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ ታዋቂ ሙዚቃዎች ላይ ዘ ሮሊንግ ስቶንስ፣ ፣ ፣ ፣ እና ፣ ሁሉም በዓለም አቀፍ ደረጃ 200 ሚሊዮን ወይም ከዚያ በላይ ሽያጭ ያስመዘገቡ ናቸው። የብሪቲሽ ሽልማቶች የ አመታዊ የሙዚቃ ሽልማቶች ሲሆኑ ከብሪቲሽ ለሙዚቃ የላቀ አስተዋፅዖ ሽልማት ከተበረከቱት መካከል አንዳንዶቹ፣ ማን፣ ዴቪድ ቦዊ፣ ኤሪክ ክላፕቶን፣ ሮድ ስቱዋርት፣ ፖሊስ፣ እና ፍሊትዉድ ማክ (የብሪቲሽ-አሜሪካዊ ባንድ የሆኑ)። አለምአቀፍ ስኬት ያስመዘገቡ የቅርብ ጊዜ የዩኬ የሙዚቃ ስራዎች ጆርጅ ሚካኤል፣ ኦሳይስ፣ ስፓይስ ገርልስ፣ ራዲዮሄድ፣ ኮልድፕሌይ፣ አርክቲክ ጦጣዎች፣ ሮቢ ዊሊያምስ፣ ኤሚ ወይን ሃውስ፣ አዴሌ፣ ኢድ ሺራን፣ አንድ አቅጣጫ እና ሃሪ ስታይልስ ያካትታሉ። በርካታ የዩኬ ከተሞች በሙዚቃቸው ይታወቃሉ። የሊቨርፑል የሐዋርያት ሥራ 54 የዩናይትድ ኪንግደም ገበታ ቁጥር 1 ነጠላ ነጠላዎችን አግኝቷል። ግላስጎው ለሙዚቃ ያበረከተው አስተዋፅዖ በ2008 የዩኔስኮ ከተማ የሙዚቃ ከተማ ስትባል ታወቀ።ማንችስተር እንደ አሲድ ቤት ባሉ የዳንስ ሙዚቃዎች መስፋፋት እና ከ1990ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ ብሪትፖፕ ሚና ተጫውቷል። ለንደን እና ብሪስቶል እንደ ከበሮ እና ባስ እና ጉዞ ሆፕ ካሉ የኤሌክትሮኒካዊ ሙዚቃ ንዑስ ዘውጎች አመጣጥ ጋር በቅርበት የተቆራኙ ናቸው።ቢርሚንግሃም የሄቪ ሜታል የትውልድ ቦታ በመባል ይታወቅ ነበር፣የጥቁር ሰንበት ባንድ በ1960ዎቹ ጀምሮ ነበር። ፖፕ በነጠላ ነጠላ ሽያጭ እና ዥረቶች በጣም ታዋቂው የሙዚቃ ዘውግ ሆኖ ይቆያል ፣ በ 2016 ከገበያው 33.4 በመቶ ፣ በመቀጠል ሂፕ-ሆፕ እና በ 24.5 በመቶ። ሮክ በ 22.6 በመቶ ወደ ኋላ ሩቅ አይደለም ። ዘመናዊው እንግሊዝ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመሆን ስቶርምዚ ፣ ካኖ ፣ ያክስንግ ባኔ ፣ ራምዝ እና ስኬፕታ የተባሉትን ታዋቂ የእንግሊዝኛ ተናጋሪ ራፕዎችን በማፍራት ይታወቃል። የማህበር እግር ኳስ፣ ቴኒስ፣ የጠረጴዛ ቴኒስ፣ ባድሚንተን፣ ራግቢ ዩኒየን፣ ራግቢ ሊግ፣ ራግቢ ሰባት፣ ጎልፍ፣ ቦክስ፣ መረብ ኳስ፣ የውሃ ፖሎ፣ የሜዳ ሆኪ፣ ቢሊያርድ፣ ዳርት፣ ቀዘፋ፣ ዙሮች እና ክሪኬት የተፈጠሩት ወይም በከፍተኛ ደረጃ የተገነቡት በዩኬ ውስጥ ነው። በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ የቪክቶሪያ ብሪታንያ የብዙ ዘመናዊ ስፖርቶች ህጎች እና ኮዶች ተፈለሰፉ እና ተስተካክለዋል። እ.ኤ.አ. በ 2012 የ ፕሬዝዳንት ዣክ ሮጌ “ይህች ታላቅ ፣ ስፖርት ወዳድ ሀገር የዘመናዊ ስፖርት መፍለቂያ እንደሆነች በሰፊው ትታወቃለች ። የስፖርታዊ ጨዋነት እና የፍትሃዊ ጨዋታ ፅንሰ-ሀሳቦች በመጀመሪያ ግልፅ ህጎች እና የተቀናጁት እዚህ ነበር ። እዚህ ነበር ስፖርት በትምህርት ቤት ሥርዓተ-ትምህርት ውስጥ እንደ ትምህርታዊ መሣሪያ የተካተተው። እ.ኤ.አ. በ 2003 በተደረገ የሕዝብ አስተያየት እግር ኳስ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ በጣም ተወዳጅ ስፖርት ነው ። እንግሊዝ የክለቦች እግር ኳስ መፍለቂያ በፊፋ እውቅና ያገኘች ሲሆን የእግር ኳስ ማህበርም የዚህ አይነት ጥንታዊ ሲሆን የእግር ኳስ ህግጋት በ1863 በአቤኔዘር ኮብ ሞርሊ ተዘጋጅቷል። እያንዳንዱ አገር ቤት የራሱ የእግር ኳስ ማህበር፣ ብሔራዊ ቡድን እና ሊግ ስርዓት ያለው ሲሆን በግለሰብ ደረጃ ከፊፋ ጎን ለጎን የአለም አቀፍ እግር ኳስ ማህበር የቦርድ አስተዳዳሪ አባላት ናቸው። የእንግሊዝ ከፍተኛ ዲቪዚዮን ፕሪሚየር ሊግ በአለም ላይ በብዛት የታየ የእግር ኳስ ሊግ ነው። የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ግጥሚያ በእንግሊዝ እና በስኮትላንድ የተካሄደው እ.ኤ.አ. ህዳር 30 ቀን 1872 ነበር። እንግሊዝ፣ ስኮትላንድ፣ ዌልስ እና ሰሜን አየርላንድ እንደ ተለያዩ አገሮች በአለም አቀፍ ውድድር ይወዳደራሉ።እ.ኤ.አ. በ 2003 የራግቢ ህብረት በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ሁለተኛው በጣም ተወዳጅ ስፖርት ነበር ። ስፖርቱ የተፈጠረው በዋርዊክሻየር በራግቢ ትምህርት ቤት ሲሆን የመጀመሪያው ራግቢ ዓለም አቀፍ እ.ኤ.አ. በማርች 27 ቀን 1871 በእንግሊዝ እና በስኮትላንድ መካከል ተካሄዷል። እንግሊዝ፣ ስኮትላንድ፣ ዌልስ፣ አየርላንድ፣ ፈረንሳይ እና ጣሊያን በስድስት ሀገራት ሻምፒዮና ውስጥ ይወዳደራሉ። በሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ የመጀመሪያ ደረጃ ዓለም አቀፍ ውድድር። በእንግሊዝ፣ በስኮትላንድ፣ በዌልስ እና በአየርላንድ ያሉ የስፖርት አስተዳዳሪ አካላት ጨዋታውን በተናጥል ያደራጁ እና ይቆጣጠራሉ። በየአራት ዓመቱ እንግሊዝ፣ አየርላንድ፣ ስኮትላንድ እና ዌልስ ብሪቲሽ እና አይሪሽ አንበሶች በመባል የሚታወቁትን ጥምር ቡድን ያደርጋሉ። ቡድኑ አውስትራሊያን፣ ኒውዚላንድን እና ደቡብ አፍሪካን ጎብኝቷል። ክሪኬት የተፈለሰፈው በእንግሊዝ ሲሆን ሕጎቹ የተቋቋሙት በሜሪሌቦን ክሪኬት ክለብ እ.ኤ.አ. ዩኬ ከሙከራ ሁኔታ ጋር። የቡድን አባላት ከዋናው የካውንቲ ጎኖች የተውጣጡ ናቸው, እና ሁለቱንም የእንግሊዝኛ እና የዌልስ ተጫዋቾችን ያካትታሉ. ክሪኬት ዌልስ እና እንግሊዝ ብሔራዊ ቡድኖችን የሚለያዩበት ከእግር ኳስ እና ከራግቢ የተለየ ነው፣ ምንም እንኳን ዌልስ ከዚህ ቀደም የራሷን ቡድን ብታሰልፍም። የስኮትላንድ ተጫዋቾች ለእንግሊዝ ተጫውተዋል ምክንያቱም ስኮትላንድ የፈተና ደረጃ ስለሌላት እና በቅርቡ በአንድ ቀን ኢንተርናሽናልስ መጫወት የጀመረው። ስኮትላንድ፣ ኢንግላንድ (እና ዌልስ) እና አየርላንድ (ሰሜን አየርላንድን ጨምሮ) በክሪኬት የዓለም ዋንጫ ተወዳድረዋል፣ እንግሊዝ በ2019 ውድድሩን አሸንፋለች። 17 የእንግሊዝ ካውንቲዎችን እና 1 የዌልስ ካውንቲ የሚወክሉ ክለቦች የሚወዳደሩበት የፕሮፌሽናል ሊግ ሻምፒዮና አለ።ዘመናዊው የቴኒስ ጨዋታ በአለም ዙሪያ ከመስፋፋቱ በፊት በ1860ዎቹ በእንግሊዝ በርሚንግሃም የተጀመረ ነው። የዓለማችን አንጋፋው የቴኒስ ውድድር የዊምብልደን ሻምፒዮና ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው እ.ኤ.አ. በ1877 ሲሆን ዛሬ ዝግጅቱ የሚካሄደው በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ በሰኔ መጨረሻ እና በሐምሌ ወር መጀመሪያ ላይ ነው። ዩናይትድ ኪንግደም ከሞተር ስፖርት ጋር በቅርብ የተቆራኘ ነው። በፎርሙላ አንድ ውስጥ ያሉ ብዙ ቡድኖች እና አሽከርካሪዎች በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የተመሰረቱ ናቸው፣ እና ሀገሪቱ ከማንም በላይ የአሽከርካሪዎች እና የግንባታ አርእስቶች አሸንፋለች። ዩናይትድ ኪንግደም እ.ኤ.አ. በ1950 የመጀመሪያውን ኤፍ 1 ግራንድ ፕሪክስን በሲልቨርስቶን አስተናግዳለች፣ የብሪቲሽ ግራንድ ፕሪክስ በየዓመቱ በጁላይ ይካሔዳል።ጎልፍ በዩኬ ውስጥ በተሳታፊነት ስድስተኛው በጣም ተወዳጅ ስፖርት ነው። በስኮትላንድ የሚገኘው የቅዱስ አንድሪውስ የሮያል እና ጥንታዊ ጎልፍ ክለብ የስፖርቱ የቤት ኮርስ ቢሆንም የዓለማችን አንጋፋው የጎልፍ ኮርስ በእውነቱ የሙስልበርግ ሊንኮች የድሮ ጎልፍ ኮርስ ነው። እ.ኤ.አ. በ 1764 መደበኛው ባለ 18-ቀዳዳ የጎልፍ ኮርስ በሴንት አንድሪስ አባላት ትምህርቱን ከ22 ወደ 18 ጉድጓዶች ሲያሻሽሉ ተፈጠረ።በአለም ላይ እጅግ ጥንታዊው የጎልፍ ውድድር እና በጎልፍ ውስጥ የመጀመሪያው ትልቅ ሻምፒዮና የሆነው ዘ ክፍት ሻምፒዮና በየአመቱ ይጫወታሉ። በሐምሌ ወር ሶስተኛው አርብ ቅዳሜና እሁድ. ራግቢ ሊግ በ 1895 በሁደርስፊልድ ፣ ዌስት ዮርክሻየር የጀመረ ሲሆን በአጠቃላይ በሰሜን እንግሊዝ ውስጥ ይጫወታል። አንድ ነጠላ 'የታላቋ ብሪታኒያ አንበሶች' ቡድን በራግቢ የአለም ዋንጫ እና የሙከራ ግጥሚያ ጨዋታዎች ተወዳድሮ ነበር፣ ነገር ግን ይህ በ2008 እንግሊዝ፣ ስኮትላንድ እና አየርላንድ እንደ ተለያዩ ሀገራት ሲወዳደሩ ተለወጠ። ታላቋ ብሪታንያ አሁንም እንደ ሙሉ ብሔራዊ ቡድን ሆና ቆይታለች። ሱፐር ሊግ በዩኬ እና በአውሮፓ ከፍተኛው የፕሮፌሽናል ራግቢ ሊግ ነው። ከሰሜን እንግሊዝ 11 ቡድኖችን ያቀፈ ሲሆን እያንዳንዳቸው ከለንደን፣ ዌልስ እና ፈረንሳይ አንድ ቡድን ናቸው። በቦክስ ውስጥ የአጠቃላይ ህጎች ኮድ የሆነው '' የተሰየመው በ 1867 በኩዊንስቤሪ 9ኛ ማርከስ በጆን ዳግላስ ስም የተሰየመ ሲሆን የዘመናዊ ቦክስ መሰረትን ፈጠረ። ስኑከር የዩናይትድ ኪንግደም ታዋቂ የስፖርት ኤክስፖርት አንዱ ሲሆን የአለም ሻምፒዮናዎች በየዓመቱ በሼፊልድ ይካሄዳሉ። በሰሜን አየርላንድ የጌሊክ እግር ኳስ እና መወርወር በተሳታፊም ሆነ በተመልካቾች ዘንድ ተወዳጅ የቡድን ስፖርቶች ናቸው። በዩኬ እና በዩኤስ ያሉ የአየርላንድ ስደተኞችም ይጫወቷቸዋል። (ወይም ) በስኮትላንድ ደጋማ ቦታዎች ታዋቂ ነው። የሃይላንድ ጨዋታዎች በፀደይ እና በበጋ በስኮትላንድ ውስጥ ይካሄዳሉ፣ የስኮትላንድ እና የሴልቲክ ባህል እና ቅርስ በተለይም የስኮትላንድ ሀይላንድን ያከብራሉ። ዩናይትድ ኪንግደም በ1908፣ 1948 እና 2012 የበጋ ኦሊምፒክ ጨዋታዎችን ለሶስት ጊዜያት አስተናግዳለች፣ ለንደን የሶስቱንም ጨዋታዎች አስተናጋጅ ሆናለች። በበርሚንግሃም ሊካሄድ የታቀደው የ2022 የኮመንዌልዝ ጨዋታዎች እንግሊዝ ለሰባተኛ ጊዜ የኮመንዌልዝ ጨዋታዎችን ስታዘጋጅ ነው።
4129
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%96%E1%88%AD%E1%8B%8C%E1%8B%AD
ኖርዌይ
ኖርዌይ ፣ በይፋ የኖርዌይ መንግሥት ፣ በሰሜን አውሮፓ ውስጥ ኖርዲክ ሀገር ናት ፣ የዋናው መሬት ግዛት የምእራባዊ እና ሰሜናዊውን የስካንዲኔቪያን ባሕረ ገብ መሬትን ያጠቃልላል። የራቀ የአርክቲክ ደሴት ጃን ማየን እና የስቫልባርድ ደሴቶች የኖርዌይ አካል ናቸው። ቡቬት ደሴት፣ በሱባታርክቲክ ውስጥ የምትገኘው፣ የኖርዌይ ጥገኝነት ነች። እንዲሁም የጴጥሮስ 1 ደሴት እና የኩዊን ሞድ ምድር የአንታርክቲክ ግዛቶችን የይገባኛል ጥያቄ ያቀርባል። የኖርዌይ ዋና ከተማ እና ትልቁ ከተማ ኦስሎ ነው። ኖርዌይ በድምሩ 385,207 ስኩዌር ኪሎ ሜትር (148,729 ካሬ ማይል) ያላት ሲሆን በጥር 2022 5,425,270 ህዝብ ነበራት። ሀገሪቱ በ1,619 ኪሜ (1,006 ማይል) ርዝመት ያለው ረጅም ምስራቃዊ ድንበር ከስዊድን ጋር ትጋራለች። በሰሜን ምስራቅ ፊንላንድ እና ሩሲያ እና በስካገርራክ የባህር ዳርቻ በደቡብ ፣ በሌላኛው በኩል ዴንማርክ እና እንግሊዝ ናቸው። ኖርዌይ ከሰሜን አትላንቲክ ውቅያኖስ እና ከባረንትስ ባህር ጋር ትይዩ ሰፊ የባህር ዳርቻ አላት። የባህር ላይ ተጽእኖ የኖርዌይን የአየር ንብረት ይቆጣጠራል, በባህር ዳርቻዎች ላይ መጠነኛ ዝቅተኛ የሙቀት መጠኖች; የውስጠኛው ክፍል ቀዝቀዝ እያለ ፣እንዲሁም በሰሜን ኬክሮስ ላይ ካሉ ሌሎች የአለም አካባቢዎች በጣም ገር ነው። በሰሜናዊው የዋልታ ምሽት እንኳን, ከቅዝቃዜ በላይ ያለው የሙቀት መጠን በባህር ዳርቻ ላይ የተለመደ ነገር ነው. የባህር ላይ ተጽእኖ በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች ከፍተኛ ዝናብ እና የበረዶ ዝናብ ያመጣል. የግሉክስበርግ ቤት ሃራልድ አምስተኛ የኖርዌይ ንጉስ ነው። ኤርና ሶልበርግን በመተካት ዮናስ ጋህር ስቶሬ ከ2021 ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል። ኖርዌይ ሕገ መንግሥታዊ ንጉሣዊ ሥርዓት ያላት አሃዳዊ ሉዓላዊ አገር እንደመሆኗ መጠን የመንግሥትን ሥልጣን በፓርላማ፣ በካቢኔና በጠቅላይ ፍርድ ቤት መካከል ትከፋፍላለች፣ በ1814 ሕገ መንግሥት ይወሰናል። ግዛቱ የተመሰረተው በ872 የበርካታ ጥቃቅን መንግስታት ውህደት ሲሆን ለ1,150 አመታት ያለማቋረጥ ኖሯል። ከ1537 እስከ 1814፣ ኖርዌይ የዴንማርክ – ኖርዌይ ግዛት አካል ነበረች፣ እና ከ1814 እስከ 1905፣ ከስዊድን መንግስት ጋር በግላዊ ህብረት ውስጥ ነበረች። ኖርዌይ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ገለልተኛ ነበረች እና እስከ ሚያዚያ 1940 ድረስ አገሪቱ በናዚ ጀርመን በተወረረችበት እና እስከ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ ድረስ ቆየች። ኖርዌይ በሁለት ደረጃዎች የአስተዳደር እና የፖለቲካ ንዑስ ክፍሎች አሏት-አውራጃዎች እና ማዘጋጃ ቤቶች። የሳሚ ህዝብ በሳሚ ፓርላማ እና በፊንማርክ ህግ በኩል በባህላዊ ግዛቶች ላይ የተወሰነ መጠን ያለው የራስን እድል በራስ የመወሰን እና ተጽእኖ ይኖረዋል። ኖርዌይ ከአውሮፓ ህብረት እና ከአሜሪካ ጋር የጠበቀ ግንኙነት አላት። ኖርዌይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ኔቶ፣ የአውሮፓ ነፃ ንግድ ማህበር፣ የአውሮፓ ምክር ቤት፣ የአንታርክቲክ ስምምነት እና የኖርዲክ ካውንስል መስራች አባል ነች። የአውሮፓ ኢኮኖሚ አካባቢ፣ እና አባል; እና የ አካባቢ አካል. በተጨማሪም የኖርዌይ ቋንቋዎች ከዴንማርክ እና ከስዊድን ጋር የጋራ ግንዛቤን ይጋራሉ። ኖርዌይ የኖርዲክ የበጎ አድራጎት ሞዴልን ከአለም አቀፍ የጤና እንክብካቤ እና አጠቃላይ የማህበራዊ ደህንነት ስርዓት ጋር ትይዛለች፣ እና እሴቶቿ በእኩልነት አስተሳሰብ ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የኖርዌይ ግዛት በፔትሮሊየም ፣ በተፈጥሮ ጋዝ ፣ በማዕድን ፣ በእንጨት ፣ በባህር ምግብ እና በንፁህ ውሃ ውስጥ ትልቅ የባለቤትነት ቦታዎች አሉት ። የፔትሮሊየም ኢንዱስትሪው የአገሪቱን አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒ) ሩቡን ይይዛል። በነፍስ ወከፍ፣ ኖርዌይ ከመካከለኛው ምስራቅ ውጪ በነዳጅ እና በተፈጥሮ ጋዝ ከፍተኛ መጠን ያለው የአለም ቀዳሚ ነች። ሀገሪቱ በአለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ዝርዝር ውስጥ ከአለም በአራተኛው ከፍተኛ የነፍስ ወከፍ ገቢ አላት። በሲአይኤ የሀገር ውስጥ ምርት () የነፍስ ወከፍ ዝርዝር (2015 ግምታዊ) የራስ ገዝ ግዛቶችን እና ክልሎችን ጨምሮ፣ ኖርዌይ በአስራ አንድ ደረጃ ላይ ትገኛለች። 1 ትሪሊየን ዶላር ዋጋ ያለው የአለም ትልቁ የሉዓላዊ የሀብት ፈንድ አላት። ኖርዌይ ከ 2009 ጀምሮ በዓለም ላይ ከፍተኛውን የሰብአዊ ልማት መረጃ ጠቋሚ አላት ። ይህ ቦታ ቀደም ሲል በ 2001 እና 2006 መካከል ይገኝ ነበር ። በ 2018 ከፍተኛውን በእኩልነት የተስተካከለ ደረጃ አላት ። ኖርዌይ በ 2017 የአለም ደስታ ሪፖርት ላይ አንደኛ ሆናለች እና በአሁኑ ጊዜ በ የተሻለ ህይወት ማውጫ ፣ የህዝብ ታማኝነት ማውጫ ፣ የነፃነት መረጃ ጠቋሚ እና የዲሞክራሲ መረጃ ጠቋሚ አንደኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ኖርዌይ እንዲሁ በአለም ላይ ካሉ ዝቅተኛ የወንጀል ደረጃዎች አንዷ ነች። ምንም እንኳን አብዛኛው የኖርዌይ ህዝብ የኖርዌይ ብሄረሰብ ቢሆንም በ21ኛው ክፍለ ዘመን ኢሚግሬሽን የህዝብ ቁጥር እድገትን ከግማሽ በላይ ይይዛል። እ.ኤ.አ. በ 2021 በሀገሪቱ ውስጥ አምስት ትልልቅ አናሳ ቡድኖች የፖላንድ ፣ የሊትዌኒያ ፣ የሶማሌ ፣ የፓኪስታን እና የስዊድን ስደተኞች ዘሮች ነበሩ። ዋቢ ምንጮች
10082
https://am.wikipedia.org/wiki/20%E1%8A%9B%E1%8B%8D%20%E1%88%9D%E1%8B%95%E1%89%B0%20%E1%8B%93%E1%88%98%E1%89%B5
20ኛው ምዕተ ዓመት
1901 ዓ.ም. መስከረም 26 ቀን፦ ኦስትሪያ-ሀንጋሪ ከ1870 ዓ.ም. ጀምሮ በጥብቅ ግዛትነት ያስተዳደረችው የኦቶማን መንግሥት ክፍላገር የሆነው ቦስኒያ «በይፋ» ወደ ኦስትሪያ-ሀንጋሪ ተጨመረ። ጥቅምት 8 ቀን፦ የቤልጅግ ንጉሥ 2 ሌዎፖልድ ግዛት የነበረው ኮንጎ ነፃ መንግሥት «በይፋ» ቅኝ አገር የቤልጅግ ኮንጎ ሆነ። 1902 ዓ.ም. ግንቦት 23 ቀን፦ አራት የብሪታንያ ቅኝ አገሮች አንድላይ ተዋህደው የደቡብ አፍሪካ ኅብረት የተባለ የብሪታንያ ግዛት ሆነ። ነሐሴ 16 ቀን፦ ጃፓን ከ1897 ዓም ጀምሮ በጥብቅ ግዛትነት ያስተዳደረችው ኮርያ አገር «በይፋ» ወደ ጃፓን ግዛት ተጨመረ። 1904 ዓ.ም. ታኅሣሥ 19 ቀን፦ ሞንጎሊያ ከነታኑ ኡሪያንኻይ ነጻነታቸውን ከቻይና ጪንግ መንግሥት አወጁ። መጋቢት 21 ቀን፦ የፌዝ ውል፣ በዚህ ውል ሞሮኮ የፈረንሳይ ጥብቅ ግዛት ሆነ። 1905 ዓ.ም. ኅዳር 18 ቀን፦ ፈረንሳይ የሞሮኮ ስሜናዊና ደቡባዊ ክልሎች ለእስፓንያ ጥብቅ ግዛት እንዲሆኑ መስጠቷን ተዋወለች። ኅዳር 19 ቀን፦ አልባኒያ ነጻነቱን ከኦቶማን መንግሥት አወጀ። የካቲት 6 ቀን፦ ቲበት ነጻነቱን ከቻይና አወጀ። 1906 - 1ኛ አለማዊ ጦርነት በአውሮፓ ጀመረ። 1907 - የደቡብ አፍሪካ ጭፍሮች ጀርመን ደቡብ-ምዕራባዊ አፍሪካ (ናሚቢያ) ወረሩ። ጳጉሜ 1 ቀን - ታንክ የሚባል የጦርነት መሳርያ ለመጀመርያ ጊዜ በእንግሊዞች ተፈተነ። 1911 - በሳንዠርመን ውል ዩጎስላቪያ፣ ሃንጋሪና ቸኮስሎቫኪያ ከኦስትሪያ ነጻነታቸውን አገኙ። 1912 - ፖሎኝ በዋርሳው ውጊያ በሩሲያ ቀይ ጭፍሮች ላይ ያሸነፋል። ነሐሴ 20 ቀን - ሴቶች በአሜሪካ ዩናይትድ እስቴት የምርጫ መብት አገኙ። 1914 - ቱርኮች በግሪክ-ቱርክ ጦርነት አሸንፈው ስምርኔስ ከተማ ተቃጠለ። 1915 - የእንግሊዝ አስተዳደር በፍልስጤም ጀመረ። ነሐሴ 26 ቀን - ታላቅ ምድር መንቀጥቀጥ በጃፓን መቶ ሺህ የሚያህሉ ሰዎች ገደለ። 1920 - ጦርነት የሚከላከል የኬሎግ-ብሪያንድ ውል በ60 አገሮች ተፈረመ። - የዓለሙ መጀመርያው ቴሌቪዥን ስርጭት ፈተና ተደረገ። 1921 - ሄርበርት ሁቨር የአሜሪካ ፕረዝዳንት ሆነ። - የእስቶክ ገበያ ውድቀት በመከሠቱ የመላ አለም ምጣኔ ሀብት ወደ 'ታላቁ ጭፍግግ' በ1 አመት ውስጥ ቶሎ ወረደ። 1924 - ጃፓን ማንቹርያን ወረረ። 1928 - የሙሶሊኒ ፋሺስታዊ ሠራዊቶች አገራችንን ኢትዮጵያን ወረሩ። 1931 - ሂትለርና ስታሊን በሥውር ፊርማ ፖሎኝን አካፈሉ። ነሐሴ 26 ቀን - አዶልፍ ሂትለር ፖሎኝን በመውረሩ ሁለተኛ ዓለማዊ ጦርነት ጀመረ። 1932 - ጀርመኖች በ2ኛ ዓለማዊ ጦርነት ለንደንን በቦምብ ለመደብደብ ጀመሩ። 1934 - የአላም አል ሓልፋ ውጊያ በጀርመንና እንግሊዝ ታንኮች መኃል በግብፅ በረሃ ጀመረ። ኅዳር 18 ቀን - የፋሺስት ኢጣሊያ ሠራዊቶች በኢትዮጵያ ልጆችና አባቶቻችን አርበኞት ጎንደር ላይ ተሸንፈው አገራችንን ለቀቁ። ጳጉሜ 5 ቀን - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት የጓደኞች ሃያላት በማጁንጋ ማዳጋስካር ደረሱ። 1935 - የጓደኞች ወታደርና 1,800 የጣልያ እስረኞች ተሸክማ ላኮኒያ የምትባል መርከብ አፍሪካን ስትቀርብ በጀርመኖች ተተኩሳ ሰጠመች። ነሐሴ 28 ቀን - በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቹ ሃያላት ተወረረች። ጳጉሜ 3 ቀን - የአሜሪካ ጄኔራል አይዘንሃወር ኢጣልያ እጅ በጦርነት ተሸንፋ እጅ መስጠቷን አወጀ። 1936 - ፓሪስ ከተማ በጓደኞች አርበኞች ከጀርመን ነጻ ወጣች። 1941 - የሶቭየት ኅብረት መጀመርያውን ንዩክሌያር መሣሪያ በፈተና አፈነዳ። 1946 - የቻይና ሃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። 1947 - በኢስታንቡል ቱርክ በኖረበት በግሪክ ህብረተሰብ ላይ እልቂት ተደረገ። 1949 - የአርካንሳው አገረ ገዥ ኦርቪል ፋውበስ ጥቁር ተማሮች ከነጭ ጋራ እንዳይማሩ የክፍላገሩን ወታደሮች በሊተል ሮክ ሰበሰበ። 1951 - የቅብጥ አቡና 6ኛ ቂርሎስ ለኢትዮጵያ የራሱን አቡነ እንዲኖሩት ፈቀዱለት። 1952 - መጀመርያው ሰው ሰራሽ መንኮራኩር (የሩሲያ) ጨረቃን ደረሰ። 1953 - «ኦፐክ» - የዘይት አስወጪ አገሮች ድርጅት - ተመሰረተ። 1954 - መጀመርያ ቴሌቪዥን ግንኙነት በአሜሪካና በአውሮጳ መካከል 1955 - ዶ/ር ማርቲን ሉጠር ኪንግ «እኔ ሕልም አለኝ» ያለበትን ቃል ለሰላማዊ ሰልፍ ተናገረ። 1958 - መጀመርያ የምድር ፎቶ በጨረቃ ምኋር ካለ ሰው ሰራሽ መንኮራኩር ተነሣ። 1959 - ጡርጉድ ማርሻል መጀመርያ አፍሪቃ-አሜሪካዊ የዋና ብሔራዊ ችሎት ፈራጅ ተሾሙ። 1960 - ፈረንሳይ ንዩክሌር ቦምብ በፈተና በመፈንዳቷ ወደ ንዩክሌር ሃያላት ገባች። 1961 - መንፈቅለ መንግስት በሊቢያ ሙአማር ጋዳፊን ከፍ አደረገው። 1963 - በአቲካ እስር ቤት ኒው ዮርክ ሁከት ተደረገ። 1966 - ጊኔ-ቢሳው ነጻነቱን ከፖርቱጋል አገኘ። 1969 - የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተር የፓናማ ካናል አስተዳደር ለፓናማ በ1992 ዓ.ም. ለማዛወር ውል ፈረሙ። 1970 - የጸረ-አፓርትሃይድ ወኪል ስቲቭ ቢኮ በደቡብ አፍሪካ ፖሊስ ታስሮ ተገደለ። 1972 - ነጻነት ለቨንዳ ተሰጠ - ይህ ግን ከደቡብ አፍሪካ ውጭ አልተቀበለም። 1975 - የኮሪያ አየር መንገድ አይሮፕላን በሶቭየት ኅብረት ላይ ሲተኮስ 269 መንገደኞች ሞቱ። 1978 - በመርዝ ጋዝ አደጋ በካሜሩን 1700 ሰዎች ሞቱ። ጳጉሜ 2 ቀን - ዴስሞንድ ቱቱ በኤጲስቆፖሳዊ ቤተክርስቲያን በደቡብ አፍሪካ መጀመርያ ጥቁር ኤጲስ ቆጶስ ሆኑ። 1979 - የሬጌ ሙዚቃ ዘፋኝ ፒተር ቶሽ ቤቱ በኪንግስተን ጃማይካ በሌቦች ተገደለ። 1981 - ቮየጀር የተባለ ሰው ሰራሽ መንኮራኩር በኔፕቱን ፈልክ አለፈ። 1982 - የብረት መጋረጃ በኰሙኒስት ሃንጋሪና በኦስትሪያ መሃል ተከፍቶ ወዲያው ብዙ ሺህ ጀርመኖች ወደ ምእራብ ፈለሱ። ነሐሴ 22 ቀን - ሳዳም ሁሰይን ኩወይት የኢራቅ ክፍላገር ነው ይላል። 1983 - ዑዝበክስታን ነጻነቱን ከሶቭየት ኅብረት አዋጀ። 1984 - ፓስካል ሊሱባ በኮንጎ ሪፑብሊክ ምርጫ ፕሬዚዳንት ሆኑ፤ ይህ ምርጫ የረጅም ዘመን አንድ ፓርቲ ግዛት ጨረሰ። 1985 - መይ ካሮል ጀሚሶን መጀመርያ ጥቁር አሜሪካዊት በጠፈር ሆነች። 1987 - ናቶ በቦስኒያ ሰርቦች ላይ ዘመቻ ጀመረ። 1988 - የራፕ ሙዚቃ ተጫዋች ቱፓክ ሻኩር በላስ ቬጋስ ተተኲሶ ተገደለ። 1989 - በእስላም ታጣቂዎች በአልጄሪያ በተገረገ እልቂት 60-100 ሰዎች ተገደሉ። 1990 - ስሜን ኮሪያ የራሱን ሰው ሠራሽ መንኮራኩር መጀመርያ ጊዜ ላከ። 1994 - አራት አውሮፕላኖች በአረብ ታጣቂዎች ተሰርቀው በአለም ንግድ ሕንጻና በፔንታጎን ተጋጭተው 3000 ያህል ሰዎች ተገደሉ። ነሐሴ 20 ቀን - የምድር ጉባኤ ስብሰባ በጆሃነስበርግ ደቡብ አፍሪቃ ጀመረ። ጳጉሜ 5 ቀን - ገለልተኛ አገር የሆነ ስዊስ በመጨረሻ የተባበሩት መንግስታት አባል ሆነ። 1996 - ስዊድን በምርጫ ለዩሮ እምቢ አለች። ክፍለ ዘመናት
3270
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%B8%E1%8C%8B%E1%8B%AC%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A8%20%E1%88%98%E1%8B%B5%E1%88%85%E1%8A%95
ጸጋዬ ገብረ መድህን
ፀጋዬ ገብረመድኅን ቦዳ ተብላ በምትታውቅ አምቦ ካተማ አካባቢ በምትገኝ ተራራማ ቦታ ተወለዱ። በአምቦ ማአረገ ሕይወት ቀ.ኃ.ሥ. ትምህርት ቤት ከዚያም ጀነራል ዊንጌትና በአዲስ አበባ የንግድ ትምህርት ቤት በአገር ውስጥ ትምህርታችውን ከገፉ በኋላ በቺካጎ ብላክስቶን በህግ ትምህርት ተመርቀው በ1952 እንደ ወጡ በለንደን ከተማ የቴአትር ትምህርት በሮያል ኮርት ቴአትርና በፓሪስ ኮሜዲ ፍራንሴዝ ተከታትለዋል። ከ1954 እስከ 1964 የብሔራዊ ቴአትር በአርቲስቲክ ዳይሬክተርነት አገለግለዋል። ከዚያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ዲፓርትመንትን አቋቁመዋል። ሆኖም በ1960ዎቹ ደርግ አብዛኛውን የቴአትር ሥራዎቻቸውን ሲያግድ እሳቸውንም ለማሰር በቅቷል። ብላቴን ሎሬት ጸጋዬ በርካታ ግጥሞችን፥ የቴአትር ሥራዎችን የተለያዩ መጣጥፎችንና ዘፈኖችን አበርክታዋል። ጸጋዬ በ1990 ለጉበት በሽታ ሕክምና በመሻት ወደ ማንሃታን በሄዱበት አርፈዋል። በአዲስ አበባ በቅድስት ሥላሴ ቤተክርቲያን ተቀብረዋል። ነፍሳቸውን በአብርሃም እቅፍ ያኑርልን:: እንደ፡ አዉሮፓ፡ አቈጣጠር፡ በ 2002 ዓ.ም. የብላቴን ሎሬት ጸጋዬ፡ ገብረ መድህን፡ ግጥም፡ አዲስ፡ በተመሰረተው፡ የአፍሪካ፡ ኣንድነት፡ ማሕበር፡ በሕዝብ፥ መዝሙርነት፡ ተመርጧል። ከሳቸዉ፡ ጽሁፎች፡ መካከል፡ የሚከተሉት፡ ዪገኛሉ ። ዝክረ ፀጋዬ< ብላቴን ጌታ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድሕን እነሆ በሞት ከተለየን ድፍን አራት አመታት ተቆጠሩ። ትዝታም አራተኛ ሙት አመቱን በማሰብ ስራዎቹን በግርድፉም ቢሆን በማውሳት እነሆ የፀጋዬ ዝክር ትላለች።< የእረፍት ዋዜማ፦< ፀጋዬ ከማረፉ አራት አመታት ቀደም ብሎም በዶ/ር ኄራን ሠረቀብርሃን አማካይነት በዋሽንግተን ዲሲ የፀጋዬ ግጥሞች በሲዲ ተቀርፀው ተመርቀዋል። 1 የስንብት ዝግጅት ይሆን። ትንቢት አስቀድሞ ለነገር እንዲሉ።< ፀጋዬ ከማረፉ አስራ አምስት ቀን አስቀድሞ የ«አንድምታ» ባልደረባ አናግሮት ነበር። እስኪ ሁለቱን የሎሬት ፀጋዬን ጥኡም ወጎች ላስቀድም።< በአፄ ምኒልክ ዘመን እንግሊዞች ቱርካና ሃይቅ አካባቢ ዝሆን ያድኑ ነበርና አንዴ አደናቸውን ተከትለው ሲገስግሱ ከኢትዮጵያ ኬላ ደርሰው ኖሮ ድንበር አላሳልፍ ካሉ የኬላ ጠባቂዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ይደረግና ከአዳኞቹ አንዱ በዚሁ ምክንያት ይሞታል። እንግሊዞችም አቤቱታ ያሰሙና ነገሩ አባ መላ (ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ) ዘንድ ይደርሳል። እንግሊዞቹ ያለአግባብ ሰው እንደተገደለባቸው አመልክተው የደም ካሳ እንዲሆናቸው ከኢትዮጵያ ድንበር ውስጥ መሬት እንዲሰጣቸው ነበር የጠየቁት። አባመላ ነገሩን ያጠኑና ችግር እንደሌለው ለእንግሊዞቹ ይገልጻሉ። ነገሩ ከመፈጸሙ በፊት ግን “ይኸ ህግ እናንተ ሃገርም እንደሚሰራበት ማየት ስለምንሻ በሰነድ መልክ ረቂቁ ካለ እስቲ እንየው። እውነት የእንግሊዝ ሰው የዌልስን ሰው ቢገድል እንግሊዝ ከመሬቷ ለዌልስ የምትሰጥ ከሆነ እኛም እንሰጣለን። እሱም የሚሆነው ለተገደለብን የኬላ ጠባቂ ካሳ የሚሆን ከቱርካና ሃይቅ አካባቢ መሬት ከተረከብን ይሆናል ብለው መለሷቸው።< ሌላው ደግሞ የሎሬት ፀጋዬ ከ«ሕይወት ቢራቢሮ» መታተም ጋራ ተያይዞ ለአንድምታ ባልደረባ ያወጋው ነው። መጀመሪያ የግጥሟን ቅንጫቢ ነቢይ መኮንን ከተረካው እነሆ!]]< «...ምን አይተሻል ከቄጤማ፣ ምን አይተሻል ከለምለሙ< ቀን አብረሽ አብበሽ ውለሽ፣ ሲመሽ አብረሽ መስለምለሙ?...< አስተምሪኝ ቢራ ቢሮ፣ ሰው ለመባል አለኝታዬ< ቀድሞ የት ነው መነሻዬ& ሲመሽ የት ነው መድረሻዬ...< ሲተረትማ ሲወጋ፣ ከየብልጭታው ውጋጋን< የሰው አራዊት የአእዋፍ፣ ውስብስብ ነገደ-ጉንዳን< ሲነሳ ሲሮጥ ሲደፋ፣ ሲያጋድል ሲያዛባ ሚዛን< በማይመጠን ታላቅ ኃይል፣ በተፈጥሮ ግዙፍ ሥልጣን< ሊፍተለተል ይወለዳል፣ ሳይነቃ ይወድማል ይባላል< ልደቱ ዕድሜና ሞቱ፣ አለማቋረጥ ይጓዛል፤< ይኸ ይሆን አልፋ - ኦሜጋ? ይኸ ይሆን አስቀድሞ ቃል?» < ፀጋዬ እንዲህ አለ። «እሷ ግጥም በጋዜጣ ታትማ በወጣች ማግስት መንግስቱ ለማ ከቢሮዬ መጥቶ ቢራውን እስቲ አምጣው ወይስ ዝም ብለህ ነው ቢራ ቢሮ ያልከው» ብሎ እንደቀለደብኝ ትዝ ይለኛል።ትንሽ ትከዝ ብሎም «መንግስቱ ምን የመሰለ ደማም ቋንቋ የነበረው ሰው ነበር።አሁን እኮ ደማም ቋንቋ የሚናገር ሰው ሁሉ ጠፋ»።አፈሩ ይቅለለውና ሎሬት ፀጋዬ የኛን ትውልድ <<ጫት አመንዣኪ>> ትውልድ ነበር የሚለው።እንዲህ እንደነሱ ዘመን ባይጎሉም ውድድሩም ቢጠናባቸውም አሁንም እኮ አንቱ የተባሉ ወጣት ደራሲያን ገጣሚያን አሉን። ጊዜው ሲደርስ እንዘክራቸዋለን።< አምቦ አካባቢ ልዩ ስሟ ቦዳ ከኦሮሞና ከአማራ ወገኖቹ የተወለደው ፀጋዬ ገና በልጅነቱ ነበር ሶስቱ ቋንቋዎች አማርኛ፡ እንግሊዘኛና ኦሮሞኛ የተገሩለት። በትምሕርት እየጎለመሰ ሲሄድም ደራሲነቱን ገጣሚነቱን እንዲያ ሲልም ፀሃፊ-ተውኔትነቱን በዋነኛነት በጎልማሳነት ዘመኑ ደግሞ ማህበረሰባዊ ሃያሲነት እና የአፍሪካ የሰው ዘር እና የቅብጥ ቋንቋ እና ባህል ጠቢብነትን አክሎበት እስከ እለተ ህልፈቱ ዘልቋል። በኩላሊት በሽታ መለከፉ እና አለመዳኑን እንዲያም ሲል በጉብዝናው ወራት ያላሰበውን ስደት በሕክምና ሳቢያ የአብራኩ ክፋይ ልጆቹ ወዳሉበት አሜሪካ አቅንቶ በዚያው አሸልቧል። የማሳረጊያ ግጥሙም ይህንን ተስፋ ቢስነትን አመላካች ይሆን።< የማይነጋ ሕልም ሳልም< የማይድን በሽታ ሳክም< የማያድግ ችግኝ ሳርም< የሰው ሕይወት ስከረክም< እኔ ለኔ ኖሬ አላውቅም< እሳት ወይስ አበባ የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች የኢትዮጵያ ሰዎች መደብ:የኢትይዮጵያ ሰዎች
45226
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A3%E1%8B%9E
ኣዞ
ሳይወድሙ ከቀሩት ሕያው ገበሎ አስተኔዎች መካከል አዞዎች ይገኙበታል። እኒህ አዞዎችም በጥቂት ዝርያዎች ብቻ የሚወከሉ ናቸው። በዓለም ላይ 23 የሚሆኑ ዝርያዎች አሏቸው። አዞዎች ረዘም ብሎ ጠንካራ የሆነ የራስ ቅል አላቸው። በዛ ያሉ ጠንካራ ጥርስ አፋቸው ውስጥ ተደርድረው ይታያሉ። ውኃና ምግብ በአፋቸው በያዙበት ጊዜ እንኳን መተንፈስ የሚያስችላቸው ተፈጥሮ አላቸው። አዞዎች እንቁላል ጣዮች ናቸው። ከ20 እስከ 50 እንቁላሎች ብስባሽ ቅጠላ ቅጠሎች ውስጥ ጥለው እናቶቻቸው ይጠብቋቸዋል። ይህም እንቁላሉ ሊፈለፈል ሲቃረብ ከእንቁላሉ ውስጥ የሚሰሙት ድምፅ እንቁላሉን ሰብረው ጫጩቶቹ እንዲወጡ ለማድረግ ያስችላቸዋል። እንደ ኤሊዎችና አንዳንድ እንሽላሊቶች ሁሉ እንቁላሎቹ የተጣሉበት ሁኔታ (ጎጆ) የሙቀት መጠን የሚፈለፈሉትን ጫጩቶች ጾታ ይወስናል። ሆኖም ከኤሊዎች በተቃራኒ የእንቁላሉ ጎጆ የሙቀት መጠን መቀነስ ሴቶችን፣ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ደግሞ ወንዶችን እንዲፈለፈሉ ያደርጋል። አዞዎች ከኢሊጌተሮች በቀላሉ ይለያሉ። የአዞ ጭንቅላት ከዓይኑ አካባቢ ጀምሮ ወደ አፍንጫው ሲወርድ እየጠበበ ይሄዳል። መንጋጋው በሚዘጋበትም ጊዜ ታችኛው መንጋጋ ውስጥ የሚገኘው ትልቅ ጥርስ ወደ ውጭ ይወጣል። የአሊጌተር ጭንቅላት ግን ከዓይኑ ጀምረን ወደ አፍንጫውም ስንሄድ እኩል ስፋት ያለው ነው። ታችኛው መንጋጋ ውስጥ የሚገኘው ጥርስም ገጦ አይወጣም። በዓለም ላይ ሁለት ዓይነት አሊጌተሮች ይገኛሉ። አንደኛው በደቡብ ምሥራቅ አሜሪካ ሌላኛው በቻይና ሲገኝ፤ አዞዎች ግን በሁሉም የዓለም ክፍል ይገኛሉ። ሁሉም አዞቻች አምፊቢየስ ይባላሉ። ምክንያቱም ታዳጊዎቹም ትልልቆቹም ከፊሉን ጊዜያቸውን ውኃ ውስጥ ከፊሉን መት ላይ ስለሚያሳልፉት ነው። በአንፃራዊ ሁኔታ መሬት ላይ ያላቸው እንቅስቃሴ እዚህ ግባ የማይባል ነው። አንዳንድ ጊዜ ሁኔታዎች ሲያስገድዱ ግን አካላቸውን ከፍ በማድረግ አጭርና ወፍራም በሆነ እግራቸው ለአጭር ርቀት በራማያስገርም ፍጥነት ይሮጣሉ። ባሕር ዳርርቻ ላይ ፀሐይ እየሞቀ ያለን አዞ ለመቅረብ በጥንቃቄ መሆን አለበት። ምክንያቱም ብዙዎቹ ሰውን እንዳዩ ወዲያው ወደ ውኃው ዘለው ይገባሉ። አንዳንድ የተራቡ ካሉ ግን በቀጥታ ወደሚጠጋቸው ሰው በመቅረብ ጥቃት ያደርሳሉ። ረጅምና ጠንካራ ጭራቸው እንደ መሣሪያ በማገልገል ሰውንም ሆነ ሌላ እንስሳ ፊቱ ላይ መትቶ በመጣል ለጥርሳቸው ያቀርብላቸዋል። በውኃ ውስጥም ባላቸው ፈጣን እንቅስቃሴ ከእነሱ ለማምለጥ ከባድ ይሆናል። ለረጅም ጊዜ ከውኃ ሥር ሆነው መቆየት ቢችሉም እንደሌሎቹ ገበሎ አስተኔዎች በሳምባ የሚተነፍሱ ናቸው። ስለዚህም አፍንጫቸውን ከውኃው በላይ በማውጣት አየር ይስባሉ። አፍንጫቸው ከላይ ስለሚገኝ ጫፉን ብቻ በማውጣት በቀላሉ አየር ሊስቡ ይችላሉ። ብዙዎቹ አዞዎች ከውኃ ዳርቻ አካባቢ ዋሻ ይሠራሉ። የዋሻው መግቢያ ከውኃው ሥር ሊሆን ቢችልም ብዙው ክፍል ግን ከውኃው በላይ ነው። ዋሻውን ለማረፍና ደኅንነቱን ለመጠበቅ ሲገለገልበት እንዳንዴም አዞው የገደለውን እንስሳ (ሰውን ጭምር) ተሸክሞ ይዞ መጥቶ ተረጋግቶ (ተዝናንቶ) የሚመገብበት ሆኖ ይገኛል። ሁሉም አዞዎች እንቁላል ይጥላሉ። እንደሌሎቹ ገበሎ አስተኔዎችም እንቁላሎቹን መሬት ውስጥ ይቀብራሉ። ሴቶቹ አዞዎች በሚሠሯቸው ጎጆዎች ይለያያሉ። አንዳንዶቹ አሸዋ ውስጥ ቀዳዳ በመቆፈር እንቁላሉን ይቀብሩትና ይሸፍኑታል። ሌሎቹ እንደ አሊጌተር ዓይነቶቹ ብዛት ያለው የበሰበሰ ቅጠላ ቅጠፀል በመሰብሰብ እዛ መሃል እንቁላሉን ይጥሉታል። ብዛት ያላቸው ደርዘን እንቁላሎች (እያንዳንዱ በመጠን ከዶሮ የበለጠ) በአንድ ቁጭታ ሊጥሉ ይችላሉ። ሲፈለፈሉ ታዳጊዎቹ አዞዎች ከ22-25 ሳንቲ ሜትር ቁመት ይኖራቸዋ”ል። አዞዎች ጥርሳቸውን በተደጋጋሚ ይተካሉ። የሚተካው (ያረጀው) ጥርስ ሥር ያለው አዲስ ጥርስ ሲሆን፤ አዲሱ ተኪ ጥርስ አድጎ ትልቅ ካልሆነ በስተቀር አሮጌው ቶሎ ብሎ ወልቆ አይወድቅም። -ማንይንገረው ሸንቁጥ ‹‹ባለአከርካሪዎች›› ሪፖርተር፤ 'ኪንና ባህል' - "አዞዎች" (እሑድ ኅዳር ፲፬ ቀን ፳፻፯ ዓ/ም) ተሳቢ እንስሳ የአዞ አይን 360 ዲግሪ ማየት ይችላል። እንዲሁም ሰው 180 ዲግሪ ዘውሮ ማየት ይችላል።
50920
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%80%E1%8B%AD%E1%88%89%20%E1%8B%88%E1%88%AD%E1%89%81
ሀይሉ ወርቁ
ሀይሉ ወርቁ በኢትዮጵያ ስነፅሑፍ ራሱን በራሱ ስነፅሑፍን በማስተማር ከአስር በላይ መፅሐፍትን የፃፈ ደራሲ ነው። በሦስት ቋንቋም ይፅፋል። ደራሲው ሐይሉ ወርቁ የአስራ አንድ መጽሐፍት ደራሲ፥ ላለፉት አስር ዓመታት በበርካታ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ጥናት አድርጎ ከአስር ባላይ መፅሐፍትን የፃፈ፣ በበርካታ አገራዊ ጥናቶች ላይ የተሳተፈ፣ የመጀመሪያው የአማርኛ ቃላት መሰብሰብ ፕሮጅክት የመራ እና እየሰራ ያለ፣ የውጪ ሐይሎች በኢትዮጵያ የሚሰሩትን የዳርስቶጵያ ፕሮጀክትን በጥናት በተደገፈ ሰነድ ያዘጋጀ እና በዚሁ ጥናት ላይ ተመስርቶም የፓቶጵያ ፍቅር የተሰኘ መፅሐፍ የፃፈ፣ የፒ.ኤች.ዲ ትምህርቱን እየተማረ ያለ ለአገር እና ለወገን ተቆርቋሪ፣ በሥራው ታታሪ ሰው ነው። ሞት በውክልና የመፅሐፊ አጠቃላይ ሁኔታ ሞት በውክልናመፅሐፍ ታሪክ ግጥም የተገጥመለት፣ ዘፈን የተዘፈነለት ድንቅ ታሪክ ነው። ሞት በውክልና በፍቅር ዘውግ የተፃፈ መፅሐፍ ሲሆን ፥ ልብን ትርክክ አድርጎ፣ አኧምሮን በማመራመር ፤ አንጀት የሚያላውስ ድንቅ የፍቅር ታሪክ ላይ የተፃፈ ነው ታሪካዊ መፅሐፍ ነው። ይህ ታሪክ በታገል ሰይፉ ተፅፎ፣ በሀይለየሱስ ግርማ ዜማ ስላዜመለት ሰው ታሪክ ብቻ አይደለም። ያ ሚስኪን ሰው ስላፈቀራት እና በስተመጨረሻ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ፤ ለሦስተኛ ጊዜ ሞተች ተብሎ ዕድርተኛው ቀብሩን ሊቀብር፣ በእአባቷ ግቢ ቢሰበሰብም፤ እሷ ግን ዛሬም እንደ ባለፈው መሞት አቅቷት ክፉኛ ተሰቃይታ፤ ቤተሰቡን እያሰቃየች ስለነበረች እና መሞት አቅቷት በጣዕረ ሞት ከተያዘች እነሆ ዛሬ ዘጠና አራተኛ ስላስቆጠረች ልዩ ሴት ነው። ይህን ባለ 256 ገፅ የሆነው መፅሐፍ፥ የአርታኦት ሥራው የሰራው ታዋቂው አርታኢ እና የፊልም ተዋናይ፣ የአማርኛ ቋንቋና ሥነጽሑፍ ምሩቅ ዳዊት (ዴቮ) ነው። አንድ ሰው ነበረ፤ የተለየ ልብ ያለው። አኧምሮውን ማዘዝ እና ማስቆም የሚችል ልብ። አኧምሮው ሲያስቆመው አካሉም እዛው ተገተረ። ያለ ተስፋ፣ ያለረዳት፣ እዛው እንድቆመ ፤ ለምን እንደሆነ ባላወቀው ምክንያት፣ ሁሉም ነገር በዙሪያው በፍጥነት ይለዋወጥ ነበር። ለተመለከተው ፊቱ ይናገራል፣ እሱ ለውጡ አልገባውም። እዛው በመንገዱ ዳር እንደቆመ መልኩ ጠፉ፣ ውበቱ ረገፈ። ዓመታት አለፉ። መንገደኛው ሁሉ ይህ ሰው ብቸኛ ነው ብሎ ያዝናል። እሱ ግን ለምን እንደታዘነለት፣ ነገሮችም ሁሉ እየተለወጡ መሆናቸውን አያውቅም። በዚያች ቦታ ለዓመታት ከመቆሙ የተንሳ፣ እርሱ የቦታው ምልክት ሆኗል። ሰው ሁሉ ቦታውን ለመለየት የተለየ ሥዕሎች እና ማስታወቂያ አላስፈልገውም። ሰዎች እሱን እዚያ ቦታ ላይ ለሲሶ ምዕተ ዓመት ያህል ዘመን የገተረው ጉዳይ ምን እንደሆነ አያውቁትም፣ ቢያውቁትም አይገባቸውም። ምክንያቱም ሰዎች ሁሉ እሱ ያለው ዓይነት ልብ የላቸውም ! ይህ መፅሐፍ ግን ስለእርሱ ሳይሆን፤ እርሱ ስለሚያውቃት፣ እና መኖርም መሞትም አቅቷት ስለምትሰቃይ ቤተልሔም ስለተባለች ሴት እንጂ። ሁሉም ገፀባህሪያት የየራሳቸው ቀለም አላቸው። ሞትን ለዘጠና አራት ቀናት የተዋጉትን ቀስ አገኘውን፣ ሰላቢዋ ፅጌ፣ ቀላብላባዋ ወ/ሮ ማንጠግቦሽ፣ የሰውን ሚስት ይዞ አሜሪካ በመግባት፣ ሰውን 32 ዓመታት መንገድ ላይ የገተረውን ይሀይስን …. ብቻ ሁሉንም ማንም መርሳት አይችል። አፃፃፉ ዘይቤ በልማዱ የልብ ወለድ ድርሰት ደራሲዎች ከፍ ወይም ዝቅ ብለው የሚገመቱት ለድርሰታቸው የሚፈጥሩት ታሪክ፣ ላንባቢዎች በሚሰጠው ትምህርት እና ታሪኩን በጥሩ አጻጻፍ አስጊጦ ለማቅረብ ባላቸው ችሎታ ነው። ላንባቢዎች አኧምሮ ትምርትን፣ ለልባቸው ደስታን የሚሰጥ ልብ ወለድ ድርሰት ጥሩ ድርሰት ይባላል። እንዲህ ላሉ ድርሰቶች ደራሲዎችም ትልቅ ደራሲዎች ይባላሉ። እኔ ይህች “ሞት በውክልና” ብዬ ሰይሜ ላንባቢዎች የማበረክታት ልብ ወለድ ድርሰት በታሪክዋም ሆነ ባጻጻፍዋ ጥሩ ድርሰቶች የሚባሉት በያዙት ደረጃ እንኩዋንስ ልትደርስ እንደማትቀርብ አውቃለሁ። ነገር ግን ብዙ ጥሩ ድርሰቶች ያልያዙት መልክት ላንባቢዎች ለማድረስ የተሰናዳች ስለሆነችና በተለይ የኢትዮጵያን አንባቢዎች ለሚያሳስቡ እስከ ዛሬ ድረስ መልስ ላላገኙ አንዳንድ ጥያቄዎች መልስ ሊሆኑ የሚችሉ አሳቦች ይዛ ስለምትቀርብ አንባቢዎች ሳይሰለቹ በማስተዋል እንዲመለከቱልኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ሌሎች የደራሲው ሥራዎች በማስተዋል ወደ ባለጠኘት ማደግ የፓቶጵያ ፍቅር ምናሴ መናጢው እና የኢትዮጵያ መምህራን ዕብዱ አጥናፉ ወርቁ ዕጸ ሐበቅ እና ጭራ አልባዎቹ የነፍስ እናት እና ልጇ የዴልታው ጌታ የሁፐስ ፍቅር የጠፏ የአዲስ አበባ ሴቶች ዲ ሳንግዌ የመጨረሻው ወታደር ልጅ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ጸሓፊዎች
9600
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%89%B0%E1%88%A8%E1%89%B5%20%E1%8B%A8
ተረት የ
የሀምሌ ብራ የባልቴት ወብራ የሀምሌን ውሀ ጥም የህዳርን ራብ የሚያውቅ ያውቀዋል የሀምሌ ጭቃ ቅቤ ለጋ የሀር ገመድ የበቅሎ ክበድ የሀብታም ልጅ ሲጫወት የድሀ ልጅ ይሞታል የሀብታም ልጅ ወደ ቦሌ የድሀ ልጅ ወደ ባሌ የሀጢአት ክፉ ጉቦ የበሽታ ክፉ ተስቦ የሀጥኡ ዳፋ ጻድቁን ያዳፋ የሁለት ሴቶች ባል ይሞታል ይበላል ሲባል የሁለት አገር ስደተኛ የሁለት እዳ ከፋይ የኋላ የኋላ አይቀርም ዱላ የህልም ሩጫ የጨለማ ፍጥጫ የሆነ አይመለስ እሳት አይጎረስ የሆድ ማበድ ያስቃል በግድ የሆድ ምቀኛ አፍ ነው የሆድ ምቀኛው አፍ ነው የሆድ ብልሀት የጋን መብራት የሆድ ነገር ሆድ ይቆርጣል የለመነ መነመነ የለመነ ያገኛል የነገደ ያተርፋል የለመኑትን የማይረሳ የነገሩትን የማይረሳ የለመደ ለማኝ ቁርንጮዬን ቀማኝ የለመደ ልማድ ያሰርቃል ከማእድ የለመደ ልማድ ያሰድዳል ከማእድ የለመደ መደመደ የለመደ እጅ ጆሮ ግንድ ያስመታል የለመደ ፈረሰኛ ዛብ አይጨብጥ እርካብ አይረግጥ የለመደች ጦጣ ሁልጊዜ ሽምጠጣ የለማኝ ስልቻ ሲንከባለል ከለማኝ እጅ ይወድቃል የለማኝ ቅንጡ ይላል በወጥ አምጡ የለም ቀሪ ካለ ፈጣሪ የለበሰ የማንንም ጎረሰ የለበሱት ያልቃል የሰጡት ያጸድቃል የለጋስ ምስክሩ መስጠቱ የላሜ ልጅ ያውራዬ ውላጅ የላም መንጃ የሰማ መከንጃ የማር መቅጃ የላም ወተቱን የጌታ ከብቱን የላከ እንደ አፉ ያከከ እንደ እጁ አይሆንለትም የላይ ለምጡን የውስጥ እብጡን ባለቤቱ ያውቀዋል የላይ አልጋ የውስጥ ቀጋ የላይኛው ከንፈር ለክርክር የታችኛው ከንፈር ለምስክር የላጭ ልጅ ጸጉሩ ድሬድ ሆነ የላጭን ልጅ ቅማል በላት የላጭን ልጅ ቅማል በላው ያናጢን ልጅ ጅብ በላው የሌለው ልብም የለው የሌለው ልብ የለው ወዳጅ የለው የሌለው ሚስት የለው ወዳጅ የለው የሌሊት ግስገሳ የቀን ዘለሳ የሌላት እራት ደግሞ ምሳ አማራት የሌባ መኝታው አመድ መታሰሪያው ገመድ የሌባ ምኝታው ካመድ መታሰሪያው ገመድ የሌባ ሞኝ ከጎተራ ስር ይገኝ የሌባ አይነደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ የሌባ እጁን የፍየል ልጁን የሌባ ዋሻ የቀማኛ መሸሻ የሌባን ጠበቃ አደባልቀህ ውቃ የሌባን ጠበቃ ደርበህ ውቃ የልመና በሬ ትክክል አይሄድም የልመና እንጀራ ምንጊዜም ከልመና አያወጣም የልቡ ሳይደርስ እድሜ ይደርስ የልቡን ሲነግሩት የኮረኮሩትን ያህል ይስቃል የልቡን አድራጊ አይናደድም የልብህን ቢያናግሩህ አለ እዳ ቢለቁህ የልብህን ቢያናግሩህ አለ እዳ ቢሰዱህ የልብስ ቀላል ባለቤቱን ያቀላል የልጅ ልጅ እህል ፈጅ ኋላም ጅብ ያስፈጅ የልጅ ልጅ ጅብ አስፈጅ የልጅ መልከ ጥፉ በስም ይደግፉ የልጅ ሞት የእግር እሳት የልጅ ስጋ በናቷ ቅቤ የልጅ ቀላቢ የአህያ ጋላቢ የልጅ ብልጥ እየቀደመ ይውጥ የልጅ ብልጥ የፊት የፊቱን የልጅ ብልጥ የሰጡትን የልጅ እናት አባይ ናት የልጅ ተሟጋች በፊት ሰማይ ያያል ኋላ መሬት የልጅ ተሟጋች ጠዋት ሰማይ ማታ ምድር ምድር ያይ የልጅ ነገር ሁለት ፍሬ አንዱ ብስል አንዱ ጥሬ የልጅ ነገር ጥሬ በገል የልጅ ክፉ ዲቃላ የቤት ክፉ ሰቃላ የልብስ ክፉ ነጠላ የልጅ ክፋቱ አለመከማቸቱ የልጅ ጥፉ በስም ይደግፉ የልጅ ፍቅር የሴት ከንፈር እናትን አያስቀብር የልጅቷን ስጋ በእናቷ ቅቤ የልጅ ፍሬ አንዱ ብስል አንዱ ጥሬ የሎሌ አልቃሽ የሴት ቀዳሽ የሎሌ አልቃሽ የሴት ቀዳሽ የቄስ አውደሽዳሽ የመልኳን ሲሏት የጠባዩዋን የመሬት ሴሰኛ ከመንገድ ዳር ይተኛ የመሬት እርጥብ እሸቱን ደረቅ ምርቱን የመስከረም ውስጡ በጋ ያረመኔ ልቡ ቀጋ የመቀናጆ በሬ ሲመሽ ወደ ቤቱ ይስባል የመበደሪያ አፍ መክፈያ አይሆንም የመተሩበት እጅ ይወዛል የተማከሩት ዳኛ ያግዛል የመታሰር ምልክቱ መጋዝ የመዳኘት ምልክቱ መያዝ የመነነ ከዱር የሞተ ከመቃብር የመነነ ከዱር የሞተ ከመቃብር አይወጣም የመነኩሴ ሎሌ የክረምት አሞሌ የመንማና የለው ገናና የመንታ እናት ተንጋላ ትሞት የመንገድ ዳር እሸት ባል የሌላት ሴት የመንገድ ዳር እሸት ባል የሌላት ሴት ለማንም ናት የመንዝ ልጅ እራያ ሂዶ ብልቱን አያወዛውዝም የመከሩበት ሞተ የወርወሩበት ተሳተ የመከራ ልጅ ሁል ጊዜ መከራ መስሎ ይታያል የመከራ ሌሊት አያልቅም የመከራ ሎሌ መከራ መስሎ ይታያል የመከራ ውዝፍ ያለበት ነጋዴ ከሚወረር አገር ይደርሳል የመከራን ጉድጓድ ሚዳቋ አትዘለውም የመኮንን ልጅ በከተማ የድሀ ልጅ በውድማ የመኮንን ልጅ አዘን ቢነግሩት አደን የመዝሙር መጀመሪያ ሀሌታ የዘፈን መጀመሪያ እስክስታ የመጠጡት ቅልጥም ከብርንዶ ይጥም የመጣ ሳይመጣ የውሃ ቦይ ጥረግ የመጣው ቢመጣ ወይ ፍንክች ያባ ቢላዋ ልጅ የመጣ ቢመጣ ከቤቴም አልወጣ የመጥረቢያ ልጅ መዝለፊያ የመጥረቢያ ልጅ ጥልቆ አይደል የሚባለው የሙሽራ እድሜ ቢያጥር የሰርጉ ድግስ ሆነ ለተዝካር የሙት ቀናተኛ ሚስቴን አደራ ይላል የሙት አልቃሹ የቁም ወራሹ የሙት አልቃሹ የቁም ወራሽ የሙት የለውም መብት የሚሆን ቢሆን ዝሆን ይበላ ቢሆን የሚሉሽን በሰማሽ ገበያም ሳልወጣሽ የሚሉሽን በሰማሽ ገበያም ባልወጣሽ የሚመክተው ጋሻ የሚጠጋበት ዋሻ የሚመክተው ጋሻ የሚጠጋበት ዋሻ የለውም የሚመጣውን እንድታውቅ ያለፈውን እወቅ የሚሞት ልጅ አንገቱ ረጅም ነው የሚሮጡበት ሜዳ የሚወጡበት ቀዳዳ የሚሰራ ምንም አያወራ የሚሰርቀውን ያጣ ሌባ ሰላማዊ መስሎ ይገባ የሚሰርቀውን ያጣ ሌባ ሰላማዊ መስሎ ይገባል የሚሰርቅ ሰው አደራ ቢያስቀምጡት እጅ ይነሳል የሚክድ ሰው አደራ ቢያስቀምጡት እጅ ይነሳል የሚሰጥም እሾህ ይጨብጣል የሚሰጥም ገለባ ይጨብጣል የሚስት መናኝ የእናት አገር ለማኝ የሚስት አንባሻ የጎረቤት ውሻ የደጅ እርሻ የሚስት አሳቢ የጥንድ በሬ ሳቢ ይስጥህ የሚስት ወይዘሮ እርሻው ጋራ ዞሮ የሚስት ዘመድ የማር አንገት የሚስት ዘመድ የማር እንጎቻ የሚሸሹበት አምባ ሲሸሽ ተገኘ የሚበላው ካጣ ይበላለት ያጣ የሚበላው ካጣ ይበላበት ያጣ የሚበጀውን ባለቤት ያውቃል የሚከርመውም የማይከርመውም ባንድነት ዝናብ ይለምናል የሚከርመውም የማይከርመውም አንድነት ዝናብ ይለምናል የሚካኤል ስለት ለገብርኤል ምኑ ነው የሚካኤል እለት ለገብርኤል ምኑ ነው የሚወዱትን ሲያጡ የጠሉትን ይቀላውጡ የሚወዱትን አቅፎ የሚጠሉትን ነቅፎ የሚወዱትን እቅፍ የሚጠሉትን ንቅፍ የሚወጋ ጦር ከእጅ ሲወጣ ያስታውቃል የሚውል ሆድ ማለዳ ያረግዳል የሚውል ሆድ ማለዳ ይርበዋል የሚወጡበት ገደል የሚንጠለጠሉበት ቅጠል የሚጠጉበት ገደል የሚንጠለጠሉበት ቅጠል የሚዛንን አባይ ለእሳት የዳኛን አባይ ለሰንሰለት የሚያልቅ እህል ከማያልቅ ዘመድ ያጣላል የሚያልፍ ቀን የማያልፈውን ስም ያወርሳል የሚያልፍ ቀን የማያልፍ ስም ያወርሳል የሚያልፍ ነገር የማያልፍ ስም ይሰጣል የሚያልፍ ውሀ አደረገኝ ድሀ የሚያልፍ ውሀ አደረገኝ ድሀ አለች ልጅዋን ጎርፍ የወሰደባት የሚያልፍ ዝናም አይምታህ የሚሞት ሽማግሌ አይርገምህ የሚያልፍ ዝናም አይምታህ የሚያድግ ልጅ አይጥላህ የሚያማ ጠበኛ ዘወር ይበል ከኛ የሚያስፈራውን ለሚነግርህ የሚያስቀዝነውን ንገረው የሚያስፈሳውን ለሚነግርህ የሚያስቀዝነውን ንገረው የሚያብረቀርቅ ሁሉ ወርቅ አይደለም የሚያድግ ልጅ በእናቱ እጅ የሚያድግ ልጅ አትበድል የሚሞት ሽማግሌ አታቃልል የሚያድግ ልጅ አትበድል የሚሞት ሽማግሌ አታቅል የሚያድግ ልጅ አይጥላህ የሚሞት ሽማግሌ አይርገምህ የሚያድግ ልጅ አይጥላህ የሚያልፍ ዝናብ አይምታህ የሚያድግ ዛፍ በቁጥቋጦው ያስታውቃል የሚያድግ ዛፍ ከቁጥቋጦው ያስታውቃል የሚያጠግብ ቂጣ ከምጣዱ የሚወጣ ጥጃ ከገመዱ የሚያጠግብ ቂጣ ከምጣዱ የሚወጣ ጥጃ ከገመዱ ያስታውቃል የሚያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል የሚያፈስ ቤት ጨቅጫቃ ሚስት የሚዳቋ ብዛት ለነአቶ ውሻ ሰርግ ነው የሚዳቋ ብዛት ለውሻ ሰርግ ነው የሚዳቋ ግርግርታ ለውሻ ሰርጉ ነው የሚዳቋ ግርግርታ ለውሻ ሰርግ ነው የሚጣፍጥ ምግብ ምንድን ነው ቢሉት ሲርብ የበሉት የሚጣፍጥ ምግብ ሲርብ የበሉት ነው የሚጣፍጥ ምግብ ምንድን ነው ቢሉት ሲርብ የበሉት ነው የሚፈልግ ያገኛል የሚተኛ ያልማል የሚያፈስ ቤት ጨቅጫቃ ሚስት የሚፈርስ ከተማ ነጋሪት ቢመታ አይሰማ የሚፈታ ከተማ አዋጅ ቢነግሩበት አይሰማ የማህበር አሽከር በልቶም አይጠገን ታሞም አይድን የማሚቴን እጅ ያላየ በእሳት ይጫወታል የማሽላ ዘር ከነአገዳው ቸር የማታ ማታ እውነት ይረታ የማታ ማታ ጭምት ይረታ የማታ ምግብ ለእንግዳ የጠዋት ምግብ ለአገዳ የጠዋት መጠጥ ለእዳ የማታ ሩጫ እንቅፋት ትርፉ የማታርፍ ጣት አር ጠንቁላ ወጣች የማታድግ ውርንጫ እናትዋን ትመራለች የማታድግ ጥጃ እናቷ ን ትመራለች የማታ አፍ ከጋን ይሰፋል የማታድግ ፍየል አምስት ትወልዳለች ልጆቹዋም ያልቃሉ እሷም ትሞታለች የማታፍር ድመት ስሜ ገብረማሪያም ነው ትላለች የማትሄድ መበለት ዞራ ዞራ ትሰናበት የማትረባ ፍየል ዘጠኝ ትወልዳለች ዘጠኙም ያልቁና እሷም ትሞታለች የማትሰማው ስድብ ከቀረርቶ ይቆጠራል የማነው እህል ያሰኝሃል ክምር የማነው ቤት ያሰኝሃል አጥር የማን እርሻ ብለህ እረስ የማን ሚስት ብለህ ውረስ የማን ገበሬ ሹሩባ ይሰራል የማን ዘር ጎመን ዘር የማያልፍለት ዘበኛ ከዋርካ ስር አይጠፋም የማያልፍ ነገር የለም ምሽትም በማለዳ ይተካል የማያመሽ ባል ቅንድብ ይስማል የማያስተኛ ነግረውህ ተኝተው ያድራሉ የማያስተኛ ነግረውት ሳይተኛ አደረ የማያበላ ቢገላምጥ አያስደነግጥ የማያበድር ደመና የማይመልስ ቀማኛ የማያበድር ገዳይ የማይመልስ አባይ የማያዋጣ ማህበር በጠጅ ይጀመራል የማያዋጣ ባል ቅንድብ ይስማል የማያውቁት ስድብ ከዘፈን ይቆጠራል የማያውቁት አገር አይናፍቅም የማያውቁትን መስራት ከጥቅሙ ጉዳቱ ይብስ የማያውቁት ምን ያውቅ የማያዛልቅ ጸሎት ለቅስፈት የማያደርግ እንትን ከቤተክርስቲያን ይቆማል የማያድግ ልጅ ባራስ ቤቱ ዳንኪራ ይመታል የማያድግ ልጅ ታዝሎ ያፏጫል የማያድግ ልጅ ቅዘን ይበዛዋል የማያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል የማያድግ ጥጃ ከበሬ ፊት ይነጫል የማያግዙ በፈር ያግዛሉ በከንፈር የማያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል የማያፍር እንግዳ ባለቤቱን ይጋብዛል የማይሆን ነገር የተገላቢጦሽ ያችን ላንቺ ማናለሽ የማይመለስ ማር ሹመኛ ይበደረዋል የማይመስል ነገር ለሚስትህ አትንገር የማይመስል ነገር ለሴት አትንገር የማይመቱት ልጅ ሲቆጡት ያለቅሳል የማይመቱት ልጅ ቢቆጡት ያለቅሳል የማይሰማ ሰው ልቤን አፈረሰው የማይሰማ ጆሮ ከጎረቤት ያጣላል የማይሰራ አይብላ የማይረዳ አይጥላ የማይስማሙ ዝንቦች ጥምብ ይልሳሉ የሚስማሙ ንቦች ማር ይጎርሳሉ የማይቀርልህን እንግዳ አጥበቀህ ሳመው የማይቀና ባይወለድ የማያስብ ባይነግድ የማይቀና ባይወለድ የማያስብ ባይነግድ ይሻላል የማይቀና ባይወልድ የማያስብ ባይነግድ የማይቀና ባይወልድ የማያስብ ባይነግድ ይሻላል የማይበሉት እህል ከአፈር እኩል ነው የማይበላ የለም የማይጠግብ ባሰ የማይተማመኑ ባልንጀሮች በየወንዙ ይማማላሉ የማይተማመኑ ባልንጀሮች እየወንዙ ይማማላሉ የማይተማመን ባልንጀራ በየወንዙ ይማማላል የማይተች አይፍረድ የማያተርፍ አይነግድ የማይቻል ጠላት ስለ ወዳጅ ይቆጠራል የማይቻል ጠላት ከወዳጅ ይቆጠራል የማይችሉት ድንጋይ ሲያወጡት ደረት ሲያወርዱት ጉልበት ይመታል የማይከፍል ባለእዳ የሰጡትን ይቀበላል የማይነጋ መስሏት እቋቱ ላይ አራች የማይዘልቅ ማህበር በጠጅ ይጀመራል የማይዘልቅ ማህበር አሜሪካ ይጀመራል የማይዘልቅ ባል ቅንድብ ይስማል የማይዘልቅ ጸሎት ለቅስፈት የማይደርሱበትን አያኩም የማይድን በሽተኛ በጥር እሸት አምጡ ይላል የማይድን በሽተኛ በበጋ እሸት አምጡልኝ ይላል የማይድን በሽተኛ የማይመለስ ሀጢአተኛ የማይድን ባህታዊ ወተት አምጡ የማይድን ፉቅራ ጠላ ስጡ የማይገባ ሱሪ የማይበቅል ዘሪ የማይጠረጥር ቤቱን አያጥር የማይጣሉ መላእክት የማይታረቁ አጋንንት የማይጽፍ ደብተራ ክንፍ የሌለው አሞራ የማይፈርስ ምሽግ የለም የማይፈወስ ድዉይ የማይመለስ ጊጉይ የሜዳ ንስንሱን የቤት ጉስጉሱን የሜዳ ንስንሱን የቤት ጉዝጓዙን የምህረት ጎደሎ የባሪያ ወይዘሮ የምላስ ወለምታ ሪፈር የለውም የምላስ ወለምታ በቅቤ አይታሽም የምላስ ጦር ቢታከም አይድንም የምመክተው ጋሻ የምጠጋበት ዋሻ የምሮጥበት ሜዳ የምወጣበት ቀዳዳ የለም የምስራች በቃሏ መላች የምስራች በቃሏ መጣች የምበላው ሳጣ ልጄ ጥርስ አወጣ የምበላው ሳጣ ማእቀብ ሊጣል ነው የምታሸንፈውን ምታ ቢሉት ወደ ሚስቱ ሮጠ የምትለብሰው የላት ሻንጣ ቆለፈች የምትለብሰው የላት የምትከናነበው አማራት የምትመክተው ጋሻ የምትሰወርበት ዋሻ የምትሮጥበት ሜዳ የምትገባበት ቀዳዳ የምትበላው እህል ከማታየው መሬት ይበቅላል የምትታጠቀው የሌላት የምትከናነበው አማራት የምትነቃነቅ ግንድና የምትስቅ ሴት ልብ ሩቅ ነው የምትኮነን ነፍስ ጎረቤት ያውቃታል የምትጠላው ሰው ፈሱ እሆዱ ውስጥ ሳለ ይሸታል የምትጠላውን የምትወደውን ሰጥተህ ሸኘው የምትጠባ ጥጃ አትጮህም የምትጠባ ጥጃ አትጮህም የማይደርሱበትን አያኩም የምኞት ፈረስ ልጓም አይገታውም የምናውቃትን ክምር በድባብ ሸፈኑዋት የምድሩን በአፍ የሰማዩን በመጣፍ የምጣዱ ሳለ የእንቅቡ ተንጣጣ የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጫጫ የምጥ መድሀኒቱ አንድ እግር ማስቀደም ነው የሞላለት ድመት በሞዝቮልድ ይተኛል የሞላለት ድመት ሳንባ ያማርጣል የሞተ ልጅ አንገቱ ረጅም ነው የሞተ ቢሞት ያለን እንጫወት የሞተ አይከሰስ የፈስስ አይታፈስ የሞተው ባልሽ የገደለው ውሽማሽ የሞተው ባልሽ ገዳዩ ወንድምሽ (ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ) የሞተ ያልነበረ ይመስላል ያለ የማይሞት ይመስላል የሞተን አትርሳ የወደቀን አንሳ የሞተውን አያ ይለዋል የሞት በደለኛ አያይዞ በዳኛ የሞኝ ለቅሶ መልሶ መልሶ የሞኝ ልቅሶ መልሶ መልሶ የሞኝ ልጅ ባባቱ ምን ይጫወታል አሉ የሞኝ ሚስት በምልክት የሞኝ ምስጋና የግንቦት ደመና የሞኝ ቄስ ጸሎት ዘወትር አቡነ ዘበሰማያት የሞኝ በትር ሆድ ይቀትር የሞኝ እጁን ሁለት ጊዜ እባብ ነከሰው አንድ ጊዜ ሳያይ ሁለተኛው ሲያሳይ የሞኝ ዘመድ ያፍራል የሞኝ ዘፈን ሁልጊዜ አበባዬ የሞኝን ጠላ በለው በአንኮላ የሞኝ ጀርባ ሲመታ ለአዋቂ ይስማማል የሞኝን ጥርስ ብርድ ፈጀው የሞኝ ገበሬ እርሻ በሰኔ የረጋ ወተት ምርጫ ይደገምለታል የረጋ ወተት ቅቤ ይወጣዋል የራሷ ሲያርባት የሰው ታማስላለች የራስህን አትበላ ገንዘብ የለህ የሰው አትበላ ዐመል የለህ የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች የራስዋ እያረረባት የስው ታማስላለች የሰማ ያውራ ያየ ይናገር የሰካራም ግጥም ሁልጊዜ ቅዳ ቅዳ የሰው አመሉ ዳውላ ሙሉ መቼ ያስታውቃል አብረው ካልዋሉ የሰው አገሩ ምግባሩ የከብት አገሩ ሳሩ የሰው አገር ዝናብና የእንጀራ አባት አይምታህ የሰው እንጂ የቃል ውሸት የለም የሰው ወርቅ አያደምቅ የሰው ፈላጊ የራሱን ያጣል የሴት ምራቋ ወፍራም ነው የሴትን ብልሀት የጉንዳንን ጉልበት ይስጥህ የሴት አገር ባልዋ የሴት አጭር ወይዘሮ የወንድ አጭር አውራ ዶሮ የሴት ጠጭና የአህያ ፈንጪ አያድርስ ነው የሴት ልባም ያህያ ቀንዳም የሴት ልቧ እንጂ ሆዷ አይመርጥም የሴት መልኳ ምንድር ነው እጅዋን ታጥባ እንኩ ስትል ነው የሴት መጠጥ ደፋር የወንድ አይን አፋር የሴት ምክር ማሰሪያው አሽከቴ የሴት ምክር የሾህ አጥር የሴት ሞቷ በማጀቷ የሴት ረዥም የማቅ ውዥምዥም እንብዛም አያስጎመጅም የሴት ስካር ያጭር ሰው ኩራት አይታይም የሴት ብቻዋን ሂያጅ የቄስ አርፋጅ ሁለቱም ነገር ወዳጅ የሴት አመዳም የአህያ ሆዳም የሴት አመዳም የአሮጌ ሆዳም የሴት አገሩዋ ባሏ የሴት አገሩዋ ባሏ ማደሪያዋ አመሏ የሴት እንግዳ የመርፌ ጎዳ የሴት ቀበጥ የበቅሎ መድን ለመሆን ገበያ ትወጣለች የሴት ትንሽ የለውም የሴት ጉልበት ምላሱዋ የሴት ጠጪ የግመል ፈንጪ የሴት ዘበናይ የፊትዋን እንጂ የኋላዋን አታይ የሽማግሌ ፍቅር እና የክረምት አበባ አንድ ነው የሽሮ ድንፋታ እንጀራው እስኪመጣ ነው የሽሮ ድንፋታ እስኪቀርብ ድረስ የቀረ ይቀራል እንጂ ቀርቅር ብዬ አልጣራም የቀበሮ ባህታዊ የለም የቀበጠች አይጥ በድመት ጭራ ዘፈን ትዘፍናለች የቀበጠች አይጥ የድመትን አፍንጫ ታሸታለች የቀበጠ እንትን ቅቤ ቀቡኝ ይላል የቀበጡ እለት ሞት አይገኝም የቀን ጠማማን ሚዳቆ አትዘለውም የቀጣፊ እንባ ባቄላ ያክላል የቂጥ አጋሚ ፈስ ነው ወሮታው የቃመ ተጠቀመ ያልቃመ ተለቀመ የቃርያ እልክ አወፈረኝ የቄስ ጠበቃ ዳዊት ይጠቅሳል የቅርብ ጠበል የልጥ መንከሪያ ይሆናል የቅድሙ በዛ ያሁኑ ተንዛዛ የቆጡን አወርድ ብላ መሰላል አመጣች የቆጡን አወርድ ብላ ቤቷን ከርቸሌ አደረገች የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷ ጸጉር ታየ የቆጡን አወርድ ብላ የጣራውን አወረደች የበላ በለጠኝ የሮጠ አመለጠኝ የበላ ባይማታም ዱላ ይችላል የበላችው ያገሳታል በላይ በላዩ ያጎርሳታል የበላና የተደገፈ ወድቆ አይወድቅም የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም የቡና ስባቱ መፋጀቱ የባለጌ ባለሟል ቂጥ ገልቦ ያያል የባሪያ ደግ የቁልቋል ዘንግ የለውም የባስ አለ ሚስትህን አትፍታ የባሰ አለና አገርህን አትልቀቅ የቤቴ መቃጠል ለትኌኔ በጀኝ! አለች አሉ! የባህር ዳር ሲታረስ ጓጉንቸር ሆድ ይብሳታል የባልቴት ወብራ የክረምት ብራ የባል ደግነቱ ውሽሜን መርሳቱ የባል ደግነቱ ውሽምን መርሳቱ የባሰ አለና አገርህን አትልቀቅ የባእድ ፍቅር የውሀ ጌጥ አንድ ነው የቤት ቀጋ የደጅ አልጋ የተለጎመ በሬ ከቀንበሩ ቢያመልጥ ቢላዋ ይጠብቀዋል የተመረረ ድሀ ይገባል ከውሀ የተማረና ታጥቦ የተቀመጠ ብርጭቆ ፈላጊ አያጣም የተጠማ ከፈሳሽ የተጠቃ ከነጋሽ የተናቀ ሰፈር በአህያ ይወረራል የተናቀ ብእር ይገነፍላል የተናቀ እንትን ያስረግዛል የተናቀ ያስረግዛል የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ የተናገሩት ከሚጠፋ ጽፎ ማስቀመጥ የተናጠ ወተት ቅቤ ይወጣዋል የተንቀለቀለች አፍሳ ለቀመች የተንቀዠቀዠች ውሻ ላፏ ሊጥ ለወገቧ ፍልጥ አታጣም የተከፋ ተደፋ የተገነዘች ነፍስ የተለጎመች ፈረስ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው የት ትሂጃለሽ ቢላት በታክሲ አለች የት ትሂጃለሽ ቢሏት በታክሲ የት አውቅሽ ብሎ አጥብቆ ሳመኝ የቸኮለ አፍስሶ ለቀመ የቸገረው እርጉዝ ያገባል ስትወልድበት ገደል ይገባል የባሰበት እመጫቷን የቸገረው ዱቄት ከንፋስ ይጠጋል የነሀሴ ውሀ ጥሩ ነው የሚጠጣው የለም የድሀ ነገር ፍሬ ነው የሚሰማው የለም የነብርን ጭራ አይዙም ከያዙም አይለቁም የነቶሎ ቶሎ ቤት ግድግዳው ሰንበሌጥ የነቶሎ ቶሎ ቤት ግድግዳው ብሎኬት የነቶሎ ቶሎ ቤት ግድግዳው አስቤስቶስ የነቶሎ ቶሎ ቤት ግርግዳው ጭራሮ የነቶሎ ቶሎ ቤት በሊዝ ተሸጠ የነቶሎ ቶሎ ቤት ዘበኛው ቶሎሳ የነፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል የእናት እርግማን ወለምታ ነው የእናት ሞትና የግር እሳት እያደር ያንገበግባል የእናት ልጅ ቢጣላ እውነት ይመስላል ለሌላ የእናት ልጅ የሌለው አይበላ ሽሮ የሌለው ምንቸት አይፈላ የናት ሆድ ዥንጉርጉር የናት ሆድ ዥንጉርጉር ወላጅ ቀይና ጥቁር የናት ልጅ የጎን አሳጅ የናት ሞትና የድንጋይ መቀመጫ እያደር ይቆረቁራል የናትን ክፋት የደመናን ውሀ ጥማት ባለቤቱ ያውቀዋል የናት ድሀ የለውም የንግዳ አይን አፋር ባለቤቱን ይጋብዛል የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም የአህያ "እቃው" ሆዱ ውስጥ ነው የአሳ ግማቱ ከወደ አናቱ የአሳ ግማቱ ከወደ ጭንቅላቱ የ10 አለቃዬ ምክትሌ ሆይ አንተም እንደ መቶ ትኮራለህ ወይ የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ የአባይ ልጅ ኩሬ የአባይን ልጅ ወዳቂ የዞማ ልጅ ሳቂ የአባይን ልጅ ውሀ ጠማው የላጭን ልጅ ቅማል በላው የአንዱ ሀገር ዘፈን ለአንዱ ሀገር ለቅሶ ነው የአንድ ቀን መዘዝ ያለ ዘጠኝ ወር አይመዘዝ የአይጦች አድማ ምርጫ እስኪደርስ ነው የአገሬ ሰዎች ተጠንቀቁ የሰረቁት ስጋ ያስይዛል መረቁ የአፍ ወለምታ በቅቤ አይታሽም የአፍ ወለምታ በፖሊስ ይታሻል የእህል ክፉ አጃ የሳር ክፉ ሙጃ የነገር ክፉ እንጃ የእህል ጣም በጉረሮ የነገር ጣም በዦሮ የእብድ ገላጋይ ድንጋይ ያቀብላል የእናት ሞትና የድንጋይ መቀመጫ እያደር ይቆረቁራል የእንጨት ምንቸት እራሱ አይድን ሌላ አያድን የክፉ ሰው ተዝካር ውሀ ያስወስዳል በህዳር የክረምት ጥማትና የመከር ጊዜ ረሀብ አለባለቤቱ የሚያውቀው የለም የወረት ውሻ ስሟ ወለተኪሮስ የወረቀት ላይ ነብር የተግባር ስንኩል (አንሁን) የወንድ አልጫ የእንዶድ ሙቀጫ የወንድ አጭር ዝንጀሮ የሴት አጭር ወይዘሮ የወንድም ልጅ ባይወልዱትም ልጅ የወንዶች ባል አይተህ ማር የወንድ ልጅ ሞት ያደረገውን የዘነጋለት የወንድ አልጫ እንዶድ ሙቀጫ የወንድምህ ጢም ሲላጭ ጢምህን ውሀ አርስ የወጣ ቢገባ የገባ ይወጣል የወደቀ ዛፍ መንገዱን ዘጋ የወደደና የአበደ አንድ ነው የወደዱትን ሲያጡ የጠሉትን ይቀላውጡ የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም የወጋ ቢረሳ ፖሊስ ያስታውሳል የወጌሻ ልጅ ዛፍ ላይ ያድራል የወደቀ ዛፍ ምሳር ይበዛበታል የዋኘ ይሻገራል የሰራ ይከብራል የውሀ ሽታ የእባብ ፍለጋ የለውም የውሀ ውሀ ምን አለኝ ቀሀ የውሀ ጡር በእድፍ ያስታጥባል የውድማ ዘንዶ ይቀጠቀጣል እንደበረዶ የዘመድ ዘመድ ወንዝ ያሻግራል የዘመድ ጥል የስጋ ትል የዘሬን ብለቅ ይቆማምጠኝ አለ ቆማጣ የዘንድሮውስ ብርድ ቆማጥ ያሳቅፋል የዘገነ አዘነ ያልዘገነ አዘነ የዝንጀሮ ለቅሶ መልሶ መላልሶ የዝንጀሮ ስብሰባ በውሻ ጩኸት ይበተናል የዝንጀሮ ንጉስ እሱ ይከምር እሱ ያፈርስ የየጁ ቄስ አንደዜ ቅኔው ቢጎልበት ቀረርቶ ሞላበት የየጁ ደብተራ ቅኔ ቢያልቅበት ቀረርቶ ጨመረበት የደላው ሙቅ ያኝካል የደላው ወርቅ ያስራል የደመና ውሀ ጥምና የእናት በደል አይታወቅም የደንቆሮ ለቅሶ መልሶ መልሶ የደንቆሮ ለቅሶ መልሶ መላልሶ የደንቆሮ ሰርግ በሽብሸባ ያልቃል የድመት ልጅ መቧጨሯን አትረሳም የድሮው ኮንጎዬ ካሁኑ ስቶኪንጌ ተሻለኝ የድፍድፍ ኩራቱ ውሀ እስኪገባበት የድፍድፍ ኩራቱ ውሀ እስኪገባ ነው የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል የጅብ ችኩል ቶሎ ያፏጫል የገበያ ሽብር ለሌባ ሰርጉ ነው የገበያ ግርግር ለሌባ ይበጃል የገንዘብን ነገር ካሰላሰሉት አባ ሀናም ሞቱ እንደጨበጡት የገጣጣ ሚስት ችግሩን አልቅሶ ካልነገራት አይገባትም የጉልበት ግማሹ አፍ ነው የጉድ አገር ገንፎ በጣም ይጣፍጣል የጉድ አገር ገንፎ እያደር ይፋጃል የጉሮሮን መታነቅ ያይን መደንቆል ያስጥለዋል የጎረምሳ መልኩ እንጂ አነጋገሩ አያምርም የጎጃም አዝመራ ሽንብራ ነው አሉ እኛም እንዳንበላ ተነቀለ አሉ የጊዜ ግልባጭ እግር ሰውነት ያካል የግመል ሽንት ይመስል ሁሌ ወደኋላ የግፍ ግፍ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ የጥቅምት ቀን እና የቆንጆ ሳቅ አያታልልህ የጥንት ወዳጅክን በምን ሽኘኸው በሻሽ አዲሱ እንዳይሽሽ የጨለማ አፍጣጭ የእውር ገልማጭ የጨለማ አፍጣጭ የእውር ገልማጭ አይረባም የጨረቃ ሂያጅ የምስክር ፈራጅ የጨረቃ ሂያጅ የምስክር ፈራጅ የጨረቃ ንጋትና የእውር ሞት አይታወቅም የጨርቅ ነጩ የበራ ልጩ የጨነቀው እርጉዝ ያገባል የጨነቀው እርጉዝ ያገባል ስትወልድበት ገደል ይገባል የጨነቀው ይዋጋል ያልደረሰበት ያወጋል የጨዋ ልጅ ሁሉ አርግዟል ሆዱ የጨዋ ልጅ ሁሉ አርግዟል በሆዱ የጨዋ ልጅ ሲያዝን አሳ በወንዝ ይመክን የጨዋ ልጅ ሲያዝን ውሀ በወንዝ ይመክን የጨዋ ልጅ ሲፋታ ይጋባ ይመስላል የጨዋ ልጅ ከከተማ የድሀ ልጅ ከውድማ የጨዋ ልጅና ቅል ተሰባሪ ነው የጨው ገደል ሲናድ ሞኝ ይስቃል ብልህ ያለቅሳል የጨው ገደል ሲናድ ብልህ ያለቅሳል ሞኝ ይልሳል የጨውን ባለእዳ በጨው ቢያባብሉት ጨዌን ማለቱ አይቀርም የጨጌ ከብት በየወገኑ ይከተት የጫማ ጠጠርና የእንጀራ ልጅ እያደር መቆርቆሩ አይቀርም የጫማ ጠጠርና የእንጀራ እናት እያደር መቆርቆሩ አይቀርም የፈላ ጠጅ የደረሰ ልጅ የፈረሰኛ ማቅ ለባሽ የሴት ትምባሆ ቀማሽ የፈረሰኛ ማቅ ለባሽ የሴት ትምባሆ ጎራሽ የፈረሰ አልጋ የተሸበረ ዜጋ የፈረንጅ አሽከር ነጭ ለባሽ ሳህን አመላላሽ የፈሩት ይደርሳል የጠሉት ይወርሳል የፈሪ ዱላ ሰላሳ ነው የፈሪ ዱላ አያዳግምም የፈሪ በትር አስር የፈሪ ገዳይነት ለማታ የፈሰሰ ውሀን ማቆር ይጠቅማል የፈሰሰ ውሀ አይታፈስ የፈሰሰ አይታፈስ የሞተ አይመለስ የፈሲታ ተቆጢታ የፈሳ የጥጋብም አይደል ሲረሳ የፈስ ማደናገሪያው ዳባ የፈስ ማደናገሪያው ዳቦ የፈቷት ሴት ያጠቡት ወጪት የወጡበት ቤት አንድ ነው የፈቷት ሴት ያጠቡት ወጪት የወጡበት ቤት አንድ ናቸው የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል የፊተኛውን አሳረርሽ ቢሏት የኋለኛውን ጥሬ አወጣች የፊት መሪ የኋላ ቀሪ የፊት ምስጋና ለኋላ ሀሜት ያስቸግራል የፊት እድፍ በመስታወት የሀጢአት እድፍ በካህናት የፊት ከብት የእጅ ወረት የፊት ወዳጅህን በምን ቀበርከው በሻሽ የኋለኛው እንዳይሸሽ የፊት የፊቱን አለ ጓያ ነቃይ የፋቂ ልጅ ሰነፍ አንዱን ሳይፍቅ አንዱን ይዘፍቅ የፋቂ ሰነፍ አንዱን ሳይፍቅ አንዱን ይዘፍቅ የፋቂ ቆንጆ ቡድነቱን አይተውም የፌጦ መስሎሽ ሰናፍጭ ትቀምሽ የፌጦ ብቅል የብሳና ጌሾ የተልባ አሻሮ ይህን ጠምቆ ለማ የሰው ነገር ለማይሰማ የፍቅር ጣእሙ በመሳለሙ የፍቅር ጣእሙ አልጋ ላይ የፍቅር ጣእሙ ተቃቅፈው ሲተኙ የፍቅር ደስታው ከሴት ጭን መሃል ይገኛል ፈልጉ የፍየል ልጁን የሌባ እጁን የፍየል ጅራት ቂጥ አይከድን ከብርድ አያድን የፍየል ጅራት ብልት አይከድን ከብርድ አያድን የፍየል ጅራት ከብርድ አያድን ብልት አይከድን የፍየል ጅራት ከብርድ አያድን አፍረት አይከድን የፍየል ጅራት ከብርድ አያድን እፍረት አይከድን የፍየል ጭራና የሰው ሀሳብ ሁልጊዜ ወደ ላይ ነው የፍጅት ወራት እሳት በወንፊት የፖሊስ ዘመድና የቤንዚን አመድ የፖሊስ ዘመድ የቤንዚን አመድ የለውም ዪዪዪዪዪ .........አለ !አምቡላንስ (የቁጭት አባባል) ያህያ ስጋ አልጋ ቢሉት አመድ ያህያ ባል ቀለበት አያስርም ያህያ ባል ከጅብ ጉቦ በላ ያህያ ባል ከዥብ አያስጥል ያህያ ውሀ ጠጭ ሳይታወቅ መጣጭ ያህያ ልጅ ጥሎ ይረግጣል የፈረስ ልጅ ጥሎ ይደነግጣል ያህያ ስጋ ካልጋ ሲሉት ካመድ ያህያ ካልጋ ሲሉት እምድር ያህያ ስጋ ውርደተኛ አልጋ ላይ ቢያኖሩት እመሬት ይተኛ ያህያ ቀበጥ ከጅብ ጡት ይጣባል ያህያ ባል ከጅብ አያስጥል ያህያ እንግዳ የጅብ እራት ነው ያህያ ደግነት ጭነት ማብዛት ያህያ ውሀ ጠጭ ሳይታወቅ መጣጭ ያህያ ጀላፋ መስክ ያጠፋ የሹም ዘፋፋ አገር ያጠፋ ያህያ ፍለጋና የጥሬ እራት በግዜ ነው ያህያ ፍሪዳ የእባብ ለማዳ የለውም ያለባለቤቱ አይነድም እሳቱ ያለአንድ የላት በዘነዘና ትነቀስ ያለውን የሰጠ ንፉግ አይባልም ያለውን የወረወረ ንፉግ አይባልም ያለአዋቂ ተራች የራሱን አመልካች ያለ ዝናብ ነጎዳ ያለ ብድር እዳ ያለ ወጉ አህዮች ተዋጉ ያለ ባለቤቱ አይነድም እሳቱ ያለ የሚኖር ይመስላል የሞተ ያልነበረ ይመስላል ያለ ይበዛል (አለ ወፍጮ) ያለህ ምዘዝ የሌለህ ፍዘዝ ያለ መሰረት ቤት ያለ ትምህርት እውቀት የለም ያለ መከራ አይገኝም እንጀራ ያለ መከራ ጸጋ ያለ ድካም ዋጋ አይገኝም ያለ መጥረቢያ እንጨት ሰባሪ የቆማጣ ዘንግ ወርዋሪ ያለ ምቀኛ አይገኝ ፍቅረኛ ያለ ሴት ምን ያደርጋል ቤት ያለ ሴት ቤት ያለበሬ መሬት ያለ ስራ መብል ያለዳኛ ውል ያለ ስራ መብል ያለዳኛ ውል አይቻልም ያለ ስራ አይበላ እንጀራ ያለ ስራ አይበላ እንጀራ አለባል ቆጥ አይሰራ ያለስፍራው የተስበረ ሲጠግኑት አስቸገረ ያለስፍራው የተስበረ ሲጠግኑት ያስቸግራል ያለ በሬ ምን ያደርጋል ገበሬ ያለበት ይብላላበት ያለበት ይጉላላበት ያለ ባለቤቱ አይነድም እሳቱ ያላባቱ ቢዛቁን አባክኖ ያባክን ያለአቻ ጋብቻ ቆይ ብቻ ቆይ ብቻ ያለ እዳው መዝመት ዋ ብሎ መቅረት ያለ እዳው ዘማች ዋ ብሎ መቅረት ያለ ክንፍ መብረር ያለ ስራ መክበር ያለው ሳይዋደድ ለሞተው መናደድ ያለው ይምዘዝ የሌለው ይፍዘዝ ያለው ይመዛል የሌለው ይፈዛል ያለው ይበላል የሌለው ያፈጣል ያለውን ካልሰቱ በስም አይበሉ ያለ ዘዴ ጋሻ እንቅብ ነው ያለ ዘመድ ነግሶ ያለ አቡን ቀስሶ ያለ ዝናብ ነጎዳ ያለብድር እዳ ያለ የሚኖር ይመስላል የሞተ ያልነበረ ይመስላል ያለ ጊዜው የተወለደ ልጅ አባቱን ጥሎ አያቱን ያስረጅ ያለ ጎረቤት ቡና ያለ ሙያ ዝና ያለ ጎታ ደረባ ያለልብስ ካባ ያለ ጎተራ ደረባ ያለልብስ ካባ ያለ ጎታ ደረባ ምንድን ነው ያለ ይበዛል አለ ወፍጮ ያለ ጥርስ ቆሎ ያለ ጓድ አምባጓሮ ያለ ጨው በርበሬ ያለሞፈር በሬ ያለ ፊቱ አይቆርስ ያለባለቤቱ አይወርስ ያለ ፍርድ ማሰር በፈጣሪ ማማረር ያለ ፍቅር ሰላም ያለ ደመና ዝናብ ያለ ፍቅር ጸሎት ያለ እንጨት እሳት ያሉሽን በስማሽ ኖርዌይ ባልመጣሽ ያሉሽን በሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ ያላማረ ሰርግ ጉልቻው ይሽረፋል ያላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል ያላዩት አገር አይናፍቅም ያላረፈች ምላስ ሸማ ትልስ ያላረፈች እግር ከዘንዶ ጉድጓድ ትገባለች ያላሰብከውን አግኝ መረገመም ምርቃን አይደል ያላስደጉት ውሻ ቤት ዘግተው ቢመቱት ዞሮ ይናከሳል ያላባቱ ቢዛቁን አባክኖ ያባክን ያላዋቂ ሳሚ ምላስ ይነክሳል ያላወቁ አለቁ ያላዞረ ሲዞር አደረ ያላዋቂ ቆራሽ ማእድ አበላሽ ያላየ ልጅ ዳቦ ፍሪዳው ያላዩት አገር አይናፍቅም ያላዩት ነገር ክፉ አይደለም መልካምም አይደለም ያልሰማ ጆሮ ከጎረቤት ያጣላል ያልበላህን አትከክ ያልበላ ዳኛ አያሟግት ያልጠጣ እንግዳ አይጫወት ያልተመካ ግልግል ያውቃል ያልተማረ ዋናተኛ ከዳኛ ፊት እንቢተኛ ያልተነካ ግልግል ያውቃል ያልተገላበጠ ያራል ያልታደለ ቆዳ ሲላፋ ያድራል ያልታደለ በረዶ ከድንጋይ ላይ ያርፋል ያልታደለች ከንፈር ሳትሳም ታድራለች ያልታደለ ከንፈር ሊፕስቲክ ያበዛል ያልታደለ ከንፈር ሳይሳም ያረጃል ያልነበረ ያፈርሳል ቀዳዳ ያፈሳል ያልወለደ አጋድሞ አረደ ያልወለድኩት ልጅ አባባ ቢለኝ ሆዴን ባርባር አለኝ ያልወለድኩት ልጅ አባዬ ቢለኝ አፌን ዳባ ዳባ አለኝ ያልጠረጠረ ተመነጠረ ያልሟል ይተረጉሟል ያልሞላ ተርፎ አይፈስም ያልሞተና ያልተኛ ብዙ ይሰማል ያልሰማ ጆሮ ከጎረቤት ያጣላል ያልሰማ ጥኑ ነው ባልሽ ወዳጄ ነው ያልሰሙት ነገር ክፉም መልካምም አይደለም ያልሰጡት ተቀባይ ያልጠሩት አቤት ባይ ያልሳሉት አይላጭ ያላዩት አይቆጭ ያልቆረጠ እግብ አይደርስም ያልበሉት እዳ ያልጠሩት እንግዳ ያልበላ ሬሳ ያልለበሰ እንሰሳ ያልበላ ዳኛ አያሟግት ያልጠጣ እንግዳ አያጫውት ያልበላኝን ቢያከኝ አይገባኝ ያልበጀው እሳት ፈጀው ያልተማረ አይጸድቅ ያልተወቀረ አያደቅ ያልተማረ አይምርም ያልተወቀረ አያደቅም ያልተመታ ልጅ ሲቆጡት ያለቅሳል ያልተማረ ዋናተኛ ከዳኛ ፊት እንቢተኛ ያልተረታ አይረታ ያልጠገበ አይማታ ያልተሾመ አያዝ ያልቀሰሰ አያናዝዝ ያልተሾመ አያዝ ያልቀሰሰ አይናዝዝ ያልተቀጣ ልጅ ቢቆጡት ያለቅሳል ያልተቀጣ ልጅ ያልታጠበ እጅ ያልተነካ ግልግል ያውቃል ያልደረሰበት ግልግል ያውቃል ያልተገላበጠ ያራል ያልተገላበጠ ያራል ያለ ይበዛል አለ ወፍጮ ያልተገራ ፈረስ ይጥላል በደንደስ ያልተጠናከረ ድንገት ተሰበረ ያልተፈተነ ወዳጅ ያልተተኮሰ ሸክላ ያልተፈተነ ወዳጅ ያልተተኮሰ ሸክላ ነው ያልታረመ አፍ ከዋንጫ ይሰፋል ያልታየ እንጂ ያልተሰማ ያልተደረገ እንጂ ያልተባለ ነገር የለም ያልታደለ በረዶ ከድንጋይ ላይ ያርፋል ያልታደለ ከንፈር ሳይሳም ያረጃል ያልታደች ወፍ አይኗ በጥቅምት ይጠፋል ያልነበረ ያፈርሳል ቀዳዳ ያፈሳል ያልወለደ አንጀት ጨካኝ ነው ያልወለደ አይነሳ የሽምብራ ማሳ ያልወለደ አጋድሞ አረደ ያልወለዱ ሁሉ ጊደሮች ይባላሉ ያልወለደኩት ልጅ አባባ ቢለኝ አፌን ዳባ ዳባ አለኝ ያልወለደኩት ልጅ አባ አባ ቢለኝ አፌን ዳባ ዳባ አለኝ ያልዘሩት አይበቅልም ያልዘራሁት በቀለብኝ ዱባ ያልኩት ቅል ሆነብኝ ያልዘራውን የሚበላ ዝንጀሮ ነው ያልገደለ በሽታ ምስጋና የለውም ያልገደለ ዘማች ያልወለደ አማች ያልጋ ሴሰኛ ሶስት ያስተኛ ያልጠረጠረ ተመነጠረ ያልጠሩት መካሪ ያልሾሙት ፊታውራሪ ያልጠሩት ሰርገኛ በትረኛ ያልጫ ድንፋታ እንጀራ እስኪቀርብ ያልጫ ድንፋታ እንጀራ እስኪቀርብ ነው ያልፋል እስኪያልፍ ያለፋል ያመል ትንሽ ይጥላል በጭራሽ ያመሰገኗት ቅል ባፏ ታፈሳለች ያሞሌ ጥጃ በወንዙዋ ትናፋ ያመነታ ተመታ ያመኑት ሲከዳ ይቀላል እዳ ያመኑት ፈረስ ጣለ በደንደስ ያመጣሁት ውሻ ነከሰኝ ያነደድኩት እሳት ጠበሰኝ ያመጣል አንበሴ ይበላል ኮሳሴ ያማከሩት ዳኛ ያግዛል የመተሩበት እጅ ይወዛል ያምላክን ነገር ምኑን አውቀሽው ወይ እኔ እበላው አንቺ አርመሽው ያምላክን ነገር ስንቱን አውቀሽው ወይ እኔ እበላው አንቺ አርመሽው ያምራል ብለው ለነብር ልጅ አይድሩም ያምራል ብለው ከተናገሩት ይከፋል ብለው ያስቀሩት ያምራል ብለው ከመናገር ይከፋል ብሎ መተው ያምራል ብሎ ይሸልሟል ያውቃል ብሎ ይሾሟል ያምሩዋል ይታደሏል ያምና ሞኝ ዘንድሮም ደገመኝ ያምናውን ዘንድሮ የአዋጁን በጆሮ ያሞላቀቁት ልጅ አይሆንም ወዳጅ ያሞሌ ጥጃ በወንዙዋ ትነፋ ያረረበት ያማስል ያረሮ ልጅ ጠለፋ ያረሰ እንደ ልቡ ጎረሰ ያረገዘች ታስታውቅ ከደረቷ ትታጠቅ ያረጀን ሹም ገባር ይከሰዋል ያረጀን ጅብ አህያ ይጥለዋል ያራስ ክፉ መበለት ያደጋ ክፉ እሳት ያራሷን በርጉዙዋ ያራሷን ገንፎ እርጉዙዋ ውጣ ሞተች ያርጋጅ አናጋጅ ያርጋጅ አንጓጅ ያሳደግሁት ውሻ ነከሰኝ ያነደድሁት እሳት ጠበሰኝ ያስረ ይፈታል የሰጠ ይረታል ያስለመዱት ሰው ሁልጊዜ እጅ ያያል ያሰቡት አይገድም ጎኔን ላርገው ጋደም ያሳደግኋት ጥጃ አለችኝ በርግጫ ያሳደኩት ውሻ ነከሰኝ ያነደድኩት እሳት ጠበሰኝ ያስታርቀኛል ሙተራ እያንዳንዱ እየኮራ ያሽላል ያሉት ኩል አይን ያጠፋል ያቀረቡልህን ጉረስ የተረፈህን መልስ ያበረ ወገኑን አስከበረ ያበራሽን ጠባሳ ያየ በእሳት አይጫወትም ያ በሬ ባላገደደ ያ በሬ ገደል ባልገባ ያ በሬ ባገደደ ያ በሬ ገደል ገባ ያ በሬ ባገደደ ያ በሬ ገደል ገባ ያበጠው ይፈንዳ ያበደ ለኑሮው የፈረደ ለጉሮሮው ያበደች ጋለሞታ እናቷን ትመታ ያበደና የወደደ አንድ ነው ያበጠው ይፈንዳ ያባ ሆይ መቋሚያ ላዩ ባላ ታቹ ዱላ ያባ ጎፍናኔ ቤቱ በሪድ ያባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ ያባት ወዳጅ የድንጊያ ገድጋጅ ያባቱን ቢሰጡት ህይወቱ ያባቱን ቢነሱት ሞቱ ያባቱን ያገኘ ህይወቱ ያባቱን ያጣ ሞቱ ያባት ልጅ የደንደስ ስጋ ያባት ልጅና ጆሮ አንድ ነው ያባት ምርቃት አያስገባም ጥቃት ያባት ልጅ የማድጋ ዶሮ ነው ያባት ልጅ የማድጋ ዶሮ አንድ ነው ያባት ሞቱን አይወዱ ረጃቱን አይሰዱ ያባት ሞቱን አይወዱ ረድኤቱን አይሰዱ ያባት ሲቀር ምሰህ ቅበር ያባት አገር ከሞት አያስጥልም ያባት እርግማን ሲዳሩ ማልቀስ ያባት እዳ ለልጅ ያፍንጫ እድፍ ለእጅ የወፍጮ እዳ ለመጅ ያባት ወርቅ ባለዝና እህል ለቀጠና ያባት ያምራል የባእድ ያናግራል ያባት ያምራል የባእድ ያኖራል ያባት ደግ ይደልላል ያባት ክፉ ለእንጀራ ልጅ ያደላል ያባትህ ቤት ሲበዘበዝ አብረህ ዝረፍ ያባትህና የናትህ ወገኖች ሲጣሉ ጥግህን ያዝ ያባያ ልጅ ወዳቂ ያራኝ ልጅ አጥባቂ ያባያ እናት አትታረድም ያባያ ወንድሙ አይታረድም ያባይ ምልክቱ አንደበቱ የገዳይ ምልክቱ ሽልማቱ ያባይ እንባ አይታገድም ያባይን እናት ውሀ ጠማት ያባይ ውሀ ተለያየ ሲሉ ተገናኘ ያባይን ልጅ ውሀ ጠማው የላጭን ልጅ ቅማል በላው የአብሮ አደግ ልብ በቁና ይሰፈራል ያብዬን እከክ ወደ እምዬ ላከከ ያብዬን እከክ ወደ እምዬ ልክክ ያተር ክምር የጭሰኛ ክብር ያናጢን ልጅ ጅብ በላው የላጭን ልጅ ቅማል ፈጀው ያንበሳ ልመና ጋማ ይዞ ነው ያንበሳ ልመና ጋማ ይዞ የቄስ ልመና አናዞ ያንበሳ ማላጅ ጋማ ይዞ ጅብን መውጋት አህያን ተጎዝጉዞ ያንበሳ ማላጅ ጋማ ይዞ ጅብን መውጋት አህያን ተገን ይዞ ያንበሳ አማላጅ ጋም ይዞ ጅብን መውጋት አህያን ተገን ይዞ ያንበሳ ኮርዲዳና የጨዋ ልጅ ሞግዚት ከመሆን ይሰውርህ ያንበሳ ገራም ይውላል ከላም ያንተን የሚመስል የኔም አለኝ ቁስል ያንቺን አትበይ ገንዘብ የለሽ የሰው አትበይ ምግባር የለሽ ያንካሳ ልቡ ኢየሩሳሌም ያንዱ በሬ ሲሞት ላንዱ አጋዘኑ ፍስሀው ላንዱ ሀዘኑ ያንዱ ቤት ሲቃጠል ላንዱ ቋያው ነው ያንዱ ቤት ሳይጠፋ ያንዱ ቤት አይለማ ያንዱ ቤት ካልጠፋ ያንዱ ቤት አይለማም ያንዱ ነገር ላንዱ የእንጀራ ልጁ ነው ያንዱ አገር መልከኛ ላንዱ አገር ገባር ነው ያንዱ ላም ወተት ያንድ እርሻ እሸት ያንድ ሚስቱን የሺ ከብቱን ያንድ ሰው ፍቅር ባንድ እጅ እንደማጨብጨብ ያለ ነው ያንድ ሰው ነገር ሰምተህ አትፍረድ ያንድ በሬ እሸት ያንድ ላም ወተት ያንድ እርሻ እሸት ያንድ ላም ወተት ያንድ ቀን ስህተት ለዘላለም እውቀት ነው ያንድ ቀን ስህተት የዘላለም ጸጸት ነው ያንድዋ እለት አንድዋ ባልቴት ያንጎርጓሪ ጉልበት የተራጋጭ ወተት ያኖሩት እንቅርት መለያ ይሆናል ያኖሩት እንቅርት ያገለግላል ያኩራፊ ምሳ እራት ይሆነዋል ያኩራፊ ምሳው የነበረ እራት ይሆነዋል ያኮረፈ ልብሱን አራገፈ ያኮረፈ ምሳው እራቱ ነው ያወረደ መአቱን ያመጣ ምህረቱን ያወቀ ተጠነቀቀ የዘነጋ ተነጠቀ ያወቀ ተጠነቀቀ የዘነጋ ተወጋ ያወቀ ተጠነቀቀ ያላወቀ ተነጠቀ ያወቀ ናቀ ያወቀ ዘለቀ ያላወቀ አለቀ ያወቁ ሲታጠቁ ያላወቁ ተሳቀቁ ያዋቂ ሴት ቤት አለው ውበት ያዋቂ አጥፊ የእስራኤል ጣፊ ያዋቂ አጥፊ የጾመኛ ገዳፊ ያዋጁን በጆሮ የእለቱን በቀጠሮ ያውሬ ስጋ ለወሬ ያውቃል ብሎ ያሟል ያምራል ብሎ ይሸልሟል ያውቃል ብሎ ይሾሟል ያምራል ብሎ ይሸልሟል ያው እንዳያችሁኝ ቅዳሜ የወጣሁ ይቆጡኛል ብዪ አርብ ማታ መጣሁ ያዙኝ ልቀቁኝ ያዛዥ ቤተ ክርስቲያን ሳሚ ያጋፋሪ ራስጌ ቋሚ ያየ ላውራ ቢል ያልሰማ አወራ ያየ ላውራ ቢል የሰማ አወራ ያየ ልናገር ቢል የሰማ ላውራ አለ ያየ ቢሄድ የሰማ ይመጣል ያየ ቢሄድ ያልሰማ ይመጣል ያየ ይናገራል የተወለደ ይወርሳል ያዩትን ሊሰሩ አይናቸውን ታወሩ ያዩትን ቢያጡ ያላዩትን ይቀላውጡ ያያን ጨንቋራ ሁሉ ያየዋል ያይጥ ምስክሯ ድንቢጥ ያይጥ ሞት የድመት ሰርግ ያይጥ እርዳታ በጭራንፎ ያልቃል ያይጥ ፉከራ ለመከራ ድመት ምን ሊበላ ያይጦች ዝላይ ለነአቶ ውሮ ሲሳይ ያደረገችውን ታስታውቅ ከደረቷ ትታጠቅ ያደፈ በእንዶድ የጎለደፈ በሞረድ ያደፈውን በእንዶድ የጎለደፈውን በሞረድ ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይቀርም ያዳቆነ ሰይጣን የግል ኮሌጅ ከፈተ ያዛቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይቀርም ያዳኝ ውሻ ጠጉር ባፉ ብትር ትርፉ ያገሩን ሰርዶ ባገሩ በሬ ያገሩን ሰርዶ ያገሩ በሬ ይወጣዋል ያገር ልማት የገበሬ ሀብት ያገር ልጅ በምን ይመታል በኩበት ያም እንዳይሄድ ያም እንዳይሞት ያገር ልጅ በምን ይማታል በኩበት ያ እንዳይሄድ ያ እንዳይሞት ያገር ልጅ የማር እጅ ያገር ልጅ የማር ጠጅ ያገር እድር ለንጉስ ያስቸግር ያገር እድር ጦም ያሳድር ያገርህ ልጅ ብታገባት ሚስትህ ብትፈታት እህትህ ያገርህ ልጅ ብታገባት ሚስትህ ብትፈታት እትህ ያገርህ ዱር ፍራትን ያስወግዳል እንጂ ከሞት አያድንም ያገርን ሰርዶ ያገር በሬ ያወጣዋል ያገባሽስ ይፈታሻል ይብላኝ ለወለደሽ ያገባሽ ይፈታሻል ይብላኝ ለወለደሽ ያገባሽ ይፈታሻል ወዮለት ለወለደሽ ያገኘ ከራሱ ያጣ ከዋሱ ያጓኑት ድንጋይ ተመልሶ ራስን ያጓኑት ድንጋይ ተመልሶ ራስን ይመታል ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል ያጣጣመ የቆረጠመ ያጣ ሰው ያገኝ አይመስለውም ያጥንት ፍላጭ የስጋ ቁራጭ ያፍ እማኝ አደረገኝ ለማኝ ያፌን እስክውጥ እድሜ ይስጠኝ ይላል እርኩም ያፍ ወለምታ በቅቤ አይታሽም ያፍ ዘመድ በመንገድ አይገድ ያፍላ ለማኝ አደረገኝ ለማኝ ያፍላ የለው ቀርፋፋ ያፍላ የለው ቀፋፋ ይሄ እንግዳ ቸኮለ ሊያድር ነው መሰለኝ ይህ ሁሉ ከርከሬሻ ባንቺ የተነሳ ይህ ሁሉ ጠባሳ ባንቺ የተነሳ ይህ አንበሳ ደም ደም አገሳ ይህ እንግዳ ቸኮለ ሊያድር ነው መሰለኝ ይህ ከርከሬሻ ዳቦዬን ለማንሻ ይህን ብሰጥ ምን እውጥ ይህን ብትሰጥ ምን ትውጥ ይህንን ፈርቼ ደጄን በቀን ዘግቼ ይህን ፈርቼ ደጄን በቀን ዘግቼ ይህች ባቄላ ካደረች አትቆረጠምም ይህች ተፍተፍ እኔን ለመመንተፍ ይሆናል ብዬ ጎሽ ጠመድኩ የማይሆን ቢሆን ፈትቼ ሰደድኩ ይሆን ቢሆን ዝሆን ይበላ ቢሆን ይሉሽን በሰማሽ ገበያም ባልወጣሽ ይሉሽን ባልሰማሽ ገበያም ባልወጣሽ ይሉሽን ባወቅሽ ገበያም ባልወጣሽ ይሉ አይሉ የት አለ ቅሉ ይሉሽን ብትሰሚ ጎንደር ላይ ክረሚ ይሉኝ አይል ውሽማ ዶሮ ሲጮህ ይማለላል ይሉኝ አይል የኋላውን አያይ ይሉኝ አይል ጸሀፊ ከሙሴ ይገድፋል ይሉኝታ ተፈርቶ እስከመቼ ተቆራምቶ ይሉኝታና መጠቀም ባንድነት አይገኙም ይሉኝታ የራስ አሊን ቤት ፈታ ይመሰክረዋል ለነፍሱ ይፈተፍተዋል ለከርሱ ይመስል አይመስል የጠይብ እጅ ተከሰል ይመታሉ የሚጠሉ ይመስል ይስማሉ የሚወዱ ይመስል ይሙት የገደለ ይካስ የበደለ ይማሩኝ እያልክ ከምትታማበት አትገኝ ይማሰላል ካሉ ይዛመዳል አይገድም ይሰጠኝ መስሎ ሊሸጠኝ ይሰጡኛል ብሎ ከሰጠ ቆጥቦ የበላ በለጠ ይስጡ ብሎ ከሰጠ ቆጥቦ የበላ በለጠ ይሰጣል መስሎ ይሸጣል ይስብረኝ ይሰንጥረኝ የሚሉ የሰውን ልብ ሊሰብሩ ይቅር ለእግዜር ወድቆ እማይሰበር ይቅር ለእግዜር ወድቆ አይሰበር ሞቶ አይቀበር ይቅደም ደግነት ይከተል ቸርነት ይበላ እንደ ቤቱ ይሰራ እንደ ጉልበቱ ይበላ እንደ ቤቱ ይሰራ እንደ ጎረቤቱ ይበላው ካጣ ይበላበት ያጣ ይበጃል ያሉት መድሀኒት አይን አጠፋ ይበጃል ያሉት ኩል አይን አጠፋ ይብላ እንደ ቤቱ ይስራ እንደ ጎረቤቱ ይብላኝ ለወለደሽ ያገባሽስ ይፈታሻል ይብራና ይብራ ተጣሉ በሰው ሽንብራ ይታደሏል እንጂ ይታገሏል ይታደሉታል እንጂ አይታገሉትም ይቺ ባቄላ ያደረች እንደሆን አትቆረጠምም ይቺ ጎንበስ ጎንበስ አንድም ለመፍሳት አንድም እቃ ለማንሳት ይቺን ለኛ ጥሬን ለጌኛ ይቺም ቂንጥር ሆና ቡታንታ አማራት ይቺን በላህ ብለህ ጦሜን አታሳድረኝ አለ አሉ ይውደደኝ የጀርባዪ ቅማል አለች አንዷ ይገርማል አህያ ከዥብ ይከርማል ይደንቃል ይገርማል አህያ ከዥብ ይከርማል ይኖሩዋል በደጋ ይተኙዋል በአልጋ ይወልደዋል ካሉ ይመሰለዋል አይገድም ይውጋሽ ብሎ ይማርሽ ይጥሉህ አትጥላቸው ይበድሉህ አትበድላቸው ይጠላኝ ይመስል ይመታኛል ይወደኝ ይመስል ይስመኛል ይወደዋል ካሉ ይመክሩዋል ይወልደዋል ካሉ ይመስሏል ይውጋህ ብሎ ይማርህ ይውጋህ ብሎ ይማርክህ ይገርመኛል ገንፎ ከራቴ ተርፎ
33755
https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8C%8B%E1%8A%94%E1%8A%95
ጋኔን
ጋኔን (ነጠላ) ወይንም አጋንንት (ብዙ ቁጥር) የእርኩስ መንፈስ አይነት ሲሆን ከመጽሐፍ ቅዱስ ተመዘው በተስፋፉ ጽሑፎች ላይ የዚህ መንፈስ ታሪክ/አፈ-ታሪክ ተጽፎ ይገኛል። ለምሳሌ ቀኖናዊ ባልሆኑት ስነ ፍጥረት እና ሰይፈ ስላሴ በተባሉ የግዕዝ መጻሕፍት። አሁንም ብዙው ህብረተሰብ እንዲህ ያስባል። በመጽሐፍ ቅዱስ ስለሚጠቀሱ፣ እስካሁን ድረስ በዓለም ዙሪያ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ትምህርት እንዲህ ይመስላል። አጋንንት የሳይንስ እውቀት ባላቸውም ሆነ በሌላቸው ኢትዮጵያውን ዘንድ እጅግ ከፍተኛ ፍርሃቻን የሚፈጥር አስተሳሰብ ነው። ነገር ግን የአጋንንት ታሪክ የሚመነጨው የሳይንስ አስተሳሰብ ባልተስፋፋበትና ስለቫይረስም ሆነ ጀርም በማይታወቅበት ዘመን ሲሆን ዘመናዊው የሳይንስ አስተሳሰብ ከዚህ ይለያል፣ እንደሚከተለው ይላል፦ ዋና ዓላማውም የበሽታዎችን አመጣጥ በሚያሳምን መልኩ ለመረዳት እና ለመተንበይ ነበር። ይሄ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአብዛኛው ያልተማረ ህብረተሰብ የሚሰራበት የነበር ነው። ስለሆነም ሆድ ቁርጠት፣ ጉስምት፣ ብድብድ ወዘተ በአጋንንት ምክንያት የሚመጡ ተደርገው ይታሰቡ ነበር። የተለምዶ የአጋንንት አመጣጥ ታሪክ እንደ ሰይፈ ስላሴ ታሪክ፣ በሰማይ ቤት 100 የመላዕክት ነገዶች ነበሩ። ከለታት አንድ ቀን እግዚአብሔር በሌለበት፣ ሰባልስዮስ ወይንም ሰይፈ ስላሴ የተሰኘ የመላዕክት አለቃ እኔ ሁሉን ፈጠርኩ አለ። ከ100ዎቹ ነግዶች አንደኛው ወገን ይህን የሰባልስዮስን ቃል አመነ። ይሄው ቡድን ወደ እሳት ተጣለ። ከሳት ከወጣም በኋላ የሰይጣን አገልጋይ ሆነ፡፡ የነገዱ አባላቶችም መጠሪያ ስማቸውም አጋንንት ሆነ። እንደዚሁ አፈ ታሪክ 99 የመላዕክት ነገዶች ስለቀሩ እግዚአብሔር 100ውን ለመሙላት አዳምን ፈጠረ፡፡ ሆኖም አዳም ከጭቃ ስለተሰራ እና ሰይጣን ደግሞ ከአየር እና ብርሃን ስለተሰራ፣ ሰይጣን ለሰው ልጅ ክብር መስጠት እምቢ አለ፣ ስለዚህም በሁለቱ መካከል የማያቋርጥ ጠብ አለ። የጋኔን በሽታና ባህላዊውን መድሃኒቱ ከላይ እንደተጠቀሰው አብዛኛው በሽታ በአጋንንት ምክንያት የሚመጡ እንደንበር በብዙዎች ይታመን ነበር። ስለሆነም አንድ ግለሰብ በሽታ ሲይዘው እርሱን ለማዳን አንዱ አማራጭ አጋንንት የያዘውን ሰው በዛር መንፈስ በማስያዝ አጋንንቱን ከውስጡ ማስለቀቅ ነበር። የዛር መንፈስ ከአጋንንት ይሻላል ተብሎ ስለሚታመን። ፀበል፣ ቁርባን እና እንዲሁም የእርግፍጋፎ እንጨት () ለፈውስ ይረዳሉ ተብለው ተጠቃሚነትን ያገኛሉ። ለኤድስ እና ሌሎች የቫይረስ እና ጀርም በሽታዎች በፀበል ፈውስ መፈለግ መሰረቱ ከዚህ የተዛባ ግንዛቤ ይፈልቃል። በመጽሐፍ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን በኦሪት ዘዳግም 32፡15 ፣17 መሠረት በሙሴ መዝሙር፣ ይሹሩን (የእስራኤል ሕዝብ መጠሪያ) እግዚአብሔርን ተወ፣ እግዚአብሔር ላልሆኑ አጋንንት እንደ ሠዉ ይጠቅሳል። በመጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 11፡14-15 ኢዮርብዓም ከይሁዳ ተለይቶ የእስራኤል ንጉሥ በሆነበት ጊዜ የይሖዋ ካህናት ትቶ ለራሱ አጋንንት ካህናት እንዳቆመ ይላል። በመዝሙረ ዳዊት 91፡6 በእግዚአብሔር መጠጊያ የሚኖር ሰው ልጅ «ከቀትር ጋኔን» እንደማይፈራ ያረጋግጣል። የጥንታዊ ግሪክ («ሳባ ሊቃውንት») ትርጉም እንዲህ ይላል፤ አሁን ግን በይፋዊው ዕብራይስጥ ትርጉም «በቀትር ከሚያጥፋው ጥፋት» እንደማይፈራ ይላል። በመዝሙረ ዳዊት 95፡5 የአረመኔ ጣኦታት ሁሉ ለአጋንንት እንደ ሆኑ ይገልጻል። በመዝሙረ ዳዊት 105፡35-7 እስራኤላውያን የአሕዛብ እምነቶች ሲከተሉ እንኳን ልጆቻቸውን ለአጋንንት እንደ ሠዉ ይነግራል። በትንቢተ ኢሳይያስ 13፡21 የባቢሎን ውድቀት ሲነበይ አጋንንት በዚያ ይዘፍናሉ ይላል። (በአንዳንድ ትርጉም ግን «አጋንንት» የሚለው የዕብራይስጥ ቃል ደግሞ ፍየል ማለት ሊሆን ይችላል።) እንዲሁም ትንቢተ ኢሳይያስ 34፡14 የኤዶምያስ ጥፋት ሲነበይ፣ አጋንንት (ወይም ፍየሎች?) እርስ በርስ በዚያ ይጠራራሉ ይነግራል። አዋልድ መጻሕፍት በአዲስ ኪዳን በወንጌሎች በተለይም በማርቆስ ወንጌል ዘንድ፣ ኢየሱስ በልዩ ልዩ ደዌ ወይም በሽታ የተሰቃዩትን ሰዎች እየፈወሰ፣ ጋኔን ወይም ርኩስ መንፈስ ካደረበት ሰው ጋኔኑን በቃሉ ያወጣል። (ማቴ. 4፡24፣ 8፡16፣ ማርቆስ 1፡32-34፣ 39፤ ወዘተ.) የማቴዎስ ወንጌል 8፡28-33 - በጌርጌሴኖን አገር መቃብር ውስጥ ከኖሩ አጋንንት ካደሩባቸው ከ2 ግፈኛ ሰዎች አጋንንቱን አወጣና ወደ እሪያ መንጋ እንዲገቡ ፈቀደ። በማርቆስ 5 እና ሉቃስ 8 መሠረት የአንዱ ጋኔን ስም ሌጌዎን («ጭፍራ» ወይም «ሠራዊት» በሮማይስጥ) ይባል ነበር። ማቴዎስ 9፡32 - ኢየሱስ ጋኔን ካደረበት ዲዳ ሰው ጋኔኑን አወጣና ዲዳው ተናገረ፤ የፈሪሳውያን አይሁድ ወገን ግን «በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል አሉ»። ማቴዎስ 10፡8፣ የማርቆስ ወንጌል 3፡15፣ 16፡17፤ የሉቃስ ወንጌል 9፡1 - ኢየሱስ 12 ሐዋርያቱን አጋንንት እንዲያውጡ አዘዛቸው። ማቴዎስ 11፡18፣ የሉቃስ 7፡33 - ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ መጥምቁ ሲያስተምር አንዳንድ ሰዎች ጋኔን እንደ ነበረበት ይሉ እንደ ነበር ይገልጻል። ማቴዎስ 12፡22 - ኢየሱስ ጋኔን ካደረበት ዕውር ዲዳ ጋኔኑን አወጣና ሰውዬው ተፈወሰ። ሕዝቡ ተገርሞ ኢየሱስ የዳዊት ልጅ (መሢሕ) እንደ ነበር ገመተ። የፈሪሳውያን ወገን ግን ይህ በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ ነው አሉ። ማቴዎስ 15፡22-28 - አንዲት ከነዓናዊ ሴት ኢየሱስን «የዳዊት ልጅ ሆይ» ስትለው ጋኔን ከሴት ልጅዋ እንዲያውጣ ለመነችው። የማርቆስ ወንጌል 7፡25-30 - ከነዓናዊት ሴት «ግሪክ፣ ትውልድዋም ሲሮፊኒቃዊት» ይባላል። ማርቆስ 16፡9፣ ሉቃስ 8፡2 - ኢየሱስ ከመግደላዊት ማርያም 7 አጋንንት እንዳወጣ ይጻፋል። ሉቃስ 4፡33 - ኢየሱስ በምኲራብ ሲያስተምር፣ አንድ ርኲስ ጋኔን መንፈስ ያደረበት ሰው ጮኸበት። ኢየሱስ ጋኔኑ ከዚህ ሰው እንዲወጣ አዘዘና ጋኔኑ ሰውዬውን በመካከላቸው ጥሎት ከእርሱ ወጣ። ሉቃስ 4፡41 - ብዙ ጊዜ አጋንንትን ሲያውጣ፣ እንዲህ ይጮሁ ነበር፤ የኢየሱስ መታወቂያ ክርስቶስ (መሢሕ) መሆኑን ስላወቁ ነበር። ሉቃስ 9፡37-42 - አንድ ሰው ኢየሱስ ጋኔን ከወንድ ልጁ እንዲያወጣ ለመነው። ይህ ጋኔን ልጁን ሲይዘው ይጮህና አረፋም እያስደፈቀው ያንፈራግጠው ነበር። ሉቃስ 11፡14-26፤ ማርቆስ 3፡22-30፣ - ኢየሱስ ጋኔን ከዲዳ ሰው አወጣና አንዳንድ በብኤል ዜቡል ነው ሲሉ ገሰጻችው፤ እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ትጠፋለች ሲላቸው። ከዚያ ርኩስ መንፈስ ከሰው በወጣ ጊዜ ዕረፍት እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ማለፉን ያስተምራል። ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1 10፡20-22 - ቅዱስ ጳውሎስ የአረመኔ መሥዋዕት በእውኑ ለአጋንንት ስለ ሆነ ክርስቲያኖች ከእርሱ እንዲራቁ ያዝዛል። ሌሎች ምንጮች የአዕምሮ በሽታ